ዘ ሄግ ፣ ኔዘርላንድስ የሚገኘው ዓለም አቀፍ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት የጦር ባላባት ጀርሜን ካታንጋን እአአ የካቲት 24፣ በ2003 ዓም በአንድ መንደር 200 ሰዎች አንድም በስለት ተጨፍጭፈው ወይም በጥይት

በሳህል አካባቢ የተከሰተው ድርቅ፣ የሰብል መበላሸት፣ የዋጋ መወደድ፣ በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች የረሀብ አደጋ አሰጋቸው። በተመድ የምግብ ይዞታ ተመልካች መስሪያ ቤት ያወጣው ዘገባ እንደሚያሳየው፣ በሞሪታንያ ብቻ ከየአምስቱ ነዋሪዎች መካከል አንዱ በምግብ እጥረት ተጎድቶዋል።

ስለ ማኅበራት የሰጡትን አስተያየት መልሰው እንዲያጤኑት ተጠየቀ ‹‹ማኅበራት በትኩረት ሊመሩና ጉዟቸውም እየተፈተሸ ሊስተካከል ይገባል›› መንግሥት (አዲስ አድማስ፤ ቅጽ ፲፫ ቁጥር ፯፻፴፰፤ የካቲት ፳፱ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ‹‹ከዩኒቨርስቲ ተመርቀው ቤተ ክርስቲያንን እንምራ እያሉ ነው፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ ትውፊትና ሥርዓት አላት፤ እንዲህ ማለት አይችሉም›› በማለት የሰጡትን አስተያየት መልሰው …

By Addis Admass Newspaper , Written by Administrator

Image

ኪሳራው በጊዜ ሲሰላ፣ የአገሪቱን የስልጣኔ ጭላንጭል ያዳፈነ፣ የ30 ዓመት የኋሊት ጉዞ ነው።
30 ዓመት ቀላል አይደለም፤ እነ ደቡብ ኮሪያ ከድህነት ወደ ብልፅግና የተሸጋገሩበት ጊዜ ነው።
“የአብዮተኛው ትውልድ”ን ኪሳራዎችን ለመደበቅ ተብሎ ብዙ ታሪክ ተድበስብሷል
ትምህርት የተስፋፋው፣ የሴት ተማሪዎች ቁጥር ያደገው ከአብዮቱ በፊት ነው ወይስ በኋላ?
የኤሌክትሪክ፣ የስልክ፣ የመንገድና የአየር ትራንስፖርት በፍጥነት የተሻሻለውስ መቼ ነው?
በእህል ምርት፣ በኢንዱስትሪ፣ በኤክስፖርት መስኮች የብልፅግና ምልክት የታየውና የጠፋውስ?
የሙያ ፍቅር ያበበው፤ ስነፅሁፍ፣ ትያትርና ሙዚቃ ያደገው፤ ስፖርት የተሻሻለው መቼ ይሆን?

በ1950 ዓ.ም በአዲስ አበባ፣ ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የመጡ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ላይ የዳሰሳ ጥናት ያካሄዱት ዊሊያም ሻክ፤ በአገሪቱ እያቆጠቆጠ ከመጣው የትምህርትና የስልጣኔ ጅምር ጋር መልካም የአስተሳሰብ ለውጥ እየመጣ እንደነበር ይገልፃሉ። አንደኛ፤ የዘመኑ ወጣቶች እንደ ጥንቱ የመንግስት ስልጣንንና ተቀጣሪነትን አልያም የሃይማኖት መሪነትንና ሰባኪነትን የሚመኙ አይደሉም። ሁለተኛ፤ “ይሄኛው ሙያና ይሄኛው የሕይወት ዘይቤ፣ ለአማራ፣ ለኦሮሞ ወይም ለሶማሌ ተወላጅ ነው። ያኛው ሙያና ያኛው የኑሮ ዘይቤ ደግሞ ለትግራይ፣ ለወላይታ ወይም ለጉራጌ ተወላጅ ነው” የሚሉ የዘልማድ አዝማሚያዎችን አይቀበሉም። የ1950ዎቹ ወጣቶች የሙያና የግል ሕይወታቸውን በራሳቸው መንገድ መምራት እንደሚችሉ የሚያምኑ ሆነዋል።
ተማሪዎቹ ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የመጡ ቢሆኑም፤ የሙያ ምርጫቸው ይመሳሰላል። ከመንግስት ስልጣንና ተቀጣሪነት ወይም ከሃይማኖት ሰባኪነት ይልቅ፤ ከሁሉም በላይ ቅድሚያ የሚሰጡት ለምህንድስና ወይም ለህክምና ሙያ፣ ለሜካኒክነት ወይም ለአስተማሪነት ሙያ እንደሆነ ጥናቱ ገልጿል። በአጭሩ፤ በያኔው የስልጣኔ ጭላንጭል፤ ለእውቀትና ለሳይንስ፤ ለሙያዊና ለምርታማ ስራ ክብር የሚሰጥ ትውልድ እየተፈጠረ ነበር። በአገሪቱ እየታየ የነበረውንም የትምህርትና የኢኮኖሚ ብሩህ አቅጣጫ ያመላክታል። Occupational Prestige, Status, and Social Change in Modern Ethiopia: William A. ShackSource: Africa: Journal of the International African Institute, Vol. 46, No. 2 (1976), pp. 166-181
በ1950ዎቹ ዓ.ም ኢትዮጵያ በሁሉም መስኮች ከእንቅልፏ እየነቃች እንደነበረ የሚያሳዩ የጥበብ ስራዎችንም መጥቀስ ይቻላል። የሃዲስ አለማየሁና የፀጋዬ ገብረመድህን ድርሰቶች፣ የነጥላሁን ገሠሠና የነምኒልክ ወስናቸው የሙዚቃ ስራዎች፣ ዛሬ ከአርባ እና ሃምሳ አመታት በኋላም፣ ወደር አልተገኘላቸውም። በእግር ኳስ እና በሩጫ ስፖርቶችም እንዲሁ።
በመንግስት አስተዳደር በኩልም፤ ትልቅ “የስልጣኔ አብዮት” የተካሄደው፣ ከ1960ዎቹ “አብዮተኛ ትውልድ” በፊት ነው። ለሺ አመታት በሃይማኖታዊ ሰነዶች (በክብረ ነገስትንና በፍትሃ ነገስት) ላይ ተመስርቶ የቆየውን የአገሪቱ ሥርዓትና ሕግ፣ ከኋላቀርነት ለማላቀቅና የስልጣኔ እድል ለመፍጠር ያስችላሉ የተባሉ የሕገመንግስት እና የምርጫ ህጎች ከ1923 እስከ 1948 ዓ.ም ፀድቀዋል። የተለያዩ የፍትሐ ብሄርና የወንጀል ሕጎች ከ1935 እስከ 1960ዎቹ መግቢያ ድረስ ታውጀዋል። የወንጀልና የፍትሐ ብሄር ህጎቹ እስከ ዛሬ ድረስ ይሰራሉ – (በ2000 ዓ.ም የተወሰነ ማሻሻያ ቢታከልባቸውም)።
ነገር ግን ሕጎችን በማወጅ ብቻ ሳይሆን፤ በግል አርአያነትና ጥረትም አገሬውን ወደ ስልጣኔ ለማራመድ ሙከራዎች ተደርገዋል። “በለውጥ ላይ የምትገኝ ኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በ1948 ዓ.ም ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡ ሲሞን ሜሲን፤ በ1925 ገደማ ዓ.ም የንጉሡ ሴት ልጅ መሞቷን ጠቅሰው፤ ለሟቿ ልዕልት የተዝካር ድግስ እንደማይዘጋጅ በአዋጅ መነገሩን ይገልፃሉ። ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች ያለ አቅማቸው በሚደግሱት ተዝካር ኑሯቸው መናጋቱ ብቻ አይደለም ችግሩ። የየአካባቢው የመንግስት ባለስልጣናት በየፊናቸው ተዝካር ሲደግሱ፤ የአካባቢው ነዋሪና ገበሬ፤ ወደደም ጠላም፤ እህል፣ ከብት እና ገንዘብ እንዲያዋጣ ይገደዳል። ገበሬዎችን ከዚህ ልማዳዊ ሸክም ለመገላገል ነበር የንጉሡ ሙከራ – ይላሉ ፀሐፊው።
ይህም ብቻ አይደለም። የድሮ ለቅሶ እንደዛሬ አይደለም። በእርግጥ ዛሬም ቢሆን፤ የአገራችን ለቅሶ ለታይታ የሚቀርብ ቅጥ ያጣ ልማድ ነው። ግን የድሮው ይብሳል። ሰው ሲሞት፣ ልብስ መቅደድና ፀጉር መንጨት፤ ፊት መቧጨርና ደረት መደለቅ፤ መሬት ላይ መንከባለልና አፈር መልበስ የተለመደ ነበር። ነውጠኛ ለቅሶ ይሉሃል ይሄ ነው። ይህን ለማስቀረት ንጉሡ እንደጣሩ የሚገልፁት ሲሞን ሜሲን፤ ነጠላ አዘቅዝቆ መልበስ የተጀመረው ያኔ ነው ይላሉ። Changing Ethiopia፡ Simon D. MessingSource: Middle East Journal, Vol. 9, No. 4 (Autumn, 1955), pp. 413-432።
እንዲህ በየመስኩ የስልጣኔ ጭላንጭሎች ብቅ ብቅ ቢሉም፤ የ1960ዎቹ ተማሪዎችና ወጣት ምሁራን፤ በንጉሡ ደስተኛ አልነበሩም። እንዲያውም፤ ንጉሡን እንደ ዋነኛ ጠላት ፈርጀዋቸዋል። “ንጉሡ አገሪቱን በኋላቀርነት አስረው ይዘዋል። ህዝቡን ከትምህርት አራርቀውታል፤ በተለይ ሴቶች በመሃይምነት ጨለማ ተውጠዋል (ድርብ ጭቆና እንዲሉ)። ህዝቡ ከመሰረተ ልማትና ከኢኮኖሚ እድገት፣ ከኤሌክትሪክና ከስልክ፣ ከመንገድና ከትራንስፖርት አገልግሎቶች እንዳይተዋወቅ፤ የእርሻና የኢንዱስትሪ እድገት እንዳያይ ያደረጉት ንጉሡ ናቸው” የሚሉ ውግዘቶች፤ በያኔዎቹ “የአብዮታዊ ትውልድ” አባላት እንደተጀመሩ እስከዛሬ ዘልቀዋል።
እውነታው ግን፤ ሙሉ ለሙሉ የዚህ ተቃራኒ ነው። በእርግጥ፤ የንጉሡን ዘመን በብዙ ምክንያቶች መተቸት ይቻላል። “የአገሪቱ የስልጣኔ ጅምር ተንቀራፈፈ፤ መፍጠን ነበረበት” ብሎ መተቸት ስህተት አይሆንም። በአብዮቱ የመጣው ለውጥ ግን፤ ጭራሽ የስልጣኔ ጅምርን አዳፍኖ የሚደመስስ ሆነ። ከንጉሡ ድክመት ይልቅ “የአብዮታዊው ትውልድ” ጥፋት በብዙ እጥፍ ይልቃል። “የአብዮታዊው ትውልድ” በርካታ አባላት ታዲያ፣ ይህ ታሪካዊ ውድቀታቸውና ኪሳራቸው በግልፅ እንዲታወቅ አይፈልጉም። ለዚህም ነው፤ እንደያኔው አሁንም ጨምር፤ የንጉሡን አስተዳደር ከማውገዝና ከማጥላላት ያልቦዘኑት። ነገር ግን እውነታውን ለዘላለም መሸፈን አይችሉም። የንጉሡንና የአብዮቱን ዘመናት፤ የዛሬውንም ጭምር ለመመዘንና ለማነፃፀር የምንችልባቸው መረጃዎች ብዙ ናቸው። ዛሬ ጥቂቶቹን ብቻ እንመልከት።

ትምህርት ከጀማሪ እስከ ዩኒቨርስቲ
በ1938 ዓ.ም የአንደኛና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ቁጥር፣ 35ሺ እንደነበር የሚገልፁት ዶ/ር ተከስተ ነጋሽ፣ ከአስር አመት በኋላ 95ሺ እንደደረሰ ይገልፃሉ – ዘጠኛ ሺ ገደማ የአንደኛ ደረጃ፣ አራት ሺ ገደማ የሁለተኛ ደረጃ፣ አራት መቶ ገደማ የከፍተኛ ትምህረት ተማሪዎች። በ1955 ዓ.ም፣ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች አስር ሺ፣ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ደግሞ 305 ሺ መድረሱን ዶ/ር ተከስተ ጠቅሰዋል – በወቅቱ የስምንተኛ ክፍል ተማሪ እንደነበሩ በማስታወስ Education in Ethiopia Nordiska Afrikainstitutet, Uppsala። እንደገና ከአስር አመት በኋላ በአብዮቱ ዋዜማ፣ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ቁጥር 1.04 ሚሊዮን ደርሷል – በሃያ አመታት ውስጥ ከአስር እጥፍ በላይ በማደግ።
በደርግ ዘመን፣ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት የተመዘገበው የተማሪዎች ቁጥር ወደ 2.9 ሚሊዮን ገደማ ነው – በሶስት እጥፍ አድጓል ማለት ነው። በኢህአዴግ 20 አመታት ውስጥስ? የተማሪዎቹ ቁጥር ወደ 15 ሚሊዮን ገደማ ሆኗል። በደርግ ዘመን ከነበረው ቁጥር ጋር ሲነፃፀር በአምስት እጥፍ ይበልጣል።
በንጉሡ ዘመን በሃያ አመታት ውስጥ ከሃያ እጥፍ በላይ የጨመረው የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ቁጥር በ1966 ዓ.ም 190ሺ ገደማ እንደደረሰ የሚገልፀው የአለም ባንክ መረጃ፣ በደርግ ዘመን ወደ 900ሺ እንደተጠጋ ይገልፃል። የደርግ ዘመን የተመዘገበው የአራት እጥፍ እድገት ከንጉሡ ዘመን ያነሰ ነው። በኢህአዴግ ጊዜም እንዲሁ። ኢህአዴግ ደግሞ በሃያ አመታት ውስጥ ወደ አምስት እጥፍ ገደማ በማሳደግ 4.5 ሚሊዮን አድርሶታል።
የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ቁጥር፣ በንጉሡ ዘመን በሃያ አመታት ውስጥ፣ ከአራት መቶ ገደማ ወደ 6500 አካባቢ ጨምሯል – በአስራ አምስት እጥፍ። በደርግ ዘመን ወደ ሶስት እጥፍ ገደማ አድጎ 18ሺ የደረሰ ሲሆን፣ በኢህአዴግ የሃያ አመታት ጊዜ፣ እንደ ንጉሡ ዘመን ከአስራ አምስት እጥፍ በማደግ ከ350ሺ በላይ ሆኗል።

ትምህርት በወንዶችና በሴቶች
የአብዮተኞቹ አንዱ መፈክር፣ የፆታ እኩልነት የሚል አልነበር? እስቲ የሴት ተማሪዎችን ድርሻ እንመልከት። አብዮተኞቹ የንጉሡን ዘመን ሲያወግዙ ስትሰሙ፤ በአብዮቱ ዋዜማ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት፣ የሴቶች ድርሻ ከዜሮ በታች የነበረ ነው የሚመስላችሁ። ነገር ግን፣ የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያመለክተው፣ በ66 ዓ.ም. ከአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች መካከል 32 በመቶ ያህሉ ሴቶች ነበሩ። በደርግ ዘመን የሴቶች ድርሻ ወደ 40 በመቶ ገደማ ደረሰ፣ በኢህአዴግ ደግሞ ወደ 47 በመቶ።
በከፍተኛ ትምህርት፣ እዚህ ግባ የማይባል ድርሻ የነበራቸው ሴቶች፣ በ1952 ዓ.ም ወደ 3 በመቶ ድርሻ ካገኙ በኋላ፣ በሶስት እጥፍ አድጎ በአብዮቱ ዋዜማ ወደ አስር በመቶ ገደማ ድርሻ ለመያዝ የበቁ ሲሆን፣ በደርግ ዘመን የሴቶች ድርሻ ወደ 18 በመቶ አድጓል። በኢህአዴግ ዘመን ደግሞ፣ ወደ 30 በመቶ ገደማ ደርሷል።
በሴቶች ትምህርት ዙሪያ ፈጣን እድገት የተመዘገበው መቼ እንደነበር፤ ይሄው መረጃው ራሱ ይናገራል።
የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ላይም አብዮተኞቹ ለውጥ አላመጡም። በንጉሡ ዘመን፣ በመጨረሻዎቹ ሃያ አመታት፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ከሰላሳ እጥፍ በላይ ስለጨመረ፣ የተማሪዎቹ ቁጥር በአብዮቱ ዋዜማ 8700 ገደማ ደርሶ ነበር። በደርግ ዘመን የታየው እድገት ኢምንት ነው። የተማሪዎች ቁጥር ከአስር ሺ ብዙም ፈቀቅ አላለም። በመጀመሪያዎቹ የኢህአዴግ አስር አመታትም እንዲሁ፣ የእድገት ፍንጭ አልታየም። ከዚያ በኋላ ነው በፍጥነት ማደግ የጀመረው። በኢህአዴግ ሃያኛ አመት ላይ፣ የቴክኒክና ሙያ ተማሪዎች ቁጥር፣ ከሰላሳ እጥፍ በላይ በማደግ ከ350ሺ በላይ ሆኗል።

