ባለፈው ሳምንት እሑድ በክፍል አንድ ውይይታችን ፣ የገባውን አዲሱን ዘመን 2007 ዓ ም ን መንስዔ በማድረግ፤ በኢትዮጵያ ፣ ከገሐዳዊው ይዞታ ጋር ምኞትና ተስፋ እንዴትና ምን ቢደረግ እውን ሊሆኑ እንደሚችሉ 3 ቱ ተጋባዥ እንግዶቻችን ፣ ከአዲስ ዓመት

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በኬንያ መዲና ናይሮቢ የሚገኘው ዌስትጌት የተባለው ትልቅ የገበያ ማዕከል በአሸባሪዎች ጥቃት ከተሰነዘረበት በነገው ዕለት ልክ አንድ ዓመት ይሞላል። ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደው የሶማልያ አክራሪ ታጣቂ ኃይል ታጣቂዎቹ እአአ መስከረም 21፣ 2013 ዓም ማዕከሉን በማጥቃት ለቀጠሉት አራት ቀናት በመያዝ ሕዝቡን ማሸበራቸው የሚታወስ ነው።

በኬንያ መዲና ናይሮቢ የሚገኘው ዌስትጌት የተባለው ትልቅ የገበያ ማዕከል በአሸባሪዎች ጥቃት ከተሰነዘረበት በነገው ዕለት ልክ አንድ ዓመት ይሞላል። ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደው የሶማልያ አክራሪ ታጣቂ ኃይል ታጣቂዎቹ እአአ መስከረም 21፣ 2013 ዓም ማዕከሉን በማጥቃት ለቀጠሉት አራት ቀናት በመያዝ ሕዝቡን ማሸበራቸው የሚታወስ ነው።

በጄኔቭ የሚገኘዉ የተ.መ የስደተኞች ርዳታ ሰጭ ጉዳይ መሥርያ ቤት እንዳስታወቀዉ፤ በ24 ሰዓታት ዉስጥ ብቻ ወደ 70 ሺ የሚጠጉ ሰዎች ጥገኝነት በመፈለግ ቦታዉ ላይ ደርሰዋል።

በጄኔቭ የሚገኘዉ የተ.መ የስደተኞች ርዳታ ሰጭ ጉዳይ መሥርያ ቤት እንዳስታወቀዉ፤ በ24 ሰዓታት ዉስጥ ብቻ ወደ 70 ሺ የሚጠጉ ሰዎች ጥገኝነት በመፈለግ ቦታዉ ላይ ደርሰዋል።

ቱርክ በሺዎች የሚቆጠሩ እና ከሶርያ የሸሹ ኩርዶች ድንበሯን ተሻግረው እየገቡ መሆኑን አስታወቀች። ከአማፂው አይ ኤስ ቡድን የሸሹ 45 ሺ የሚጠጉ ሰዎች ከዓርብ ዕለት አንስተው የቱርክ -ሶርያን ድንበር አልፈዋል ሲሉ የቱርክ ምክትል ጠ/ሚኒስትር ኑማን ኩርቱልሙስ ለCNN ቱርክ የመገናኛ ብዙኃን ገልጸዋል።

