የቡድን ሰባት ሀገራት መሪዎች ትናንት በዘ ሄግ፣ ኔዘርላንድ ስለዩክሬይን ውዝግብ ለመምከር በጠሩት ልዩ ስብሰባ ላይ፣ ሩስያ የዩክሬይን ግዛት የነበረችውን ክሪሚያን የግዛቷ አካል አድርጋ በመቀበሏ ፣ ሞስኮ

የዓይን ማዝ በሽታን በቀላሉ መከላከል ሲቻል ዛሬም ለብዙዎ የዐይን ብርሃን ማጣት ምክንያት እየሆነ ነዉ። የድህነት በሽታ በመባል የሚገለፀዉ ይህ የዐይን ህመም በዓለም 21 ሚሊዮን ሰዎችን እንደጎዳ የዓለም የጤና ድርጅት መረጃዎች ያመለክታሉ። ኢትዮጵያ ዉስጥም ይህ የዓይን ሕመም በተለያዩ ክልሎች ተንሰራፍቶ እንደሚገኝ እየተገለጸ ነዉ።

በትናንትናዉ ዕለት የግብፅ ፍርድ ቤት በ529 የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር አባላት ላይ የሞት ቅጣት በይኗል። ዉሳኔዉ በተሰጠበት በዚሁ ችሎት 147ቱ ብቻ ናቸዉ በስፍራዉ ተገኝተዉ ፍርዱን ያደመጡ ሲሆን ቀሪዎቹ ከሚጠብቃቸዉ ፍርድ ለማምለጥ በሽሽት ላይ መሆናቸዉ ተገልጿል።

ደቡብ ሱዳን ከግብፅ ጋ የሁለትዮሽ ወታደራዊ ትብብር ስምምነት መፈራረሟን ዘገባዎች ያመለክታሉ። ጁባ ተመሳሳይ መግባባት ላይ ከሁለት ዓመታት በፊት ከተነጠለቻት ሰሜን ሱዳን ጋም መድረሷ ተገልጿል።


(ደጀ ሰላም፣ መጋቢት 14/2006 ዓ.ም፤ ማርች 24/2014/ PDF በፍቅር ለይኩን):- ባለፈው ሳምንት ‹‹የፓትርያርኩ የለውጥ ተስፋዎች ወዴት ገቡ?›› በሚል አቶ መብራቱ መርሳ የተባሉ ግለሰብ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ን ፓትርያርክ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ በቤተ ክህነቱ ተቋም የተንሰራፋውን ሙሰኝነትንና ጎጠኝነትን በተመለከተ የተማፅኖ ጦማራቸውን በሪፖርተር ጋዜጣ በኩል ለቅዱስ ፓትርያርኩ ይደርስ ዘንድ አቅርበው ነበር፡፡ እኚህ ግለሰብም ባቀረቡት የተማፅኖ ደብዳቤያቸው ዋና አሳብም፣ ቅዱስ ፓትርያርኩ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደር ውስጥ የነገሠውን አድር ባይነት፣ ዘረኝነት/ጎጠኝነትና ሙስና ለማጥፋት በአደባባይ ቃል የገቡበትን ዘመቻቸውን አጠንክረው እንዲቀጥሉበትና ፍሬውን በተግባር እንዲያሳዩ የሚጠይቅ ነው፡፡

በእርግጥ ይህ የአንድ ግለሰብ ብቻ ሳይሆን የበርካታዎች የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ መሪዎች፣ አባቶች፣ አገልጋዮችና ምእመናን የቀን ተሌት ብርቱ ምኞትና ተማፅኖ ነው፡፡ እኚህ ሰው ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ወደ ፕትርክና መንበር በመጡ ማግሥት የቤተ ክህነቱን ተቋም ከጎጠኞችና ከሙሰኞች ለማጥራት የገቡት ቃል ተግባራዊ ኾኖ ለማየት የነበራቸው ምኞት ከዓመት በኋላ የተጠበቀውን ያህል ዘመቻው ስኬት ባለማሳየቱና የለውጡም ሂደት በመንቀራፈፉ ሥጋት ቢጤ ገብቷቸው ይመስላል ይህን የተማፅኖ ደብዳቤ ለፓትርያርኩና ለሚመሩት የቤተ ክህነት ተቋም ለማድረስ የወደዱት፣ የተገደዱት፡፡