የ“መሰረተ ልማት” አቅርቦት
በ1947 ዓ.ም፣ በአገሪቱ የነበረው አመታዊ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት፣ 33 ጊጋዋትሃወር እንደነበር የውሃ ሚኒስቴር ባለሙያ መረጃ ያሳያል። በአማካይ ለአንድ ሰው 1600 ዋትአወር… በጣም ትንሽ ነው። ለአንድ ቤተሰብ በቀን ለ25 ደቂቃ አንድ አምፖል ብቻ ያበራ ነበር እንደማለት ነው። እስከ አብዮቱ ዋዜማ ድረስ ሃያ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ግን፣ አቅርቦቱ በ18 እጥፍ ጨምሯል። 18 እጥፍ? ፈጣን እድገት ነው።
የአለም ባንክ መረጃ እንደሚያሳየው፣ በአብዮቱ ዋዜማ አመታዊው የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት 590 ጊጋዋትአወር ደርሶ ነበር። ግን በእነዚሁ አመታት ውስጥ የሕዝብ ቁጥርም ስለጨመረ፣ የኤሌክትሪክ ሃይል የማግኘት እድል በ18 እጥፍ ሳይሆን በ11 እጥፍ ነው የጨመረው። ይሄም ቀላል አይደለም። በቤተሰብ በየቀኑ 5 ሰዓት ያህል አምፖል እንደማብራት ቁጠሩት። ይሄ በንጉሡ ዘመን ነው።
በደርግ ዘመንስ? በ17 የደርግ አመታት ውስጥ፣ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት 1210 ጊጋዋትአወር ነው የደረሰው። በንጉሡ ዘመን ከነበረው ጋር ሲነፃፀር በአንድ እጥፍ ብቻ ነው የጨመረው። ግን ኢትዮጵያውያን የኤሌክትሪክ ሃይል የማግኘት እድላቸው ብዙም አልጨመረም። ለምን ቢባል፣ የሕዝብ ቁጥርም ጨምሯላ። እናም፣ በቤተሰብ ሲሰላ፣ በየቀኑ 6 ሰዓት ለማይሞላ ጊዜ አንድ አምፖል የማብራት ያህል ነው። በአጭሩ፣ በደርግ ዘመን ኤሌክትሪክ የመጠቀም እድል የተሻሻለው፣ ከሰባት በመቶ ባነሰ መጠን ነው።
በኢህአዴግ ዘመንስ? ከ1983 ዓ.ም እስከ 2003 ዓ.ም ድረስ ያለውን የሃያ አመታት እድገት እንመልከት። የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦቱ በምን ያህል ጨመረ? አሁንም የአለም ባንክ መረጃን ነው የምጠቅሰው። በጊጋዋትአወር፣ 1210 የነበረው ወደ 5000 ገደማ ጨምሯል። በአራት እጥፍ ገደማ ማለት ነው። ነገር ግን፣ በንጉሡ ዘመን እስከ አብዮቱ ዋዜማ ድረስ በነበሩ ሃያ ዓመታት፣ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ከ18 እጥፍ በላይ ማደጉን መዘንጋት የለብንም። በደርግ ዘመን ከነበረው ጋር ሲነፃፀር ግን፣ በኢህአዴግ ዘመን የታየው እድገት በእጅጉ የተሻለ ነው። ሰዎች በኤሌክትሪክ የመጠቀም እድላቸውስ ምን ያህል ተሻሻለ? በኢህአዴግ ሃያ አመታት ውስጥ፣ ከአንድ እጥፍ በላይ ተሻሽሏል። በቤተሰብ ሲሰላ፣ በየቀኑ ወደ 15 ሰዓታት ያህል አንድ አምፖል ለማብራት የሚችል የኤሌክትሪክ ሃይል ተገኝቷል እንደማለት ነው።
እንግዲህ አስቡት። በ1947 ዓ.ም አንድ የኢትዮጵያ ቤተሰብ በአማካይ በየቀኑ ለ25 ደቂቃ ብቻ አንዲት አምፑል ማብራት ይችል ነበር። በ1966 ዓ.ም፣ በየቀኑ ለ5 ሰዓታት ያህል ማብራት ቻለ። በ1983 ዓ.ም ወደ 6 ሰዓት ያህል ፎቀቅ አለ። በ2003 ዓ.ም፣ ወደ 15 ሰዓት ገደማ አደገ። የትኛው ዘመን እድገት ይሻላል?
እንደ ኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት ሁሉ፤ የመንገድ ግንባታ፣ የአውሮፕላን ትራንስፖርትና የስልክ መስመር አገልግሎትም እንዲሁ፤ ከአብዮቱ ዘመናት ይልቅ በንጉሡ ጊዜ የተሻለ እድገት ተመዝግቧል። ለምሳሌ በቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፍ፤ ከ1950 ዓ.ም እስከ 1966 ዓ.ም ድረስ ወደ ስድስት እጥፍ ገደማ በመስፋፋት፣ 45ሺ ገደማ የስልክ መስመሮች አገልግሎት ላይ ውለዋል።
በደርግ ዘመንስ? በሁለት እጥፍ ገደማ ነው ያደገው – ወደ 135ሺ ገደማ የስልክ መስመሮች። እንደ ንጉሡ ዘመን ከስድስት እጥፍ በላይ እድገት የታየው በኢህአዴግ ዘመን ነው። የስልክ መስመሮች ቁጥር በሃያ አመታት ውስጥ 900ሺ ደርሰዋል።
ይህም ብቻ አይደለም። እስከ አብዮቱ ዋዜማ ድረስ፣ የኤክስፖርት ገበያ አራት እጥፍ ገደማ አድጓል – ከ70 ሚሊዮን ዶላር ወደ 270 ሚሊዮን ዶላር። በደርግ ዘመን፣ በእነዚያ ሁሉ አመታት፣ የኤክስፖርት ገበያ በአንድ እጥፍ እንኳ ማደግ አልቻለም። ከ470 ሚሊዮን ዶላር አካባቢ አላለፈም። በኢህአዴግ ዘመንም በመጀመሪያዎቹ አስር አመታት፣ ከኤስፖርት ገበያ የተገኘው ገቢ እዚያው ገደማ ተገድቦ ቆይቷል። ከዚያ በኋላ ነው ከቀድሞው የተሻለ ፈጣን እድገት መታየት የጀመረው። በጥቅሉ፣ በሃያ የኢህአዴግ አመታት ውስጥ እስከ 2003 ዓ.ም ድረስ የኤክስፖርት ገቢ፣ ከአራት እጥፍ በላይ በማደግ፣ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ሆኗል – በንጉሡ ዘመን ከተመዘገበው እድገት ጋር ተቀራራቢ ነው።

የእህል ምርትና እጦት
የእህል ምርትን ደግሞ እንመልከት። ከአብዮቱ በፊት በነበሩ 20 ዓመታት፣ ለአንድ ሰው በአማካይ በየአመቱ 175 ኪሎ ገደማ እህል ይመረት ነበር። በአብዮቱ ዘመናት በደርግ ጊዜስ? ለአንድ ሰው በአማካይ 135 ኪሎ ገደማ እህል ነው በየዓመቱ ሲመረት የነበረው። በሌላ አነጋገር፤ የሕዝብ ብዛትን ከግምት አስገብተን ስናሰላው የእህል ምርት፣ በንጉሡ ዘመን የ30 በመቶ ብልጫ ነበረው።
በኢህአዴግ ዘመንስ? በመጀመሪያዎቹ የኢህአዴግ አስር አመታት፣ የአገሪቱ የእህል ምርት፣ ከደርግ ዘመንም የባሰ ነበር – በየአመቱ በአማካይ ለአንድ ሰው 125 ኪሎ እህል ነበር የሚመረተው። ቀጥለው ባሉት አስር አመታትስ? ምርቱ በአማካይ ወደ 165 ኪሎ ግራም ገደማ ደርሷል። በእርግጥ ያለፉትን ስምንት አመታት ብቻ ካየን፣ የአገሪቱ የእህል ምርት እየተሻሻለ፣ በአማካይ 175 ኪሎ ገደማ እንደደረሰ እናያለን። በአጠቃላይ ሲታይ፤ ከአብዮቱ ዋዜማ ጀምሮ ወደ ታች ሲያሽቆለቁል የነበረው አብዮታዊ የውድቀት ጉዞ ቀስ በቀስ የተገታው፤ የሶሻሊዝም አብዮት ከተገታ በኋላ ነው። ቀስ በቀስም እያገገመ፣ የአገሪቱ ኢኮኖሚ በንጉሱ ዘመን ወደ ነበረበት ደረጃ ለማደግ ችሏል። በሌላ አነጋገር፤ ኢትዮጵና ኢትዮጵያዊያን በአብዮቱ ሳቢያ ለድህነትና ለረሃብ ከመዳረጋቸው በተጨማሪ፤ ለ30 አመታት ያህል የኋሊት ተጉዘዋል። አዲሳድማስ ጋዘጣ ነጻ አስተያየት

ብሄር ብሄረሰብ፤ የዘር ፓለቲካ… ደስታው አንዳርጌ (ዶ/ር)

እውቀት ይስፋ፣ ድንቁርና ይጥfa
ይህ ነው የኢትዮጵያ ተስፋ።
ተስፋ ገብረሥላሴ
ፊደል የቆጠርሁት በአገራችን የህትመት ፋናወጊ (እና አርበኛ) የሆኑት ተስፋ ገብረሥላሴ ያሳትሟት በነበረው የባለ ፲ ሣንቲም ፊደል ነበር። ከፊደሏ ሽፋን ላይ ታዲያ ‘ተስፋገብረሥላሴ ዘብሄረ ቡልጋ’ ይላል። መጠየቅ እወድ ነበርና መርጌታን ‘የንታ ብሄረ ቡልጋ ምን ማለት ነው?’ ብየ ጠየኳቸው። የንታም ልጄ ብሄር ማለት በግእዝ አገር ማለት ነው። ቡልጋ ደሞ ሽዋ ክፍላገር ውስጥ የሚገኝ አውራጃ ነው። የተስፋ ገብረሥላሴ አገር እዚያ ነው፤ አሉኝ።
ከዚያ አስኮላ ትምርት ገብቸ ፬ኛ ክፍል ህብረተሰብ መጽሀፍ ውስጥ የኢትዮጵያ ‘ብሄረሰቦችን’ የሚያሳይ ስዕል ተደርድሮ አየሁ። በተለይ ሲዳማን የዎከሉት ቆንጃጅት ሙገጫ ሲዎግጡ የሚያሳየው ስእል አይረሳኝም። ይሁን እንጅ ብሄረሰብ የሚለው ቃል አልገባኝም ነበርና አስተማሪየን ጠየኳት። እሷ ግን ጎሳ፣ ነገድ ቅብጥርሴ ብላ የባሰ ግራ አጋባችኝ። ደግነቱ ማታ ማታ የንታ ዘንድ ወንጌል እማር ነበርና ወንበር ከመጀመሩ በፊት ቀደም ብዬ ሄጄ የንታን ‘ብሄረሰብ ምን ማለት ነው?’ ብዬ ጠየኳችው። የንታም ብሄር ማለት አገር ነው፣ ሰብ ደሞ ሰው ማለት ነው። እንግዲህ ብሄረሰብ ያው የሰው አገር መሆኑ ነዋ አሉኝ። የበለጠ ግራ ተጋባሁ። ህብረተሰብ መጽሀፌ ውስጥ ያዬሁት የሚያማምሩ ቆንጃጅትን ምስል እንጅ ወንዝ ወይ ጋራና ሸንተረር አልነበረማ።Ethiopia and Eritrea map
ሁሉ ሆነና ደርግም በኢሕአዴግ ተተካ። አሁን ግራ ያጋባኝ የነበረው ‘ብሄረሰብ’ የሚለው ቃል ‘ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች’ ተብሎ ተራብቶ መጣ። የግዕዙን ቀጥተኛ ትርጉም ካየን እንግዲህ አገራት፣ የሰው አገራትና ህዝቦች እያልን መሆኑ ነው። ይሁንና ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች ተብለው ይጠሩ የነበሩት የሁሉም ቋንቋ ተናጋሪዎች አሁን ‘ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች’ ሆነው የተባዙት አንዳንዶቹ ብሄረሰቦች ወደ ብሄርነት ሌሎቹ ደግሞ ወደ ህዝብነት ተለውጠው ይሁን በሌላ ምክንያት በውል አይታዎቅም። በአንጻሩ አሁን የኢትዮጵያ ህዝብ ብሎ ነገር የለም። በኢትዮጵያ ሕገ፡መንግስት ውስጥ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚል ቃል አይገኝም። ፖለቲከኞችም ‘የኢትዮጵያ ህዝቦች’ እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ ሲሉ አትሰሙም። ይህ አጋጣሚ የሚመስለው ካለ እሱ የዋህ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ማለት (ልክ በኢህአዴግ የመጀመሪያዎቹ ሰባት የስልጣን አመታት ኢትዮጵያ አገሬ የሚል ዘፈን እንደማዳመጥ ያለ) በትምክህተኝነት ሊያስከስስ የሚችል የፖለቲካ ፋውል መሆኑን እያንዳንዱ ካድሬ ስለሚረዳ ነው።
የኢትዮጵያ ሕገ፡መንግስት በአገሪቱ ውስጥ የፖለቲካ ስልጣኑም ሆነ ምድሩ አንዲሁም በላዩና በውስጡ ያለው ሀብት ሁሉ ‘የብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች’ የጋራ ሀብት ነው ይላል። ይህ ደግሞ ከሌሎች ኣገሮች ሕገ፡መንግስታት ሁሉ ልዩ ያደርገዋል (ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች የሚለው ሀረግ እንደ ዋሊያ ኢትዮጵያ ብቻ ነው የሚታወቀው)። ይህ ይገርመኝ ነበርና ከአስር ኣመታት በፊት ከህገ፡መንግስት ጋር በተገናኘ የመመረቂያ ጽሁፍ ሳዘጋጅ ለመሆኑ አነዚህ የኣገሪቱን የፖለቲካ ስልጣንና ሀብት ኣንድም ሳያስቀሩ ጠቅልለው የያዙ ፍጡራን በትክክል አነማን ናቸው? ኣንዳቸው ከሌላቸው የሚለዩት በምን ነው? በአገሪቱ ውስጥስ ስንት ብሄሮች፣ ስንት ብሄረሰቦችና ስንት ህዝቦች አሉ? ለምሳሌ የቀበሌ መታወቂያ ስትወስድ ብሄርህን ተጠይቀህ ጉራጌ ብለህ ከሞላህ በኋላ ማታ በኢቲቪ የጉራጌ ብሄረሰብ ስላስመዘገበው ልማት ትሰማለህ። ታዲያ ብሄርና ብሄረሰብ አንድም ሁለትም ናቸው? ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎችን ይዠ መልስ ፍለጋ ሰነዶች ማገላበጥ ነበረብኝ። የህገ፡መንግስቱን ረቂቅ (ፕሪፓራቶሪ ዎርክስ) ሳይቀር አገላብጨ የሚረባ ነገር ላገኝ አልቻልሁም። ሕገ፡መንግስቱን በማርቀቅ የጎላ ድርሻ ነበራቸው የሚባሉትን ሰዎችም ጠይቄ ያገኘሁት ውጤት ኣልነበረም። በጣም ተገረምሁ። በአገራችን ላይ ከፈጣሪ ቀጥሎ ሁሉን ሀብትና ስልጣን ‘የተቆጣጠሩት’ ግኡዛን ማንነት እንዴት አይታዎቅም? ይህ እኮ እጅግ መሰረታዊ ጥያቄ ነው።
በተለይ ህዝቦች የሚለው ቃል ግራ አጋቢ ነው። በአለም ላይ አንድ ቋንቋ ተናጋሪ ወይም እንድ አይነት ማንነት ያላቸው ሰዎች ብቻ የሚኖሩባቸው አገራት ከአምስት አይበልጡም፤ ይህም ቢሆን በጣም የሚያከራክር ነው። ይሁን እንጅ የብራዚል ህዝቦች ወይንም የኬንያ ህዝቦች ቢባል እንግዳ ነው የሚሆነው። ምክንያቱም ህዝብ በትርጉሙ ያልተወሰነ ቁጥርና ማንነት ያላቸው ሰዎችን ያካተተ የጥቅል (የወል) ስም ስለሆነ ነው። ለዚህም ነው የአለም ህዝብ ቁጥር እንጅ የአለም ህዝቦች ቁጥር የማንለው። በርግጥ ፈረንጆቹም ከቅኝ በፊት ይኖሩ የነበሩ ቀደምት ጎሳዎችን (ትራይብስ) ለማመልከት ኢንዲጅነስ ህዝቦች ወይም አማዞን ውስጥ የሚኖሩ ህዝቦች ይላሉ። ይህ ግን ቀደምት ጎሳዎችን (ነገዶችን)የሚተካ ተለዋጭ ቃል እንጂ ተደራቢ ስያሜ አይደለም። ስለሆነም ቀደምት ጎሳዎችና ኢንዲጅነስ ህዝቦች አይሉም። እንዲያውም ኢንዲጅነስ ህዝቦች የየአገራቸው (ሰፊ)ህዝብ አካል ናቸው። ለምሳሌ የካናዳ ህዝብ በአገሩ የሚኖሩ ኢንዲጅነስ ህዝቦችን ያጠቃልላል። በዚህ አግባብ ከመደበኛ ሰዋሰው ርባታ ተቃራኒ ቢመስልም በአንድ አገር ውስጥ ህዝብ የሚለው ቃል ህዝቦች ከሚለው ቃል ይሰፋል ማለት ነው። ከላይ በጠቀሁት ምሳሌ የካናዳ ህዝብ ካናዳዊያንን በሙሉ ሲያመለክት የካናዳ ኢንዲጅነስ ህዝቦች ግን የካናዳ ህዝብ አካል የሆኑ (ከአጠቃላዩ ህዝብ ፭ ፕርሰንት እንኳን የማይሞሉ) ግን ደግሞ የየራሳቸው የተለየ ማንነት ያላቸውን ነገዶችን ብቻ የሚያመለክት ነው። በሁሉም አገሮች የሚኖሩ የተለያዬ ቋንቋና ማንነት ያላቸው ሁሉ በአንድ ላይ የዚያ አገር ህዝብ ተብለው ነው የሚታዎቁት።
ወደ አገራችን ስንመጣ ግን ሁለት አደናጋሪ ነገሮችን እናገኛለን። የመጀመሪያው ህዝቦች የሚለው ቃል አግባብ በሌላው አለም እንደሚታወቀው ሁሉ ቀደምት ነዋሪወችን (ኢንዲጅነስ ትራይብስ) ለማመልከት ነው እንዳይባል ኢትዮጵያ ውስጥ ቀደምት ያልሆነው ማን እንደሆነና ማን ከማን እንደሚቀድም አይታወቅም። እንዲያውም ሁሉም ‘ብሄር ብሄረሰቦች’ ቀደምት ነዋሪወች ናቸው ማለት ይቻላል። ቢያንስ ይህ ላለመሆኑ ተቃራኒ ማስርጃ የለም (እንዲያውም እኮ እንደ ሳይንሱ ከሆነ የአለም ህዝብ ሁሉ የተገኘው ከኢትዮጵያ ነው)። ‘ህዝቦች’ የሚለው ቃል አንዳንዶች እንደሚሉት አናሳ ቁጥርና አገራዊ የፖለቲካ ተሳትፎ ያላቸውን የተለያየ ቋንቋ ተናጋሪዎችን ለማመልከት ነው እንዳንል እነሱው መልሰው ታዳጊ ብሄረሰቦች (አንዳንዴ አናሳ ብሄረሰቦች) ሲሏቸው እንሰማለን። ያ ከሆነ ደግሞ ብሄር ብሄረሰቦች በሚለው አገላለጽ ብንስማማ እንኳን ‘ህዝቦች’ የሚለው ቃል አላስፈላጊ ድግግሞሽ ከመሆንና ከማደናገር ኣልፎ የሚጨምረው ነገር የለም ማለት ነው። ሁለተኛውና በጣም የሚገርመው በአለም ላይ ባልተለመደ ሁኔታ በአገሪቱ የሚኖሩት ‘ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች’ በአንድላይ የኢትዮጵያ ህዝብ አይሆኑም። ይህ የሆነው አንድ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ሕገ፡ መንግስታዊ ቃልኪዳን ገብተናል ያሉት ‘ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች’ የሚጋሩት ማንነት ሳይኖራቸው ቀርቶ ይሁን በሌላ ምክንያት አይታወቅም። ለነገሩ የአንድ አገር ህዝብ አካል ለመሆን የዚያ አገር ዜጋ ከመሆን ሌላ ምን የተለየ የጋራ ማንነት ያስፈልጋል?
ግድየለም፤ ያ ሁሉ ፖለቲካ ነው ብለን እንለፈው። እኛስ ቢሆን ቃላትን (አንደኣብዛኛዉ ነገራችን) እንደልባችን የምንጠቀመው ለምን ይሆን? ኢትዮጵያ በዘር ተከፋፈለች፣ የዘር ፖለቲካ ያጠፋናል፣ የጦር ሰራዊቱ ከኣንድ ዘር በወጡ አዛዦች ቁጥጥር ስር ነው፣ አቶ እከሌ በተቋሙ ውስጥ የነገሰውን ዘረኝነት በመቃዎም ስልጣናቸውን ለቀቁ፣ ወዘተ…በየቀኑ የምንሰማው ሮሮ ነው። ለመሆኑ ዘር ምንድን ነው? ኢትዮጵያ ውስጥ ስንት ዘር አለ? ለምሳሌ አማራ አንድ ዘር ትግሬ ደግሞ ሌላ ዘር ናቸው? ከሆነስ ከየት ነው የመጡት? እንደሚታወቀው ያን ያህል ሩቅ ከማይባል ጊዜ በፊት ግእዝ እንጂ ትግርኛም አማርኛም ኣልነበሩም። ታዲያ ያኔ ትግሬ ነበር? ኣማራስ? ሌላው ቀርቶ ሴሜቲክ፣ ኩሽቲክ የሚባለውስ ምናልባት ቋንቋን ከመግለጽ (ይህም አከራካሪ ይመስለኛል) የዘለለ ያለው አንድምታ ምንድን ነው? ለነዚህ ጥያቄዎች መልስ መስጠት ችሎታየም አላማየም አይደለም፤ ነገር ግን በጥንቃቄ መታየት የሚገባቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች ይመስሉኛል። እንዲያውም ስለማንነታችን ሳይንሳዊ ብንሆን ብዙ ችግራችን የሚቃለል ይመስለኛል። ኢሕአዴግ ኢትዮጵያ ውስጥ ‘ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች’ እንጅ እናንተ ቦታ የላችሁም፤ መሬቱ በሙሉ የእነሱ በመሆኑ እናንተ የመሬት ባለቤት መሆን አትችሉም ሲለን ቢያንስ እነዚያ ‘ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች’ በትክክል እነማን እንደሆኑ እንዲነግረን እንጠይቃለን። በአንጻሩ ደግሞ እኛ የዘር ፖለቲካ ወዘተ…ስንል ምን ማለታችን እንደሆነ መረዳትና ማስረዳት ያለብን ይመስለኛል።
[email protected]
በዚሁ ላብቃ።
ሰላም