Befekadu Hailu

There was a time in my life when I used to think a lot about revolution in Ethiopia. In fact, in 2011 during the so called ‘Arab Spring’ I wrote a rejoinder article when Ethiopian democracy activists (especially those who are based in diaspora) planned a ‘Day of Rage’ using Facebook and aimed at ending EPRDF’s two-decade authoritarian rule. Just after a year I wrote one more rejoinder titled “Revolution is Ephemeral ’. In this article I tried to highlight what Ethiopians truly lack to launch a genuine social revolution using social media. In these couple of articles it appeared that I went up against proponents of revolution but I was trying to explain the traceable causes and conditions of social revolution. In a nutshell, I was saying that the significant portion of the Ethiopian population, the opposition politicians, and the intellectuals and generally the elite and social ideals and social reality were not sufficiently prepared to kick-start an authentic and organic social change.
Yet again in 2012, I was inspired enough to write a series of articles under a general title ‘Concerning Change’ on our own blog Zone9. In the first of my series of articles titled “Will EPRDF hand over power by means of election?”  I tried to explain why EPRDF will keep on clinging to power. I argued that EPRDF is not yet ready for an electoral democracy. In a bid to demonstrate an alternative yet constitutional means of possible social change such as civil disobedience I wrote further articles as a follow up to my critique and highlighted different elements of social change across a spectrum of societal issues. As much as I can  I tried to kindle genuine public conversations in bringing these issues to the public’s attention through my articles such as ‘Fear and Social Change’ ‘Regime Change and Religion’, ‘The Role of Civil Society in 1974 Ethiopian Revolution’ and “Revolution or Sluggish Change”  It was during this time that I contemplated deeply about revolution. It was one phase of my life in which I have tried to articulate my comprehension of revolution into pieces of writings but it was also a stage of my life in which my belief on revolution was dropped off significantly.  But I have to confess here that my belief on revolution plummeted to its all-time low merely in 2013. Subsequently, I found myself turned into an activist of an organic social change through processes (not a transient revolution) from an avid reader and advocate of revolutionary ideas.  I have to put in plain words that what made me skeptic of transient revolutions; I have to explain at length that how I progressed (say it regress if you like) from being optimistic revolutionary to a proponent of an organic and authentic social change through processes, as the 1960s Ethiopian Marxist revolutionaries put it, what turned me from being ‘Revo’ (revolutionary) to ‘Sabo’ (Saboteur). Please note that I was only an enthusiastic reader of revolutionary ideas.  
  At some stage while I was grappling with the revolutionary ideals of intending to bring fundamental structural change in favor of the mass but unexpectedly might turn to be like unrestrained wildfire which could be destructive; Mohamed Morsi was ousted in Egypt’s second revolution just in two years. The second Egyptian rebellion (revolution) made me feel perplexed about revolutions. But I thought in his short-lived presidency Morsi operated against basic principles of democracy and hence I believed the second revolution was born in resistance to another form of dictatorship. Certainly the second revolution even made me assert “A Conscious public will not be a possession of a despot and Egyptians are a proof”. I genuinely took the idea seriously that Egyptians would thrive in protesting until they get their preferred form of government; just like the 18th century series of French Revolutions which profoundly affected modern history. However, I realized that this is not the case when I observe the Egyptian army suspended the constitution and took control the revolution. In a similar manner of the 1974 Ethiopian Revolution during which the Ethiopian army  hacked the revolution the Egyptian army did the same. After that I even went as far as asking “If Revolutions are inherently similar?” 
In the meantime the Ethiopian social media sphere and the private press spontaneously embarked on entertaining a sort of peculiar conversations. These conversations were prompted by Jawar Mohamed’s public comment on Al Jazeera’s English daily television program called The Stream. On the show when Jawar was pressed by the host of the show what he prefers, flanked by his ethnic and national identity; he declared his ethnicity comes first over his national identity and acknowledged himself as ‘Oromo First’. Many consider the public discussion which followed the Jawar incident as a pointless exercise of talking past each other but I think of this spectacle in a different way.  I consider this incident as one of fascinating things because it really helped many people to re-examine their understanding of Ethiopia’s historical and political phenomenon. For me that incident was an excellent opportunity and serves as an evidence that we need a ground for long-running debates and a continuous scholarship on Ethiopia’s historical and political phenomenon. The spectacle should be an eye opening and insightful opportunity especially for those of us who are a loosely-knit community of dissents, oppositions groups, writers and activists whose organizing purpose is only to triumph over EPRDF. It was an incident that tasked all of us to find a possible way and build a system that can maintain a consensus among opponents. Furthermore, the incident made it clearer than ever that most of us only know what we do not want but we do not clearly know what we really want. To conclude on this, the incident exposed that Ethiopians struggle for democracy is not principled but rather it is based on indignation and grudge.  
