ጥቅምት ፲፪(አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅዱስ ላሊበላ ገዳም የሰው ሃይል አስተዳደር የሆኑት ቀኝ ጌታ በላይ አናውጥ ከልዩ ልዩ አካባቢ ለመጡ ጋዜጠኞችና ጎብኝዎች እንደ ገለጹት ገዳሙ በዝናብና ጸሃይ እየደረሰበት ያለው ጉዳት ቅርሶቹን በአስከፊ ደረጃ እያፈረሳቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ቅርሶቹን ከጸሐይና ዝናብ ይከላከላል ተብሎ ከለጋሽ ሃገሮች በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የተሰራው መጠለያም ምሰሶዎች ብረት የተተከሉት በቤተ …

ጥቅምት ፲፪(አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግሪሳ ወፍ በሰብል ላይ ጉዳት ሳያደርስ ለመከላከልና ብሎም ለማጥፋት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የፌዴራል ግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ዛሬ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ የሰጡት በፌዴራል ግብርና ሚኒስቴር ከፍተኛ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ከበደ ላቀው እንዳሉት በኦሮሚያ ክልል ዝዋይና መቄ አካባቢዎች 8 ሚሊዮን ሚጠጋ የግሪሳ ወፍ ተከስቷል፡፡ በአማራ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ክትባቶቹን ለማምረትና ለማሰራጨት የሚያስፈልገዉን በቢሊዮን የሚቆጠር ወጪ ያስፈልጋል።ወጪዉን የሚሽፍነዉ ወገን እስካሁን በግልፅ አልታወቀም።ጥረቱ በብዙዎች እምነት የዘገየ ያም ሆኖ ገዳዩን በሽታ ድል ለማድረግ ተስፋ ሰጪ ነዉ።ተስፋዉ ግን የዓለም ጤና ድርጅት ባለሥልጣን እንደሚሉት አሁንም በብዙ ጥያቄዎች የተከበበ ነዉ።

የጎርጎረሳዉያኑ መስከረም ወር በገባ በሶስተኛዉ ቅዳሜ በጀርመን የባቫርያ ግዛት መዲና በሆነችዉ ሙኒክ ከተማ ላይ የሚጀምረዉ ባህላዊዉ የቢራ ድግስ፤ ዘንድሮ ከተለያዩ የዓለም ሀገራትና አካባቢዎች የተሰባሰቡ 6, 3 ሚሊዮን እንግዶችን አስተናግዶ የዛሬ አስር ቀን ግድም ተጠናቅዋል።

በተደጋጋሚና ተራበራ ወጣት ሴቶች የሞቀ ቤታቸዉ እየጣሉ ወደሶርያና ኢራቅ በጦር ፍልሚያዉና እስላማዊ መንግሥት እዚያ አብሮ በማቋቋሙ ሂደት ላይ ራሳቸዉ እንደሚሉት ለመሳተፍ ከአዉሮጳና ከአሜሪካ እየተነሱ መንጎድ ከጀመሩ ጊዜዉ ትንሽ ሰንበት ብሏል።

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት የመንግስት ሃብትና ንብረትን ላለፉት ሶስት አመታት የህዝብን ሃብት በህገወጥ መንገድ በማባከን ሪኮርድ የሰበሩ መንግስታዊ ተቋማት እርምጃ እንዳልተወሰደባቸው ለተወካዮች ምክር ቤት ያዘጋጀው ሪፖርት ያመለክታል። የተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ አባዱላ ገመዳ ግምገማው ለኢትዮጵያ ህዝብ መቅረብ የለበትም ብለዋል። ባለፉት 3 አመታት ሂሳባቸውን በወቅቱ ያልዘጉ መ/ቤቶች …

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአካባቢው ምንጮች እንደገለጹት በአሚባራ በአፋርና በኢሳ መካከል የተነሳውን ግጭት  ተከትሎ የፌደራል ፖሊስ አባላት በወሰዱት እርምጃ አንድ ሰው ገድለው ሌላ የአፋር ተወላጅን ደግሞ አቁስለዋል። በአካባቢው ውጥረቱ አሁንም መቀጠሉን ገልጸዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ከትናንት ጀምሮ ገዋኔና ቡድመዳ ወረዳዎች በጎርፍ መጥለቅለቃቸው ታውቋል። የአካባቢው ነዋሪዎች መንግስት በቂ ድጋፍ እያደረገ አይደለም …

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአቶ ሬድዋን ሁሴን የሚመራው የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት አሰልጥኖ በፌዴራል የመንግስት ተቋማት በህዝብ ግንኙነት ኃላፊነት ለመደባቸው ካድሬዎች የሁለት ቀናት የማህበራዊ ድረገጾች አጠቃቀም ስልጠና በመስጠት በተለይ በግንቦት ወር ከሚካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ እንዲሳካ የበኩላቸውን አዎንታዊ ሚና እንዲጫወቱ አደራ ተጥሎባቸዋል፡፡ የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን እንደገለጸው የኮምኒኬሽን ጽ/ቤቱ በሚኒስትሮች ምክርቤት …

