ቦስተን መስከረም 17/2007 (ሴፕቴምበር 27፣ 2014 ዓ.ም) የደመራ በዓል በካምብሪድጅ ከተማ 808 Memorial Dr. አጠገብ በሚገኘው ፓርክ በቦስተን እና አካባቢዋ ነዋሪ በሆኑ የመካነ ሕይወት ቅዱስ ሚካዔል ቤተ ክርስቲያን እና የመካነ ሰላም ቅዱስ ሚካዔል ቤተ ክርስቲያን እና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕምናን ዘንድ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ተከበረ። በበዓሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን የመካነ ሕይወት ቅዱስ ሚካዔል ቤተ […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የናይጀሪያ ጦር በቦኮ ሀራም አንፃር በጀመረው ትግሉ እንደቀናው ገለጸ። የናይጀሪያ ጦር ባለፉት ጊዚያት በአሸባሪው ድርጅት ቦኮ ሀራም አንፃር በተደጋጋሚ አሰመዘገብኩት ያለው ድል ብዙ ማነጋገር ይዞዋል።

መስከረም ፲፮(አሥራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ዓመት በዘጠኝ ወራት ብቻ የሥራ ፈላጊዎችን መረጃ ለማጠናቀር ታስቦ በተካሄደ ምዝገባ በመላ ሀገሪቱ 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ሥራ ፈላጊዎች በፈቃደኝነት መመዝገባቸውንና ከነዚህ ውስጥ ከ351ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲና የኮሌጆች ምሩቃን መሆናቸውን ከከተማ ልማት፣ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የተገኘ ጥናት አመለከተ፡፡ ይህ ጉዳይ መጪው ምርጫ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል …

መስከረም ፲፮(አሥራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦሞ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ህብረት መሪ የሆኑት አቶ አለማየሁ መኮንን ለኢሳት እንደገለጹት መንግስት ከጀመረው የሸንኮራ እርሻ ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ እየጠፋ ያለው ሰው ህይወት መንግስት መፍትሄ ሊሰጠው ካለመቻሉ ጋር ተያይዞ የሚመጣ ነው። በጅንካ ነዋሪ የሆነው  ኡመር ንጋቱ  በሙርሲ ብሄረሰብ አባላት በጥይት ተደብድቦ እንደሞተ መነገሩን ተከትሎ ሃሙስ እለት ከቀብር መልስ …

መስከረም ፲፮(አሥራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ ጋር የተገናኙነት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ፣ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ፣ በሰላም ማስጠበቅና ሽብርተኝነትን በመዋጋት በኩል እያደረገች ያለውን ሚና አወድሰዋል። አገሪቱ በደቡብ ሱዳንና በሶማሊያ ሰላም በማስጠበቅ በኩለ ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ ኢትዮጵያ  የሰላም አስከባሪ በመላክ ቁጥር በአለም ግንባር ቀደም ከሆኑ መንግስታት ተርታ እንደምትመደብም ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መንግስት …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የአንድነት ፓርቲ የኦዲት ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ዳግም ተሰማ ከትላንት መስከረም 15 ቀን ጀመሮ መሰወራቸዉን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል። « ዳግም፣ ድህንነቶች መኖሪያ ቤቱድረስ (ኦሎምፒያ) ሰሞኑን በዲኤክስ መኪና መጥተው ያነጋሩትንና ያስፈራሩትን አውግቶን ነበር፡፡ ይህንን ሲያወጋን ግን በራስ መታማመኑ እና ድፍረቱ ከራሱ ጋር ሆኖ ነው፡፡ ለዛሬጥዋት ፖሊስ ጋር ተጠርቶ ቀጠሮ ቢኖርበትም እሱ ግን ይበልጥ ትኩረት […]

በአንድነት ፓርቲ ወጣቶች አነሳሽነት፣ በአዲሱ የ2007 ዓ.ም ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎችን ለማድረግ የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ወጣቶች ኮሚቴ እየተንቀሳቀሰ ነው። እንደለመዱትና እንደከዚህ በፊቱም ሕወአት/ኢሕአዴጎች የዜጎችን ነጻ የመስብሰብ መብት እየረገጡ ፣ ሕገ መንግስቱን እየሻሩ ፣ እነርሱ ከሚፈልጉት ስብሰባ በቀር ምንም አይነት ሕዝባዊ እንቅስቃሴ እንዳይደረግ ጫና እያሳደሩ ነው። የፓርቲው ብሄራዊ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ በቢሮ ዉስጥ በሚደረጉ ስራዎች ተጠምዶ፣ […]

“ምንም አይነት ደብዳቤ አልደረሰንም” አቶ ማርቆስ ብዙነህ የአ.አ.ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና የስብሰባ ማሳወቂያ ቢሮ አንድነት ለዴሞክራሲ ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የህሊና እስረኞችን ለማሰብ በመስከረም 3 እና መስከረም 11 ቀን 2007 ዓ.ም ለማድረግ ያሰብኩት የሻማ ማብራት ሥነ ሥርዓት ሊሳካልኝ ባይችልም፣ በመጪው መስከረም 25 ቀን 2007 ዓ.ም ግን ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ አቅጃለሁ ሲል አስታወቀ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር […]

በይርጋለም ከተማ የሚገኘው የቤዛዊት የወጣቶች ማዕከል ባዘጋጀው የበጎ ፍቃደኛ ወጣቶች የክረምት መርሃግብር የተሳተፉ ወጣቶችን እና ስራዎቻቸውን ዝግጅቱ ባጭሩ ይቃኛል።

