በቅድሚያ መጽሓፉን ጊዜ ሰጥተህ በማንበብ አስደማሚ ምልከታ በመስጠትህ ከልብ አመሰግናለሁ ። የተጻፈበትም አንዱ አላማ ይህ ስለሆነ። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በእይታህ ላይ እነዚህ ጉድለት ይታይባቸዋል ብለህ ያነሳኸው እና የወደፊት ግምቶችህ ላይ የተወሰነ አስተያየት ለመስጠት የሚጋብዙ ስለሆነ ትንሽ ማለት ፈለኩ። በዚህ አጋጣሚ ሌሎች በመጵሀፉ ይዘት ላይ ዝርዝር ግምገማ ላደረጉ ሰዎች ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። ለእያንዳንዱ አስተያየት መስጠት ከጊዜ አኳያ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ የማልዘልቅበትን መንገድ ልጀምረው አልፈለኩም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ተመስገን ደሳለኝ

በዚህ ተጠየቅ ጨርፈን የምንመለከተው በኮሙኑዮኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ የነበረውና ዛሬ በስደት የሚገኘው የአቶ ኤርሚያስ ለገሰን “የመለስ ትሩፋቶች፣ ባለቤት አልባ ከተማ” የተሰኘው መጽሐፍን ነው፡፡ የመድብሉ ጻሐፊ ኤርሚያስን በግል አላውቀውም፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል ያየሁት አቶ በረከት ስምዖን እርሱን እና ሽመልስ ከማልን ምክትሎቹ አድርጐ በሚኒስቴር ዲኤታ ማዕረግ መሾሙን በግዮን ሆቴል ለጋዜጠኞች ይፋ ባደረገበት ዝግጅት ላይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

“ዩናይትድ ስቴትስ የራሷን ጥቅሞች ለማስጠበቅ ወደ ኋላ እንደማትል ሁሉ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተመሰረተበትና ያለበትን ዓላማም ከማክበርም አታፈገፍግም፤” የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ።

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

መስከረም ፲፬(አሥራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎችን የአብዮታዊ ዲሞክራሲ የትምህርት መመሪያን ለማጥመቅ ያወጣውን መመሪያ ተከትሎ በአገሪቱ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ስልጠናውን በግዳጅ እንዲወስዱ እየተደረጉ ነው። በአንዳንድ አካባቢዎች ተማሪዎቹ የፖለቲካ ስልጠና እንዳለ አስቀድመው በመስማታቸው ፣ ከስልጠናውን የቀሩ ሲሆን፣ የገዢው ፓርቲ የወረዳ ሹሞች መምህራን ተማሪዎችን እንዲያመጡ የተለያዩ ዘዴዎችን እንዲጠቀሙ እያግባቡ ነው። አንድ …

መስከረም ፲፬(አሥራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የብአዴን ንብረት በሆነው ጥረት ኮርፖሬት ውስጥ የሚገኙት ጣና ሞባይል ና ዘለቀ እርሻ ልማት ድርጅቶች በያዝነው አመት ከ225 ሚልዩን ብር በላይ ኪሳራ እንዳጋጠማቸው በ2007 ዓም መግቢያ ላይ በተደረገው የድርጅቱ ግምገማ ላይ ተገልጧል። አቶ አለምነው መኮንን የአማራውን ህዝብ መሳደባቸውን ተከትሎ በክልሉ ውስጥ የሚገኙ አመራሮችን ለማሳመን የተደረጉ ስብሰባዎች ና የተሃድሶ …

መስከረም ፲፬(አሥራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመላ አገሪቱ ከ40 ሚሊዮን በላይ መጻፍና ማንበብ የማይችሉ ወጣት እና ጎልማሶች አሉ ያሉት አቶ ሺፈራው ፤  ይህንን የትምህርት እድል ያለገኙ ወጣቶች እና ጎልማሶች አማራጭ ትምህርት እንዲያገኙ የተደረገው ሙከራ አፈፃጸሙ ከዜሮ በታች ነው ብለዋል። በኢህአዴግ የእቅድ ትውውቅ መድረክ ላይ እንደቀረበው በጎልማሶች የትምህርት አቀራረብ  አማራ 0.9፣ ኦሮምያ ፣ 0.71 …

መስከረም ፲፬(አሥራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዋጋ ንረትን ያረጋጋሉ ተብሎ በመንግሥት ልዩ ድጋፍ በተለይ በአዲስአበባ ከተማ የተቋቋሙት የሸማቾች የህብረት ሥራ ማህበራት በሙስናና ብልሹ አሠራር ውስጥ በመዘፈቅ አንዳንዶቹ በተቃራኒው የዋጋ ንረትን የሚያባብሱ ሥራዎች ውስጥ መሰማራታቸው መረጋገጡን ከአስተዳደሩ የተገኘ ሰነድ ጠቆመ፡፡ 250ሺ ያህል አባላት ያሉዋቸው 153 መሰረታዊ ማህበራትና 10 ዩኒየኖች እንዲሁም 1 ሺ 815 አዲስ …

ዓለም በኤቦላ ስጋት መታመስ ሲጀምር በቀድሞዋ ዛየር በዛሬዋ ዴሞክራቲክ ሬፐብሊክ ኮንጎ ተኅዋሲውን ያገኙት የቤልጅየም ተወላጁ ፕሮፌሰር ፒተር ፒዮ መታወስ ጀመሩ።ፕሮፌሰሩ በአሁኑ ወቅት የለንደን የግል ንጽህናና የምድር ወገብ አካባቢ በሽታዎች ትምህርት ቤትን በሃላፊነት ይመራሉ።

Jennifer Hudson ሶስትኛዋ የሆንውን የእስቱዲዮ አልበሟን በገበያ ላይ አወላለቸ ፡፡ የአልበሙ መጠሪያ JHUD የተባለ ሲሆን በወስጡ 10 ዜማዎችን አካቷል በዛሬው የሙዚቃ ቃና ፕሮግራም ከዚሁ አዲስ አልበም የተመረጡ ዜማዎችን እና ሰለሞን ክፍሌ ስለ Frank Sinatra ያዘጋጀው ፕሮግራም ትካቷል፡፡