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ በቅርቡ በአዳማ ከተማ   ለጋዜጠኞች ባዘጋጀው ሴሚናር ከኢትዮጵያ ስፖርት ኮሚሽን ተወክለው በስብሰባው በመገኘት ንግግር ያደረጉት አቶ ናስር ለገሰ ባቀረቡት የኢትዮጵያ ሰፖርት ታሪክ ንግግራቸው የቀደሙት መንግስታትን ስራ በማጣጣል የገዢውን መንግስት ስራ በማግዘፍ ባቀረቡት ጽሁፍ ከጋዜጠኞች ከፍተኛ ተቃውሞ ደርሶባቸዋል፡፡ የገዢው መንግስት አሁን የሚያንቀሳቅሰው ከፍተኛ በጀት ስፖርቱ እንዲጎለብት ለማድረግ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የአውሮፓ ፓርላማ ጥቅምት 22 ቀን 200 7 ሥልጣን የሚረከቡትን ፣ አዲሱ የአውሮፓ ሕብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ዣን ክሎድ ዩንከር ያቀረቧቸውን የኮሚሽን ሹማማንት የሥልጣን ቦታ በዛሬው ዕለት በድምጽ ማጽደቁ ተነገረ።

የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊና የሚሊዮኖች ግብረ ኃይል ሰብሳቢ የነበሩት፣ አቶ ሃብታሙ አያሌው በጸና መታመማቸዉንና ዛሬ በሆስፒታል መዋላቸዉን ለማረጋገጥ ችለናል። የማእከላዊ እሥር ቤት ብዙ ቶርቸር የሚደረግበት እስር ቤት እንደሆነ ይታወቃል። አቶ ሃብታሙ አያሌው ከብሎገር አብርሃ ደሳታ፣ ዳን ኤል ሺበሺና የዚዋስ አሰፋ ጋር ሐመሌ 1 ቀን የታሰሩ ሲሆን፣ ፖሊስ «መረጃ ለማሰባሰብ ጊዜ ይሰጠኝ» በሚል አራት […]

ባለፈው እሁድ ፣ አንድ ስባሪ ኮከብ ወደ ማርስ ከዚያ በፊት ታይቶ ባልታወቀ ሁኔታ መጠጋቱ ፤ ለምን የሥነ ፈለክ ጠበብትን ትኩረት ሳበ? ስባሪ ከዋክብት ከየት ነው መነሻቸው? 9ኛው ፕላኔት አይደለም ተብሎ እ ጎ አ በ 2006 ከ ዝርዝር እንዲወጣ የተደረገው

በቃለ ዐዋዲው ደንብ መሠረት፣ በካህናት እና ምእመናን አንድነት በየደረጃው የተዋቀረውና የቤተ ክርስቲያናችንን አስተዳደር ለመምራት ከፍተኛ የሥራ አስፈጻሚነት ሥልጣን የተሰጠው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ፣ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ደረጃ ያካሔደውን ፴፫ኛ ሀገር አቀፍ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ጥቅምት ፰ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. ቀትር ላይ የአቋም መግለጫ በማውጣትና የውሳኔ ሐሳብ በማቅረብ አጠናቅቋል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን መዋቅር …

በአሳሳቢው የኢቦላ ወረሽኝ ላይ ያተኮሩ ትምሕርታዊ ጽሁፎችን በአማርኛ አዘጋጅተው በተለያዩ የኢትዮጵያውያን ድረ ገጾችና የሕክምና መወያያ መድረኮች አማካኝነት በማሰራጨት ለንባብ ያበቁ ሃኪም ናቸው።

ዶ/ር አሸናፊ ዋቅቶላ ይባላሉ። በኢቦላና ተዛማች ርዕሶቹ ዙሪያ ትኩረት በማድረግ የሚቀናበረው የሃኪምዎን ይጠይቁ ተከታታይ ፕሮግራም እንግዳ አደርገናቸዋል።

የቃለ ምልልሱን የመጀመሪያ ክፍል ከዚህ ያድምጡ፤

 

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌዴራል ፖሊስ በ2006 በጀት ዓመት በ36 መዝገቦች በኦነግ፣ በግንቦት ሰባት፣ በኦብነግ፣ በጋህነን፣ በቤህነን እንዲሁም በአልሻባብ ተጠርጥረው የተያዙ ሰዎችን መክሰሱን በመጥቀስ የፌደራል ፖሊስ ሽብርን የመከላከል አቅሙ እንዳደገ በመግለጽ ራሱን አሞካሽቷል፡፡ ፌዴራል ፖሊስ ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ ባለፈው ዓመት 36 የሽብር መዝገቦች መካከል በ27 ቱ ላይ ምርመራ ተጠናቆ …