የእኚህ ግለሰብ ‹‹የለውጥ ያለኽ›› ተማፅኖ ጦማር በርካታዎችን የቤተ ክርስቲያኒቱን አባቶችን፣ አገልጋዮችንና ምእመናን የሚወክል እንደሆነ ነው በግሌ የማምነው፣ የምቀበለውም፡፡ የብዙዎች የአባት ያለኽ፣ የመሪ ያለኽ፣ የፍቅር ያለኽ፣ የእውነት ያለኽ፣ የፍትሕ ያለኽ፣ የበጎነት ያለኽ፣ የቅንነት ያለኽ፣ የመንፈሳዊነት ያለኽ፣ የለውጥ ንፋስ ያለኽ ጩኸትና አቤቱታ የቤተ ክህነቱን ተቋምና የአገሪቱን ሰማይ ክፉኛ ካደፈረሰው ሰንብቷል፣ ከራርሟልም፡፡
እውነተኛ የኾኑ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች፣ መንፈሳዊ መሪዎች፣ አገልጋዮችና ምእመናንም፣ አምላክ ሆይ ዝምታህ እስከ መቼ ነው?!፣ በቅዱስ መቅደስህ አደባባይ በትእቢትና በድፍረት እየተንጎማለሉ መሠውያህን በድሆች ዕንባና ደም የሞሉ ክፉዎችን የምትታገሳቸው እስከ መቼ ነው?!፣ በአፍቅሮተ ንዋይ አቅላቸውን የሳቱ፣ በክቡር ደምህ በዋጃኻቸው በጎችህ/በመንጋዎችህ ላይ በዋጋ የሚደራደሩ ይሁዳዎች- ምንደኞችና ነጋዴዎች ላይ የተግሣጽህ፣ የቁጣህ ጅራፍህ መቼ ነው የሚነሳው?!፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በዘርና በጎሳ የሚለያዩና የሚከፋፍሉ ዘረኞችና ጎጠኞችስ መቼ ነው ክፉ ዘራቸው የሚመክነው?!
የወንጌልን እውነት ቃል የሚሸቃቅጡ፣ መንፈሳዊ ሕይወትንና ስኬትን በግፍ በተከማቸ የዓመፃ ገንዘብና በዓለማዊ ሀብት የሚለኩ፣ የእግዚአብሔርን ስጦታ እንደ ስምኦን መሰሪ በገንዘብ ገዝተው በመቸርቸር ሀብትና ዝናቸውን ሰማይ ለማድረስ ዓውደ ምሕረቱን ያረከሱ አስመሳይ ነጋዴዎችና ምንደኞችስ ስለምን ቤትህን አጣበቡት?!፣ በቅድስናህ መቅደስ ላይ የሚዘባበቱ ፌዘኞችስ እስከ መቼ ሕዝብህን በሽንገላ ቃል ያባብሉታል፣ በክፉ ሥራቸውስ ያሰጨንቁታል፣ ያሰቃዩታል፣ ያስለቅሱታል?!
ስለ ሕዝብ መከራና ሰቆቃ፣ በየቀኑ እየፈራረሱ ስላሉ በክቡር ደምህ ስለዋጃኻቸው መቅደሶችህ/ሕዝበ ክርስቲያን ግድ የሚለውና በፈረሰው ቅጥር በኩል የሚቆም ነቢይ ኢሳይያስ ወዴት ይገኝ ይሆን?!፣ በመቅደስህ አጥር ስር ስለወደቁ የምድሪቱ ጎስቋሎችና መፃጉዎች፣ በረሃብ አለንጋ እየተገረፉ በቤተ መቅደስ ደጃፍ ስለሚያነቡ የዋኃን ሕፃናትና እናቶቻቸውስ ማን ነው ግድ የሚለው?!፣ ሕዝብህ በየቀኑ እየፈረሰ፣ እየተናደ ባለበት፣ የአንተን ቤት በዕብነ በረድና በከበሩ ድንጋዮች አንሠራለን፣ እነገነባለን የሚሉ ግብዞችንና ሙሰኞችንስ የሚገሥጻቸው ማን ይሆን?!
ነገሥታትንና መሪዎችን በአደባባይ የሚገጥሙ፣ ስለ ክፋታቸው፣ ኃጢአታቸውና በደላቸው ፊት ለፊት የሚገሥጹ፣ ስለ እውነትና ፍትሕ የሚቆሙ መንፈሳዊ ዐርበኛ የኾኑ ባህታውያን ዮሐንሶች ወዴት አሉ?!፣ ሕዝብን ከአስጨናቂው የፈረዖን አገዛዝ ነፃ የሚያወጡ፣ በሕዝባቸውና በወገናቸው ፍቅር የነደዱ የዘመናችን ሙሴዎችስ አድራሻቸው ወዴየት ነው?!፣ እንደ ነቢዩ ኤርምያስ ዕንባቸውን እያፈሰሱ ‹‹አቤቱ የኾነብንን አስብ፣ ስለ ቅዱስ ስምህ ስትልም ዘመናችን አድስ!›› የሚሉ ኤርምያሶችን ከወዴት እናገኝ ይሆን በማለት ብዙዎች በተማፅኖ ዕንባቸውን እንደ ራሄል ወደ ጸባዖት፣ ወደ አርያም እየረጩት ነው፡፡
ምድሪቱን በከደነው በዚህ ሁሉ ዋይታ፣ ጩኸትና ሰቆቃ መካከል እጅግ ወደ ተከበረው መንፈሳዊ መንበር፣ ሥልጣንና ኃላፊነት የመጡት ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ በሹመታቸው ማግሥት ሙሰኝነትንና ጎሰኝነትን አልታገሥም፡፡ ይህ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ የልጆቻችን ብርቱ ጩኸትና ዋይታ ወደ ጆሮዬ ደርሷል እናም ጊዜው የለውጥ ነው፡፡ ከቅዱስ ሲኖዶስ፣ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች፣ መንፈሳዊ አገልጋዮችና ልጆቻችን ጋር በመሆን ለለውጥ እንሠራለን፣ እንደክማለን በማለት የብዙዎችን ልብና ስሜት ከፍ አደርገውት ነበር፡፡ በዚሁ መንፈሳዊ ቆራጥነትና ትጋትም የተወሰዱ የብዙዎችን ልብ በተስፋና በሐሤት የሞሉ አንዳንድ የለውጥ ዕርምጃዎችም ነበሩ ማለት ይቻል ይመስለኛል፡፡
በመጀመሪያ ደረጃ ቅዱስ ፓትርያርኩ በቤተ ክርስቲያኒቱ የተንሰራፋውን የጎጠኝነትና የሙሰኝነት ችግሮች መኖራቸውን አምነው መቀበላቸው አንድ የለውጥ ዕርምጃ ነው ማለት የሚቻል ይመስለኛል፡፡ ‹‹በቅጡ ተለይቶ የታወቀ ችግር በከፊል እንደተፈታ ይቆጠራል፡፡›› እንዲሉ፡፡ ሲቀጥልም ፓትርያርኩ እነዚህ ለበርካታ ዓመታት ሲንከባለሉ የቆዩ ችግሮችን በትክክል ለይቶ ከማስቀመጥና ባለፈም ተግባራዊ ዕርምጃዎችን በመውሰድ የለውጥ ዕርምጃው በአምላካችን ረዳትነት ፍሬ እንዲያፈራ እናደርጋለን በማለት እንቅስቃሴ መጀመራቸው ለብዙዎች ብሩሕ የለውጥ ተስፋን የፈነጠቀ ነበር ማለት ይቻላል፡፡
ለአብነትም ያህል ፓትርያርኩና ቅዱስ ሲኖዶሱ በበዓለ ሲመትና በሌሎች ክብረ በዓላት ሰበብ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪና የተንዛዛ ድግስና ውዳሴዎች እንዲቀሩ ማድረጋቸው፣ በድግስ ሰበብና በበዓላት ሽርጉድ ኪሳቸውን የሚያደልቡ ሙሰኞችን በሩ እንዲዘጋባቸው አድርጓል፡፡ በዚህም በውድ ስጦታዎችና ገጸ በረከቶች ሰበብ፣ እጅ የመጠመዘዝ ያህል ድብቅ አጀንዳቸውንና ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም የሚተጉና የሚሯሯጡ አስመሳዮችና ሙሰኞችም ቀኑ እንዲጨልምባቸው ኾኗል፡፡