የስዊድን የሕግ ባለሞያዎች በስብዕና ላይ ወንጀል ፈፅመዋል ባሉዋቸው ከፍተኛ የኤርትራ ባለሥልጣናት ላይ ክስ እንዲመሠረት ያቀረቡበትን ጥያቄ የስዊድን ዓቃቤ ሕግ ውድቅ ካደረገባቸው በኋላ ይግባኝ ማመልከቻ አስገብተው መልሳቸውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።

በሶርያ እና በኢራቅ የሚንቀሳቀሱትን የ«አይ ኤስ» ተዋጊዎች የሚቀላቀሉት አውሮጳውያን ቁጥር ባለፉት ጥቂት ወራት ውስጥ በአንድ ሶስተኛ መጨመሩን የአውሮጳ ኅብረት የፀረ ሽብርተኝነት ክፍል አስታወቀ።

በተወለዱ 28 ቀናት ጨቅላዎች ለሞት የሚዳረጉበት ምክንያት ከነፍሰጡር እናት ጤንነትና አመጋገብ ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው። የእርግዝና ክትትልና በወሊድ ወቅትና ከወሊድ በኋላ እንክብካቤ በማድረግ በተወለዱ እስከ 28 ቀናት ውስጥ የሚሞቱ ህጻናትን ቁጥር መቀነስ ይቻላል።

መስከረም ፲፫(አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጄኔቫ ሲካሄድ በሰነበተው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብት ግምገማ ላይ አቋሙን ያስታወቀው አለማቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ ኢትዮጵያ የሰአብአዊ መብት ድንጋጌዎችን እንደምታከብር ቃል መግባት ብቻ ሳይሆን፣ በተጨባጭ ገለልተኛ ወገኖች እስር ቤቶችን እንዲገበኙ፣ የሰብአዊ መብት ጥሰት የሚካሄዱባቸውን ቦታዎች እንዲጎበኙና በደል የደረሰባቸውን ወገኖች ለማነጋገር እንዲፈቀድላቸው ጠይቋል። የሰብአዊ …

መስከረም ፲፫(አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው በአቶ ገዱ አንዳርጋቸው በተመራው ስብሰባ ላይ ዳኞች የስርአቲ ደጋፊ እንዲሆኑ እየተገደዱ ባለበት ሁኔታ እንዴት ነጻ ዳኝነት ሊሰጥ ይችላል በማለት ጠይቀዋል። የድርጅት አባላት ያልሆኑ ዳኞችም ስራቸውን ለመስራት እየተቸገሩ መምጣታቸውን መናገራቸውን ጋዜጣው ዘግቧል። ይሄው በመላው አገሪቱ በሚደረገው የፖለቲካ ስልጠና የገዢው ፓርቲ ደጋፊ አባላት ሳይቀሩ በስርአቱ ላይ …

መስከረም ፲፫(አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ስራ በሚገኘው ደጀና አቬሺን ውስጥ የሚሰራ ስሙ በውል ያልታወቀ አንድ ወታደር በግቢው ውስጥ ለሚሰሩ  ሰራተኞች  በተከፈተው ሻሂ ቤት ውስጥ በአስተናጋጅነት የምትሰራዋን በደብረዘይት ነዋሪ የሆነች ወጣት በስድስት ጥይቶች ተኩሶ መግደሉን የአይን እማኞች ገለጹ። ትናንት 11 ሰአት ላይ ሰራተኞች ሰርቪስ አውቶቡስ ለመያዝ በተሰለፉበት ወቅት፣ ወታደሩ በአስራዎች …

መስከረም ፲፫(አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከደቡብ ሱዳን ታፍነው የተወሰዱት የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ኦኬሎ አኳይ በእስር ቤት ውስጥ ከሌላ እስረኛ ጋር ተጋጭተዋል በሚል ሰበብ ከፍተኛ ድብደባ ከደረሰባቸው በሁዋላ ጸሃይ ላይ ለረጅም ሰአት እንዲቀመጡ ተደርገዋል። አቶ ኦኬሎ ድብደባው የተፈጸመባቸው ቂልንጦ እየተባለ በሚጠራው  እስር ቤት ውስጥ ሲሆን፣ በእስር ቤት ሃላፊዎች መረጃ እንዲያቀርብ ተብሎ …

መስከረም ፲፫(አሥራ ሦስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው መግለጫ 130 የሚሆኑ የቻይና ኩባንያዎች ለአፍሪካ መሪዎች በእስር ቤት ጥቅም ላይ የሚሆኑ የማሰቃያ መሳሪያዎችን ይሸጣሉ። የኤልክትሪክ ንዝረት ያላቸው   ከብረት የተሰሩ ሹል ዱላዎችና ሌሎችም  የማሰቃያ መሳሪያዎች ለአፍሪካ እና ለእስያ አገራት መሸጣቸው በአህጉራቱ ውስጥ የሚታየውን ሰብአዊ መብት እረገጣ አባብሶታል። በአለም ላይ ስለት ያላቸውን የንዝረት ብረቶችን የምታመርተው …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በተወለዱ 28 ቀናት ጨቅላዎች ለሞት የሚዳረጉበት ምክንያት ከነፍሰጡር እናት ጤንነትና አመጋገብ ጋር በቀጥታ የተገናኘ ነው። የእርግዝና ክትትልና በወሊድ ወቅትና ከወሊድ በኋላ እንክብካቤ በማድረግ በተወለዱ እስከ 28 ቀናት ውስጥ የሚሞቱ ህጻናትን ቁጥር መቀነስ ይቻላል።

ሐይማኖት አለሙ በተዋኝነት፤በአዘጋጅነትና በፀፌ ተዉኔትነት በኢትዮጵያና ከኢትዮጵያ ዉጪ በተለይ ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ በበርካታ ድራማዎች ተሳትፏል። ሐይማኖት በተለያዩ ቲያትሮች በሥራ-አስኪያጅነትና በአዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲም በመምሕርነት ያገለገለ የጥበበብ ሰዉ ነበር። 68 ዓመቱ ነበር።