ባለፉት አራትና አምስት አመታት በግልጽ እንዳየነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እኩልነቱን፤ መብቱንና ነጻነቱን ለማስከበር የሚያደርገዉ ትግል ጫና በፈጠረበት ቁጥር ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ የራሱን ህገመንግስት የሚደፈጥጡ ህጎች አርቅቆ አያጸደቀ ሠላማዊ ዜጎችን አስሯል፤ ገድሏል ከአገር እንዲሰደዱም አድርጓል። ለምሳሌ በ2003 ዓም የኢትዮጵያ ፓርላማ ከቤተመንግሰት የተላለፈለትን ትዕዛዝ አክብሮ ለኢትዮጵያ ህዝብ መብትና ነፃነት መከበር የሚታገለዉን የግንቦት 7 ንቅናቄ ሽብርተኛ አድርጎ ፈርጇል። ይህ ፈር የለቀቀ ፍረጃ ደግሞ ወያኔ የሱን ዘረኛ ስርዐት የሚቃወሙ ግለሰቦችን፤ ሀሳባቸዉን በነፃነት የሚገልጹ ዜጎችን፤ ጋዜጠኞችን፤ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና ከወያኔ ጋር አናብርም ያሉ ወጣት ኢትዮጵያዉያንን “ግንቦት ሰባቶች” ናችሁ እያለ በጅምላ እያሰረ እንዲያሰቃይ ህጋዊ ሽፋን ሰጥቶታል። ለምሳሌ ከፍትህና ከነጻነት ጥማት ዉጭ ከግንቦት 7 ንቅናቄ ጋር ምንም አይነት ግኑኝነት የሌለዉን የፖለቲካ ፓርቲ መሪዉን አንዱአለም አራጌን፤ ታዋቂዉን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና መምህርት ርኢዮት አለሙን የግንቦት 7 አባላት ናቸዉ የሚል ሰንካላና መሠረተ ቢስ ክስ መስርቶ ለረጂም ዘመን እስራት ዳርጓቸዋል።
ወያኔ እንደ ዛሬዉ ከተማ ዉስጥ ሆኖ ሥልጣን ሳይቆጣጠር ገና ጫካ ዉስጥ እያለ ጥርሱን ከነከሰባቸዉና ከተቻለ አጠፋቸዋለሁ ካለዚያም አሽመደምዳቸዋለሁ ብሎ አስራ ሰባት አመት ሙሉ ከተዘጋጀላቸዉ የኢትዮጵያ ብሄረሰቦች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ የአማራ ብሄረሰብ ነዉ። በለስ ቀንቶት ሥልጣን ከጨበጠ ማግስት ጀምሮም በወሎና በጎንደር በኩል ከትግራይ ጋር የሚያዋሰኑ ሰፊ የሆነ ለም መሬቱን ጠቅልሎ በመውሰድ ዘረኛ ሥርዓቱን ዕድሜ ሊያራዝሙልኛል ይችላሉ ብሎ የሚተማመንባቸውን የቀድሞ የትግል አጋሮቹንና ካድሬዎቹን አስፍሮበታል:: ይህ በደልና ግፍ አልበቃ ብሎትም ቀደምቶቹ የኢትዮጵያ ገዥዎች ለፈጸሙት ግፍና የአስተዳደር በደሎች ሁሉ አማራዉን በጅምላ ተጠያቂ የሚያደርግ ፕሮፖጋንዳ እነሆ እስከዛሬ በመርጨት ለዘመናት በሠላም ከኖረው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ጋር በጠላትነት እንዲተያይ አድርጎታል:: በወያኔ አጋፋሪነት በበደኖ ፡በአርሲ በአረካና ሌሎች አካባቢዎች አማራው ላይ በግፍ የተፈጸመው ጭፍጨፋና ከ2004 እስከ 2005 ዓም አማራዉን ከጉራፈርዳና ከቤንሻንጉል ለማፈናቀል የተወሰደው እርምጃ የዚህ የወያኔ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ውጤት መሆኑን የምስት የለም::
ሟቹ መለስ ዜናዊና በህይወት የሚገኙ ቀንደኛ የወያኔ መሪዎች የተጠናወታቸው የአማራ ጥላቻ በጸረ ፋሽስት ዘመቻ ወቅት ባንዳ ከነበሩ አባቶቻቸዉና አያቶቻቸዉ የተወረሰ ፋሽስት ጣሊያን ለደረሰባት ሽንፈት በዘርና በሃይማኖት ተከፋፍለን እርስ በርሳችን እንድንጠፋፋ ተክላብን የሄደቺው ተንኮል አካል ነው ::
የዚህ የጥፋት አጀንዳ አስፈጻሚ የሆነው ወያኔ የጀመረውን አገር የማፍረስና ህዝብ የመከፋፈል አጀንዳ ለማሳካት በየክልሉ የተኮለኮሉ ምስሌኔዎች እንወክለዋለን በሚሉት ህዝብና ክልል ላይ እየፈጸሙት ያለው በደልና ሰቆቃ አዲስ ምዕራፍ በያዘበት በአሁኑ ወቅት እራሳቸዏን ለባርነት አዋርደው ህዝባቸውን በማዋረድ ላይ የሚገኙት የብአዴኑ አለምነህ መኮንንን የመሳሰሉ ሆድ አደሮች ውርደት በቃን ዘረኝነት በቃን ብለው በተነሱ ዜጎች ላይ እየወሰዱ ያለው ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እጅግ አሳሳቢ ሆኖአል::
ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና ሞክራሲ ንቅናቄ ከሰሞኑ በደረሰው መረጃ ወያኔ ከአማራው ቀምቶ በትግራይ ክልል ባስገባቸው ወረዳዎች ላይ የሚኖሩ ንጽሃን ዜጎች ለምን በወያኔ የግፍ አገዛዝ ትማረራላችሁ እየተባሉ በወያኔ ታማኝ ሚሊሻዎች
እስር እንግልትና ድብደባ እየተፈጸመባቸው መሆኑን አረጋግጦአል:: በዚህ በአዲስ መልክ በተጀመረዉ የወያኔ የጥቃት ዘመቻ መሳሪያ ያነገቡ የህወሃት ሚሊሻዎች ከክልላቸዉ ዉጭ ወደ ተለያዩ የአማራ ከተማዎችና ወረዳዎች ሰርገዉ እየገቡ የእነሱን ቋንቋ የማይናገረዉን ሁሉ የግንቦት 7 ተላላኪዎች ናችሁ በሚል እያሰሩ በመደብደብ ላይ ናቸዉ።
ይህ በመሆኑ ዛሬ አትዮጵያን ከሱዳንና ትግራይን ከጎንደር ጋር በሚያዋስኑ የአማራ ክልል ዉስጥ የሚገኙ ገበሬዎች እጃቸዉ እርፍ ከሚጨብጥበት ግዜ በወያኔ ሰንሰለት የሚታሽበት ግዜ ይበልጣል፤ የመንግስት ሰራተኛዉና የከተማ ነዋሪዉም ቢሆን አብዛኛዉን ግዜ የሚያጠፋዉ ከወያኔ ካድሬዎች ጋር ግምገማ በመቀመጥ ሲሆን ተማሪዉና ወጣቱ ህብረተሰብ ደግሞ “መጡ አልመጡም” እያለ ሌሊቱን የሚያሳልፈዉ በየጫካዉ እየተሸሸገ ነዉ።
የዚህ አይነት አስከፊ ግፍና መከራ በአፋር ፡ በጋምቤላ በኦጋዴንና በኦሮሚያ በሚኖሩ ዜጎቻችን ላይ ሲፈጸም ቆይቶአል:: ? ወያኔ እራሱ አርቅቆ ባጸደቀውና በሐምሌ ወር 1987 ዓም በስራ ላይ የዋለዉ የወያኔ ህገ መንግስት ኢትዮጵያ በዘጠኝ የፌዴራል ክልሎች መከፈሏንና እያንዳንዱ ክልል እራሱን በእራሱ የማስተዳደር መብቱ የተረጋገጠ እንደሆነ ይደነግጋል። በዚህ ህገ መንግስት መሠረት እያንዳንዱ ክልል የራሱ ቋንቋ፤ የአስተዳደር ማዕከልና እንዲሁም የክልሉን ሠላምና ጸጥታ የሚያስከብር የፖሊስ ኃይል ይኖረዋል ይላል። ታድያ ለምንድነዉ እያንዳንዱ ክልል የራሱ ፖሊስ ኃይል አያለዉ ከትግርኛ ቋንቋ ዉጭ ሌላ ቋንቋ የማይናገሩ የህወሃት ታማኝ ሚሊሻዎች አማራ ክልል ዉስጥ እየገቡ አማራዉን የሚያሰቃዩት?
መልሱ ቀላል ነዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ ህዝባዊ አምቢተኝነቱ እያየለ በመጣና የነጻነት ኃይሎች ጡንቻ በፈረጠመ ቁጥር ወያኔ አንገቷ ላይ ቀጭል እንደታሰረባት በቅሎ ይደነብራል። የደነበረ ደግሞ መራገጡ አይቀርምና መሳሪያ ያነገቡ ኃይሎችን እንቅስቃሴ እገታለሁ በሚል ከንቱ ጥረት ደንባራዉ ወያኔ የፈሪ በትሩን በድንበር አካባቢ በሚኖሩ የአማራ ክልል አርሶ አደሮች፤ ወጣቶችና ሠራተኞች ላይ ማሳረፍ ጀምሯል።
ወያኔ እንደ ግንቦት ሰባት የኮነነዉና የህዝብና የአገር ጠላት አድርጎ የሳለዉ ድርጅት የለም፤ የወያኔ የዜና ማሰራጫዎችም ይህንን የአገዛዙን አቋም በተደጋጋሚ ለኢትዮጵያ ህዝብ አሰምተዋል።የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ማን ለመብቱና ለነጻነቱ እንደቆመና ማን መብቱና ነጻነቱ ላይ እንደቆመበት ለይቶ የሚያዉቅ ህዝብ ነዉ። ስለዚህም ግንቦት ሰባት ወያኔዎች አላፊዉንና አግዳሚዉን “ግንቦት ሰባት” ነህ እያሉ ከሚያሰቃዩ፤ ህዝብንና ግንቦት ሰባትን ያስተሳሰረዉ ነጻነት፤ ፍትህና ዲሞክራሲ ነዉና የኢትዮጵያን ህዝብ ጥያቄ ቢመልሱ ለእነሱም፤ ለእኛም ለአገርም ይበጃል የሚል የጸና እምነት አለዉ። ወያኔ በኢህአዴግ ስም ያሰጠጋቸዉን ምሰለኔዎች ጨምሮ ከራሱ ዉጭ ሌላ ማንንም አያምንም፤ ስለዚህም ነዉ የአገሪቱን የመከላከያ፤ የደህንነትና የፖሊስ ተቋሞች በራሱ ሰዎች ቁጥጥር ስር ያደረገዉ። ዛሬ በግልጽ እንደምንመለከተዉ ወያኔ በጉልበት ለያዘዉ ስልጣን ያሰገኛል ብሎ በሚጠረጥረዉ ቦታ ሁሉ የራሱን ልዩ ሚሊሺያ እየለላከ የኢትዮጵያን ህዝብ መኖሪያ ቤቱ ድረስ አየሄደ እያጠቃ ነዉ። ግንቦት ሰባት ወያኔና የፈጠረዉ ዘረኛ ስርዐቱ የቆሙት በፍጹም ማንሰራራት የማይችሉበትት የመጨረሻ መቀበሪያ ጉድጓዳቸዉ ጫፍ ላይ ነዉ የሚል ጽኑ እምነት አለዉ። ሆኖም ጉድጓድ ጫፍ ላይ የቆመ ጠላት በራሱ ተወርዉሮ ጉድጓዱ ዉስጥ አይገባምና ይህንን የተዳከመ ጠላት እተፈራገጠ ጉዳት ከማብዛቱ በፊት ለመደምሰስ ክንዳችንን አጠናክረን በህብረት እንደ አንድ ሰዉ እንነሳ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

እየደጋገምን የምናጠፋው ጥፋት እኛን ራሳችንን ይዞ እንዳይጠፋ መጠንቀቅ ያባት ነው!