As difficult as this issue to contemplate I started to realize the fact that despotic leaders are generally results of broader and yet fundamental societal flaws. For me this was like the aha! moment. So when revolution is conceived in a society with a high degree of authoritarianism, the end result is usually more authoritarianism. I think it comes down to individual elite who appeared liberal and revolutionary from authoritarian society are either concealed  authoritarian themselves or the society is not yet ready to allow  them to exercise their liberty. This is like a classic causality dilemma, which one came first a chicken or the egg.  But I think one should change first and it should be the society. It is with this eureka effect that I tried to revisit the revolutions in the Arab world. Tunisia, Egypt, Libya, and Syria… and I tend to think that the revolutions in these countries have done more harm than good. They caused a great deal of human suffering. Removing a despot does not necessarily guarantee a change. In similar manner the 1974 Ethiopian Revolution which removed HaileSelassie’s rule and replaced with the Dergue, a Marxist military junta is just as bad (If not worse) than the revolutions of the Arab world. It is even worse if we consider the human suffering that was caused by the infighting and power struggle of the political parties of the time. I have watched when the storied Ukraine for its Orange revolution of 2004 back to revolution all over again in 2014. I even tweeted about it ‘to revolution then calmness and back’. The February 2014 Ukrainian revolution culminated (I am not sure if I can say it is culminated) in turning over its own State Crimea to pro-Russian forces even though it appeared the Russian involvement in Ukrainian affairs cited as one of the cause of the revolution. I also wrote a commentary on my personal blog asking Are revolutions meant to be betrayed? ››My point in this particular blog post was showing reasons why elite citizens who usually initiate revolutions would end up in brawl and infighting after they started revolutions. I used the old Amharic saying to illustrate my point ‘Thieves usually do not fight when they steal but they brawl when they divide what they robbed”.  I intentionally used the word ‘thieves’ to illustrate the context of Ethiopian political reality. I am referring to Ethiopian astroturf political originations (formal or informal) that are organized in the name of interest group to bring social change. Beyond their being astroturf in their nature they fight each other. We have numerous such groups and their sole propose is to get hold of political power and harvest the benefits from it not brining genuine revolution.
For this reason I truly believe we can bring change without going through an instantaneous revolution. We can take a good lesson from the history of English people. The English people have a lot of exemplary deeds. Rule of law, discussion and public engagement though grass root organizations can bring the desired form of government and we can also achieve social change peacefully.
An acquaintance of mine who knows my stance of instantaneous social change came to visit me in prison after I was unjustly accused of inciting revolution.  He looked at me and said ” Aha, what did I told you, there will never be a change without revolution’. But remarkably even in the injustices and sufferings me and my zone9 blogging collective colleagues have been through I still see the need for an authentic social change. Had the society have had the consciousness; they would have seen the impunity of the Ethiopian government (police) enjoy and the injustice we are suffering from. Apparently the Ethiopian government does not have the slightest concern for legitimate questions of Ethiopians but rather they are deeply bothered by the ‘noise of foreign powers’.   Suffering the consequence of using the right to freedom of expression has become a social reality because the society sits silently and watches all the injustice. Society should start to speak up against injustice but to do so we should embark on educative and liberating process through grassroots activism and peaceful disobedience which are yet not happened in Ethiopia. Once a society has become conscious of the benefits of liberating social change and developed a test for liberty there is no way back. I believe consciousness comes first then liberty follows. We have failed spectacularly because as a society we havethe cart before the horse in mostof our projects.  That is how explained for my acquaintance who visited me in prison as well. However, as Kiflu Tadesse put it on the first of two volumed books “That Generation” which dealt with the 1974 Ethiopian Revolution Haile Fida one of the iconic figures of the storied Ethiopian Socialist Movement never predicted Ethiopians would revolted just one year ahead of the 1974 Ethiopian Revolution. According to Kiflu, in 1973 Haile said for Ethiopians to start a revolution it would take them a minimum of twenty five years. Unless I blunder like Haile I don’t think there will be a revolution in Ethiopia in the foreseeable future. Finally like the Ethiopian satirist Abebe Tola usually say if I screw-up on this screw me over. 