ተቀማጭነቱን በኒውዮርክ ያደረገው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (CPJ) መሰረት ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን ለስደት በመዳረግ ኤርትራን ተከትላ ከአፍሪቃ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። የኢትዮጵያ መንግስት በአከራካሪው የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ጋዜጠኞችን ለእስር፤እንግልትና ስደት ይዳርጋል ሲሉ አለም አቀፍ ተቋማት ይተቻሉ።

የዩኤስ አሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር በሁለቱ ሀገራት ዙርያ ዉይይት አደረጉ። የሁለቱ መንግሥታት መሪዎች ትናንት ኒዮርክ ላይ ዉይይት ከማድረጋቸዉ በፊት በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤

ያ ትውልድ ያመነበትን ተግባራዊ ለማድረግ ብዙ መስዋዕትነትን እንደከፈለው ሁሉ እህት በወንድም ላይ ጠቁማ ወደ ሞት የነዳችበትም አጋጣሚዎች ተፈጥረዋል ወንድም ከወንድም ጋር የሚያፋጅ ግዜ ላይም ነበሩ፤ ዛሬ ላይ እንደቀልድ ምንሰማው ለመፍረድም ቀላል የሚመስሉትአስቀያሚ የታሪኮቻችን አጋጣሚዎች ዛሬም ላይ ይከሰታሉ እኛም ስህተቶችን የምንደግም እንጂ ከስህተቶቻችን የምንማር ዓይነቶች አይደለንም፡፡
ከኢህአዴግ ወገን ላልሆነው ፖለቲካ የሚወደድ ሆኖባይሆንም በአገር ጉዳይ ያገባኛል ያሉ ሰዎች የሚገናኙባቸው ቦታዎች የተለመዱ ናቸው እስር ቤት፣ ሰላማዊ ሰልፍ(እጥረት ቢኖርብንም)እንዲሁም ፌስቡክ የመጀመሪያውን ተርታ ይይዛሉ፡፡ እንደውም ማህበረሰብ ሚዲያው እርስ በርስ ለመግባባት ለመገማገምና  ለመተዋወቅ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡ በኤዶም ካሳዬ እና በእኔ መካከልም ትውውቅምክንያት የሆነውና በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ የተገናኘነው ወደ ቂሊንጦ እስር ቤት ለመሄድ ከተሰባሰቡት የዞን ዘጠኝ አባላት ጋር ተሰባስበን በነበረበት ወቅት ነበር ወዲያውም ኤዲ ጆማ ተባብለን ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ሞቅ ወዳለው የፖለቲካ ጨዋታ ስንገባ አይተውን የተጠራጠሩት ጓደኞቻችን ከዛሬ በፊትም ሳትገናኙ አልቀራችሁም አይነት ትንኮሳ ጀምረው ነበር የምንታጨቅበት ታክሲ ሲመጣ ወሬያችን ቢቋረጥም፡፡
Journalist Edom Kassaye
ከቂሊንጦው እስር ቤት የጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ጥየቃ በኋላ በተለያዩ አጋጣሚዎች ተገናኝተን ተጨዋውተናል፣ እንደውም በአንድ ወቅት በጨዋታችን ውስጥ ደጋፊና ተቃዋሚ ጥግ እና ጥግ (አንዳንዴም ጽንፍ) የያዙ ፍረጃዎች ኑሮ ፈተና ለሆነባቸው የቤተሰብ ሃላፊዎች ስራቸው አስተማማኝ ይሆን ዘንድ አባልነት ግዴታ ሆኖባቸው አባል የሆኑትንና ያልሆኑት ግን ውሳኔዎችን ለማስቀየር ምንም ዓይነት አቅም እና ስልጣን የሌላቸው ነገር ግን በተቃውሞ ጎራ በካድሬነት የመፈረጅና የመዘለፍ አጋጣሚዎችን ያስተናገዱ ሰዎች ስለመኖራቸውና አንዳንዶች በብሔር ፖለቲካ ቅርቃር ውስጥ ተቸንክረው ወደ መከላከልና ጽንፍ የያዙ ደጋፊ ሆነው ስለመገኘታቸው እንዲሁም በኑሮ ውድነት ምክንያት መቃወም እየፈለገ ቤተሰቡን ማስተዳደር ፈተና ሆኖበት ከቤት ኪራይና ከሌሎች ወጪዎች የሚናጡ ባልና ሚስቶች ብሶትን መሰረት አድርገን መሃከል ላይ ስለምንገናኝበት አልያም የእነኚህን ሰዎች ስሜት ሌሎች እንዲረዱ ለማድረግ አንድ ጽሁፍ በጋራ ለመጻፍ ሁሉ ተመካክረን ነበር፡፡

በጋዜጠኛነት በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶችውስጥ ያሳለፈችው ኤዶም ከዞን ዘጠኞችና ከእነ አስማማውና ተስፋለም ጋር ስትከሰስ የግድ ዞን ዘጠኝ ነሽ እያሉ ነበር በሕግ የሚቀልዱትፖሊሶች የከሰሷት፡፡