ያለ ለውጥ፣ ያለ ዋስትና መራመድ አይቻልም፡፡
በማንኛውም ረገድ ራስን መቻል እንደሚኖርብን ልብ እንበል፡፡ በምግብ ራሳችንን ችለን ረሀብተኛ ዲሞክራሲ ይዘን እንጓዝ ብንል የማያዋጣንን ያህል፤ በባዶ ሆድም ዲሞክራሲን አንግቦ መጓዝ ወንዝ አያሻግረንም፡፡ ጥቂት የናጠጡ ሀብታሞችና አያሌ የኔ-ብጤዎች ያሏት ሀገርም ሆነ ሰላሟን አጥታ ብዙ ሀብታሞችን ያፈራች ሀገር እንድትኖረን አይደለም ደፋ-ቀና የምንለው፡፡

እንደጥንቱ መፈክር “ጉዟችን ረጅም ትግላችን መራራ” ነው ማለትም አያዛልቀንም፡፡ ሁሌም ረጅም፣ ሁሌም መራራ መሆን የለበትምና! ያለ ለውጥ፣ ያለ ዋስትና መራመድ አይቻልም፡፡ የለውጥ አንቀሳቃሹ በአብዛኛው ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ በዕውቀት የተገነባ፣ ለውጥ የገባው፣ ዛሬ ላይ የተደረሰው ብዙ ለውጥና መስዋዕትነት ታይቶ መሆኑን የተረዳ ወጣት እንጂ “ፋስት” በሚል ታርጋ የታሸገ የቢዝነስ ተሯሯጭ ለብ-ለብ ትውልድ ብቻ እንዳይሆን አገርና ነገር የገባው ወጣት መገንባት ያስፈልጋል፡፡ባለራዕይ-ለማኝ ዐባይ ሲገደብ የምሰጥህ ሁለት ብር አበድረኝ ይላል::

ያልፈጠርነውን፣ ያላስተማርነውን፣ በአግባቡ ያላነፅነውን ልጅ የሌለ ቅፅል ሰጥተን ብናሞካሸው ረብነት የለውም፡፡ በአናቱ ቅቤ ጣል ያለበት ሹሮ ዓይነት ካፒታሊዝም ኑሮአችን ቅቤ በቅቤ ነው እንደማያሰኝ ሁሉ፤ በእንዲህ ያለ ሥርዓት ውስጥ የሚያድግም ልጅ በአርቲፊሻል የተኳኳለ ከመሆን በቀር ኦርጅናሌ እንደማይሆን እናስተውል፡፡

ከመጠላለፍ ይሰውረን፡፡አደቡን ይስጠን፡፡ በተጠራጠርነው ሁሉ ፍርድ ከመስጠት ያድነን፡፡ እየደጋገምን የምናጠፋው ጥፋት እኛን ራሳችንን ይዞ እንዳይጠፋ መጠንቀቅ ያባት ነው! የምንገባው ቃል መፈፀሙን የሚያረጋግጥልን አንድም ታሪካችን፣ ሁለትም ለራስ መታመናችን ነው! በተግባር የምንሠራው በቃል የምናወራውን ካልመሰለ ዕቅዳችን፣ ስትራቴጂያችን ሁሉ፤ ውሃ የበላው ቤት እንደሚሆን አንርሳ! በታሪክ ያየነው ስህተት እንዳይደገም መጣጣር አዲስ ታሪክ መሥራት ነው!

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ህዝባዊ ንቅናቄው የሚካሄድባቸው 17 ከተሞችም ተለይተው ታውቀዋል፤ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዛሬ ይፋ ያደረገው የህዝባዊ ንቅናቄ መርሃ ግብር በተከታታይ ሊካሂዳባቸው ካቀዳቸው ህዝባዊ ንቅናቄዎች መካከል አንዱ የሆነውን “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባቤትነት”(Millions of voices for land ownership) የሚል ስያሜ የሰጠውን የህዝባዊ ንቅናቄ ነው፡፡ መረሃ ግብሩ በዛሬው እለት ይፋ የተደረገው ቀበና መድኃኔዓለም ቤ/ክ ፊት ለፊት በሚገኘው የፓርቲው ጽ/ቤት […]

ናትና ህጻን ልጅዋን ገድሎ የተሰወረው ሰውዬ ትውልዱ ኢትዮጵያዊ ሲሆን በፈረንሳይ ፓሪስ ክርተማ የጎዳና ላይ ተዳዳሪ ነበር:: ሟች ወ/ሮ ክውን ገዳሙ ትባላለች:: ከቤትዋ ወደ ስራ ቦታ ሲመላለሱ ተጠርጣሪውን የዩታል:: በጎዳናው የተጎሳቆለውን ሰው(ጉዳዩ በህግ ስለተያዘ ስሙን እዚህ ላይ አንጠቅሰውም) ስለሚያሳዝናቸው ባለፉ ባገደሙ ቁጥር እጃቸውን ይዘረጉለት ነበር::

ከግዜ በኋላ ከክረምቱ ብርድ እንዲገላገል ሲሉ ይህንን የጎዳና ተዳዳሪ ለግዜው በቤታቸው አስጠጉት:: የአቅማቸውን እየረዱት አብረው ለወራት ኖሩ::

ባለፈው ሳምንት አንድ አስደንጋጭ ክስተት በቤተሰቡ ውስጥ ተፈጸመ:: በችግሩ ያስጠጉት ሰው ከተኙበት በጭካኔ ገድሏቸው አመለጠ::

ወ/ሮ ክውን ገዳሙ የሶስት ልጆች እናት ሲሆኑ በፈረንሳይ ፓሪስ ለረጅም ግዜ ኖረዋል:: የሶስት ልጆች እናትም ናቸው:: ያለአባት ከሚያሳድጓቸውን ሶስት ልጆች ውስጥ አንደኛዋና የሁሉም ታናሽ ከሆነችው ጋር ላይመለሱ ይህችን አለም ባለፈው ሳምንት ተሰናበቱ::

ገዳዩ ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በጩቤ ሰነጣትቆ ነው እናትና ልጅን ለህልፈት የዳረገው- እንደ ፈረንሳይ የዜና ምንጭ:: ባጎረሱት እጅ ተነከሱ:: ደግ ባደረጉ ምላሹ ግድያ ሆነ: ለዚያውም አረመኔያዊ ግድያ::

ነብሰ ገዳዩ ለግዜው ተሰውሯል:: የፈረንሳይ ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር በመሆን ጉዳዩን በጥብቅ ይዞታል:: እኛም እየተከታተልን ጉዳዩ ምን እንደደረሰ እናቀርብላችኋላን::
ክንፉ አሰፋ

የተማረ ወይም የእውቀት ባለቤት እንደሆነ የሚነገርለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ክፍል ከወያኔ ጋር የሚደረገው ትግል ሰላማዊ ይሁን ወይስ በትጥቅ ትግል የሚለውን የጦፈ ክርክር ሲያደርግ ሃያ ሁለት ዓመታት ሆነው፤ ዳኛ የሌለበት ክርክር ስለሆነ የመደማመጥ ግዴታ ታይቶበት አይታወቅም፤ ስለዚህም በሁለቱ መሀከል ያለው ልዩነት ግልጽ ሆኖ አያውቅም፤

አንድ፣ ከሁሉ በፊት ሰላማዊ ትግል በሀሳብ ደረጃ መሆኑንና የትጥቅ ትግል ደግሞ በተግባር መሆኑን ለይቶ ለመረዳት ችግር ሆኖ ቆይቶኣል፤ በሌላ አነጋገር ሰላማዊ ትግል በሀሳብ፣ በንግግር፣ በተለያዩ ሀሳብን ለማስለወጥ መቀስቀሻ በሚሆኑ መንገዶች ተቃውሞን መግለጽ ነው፤ በአንጻሩ የትጥቅ ትግል በጠመንጃ ወይም በጉልበት ያለውን የአገዛዝ ሥርዓት ለመለወጥ የሚደረግ ሙከራ ነው፤

ሁለት፣ እንዲህ ከሆነ በሰላማዊ ትግል ለሚያምኑ ሰዎች ያለምንም ጥርጥር በተለያዩ ዓላማዎችና ዘዴዎች ላይ መከራከርና ሀሳብን ማጥራት አስፈላጊ ነው፤ በሰላማዊ ትግል ተግባር አለ ቢባልም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የድጋፍ ወይም የተቃውሞ አቅዋሞችን ከማሳየት አያልፍም፤ አገዛዞች ጃዝ! ብለው ውሻና ፖሊስ በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ ሲለቁ የጉልበት ጥርስና ዱላ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ያርፋል፤ ጉዳት ይደርሳል፤ ሰላም ይቃወሳል፤ በሕዝብና በአገዛዙ መሀከል ቂም ይጀመራል።

ሦስት፣ የትጥቅ ትግል ደግሞ በተዋረድ በሚተላለፍ ትእዛዝ የሚፈጸም ግዴታ ነው፤ በትጥቅ ትግል ጉልበተኛ ከጉልበተኛ ጋር፣ ብረት ከብረት ጋር ይጋጠማል፤ የሰው ልጅ ለእርድ ይቀርባል፤ በሕይወታቸው በልተው ያልጠገቡ ምስኪኖች ለጥቂት ሰዎች የሥልጣን ጉጉት ይታረዳሉ፤ ያለቀባሪ በጅብና በአሞራ ይበላሉ፤ ዕድለኞች የሚባሉት እጆቻቸው፣ ወይም እግሮቻቸው ተቆርጠው፣ ወይም ዓይኖቻቸው ጠፍተው፣ ወይም ከዚህ ሁሉ የባሰ ጉዳት ደርሶባቸው በሕይወት የሚቀሩት ናቸው፤ ከነዚህ በሕይወት በቀሩት የጦር ጉዳተኞችና በጦርነቱ ላይ በሞቱት መሀከል የትኛው የተሻለ አንደሆነ የሞቱት ባይናገሩም ጉዳተኞቹ ይናገራሉ፤ ‹የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ!› እያሉ።

አራት፣ ሁለቱ የትግል ስልት ዓይነቶች በባሕርይ የተለዩ ናቸው፤ አንዱ ሌላውን የሚደግፍ አይደለም፤ ሰላማዊ ትግል የትጥቅ ትግልን ለመደገፍ ሰላማዊ የሚለውን ስያሜ መጣል አለበት፤ የትጥቅ ትግልም ሰላማዊ ትግልን ለመደገፍ ትጥቅ የሚለውን ስያሜ መተው አለበት፤ ሰላማዊ ትግልና የትጥቅ ትግል አራማጆች ድል ቢያደርጉ ማን ወንበሩ ላይ እንደሚወጣ ሳይታለም የተፈታ ነው፤ ጠመንጃ የያዘው ሥልጣኑን ሲይዝ ሰላማዊ ትግሉ ይቀጥላል! ያውም ከተፈቀደለት!

በኢትዮጵያ የቅርብ ጊዜ ታሪክ አርበኞች ሳይቀሩ በሩ ተዘግቶባቸው ለደጅ ጥናት እንደተዳረጉ አይተናል፤ መልኩን ለወጥ ቢያደርግም ደርግን ከተፋለሙት ውስጥ በአዲስ አበባና በአስመራ ወንበሮች ላይ ሲወጡ የተሸነፉት ወይ ለወያኔ ገብረው ሎሌነት ገቡ፤ ወይም በአሜሪካ መሽገው ያቅራራሉ፤ ዘመኑ እንዳለፈባቸውም ገና አልተረዱም።

አምስት፣ ሰላማዊ ትግልና የትጥቅ ትግል ሁለቱም ብርቱ ቃል ኪዳንን ይጠይቃሉ፤የቃል ኪዳናቸው ልዩነት አንዱ እስከሞት ለመታገል፣ ሌላው ደግሞ እስከመግደልና እስከመሞት ለመታገል መሆኑ ነው፤ ለሰላማዊው ትግል ከፍተኛ መንፈሳዊ ወኔ የሚያጎናጽፈው ለመግደል ያለው ተቃውሞ ነው፤ ሕይወትን ለማልማት ሕይወትን መቅጠፍ የአስተሳሰብም የመንፈስም ጉድፍ ያለበት ሥራ ነው።

የሰላማዊ ትግል ዋናውና ቀጥተኛው ተልእኮ ሕዝብን ለሥልጣን ባለቤትነት ማብቃት ነው፤ ሥልጣንን ለመያዝ አይደለም፤ ስለዚህም ኢላማው ሕዝብ ነው፤ በሥልጣን ወንበሩ ላይ ያሉት የሰላማዊ ትግሉን የሚቃወሙት በሕዝብ ዘንድ ተሰሚነትና ተቀባይነት እንዳያገኝ ለማድረግ ነው፤ ሰላማዊ ትግሉ የሚያተኩረው በሕዝቡ ጆሮ፣ አእምሮና ልብ ላይ ነው፤ አገዛዙ በበኩሉ ጸጥ-ለጥ ብሎ የሚገዛለት ሕዝብ እውቀቱ ዳብሮ፣ መብቶቹን ሁሉ ተገንዝቦ፣ በሕግ ለሕግ እንጂ ለሰው አልገዛም በማለት ልቡ እንዳይሸፍት አፈናውንና ማነቆውን በማጠናከር እያደነቆረ ለመግዛት ይፈልጋል፤ የሰብአዊ መብቶችን የሚያስተምሩና በአገዛዙ አካላት የሚፈጸሙትን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን የሚያጋልጡ ድርጅቶችን ማዳከም ወይም ማጥፋት ለአገዛዙ አስፈላጊ የሚሆነው ለዚህ ነው፤ ኢሳት የሚባለው የቴሌቪዥንና የራድዮ ፐሮግራም ለወያኔ የውስጥ እግር እሳት የሆነበት ለዚህ ነው፡፡ በሰውነት ደረጃ ሕዝቡ መብቶቹን ሁሉ እንዲያውቅና እንዲረዳ ማድረግ፣

በዜግነት ደረጃ ሕዝቡ ለሥልጣን የሚያበቃውን የዜግነትና የፖሊቲካ መብቶች እንዲያውቅና እንዲረዳ ማድረግ፣ ሕዝቡ የሰውነትና የዜግነት መብቶቹን ተገንዝቦ በአገዛዝ ስር አልተዳደርም የማለት መንፈሳዊ እምቢተኛነት እንዲያድርበት ማድረግ፣ በግልጽ ጭቆናን የሚጠላና ለመብቶቹና ለነጻነቱ በቆራጥነት የሚቆም ሕዝብ እንዲፈጠር ማበረታታት፣ መብቶቹንና የሥልጣን ባለቤትነቱን የተረዳና ከጭቆና ጋር የተጣላ ሕዝብ በፖሊቲካ መስመር ቡድኖችን እየፈጠረ እንዲደራጅ ማድረግ፣ ያወቀና የነቃ፣ በፖሊቲካ መስመር የተደራጀና ማናቸውንም ዓይነት ጭቆና የሚጠላ ሕዝብ ለማንም ጉልበተኛ የማይንበረከክ ሕዝባዊ ኃይል እንዲሆን መጣር፣

የትጥቅ ትግል ዋናውና ቀጥተኛው ተልእኮ በሥልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ አውርዶ ወንበሩን ለራሱ ለመውሰድ ነው፤ ይህንን ሲያደርግ ሕዝቡን ወደጎን ትቶ ወይም ዘልሎ ነው፤ ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ በጠመንጃ ሥልጣን የሚይዙ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥልጣኑን ለሕዝብ እናስረክባለን፤ ትክክለኛ ምርጫ እናካሂዳለን በማለት ሕዝቡን በተስፋና በጠመንጃ ይዞ ነው፤ ነገር ግን ሥልጣንን ሕዝብ ለፈቀደው አስረክበው ከቤተ መንግሥት ሲወጡ አናይም፤ ሲሸሹ ወይም ሬሳቸው ሲወጣ እንጂ።