የምርጫ አመት ነው። ነጻ ጋዜጦጭ በሙሉ ተዘግተዋል። አገዛዙ በሕዝብና በመንግስት ገንዘብ በየተቋማቱና መስሪያ ቤቶች ስብሰባ እየጠራ ፣ በኢቲቪ ህዝቡን የሚያደነቁረው አንሶት፣ እንደገና በስብሰባ ዜጎችን እያደነቆረ ነው። ኢትዮጵያዊያን የዲሞክራሲያዊ እና ሰብአዊ መብታቸው ተረግጦ በግድ ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረጉ ናቸው። አንዳንዶች “ዉሸት ነው። ኢሕአዴግ ለዲሞክራሲ የቆመ ተራማጅ ድርጅት ነው” ሊሉ ይችላሉ። ይችን አብራ የተያያዘቸውን ማስታወቂይ እንዲያነቡ እናበረታታለን። ይህ […]

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የህሊናና የፖለቲካ እስረኞችን በአደባባይ ሻማ ማብራት ፕሮግራም ለማሰብ፣ የአዲስ አበባ አስተዳደርን በደብዳቤ መጠየቁንና የአስተዳደሩ የሕዝባዊ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ለፕሮግራሙ የተመረጠውን ቦታ የተለያዩ ምክንያቶችን በመስጠት ዕውቅና እንደነፈገው ፓርቲው አሳውቋል፡፡ በመሆኑም ድርጊቱ የተለመደ የሕገ-መንግስታዊና የሕግ ጥሰት መሆኑን በመገንዘብ በጥልቀት ተወያይቶበታል፡፡ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ህብረተሰቡን በግዳጅ ስልጠና ወጥሮ በፈለገበት ቦታ ላይ […]

መስከረም ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአካባቢው ምንጮች እንደገለጹት ለቀናት ጋብ ብሎ የቆየው ግጭት ከትናንት ጀምሮ እንደገና አገርሽቷል። የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ጋትሉዋክ ቱት የገዢው ፓርቲ ልሳን ለሆነው ፋና ሬዲዮ ” ኪራይ ሰብሳቢዎችና የመሬት ደላሎች በጠነሰሱት ሴራ ለዘመናት ተቻችሎ የኖረውን ህዝብ ለመከፋፈል ጥረት በማድረጋቸው መስከረም አንድ በሚጤ ከተማ በተፈጠረው ግጭት 13 ሰዎች” መሞታቸውን፣ በገጠር …

መስከረም ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት በመላ አገሪቱ የሚገኙ የትምህርት ተቋማት መስከረም 5 ትምህርት እንዲጀምሩ ቀደም ብሎ ይዞት የነበረውን እቅድ በመሰረዝ አዲሱ የትምህርት ዘመን ከመስከረም 30 በሁዋላ እንዲጀመር ትእዛዝ አስተላልፏል። በትምህርት ሚ/ር ደኤታ ዶ/ር ካባ ኡርጌሳ ዲንሳ ለሁሉም ዩኒቨርስቲዎች መስከረም 5፣ 2007 ዓም የተጻፈው ደብዳቤ   የአንደኛ አመት ወይም አዲስ ገቢ ተማሪዎች ጥሪ ተደርጎ …

መስከረም ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተመድ የሰብአዊ መብት  ኤክስፐርቶች  ኢትዮጵያ  የጸረ ሽብር ህግን  ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ለማፈን እና የማህበራት ነጻነትን ለመጋፋት እየተጠቀመችበት እንደሆነ በመጥቀስ፤ ህጉን አላግባብ መጠቀሙዋን እንድታቆም መጠየቃቸውን-ከጄኔቫ የወጣ መግለጫ ያመለክታል። የተመድ የሰብ ዓዊ መብት ባለሙያዎች አያይሰውም ኢትዮጵያ  በተያሰው ዓመት መጀመሪያ በሰብአዊ መብት ካውንስል አባላት የጸደቀውንና በ 193 ቱም የመንግስታቱ ድርጅት …

መስከረም ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል በቢቸና አውራጃ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ 2 የቀድሞ የቅንጅት አባሎች ተገድለዋል። ገዢው ፓርቲ እንዳደራጀ የሚነገረው ቡችሌ የተባለው ቡድን ክንዳየ አለሙና አባይነህ በተባሉ የቀድሞ የቅንጅት አባላት ላይ ስዋ ወንዝ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ግድያ መፈጸሙን ለማወቅ ተችሎአል። ሁለቱም ሰዎች በተመሳሳይ መንገድ አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ ተደብድበው መሞታቸው ታውቛል። ከ10 …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የዛሬው የወጣቶች ዓለም ዝግጅት የምልክት ቋንቋ ላይ ያተኩራል። ይህንን በተመለከተ ያነጋገርናቸው ሶስት የአካል ጉዳተኛ ያልሆኑ ነገር ግን የምዕልክት ቋንቋን ኢትዮጵያ ውስጥ ተምረው በዚህ ሙያ የተሰማሩ ወጣቶችን ነው።

የፊታችን እሁድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታስቦ የሚዉለዉ «ዓለም አቀፍ የሰላም ዕለት» ዛሪ በአፍሪቃ ሕብረት ታስቦ ዋለ። የተ.መ ተጠሪዎችና ተቀማጭነታ ቸዉ አዲስ አበባ የሆኑ የሕብረቱ አባል ሃገራት አምባሳደሮች ተገኝተዋል።