ከዛ በፊት ግን ዞን ዘጠኝ ባትሆኚም ከእነሱ ጋርስለምትቀራረቢ መረጃ ስጪን እያሉ የገባችበት የሚገቡ በስልክ ፋታ የሚያሳጧት “ደህንነቶች” ነበሩ፤ ኤዲ በአንድ ወቅት የሆነ መስሪያ ቤት ስራ ለማመልከት ጎራ ብላ ስትወጣ አፍታም ሳይቆይ ይደወልላታል በዚህ ወቅት የደወለው ደህንነቱ ነበር የመስሪያ ቤቱን ባለቤትስም ጠርቶ “ ሥራ እንዳመለከትሽ ሰምቼያለሁ ከእኛ ጋር እኮ ብትተባበሪ የተሻለ ደረጃ በተሻለ ደሞዝ አስቀጥርሻለሁ” ብሏት ነበር፤በተደጋጋሚ ወቅትም “ዞን ዘጠኞች ለምን መጻፍ አቆሙ የተደበቀ ህቡህ ሥራ ስለጀመሩ ነውና መረጃ እንድትሰጪኝ እፈልጋለሁ አለበለዚያ ውጪ አገር ስብሰባ ላይ መንግስትን ለማሳጣት የተናገርሻቸውን ምክንያት አድርገን ልናስርሽ እንችላለን አንቺ ብቻ ተባበሪን እንጂ ወደ ውጪም መሄድ ከፈለግሽ አሜሪካም ሆነ አውሮፓ ምንም ችግር የለውም ትሄጃለሽ አንቺ ብቻ ተባበሪን “ የሚሉ ማስፈራሪያዎችና ማግባቢያዎች ይቀርቡላት ነበር ፡፡ ኤዶም በመልሷ “እኔ እስከማውቀው ልጆቹ ምንም እየሰሩ አይደለም ትልልቅ ሆቴል ውስጥ ኢንተርኔት ነጻ ስለሆነ እና ሰውም ስለማይበዛ ማኪያቶ  እየጠጡ የሚጨዋወቱናቸው መጻፍ ስላቆሙ ጓደኝታቸው ተቋረጠ ማለት ስላልሆነ ይገናኛሉ ከመንግስት ጫና ስላበዛችሁባቸው እንዲሁም በግል ምክንያቶቻቸውእንጂ ሌላ ነገር ስላሰቡ አይደለም” ብላ መልሳላቸው ነበር፡፡ የደህንነቶች ክትትል አሁንም የተባበሪና መረጃ አምጪ ትዕዛዝ ለረጅም ጊዜ ፋታ አልሰጣትም ነበር ፡፡በአንድ ወቅት ስብሰባ ላይ ሆና ስልክ ባለማንሳቷ የገባችበት እንደሚገባ እና እንደማታመልጣቸው ከዛቻ ጋር የጽሁፍ መልዕክት ተልኮላት እነደነበር ትዝ ይለኛል፡፡
ደህንነቱና አለቆቹ የሆነ ነገር እየተካሄደ ነው የሚል ስጋት መስከራቸው ምንም የሚያጠያይቅ አልነበረም፡፡ ( እኛም እነደ ቡድን አውነቱን ሲያውቁ ይተውታል የሚል የዋህነት ነበረብን) እናም ኤዶም የምታቀርበው እውነተኛ መረጃ ከሌለ በፈጠራም ቢሆን እንድትተባበራቸው ግፊት ሲደርጉባት የቆየ ቢሆንምለእንደዚህ አይነት ርካሽ ተግባር ተባባሪ ባለመሆኗ የጅምላ እስሩ ተቋዳሽ ሆናለች፡፡ የእኔም መትረፍ ያለኤዶም እና ናትናኤል ፈለቀ(ናቲ) የሚቻል አልነበረም፡፡ “freedom of expression ትሰራላችሁ ወንጀል አንደሆነ አታውቁም?” የሚሉ የእውቀት ደረጃቸው ለመግባባት አንኳን የሚያስቸግሩ ሰዎቸን እነ ኤዲ ለወራት ለማሳመን ሲጥሩ ከርመዋል፡፡
በታሰሩ ቀን ማግስት በነበረው ቅዳሜ ጠዋት ላይ በቅርቡ የልጅ አባት የሆኑትን ወዳጆቼንለመጠየቅ ከሰአት በኋላ ከዞን ዘጠኞች ጋር ቴስት ኦፍ አዲስ የምግብ ፌስቲቫልን ለመታደም ማታ ላይ የቴዲ አፍሮን ኮንሰርት ለመታደምአስቀድሜ አቅጄ የነበረ ቢሆንም ሰው ያስባል ኢህአዴግ ያስራል ሆነና የሕይወቴ አንዱ እና ትልቁ የምለው ብዙ ወንድሞቼንና እህቶቼን በእስር ያጣሁበት ማግስት ሆነ፡፡
#TimeStandStill pic edited by Mahilet Solomon
ጊዜው አምስት ወራት ተቆጥረዋል ቢልም ለብዙዎቻችን እንደቆመ ነው፣ ንጹህ ኅሊና ያላቸው ለትውልድ ምሳሌ የሚሆኑ ጓደኞቼን ህገ መንግስታዊ መብት ባልተከበረበት፣ የህግ የበላይነት እና የህግ ስርአት መመራት ቀልድ በሆነበት በስርአቱ አገልጋዩች መነካታቸው ያንገበግበኛል፣  ለኔ ጊዜው አሁንም እንደቆመ ነው ሻንጣዬ ውስጥ ያለውን እቃ አውጥቼ ቁምሳጥን ውስጥ ለመጨመር አዲስ ሕይወት ከጀመርኩ እነሱን የምረሳ እየመሰለኝ እንዳለ አለ ተመልሶ እነሱን እንደሚያገኝ ለጉዞ እነደተሰናዳ ሰው ልቤ እንደተሰቀለ እስካሁን አለሁ፡፡ ይህ እኔም ሆነ የተረፍነው ወዳጆቼ የምንጋራው ስሜት ነው፡፡
ራሳቸውንም ሆነ ቤተሰባቸውን የሚያኮራ መከራን ለመጋፈጥ የቆረጡ እውነተኛና ሃቀኛ ሰዎች ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል፤ እነሱንም የወለዱ እናትና አባቶች ሊኮሩ እንጂ ሊያዝኑ አይገባም፡፡
ኤዲ ያንቺ ጓደኛ ስለሆንኩ ኩራት ይሰማኛል፡፡