የጀርመን መከላከያ ሚኒስትር ኦዙላ ፎንዴር ላይን፤ የኤቦላ ተዋኅሲ ስርጭትን ለመግታት በሚደረገዉ ጥረት ለመካፈል በፈቃደኝነት ወደ ምዕራብ አፍሪቃ ለሚሄዱ ወታደሮችን እና ሲቪል ሰራተኞች ትናንት ጥሪ አደረጉ።

ከፊል ሰነዓን ባመሰቃቀለዉ ዉጊያ 350 ሐምሳ ያክል ሰዎች ተገድለዋል።በሺሕ የሚቆጠሩትን ከቤት ንብረታቸዉ አፈነቃሏል።ሁለቱ አማፂያንና የሐገሪቱ መንግሥት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሸምጋይነት ተኩስ ለማቆም ከተስማሙ ካለፈዉ ዕሁድ ወዲሕ ግን ከተማይቱ ተረጋግታለች።

ትክክለኛ የቋሚና አላቂ ንብረት ምዝገባና አስተዳደር፣ ተቀባይነት ያለውና እምነት የሚጣልበት የገንዘብ ገቢና ወጪ እንቅስቃሴ፣ ግልጽና ወጥነት ያለው የግዥ አፈጻጸም፣ ብቁ የቁጥጥር ሥርዐት ባለመዘርጋቱ የቤተ ክርስቲያናችን ጥቅል ሀብት አይታወቅም፡፡ በማንኛውም ሕጋዊና ዘመናዊ የሒሳብ ምርመራ አሠራር እጅግ ኋላ ቀር በኾነው በነጠላ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ እና በሞዴላሞዴሎች አሠራር የቤተ ክርስቲያንን ገንዘብ እና ንብረት ከብኩንነት፣ ከመዘረፍ እና ከመጭበርበር ለማዳን …

መስከረም ፲፪(አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምዕራብ አርማጮሆ ወረዳ የአብርሃጅራ ነዋሪዎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በተደረገው ህዝባዊ ስብሰባ በመሬት ስሪት ፣በልማት ና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ዙሪያ ቅሬታወች ቀርበዋል፡፡በውይይቱ ላይ በመገኘት ቅሬታቸውን ያቀረቡት ነዋሪዎቹ “የወረዳው አመራሮች እርስ በርስ በመሻኮት ስልጣን ለመያዝ ሰዎችን ያስገድላሉ የበላይ አመራሮችን የኑሮ ሁኔታ በማጥናት ቤት ሰርተዋል፣ሃብት አከማችተዋል በማለት እነርሱም የበላይ አለቆቻቸውን …

መስከረም ፲፪(አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ባወጣው መግለጫ ፍትህ ሚኒስቴር ሃምሌ 28፣ ቀን 2006 ዓም በፋክት፣ ሎሚ፣ ጃኖ፣ አዲስ ጉዳይ፣ እንቁ መጽሄቶችና አፍሮ ታይምስ ጋዜጣ ላይ ያቀረበው ክስ በህገመንግስቱ የሰፈረውን ሃሳብን የመግለጽ ነጻነት ፣  ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው የሰብአዊ መብቶች አለማቀፍ መግለጫ አንቀጽ 19 ፣ የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች አለማቀፍ ቃልኪዳን አንቀጽ 19 …

መስከረም ፲፪(አሥራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ገዢው ፓርቲ ለመጪው ምርጫ በሚያደርገው ዝግጀቱ የመንግስት ሰራተኞችን፣ መመህራንና ተማሪዎችን በማስገደድ የሚሰጠው የፖለቲካ ስልጠና እንደቀጠለ ሲሆን፣ ባሳለፍነው ሳምንትም በርካታ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጥያቄዎች ተነስተዋል። በአዲስ አበባ በኢትዮ-ቻይና ቲቪቲ በነበረው ስልጠና ላይ ” ከ23 አመታት በሁዋላ አሁንም እራሳችሁን ከደርግ ጋር እያነጻጸራችሁ ነው? ደርግ ከሻእቢያ፣ ከእናንተ ጋርና ከሶማሊያ ጋር ጦርነት …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የ85 ሰዎች ገቢ ከግማሽ ከሚበልጠዉ የዓለም ሕዝብ ይበልጣል።—የዓመዓቱ ግብ ያልተሳካዉ በፖለቲካዊ ዳተኝነት፤ በዕዉቀት እጦት ብቻ አይደለም።በጥቅም ሽኩቻ እና ዕቅዱ የሐብት ክፍፍል የሚያነሳ በመሆኑም ጭምር እንጂ

የአፍጋኒስታኑ የቀድሞ የገንዘብ ሚኒስትር አሽራፍ ጋኒና የቀድሞዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱላህ አብዱላህ ምንም እንኳን ሁለቱ ተፎካካሪዎች ስለምርጫዉ ዉጤትና ስለወደፊት የስልጣን ክፍፍል ሲወዛገቡ ቢቆዩም በመጨረሻ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ለመመስረት ተስማምተዋል። ይህ ለአፍጋኒስታን የስልጣን ፉክክር መጨረሻ ይሆን ይሆን?

ከአምስት ወራት ገደማ በፊት የተመረቀው የአዳማ አዲስ አበባ የፍጥነት መንገድ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ አንድ ሳምንት ሆነው። አዲሱ መንገድ የባለአሽከርካሪዎችን ጊዜ መቆጠብ ማስቻሉንተገልጋዮች በደስታ ገልጸዋል።

ደራሲ – እንዳለ ጌታ ከበደ

ዋጋ – 49 ብር

አታሚ – ኤች ዋይ ማተሚያ ቤት

እንዳለ ጌታ የጻፈውን እምቢታ መጽሐፍ ከአዲስ አበባ ወደ አውስትራልያ እየተጓዝኩ አውሮፕላን ውስጥ ነው ያነበብኩት፡፡ መጽሐፉ ለገበያ ሲቀርብ እንደማልኖር ስላወቀ ቀድሜ እንዳገኘው በማድረጉ አመሰግነዋለሁ፡፡ ይኼ በታሪክና በሥነ ቃል(ፎክሎር) ላይ የተመሠረተ ልቦለድ በአንዲት ብዙዎቻችን በማናውቃት ከዘመን የቀደመች ሴት ጀግና ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡

ቃቄ ወርድወት ትባላለች፡፡ በነገራችን ላይ ቃቄ የአባቷ ስም ነው፡፡ የእርሷ ስም ወርድወት ነው፡፡ በጉራጌ ባሕል የአባትን ስም ከልጅ የሚያስቀድም ጥንታዊ ሥርዓት ነበረ ማለት ነው፡፡ ምናልባትም በዕውቀቱ ስዩም ‹በኢትዮጵያ ከልጅ ስም በፊት የአባት እንደሚቀድም ማስረጃ አለኝ› ያለው አንዱ ይኼንን ሳይሆን አይቀርም ብዬ ገምቻለሁ፡፡ የመጽሐፉን ረቂቅ መመልከቱን መግቢያው ላይ ያሳያልና፡፡

ቃቄ ወርድወት በ1840ዎቹ አካባቢ ከጉራጌ ማኅበረሰብ የፈነጠቀች ኢትዮጵያዊት ኮከብ ነበረች፡፡ በሴቶች ላይ የነበረውን አድሏዊ ልማዳዊ ሥርዓት ለመታገል፣ በጋብቻ ሥርዓት ወንዶቹ ከሴቶቹ ይልቅ ሥልጣን ለማደላደል፤ ሴቶች ከለፉበት ትዳራቸው ያለ አንዳች ንብረት በፍቺ መባረራቸውን ለማስቀረት የታገለች ጀግና፡፡ ዛሬ እንኳን ለብዙ ኢትዮጵያውያን ሴቶች አስቸጋሪ የሆነውን ‹ሴት ልጅ ተመርጣ ብቻ ሳይሆን መርጣም ማግባት አለባት› የሚለውን ሐሳብ ይዛ የታገለች፤ ታግላም በራሷ ላይ የፈጸመች ጀግና ሴት ናት፡፡

በዚያ የሴቶች መብት፣ የጾታ እኩልነት የሚሉ ዘመናዊ ሐሳቦች ባልዳበሩበት፤ ለሴቶች መብት ቆመናል የሚሉ ተቋማት ባልነበሩበት ዘመን ከዘመኗ ቀድማ ችግሩን የተረዳች፤ የሴቶችን ችግር ለመቅረፍና እናቶቻችን ፍትሕ እንዲያገኙ ለማድረግ በጉራጌ ማኅበረሰብ ባሕል ከፍተኛው ሸንጎ እስከሆነው ኧጆካ አደባባይ ድረስ የተሟገተች ጀግና ናት፡፡

እንዳለ ጌታ የዚህችን የማናውቃትን ጀግናችንን የተጋድሎ ታሪክ ከልዩ ልዩ ምንጮች ሰብስቦ፣ ሥነ ቃሉን አስማምቶ፣ ከሀገራችን ታሪካዊ መዛግብት ጋር አዋሕዶ በልቦለድ መልክ አቅርቦልናል፡፡ ወጥ ልቦለዶች እያነሡ፣ የትርጉም ሥራዎች ቦታችንን እየወሰዱ ባሉበት ዘመን የራሳችንን ታሪክ መልሰን እንድናይ የሚያደርግ እንዲህ ያለውን ሥራ ማግኘት ለሥነ ጽሑፋችን አንድ እመርታ ነው፡፡

ሰው የሚያውቀውን ሲያቀርብ፣ የሚያቀርበውንም ሲያውቅ ደስ ይላል፡፡ የኖረበትን፣ የተሠራበትንና የተዋሐደውን ነገር ሲተርክ ከውስጡ ስለሚመነጭ ከዛፍ ሥር የሚመነጭን ውኃ እንደመጠጣት ይቆጠራል፡፡ አንድን ማኅበረሰብ በዕንግዳ ዓይን ማየት ተለምዶ የሚመስሉትን ነገሮች በሚገባ ለማንጠር ይረዳል፡፡ የውስጡ ሰው ለምዶት የሚያልፈውን ዕንግዳ ሰው ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ አንድን ማኅበረሰብ በውስጥ ሰው ማየት ደግሞ የሚያውቁትን፣ የኖሩበትንና ትርጉሙንም በሚገባ የሚያውቁትን ነገር እንደ ልብ ምት አዳምጦ ለማቅረብ ይረዳል፡፡ የቃቄ ወርድወት ታሪክ እንዲህ ሆኖ ነው የቀረበው፡፡ ማኅበረሰቡ የተሰፋበትን እያንዳንዷን ሰበዝ ታዩበታላችሁ፡፤ ያውም ሳይታወቃችሁ፡፡

የእንዳለ ጌታ መጽሐፍም የኖረበትንና ያጠናውን ማኅበረሰብ ያቀረበበት ስለሆነ ሁለት መቶ ዓመታትን ተሻግራችሁ ትነጉዱና ከቃቄ ወርድወት ጋር ለመብት ትታገላላችሁ፣ ጉራጌ ገብታችሁ ደመራ ታበራላችሁ፣ መስቀል ታከብራላችሁ፣ ክትፎ ትበላላችሁ፣ ከነገሥታቱና መኳንንቱ ጋር ትዋጋላችሁ፡፡ ኧጆካ ትወጣላችሁ፣ ጀፎረ ላይ ትቀመጣላችሁ፡፡

በጉራጌ ማኅበረሰብና በማዕከላዊው መንግሥት መካከል፣ በጉራጌ ማኅበረሰብና በሌሎች የአካባቢው ማኅበረሰቦች መካከል ፍቅርም፣ ጠብም፣ ጦርነትም፣ ዕርቅም ነበረ፡፡ እነዚህ ግንኙነቶች በማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጥሩትን አሉታዊና አዎንታዊ ነገሮች በእንዳለ ጌታ ዓይን ስናያቸው አንድን ታላቅ ማኅበረሰብ በመፍጠር ሂደት ውስጥ የተከናወኑ የሂደቱ መገለጫዎች እንጂ የቂም መቋጠሪያዎች ሆነው አናገኛቸውም፡፡ በአንድ ቤተሰብ ውስጥ በሚገኙ ልጆች መካከል የሚኖር መጣላትና መዋደድ የልጆቹ የዕድገታቸው ሂደት አካል እንደሚሆነው ማለት ነው፡፡