ሌላውና በተለይም በግንባር ቀደምትነት ሊጠቀስ የሚገባው የለውጥ እንቅስቃሴ ደግሞ በቤተ ክህነቱ አስተዳደር ሥራ ውስጥ ግልፅነትና ተጠያቂነት ያለበት፣ መንፈሳዊ ትጋት፣ በጎነትና ቅንነት የሚንጸባረቅበት ሙያዊ/ፕሮፌሽናል አሠራር እንዲኖርና ለማድረግ ከመነጋገር አንስቶ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ ልጆችና ምሁራን የተሳተፉበት ‹‹የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መዋቅር አደረጃጀትና የአሠራር መመሪያ ጥናት›› ሰነድ ቀርቦ ሰፋ ያለ ተከታታይ ውይይቶች የተደረገበት የዛን ሰሞኑ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የቤተ ክህነቱ የአስተዳደር ሠራተኞችና መንፈሳዊ አባቶች የተሳተፉበት ጉባኤ በዋናነት የሚጠቀስ ነው፡፡
ይህን የለውጥ ትግበራ ጥናት ሰነድን ያዘጋጀው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶችና ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ነው፡፡ ይህ ዳጎስ ያለ ጥናትም በቁጥር ጥቂት የማይባሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች የኾኑ ምሁራንና ባለሙያዎች የተሳተፉበትና በገንዘብ ሲሰላም ቤተ ክርስቲያኒቱን በመቶ ሺኅዎች የሚገመት ወጪን ከማውጣት የታደጋት በብዙ ድካምና በብርቱ ጥንቃቄ የተዘጋጀ የጥናት ሰነድ እንደሆነ ነው አብዝቶ የተነገረለት፡፡
በዚህ የጥናት ሰነድ ላይም በየደረጃው ተከታታይ የኾኑና ውጤታማ ነበሩ ሊባሉ የሚችሉ ውይይቶች ተደርጎባቸዋል፡፡ ይሁን እንጂ በጉባኤው ላይ ይህን የመዋቅር አደረጃጀትና የአሠራር ጥናት ሰነድ በምን መልኩ ሥራ ላይ ልናውለው እንችላለን የሚለው ላይ በተነሡ አንዳንድ ልዩነቶችና አለመግባባቶች የተነሳ የተለያዩ ቡድኖች ጎራ ለይተው የቃላት ጦር ሲማዘዙ፣ ሲጠዛጠዙ ታዝበናል፡፡ አሁንም የቃላት ጦርነቱ፣ መወራረፉና መጎነታተሉ እንደቀጠለ ነው፡፡ በአንፃሩም ችግሩንና ቀውሱን ከቤተ ክህነቱ ክልል በማውጣት በስውርም ኾነ በግልጽ እየታየ ያለ ሌላ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መሠረት ያለው ጠንካራ ግፊት እንዳለ የሚከራከሩ ድምፆች ደግሞ እዚህም እዛም እየተሰሙ ናቸው፡፡
ለቤተ ክርስቲያኒቱ የሚቆረቆሩ፣ በአገር ውስጥና በውጭ አገራት ባሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች የተማሩ ምሁራንን በሥሩ አሳባስቦ የያዘው ማህበረ ቅዱሳን ለዚህ የለውጥ ዕርምጃ የበኩሉን ዕገዛና ጥረት ለማድረግ ደፋ ቀና ቢልም፣ ማኅበሩ ያቀረበው የዳጎሰ የጥናት ሰነድ ሁሉንም የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችና አባቶች ባስማማ መልኩ ተቀባይነት አግኝቶ የለውጥ ትግበራውን ዕውን ለማድረግ ዕንቅፋት እንደገጠመው ግን በግልጽ እየተስተዋለ ነው፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ይህ የጥናት ሰነዱ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ተዛማጅ የኾኑ እንቅስቃሴዎቹም ከሰሞኑን እክል እንደገጠማቸው ሰምተናል፣ ታዝበናልም፡፡ ለአብነትም የአብነት መምህራንን በተመለከተ የጠራው አገር አቀፍ ጉባኤ መታገዱ የሰሞኑን በርካታዎችን ያሳዘነ ዜና ሆነ ማለፉን ልብ ይሏል፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ቅዱስ ፓትርያርኩ ከሰሞኑን፣ ‹‹ቤተ ክርስቲያን በባይሎጂና በኬምስትሪ ምሩቃን አትመራም፡፡›› የሚለው መረርና ከረር ያለ ውስጠ ወይራ ንግግራቸው በማኅበሩ ማንነትና አቋም ላይ ያነጣጠረና ጥርጣሬያቸውንም ገሃድ ያወጣ ንግግር እንደሆነ ነው ብዙዎች ሲናገሩ የተደመጡት፡፡