የታላቅዋ ብሪታንያ አካል ስኮትላንድ ለመገንጠል፤ ወይም በሕብረቱ ታቅፎ ለመቀጠል፤ በቀረበዉ ጥያቄ መሰረት ትናንት ሕዝበ ዉሳኔ ከተካሄደ በኋላ፤ ስኮትላንድ እንዳትገነጠል የሚፈልገዉ ወገን ማሸነፉ ታዉቋል። በድምፅ ቆጠራዉ መሰረት የስኮትላንድን በብሪታንያ ሕብረት መቆየትን የሚሹት 55,3 በመቶ አብላጫ ድምፅን ሲያገኙ፤

በፍቃዱ ዘ ኃይሉ
 

ርዕሱን  አላስታውሰውም ‘ንጂ እ.ኤ.አ በ2011 Arab Uprising በመባል የሚታወሰውን አብዮትተከትሎ፣ ኢትዮጵያውያን ፌስቡከኞችም (በተለይ ዲያስፖራ የሚገኙ) ግንቦት 20 ላይ (ልክ በኢሕአዴግ የ20ኛ አገዛዝ ዕድሜ)   “Anger day” በሚል በፌስቡክ አብዮትመጥራታቸውን ተቃውሜ አንዲት ጽሑፍ ጽፌ ነበር፡፡ በዓመቱ ደግሞ ‹‹ አብዮት ወረት ነው›› በሚል ርዕስ በፌስቡክ አብዮት ለማስነሳት ፍላጎት ያላቸው በርካቶች እንዳሉ ገልጬ ነገር ግን ይጎድላቸዋል የሚባሉትንነገሮች ዘርዝሬ ጽፌ ነበር፡፡ በነዚህ ሁለት ጽሑፎች ላይ፣ ላዩን አብዮትን የተቃወምኩ ቢመስልም እውነታው ግን ጽሑፎቹ በተጻፉበትወቅት ሕዝቡም፣ ተቃዋሚ ልሂቃኑም፣ ሁኔታዎቹም ለአብዮት ዝግጁ አይደሉም የሚል ዝንባሌ ማሳየቱ ነበር፡፡
ከሌላ ዓመት በኋላደግሞ ‹‹ስለለውጥ›› በሚል ርዕስ ተከታታይ ጽሑፎችን በ‹‹ዞን 9›› ላይ በግል ተነሳሽነት ማስፈር ጀምሬ ነበር፡፡ ጽሑፉን የጀመርኩት ‹‹ኢሕአዴግ ሥልጣኑን በምርጫ ይለቃል?›› በሚል ጥያቄ ነበር፡፡ ‹‹አይለቅም›› የምልባቸውን ምክንያቶች ካስቀመጥኩ በኋላ የለውጥ አማራጭ የምላቸውን (አብዮት፣ሰላማዊ አለመታዘዝ /civil disobedience/ የመሳሰሉትን) በየዘርፉ እየቀነጫጨብኩ ለማሳየት ነበር ዓላማዬ ከዚያም ‹‹የለውጥ ፍርሃት››፣ ‹‹የሥርዓት ለውጥ እና ሃይማኖት››፣ ‹‹የ1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት እና የማኅበራት ሚና›› የሚሉ ርዕሶችን በማንሳት በሐሳቦቹ ላይ በሐቀኝነት ለመከራከር ጥረት አድርጌያለሁ (ከዚህ በላይ አልገፋሁበትም እንጂ)፡፡ በበኩሌ ስለአብዮት በደንብ ያነበብኩትም፣ ያሰብኩትም፣ የጻፍኩትም፣ የተረዳሁትም ያኔ ነበር፡፡ ያኔ በአብዮት ላይ የነበረኝ እምነት ተሸርሽሮ ግማሽ ደርሶ ነበር፡፡ ተንጠፍጥፎ ያለቀው ግን አሁንም በዓመቱ (በ2006 አጋማሽ) ነው፡፡ አንባቢ ከአብዮት አድናቂነት ወደ ዝግመተ ለውጥ አራማጅነት (በ ‹‹ያ ትውልድ›› ሰዎች አጠራር ከRevo ወደ Sabo) የተሸጋገርኩበትን የሐሳብ ዳገት (ከፈለጋችሁ ቁልቁለት በሉት) ይረዳ ዘንድ በመጠኑ ዘርዘርአድርጌ ማስረዳት አለብኝ፡፡ (ታዲያ አብዮት አድናቆቱም ቢሆን ከወረቀት እንዳላለፈ ልብ በሉልኝ)፡፡
እነዚያን ተከታታይ ጽሑፎች በጻፍኩበት ሰሞን  ‹አብዮት ‹‹እቆጣጠረዋለሁ›› ብለው ያሰቡትንነገር ግን ድንገት ከቁጥጥር ውጭ ሊሆን የሚችል እሳትን መለኮስ› እንደሆነ እያሰብኩ ባለሁበት ሰሞን ግብጻውያን ሙርሲን ለመጣል ያምጹ ጀመር፡፡ የግብጹ ድጋሚ አመጽ (አብዮት) በጣም የተዘበራረቀ ስሜት ፈጥሮብኝ ነበር፡፡ ሙርሲ እኔ በግሌ ከማምንባቸውና ቋሚም ከሆኑ የዲሞክራሲ መርሆች እያፈነገጠ ነበር፡፡ ስለዚህ የግብጾች ማበይ ምክንያታዊ ነው ብዬ አምኛለሁ፤ እንዲያውም ሕዝብ አንዴ ‹ከነቃ አይሆንም ዕቃ› ብዬ ነበር፡፡ የግብጽ ሕዝብ የሚፈልገውን ዓይነት ሥርዓት እስከሚያገኝ እያበየ ይቀጥላል የሚል ግምት ነበረኝ- ልክ እንደ ፈረንሳዮቹ ተከታታይ አብዮቶች፡፡  ነገር ግን የግብጽ ሕዝብ እያበየ ቢቀጥልም እንኳን የፈለገውን ላያገኝ እንደሚችል የተረዳሁት ወታደራዊ ክንፍ ቀስ በቀስ አገሪቱን በአብዮቱ ተከልሎ ሲጠቀልላት ስመለከት ነበር ፡፡ ከአገራችን የደርግ አመጣጥ አልለይ ብሎኝ ‹አብዮቶች ሁሉ አንድ ናቸው እንዴ?› እስከሚያስብል ድረስ ተመሳስሎብኝም ነበር፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ሚዲያ እና ፕሬሶች በአንዳች ተዋስኦ ይናጡ ጀመር፡፡ ተዋስኦው የተጀመረው የጃዋር መሐመድን ‹ኦሮሞ ቅድሚያ›(Oromo First) የአልጄዚራ ምላሹን ተከትሎ ነበር፡፡ ብዙዎች ይሄን ወቅት የሚያስታውሱት እንደአላስፈላጊ የንትርክ ወቅት ቢሆንም፣በበኩሌ ብዙዎች ቆም ብለው አቋማቸውን እና የአቋማቸውን መሠረት እንዲፈትሹ፣ በታሪካዊ እና ፖለቲካዊ ኩነቶች ላይ ንባባቸውን እንዲቀጥሉ ያስታወሰ መልካም አጋጣሚ ነው ባይ ነኝ፡፡ ይህ አጋጣሚ በስመ ተቃዋሚ (dissent) የአንድ ኢሕአዴግን ከሥልጣን መውረድ ብቻ እንደ ለውጥ ግብ አድርገን በጋራ ስንንቀሳቀስ የነበርን ተቃዋሚ ግለሰቦች እና ቡድኖች እርስ በርስ ያሉትን ልዩነቶች እና ልዩነቶቻችንን የምናቻችልባቸውን መንገዶች እንድናስተውል መንገድ ፈጥሯል፡፡ ብዙዎቻችን የማንፈልገውን እንጂ የምንፈልገው ምን እንደሆነ በቅጡ እንደማናውቅ፣ትግላችን ከመርሕ ይልቅ በእልሕ እንደሚመራ ያጋለጠ፣ ራሳችንን እንድንገመግም ያስገደደ አጋጣሚ ነበር፡፡