በየአካባቢው የሚገኘውና የማናውቀው ታሪካችንና ባሕላችን እንዲህ ለነገዋ ሀገራችን መቀመሚያ በሚሆን፣ ያለፈውንም ለማወቂያና ለማረሚያ በሚያገለግል፣ በሌላ በኩል ደግሞ አቃፊ እንጂ አግላይ ባልሆነ መንገድ ቢቀርብልን የአንዱ አካባቢ ታሪክ የሁላችንም እየሆነ ‹የኢትዮጵያ› ስንል የሚጎድለን አይኖርም ነበር፡፡ አሁን አሁን ግን ‹የኢትዮጵያ› ስንል የሚጎድሉን ነገሮች አሉ፡፡ አንድም አንዳንዶች ‹የኼማ የራሳችን ብቻ ነው› ብለው ቆርጠው በማስቀረታቸው፣ አንድም ደግሞ ‹የኢትዮጵያ› የተባለው ነገር አንዳንዶችን አግልሎ በማስቀረቱ፡፡ ሁለቱም ግን እኩል ነው የሚጎዱት፡፡ የጉራጌ ክትፎ የሁላችንም እንደሆነው ሁሉ የየአካባቢው ሥነ ቃል፣ ታሪክ፣ ባሕልና ቅርስ እየወጣ የሁላችንም እየሆነ መሄድና ወደ ዋናው አካል እየተቀለቀለ፣ ለዋናው አካል ግንባታም አስተዋጽዖ እያደረገ መሄድ አለበት፡፡ ማግለልም መገለልም አንድ ናቸው፡፡

የአካባቢውን ሥነ ቃል፣ ታሪክና ባሕል ከምናገኝባቸውና የራሳችን ከምናደርግባቸው መንገዶች አንዱ ኪነ ጥበባዊ በሆነ መንገድ ማግኘታችን ነው፡፡ ‹የእገሌ ብሔረሰብ ታሪክና ባሕል› እየተባሉ ብቻ የሚወጡ፣ ሲጀምሩ ሌላውን አውግዘው፣ ኮንነውና ጠልተው የሚነሡ ‹መጻሕፍት› አጥሩን በአደገኛ አጥር ከማጠናከር ያለፈ ፋይዳ አይኖራቸውም፡፡ ቁስሉን ማሳየት እንጂ ማሻርም አይፈልጉም፡፡ ምናልባትም የጉዳዩ ባለቤት ነኝ ብሎ ከሚያስበው አካል በቀር የሌላውን ልብ ለመማረክም አይችሉም፡፡ ጎጣዊ ጀግና ከመፍጠር ባለፈ ሀገራዊ ጀግና አያስገኙም፡፡ በላይ ዘለቀን የጎጃም፣ ዐፄ ዮሐንስን የትግሬ፣ ቃቄ ወርድወትን የጉራጌ ብቻ አድርገው ለማስቀረት የሚያልሙ ናቸው፡፡

ኢትዮጵያዊ ጀግና፣ ሀገራዊ ታሪክ፣ ሀገራዊም ማንነት ሊፈጠር የሚችለው እንዲህ የአንዱ አካባቢ ታሪክ የሌላው እንዲሆን አድርጎ በማቅረብና ለታሪኩና ሥነ ቃሉ ብቻ ሳይሆን ለአቀራረቡም ጭምር በመጨነቅ ነው፡፡ ‹ሲያዩት ያላመረ ሲበሉት ያቅራል› ይባል የለ፡፡ የእንዳለ ጌታን መጽሐፍ አንብቡት የምላችሁም ለዚህ ነው፡፡ በሞቴ አንብቡት፡፡  

ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

መግቢያ

ለአዘማሪ ሙያ ተስማሚ የግብር መግለጫ መሆን ያለበት የቱ ነው? አዘማሪ ወይስ አርቲስት? በሚል በአቶ ዓለም ነጻነት ሬድዮ የቀረበው ውይይት ለዚህች ጦማር መነሻ ሆኖኛል። ከቀደሙ አባቶች እንደሰማሁት አዘማሪ ብቻውን የቆመ አይደለም። ከብዙ ነገሮች ጋራ ከቅኔያችን፣ ከዜማችንና ከስሜታችን ጋራ የተያያዘ ነው። አዘማሪ የሚለውን ቃል ከነዚህ ነጥሎ ለማቅረብ መሞከር ያዘማሪን ክብርና ቦታ ዝቅ ያደርገዋል የሚል ስጋት አለኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ወንድሙ መኰንን

የለንደኖቹልማታዊካኅናትወያኔያዊዘጋቢፊልምአቀናበሩብን!

ኢንግላንድ መከረም ፯ቀን ፪፲፻፯ ዓ.ም

መግቢያ

እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሳችሁ። መባል ስላለበት ነው። ያለፈውማ ዓመትአንደኛውን ጥቁር ዓመት ተብሏል። ሲያንሰው ነው። ወያኔ ከመቼው በበለጠ ጥቃቷን በኢትዮጵያ ልጆች ላይ በሁሉም አቅጣጫ ያጧጧፈችበት ዓመት ነበር። ነጻውን መገናኛ ብዙሀን ከጨዋታ ውጪ አድርጋለች። ብዙ ጋዜጠኞች በማሠሯ ወህኔ ቤቱ ጠቧል መሰለኝ፣ አሁን አሁን የያዘችው ዜዴ፣ በቁጥጥሯ ሥር ከሌሉ፣የፋሺን ጋዜጠኞችም ሳይቀሩ ማዘዣ ሳይደርሳቸው፣ በሬዲዮዋና በጋዜጦቿ “ከስሼአቸዋለሁ!” በማለት ፣ ነጭ ሽብር እየነዛችባቸው በርግገው ከአገር እንዲጠፉ ማሳደዷን በሰፊው ተያይዛቸዋለች።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የአይሲል ( Islamic State of Iraq and the Levant – ISIL ) እንቅስቃሴ ከሰማይ ዱብ ያለ አዲስ ክስተት አይደለም። አይሲል ( አንዳንዶቹ ISIS ይሉታል – Islamic State of Iraq and Syria ) በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው የፖለቲካ ውጥንቅጥ ሀቅ ውጤት ነው። ለአነሳሱ፣ ለዕድገቱና ለሂደቱ ብዙ ነባሪ ምክንያቶች አሉት። በርግጥ የአይሲልን እንቅስቃሴ ከሀይማኖትና ከዘይት ሀብት ለይቶ ማየት […]

ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ

                                                       
—-

 እነሆ ነፍስ የሆነውን አርቲስት ልናነሳው ወደድን!! ተወዳጅ፣ ጥበበኛ፣ ባለ ተሰጥኦ ከያኒ!! እውነተኛ የሙዚቃ ቀማሪ! ሱዳን ያፈራችው የምንጊዜም ጌጥ!! ከካይሮ እስከ ዑጋንዳ፣ ከጅቡቲ እስከ ማሊ ምንጊዜም እንደተወደደ ያለ የጥበብ ዋርካ!! ሙሐመድ ወርዲ!!

  “ወርዲ” ማለት ለሱዳኖች ንጉሥ እንደማለት ነው፡፡ እኛም ከአንጋፋ አርቲስቶቻችን ነጥለን አናየውም፡፡ በድሮ ጊዜ ወርዲን በፍቅር ሰምተነዋል፡፡ ዛሬም ወርዲን በመደጋገም እየሰማነው ነው፡፡

*****

ወርዲ ከልቡ ዘፋኝ ነው፡፡ ዘፈኖቹ ከኛ ጋር ከመዛመዳቸው የተነሳ እኛን እኛን ይሸታሉ፡፡ በርካታ ዜማዎቹ እኛ የምንጊዜም ምርጦች አድርገን ለምንወዳቸው ታዋቂ ዘፈኖቻችን መነሻ ለመሆንም በቅተዋል፡፡ ለምሳሌ አንጋፋው ድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠ ያዜመውን “አንቺ ከቶ ግድየለሽም”ን ውሰዱት፡፡

አንቺ ከቶ ግድ የለሽም

ስለፍቅር አይገባሽም

ሁሉን ነገር እረስተሽው

ችላ ብለሽ ስለተውሽው

ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ፡፡

አዎን! ዛሬም ድረስ የዚህ ዜማ ተወዳጅነት አልቀነሰም፡፡ ለዚህ ዜማ መሰረቱ የሙሐመድ ወርዲ “አነ ዐርፈክ ያ ፉአዲ” ነው፡፡ ሙሐመድ ወርዲ ዘፈኑን ሲያዜመው እንዲህ ነበር ያለው፡፡

“አነ ዐርፈክ ያ ፉአዲ

ጠል ዐዛበክ ዋ ሱሃዲ

ዋ ሽጃያ አነ ዐዛቢ”

ታዲያ ሙሐመድ ወርዲ የተጫወተውን ዜማ ጋሽ ጥላሁን ወደ አማርኛ የመለሰው እንዲሁ በጋጠወጥነት አይምሰላችሁ፡፡ በነገሩ ውስጥ  የወርዲ ሙሉ ቡራኬ አለበት፡፡ በቀዳማዊ ኃይለሥላሤ ዘመን የካርቱም መንገድ ለኛ አርቲስቶች የውሃ መንገድ ነበረ፡፡ ለሱዳኖችም ከዋዲ ሃልፋ ይልቅ ሸገር ነበር የምትቀርባቸው፡፡ እናም በዚህ ምልልስ መሀል የኛዎቹ አንጋፋዎች (ጥላሁን ገሠሠ፣ ምኒልክ ወስናቸው፣ አለማየሁ እሸቴ፣ ዓሊ ሸቦ፣ ዓሊ ቢራ ወዘተ..) እና የሱዳኖቹ አንጋፋ አርቲስቶች (አሕመድ አል-ሙስጠፋ፣ ሰይድ ኸሊፋ፣ ሙሐመድ ወርዲ፣ አብዱልከሪም አል-ካብሊ፣ አብዱል ዓዚዝ አል-ሙባረክ ወዘተ…) የአንድ ቤተሰብ ልጆች ሆነው ነበር፡፡ ሱዳኖቹ ያዜሙትን የኛዎቹ ወደ አማርኛ፣ ኦሮምኛና ሶማሊኛ እየመለሱ ይጫወቱታል፡፡ የኛንም ዘፈኖች ሱዳኖች በቋንቋቸው እየተረጎሙ ይዘፍኑታል፡፡ አንዳንዴ ዕድል ሲገጥማቸው ሁለቱም ዘፋኞች አንዱን ዜማ በአንድ መድረክ ላይ በየቋንቋቸው ይጫወቱታል፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት ነው እንግዲህ የሙሐመድ ወርዲ “አነ ዐርፈክ ያ ፉአዲ” ወደ አማርኛ የተመለሰው፡፡

አዎን!! እነ ጋሽ ጥላሁን እንደ አሁኖቹ ዘፋኞች (አንዳንዶቹን ማለቴ ነው) የሱዳንና የፈረንጅ ዜማን ወደ አማርኛ እየገለበጡ “የራሴ ድርሰት ነው”  ብለው ሊያሞኙን አይከጅሉም፡፡ ዋናው አርቲስት ባለበት ጭምር እየዘፈኑ ያሳዩትና “እንዴት ነው! አበላሽቼብህ ይሆን?” በማለት ምክርና እገዛ ይጠይቁታል፡፡ ሱዳናዊው አርቲስትም በሰማው ነገር ላይ የራሱን አስተያየት ይሰጣል፡፡ የኛዎቹም ከሱዳናዊያኑ አርቲስቶች የሚሰጣቸውን አስተያየት ተንተርሰው እጅግ የተሻለ ስራ ይሰሩና ህዝቡን እንካችሁ ይሉታል፡፡ ለዚያም ነበር ስራው የሚዋጣላቸውና ዘመን ተሻጋሪ የሚሆንላቸው፡፡