 #TimeStandStill #FreeZone9Bloggres #FreeEdom#FreeTesfalem #FreeAsmamaw #FreeAllPoliticalPrisoners

ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የሟቹ የመለስ ዜናዊ ሰላባ ከሆኑት ብርቅዬ የኢትዮጵያ ልጆች መካከል አንዱ ነበሩ። ከ19 ዘጠኝ አመታት በፊት፣ በኩወቤክ ካናዳ የቀድሞ የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስተር ጆን ክሬቲየን፣ ባለፈው ሳምንት ደግሞ በስክቶላንድ የአሁኑ የእንግሊዘ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዴቪድ ካሜሮን ፣ የአገራቸውን አንድነት ለማስጠበቅ፣ ክዌቤክና ስኮትላንድ እንዳይገነጠሉ ብዙ የደከሙ፣ የድካማቸውን ፍሬ ያዩ አገራቸዉን እና ህዝባቸውን የሚወዱ መሪዎች መሆናቸውን ያስመሰከሩ […]

የኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ በመንግስታቱ ድርጅት ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር ከሁለት ሺህ አስራ አምስት በሁዋላ ለሚኖረዉ የልማት አጀንዳ የዓለም አበይት ፈተናዎች በጋራ ለመጋፈጥ ነገር ግን የየራሳቸዉ ገጽታ ያላቸዉን ሃላፊነቶች መሰረት ያደረገ መተጋገዝም ለማጠናከር እንደሚረዳ ያላቸዉን እምነት ገልጸዋል።

ዓለም አሁን ያሉባትን እጂግ ከባድ ፍላጎቶች ለማሙዋላት አቅም ሃብር እንዳላት አስምረዉበታል።

አፍሪቃ በማደግ ላይ ያለች ለንግድና ለመዋእለ ንዋይ ምደባ ግዙፍ እድል የምትሰጥ አህጉር እንደሆነችና  ኢትዮጵያን ጨምሮ ብዙዎቹ የአገሮች የሚሊኒዬሙን ግብ ለማስመዝገብ ዝግጁ መሆናቸዉን ተናግረዋል።

ሆኖም አፍሪቃ ለልማት ያላትን ጉጉት የከባቢ ዓዬር ለዉጥ ችግር  እያደናቀፈ መሆኑን ጠቅሰዉ አፍሪቃ የችግሩ ምንጭ ባትሆንም የመፍትሔ…

ከሁለት ሳምንት በፊት በአቶ በረከት ስምኦን የተከፈተውና 15 ቀን የፈጀው ባህርዳር ላይ የተደረገው የ‹‹ፍትህ አካላት›› ስብሰባ ትናንት መስከረም 14/2007 ዓ.ም በአቶ በረከት ስምኦን ማስጠንቀቂያ መጠናቀቁን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ ስብሰባውን የዘጉት አቶ በረከት ስምኦን ‹‹ፖሊስ፣ አቀቤ ህግና ዳኛ ከአስፈጻሚው (ከካቢኔው) ጋር ተስማምቶና እጅና ጓንት ሆኖ መስራ አለበት፡፡ ይህ ነው ልማታዊ የፍትህ ስርዓት፡፡›› ማለታቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ […]

ከመስከረም 10/2007 ዓ.ም እስከ መስከረም 12/2007 ዓ.ም በጥቃቅንና አነስተኛ ለተደራጁ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በተሰጠው የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› የማጥመቅ ስልጠና በምርጫው ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ኢህአዴግ እንዲመረጥ እንዲሰሩ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸውና እቅዱን ካላሳኩ ሸዳቸውን መስሪያ ቦታውን እንደሚያጡ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ሰልጣኞቹ ‹‹ግብር በዝቶብናል፣ ደንብ አስከባሪዎች በየጊዜው እየመጡ ገንዘብ ይወስዱብናል፣ በየወረዳው የመልካም አስተዳደር ችግር መፍትሄ ልናኝ አልቻልንም፣ ስለዚህ […]

የትግራይዋ ህወሓት ማለቴ በሰማእታት ሓወልት ፅሕፈት ቤትዋ ያደረገችው ህወሓት( ኣዲስ ኣበባ የህወሓት ኣንጃ ሰላለች ነው) “ኣብራሃ ደስታ የታሰረበት ምክንያት ኣላውቅም” ኣለች። ይህ ኑዛዜ የተሰማው በኣገር ደረጃ ለመንግስት ሰራተኞች እየተሰጠ ያለው ስልጠና የሚሉት(ተቃዋሚና ያለፉት ስርዓቶች የሚሰድቡበት መድረክ ስለመሰለ ነው) በትግራይ ክልል ፅህፈት ቤት(ደጀን ቢሮ) የሚሰሩ ሰራቶኞች በፕላኔት ሆቴል እየተካሄደ ባለው መድረክ ነው። በዚህ መድረክ እየተነሱ ያሉት […]

መስከረም ፲፭(አሥራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 98 በመቶ የሚሆነውን የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ የአዛዥነት ቦታዎችን ከተቆጣጠሩት የህወሃት ጄኔራሎች ባልተናነሰ በከፍተኛ የስልጣን ቦታ ላይ የነበሩት ብቸኛው የአማራ ተወላጁ ጄኔራል አበባው ታደሰ በጄ/ል ሳሞራ የኑስ ትእዛዝ ከሃላፊነታቸው ዝቅ ብልው እንዲሰሩ ከተወሰነባቸው በሁዋላ፣ በመጨረሻ ከመከላከያ ሰራዊት መሰናበታቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ጄ/ል አበባው ከጄ/ል ሞላ ሃ/ማርያም እና ከጄ/ል […]