ከዚህ ድንጋጤ ውስጥነው ‹አምባገነን መሪዎቻችን ከሕዝብ ጉያ የወጡ› የአስተሳሰብ ችግር የወለዳቸው የመሆናቸው ሐቅ ዘልቆ የገባኝ (ወይም genuinely comprehend ማድረግ የተቻለኝ) ስለዚህ አብዮት ሲፀነስ ዓላማው ባልተለወጠ ሕዝብ ላይ የተለወጠ መሪ ማስቀመጥ ቢሆንም ሲወለድ ግን አንድም ያልተለወጠ ሕዝብ የተለወጠ መሪ መውለድ ስለማይችል፣ አንድም ደግሞ የተለወጠ መሪ እና ያልተለወጠ ሕዝብ  መዋሐድ ስለማይችሉ፣ አብዮቱ (ዓላማው) ይጨናገፋል፡፡
በዚሁ ጊዜ ነበር የቅርብጊዜ ምሳሌያችንን የአረብ አብዮትን መልሼ በወፍ በረር ለመገምገም የተገደድኩት፡፡ ቱኒዚያ፣ ግብጽ፣ ሊቢያ፣ ሶሪያ…. ከተሳካው የከሸፈው፣ከለማው የወደመው ይበዛል፡፡ የአምባገነን መገርሰስ ብቻውን ለውጥ አያመጣም፤ ከነዚህኞቹ ለውጦች ይልቅ የእኛው ፊውዳሊዝምን ገርስሶ- ወታደራዊ አምባገነንነትን ያመጣው አብዮት የተሻለ ኪሳራ ነበረው ማለት ይቻላል፡፡ (እዚህጋ በኢሕአፓ፣ መኢሶን እና ሌሎችም የደርግ ፓርቲዎች መካከል የተደረገው የድኅረ አብዮት የሥልጣን ሽኩቻ ሳቢያ የጠፋውን ሕይወት ሳንቆጥር መሆኑ ነው፡፡) ከትንሽ ጊዜ በኋላ ደግሞ በብርቱካናማ አብዮቷ የምትደነቀው ዩክሬን አበየች፡፡(‹“የተውኩትን ነገር ተነግሬ፣ ተመክሬ ባገር ምን ጎትቶ አመጣብኝ፣ የአብዮትን ነገር?” Another revolution? ብዬ ትዊት አድርጌም› ነበር) አብዮቷ ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ የአካሏ ክፋይ የሆነችው ክሬሚያን በማሳጣት ይጀምራል፡፡ ምዕራብ ዩክሬናውያን ሲያብዩ ‹የአገራችን መንግሥት ከምዕብራባውያን ይልቅ ምስራቃውያን (ራሺያ….) አደላ› ብለው ቢሆንም በውጤቱ ግን ጭራሽ ራሺያ ክሬሚያን ጠቅልላ አረፈችው፡፡ልብ በሉ! አብዮቱ ከተነሳበት 360 ዲግሪ ዞሮ ተጠናቀቀ፡፡ ለነገሩ አልተጠናቀቀም፤ አሁን ወደ እርስ በእርስ ጦርነት ተሸጋግሯል፡፡
ይኼኔ ነበር በግል ጦማሬ ላይ ጥር 2006 ‹‹Are revolutions meant to be betrayed?›› ብዬ በመጠየቅ የጻፍኩት፡፡ ዜጎች አብዮትን ሲጀምሩት የማይታዩ ችግሮች ሲጨርሱት የሚስተዋለው ‹ሌባ ሲካፈል እንጂ ሲሰርቅ አይጣላም› ነበር የጽሑፌ አንኳር ሐሳብ፡፡ ‹‹ሌባ›› ያልኳቸው  በሕዝባዊ አብዮት ስም የግል ሕልማቸውን የሚያሳኩ አጀንዳ ያላቸውን ቡድኖች (interest groups) ነው፡፡ በኢትዮጵያ ነባራዊ የፖለቲካ እውነታ ደግሞ እነዚህ ዓይነቶቹ interest groups ብዙ ናቸው፡፡ ስለዚህ በአብዮት ለውጥ አማጭነት ተስፋ ስቆርጥ የመጀመሪያ ጥያቄዬ ‹‹ሳያብዩ ለውጥ ማምጣት ይቻላል?›› የሚል ነበር፡፡ የመጀመሪያ መልሴ ‹‹እንግሊዝ›› ነበረች፡፡ የእንግሊዝ ሕዝብና መንግሥት በሕግ የበላይነት ላይ ለማንም ምሳሌ መሆን የሚችል ነው፡፡ የዓለምን ግማሽ በገዙበት ጊዜም አሁንም አብየው አያውቁም- እንግሊዛውያን፡፡ ምክንያቱም ተወያይተው ችግራቸውን መፍታት ይችላሉ፡፡ ሕዝብና መንግሥት ሲለወጡ ሁሉም በሰላም ይካሄዳል፡፡
ይህንን የመጨረሻ አቋሜን ያውቅ የነበረ ወዳጄ፣ ‹‹እህ አሁንስ?›› አለኝ ‹አብዮት ልታስነሳ አሲረሃል› ተብዬ ተጠርጥሬ ከታሰርኩ በኋላ  ሊጎበኘኝ መጥቶ፡፡ ‹‹አየኸው አይደል፣ ያለአብዮት ለውጥ እንደማይመጣ?›› የሚገርመው፣ የኔና የጓደኞቼ በሕገ-ወጣዊ ማንአለብኝነት መታሰርና፣ የመንግሥት (ፖሊስ) ተጠያቂነት ማጣት ውስጥም ሕዝባዊ አለመለወጥ ነው የሚታየኝ፡፡ መንግሥት አሁንም ቢሆን የሚያስጨንቀው ‹‹የውጭ ኃይሎች ጫጫታ›› እንጂ የውስጥ ሰዎች ጥያቄ አይደለም፡፡ በእኛ ላይ የደረሰው (ሐሳብን በመግለጽ ጦስ መታሰር) በሌሎች ላይ ሲደርስ የነበረ፣ እየደረሰ ያለ ፣ ወደፊትም የሚደርስ መሆኑ ቢታወቀውም ሕዝባችን ግን ‹‹መብቴን ማስጠበቅ አለብኝ›› ከማለት ይልቅ ‹‹ዝም ብል ይሻለኛል›› (ጎመን በጤና) mode ውስጥ ነው፡፡ ሕዝብ ገና አልተለወጠም፤ የለውጥ ጣዕሙም የገባው አይመስልም፡፡ ሌሎች ሰላማዊ የትግል አማራጮችም ገና በኢትዮጵያ አልተሞከሩም፡፡ ሕዝቡ ጣዕሙን የማያውቀውን ለውጥ ከመስጠት በፊት ደግሞ የለውጡን ጣዕም አውቆ ለውጡን ራሱ ጠይቆ፣ ራሱ እንዲያመጣው ማንቃት ያስፈልጋል፡፡ አለበለዚያ እንግሊዛውያኑ እንደሚሉት ‹ጋሪው ከፈረሱ ቀድሞ› አይሆንም! ለወዳጄም ይህንኑ ሃሳቤን ነበር የነገርኩት፡፡
ለነገሩ ይህንን ሁሉአልኩ እንጂ ክፍሉ ታደሰ በ‹‹ያ ትውልድ›› (ቅጽ 1) ላይ  ‹ኃይሌፊዳ በ1965 በኢትዮጵያ በ25 ዓመት ጊዜ ውስጥ አብዮት ይነሳል ብዬ አልገምትም ብሎ ነበር› እንዳለው ካልሆንኩ በቀር እኔም በቅርቡ ኢትዮጵያ ውስጥ አብዮት ይነሳል የሚል ምንም ግምት የለኝም፤ በመጨረሻም በአቤ ቶክቻው ዋዘኛ አባባል ‹‹ካጠፋሁ፣ልጥፋ!››