በዚህ ስሌት ወደኛ ቋንቋዎች ከተቀየሩት ተወዳጅ የሱዳን ዜማዎች መካከል የጥላሁን ገሠሠ “እዩዋት ስትናፍቀኝ” (ሰይድ ኸሊፋና ኢብራሂም አውድ በጋራ ከዘፈኑት ዘፈን የተወሰደ)፣ የአሰፋ አባተ “ሸግዬ ሸጊቱ” (ከአሕመድ አል-ሙስጠፋ “ሐቢቢ በኪቱ” የተወሰደ)፣ የምንሊክ ወስናቸው “ስኳር” (ከአብዱልከሪም አል-ካብሊ “ሱከር” የተወሰደ) የዓሊ ቢራ “ኦፊ ረፋ ቡልታ” (ከሙሐመድ ወርዲ “ያ ኑረል-ዐይን” የተወሰደ) ይጠቀሳሉ፡፡

                                                                          *****

    በርካታ የሀገራችን የሙዚቃ ወዳጆች ከመሐመድ ወርዲ ዜማዎች መካከል ለ“ገመር ቦባ” እና ለ“ቲስዐተ ዐሸር ሰና” (ብዙዎች የሚያውቁት  “ሰበርታ” በሚለው ስም ነው) ልዩ ፍቅር አላቸው፡፡ ሆኖም ሱዳኖች በአንደኛ ደረጃ የሚያሰልፏቸው ሌሎች በርካታ የወርዲ ዜማዎች አሉ፡፡ በተለይም “ሱድፋ”፣ “ቃሲ ቀልበክ”፣ “አልሀወል አወል”፣ “አነ ማ በንሳክ”፣  “አንናስ አል-ጊያፋ”፣ “ሐረምተ አድ-ዱንያ”፣ “ያ ኑረል ዐይን”፣ “ሸተል ዘማ”፣ “አል-ሙርሳል” የመሳሰሉት ከምርጥ የወርዲ ዜማዎች መካከል ይሰለፋሉ፡፡ እኔ በግሌ በጣም ከምወዳቸው የሱዳን ዜማዎች መካከልም አንዱ የሙሐመድ ወርዲ “አዚብኒ ወተፈነን” ነው፡፡

ዐዚብኒ ወዚድ ዐዘባ ዩምኪን ገልቢ ይግሳዚይክ

ዜይመን ሳኒ ገልበክ ዩምኪን ገልቢ ይግሳዚክ፡፡

አዚብኒ ወተፈነን ፊ አልዋን ዐዛቢ

ማ ቲምሳሕ ዲሙዒ ማ ቲርሐም ሸባቢ፡፡
ኸሊኒ ፊሹጁኒ ዩምኪን ገልቢ ይክሳዚይክ

ዜይ መንሳኒ ገልበክ ዩምኪን ገልቢ ይክሳዚይክ፡፡

ወርዲ በዚህ ዘፈን ለወዳጁ “ልብሽ ጨክኖብኝ ፍቅርሽ አቃጥሎ እየጨረሰኝ ነው፤ መጥተሸ እምባዬን የማታብሺልኝ ልበ-ደረቅ ነሽ” የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ነው የፈለገው፡፡ ወርዲ ይህንን ዜማ የዛሬ 20 ዓመት ገደማ በአዲስ አበባ ስታዲየም እጅግ ባማረ ሁኔታ የተጫወተው ሲሆን የሀገራችን አድናቂዎችም በጋለ ስሜት ተቀብለውታል ( ቪዲዮውን በሚከተለው ሊንክ ላይ ተመልከቱት፡፡  https://www.youtube.com/watch?v=WkegFEEwjjM&feature=related

                                                                          *****

ታዲያ የወርዲ ፍቅረኛ በ“አዚብኒ-ወተፈነን” ውስጥ እንደተገለጸው በጭካኔዋ አልዘለቀችም፡፡ ወርዲ በጉንጮቹ ላይ የሚያፈሰው እምባ አሳዝኖአት ከፍቅር በረከቱ ልታቀምሰው መጥታለታለች፡፡ ወርዲም ፍቅረኛውን ያገኘበትን ቀን “የቀኖች ሁሉ ረጢብ፣ እጅግ በጣም ገዳም፣ የምኞቴን ያሳካሁበት ቀን መጥቶልኛል” በማለት ገልጾታል፡፡

“ሱድፋ” የሚለውን የሙሐመድ ወርዲን ዘፈን እናውቀው የለ?.. በዚያ ዘፈን ውስጥ ወርዲ ለወዳጁ ያለውን ፍቅር ብቻ ሳይሆን ከናፈቁት ወዳጅ ጋር መገናኘቱ የሚሰጠውን ደስታ በተዋቡ ቃላት ገልጾታል፡፡ እኔ በበኩሌ እጅግ በጣም የምወደው የወርዲ ዘፈን ይኸው ሱድፋ ነው፡፡ እነሆ የሱድፋን ሙሉ ግጥም ተጋበዙልኝ፡

ሱድፋ… ሱድፋ

ሱድፈ ወ አጅመል ሱድፈነ የውም ላቄታ

አስዓድ የውም የውሚል ሐዬታ

ኑረ ዐይነያ አያም ሓቤታ

ይህ አዝማቹ ነው እንግዲህ፡፡ “ሱድፋ” ማለት አስገራሚ ዕድል ማለት ነው (በእንግሊዝኛ fortunate የሚለው ቃል ይቀርበዋል)፡፡ ተከታዮቹ ግጥሞች የሚከተሉት ናቸው፡፡