ብዙውን ጊዜ የማይታሰብ ወይም ብዙዎች የሚዘነጉት የሁለቱ ትግሎች የገንዘብ ወጪ በጣም ከፍተኛ ልዩነት ያለው መሆኑን ነው፤ ሰላማዊ ትግል በሕይወትም፣ በንብረትም፣ በመሣሪያም በዝግጅትም የሚያስከፍለው ዋጋ ከትጥቅ ትግል ጋር ሲወዳደር በጣም አነስተኛ ነው።

ስለዚህም በሁለቱ በተለያዩ ስልቶች አራማጆች መሀከል የሚደረግ ክርክር ምን ዓይነት ነው? የሰላማዊው የመጀመሪያ ደረጃ ኢላማው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው፤ የትጥቅ ትግል የመጀመሪያ ደረጃ ኢላማው የወያኔ አገዛዝ ነው፤ በሌላ አነጋገር በሰላማዊ ትግል ሕዝቡ በሰላማዊ ትግል ትንሽም ቢሆን የነጻነትን አድማስ ለማስፋት እንዲችል ድፍረትን በማስተማር በኩል የማይናቅ አስተዋጽኦ ቢያደርግም አገዛዙን የመነቅነቅ ኃይል ገና አላዳበረም፤ አንድም ውጤት አላሳየም፤ የትጥቅ ትግሉ ከፉከራና ከሽለላ እስካሁንም አልወጣም፤ የሰላማዊ ትግል ዓላማ ሕዝቡ መብቶቹን እንዲያውቅ ለማንቃትና ለመብቶቹ እንዲታገል የሚያስችለውን ብቃት ለማስጨበጥ ነው፤ ስለዚህም ዘዴው በሕዝቡ ላይ ነው፤ የትጥቅ ትግሉ ዘዴ አገዛዙን በጉልበት ገልብጦ በዚያው ባልተለወጠ ሕዝብ ላይ ሌላ አገዛዝ ለመመሥረት ነው።

በኢትዮጵያ ለውጥ እናመጣለን የሚሉ ሁሉ የቆሙበትንና የቆሙለትን ዓላማና ዘዴ በግልጽ ተገንዝበው ካልተሰለፉ በተንፈራጠጠ አስተሳሰብ የተባበረ ተግባር ሊገኝ አይችልም።

EMF

Image

Image

ምንሊክ ሳልሳዊ፦በተመሳሳይ ቀን የወያነ ባለስልጣኖች አለማየሁ አቶምሳን በሞት ሲነጠቁ የሻእቢያ ባለስልጣኖች ደግሞ ከፍተኛ የጦር አዛዣቸውን እና ታጋይ መጀር ጀነራል ገብረዝገር “ዉጩ” አንደማሪያምን በሞት ተነጥቋል።

አቶ አለማየሁ በባንኮክ በከፍተኛ ውጪ ሲታከሙ የሞቱ ሲሆን የሻ እቢያው ጀነራል ግን በአስመራ ከተማ በህክምና ሲረዱ ቆይተው አርፈዋል። አቶ አለማየሁ አቶምሳ ከሕወሓት ሰራሹ ኦሕደድ ጋር ተቀላቅለው ታጋይ የነበሩ(ማረጋገጫ አልተገኘም) ሲሆን ጀነራል ገረዝገር ሻ እቢያ ከደርግ ጋር ባደረገው ጦርነት ከ1971 ጀምሮ የተሳተፉ ታጋይ እንደነበሩ ከአስመራ የወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ። ምንሊክ ሳልሳዊ

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በ1993 የኢሕአዴግ ዋና መሠረት የሚባለዉ ሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ሕወሐት) ለሁለት ሲገመስ ግን የአንጋፋዉ ፖለቲከኛ የኢሕአዴግነት ጀንበር ስታዘቀዝቅ-የወጣቱ ካድሬ የኢሕአዴግ የፖለቲከኛነት ጀምበር ባንፃሩ ደመቀች።አቶ አለማየሁ የያኔዉን ጠቅላይ ሚንስትር የአቶ መለስን ልዩ ትኩረት እና እንክብካቤም አገኙ።

ኦስካር ፒስቶሪየስ የተባለው ደቡብ አፍሪቃዊ የአካል ጉዳተኛ ታዋቂ አትሌት አምና «ቅዱስ ቫለታይን» በተሰኘው ዕለት ፈቅረኛውን ሌባ እቤቱ የገባ ስለመሰለው ተኮሶ በስህተተ ገደላት ከተባለ ወዲህ፣ ሰሞኑን የችሎት ሂደት ከተጀመረ ዛሬ 4 ኛ ቀኑን ይዟል። መገናኛ ብዙኀን

አቶ አለምነው መኮንን በአማራው ህዝብ ላይ ያዘነቡትን ጸያፍ ስድብ ተከትሎ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የገባው ብአዴን፣ በክልሉ ፕሬዚዳንት በአቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ በራሳቸው በአቶ አለምነው መኮንን እንዲሁም በብአዴን ሊቀመንበርና በምክትል ጠ/ሚንስትር ደመቀ መኮንን አማካኝነት መግለጫ ቢሰጠም፣ ህዝቡን ለማሳመን ባለመቻላቸው፣ በወቅቱ በስብሰባው ላይ የተገኙ ጋዜጠኞችና ሌሎች ተወያዮች ቀርበው አቶ አለምነው አልተናገሩም እያሉ እንዲያስተባብሉ እየተደረገ ነው።

ከአስተማማኝ የደህንነት ምንጮች በተገኘው መረጃ መሰረት ደግሞ መረጃውን ያቀበሉትን ሰዎች ለማወቅ በወቅቱ የነበሩትን ጋዜጠኞች፣ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊዎችና የደህንነት ሰራተኞች ስልክ በመጥለፍ ተጨማሪ ክትትል እያደረጉ ነው። ይሁን እንጅ መረጃው አስቀድሞ የደረሳቸው የደህንነት ሰዎች ማንኛውንም በስልክ የሚያደርጉትን ግንኙነት በማቆማቸው የተፈለገው ውጤት ሊገኝ ባለመቻሉ ተጨማሪ ራስ ምታት መፍጠሩ ታውቋል።አቶ ደመቀ መኮንን ተቃዋሚዎች ልማቱን ለማደናቀፍ የፈጠሩት የኮምፒዩተር ቅንብር ነው ቢሉም የብአዴን አባላት ሳይቀሩ በሊቀመንበሩ ንግግር መበሳጨታቸውን ተናግረዋል። በሚቀጥለው አርብ በሚደረገው የአማራ ክልል ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ጉዳዩ ይነሳል ተብሎ ይጠበቃል።

አንድነትና መኢአድ በባህርዳር ያደረጉት የተቃውሞ ሰልፍና ለተቃውሞ የወጣው ህዝብ ብዛት ያስደነገጣቸው የብአዴን አንዳንድtአመራሮችና አባላት፣ አቶ አለምነው በይፋ ህዝቡን ይቅርታ ይጠይቁና ይህ ምእራፍ ይዘጋ በማለት እየጠየቁ ሲሆን፣ ዋናዎቹ አመራሮች ግን ጉዳዩ የአንድ ሰሞን ጫጫታ ከመሆን አይዘልም በማለት የሌሎችን አስተያየቶች ሊቀበሉ ፈቃደኞች አልሆኑም።

በማዕከላይ አፍሪቃ ሬፓብሊክ ውስጥ ራሱን ፀረ ባላካ(ቆንጨራ) ብሎ የሚጠራ የክርስትያኖች ቡድን አባላት በሙሥሊሞች፣ የቀድሞ የሴሌካ ዓማፅያን ደግሞ በክርስትያኖች ላይ በሚሰነዝሩት ጥቃት ዜጎች በየቀኑ ይገደላሉ።

የተማረ ወይም የእውቀት ባለቤት እንደሆነ የሚነገርለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ክፍል ከወያኔ ጋር የሚደረገው ትግል ሰላማዊ ይሁን ወይስ በትጥቅ ትግል የሚለውን የጦፈ ክርክር ሲያደርግ ሃያ ሁለት ዓመታት ሆነው፤ ዳኛ የሌለበት ክርክር ስለሆነ የመደማመጥ ግዴታ ታይቶበት አይታወቅም፤ ስለዚህም በሁለቱ መሀከል ያለው ልዩነት ግልጽ ሆኖ አያውቅም፤ አንድ፣ ከሁሉ በፊት ሰላማዊ ትግል በሀሳብ ደረጃ መሆኑንና የትጥቅ ትግል ደግሞ በተግባር መሆኑን […]

አንድ ወዳጅ አለኝ፡፡ የኢትዮጵያ ጉዳይ የሚያብሰከስከው፡፡ ሯጮቻችን ሲያሸንፉ፣ ተጨዋቾቻችን ድል ሲያደርጉ፣ ስለ ኢትዮጵያ መልካም ነገር ሲሰማና ሲነገር፣ በሀገሩ ላይ ልማትና ዕድገት ሲታይ፣ አንዳች የሆነ ሀገራዊ ለውጥ ሲታይ፣ ይፈነድቃል፤ መልክዐ ገጹ ይፈካል፤ ደስታው ከልክ አልፎ ጣራ ይነካል፡፡ የሚያሳዝን፣ አንገት የሚያስደፋ፣ የሀገርን ስም የሚሰብር፣ ገጽዋን የሚያበላሽ ነገር ሲሰማና ሲያይ ደግሞ ከሥራ እንደተባረረ ሠራተኛ አንገቱን ይደፋል፤ የእናቱን መርዶ እንደ ሰማ ልጅ ዓይኑ ዕንባ ይሞላል፤ ከጨለማ እሥር ቤት እንደ ገባ እሥረኛ ፊቱ ከል ይለብሳል፤ ሲብሰከሰክ ሲብከነከን ውሎ ያድራል፡፡
አንድ ቀን ‹‹ለአንተ ግን ሀገር ማለት ምንድን ናት? ወይስ ያንተ ሀገር የተለየች ናት? ምን እንደዚህ ያብከነክንሃል?›› አልኩት፡፡

‹‹ታውቃለህ›› አለኝ ፊቱን በቀኝ መዳፉ እየሞዠለጠ፡፡ የጎፈረ ፀጉሩን ደግሞ በግራ ጣቶቹ ይልጋቸዋል፡፡ አጭርና ድንቡሼ ነው፡፡ ወግ ሲጀምር ‹ታውቃለህ› ማለት ይቀናዋል፡፡

‹‹ታውቃለህ፤ ሀገር ማለት ‹ሕመሜ› ማለት ናት›› አለኝ፡፡ ከንፈርና አፍንጫዬን አገናኚቼ በጆሮዬ በኩል ወሬውን ዋጥኩና ወደ ኋላዬ ለጠጥ አልኩ፡፡ ሰምቼው የማላውቀው ትርጓሜ ነው፡፡ ‹‹ሀገር ማለት ሕመሜ ነው››፡፡ ይህንን ሳሰላስል ‹‹ሕመም ያልኩህ እንዳይመስልህ፣ ‹ሕመሜ› ነው ያልኩህ›› አለኝ፡፡

‹‹ሕመምና ሕመሜ፣ ምን ልዩነት አላቸው››

‹‹ዘፋኞችና አንጎራጓሪዎች በጣም የሚወዱትን ሰው ‹ሕመሜ› እያሉ ሲዘፍኑለት ሰምተህ አታውቅም››

‹‹ዐውቃለሁ፡፡ ታድያ ሀገርና ያ ምን ና ምን ናቸው››

‹‹የጆሮ ጉትቻ ያንገት ሐብል ናቸው – አልልህም መቼም›› አለኝ፡፡

‹‹ሕመሜ እያሉ የሚዘፍኑትኮ ስለሚወዱት ነገር ነው፡፡ እያለቀሱ አይምሰልህ፤ ሙሾ እያወረዱም አይደለም፤ የኀዘን እንጉርጉሮ እያዘነቡም አይደለም፡፡ ደስ ብሏቸው እየዘፈኑ ነው፡፡ እስክስታ እየወረዱ የሚዘፍኑት ግን ‹ሕመሜ› እያሉ ነው፡፡ የሚወዱትን፣ ሊያገኙት የሚፈልጉትን፣ እንዲያጡት የማይሹትን፣ መልካሙን ነገር ሁሉ የሚመኙለትን፤ ልቤ፣ አንጀቴ፣ ኩላሊቴ፣ ዓይኔ፣ ሆዴ፣ ነፍሴ የሚሉትን፤ ሞትም አይለየንም፣ ካንተ ውጭ ሌላ አልሻም፣ ሌላው ሁሉ ሰው አይመስለኝም፣ የሚሉለትን ፍቅረኛቸውን ‹ሕመሜ› እያሉ ይዘፍኑለታል፡፡

‹‹ አየህ ይህ ፍቅራቸው ሕመም ያለው ፍቅር ነው፡፡ ፍቅር ብቻ አይደለም፡፡ ሰናፍጭ ነው ያድናል፣ ግን ይሰነፍጣል፤ ሚጥሚጣ ነው ደስ ይላል፣ ግን ያቃጥላል፤ መርፌ ነው ይፈውሳል፣ ግን ያማል፤ ፈረስ ነው ይጋልባል፣ ግን ይገለብጣል፤ የሱፍ አበባ ነው ይመስጣል፣ ግን በእሾህ ተከብቧል፡፡ ውስጡ ደስ የሚል ሕመም አለበት፡፡ ደስታ ነው ብለህ እፎይ እንዳትል ሕመሙ እንደ ፍልስጣ ጎን ጎንህን ይወጋሃል፤ ሕመም ነው ብለህ እንዳትተወው ደስታው እንደ ወይን ጠጅ ‹እስኩ ድግሙ ድግሙ› ያሰኝሃል፡፡ ለዚህ ነው ‹ሕመሜ› እያልክ የምትዘፍንለት፡፡ የሚዘፈንለት ሕመም አይተህ ታውቃለህ? ሕመምን ይታከሙታል እንጂ ይዘፍኑለታል እንዴ? ሕመምን ያስታግሡታል እንጂ ያዜሙለታል እንዴ? እንዲያ ነው የምልህ፡፡

‹‹እና ሀገር እንዴት ነው ‹ሕመሜ› የምትሆነው?›› አልኩት ፍልስፍናው ደስ ብሎኝ፡፡ በጎድጓዳ መንገድ እንደሚሄድ ገልባጭ መኪና ወደ ግራና ወደ ቀኝ ወዝወዝ ብዬ ተስተካከልኩ፡፡

‹‹ሀገርማ ደንበኛዋ ‹ሕመሜ› ናት፡፡ ሀገር ብለህ ስታስብ ጤናና ሕመም ነው የሚሰማህ፡፡ የምትኮራበት፣ ምነው በዚያ ዘመን በኖርኩ ብለህ የምትመኝበት፣ ስታየውና ስትሰማው ደምህ የሚሞቅበት፣ ስታስበውና ስትናገረው ኩራትህ የሚጨምርበት ነገር አላት ሀገር፡፡ ምን እንደሆነ የማታውቀው እንዲሁ ፍቅር የምታስይዝህ ነገር አላት ሀገር፡፡ ታስጨፍርሃለች፣ ታስቦርቅሃለች፣ ታስዘልልሃለች ሀገር፡፡ የትም ቦታ ሆነህ ስሟን ስትሰማው ልብህን ቀጥ የሚያደርግ ነገር አላት ሀገር፡፡ ሙትልኝ ሙትልኝ፣ ድማልኝ ድመልኝ፣ ተሠዋ፣ተሠዋ የሚያሰኝ ኃይል አላት ሀገር፡፡ ምንም ጥቅም ሳታገኝ፣ ምንም ነገር ላንተ ሳይደርስህ፣ የሞተላት ቀርቶ የገደላት እየበላ እንኳን ቢሆን፤ ሞኝ ነሽ ተላላ እያል እየዘፈንክላትም ቢሆን፣ ላንዱ በጭልፋ ላንዱ በአካፋ እየሰጠች እንኳን ቢሆን፤ አንዱ እንገሯን አንዱ አሬራዋን እየጠጣም ቢሆን፤ ላንዱ ቅቤ ላንዱ ዝቃቅቤ እየሰጠችውም ቢሆን – ግን በፍቅር እንድትሞትላት የሚያደርግ ኃይል አላት ሀገር፡፡ እንዳትቀየማት፣ ቂም እንዳትይዝባት፣ እንዲሁ ይቅር እንድትላት የሚያደርግ ኃይል አላት ሀገር፡፡

‹‹ደግሞ ገልብጠህ ስታያት ሀገር ሕመም ናት፡፡ ቀዶ ጥገና አድርገህ የማታወጣት፣ ቆርጠህ የማትገላገላት፤ ታክመህ የማትድናት፤ በአበሻ መድኃኒት ነቅለህ የማትጥላት፤ ኮሶ ወስደህ የማታሽራት፤ ሕመምህ ናት ሀገር፡፡ ምነው እዚህ ሀገር ባልተደረገ የምትለው ስንት ታሪክ አላት፤ ምነው በዜጋሽ ላይ እንዲህ ታደርጊያለሽ ብለህ የምታዝንባት ስንት ግፍ አለባት ሀገር፤ ምነው እንደ እንጀራ እናት ታዳያለሽ ብለህ አንጀትህ እርር የሚልባት ስንት አድሎ አላት ሀገር፤ አንዱ

