የቀድሞዉ ኦሮሚያ ፕሬዝዳንት ዜና ዕረፍት

በ1993 የኢሕአዴግ ዋና መሠረት የሚባለዉ ሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ሕወሐት) ለሁለት ሲገመስ ግን የአንጋፋዉ ፖለቲከኛ የኢሕአዴግነት ጀንበር ስታዘቀዝቅ-የወጣቱ ካድሬ የኢሕአዴግ የፖለቲከኛነት ጀምበር ባንፃሩ ደመቀች።አቶ አለማየሁ የያኔዉን ጠቅላይ ሚንስትር የአቶ መለስን ልዩ ትኩረት እና እንክብካቤም አገኙ።