መስከረም ፲፭(አሥራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ኦሞ ዞን በጅንካ ከተማ በአይነቱ ልዩ ነው ተባለ የተቃውሞ ሰልፍ መደረጉን የአካባቢው ምንቾች ገልጸዋል። የተቃውሞ ሰልፉ የተደረገው ከጅንካ ከተማ  ወደ ሃና በመጓዝ ላይ የነበረ አንድ ሰራተኛ መገደሉን ተከትሎ ነው። ሃና አዲሱ የስኳር ፋብሪካ ግንባታ የሚካሄድበት ቦታ ሲሆን፣ ግድያውን የፈጸሙትም የስኳር ልማቱ ከቀያቸው ያፈናቀላቸው የሙርሲ ብሄረሰብ አባላት …

መስከረም ፲፭(አሥራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-98 በመቶ የሚሆነውን  የመከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ የአዛዥነት ቦታዎችን ከተቆጣጠሩት የህወሃት ጄኔራሎች ባልተናነሰ  በከፍተኛ የስልጣን ቦታ ላይ የነበሩት ብቸኛው የአማራ ተወላጁ ጄኔራል አበባው ታደሰ በጄ/ል ሳሞራ የኑስ ትእዛዝ ከሃላፊነታቸው ዝቅ ብልው እንዲሰሩ ከተወሰነባቸው በሁዋላ በመጨረሻ ከመከላከያ ሰራዊት መሰናበታቸውን ምንጮች ገልጸዋል። ጄ/ል አበባው ከጄ/ል ሞላ ሃ/ማርያም እና ከጄ/ል ሰአረ …

መስከረም ፲፭(አሥራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ መራሹ መንግስት የመንግስትን ፖሊሲና ስትራቴጂ አልተቀበሉም ባላቸው አርሶ አደሮች ላይ በይፋ የማሸማቀቅ ስራ እየሰራ መሆኑን አርሶ አደሮች ለዘጋቢያችን ገልጸዋል። የገዢውን ፓርቲ ፖሊሶች ተቀብለው አባል ለመሆን ፈቃደኛ ያልሆኑ አርሶአደሮች ” ታካች አርሶ አደር “የሚል ስያሜ እየተሰጣቸው በተለያዩ መንገዶች እየተዋከቡና በእዳ እየተጠየቁ ሲሆን፣ የስርአቱ ደጋፊ የሆኑ አርሶአደሮች ደግሞ …

መስከረም ፲፭(አሥራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመላ አገሪቱ በሚሊዮን የሚቆጠር ሀሰተኛ የብር ኖቶች የተሰራጩ ሲሆን፣ ፖሊስ በየቀኑ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ ለመሰብሰብ ቢችልም ችግሩ አሁንም በስፋት እየታየ ነው። የፌደራል ፖሊስ መረጃ እንደሚያመለክተው በመላ አገሪቱ በተሰራጨው ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሃሰት የብር ኖቶች መንግስት በየቀኑ ከባንኮችና ከገበያ ሱቆች ለመሰብሰብ ተገዷል። ፖሊስ በዚህ ስራ ላይ ተሰማርተዋል …

የፊታችን ግንቦት 2007 ዓ.ም ምርጫ ይኖራል ተብሎ ይጠበቃል። ነገሮች ሳይበላሹና ሳይቆላለፉ ከወዲሁ እንዲታሰብበት ይችን አጭር ጽሁፍ ላቅርብ:: ምርጫ ማለት ከቀረቡ በርካታ አማራጮች መካከል አንዱን መምረጥ ማለት ነው። ሬስቶራንት ስንሄድ አስተናጋጆች ይመጣሉ። ሜኒዩ ይሰጡናል። የምግብ አይነቶች ተዘርዝረው እናነባለን።። ክትፎ፣ ጥብስ፣ ምጥን ሽሮ ..እያለ ብዙ አማራጮች ተደርድረዋል። አንዱን እንመርጣለን። ምርጫ ማለት ይሄ ነው። አማራጮች ካልቀረቡ፣ የተሰጠንን ተመገብን […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

“ይህ ውሣኔ ሰብዓዊ መብቶች፣ መሠረታዊ መብቶች፣ ለሕግ ተገዥነት አንደአማራጭ የሚቀመጡ አለመሆናቸውን፤ እንዲያውም የፀረ ሽብር ጥረቶቹ ቁልፍ አካላት መሆናቸውን ግልፅ ያደርጋል፡፡ እንዲያውም እነዚህን መብቶችና ነፃነቶች አለመጠበቅ አመፀኛ የሆነ ፅንፈኝነትን ይበልጥ እንደሚያራግብ ታሪክ ያስተምረናል፡፡”

ርዕሰ አዉዳ ዓመት፤ ወርኃ አደይ ወርኃ ጽጌን ተከትሎ በኢትዮጵያ በተለያዩ ብሄር ብሔረሰቦች በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ለመከበር በጉጉት የሚጠበቀዉ የመስቀል በዓል፤ ከሐይማኖታዊ ስርዓቱ ባሻገር ባህላዊ ገፅታዉ አከባበሩ ህብረ- ቀለማዊ ነዉ።

የተመድ አባል ሀገራት ፅንፈኞችን ለመቆጣጠር ጠንካራ ርምጃ እንዲወስዱ የየተመድ የፀጥታ ጥበቃ ምክር ቤት ትናንት ባሳለፈው ውሳኔ አሳሰበ። ሽብርተኝነትን ለማሸነፍ አባል ሀገራት ባጋራ መስራት እንዳለባቸው የተመድ ዋና ጸሐፊ ፓን ኪ ሙን ተማፀነዋል።