የኾኖ ኾኖ ፓትርያርኩ በአደባባይ ያወጁትንና ቃል የገቡለትን ቤተ ክህነቱን ተቋም ከሙሰኞችና ከጎጠኞች እናጻዳለን ዘመቻቸውም ኾነ ለዚሁ የለውጥ ዘመቻ ያግዛል በሚል በማኅበረ ቅዱሳን ያቀረበው የጥናት ሰነድ የመጨረሻው ዕጣ ፈንታ ምን ይኾናል የሚለውን በእርግጠኝነት ለመናገር ግን አሁንም በትዕግሥት መጠበቅ የሚያስፈልግ ነው የሚሉ በርካታ ታዛቢዎች አልጠፉም፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የቤተ ክህነቱ ተቋም ትልቁና ዋንኛ ችግሩ የሚጀምረው ከላይ ከመንፈሳዊ መሪዎቹ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች አካባቢ መንፈሳዊ ሕይወትና መንፈሳዊ ቆራጥነት/ቅንዓት መጥፋቱ በቤተ ክህነቱ ተቋም ለተከሰተው የዚህ ሁሉ ምስቅልቅልና ቀውስ ዋንኛው ምክንያት እንደኾነ አድርገው ያቀርባሉ፡፡ በከፋ የሞራል ውድቀትና ዝቅጠት ውስጠ የተዘፈቁ፣ ምድራዊ ሀብትና ዝና የሚያንኾልላቸው፣ የለየላቸው ሙሰኞችና ጎሰኞች ከላይ እስከ ታች በተሰገሰጉበት የቤተ ክህነቱ ተቋም ውስጥ ለውጥን ለማምጣት መንገዱ አልጋ በአልጋ ይኾናል ተብሎ አይታሰብም፣ አይጠበቅምም፡፡
ላለፉት በርካታ ዓመታት ሲንከባለል የቆየ ይህ የተወሳሰበው የቤተ ክህነቱ ተቋም ችግሮች በአንድ ጀምበር ይፈታሉ ብሎ ማሰብም የዋኽነት ነው፡፡ እናም ለውጡን ዕውን ለማድረግ ከሚያስፈልገው ትዕግሥትና ቁርጠኝነት ባሻገር የክርስትና ሃይማኖት ዓምድና መሠረት የኾኑት ፍቅር፣ በጎ ሕሊና፣ ቅንነትና ታማኝት እንዲኖሩ የግድ ይላል፡፡ መሰሪነት፣ አድር ባይነት፣ አጎብዳጅነትና ግብዝነት በነገሡበትና መንፈሳዊነት ፈፅሞ እየተሰደደበት ባለበት ተቋም ውስጥ ለቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ መሪዎችና አባቶች ፍቅርና ኅብረት፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ ህልውና፣ የመንፈስ አንድነትና ሰላም ቀዳሚና ዋና አጀንዳ ሊኾን በተገባው ነበር፡፡
ከሁሉም በፊት ፍቅርንና መንፈሳዊ አንድነትን ለማምጣት ፈቃድም ኾነ አቅም ያነሰው የቤተ ክህነቱ ተቋም ጋሪውን ከፈረሱ በማስቀደም ጉልበቱንና አቅሙን በከንቱ እያባከነ ነው በማለት የሚተቹ ብዙዎች ናቸው፡፡ የቤተ ክህነቱ ተቋምም ኾነ መሪዎች በእውነትም ሊያሳስባቸውና ሊያስጨንቃቸው የሚገባው ቀዳሚው ጉዳይ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ አንድነትና ሰላም መሆን ነበረበት፡፡ ይህ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ መሪዎችና አባቶች ወይም የቤተ ክህነቱ ተቋም ወሳኝና ቀዳሚ አጀንዳ የአንድ ሰሞን ብቻ ወሬና ግርግር ኾኖ ማለፉና አሁን አሁን ደግሞ ከእነ መፈጠሩም የመረሳቱ ነገር ለመኾኑ መቅደም ያለበት የትኛው ነው ‹‹ሰላምና አንድነት ወይስ …›› የሚል ጥያቄን በተደጋጋሚ እያስነሳ ነው፡፡