ሀገሬ ኢትዮጵያ ምድራዊት ገነት

አደላድለሽኛል በሥልጣንና በሀብት፣

ብሎ ሲያወድሳት፣ አንተ ግን –

ሀገሬ ኢትዮጵያ ምድራዊት ገነት

እስኪ ፈልጊልኝ የሚከራይ ቤት፣

 ትላታለህ፤

ለሚያሥረው ሀገር ናት፣ ለታሣሪው ሀገር፤ ለገዳይ ሀገር ናት ለሟቹም ሰው ሀገር፤ ለአሳዳጅ ሀገር ናት ለተሰዳጅ ሀገር፡፡

‹‹ ‹ሌቦ› እያሉ እንደመዝፈን ያለ፡፡ አሁን ለሌባ ምን ይዘፈንለታል፡፡ ሀገርህ ሰጭ፣ ለጋስ፣ ቸር፣ ደግ፣ ብቻ አይደለችም፡፡ ሀገርህ ሌቦም ናት፡፡ የስንቱን ሕጻን፣ ወጣት፣ ሽማግሌ፣ ልጃገረድ፣ እናት፣ ባልቴት ሕይወት ቀጥፋ ነው እዚህ የደረሰችው፡፡ ግን ሌባ አይደለችም ‹‹ሌቦ›› ናት፡፡ የሚዘፈንላት ሌባ ማለት ነው፡፡ ‹‹ያዛት፣ ያዛት፣ በላት፣ በላት፣ ኡኡኡ›› ብለህ በፖሊስ የምታስይዛት፣ በጎረምሳ የምታስደበድባት ሌባ አይደለችም፡፡የምትዘፍንላት ‹ሌቦ››፡፡

አሣሪ ሆነህ እንደወድካት ሁሉ ታሣሪም ሆነህ ትወዳታለህ፣ አሳዳጅ ሆነህ እንደወደድካት ሁሉ ተሳዳጅ ሆነህም ትወዳታለህ፤ ቀማኛ ሆነህ እንደወደድካት ሁሉ ተቀምተህም ትወዳታለህ፤ተምረህ እንደወደድካት ሁሉ ደንቁረህም ትወዳታልህ፡፡ ሀገር ማለት ይህቺ ናት፡፡ ሀገር ‹‹ሕመሜ›› ናት፡፡ ሀገር አደዋ አላት፤ ሀገር ማይጨው አላት፡፡ የአኩስም ሐውልት አላት፣ የቆሻሻ ክምርም አላት፤ መንገድ ሠሪም አላት፣ መንገድ ላይ የሚሸናም አላት፤ ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆነ የስልክ ታሪክ አላት፣ ከአፍሪካ መጨረሻ የሆነ የስልክ ኔትወርክም አላት፤ ታሪክ ትሠራለች፣ ታሪክም ታፈርሳለች፤ ቅርስ ትሠራለች፣ ቅርስም ታፈርሳለች፡፡ ሀገርህ ይህቺ ናት፡፡

‹‹ርግፍ አድርጌ ልተዋት ብትል እሺ አትልህም፡፡ ለቅቀሃት በመሄድ፣ ጥለሃት በመጥፋት፣ ዜግነት ቀይረህ፣ ቋንቋህን ለውጠህ እንኳን እሺ ብላ አትተውህም፡፡ ሞተህ እንኳን አትለቅህም፣ አስከሬን ታስጭንሃለች፡፡ ደግሞ በዚያ ወገን ዝም ብዬ ብቻ ልውደድሽ፤ ዝም ብዬ ብቻ ላድንቅሽ ስትላት ደግሞ እሺ አትልህም፡፡ አንዳች ሕመም ነገር አላት፡፡ ያለህ አማራጭ ‹‹ሕመሜ›› እያልክ መዝፈን ነው፡፡ በሳቅህ ውስጥ ልቅሶ፣ በልቅሶም ውስጥ ሳቅ ትቀላቅልብሃለች፡፡ የጠቦቱን ሥጋ ከመራራ ቅጠል ጋር ታበላሃለች፡፡

‹‹ለእኔ ሀገር ማለት ይህቺ ነች፡፡ ‹‹ሕመሜ›› ››

ዝም ብዬ አየሁት፡፡

 © ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግስት ከፍተኛ የፕሮቶኮል ዋና ሹም ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ በላይ ግርማይ ከስልጣን መነሳታቸውን የቅርብ ምንጮች ገለፁ። የሕወሐት አባል የሆኑትና ከ1990ዓ.ም ጀምሮ የጠ/ሚ/ሩ እንዲሁም የፕሬዝዳንቱ ፕሮቶኮል ሹም ሆነው በአቶ መለስ ዜናዊ ተሾመው ሲያገልግሉ መቆየታቸውን ያስታወቁት ምንጮች የአቶ በላይ ቢሮ በውጭ ጉዳይ ሚ/ር ውስጥ እንደነበረ ጠቁመዋል። የቀድሞ ፕ/ት ነጋሶ ጊዳዳ፣ የጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ እንዲሁም የፕ/ት ግርማ […]

በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ወላይታ ሶዶ 18 ሰዎች ካለፍርድ ቤት ትእዛዝ ጨለማ ቤት ታስረዋል::
“ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገር ድረስ መጥታችሁ ቅስቀሳ ለማካሄድ መሞከራችሁ በጣም ደፋሮች ናችሁ! ከዚህ በኋላም ወላይታ ላይ እንዲህ አይነት ነገር እንዳትሞክሩ!” የወላይታ ሶዶ ፖሊስ ማስፈራሪያ ለሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች

ምንሊክ ሳልሳዊ:- የጠቅላይ ሚኒስትር ተብየው ሃይለማርያም ደሳለኝ ምንጭ ናት በምትባለው በወላይታ ሶዶ ከከፍተኛ ደረጃ የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች እየተፈጸሙ መሆኑን ነዋሪዎች አጋለጡ::ነዋሪዎቹ እንዳሉት ካለምንም ምክንያት የሚያፍኑ የሚያስሩ የሚገርፉ እና ከፍትህ እና ፍርድ ቤት በላይ የሆኑ ትናንሽ ቡድናዊ መንግስታት እና እንዳሻቸው በህዝቡ ላይ የሚፈነጩ ካድሬዎች የወላይታን ህዝብ በስቃይ እና በሰቆቃ ውስጥ እያኖሩት መሆኑን ነዋሪዎቹ አማረው ተናግረዋል::

ባለፈው ሳምንታት ውስጥ እንኳን ከተያዙት የወላይታ ነዋሪዎች መካከል አቶ አየለ ሃሚሶ የሚባል የከተማውን የፍርድ ቤቶች ፕሬዚዳንት እና ዳኛ ደብድባችኋል ተብለው ካለምንም ማስረጃ 18 ሰዎች ተይዘው ላለፉት አስረ አምስት ቀናት ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ በጨለማ ቤት ታስረው ይገኛሉ::እነዚህ እስረኞች የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ሌሊሼ ኦላ እና ግብረበሮቹ ከፍተኛ ድብደባ እየተፈጸመባቸው ሲሆን እንዲሁም ደብዳቢዎቹን ጭናችሁ አድርስቹሃል የተባሉ የባጃጅ ሹፌሮች በቁጥጥር ስር ውለው እየተገረፉ መሆኑን በስቃይ ላይ ያሉት እስረኞች ተናግረዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ በህጋዊ መንገድ የተመዘገበውን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን በሽብርተኛነት እና ህገወጥ የጦር መሳሪያ ይዛቹሃል በማለት እንግልት እና መንግስታዊ ሽብር በከተማው የፖሊስ አዛዥ እና ግብረአበሮቻቸው የተፈጸመባቸው ሲሆን በሻንጣዎቻቸው ላይ ፍተሻ አድርገው ምንም የጦር መሳሪያ እንዳላገኙ እና “ወላይታ ለመግባት ምንም አይነት ፈቃድ ከማንም አንጠብቅም ምክንያቱም አገራችን ነው” በማለት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ቢመልሱም “ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገር ድረስ መጥታችሁ ቅስቀሳ ለማካሄድ መሞከራችሁ በጣም ደፋሮች ናችሁ! ከዚህ በኋላም ወላይታ ላይ እንዲህ አይነት ነገር እንዳትሞክሩ!” የሚል ዛቻና ማስፈራሪያ
አድርሰውባቸዋል::

ዛሬ የካቲት 26 2006 “አሁን መሄድ ትችላላችሁ” ብለው ከአዲስ አበባ የሄዱትን ሶስቱን የሰማዊ ፓረቲ አመራሮች 1ኛ/ አቶ ጌታነህ ባልቻ 2ኛ/ አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ 3ኛ/ አቶ ይሁን አለሙ ሲለቁዋቸው ከሀዲያ ጀምረው የሰሯቸውን ስራዎች የያዙበትን ሰነዶች፤ቃለ ጉባኤዎች እና ሁለቱን የወላይታ ተወካዮችን /አስተባባሪዎችን/ እስካሁን ያለቀቋቸው ሲሆን ስለ ንበረታችሁ የምናውቀው ነገር የለም በማለታቸው ንብረቶቻቸውን ሳይረከቡ ወደ አርባምንጭ መንቀሳቀሳቸው ታውቋል::

የታሰሩት የሰማያዊ ፓረቲ የወላይታ አስተባሪዎች ባይፈቱም፤ የተወሰዱባቸው ንብረቶች ባይመለሱላቸወም ሰራው መቀጠል ሰላለበት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ወደ አርባ-ምንጭ ተንቀሳቅሰዋል፡፡
ነገ የአርባ ምንጭ ሰራቸውን እንዳጠናቀቁ ወደ ወላይታ ሶዶ ከትማ ተመልሰው የታሰሩትን የሶዶ ከተማ አስተባባሪዎችን ለማስፈታት ትግሉ የሚቀጥል ሲሆን ንበረታቸውንም የማስመለሰ ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ትላንትና የካቲት 25 2006 በሶዶ ከትማ ላይ ያደረጉዋቸው ሰበሰባዎች https://www.facebook.com/blueparty.ethi … =notify_me ይህንን ይመሰል ነበር፡፡ምንሊክ ሳልሳዊ

እስከዛሬ ብዙ ቀልዶችን ሰምቻለው አንደዚህ ግን ያዝናናኝ ቀልድ የለም አንድ የቀድሞ የግብጽ ጀነራል ኢትዮጵያ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታን የማታቆም ከሆነ እናፈነዳቸዋለን አሉ ለአንድ የቴሌቭዥን ጣቢያ በሰጡት ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ እንድታቆም ሶስት አማራጮች አሉ ብለዋል።

የቀድሞው የግብጽ ጀነራል በቀዳሚነት ያስቀመጡት አማራጭ በኢትዮጵያ ፣በሱዳን እና በግብጽ 20 ሚልዮን የሚደርስ የሙዝ እና የዛፍ ችግኝ በመትከል እና የዝናብ ሁኔታው እንዲስተካከል በማድረግ እና አማራጭ በመስጠት ኢትዮጵያ ግድቡን የምታቆምበትን መንገድ ማመቻቸት ነው ብለዋል።

ሁለተኛው አማራጭ የቀድሞ የግብጽ ንጉስ ሱልጣን አብዱል ሃሚድ የኢትዮጵያን አንድ ሶስተኛ መሬት ያስተዳድር ስለነበር ይህን መሬት አንዲሰጠን መጠየቅ ነው ያሉት የቀድሞ ጀነራል የዩጋንዳ አንድ ሶስተኛ መሬትም የግብጽ ንብረት እንደሆነ ተናግረዋል።

ይህንንም ለማድረግ ህጋዊ እርምጃ ለመውሰድ እንደተዘጋጁ ነው የሚናገሩት። ሁለቱ አማራጮች የማይሰሩ ከሆነ ግን « በመሬታችን መሞት የለበንም መሞት ካለብንም ግድባቸው ስር ነው መሞት ያለብን ስለዚህ እዛው ሄደን ልንፈነዳቸው ይገባል በመሆኑም ኢትዮጵያ ከሶስቱ አማራጮች አንዱን መምረጥ አለባት» ብለዋል።
እንኳንስ ለሙቅ ለገንፎም አልደነግጥ አለ የሃገሬ ሰው!! አፈነዳለሁ በሎ ፈነድቶ የአሞራ እራት መሆን እንዳለ አያውቁም እንዴ ጀነራል? ቂቂቂ ቂቂቂ ቂቂቂ ቂቂቂ በነገራችን ላይ ጀነራል ሶስቱም የኛ ምርጫ አይደሉም የኛምርጫ ወንዛችንን መገደብ ነው…እኔ የሚገርመኝ ኧረ ግብፅ በጣም አበዛችው
አንድ ሰሞን ክቡር ጠ/ሚር መለስ ዜናዊ እንዲህ ሲሉ ሰምቼ ነበር ” ለሚያስፈራራክ ሰው መፍትሄው አለመፍራት ነው ” ሳስበው ሳስበው ይህ ሰው ጅል እንጂ ጄነራል አይደለም!! ቂቂቂ ቂቂቂ ደስ የሚለው ነገር ጅነራሉም ሆኑ አንዋር ሳዳት አንድ አይነት እምነት አላቸው እዚያው ሄደን እንሙት !! እኛ መግደል መገዳደል ሰልችቶናል ሁላችንም በህይወት እንኑር ነው አቋማችን እግድህ የኛ መሬት ለባዐዳን መቀበርያ ይመች ይመስል የአሁኑ ትውልድም እንደ ድርቡሽ እዚያው እንሙት ቢያንስ እንደ ጣልያኖቹ የገዳዮችና የሟቾች ሃውልት በኢትዮጵያ ምድር ይኑረን አጥንታችን በኢትዮጵያ መሬት ካልተቀበረ የሞትን አይመስለንም ካሉ ባንወደውም ባንፈልገውም ሙትን ለመቅበር ከሟቹ ይልቅ ጉልበትና አቅም ይጠይቃልና ለዚያው መዘጋጀት ነው አንድም ሞት የናፈቃቸው ግብጻውያንን እዚየው ጣሕሪር አደባባይ ላይ ሞታቸው እንድከናወን መጸለይ ነው ካልሆን ግን ምን ይደረግ ህልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደር ? ይስሙኝ እማ ጀኔራል በአባይ የመጣ እንኳን የኢትዮዻያ ወጣት እማማ አያቴ ትዘምታለች.ቂቂቂ እንዳዉም አረፈዳችሁ ቂቂቂቂቂቂ ቂቂቂ
ጀነራል እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ”ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው። ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥” ይላል እግዚአብሔር።
ትንቢተ ኢሳይያስ 19;1-10 ላይ
ስለ ግብጽ የተነገረ ሸክም። እነሆ፥ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና እይበረረ ወደ ግብጽ ይመጣል፤ የግብጽም ጣዖታት በፊቱ ይርዳሉ፥ የግብጽም ልብ በውስጥዋ ይቀልጣል።
2፤ ግብጻውያንን በግብጻውያን ላይ አስነሣለሁ፤ ወንድምም ወንድሙን፥ ሰውም ባልንጀራውን፥ ከተማም ከተማን፥ መንግሥትም መንግሥትን ይወጋል።
3፤ የግብጽም መንፈስ በውስጥዋ ባዶ ይሆናል፥ ምክራቸውንም አጠፋለሁ፤ እነርሱም ጣዖቶቻቸውን በድግምት የሚጠነቍሉትንም መናፍስት ጠሪዎቻቸውንም ጠንቋዮቻቸውንም ይጠይቃሉ።
4፤ ግብጻውያንንም በጨካኝ ጌታ እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ፤ ጨካኝ ንጉሥም ይገዛቸዋል ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።
5፤ ውኆችም ከባሕር ይደርቃሉ፥ ወንዙም ያንሳል ደረቅም ይሆናል።
6፤ ወንዞቹም ይገማሉ፥ የግብጽም መስኖች ያንሳሉ ይደርቃሉም፤ ደንገልና ቄጤማ ይጠወልጋሉ።
7፤ በዓባይ ወንዝ ዳር ያለው መስክ በዓባይም ወንዝ አጠገብ የተዘራ እርሻ ሁሉ ይደርቃል፥ ይበተንማል፥ አይገኝምም።
8፤ ዓሣ አጥማጆቹ ያዝናሉ፥ በዓባይም ወንዝ መቃጥን የሚጥሉት ሁሉ ያለቅሳሉ፥ በውኆችም ላይ መረብ የሚዘረጉት ይዝላሉ።
9፤ የተበጠረውንም የተልባ እግር የሚሠሩ፥ ነጩንም ልብስ የሚሠሩ ሸማኔዎች ያፍራሉ።
10፤ ደገፋዎችዋም ሁሉ ይሰባበራሉ፥ የደመወዘኞችም ነፍስ ትተክዛለች።

ይስሙኝ እማ ጀኔራል በነገራችን ላይ ይኼን ግድብ ማፈንዳት አይደለም መገላመጥ በነፍስ ያወራርዳል፡፡ግድቡ የኢህአዴግ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ነው፡፡ ኢጣሊያንን ያየ በእሳት አይጫወትም” አለች እማማ አያቴ . ቂቂቂ ቂቂቂ ቂቂቂ አይ አቅምን አለማወቅ ያሳዝናል የጦር መሳሪያ እስከ አፍንጫ መታጠቅ እንዲህ የሚያስፈነጭ መስሏቸው ከሆነ ከጣሊያን ይማሩ፡፡ጦርነት ሚጠይቀው ወኔና አላማ ነው ፡፡እንኳን ለግድባችን ….ይሞታል፡፡ታሪክ ጠይቁ የማን ልጆች እንደሆንን የሚኒልክ እና የቴድሮሥ አንፈራም ነገርዬው ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ አይነት ነው ግድቡ ስር ለመሞት መጀመሪያ መድረስ ይጠይቃል፤ ማፈንዳቱ ሳይሻላችሁ አይቀርም? ግን ልታፈነዱ ስትመጡ ልትፈነዱ አንደምችሉ አስባችሁ ግቡ! አገሪቱ ኢትዮጵያ, ህዝቡ ደግሞ የአድዋ ባለ ታሪክ ጀግና አንደሆነ ለአፍታም አንዳትዘነጉ! ቀልደኞች ቂቂቂ!! ጋሸ ጀነራሉ ወግ ከወግነቱ አልፎ አያውቅም ሞያ በልብ ነው ካወራህ ይበቃህል ኢትዮጵያና ህዝቦችዋ ለጠላት የተንበረከኩበት ዘመን የለም የታሪክ አሻራውን ማየት ከፈለክ ሜዳውም ፈረሱም ይህው። ጋሸ ጀነራሉ እንደዚህ አይነት ቀልድ ግብፅም ጀመረች እኛ ማን እንደሆን አታቅም እንዴ? ካላወቀች ጣሊያንን ትጠይቅ! ጀግኖቹ ኢትዮዽያኖችነን!!! ከእሳት እንዴት ችላ ትጠጋለች!! እኛ እኮ ለሚጠሉን እሳት ነን ለሚወዱን ደግሞ ዉሀ ነን.. እ!