ስኖደን የተሸለመዉ በዓለም የማትደፈረዉን ሐያል ሐገር በማጋለጥ ለመናገር ነፃነት መከበር መቆሙን በማረጋገጡ ነዉ።ለወትሮዉ የተሸላሚዎች ሥም ዝርዝር በይፋ የሚነገርበት የሲዊድን ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ግን መስሪያ ቤት ግን የዘንድሮ ተሸላሚዎች ስም ዝርዝር ከቢሮዉ እንዳይነገር አግዷል

የዓለም ጤና ድርጅት ባልደረባ ዶክተር ክርስቶፈር ዳይን እንደሚሉት ችግሩ ፈጥኖ ካልተገታ የምዕራብ አፍሪቃ ሐገራት በፖለቲካዊ ቀዉስ መናወጣቸዉ የማይቀር ነዉ።የዳይን ጥናት እንደሚማመለክተዉ የኤቦላ ስርጭት በዚሑ ከቀጠለ የተለካፊዉ ቁጥር ከአንድ ወር በኋላ ከሃያ ሺ ይበልጣል።

የኤኮኖሚክስ ፕሮፌሰር ጌታቸዉ በጋሻዉ ግን ሁለቱ ተቋማት የአሜሪካና የአዉሮጳን ጥቅም ከማስከበር አልፈዉ ለአፍሪቃ የሚረዳ ነገር መክረዉ፤አድርገዉም አያዉቁም።ኢትዮጵያም የዕዳዋን መጠን ለመቆጣጠር የራስዋን ጠቃሚ መርሕ መከተል ነዉ የሚገባት።

በ1768 እኤአ የተጻፈና ጥንታዊ አባባሎችን የያዘ አንድ ‹‹AN ETHIOPIAN SAGA›› የተሰኘ መጽሐፍ ሳነብ ‹‹ጨረቃዋን እያየህ፣ ጨለማውን ግን እየተጠነቀቅ ተጓዝ›› የሚል ጥንታዊ ብሂል አየሁ፡፡ ይህ ለጥንቱ መንገደኛ የተሰጠ የጠቢብ ምክር ነው፡፡

የጥንቱ ተጓዥ ጤፍ በምታስለቅመው ጨረቃ መጓዙ ሁለት ጥቅሞች ይሰጡት ነበር፡፡ በአንድ በኩል በቀን ከሚገጥመው ሙቀትና የፀሐይ ቃጠሎ ይድናል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ መንገዱን በሩቁ ስለማያየው ‹ለካ ገና ብዙ መንገድ ይቀረኛል› እያለ መንፈሱ እንዳይደክም ያደርገዋል፡፡

በተለይም ደግሞ መንገደኞቹ በዛ ካሉ፣ ሰብሰብ ብለው በአንድ ቤት ታዛ ሥር ወይም በአንድ ዛፍ ጥላ ሥር ያርፉና በአራተኛው ክፍለ ሌሊት(ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት በኋላ) ተነሥተው የጨረቃዋን ብርሃን እየተከተሉ መጓዝ ነው፡፡ ያን ጊዜ  ነው እንግዲህ ‹ከጨለማው እየተጠነቀቁ፣ ነገር ግን ጨረቃዋን እያዩ›› የሚጓዙት፡፡

መንገደኞቹ ጨረቃዋን የሚያዩዋት ለሁለት ነገር ነው፡፡ በአንድ በኩል ጨረቃዋ መጀመሪያ እየደመቀች፣ በኋላ ደግሞ እየደበዘዘች መጓዟ የሌሊቱን ማለፍና የቀኑን መምጣት ይነግራቸዋል፡፡ በተለይ የበረሐ መንገደኞች ከሆኑ የጨረቃዋ እየደበዘዘች መሄድ ለእነርሱ መልካም ዜና አይደለም፡፡ የሙቀቱን መምጣት እያረዳቸው ነውና፡፡ የፀሐዩን ግለትም እነርሱም ሆኑ የጭነት ከብቶቻቸው አይቋቋሙትም፡፡ በሌላም በኩል የጨረቃዋን ብርሃን እየተከተሉ የሚጓዙት፣ በአካባቢው ሌላ ብርሃን የለምና፣ አንዳንድ ጊዜ ጨረቃዋን ደመና ሲጋርዳት ተግ እያሉ፣ በጠራ ሰማይ ላይ ፍንትው ብላ ስትወጣ ደግሞ መንገዱን ያዝ ያዝ እያደረጉ ስለሚገሠግሡ ነው፡፡

በዚህ ጉዟቸው የሚከተሉት የሚያተኩሩት በጨረቃዋን ላይ ብቻ አይደለም፡፡ ምንም እንኳን ጨረቃዋ መንገዱን ብታሳያቸውም ጫካው፣ ሸለቆውና ገደላ ገደሉ ደግሞ በተቃራኒው ድቅድቅ የሆነ ጨለማን ይፈጥራል፡፡ ጥጋጥጉ ሁሉ ከጨረቃዋ ደማቅ ብርሃን ተጋርዶ አንዳች መርግ የመሰለ ጽልመት ይጋርደዋል፡፡ ይኼ ደግሞ የጨረቃዋ ብርሃን ላጋለጣቸው አራዊት ዋና መደበቂያ፣ ለሽፍቶች ዋና መሸሸጊያ ነው፡፡ አንዳንዴም ጨረቃዋ ፍንትው ብላ ስትወጣ ከተገለጠው አካባቢ ግራና ቀኝ ያለው አስፈሪና ምን እንደያዘ የማይታወቅ ሥርቻ ይሆናል፡፡

የጨረቃ ብርሃን እንደ ፀሐይ አይደለም፡፡ የፀሐይ ብርሃን ከሙቀቱ ጋር ስለሚመጣ አካባቢውን ይቀይረዋል፡፡ የብርሃኑ ወገግታም መከለያዎችን እንኳን ተሻግሮ የብርሃን ፍንጣቂ ይለቅበታል፡፡ የፀሐይ ብርሃን ከጨረቃ የተሻለ ምለክዐት አለው፡፡ ጨረቃ ግን ድምቀት ነው ያላት፡፡ አካባቢውን ታስውበዋለች እንጂ አታሞቀውም፡፡ በዚህ የተነሣ ለጨረቃ መንገደኞች ግራ ቀኙ አስፈሪ ነው፡፡  ከሆነ ርቀት በላይም በጨረቃ ብርሃን መንገዱን ማየት አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ ለዚህም ነው ‹‹ጨለማውን ተጠንቀቅ›› የተባለው፡፡

አንዳንድ ጊዜ ሕይወት የጨረቃ መንገድ ትሆናለች፡፡ ብርሃንና ጨለማ፣ ድምቀትና ፍርሃት አብረው የሚገኙባት፡፡ መንገድህን ታውቀዋለህ፤ ነገር ግን ከመንገድህ ግራና ቀኝ የሚጠብቅህን ወጥመድ በሚገባ ላታውቀው ትችላለህ፡፡ ቀና ስትል እንደምታያት ጨረቃ እጅግ የደመቁ ተስፋዎችን፣ ድሎችንና አጋጣሚዎችን ታገኛለህ፡፡ ነገር ግን ጨረቃ ጨረቃዋን ብቻ ስታይና ነፍስህን በሐሴት ስታጥለቀልቅ ደግሞ ከግራና ቀኝህ ከሚገኙት ጉድባዎች፣ ሸለቆዎች፣ ጥሻዎችና ጥጋጥጎች  የደበተ ጨለማ፣ የሚያስፈራም አውሬ፣ የሸመቀም ጠላት ያጋጥምሃል፡፡

መንገደኛው ጨረቃዋን ለማድነቅ በቂ ዕድልን አያገኝም፡፡ መጓዝ ስላለበት፡፡ አንድ ቦታ ቆሞ፣ በደስታ ተደሞ፣ በፍቅሯ ተውጦ፣ በብርሃንዋ ተመስጦ ‹ጨረቃ ድንቡል ቦቃ፣ ዐጤ ቤት ገባች ዐውቃ›› እላለሁ ቢል፣ እርሱ በጨረቃዋ ውበት በተመሰጠበት ጊዜ ከማያውቀው ጥሻ ብቅ የሚል አውሬ ወይም ጠላት አይጠፋም፡፡ አለበለዚያም ደግሞ የሚጣላ ባይሆንም የሚያስደነግጥ ኮሽታ አያጣም፡፡ ስለዚህም በአንድ ልቡ ቀና ብሎ ውበቷን እያየ፣ በአንድ ልቡም መንገድ መንገዱን እያስተዋለ፡፡ አልፎ አልፎም ደግሞ ግራና ቀኙን እየገላመጠ ይጓዛል፡፡

ሕይወት እንደ ጨረቃዋም የምታምር፣ የምትስብ፣ ኑሩብኝ ኑሩብኝ የምትል፣ አንዴ እየጎደለች ሌላ ጊዜ ብትሞላም፣ የምትፈነጥቅና መንገድ የምታሳይ፣ በተስፋና በጉጉትም የተሞላች ናት፡፡ ሕይወት እንደ ጨረቃዋ ፍስስ የምትል፣ የሚዜምላትና የምትናፈቅም ናት፡፡

በሌላም በኩል ደግሞ ሕይወት ተስፋና ደስታ፣ ርካታና ሰላም ብቻ አይደለችም፡፡ መንገደኛው ጨረቃዋን ብቻ እያየና በእርሷም እየተደሰተ ብቻ መጓዝ እንደማይችለው፡፡ ሕይወት ጥሻዎችና ገደሎች፣ ጫካዎችና ጉድባዎችም አሏት፡፡ የጨረቃዋ ብርሃን እንደሚያስደስተው ሁሉ የጫካዎቹ ጥላ፣ የጥሻዎቹ ዝምታ፣ የገደሎቹ ድብታና የገደሎቹም ጨለማ ያስፈራል፡፡ አንድም እዚያ ምን እንዳለ አለመታወቁ፣ አንድም ደግሞ እዚያ አውሬና ጠላት ሊኖር መቻሉ፡፡ የጨረቃዋን ብርሃንና ድምቀት ምን ብንወድደው፣ ጊዜ ሰጥተን ልናጣጥመውም ብንፈልግ እንኳን በግራ በቀኝ ያለው ጨለማና ፍርሃት ግን በቂ ጊዜም በቂ ልብም አይሰጠንም፡፡ ደግሞ እርሱንም እናስባለን፤ ደግሞ እርሱንም ማየት እንፈልጋለን፤ ደግሞ የእርሱንም ዝምታና ጨለማም ማጥናት እናስባለን፤ ምን ሊኖር እንደሚችል፣ ከማናውቀው ምንም ውስጥ ምን ሊወጣ እንደሚችል እንገምታለን፡፡ ከግምታችን ተነሥተንም እንሠጋለን፡፡

ያለፈውን እናስታውሳለን፡፡ ያለፉትንም እናስባለን፡፡ በዚህ ዓይነት መንገድ ስለተጓዙ ሰዎች የተነገረውንም ታሪክና ትርክት እናስታውሳለን፡፡ ተረቶቹንና ንግሮቹን እናመጣለን፡፡ ለጨለማውና ለዝምታው ትርጉም እንሰጣለን፡፡ እንጠረጥራለን፡፡ ኮሽታዎችንና ንቅናቄዎችን ሁሉ እናዳምጣለን፡፡ ለእያንዳንዱ ድምጽ ትርጉም እንሰጣለን፡፡ እንዲህ እያልንም በጨረቃ ድምቀት ተደስተን፣ በግራ ቀኙ ጨለማ ደግሞ ሠግተን እንጓዛለን፡፡ እንዲህ ናት ሕይወት፡፤ ተስፋ ብቻ አይደለችም ሥጋት አላት፣ ደስታ ብቻም አይደለችም ኀዘን አላት፤ የምትታይ ብቻ አይደለችም የማይታይም ክፍል አላት፡፡ የሚታወቅ ብቻ አይደለችም የማይታወቅም አካል አላት፡፡ ለዚህም ነው ቀደምቶቻችን ‹ጨረቃዋን እያየህ፣ ጨለማውን ግን እየተጠነቀቅክ ተጓዝ› ያሉን፡፡

ጨረቃዋን ለማያዩ ሰዎች ሕይወት ጎምዛዛ ብቻ ናት፡፡ ድብርትና ሥጋት የሞላባት፡፡ ምንም ዓይነት የደስታ ፍንጣቂ የማይታይባት፡፡ ከንቱ ብቻ ናት፡፡ ችግርና ጉስቁልና ብቻ የሰፈነባት፡፡ ጨለማውን ለማያዩ ሰዎች ደግሞ ሕይወት ደስታና ፈንጠዝያ፣ ሰላምና እርካታ፣ ፌሽታና ዝላይ ብቻ ናት፡፡ ሁለቱም ግን ይጎዳሉ፡፡ ጨረቃን የማያዩ ሰዎች ሕይወትን ለማጣጣም ዕድል አያገኙም፡፡ ምንም ዓይነት በጎ ነገርንም ከሕይወት አይጠብቁም፡፡ ምንም ዓይነት ደግ ነገር አይታያቸውም፡፡ ምንም ዓይነት ውበት አይገለጥላቸውም፡፡ ሁሉም ጨለማ ብቻ ነው፡፡ ጨለማውን የማያዩ ሰዎች ደግሞ ምንም ዓይነት ዝግጁነት፣ ጥንቃቄና ችግርን የመፍታት ጥበብ የላቸውም፡፡ ሣር ሣሩን ብቻ ሲያዩ ገደል ውስጥ የመግባት ዕጣ ይገጥማቸዋል፡፡ ማሩን እንጂ የንቧን መናደፍ፣ ጽጌረዳውን እንጂ እሾሁን አያዩም፡፡ ሕይወት መዝለልና መዘነጥ፣ መብላትና መተጣት፣ መሳቅና መጫወት ብቻ ይመስላቸዋል፡፡ ስለዚህም በተወጉና በተነደፉ ጊዜ ይደናገጣሉ፡፡ በቶሎም ተስፋ ይቆርጣሉ፡፡

በሕይወት በጤነኛ መንገድ ለመጓዝ የተሻለው ጥበብ ጨረቃዋን ማድነቅና በብርሃኗ መሄድ፣ ጨለማውንም መጠንቀቅ ነው፡፡ ሕይወት በጨረቃ ብርሃንና በጨለማው መካከል የተሠመረች ስላች መንገድ ናትና፡፡ እዚህ ላይ ጠቢብ ሰው ሚዛኑን ይጠብቃል፡፡ እዚህ ላይ ጠቢብ ሰው አንድ ዓይኑን በጨረቃዋ ሌላውንም ዓይኑን በጨለማው ላይ ተክሎ ይጓዛል፡፡ ጠቢብ ሰው ሁለቱን ዓኖቹን አንድ ነገር ላይ አይተክልም፡፡ ብዙ ጊዜ አንድን ነገር በሁለት ዓይኖቻችን ነው የምናየው፡፡ ማየት ያለብን ግን የዚያን ነገር ጨረቃና ጨለማ ነው፡፡ ጨረቃዋን በአንድ ዓይን ጨለማውን ደግሞ በሌላው ዓይን፡፡ ሕይወት በጨለማና በጨረቃ መካከል መጓዝ ነውና፡፡

ሜልበርን፣ አውስትራልያ

ዓለም በኤቦላ ስጋት መታመስ ሲጀምር በቀድሞዋ ዛየር በዛሬዋ ዴሞክራቲክ ሬፐብሊክ ኮንጎ ተኅዋሲውን ያገኙት የቤልጅየም ተወላጁ ፕሮፌሰር ፒተር ፒዮ መታወስ ጀመሩ።ፕሮፌሰሩ በአሁኑ ወቅት የለንደን የግል ንጽህናና የምድር ወገብ አካባቢ በሽታዎች ትምህርት ቤትን በሃላፊነት ይመራሉ።

ዋይ ! ዋይ ! (በሙሾ ዜማ ይውጡት) ንዋይ ዋይ! ዋይ! ንዋይ ንዋይ ሞተ አሉ በቁሙ ንዋይ ሞተ አሉ በቁሙ ጨለመችበት ዓለሙ (2) ንዋይ በንቁላል ተመታ ንዋይ በንቁላል ተመታ ሊዘፍን መጥቶ በማታ (2፟) ዋይ! ዋይ! ንዋይ ዋይ! ዋይ! ንዋይ ምን ይላት ይሆን ለሚስቱ ምን ይላት ይሆን ለሚስቱ በንቁላል ገምቶ ደረቱ (2) ጀግናው ፈረሰ ለሆዱ ጀግናው ፈረሰ […]