አን-ነዘራት በሪዓ ገመም ዘውፍጀል ኸጀል

አልበሰማት ተበዊ ዘይ ኑረል ዐመል

ወጅሂክ ቤን መዛህሪክ ዘይ በድሪ-ክ-ከመል

ወሽሻመክ ኺዴድክ ዘይ ጠዕመል ኹበል

ተስኪር ገልቢ

ወተሽዒል ሑቢ

ኢሽሀክ ረብቢ

አነ በህ ዋ

—–

ማ ቃዲር አጉል ሊክ አን ሑብቢል ከቢር

ወስፉ ዓለይያ ቃሲ መዓዪሽ ፊ-ድ-ደሚር

ቀድረል ከውን ተኩልሉሁ አክበር ቤ ከቲር

ማሊክኒ ሙሐዪይርኒ ሹፍከል ቢል ኣሲር

አስአሊ ቀልቢ

ኢኪኒ ዪቅደር

ኢሽራሕ ሑቢ

አነ ሙሕታር

——

ሱድፈ ዑዩኑ ሻፈክ ሌይሊ ባቂ ይነዊር

ያ አይያም ረቢዒ ዑምሪ መዓኪ አዝሐር

ፊሃ አጥ-ጤይር ይገኒ ሚን አል-ሓኒ ዪዝከር

ቀልቢ ፈራሸ ሐውሊ ወኢንቲ ሸባቢከ አኽደር

ያ መበሒብቢ

ባዕቡድ ሑብቢክ

አለሻን ሑብቢክ

ሩሒ ፈዳክ

*****

ለመሆኑ መሐመድ ወርዲ ማን ነው?

  ሙሉ ስሙ ሙሐመድ ዑስማን ሳሊሕ ወርዲ ነው፡፡ እርሱ ግን “ሙሐመድ ወርዲ” ወይንም በአጭሩ በቤተሰቡ ስም “ወርዲ” ተብሎ ነው የሚታወቀው፡፡ የተወለደው እ.ኤ.አ. በ1932 “ዋዲ ሀልፋ” በተሰኘው ሰሜናዊው የሱዳን ክፍለ ሀገር፣ “ሱወርዳ” በተባለች ትንሽዬ የገጠር መንደር ውስጥ ነው፡፡ እናቱ የኑቢያ ተወላጅ ስትሆን አባቱ ዐረብ ነው፡፡

ወርዲ የሙት ልጅ ነው፡፡ ሁለቱንም ወላጆቹን በልጅነቱ ነው ያጣው፡፡ በመሆኑም በዘመዶቹ ጥበቃ ስር ሆኖ ነው ያደገው፡፡ ትምህርቱን በዋዲ ሀልፋ እና በካርቱም ተከታትሏል፡፡ የተወለደበትን ሀገር እስከ 1956 በመምህርነት ሙያ ካገለገለ በኋላ በወቅቱ ይሞካክራቸው የነበሩት ዘፈኖች በኦምዱርማን ሬድዮ ጣቢያ ተቀርጸው በመተላለፋቸው በህዝብ ልብ ውስጥ ገባ፡፡ ያገኘው የሞራል ድጋፍ ማነሳሻ ስለሆነው መምህርነቱን ትቶ የአርቲስትነቱን ጎራ ተቀላቀለ፡፡ ከዚያም ሱዳኖች ከሚያፈቅሯቸው ቁንጮ ዘፋኞቻቸው አንዱ ለመሆን በቃ፡፡

 

    ወርዲ በህይወቱ የተረጋጋ ኑሮ አልኖረም፡፡ በሱዳን የተለዋወጡት መንግሥታት በተቃዋሚነት እየፈረጁት አንገላተውታል፡፡ በመሆኑም ለሀያ ዓመታት ያህል በካይሮና በለንደን ነው የኖረው፡፡ በ2002 ግን ወደ ሀገሩ በክብር ተመልሷል፡፡ ወርዲ በሙዚቃው ዕድገት ላደረገው አስተዋጽኦ ከካርቱም ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሸልሟል፡፡ ከልዩ ልዩ የአውሮጳ፣ አፍሪቃና እስያ ሀገራትም ሽልማቶችን ተቀብሏል፡፡

 መሐመድ ወርዲ በመጨረሻዎቹ ዓመታት በደረሰበት የጤና መታወክ ሁለት ኩላሊቶቹ ከጥቅም ውጪ ሆነው ነበር፡፡ ይኸው የኩላሊት ህመም ፋታ ነስቶት በየካቲት ወር 2012 ከዚህች ዓለም አሰናብቶታል፡፡

*****

ከመግቢያዬ እንደገለጽኩት የሀገራችን የሙዚቃ አፍቃሪዎች በጣም የሚወዱት የመሐመድ ወርዲ ዘፈን “ሰበርታ” ነው፡፡ እኔም “ሱድፋ”ን ከሁሉም እንደማስበልጥ ገልጫለሁ፡፡ በሱዳኖች ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆነው የመሐመድ ወርዲ ዜማ ግን “ገመር ቦባ” ነው፡፡ ሱዳኖች እ.ኤ.አ. በ2000 ባደረጉት ምርጫ “አል-ገመር ቦባ” የተሰኘው ዘፈን የክፍለ ዘመኑ ምርጥ “ነጠላ ዜማ” ተብሎ ተመርጧል፡፡እኔም ገመር ቦባን በድምጽ (ኦድዮ) ልጋብዛችሁና ላብቃ፡፡

ቦባ ዐሌክ ተጊል… ቦባ ዐሌክ ተጊል

አል-ገመር ቦባ ዐሌይክ ተጊል፡፡

አስ-ሰጊሩን አል-ማ-ከቢር

አር-ሪጌበት-ጊዛዛት አሲር

አስኑን በርራጊን የሺል

አል-ዑዩን መሥለል ፈናጂል

ቢንተ-ሱዳን አሲል

ያ ገመር ቦባ ዐሌክ ተጊል፡፡

(ገመር ቦባን በዚህ ሊንክ ላይ ይስሙት https://archive.org/details/MohammedWardi-AlQamarBoeba )

——

አፈንዲ ሙተቂ

መጀመሪያ ታሕሳስ 6/2006 ተጻፈ፡፡

እንደገና ተሻሽሎ መስከረም 9/2007 ተጻፈ፡፡

The writer, Afendi Muteki, is a researcher and author of the ethnography and history of the peoples of East Ethiopia.

 You may like his facebook page and stay in touch with his articles and analysis: Just click this link to go to his facebook page.

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች