በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስትያናት ላይ እተከሰተ ያለው ጉዳት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የቤተ ክርስቲያኗ አመራሮች አስታወቁ፡፡
ጥቅምት ፲፪(አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅዱስ ላሊበላ ገዳም የሰው ሃይል አስተዳደር የሆኑት ቀኝ ጌታ በላይ አናውጥ ከልዩ ልዩ አካባቢ ለመጡ ጋዜጠኞችና ጎብኝዎች እንደ ገለጹት ገዳሙ በዝናብና ጸሃይ እየደረሰበት ያለው ጉዳት ቅርሶቹን በአስከፊ ደረጃ እያፈረሳቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ቅርሶቹን ከጸሐይና ዝናብ ይከላከላል ተብሎ ከለጋሽ ሃገሮች በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የተሰራው መጠለያም ምሰሶዎች ብረት የተተከሉት በቤተ …