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአካባቢው ወኪል እንደገለጸው በሸኮ መዠንገር ተወካዮችና በከፋ፣ ሸካ፣ ጋምቤላና ቤንች የዞን አመራሮች መካከል በሃይማኖት አባቶች አማካኝነት በቴፒ ውይይት እያደረጉ ነው። የአካባቢው ባለስልጣናትን በማናገር እንደዘገበው የንግግሩ ዋና አላማ ሸሽተው በየጫካው ውስጥ የሚገኙ የመዠንገርና የሸኮ ተወላጆች አሳምኖ ወደ ቀያቸው ለመመለስ ነው። ይሁን እንጅ ለድርድር የሄዱ አንዳንድ የመዠንገር ተወላጆች …

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘጠኝ የኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጥቅምት 11/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት የትብብር ስምምነት መፈራረማቸውን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። ፓርቲዎቹ ነጻ አሳታፊና ታአማኒ ምርጫ እንዲካሄድ በትብብር ለመስራት፣ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋትና የዜጎችን ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ በጋራ ለመታገል መስማማታቸውን ትብብር ሰነዱ ላይ አስፍረዋል። ትብብሩን እንዲመሩ  ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ከሰማያዊ ፓርቲ …

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወኪላችን እንደሚለው በከተማው የታየውን የስኳር እጥረት ተከትሎ፣ አንድ ኪሎ ስኳር እስከ 30 ብር በመሸጥ ላይ ነው። በተመሳሳይ መልኩ የሚታየው የዘይት እጥረት  የነዋሪውን ኑሮ አስከፊ እንዳደረገው ገልጿል። የስኳር እጥረቱ በደቡብ፣ በኦሮምያና በአማራ አካባቢዎችም በስፋት እየታየ ነው። መንግስት የስኳር ፋብሪካዎች ወደ ምርት ሲገቡ ስኳር ወደ ውጭ መላክ እንችላለን በማለት …

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በክልሉ በሚገኙ የሰሜን ጎንደር ጠረፋማ ወረዳዎች፣ በአዊ፣ በዋግ ህምራ እና በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞኖች የሚገኙ መምህራን ወደ አጎራባች ክልሎች  በመፍለሳቸው  በትምህርቱ ጥራት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እያደረሰ መሆኑን  ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡ ክፍተቱን ለመሸፈን አስረኛ ክፍል ያጠናቀቁ እና በልዩ ልዩ ሙያ የተመረቁ ተማሪዎች እንዲቀጥሩ ለአራቱ ዞኖች ደብዳቤ  ስለደረሳቸው ይህንኑም እየተፈጸሙ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ቀደም ባሉ ዓመታት የበለፀጉት ሃገራት በሽታዎች ተብለዉ ከሚፈረጁት ካንሰር አንዱ ነበር። የዓለም የጤና ድርጅት መረጃ እንደሚያመለክተዉ ግን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን የኗኗር ሁኔታ መለወጥን ተከትሎ በአዳጊና ደሀ ሃገራትም መስፋፋቱ ይታያል።

ቃለ ጉባኤ፡- የበጀት ዓመቱ የሥራ አፈጻጸም ዘገባዎች ትኩረት ከሰጧቸው ዝርዝር ነጥቦች ውስጥ ስለ ማኅበረ ቅዱሳን የሥራ እንቅስቃሴ የሰፈረው የጉባኤተኛው ቃል (ገጽ 12) የአቋም መግለጫና የውሳኔ ሐሳብ፡- የማኅበራትን ታላቅ አስተዋፅኦ ስለማወቅና ችግሮቻቸውን በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ስለ መፍታት የተያዘው የጋራ አቋምና የቀረበው የውሳኔ ሐሳብ (ገጽ 20)

ጥቅምት ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሰሞኑን አሻሽሎ ያዘጋጀውና የኢህአዴግ ምክር ቤት አባላት እንዲወያዩበት የተዘጋጀው  ሰነድ ለኢሳት የደረሰ ሲሆን፣ ሰነዱ የመንግስት የመረጃና የደህንነት መስሪያ ቤት ወይም ኢንሳ በኢሳት በአሜሪካ እና በጀርመን ድምጾች ላይ እርምጃ እንዲወስድ ከመማጸን ጀምሮ መንግስት በሴቶች፣ በወጣቶችና በምሁራን ስም የሃይማኖት ማህበራትን እንዲቋቋሙ እገዛ እንዲደርግ፣ በሰርተፍኬትና በዲግሪ ደረጃ የሃይማኖት …

