የህዳሴ ግድብ የሶስትዮሹ ድርድር ውጤት

ኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ በዓባይ ወንዝ ላይ እየገነባችው ባለው በትልቁ የህዳሴ ግድብ ሰበብ የተፈጠረውን ልዩነት ለማጥበብ የኢትዮጵያ ፣የግብፅ እና የሱዳን ተወካዮች እና ባለሙያዎች ባለፈው ሐሙስ እና ዓርብ ካይሮ ውስጥ የሶስትዮሽ ውይይት አካሄዱ።