ስሙኝማ በነገራችን ላይ አረብ ሲባል የሻገተና የአስተሳሰብ ደኃ ነው፡፡ እንደልማዳችሁ እናፈነዳለን ብልችሁ ስትነሱ እራሳችሁ ላይ አፈንድታችሁ ታልቃላችሁ፡፡ አሁን የጨዋታው ህግ ተቀይሯል፤ እንኳንስ የኃይል እጥረት እያለብን ይቅርና ቢተረፈረፈንም ግድቡ አይቆምም ፡፡ ደግሞ እንዳይገርማችሁ ፤ ይህ ከአራቱ ግዶቦች የመጀመሪያው ነው 3ቱ በቅርብ ጊዜ በቅደም ተከተል ግንባታ ይጀመራል፡፡ ስለሆነም ውኃችን ነዳጃችን ነው ፡፡ ነዳጂ በነፃ አለ እንዴ??? በነገራችን ላይ ጀኔራል ሙዝ እና ችግኙም አሪፍ ሀሳብ ነው። ከግድቡ በኃላ ወደዛም እንዘምታለን ቂቂቂ ቂቂቂ በነገራችን ላይ ጀኔራል ይልቁንም ለብዙ ሺህ አመታት ያለከልካይ የአባይን ውሃ ተጠቅመዋል ስለዚህ ለኢትዮጵያ በርካታ በሊዮን ዶላር ሊከፍሉ ይገባቸዋል!!!!
አሁን ነው መበቀል አረብን እስካሁን በትንሽ ሳንቲም የአበሻን ጉልበት የበዘበዙበት ሳያሳቸው በዚም መጡ ይሄ ግድብ ክብራችንን ከፍ የሚደርግልን ነው በዛውም ልክ ግድቡ ላይ ጥቃት ደርሶ ማለባበስ በቁም እንደመሞት ነው ለአገራችን ክብር መንግስት ራሱን ሊዘጋጅበት እና በማንኛውም እንቅስቃሴ አፀፋዊ መልስ ሊሰጥ ይገባል የስካሁኑ ውርደት በአረቦች ይብቃ ካለበለዚያ ሀገርንም በማስደፈር እስካሁን ከነበሩት መንግስት ቀዳሚው የትውልድ ተወቃሽ መሆኑ ማይቀር ነው እናም መንግስት በሁሉም ነገር አፀፋዊ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆን ይገባል፡

ስሙኝማ ነገርዬው ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ አይነት ነው፡፡ ግብፆች ከድርድር ውጪ የጦርነት አማራጭ ያላቸው አይመስለኝም፡፡ የተያያዙት ተራ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ነው፡፡ ያው ማስፈራራት ነው፡፡ ቢሆንም በደካማ ጎናችን አይጠቀሙም ማለት አይታሰብም፡፡ የግብፅ ግብረሰናይ ድርጅቶችም ሆኑ ማናቸውም የግብፅ መሰረት ያላቸው የኢንቨስትመን ስራዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ካልተደረገ ሊጎዱን ይችላል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ብቻ ሊሰራ የሚችል ወታደራዊም ሲቪል ደህንነት ተቋም ሊመሰረት ይገባል፡፡ መስራት ከባድ ነው፡፡ ማፍረስ ቀላል ነው፡፡ የቁማር ጨዋታው ውጤት ግልጽ ስላይደለ መዘጋጀቱ አይከፋም፡፡ በድንበር አካባቢ ያለንን የፀጥታ አጠባበቅ ማጥበቅም ግድ ይለናል፡፡
ግድቡ ተዓምር ባያመጣልን እንኳ ግብፅ ለዘመናት ያፈራረሰችንን ማካካሻ ስለሚሆን ለእኔ ልዩ ትርጉም አለው፡፡ ለብዙ ላልተገለፁ ነገሮችም መሰረት ይሆናል፡፡ አይደለም 6ሺ 200 ሜጋ ዋትም ካመነጨ በድል አድራጊነት እንዳጠናቀቅን እቆጥራለሁ፡፡የግብፅን የውስጥ መተራመስ ፈጣሪ ለኛ ብሎ ያደረገው እንደሆነስ ማን ያውቃል! ባይሆን ኖሮ የሚተኙልን አይመስለኝም፡፡ በዚህ ምስቅልቅል ጊዜ ይህን ያህል ከተንፈራገጡ ደህና ቢሆኑ ውጤቱን ገምቱ…መንግስትም ለማናቻውም ማስፈራራት ተመጣጣኝ ምላሽ መስጠት ይኖርበታል፡፡ ግድ ነው፡፡
ይስሙኝ እማ ጀኔራል በትምቢቱ ኢሳያስ መዝ67:31 ኢትዮጵያ ላይ ጦርን እንዳታነሱ ትደቃላችሁ ብሏል።በደንብ ይወቁን ይምጡ ሙዝ እንዳሉ የርሳስ ሙዝ በልተው ይሄዳሉ።
ቂቂቂ ቂቂቂ
ህዝብ ሆይ ስማ እንደወርቅ የነጠረ እንደ ብር የነጣ ሀበሻዊ ማንነትህ በሙዝ ተቀይራል እና መሳሪያም ያለህ መሳሪያ ጀገሪያም ያለህ ጀገሪያ አንካሴም ያለህ አንካሴ እነኚህ የሌላችሁ ወኔአችሁን ይዛችሁ ወደ አባይ ውጡ ይህን ማድረግ ያልቻለ ሀበሻ ቢኖር እንጣላለን ማርያምን!!!!!!!
አሁንስ ትግስቴ እያለቀ ነዉ ያአባቴን ak-47 መሳሪያ ይዤ ልሸልል ነዉ ያበጠ ይፈንዳ ምነዉ ሸዋ
አረ ጎራው አረ ጎራው ንቡ ወለደና ቀፎውን ጨነቀው፣
ማር ብቻ መስሎታል መርዙን አላወቀው፣
የማን ዘር ነኝና ከማስ ተወልጄ
ሚኒልክ ያወረሰኝ ዛሬም አለ በጀ።
ዘራፍ ዘራፍ የማንን ሀገር ማን ይነካታል፣
ካለ ሀበሻ ያስከብራታል።
የማን ቤት ጠፍቶ የማን ሊበጅ፣
የአውሬ መውለጃ ይሆናል እንጂ።
ዘራፍ ዘራፍ!!! ዘራፍ!!! ዘራፈ!!
የምኒሊክ ልጅ ነኝ የበላይ የዛ ሳተና
ለጣልያንም ያልተኛ ቆራጡ ጀግና እኔነኝ ያለ ይሞክረኛ !!! ዘራፍ ዘራፍ!!!ተተተተተተተተተ ”ኢትዮጵያ ታበፅእ እደዊሀ ሀበ እግዚአብሄር
እንግዲ እነሱ በሚፈልጉት አማራጭ መሄድ ይችላሉ መብታቸው ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን ያለን አንድ እና አንድ ነው ያለን ያም የኃያላን ኃያል የነገስታት ንጉስ በረዶ የሚያዘንብ ፈርኦንን ከነሰራዊቱ በባህር የጣለ ድንቅ መካር እና ኃያል አምላክ ነው እሱም እጃችንን ዘርግተን ለምነን ከኛ ጋር ነው ስለዚህ ቀድመን አሸንፈናቸዋል
እኛስ እንሙት ችግር ብርቃችን አይደለምና መጪው ትውልድ ግን እኛ ያየነዉን ችግር እኛ ያለፍንበትን የድህነት ህይወት መቅመስ የለበትም ብሔር ሀይማኖት ሳይለየን ሁላችንም በአንድነት ለመጪው ትውልዳችን መስዋት ከፍለን ማለፍ አለብን ስም አይሞትም ታሪክም አይሞትም::እነሱ ያውሩ እኛ እንሰራለን ©2014 ነቆራ እና ሌሎችም ወጎች ከ Love on The way

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በዓለም ዙሪያ በሃይማኖትና በባህል ሳቢያ ቢራና ሌሎችም የአልኮል መጠጦች ከማይቀመሱባቸው ጥቂት አገሮች በስተቀር ፤ በአብዛኞቹ ፣ እንበል ፣ እዚህ ላይ በተለይ ቢራ፣ በቤት ፣ በባህላዊ ዘዴ ከሚጠመቀው አንስቶ ፣ በዘመናዊ ፋብሪካዎች፣ በገፍ ነው

የአሜሪካ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መስሪያ ቤት እ.ኤ.አ በ2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ ተፈፀሙ ያላቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ሪፖርት ተመልክተነዋል፡፡ በሪፖርቱ የተካተቱት የመብት ጥሰቶች አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ በተደጋጋሚ ያጋለጣቸው እና ከፍተኛ ትግል እያደረግንባቸው የሚገኙ አስከፊ ተግባራት እንደሆኑ ቢታወቅም የቆምንለት ዓላማ እና እየታገልነው ያለው ስርዓት በሌሎች ዘንድም ድርጊቱ የታወቀ መሆኑን ያረጋገጥንበት ነው፡፡ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በሪፖርቱ […]

“መፈክር በተሰማ ቁጥር መፈክሩን ተከትለን አንነጉድም” አቶ ጌታቸው ረዳ የጠቅላይ ሚኒሰትሩ ቃል አቀባይ የ2013 የስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት መውጣትን ተከትሎ ባለፉት አምስት ዓመታት ሲያወዛግቡ የነበሩት የፀረ-ሽብር፣ የመገናኛ ብዙሃን እና የበጎ አድራጎትና ማኅበራት (የሲቪል ማኅበረሰብ) ሕጎች ማወዛገባቸውን ቀጥለዋል። የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ መ/ቤት (ስቴት ዲፓርትመንት) በየዓመቱ በሚያወጣው ሪፖርት ላይ በሕጎቹ የሀገሪቱን ሕዝቦች ስብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ላይ ጫና እንደሚያደርጉ […]

‹‹የፀረ ሙስና አቋማቸው ራሳቸውን ከማስተዋወቅ ያለፈ ውጤት አላመጣም›› /ተቺዎች/ (ሰንደቅ፤ የካቲት ፳፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፍትሕ፣ ርትዕና እኩልነት የሞላባት፣ መልካም አስተዳደር የሰፈነባት ለማድረግ በዕለተ ሢመተ ፕትርክናቸው የተናገሩት ቃል ኹሉ እንደጸና መኾኑንና ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ከምእመናን ጋር በመኾን እንደሚያጠናክሩት ፓትርያርኩ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ተናገሩ፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ስድስተኛ …

Share:

ስለ ወቅቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውህደትና ትብብር በስፋት አትታለች

አድዋን ዘክራለች!

ለሱዳን ተላልፎ ሊሰጥ በታሰበው መሬት ህጋዊና ፖለቲካዊ ትንታኔዎች ተሰጥቶባታል

ኢትዮጵያ ለምን ወደ ኋላ እንደቀረች ተተንትኖባታል

ስለ አገራችን የምርጫ ፖለቲካና ሌሎች አገራዊ ጉዳዮችም አካትታለች
Neger Ethiopia Issue 2 In PDF

Share:

በመስክ ጉብኝት፣ አደረጃጀቶቻቸውን በማጠናከር ላይ የነበሩት ከአዲስ አበባ የሄዱት የሰማያዊ ፓርቲ ልዑካን ከአንድ ቀን እስር በኋላ ዛሬ ጠዋት ቢፈቱም የወላይታ ዞን የፓርቲው ተወካዮች ግን አሁንም ድረስ በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ የተፈቱት የፓርቲው አመራሮችም ቢሆን ቀጣይ መዳረሻቸው ወደሆነችው አርባ ምንጭ እንዳይንቀሳቀሱ ከመከልከላቸውም በተጨማሪ የስራ ሰነዶቻቸውን ጨምሮ ሌሎች ቁሳቁሶቻቸው በፖሊስ ቁጥጥር ስር በመሆናቸው ከመንቀሳቀስ እንዳገዳቸው በእስር ላይ የነበሩትና የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ብርሃኑ ተክለያሬድ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የልዑካን ቡድኑ ከወላይታ ሶዶ ወደ አርባ ምንጭ በማቅናት ላይ እያለ የከተማው ፖሊስ ‹‹በመሳሪያ ዝውውርና በሽብርተኝነት ጠርጥረናችኋል›› በሚል ከህዝብ ማመላለሻ መኪና አስወርዶ እንዳሰራቸው ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ ከታሰሩ በኋላ እንግልት የደረሰባቸው ሲሆን ‹‹ከምሽቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ አራት ሰዓት የፖሊስ አዛዦች ስራ ላይ ነን በሚል ባዶ ሜዳ ላይ ዝናብ ሲያስመቱን አምሽተዋል›› ብለዋል፡፡ በትናንትናው እለት ምግብና ጠያቂ መከልከላቸውን ነገረ ኢትዮጵያ መዘገቧ ይታወቃል፡፡
አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ የወላይታ ሶዶ ፖሊስ ለእስሩ እንደምክንያት ካነሳቸው ነገሮች መካከል ‹‹በጠቅላይ ሚኒስትሩ የትውልድ አገር ተቃውሞ የማይታሰብ ነው›› የሚል እንደሚገኝበት ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡ ለከተማው ፖሊስ ጣቢያ ማንነታችን ገልጸን ጉዳዩን ለማጣራት ያደረግነው ጥረት በአግባቡ ሊያነጋግሩን ባለመቻላቸው ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ የወላይታ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ለሊሼ ኦንን በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ማግኘት ብንችልም ጋዜጠኞች መሆናችንን ሲያውቁ ስብሰባ ውስጥ መሆናቸውን በመግለጽ መረጃ እንደማይሰጡን ገልጸውልናል፡፡ ይሁንና ለኢንስፔክተሩ በምንደውልበት ወቅት ኃላፊው ስብሰባ ላይ አለመሆናቸውንና በአቅራቢያቸው እንደሚገኙ የልዑካን ቡድኑ ገልጸውልናል፡፡

እኔ የምኖረው በአሜሪካ ነው። በአሜሪካ ሆኜ የአድዋን በዓል አከበርኩ። የኢትዮጵያዊያን ድረገፆችን እየተመላለስኩ ቃኘኋቸው። ሬዲዮኖችን አዳመጥኳቸው። የስልከ ልውውጦችንና የእንግዶችን ሃሳቦች ተከታተልኩ። ስደሰት፣ ሳዝን፣ በጣም ስደሰትና በጣም ሳዝን ዋልኩ። ሲመሽና የምኝታ ሰዓቴ ቀርቦ ባልጋዬ ላይ ስጋደም፤ እንቅልፍ ቶሎ አልወስድህ አለኝ። መገለባበጡ ለውጥ አላመጣ ሲል በሃሳብ መዋተቱን ተያያዝኩት። አድዋ ለኔ ምንድን ነው? የሚለው ጥያቄ ከዕለቱ ወደላይና ወደታች መዋዠቅ […]

ኢህአዴግ የአንድነት ፓርቲ ኃይሎች በአደረጃጀቴ ሰርገው ገብተተዋል በሚል ግምገማ ለጀምር መሆኑ ታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ጽ/ቤት የአንድ-ለ-አምስት የአደረጃጀት አመራሮች በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች የሚገኙ የአንድ-ለ-አምስት የአደረጃጀት አመራሮችን በመሰብሰብ “አንድነት ፓርቲ የአንድ-ለ-አምስት አደረጃጀታችን ውስጥ አስርጎ ያስገባቸው ኃይሎች በጊዜ በግምገማ ካልተራገፉ ቀጣዩ ምርጫ ከቁጥጥር ውጪ እንደማይሆን ማንም እርግጠኛ መሆን አይችልም፡፡” ማለታቸውን በስብሰባው ላይ የተሳተፉ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ተናግረዋል፡፡