ጥቅምት ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመንግስት የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ሬድዋን ሁሴን በተመራውና ሁሉም የክልል መንግስታት የኮሚኒኬሽንና የመገናኛ ብዙሃኖች የተሳተፉበት የኢህአዴግ የምርጫ ዘመቻ ፕሮፓጋንዳ ዝግጅት ባለፈው ቅዳሜ ሲጠናቀቅ ሁሉም የክልል ሚዲያዎች ቀጣዩን ምርጫ ሊያሳምን የሚችል አቀራረብ ፣ ዜና እና ፕሮግራም እንዲየቀርቡ እንዲሁም በምርጫው የኢህአዴግ አሸናፊት ቅኝት ውስጥ ስራዎችን እንዲሰሩ ታዘዋል። ብአዴን በምርጫው ዙሪያ ለከፍተኛ አመራሩ …

ጥቅምት ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምእራብ አርማጭሆ የመከላከያ ሰራዊትን የሚከዱ ወታደሮችን ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ፣ በአካባቢው የሚገኙት ወታደሮች በህዝቡ ላይ የአጸፋ እርምጃ እየወሰዱ ነው። የምእራብ አርማጭሆ ወረዳ ነዋሪዎች እሁድ እለት የተቃውሞ ሰልፍ ያደረጉ ሲሆን፣ ለአሁኑ ሰልፍ ምክንያት የሆነው ጥቅምት 7 አንድ ወታደር መጥፋቱን ተከትሎ የአጎቱ ልጅ የሆነ የጤና ባለሙያ ከፍተኛ ድብደባ ደርሶበት እንዲታሰር ከተደረገ …

ጥቅምት ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት በኤርትራ ድንበር አካባቢ በጥበቃ ላይ የሚገኙ ወታደሮች በመረጃ ስህተት ለ33 ዲቃዎች በባዶ ሜዳ ላይ ሲተኩሱ የዋሉ ሲሆን፣ ለጦሩ የተሳሳተ መረጃ በመስጠት መከላከያን አወናብደዋል የተባሉ 5 ወታደሮች ተይዘው እንዲታሰሩ ተደርጓል። ከግንቦት ሰባት ተኩስ ተከፈተ ተብሎ ለማዕከላዊ የጦር ሃይል ሪፖርት የተደረገ ሲሆን ይህን ተከትሎ ከፍተኛ መደናገጥ ተገብቶ …

ጥቅምት ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ በረከት ስምኦን ” የኢሳት ዘጋቢዎችን መቆጣጠር አልተቻለም፣ በውስጣችን ያሉ ሃይሎች ጣሉን” ያሉ ሲሆን፣ ከሚኒስትሮች በስተቀር የደህንነት ሃይሎችም ሆኑ ጋዜጠኞች በፖለቲካ ስብሰባ ላይ ሞባይል ይዘው እንዳይገቡ እንደከለከሉ ትእዛዝ አስተላልፈዋል። አቶ በረከት ከዚህ ቀደም እርሳቸውንና ድርጅታቸውን የተመለከቱ መረጃዎች በኢሳት ተደጋግሞ መውጣት እንዳበሳጫው የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። የኢህአዴግን ምክር ቤት ስብሰባዎች …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ በዓባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው ባለው በትልቁ የህዳሴ ግድብ ሰበብ የተፈጠረውን ልዩነት ለማጥበብ የኢትዮጵያ ፣የግብፅ እና የሱዳን ተወካዮች እና ባለሙያዎች ባለፈው ሐሙስ እና ዓርብ ካይሮ ውስጥ የሶስትዮሽ ውይይት አካሄዱ።

አክራሪው እስላማዊ ታጣቂ ቡድን ቦኮሃራም ያገታቸው ከ200 የሚበልጡ ልጃገረድ ተማሪዎችን ይፈታ ይሆን?የናይጄሪያ መንግሥትና ቦኮሃራም የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማታቸው ከተሰማ ካለፈው ዓርብ አንስቶ ትልቅ ተስፋ ተጥሎ ነበር። ይሁንና በሳምንቱ መጨረሻ በመካሄድ ላይ ያሉት ጥቃቶች ተስፋውን የሚያመናምኑ ናቸው።

ኢቦላ-ባለፉት ሰባት ወራት አራት ሺሕ ስድስት መቶ ያሕል ሰዎች ገድሏል።ከአስር ሺሕ በላይ ለክፏል።የሰወስቱን የምዕራብ አፍሪቃ ሐገራት ምጣኔ ሐብት አሽመድምዶታል።ዩናይትድ ስቴትስ እና ስፓኝም ቢያንስ አራት ዜጎቻቸዉ ተለክፈዋል።ዛሬ ሁሉም ዓለም ከISIS ቀጥሎ የመቅሰፍቱን ታላቅነት ያወራል።መቅሰፍቱን ለማስወገድ ግን አሁንም ሩቅ ነዉ።