መስከረም ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ ኒክ ኦቻላ ለኢሳት እንደገለጹት በኢትዮጵያ አዲስ አመት ደገኞች በፈጸሙት ጥቃት 8 የመዠንገር ተወላጆች ተገድለው ፣ ከ3 ሺ በላይ የሚሆኑት መሰደዳቸውን ገልጸዋል። 835 መዠንገሮች ቤተክርስቲያን ውስጥ ተጠግተው በምግብ እጥረትና በብርድ ሲሰቃዩ መቆየታቸውን አቶ ኒክ ተናግረዋል። አቶ ኒክ እንደሚሉት ለግጭቱ መንስኤ የኢትዮጵያ መንግስት ያወጣው የመሬት ቅርምት ፖሊሲ ነው። በዚህ …

መስከረም ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከዚህ በላይ የት ሄደን አቤት እንደምንል ግራ ተጋብተናልም በማለት በመንግስት አሰራር ማዘናቸውንም ተናገረዋል፡፡ የቋራ ከተማ ነዋሪዎች ከወራት በፊት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በተገኙበት የጠየቋቸው የመልካም አስተዳደር ፣የመንገድ ፣የመብራት እና ስልክ ችግሮች ይፈታሉ በማለት አመራሮቹ ቃል ቢገቡም በዚህ አመት በተደለደለው የበጀት ቀመር ተጨማሪ በጀት ሳይያዝ መቅረቱ እንዳሳዘናቸው …

መስከረም ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከክልሉ ባለስልጣናት የሚደረሱን መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ፕሬዚዳንቱ አቶ አብዲ ሙሃመድ ወደ አዲስ አበባ እንዲሄዱ ከጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ የቀረበላቸውን ጥሪ ባለመቀበል በክልላቸው የሚገኙ ሲሆን፣ ” በኢትዮጵያ ውስጥ ከህወሃቶች በስተቀር ማንም ከስልጣን ሊያነሳኝ የሚችል ሃይል የለም” በማለት፣ የአቶ ሃይለማርያምን ጥሪ ውድቅ አድርገዋል። በምስራቅ እዝ አዛዥ ጄ/ል አብርሃም ገብረማርያም እንደሚተማመኑ የገለጹት …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

መምህራኑ በዛሬው ዕለት በመቀሌ ከተማ የተለያዩ አዳራሾች ተሰብስበው በ3 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያዩ የተገለጸላቸው ሲሆን አጀንዳዎቹም፡- 1 . ስለተሃድሶ መስመራችንና የኢትዮጵያ ህዳሴ 2 . ዴሞክራሲያዊ ሥርዓታችንና ፈተናው 3 . የትምህርት ጥራትና ማነቆዎቹ የሚሉ ሲሆን ስብሰባው የሚቀጥለው ለ 7 ቀን እንደሆነና ቅዳሜና እሁድንም እንደሚጨምር ከመድረኩ መሪዎች ተገለጸላቸው፡፡ መምህራኑም ” እኛ ቅዳሜና እሁድ መሰብሰብ አንፈልግም ማረፍ አለብን:: በተጨማሪም […]

በሰሜናዊው ጫፍ የብሪታንያ ግዛት አካል ስኮትላንድ ፤ እጎአ በ2012 በተደረገ ስምምነት መሠረት፣ ተገንጥላ የራሷን ነጻነት ለማወጅ ወይም ከ 300 ዓመት በላይ ጸንቶ በቆየው ሕብረት፣ ዩናይትድ ኪንግደም በሚባለው ሀገር፣ ማለትም በብሪታንያ በሕብረት ለመኖር፤ ከሁለቱ አንዱን ለመምረጥ፣ ህዝቡ ከዛሬ ጧት አንስቶ እስከማታ ድምፁን በመስጠት ላይ ነው።

በዓለማችን «ግሎባላይዜሽን» ወይም አፅናፋዊዉን ትስስርን ተከትሎ በተለይ በአፍሪቃ ሀገራት ከተሞች የሚደረገዉ ፈጣን የግንባታ ሥራ ታሪካዊ ቅርሶችን እያወደመ መሆኑ አሳሰቢነቱን እያጎላ መጥቶአል።

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ፣ ከፍተኛ የኤኮኖሚና የንግድ ልዑካንን አስከትለው፣ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ፤ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ የአመራር አባላትና ከአፍሪቃ ሕብረት ባለሥልጣናት ጋር መወያየታቸው ታውቋል።

ራሱን «እስላማዊ መንግሥት » በማለት የሚጠራው በኢራቅና ከፊል ሶሪያ የሚንቀሳቀሰው አክራሪ ታጣቂ ንቅናቄ ፣ ከዚህ ቀደም የ ሁለት አሜሪካውያን ጋዜጠኞችንና አንድ የብሪታንያ ተወላጅ አንገት ከቀላ ወዲህ፤

ኢትዮጵያ ውስጥ ዘንድሮ በሚካሄደው ብሔራዊ ምርጫ፣ የሲቭል ማሕበራት ድርሻ ሊጠናከር ይገባል ተባለ። ይህ የተገለጠው፤ የኢትዮጵያ ራእይ ም/ቤት ለዴሞክራሲ ግንባታ « ቪዥን ኢትዮጵፕያን ኮንግረስ ፎር ዴሞክራሲ»

የመድረክ አመራር አባል ዶር በየነ ጴጥሮስ ፣ ከአዲስ አድማሷ ጋዜጠኛ ኤልሳቤጥ እቁባይ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ አስተያየት ሰጥተዋል። በተለይም በመድረክ ዉስጥ ስላሉት ችግሮች የተጠየቁት ዶር በየነ፣ ከአንድነት ፓርቲ ጋር ከተፈጠረው ችግር ዉጭ ሌላ ምንም ችግር መድረክ ዉስጥ እንደሌለ ገልጸዋል። በአረና ትግራይ ዉስጥ፣ ታዋቂው ታጋይ አቶ አስገዴን ጨምሮ ከአረና በለቀቁ አባላት ዙሪያ ምላሽ […]

የአንድነት ፓርቲ የመቱ ዞን የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ታመነ መንገሻ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ መስከረም 3 ቀን 2007 ዓ.ም በመቱ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸውን ከአካባቢው የደረሰን ዜና ያመለክታል፡፡ አቶ ታመነ መንገሻ የታሰሩት አማራ ይቀውጣ ብለሃል በሚል ሰበብ እንደሆነና ይህን ተናገሩ በተባለበት ወቅት ታመው አልጋ ላይ እንደነበሩ ምንጮቻችን የገለጹ ሲሆን ፖሊስ በሳቸው ላይ እንዲመሰክር ፖሊስ ጣቢያ ለምስክርነት […]

መስከረም ፯(ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቀድሞው የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት የህዝብ ግንኙነት ስራ አማካሪ እና የክልሉ የወጣቶች ሊቀመንበር በመሆን ካገለገለ በሁዋላ የተለያዩ የቪዲዮ ማስረጃዎችን በመያዝ ከአገር የወጣው ወጣት አብዱላሂ ሁሴን ፣ “ኦ ኦጋዴን” በሚል ኢሳት ያስተላለፈው አጭር የዶክመንታሪ ፊልም፣ በስልጣን ላይ ያሉት ገዢዎች ለሶማሊ፣ ለኢትዮጵያና በአጠቃላይ ለሰው ልጆች ያላቸውን ንቀት ያሳያል ብሎአል። ዘገባውን ከተመለከተ …

መስከረም ፯(ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ህገመንግስቱ የጸደቀበትን ህዳር 29 ቀን «የብሔር ብሔረሰቦች ቀን» በሚል በየዓመቱ ሲያከብረው የቆየው ኢህአዴግ ዘንድሮ  20ኛውን ዓመት በተለየ ድምቅት በማክበር ሕዝቦች በሕገመንግስቱ የተረጋገጡላቸውን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች አተገባበር እንከን አልባ እንደነበሩ በማጉላት በመጪው ግንቦት ወር ይካሄዳል ተብሎ በሚገመተው ምርጫ ላይ ከፍተኛ ድል ለማግኘት አቅዶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑ ለፌዴሬሽን ምክርቤት ቅርበት ያላቸው …

– ያልበሰሉ ካድሬዎች ድክመቶቻቸውን ይዘው ሃገሪቱን የማትወጣበት ከባድ አደጋ ውስጥ ከተዋታል። – የኢትዮጵያ ህዝቦች የጋራ መስዋትነት በመክፈል ታሪካዊ ድሎችን የምንቀዳጅበት ጊዜ ነው። – ወሳኙ የትግል ጊዜ እና የወያኔ በር በርግደን ነጻነታችንን የምናረጋግጥበት ቁልፉ በጃችን ነው። – አንዱ አንዱን ሲኮረኩም የወያኔን እድሜ እያስረዘምን በህዝብ ሰቆቃ እየቀለድን መሆኑን አንዘንጋ። – ግለሰቦች ላይ በማተኮር የህዝቦችን የነጻነት እና የለውጥ […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የጀርመን ርእሰ ብሔር ዮአኪም ጋውክ ፣ ከቐጠር አሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ ኧል ታኒ ጋር ፣ ባደረጉት የ 20 ደቂቃ ውይይት ራሱን እስላማዊ መንግሥት እያለ ለሚጠራው አሸባሪ ሚሊሺያ ጦር፣ ያቺው ሀገር እርዳታ ትሰጣለች ስለመባሉ ቢያነሱም ፤አ ሚሩ ማስተባበላቸው ተነገረ።

ባለፈው ኀሙስ፣ የርእሰ ዐውደ ዓመት ዕለት ወደ ራዲዮ ጣቢያችን ብቅ ብለው ከነበሩት በቦን ዩንቨርስቲ በከፍተኛ ደረጃ የግብርና ሳይንስ ትምህርት መከታተል ከጀመሩት 3 ኢትዮጵያውያን መካከል ፤ ከጂማ ዩንቨርስቲ የመጣው

የአውሮጳ ኅብረት በምዕራብ አፍሪቃ የተከሰተውን የኤቦላ ወረርሽኝ ለመከላከል እና በበሽታው የተጎዱትን ለመርዳት ሊያበረክተው ስለሚችለው ድርሻ ሰሞኑን በብራስልስ በስፋት መከረ። በዚሁ የአውሮጳ ኅብረት ኮሚሽን በጠራው

ሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተጀመረበት 75 ኛ ዓመት ከጥቂት ጊዚያት በፊት መታሰቡ የሚታወስ ነው። ይሁንና፣ ኢትዮጵያውያን የታሪክ ምሁራን ፣ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተጀመረው ፋሺስት ኢጣልያ የዓለም መንግሥታት

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ከፍተኛ የኤኮኖሚና ንግድ ልዑካንን አስከትለው ኢትዮጵያን ለመጉብኘት ትናንት አዲስ አበባ መግባታቸው ተነገረ። ው ጉ ሚንስትሩ ፣ ዛሬ ከኢትዮጵያ ጠ ሚንስትር

መስከረም ፮(ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ አብዲ ሙሃመድ 7 የስራ አስፈጻሚ የኮሚቴ አባላትን ማበረራቸውን ተከትሎ ወደ አዲስ አበባ በአስቸኳይ እንዲመጡ ቢታዘዙም፣ የቀረበላቸውን ጥሪ ባለመቀበል ጅጅጋ ውስጥ እንደሚገኙ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ምንጮች ተናግረዋል። ለአቶ አብዲ ቅርበት ያላቸው የመከላከያ ባለስልጣኖች በተደጋጋሚ ስልኮችን በመደወል አቶ አብዲን ለማግባባት እየሞከሩ ሲሆን  አቶ አብዲ በበኩላቸው ” ኢትዮጵያ ውስጥ 30 …

መስከረም ፮(ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ለሁለተኛ ዙር እየተካሄደ ያለው የኢህአዴግ ስልጠና በአንዳንድ ዩኒቨርስቲዎች በአለመግባባት ሲቀጥል፣ በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ ተማሪዎች በመሰላቸት ውይይቶችን እንደማይከታተሉ ከተሳታፊዎች የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። የተለያዩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ  ተማሪዎች  ውይይቱ አሰልቺ በመሆኑ አብዛኛው ተማሪ የግሉን ስራ እንደሚሰራና ውይይቱን እንደማይከታተል ገልጸዋል። ለመምህራን በሚሰጠው ስልጠና ደግሞ በአንዳንድ የማሰልጠኛ ቦታዎች መምህራን ሃሳብ …