ምንጮቹ ጨምረው እንደተናገሩት ኢህአዴግ የአንድ-ለ-አምስት አደረጃጀቱን የሚያስተባብሩ ከፍተኛ ካድሬዎችን አንድ-ለ-ሰላሳ ማደራጀት መጀመሩን ተከትሎ አንድነት ፓርቲ አስርጎ ያስገባቸው ኃይሎች አሉ በመባሉ ካድሬዎች እርስ በእርስ መሰላለል እና አለመተማመን ጀምረዋል፡፡ ይህ በካድሬዎቻቸው መካከል የተጠፈጠረው ትርምስ ያሰጋቸው የኢህአዴግ የአዲስ አበባ ጽ/ቤት አመራሮች ለክፍለ ከተማ አመራሮቻቸው አንድነት ሊይዝብን የሚችለው 30 በመቶ የሚሆነውን ህዝብ ነው የተቀረውን በኮንዶሚኒየም ፣ በአነስተኛ ጥቃቅንና በየአንድ-ለ-አምስት አደረጃጀት ይዘነዋል ብለዋቸዋል፡፡ ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ መረጃ የሰጡት የስብሰባው ተሳታፊዎች 750ሺ የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢ፣ 30ሺ የኮንዶሚኒየም እጣ ተጠባባቂዎች ኢህአዴግን ነው የሚመርጡት በሚል ከመድረክ የቀረበው መደምደሚያ እንዳላሳመናቸውም ተናግረዋል፡፡

ጉዳዩን በሚመለከት ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ከአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ የደረሰው ዶክሜንት እንደሚያስረዳው ፓርቲው የአዲስ አበባ አደረጃጀቱን ኢህአዴግ በዘረጋው ልክ 138 ያደረሰ ሲሆን በአሁኑ ጊዜም የወረዳ ደረጃና የሴል አደረጃጀቶቹን በኢህአዴግ የአደረጃጀት ቁጥር ልክ የማድረግ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ ያመለክታል፡፡

በብኣዴን ካድሬዎች መካከል የተነሳው ፍጥጫ የሕወሓት አመራሮች በሃይል ሊፈቱት ይችላሉ የሚል ስጋት ጨምሯል።
ሕወሓት በአማራው ክልል አዲስ የፓርቲ አደረጃጀት ጥርነፋ ሊደርግ ነው።

ምንሊክ ሳልሳዊ ፤ የብኣዴን ካድሬዎች ድርጅታቸውን እና አመራራቸው ላይ የሚታየውን ጉዳይ በተመለከተ የፖለቲካ ጥያቄዎች ማንሳታቸውን ተከትሎ ከሕወሓት አሽከር ከሆኑት ጋር በስብሰባ ላይ በተፈጠረ አለመግባባት ስብሰባው እንደተበተነ ታውቋል:: በሕወሓት እና በብኣዴን መካከል ልዩነቶች የሚፈጥሩ ሁኔታዎች ተከስተው አሁንም በስፋት ቀጥለው ይገኛሉ::የተለያዩ ነባር የብኣዴን ካድረዎችን በሰብብ አስባብ የሚያንጠባጥበው ሕወሓት አሁንም አሽከሮቹን አሰማርቶ በድርጅታቸው ውስጥ ለውጥ እንዲደረግ እና የሕወሓት ደባልነትና ፖለቲካ ጥገኝነት እንዲያበቃ የጠየቁትን ወደ ገደል ለመግፋት አየተሯሯጠ ነው::

ባለፉት ሳምንታት በባህር ዳር እና በአዲስ አበባ የተጠሩ ስብሰባዎች በሕወሓት አሽከሮች እና በለውጥ ጠያቂዎች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ስብሰባው ሲበተን …ለሁለተኛ ጊዜ የተጠራው ስብሰባ በከፊል ካድሬዎቹ ስላልመጡ ለሚመጣው ሳምንት የተላለፈ መሆኑን ታውቋል::በሕወሓት አሽከሮች እና በብኣዴን ለውጥ ፈላጊ ካድሬዎች መካከል የተነሳው ፍጥጫ የሕወሓት አመራሮች በሃይል ሊፈቱት ይችላሉ የሚል ስጋት ጨምሯል::

አዲስ በወጣው እቅድ መሰረት በአማራው ክልል በድጋሚ አዲስ የፓርቲ አደረጃጀት ጥርነፋ እንደሚደርግ እና በዚህ መካከል አስቸጋሪ እና አድመኞች የጸረ ሰላም እና የጸረ ሕዝብ ሃይሎችን የመደምሰስ እንዲሁም በአዲሱ የፓርቲ አደረጃጀት ውስጥ አስፈላጊው ጥቅማጥቅሞችን ለአዳዲስ አባላት መስጠት የሚል ይገኝበታል::ውስጥ ውስጡን እየቀሰቀሱ ችግር በፓርቲው ላይ የሚፈጥሩ ካድሬዎችን በማስወገድ በአዳዲስ ለመተካት ታቅዷል::

Image

ምንሊክ ሳልሳዊ ፦ ሰማያዊ ፓርቲ የጀመረውን ሰላማዊ ትግለ ለማጎልበትና የፓረቲውን መዋቅር የስራ እንቅሰቃሴ ለመገምገምና ለማጠናከር እነዲሁም መዋቅሩ ያለበትን ችግር መፍትሄ ለመስጠት ታስቦ የተዘጋጀ የመስክ ጉብኝት እንዲያደርጉ በሶስት ቡድን የተከፈለ ልኡካን በሃገሪቱ ማሰማራቱ ይታወቃል:: እነዚህ የልኡካን ቡድን አባላት የመስክ ጉበኝት በአጠቃላይ በ14 ዞኖችን የሚያካትት ሲሆን ወደ 200 የሚጠጉ ወረዳዎች ላይ ያሉ የሰማያዊን የፓርቲ እንቅስቃሴ ከሚመሩ አስተባባሪዎች ጋር ውይይት እያደረጉ በተግባራዊ ስራ ላይ ይገኛሉ::

በዚህም መሰረት በሚከተለው የመስክ ጉብኝት ምደባ መሰረት በሃገሪት የተለያዩ መስመሮች የተጓዙ የሰማያዊ ፓርቲ የመስክ ጉብኝት የሚያደርጉ አመራሮች …
ጉዞ መስመር አንድ ፡- ደ/ብርሀን ፤ ሸዋሮቢት ፤ ደሴ ፤ ወልዲያ
1. አቶ ስለሺ ፈይሳ – ም/ሊቀመንበርና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊ
2. አቶ ዮናታን ተሰፋዬ – የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ
3. አቶ ሔኖክ መለሰ – በአደረጃጀት ጉዳይ የጥናትና የትግል ስልት ስልጠና ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ
ሸዋ ሮቢት ጨምሮ በደሴ መስመር ላይ ያሉ የሰሜን ሸዋ የፓርቲው የዞን/የቀጠና አመራሮችን በማወያየት ጉዞውን ወደ ወልዲያ እና ደሴ ያቀና ሲሆን ……

ጉዞ መስመር ሁለት – ደብረማርቆስ ፤ ባህርዳር ፤ ወረታ ፤ ጎንደር
1. አቶ በቃሉ አዳነ – አደረጃጀት ጉዳይ ም/ኃላፊ
2. አቶ ይድነቃቸው ከበደ – የህግ ጉዳይ ኃላፊ
3. ወ/ሮ ሃና ዋለልኝ የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ የያዘ የጉዞ መስመር 2 ልዑክ ቡድን የካቲት 24 እና 25 ቀን 2006 ዓ.ም ከምስራቅ ጎጃም የዞን አስተባባሪዎች ጋር በደብር ማርቆስ ከተማ ውይይት አካሄደ፡፡
በምስራቅ ጎጃም ዞን 18 (አስራ ስምንት) ወረዳዎች የሚገኝ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ በ10 (አስሩ) ወረዳዎች ማለትም፡-
1ኛ. አነደድ 2ኛ. ደ/ማርቆስ ከተማ ወረዳ 3ኛ. ጎዛአምን 4ኛ. ማቻከል 5ኛ. ደብረ ኤሊያስ 6ኛ.ባሶ ሊበን
7ኛ. እናርጅ እናውጋ 8ኛ. ጎንቻ ሲሶእነሴ 9ኛ. እነብሴ ሳርምድርጉዞ መስመር ሁለት – ደብረማርቆስ ፤ ባህርዳር ፤ ወረታ ፤ ጎንደር/መርጦ ለማርያም 10ኛ. ሁለት እጁ እነሴ
ከላይ በተገለፁት ወረዳዎች የሰማያዊ ፓርቲ መዋቅር ተዘርግቶ ስራዎች እየተሩ ሲሆን ወደቦታው ያቀናው የልዑክ ቡድን እነዚህን ወረዳዎች ከሚያስተባብረው የዞን አስተባባሪ ኮሚቴ ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡
በቀጣይ ቀናት በባህር ዳር፣ ወረታ (ደቡብ ጐንደር) እና ጐንደር በተመሳሳይ ሁኔታ የሰሜን ኢትዮጵያ ልዕካን ቡድን የሚንቀሳቀስባቸው ቦታዎች ናቸው፡፡

ጉዞ መስመር ሶስት – ሆሳዕና ፤ ሶዶ ፤ አርባ ምንጭ ፤ ባድዋቾ ፤ አዋሳ
1. አቶ ጌታነህ ባልቻ – የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ
2. አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ – የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
3. አቶ ይሁን ዓለሙ – የአደረጃጀት ጉዳይ የክትትልና ግምገማ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ የያዘው የመስክ ጉብኝት ቡድን ሶዶ ላይ ካለው መዋቅር ጋር አሰፈለጊውን ስብሰባና ግምገማ ካካሄዱ ቦሀላ ወደ ቀጣይ ከተማ ወደሆነችው አርባ ምንጭ ጉዞ ሲጀምሩ በሰዶ ፖሊሶች ተይዘው በአሁኑ ሰአት በእስር ላይ ይገኛሉ::

ከማንኛውም ሰው ጋር እንዳይገናኙ እና ምግብ እንዳይትገባላቸው የተደረጉት የመስክ ጉብኝት ቡድን ሶስት አባላት የመንግስታዊ ሽብር አሜኬላዎች የሆኑ ያልተማሩ ካድረዎች በበላይ ትእዛዝ በሚል ህገመንግስቱን በረገጠ መልኩ ሰላማዊ ትግልን መርጦ በመንግስት ተመዝግቦ በሚገኝ ፓርቲ እና አመራሮች ላይ የእስር እርምጃ መውሰዳቸው የዲሞክራሲ እሾዎች ማበባቸውን ያመለክታል:: ምንሊክ ሳልሳዊ

የሻምበል ፍቅረ ስላሴን ባለ 440 ገጽ መጽሐፍ ላነብ ስነሳ ጸሐፊው በሃያ ዓመታት የእስር ቤት ቆይታቸው በስልጣንና የሃላፊነት ዘመናቸው የነበሩትን ብዙ ክንዋኔዎች ፣ ውሳኔዎችና ተዋናዮችን አስመልክቶ የነበራቸውን እይታ እንደገና ለማጤንና ለማሰላሰል እድል አግኝተው የጻፉት ሊሆን ስለሚችል ሚዛናዊ የሆነ ዕውቀት፤ እንዲሁም የመንግስታቸውን የውስጥ ለውስጥ ሥራዎች ከሩቅ እናይ የነበርን ተራ ዜጎች ሳናውቃቸው የቀሩ ነግሮችን የምናገኝበት ይሆናል የሚል ጉጉት […]

ዘወትር ቅዳሜ ማታ ከደሳለኝ መኮንን ጋር፣ምርጥና አዳዲስ የካንትሪ ማለትም የአሜሪካ አገር ሰብእ፣ የሮክ፣ተሶል፣የፖፕ፣የአር-ኤን-ቢ፣ብሉዝ፣የሬጌና የሂፕ-ሃፕ ዜማዎችን እንዲያደምጡ ተጋብዘዋል።

ኢህአዴግ የአንድነት ፓርቲ ኃይሎች በአደረጃጀቴ ሰርገው ገብተተዋል በሚል ግምገማ ለጀምር መሆኑ ታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ጽ/ቤት የአንድ-ለ-አምስት የአደረጃጀት አመራሮች በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች የሚገኙ የአንድ-ለ-አምስት የአደረጃጀት አመራሮችን በመሰብሰብ “አንድነት ፓርቲ የአንድ-ለ-አምስት አደረጃጀታችን ውስጥ አስርጎ ያስገባቸው ኃይሎች በጊዜ በግምገማ ካልተራገፉ ቀጣዩ ምርጫ ከቁጥጥር ውጪ እንደማይሆን ማንም እርግጠኛ መሆን አይችልም፡፡” ማለታቸውን በስብሰባው ላይ የተሳተፉ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ተናግረዋል፡፡ […]

ባሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል የዉኃና አፈር ጥበቃ (Water and Soil Conservation, ማይን ሓመድን ዕቀባ) ተግባራት የሚከናወኑበት ግዜ ነው። ህዝብ ስራው ትቶ ተገዶ በፕሮግራሙ ይሳተፋል። ለፖለቲካ ሲባል ህዝብ በፍላጎቱ ተሳተፈ ተብሎ ሪፖርት ይቀርባል። እውነታው ግን ሌላ ነው። በየዓመቱ ህዝብ ሳያምንበት ተገዶ ይሰራል። በግዜው ያልሰራ እስከ ሦስት መቶ (300) ብር ተቀጥቶ ይሰራል። በዚሁ ምክንያት ብዙ ሌሎች የግል […]

የግንቦት ሰባት በድህረ ገጹ ላይ ይፋ ባደረገዉ የሳምንቱ ርእስ አንቀጽ፡ በመኢአድ እና አንድነት ፓርቲ ለተጠራዉ የባህር ዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ ያለዉን አድናቆት ገለጸ። «ፈታኝ ሁኔታዎችን ተቋቁመው የየካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ምን ሕዝባዊ ተቃውሞ ላደራጁና በተቃውሞውም ለተካፈሉ ሁሉ ያለውን አክብሮት ይገልፃል። ሕዝብ ብሶቱን የሚገልጽበት ሕዝባዊ ተቃውሞ ማደራጀትና መምራት መቻል ትልቅ ነገር ነው። ሕዝባዊ ተቃውሞዎች ወደ ሕዝባዊ እምቢተኝነት […]

እስቲ በግልፅ እንነጋገር: ለተጋሩ ============== አንዳንድ ተቃዋሚዎች የትግራይን ህዝብ በህወሓት ዘመን የተለየ ጥቅም እንዳገኘ አስመስለው ሲያቀርቡ እንወቅሳቸዋለን። ምክንያቱም የትግራይ ህዝብ በህወሓት ዘመን እንደተጠቀመ ሳይሆን እንደተጎዳ ጠንቅቀን እናውቃለንና። በሌላ በኩል ህወሓት ለፖለቲካ ፍጆታ ሲል የትግራይ ህዝብና ህወሓት አንድ እንደሆኑ ይሰብካል። ህዝብና ገዢ ፓርቲ በምንም ስሌት አንድ ሊሆኑ እንደማይችሉ ግልፅ ነው። ፓርቲና ህዝብ አንድ አድርጎ የማሰብን ያህል […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በአፋር ክልል ወደ አፍዴራ የሚወስደዉን መንገድን ይዞ የአርተአሌ እሳተ ጎመራ ባለበት አካባቢ ፤ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ሊዘሎረ ሲሩስ፤ ባለፈው ሳምንት ጉብኝት አድርገዉ ተመልሰዋል።

ትናንት ብራሰልስ ቤልጅየም የተሰበሰቡት የአውሮፓ ህብረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ሩስያ ጦሯን ከዩክሬን ካላስወጣች ከሩስያ ጋር የተጀመረው ንግግር እንደሚቋረጥ እንዲሁም ማዕቀቦች እንደሚጣሉባት አስጠንቅቀዋል ።

በአፋር ክልል ወደ አፍዴራ የሚወስደዉን መንገድ ይዞ ወደ አርተአሌ እሳተ ጎመራ ባለበት አካባቢ ፤ የጀርመንዋ አምባሳደር ሊዘሎረ ሲሩስ፤ በጋዜጠኞች ቡድን በመታጀብ ጉብኝት አድርገዉ ተመልሰዋል።

መካከለኛዉ ምስራቅና የአረቡ ዓለም ስንዴን፤ ጃፓንን ጨምሩ በጥቅሉ እስያ ሩዝን፤ አብዛኛዉ አፍሪቃ በቆሎን ከማዕዳቸዉ አያጡም። አዉሮጳና ሰሜን አሜሪካም ቢሆን ስንዴን በብዛት እንዲሁም ገብስን ማዘዉተሩ ይታወቃል። ጤፍ ደግሞ መገኛዉም ሆነ ምግብነቱ የታወቀዉ ምስራቅ አፍሪቃ ኢትዮጵያ ነዉ።