ይህ የቤተ ክርስቲያኒቱ የአንድነትና የሰላም ጉዳይ የሚያሳስባቸው በርካታዎችም የፓትርያርኩም ኾነ የቤተ ክህነቱ ተቋም የለውጥ እንቅስቃሴ የቤቱ መሠረት ተነቃንቆ እያለ ጣርያውና ግድግዳው እንዳይፈረስ ከሚታገል የዋኽ ሰው ጋር በማመሳሰል የሚያቀርቡ ታዛቢዎች አልጠፉም፡፡
በቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ ኾኖ በማያውቅ ለሦስት ተከፍላ፣ የኢትዮጵያ ሲኖዶስ፣ ሕጋዊው ሲኖዶስ፣ ገለልተኛ በሚል የተለያዩ፣ የተከፋፈሉና ተገለባባጭና አድር ባይ የኾኑ ፖለቲከኞች እንደሻቸው የሚጠመዙዟቸው አባቶች ልዩነታቸውን በሰላም ፈተው ወደ አንድነት መምጣት እስካልፈቀዱ ድረስ፣ ለቤተ ክህነቱ የምንመኘው እውነተኛውና ተግባራዊው ለውጥ ህልም ነው ሲሉ አጥብቀው ይከራከራሉ፡፡ ዛሬ ከዳር እስከ ዳር መነጋገሪያ የኾነው ሙሰኝነትም ኾነ ጎጠኝነት የቤተ ክህነቱ ለገባበት ቀውስና የሞራል ውድቀት አንድ ወይም ጥቂቱ መገለጫ እንጂ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሠረታዊ ችግር ጥልቅ፣ የተወሳሰበና ዕድሜ ጠገብ ነው፡፡ መፍትሔውም ፍቅር፣ አንድነትና ሰላም ግድ የሚላቸው፣ ለእግዚአብሔርና ለቤቱ መንፈሳዊ ቅንአት ያላቸው መንፈሳዊ መሪዎች እንዲኖሩና እንዲበዙ መጸለይና መሥራት ነው፡፡  
የፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ ሙሰኞችንና ጎጠኞችን የማጥራት ዘመቻው ፍሬያማ እንዲኾንና ለዚሁ የለውጥ ዘመቻ ትግበራም ያግዛል ተብሎ በቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች/ምሁራን የቀረበው የጥናት ሰነድ ተግባራዊ ውጤት እንዲያመጣ ከተፈለገ መቅደም ያለበት አማራጭ ይህ ነው ሲሉም ይናገራሉ፡፡ ስለሆነም ይላሉ እነዚህ አስተያየት ሰጪዎች፣ የቤተ ክህነቱ ተቋም ማስቀደም ያለበት ዋነኛው ዕርምጃ መሆን ያለበት መንፈሳዊነትን ያስቀደሙ የእግዚአብሔርና የቤቱ ቅናት የሚያቃጥላቸው፣ መመሪያቸውና መለያቸው ፍቅር የኾነ፣ ሰላምንና ዕርቅን የሚሰብኩ፣ ለእውነትና ለፍትሕ የቆሙና የሚከራከሩ መሪዎችና አባቶች እንዲኖሩና እንዲበዙ መሥራትና መትጋት የግድ ይላል በማለት አስተያየታቸውን ይሰነዝራሉ፡፡
እነዚህ ትችቶች፣ መከራከሪያዎችና አስተያየቶች እንዳሉ ኾነው ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የጀመሩት የቤተ ክህነቱን ተቋም ከሙሰኞችና ከጎጠኞች የማፅዳት ዘመቻቸውን አጥብቀው እንዲገፉበት የሚመኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች፣ አገልጋዮችና ምእመናን ድምፅ አሁንም ጎልቶ እየተሰማ ነው፡፡ በመጨረሻ አንድ ነገር ለማለት እወዳለኹ፡፡ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በፕትርክና ዘመናቸው የተከፋፈለችውን ቤተ ክርስቲያን አንድነት በማስጠበቅ፣ የቤተ ክህነቱን ተቋም ከሙሰኞች፣ ከአስመሳዮችና ከጎጠኞች የፀዳች በማድረግ አዲስ ታሪክ ያስመዘግቡ ዘንድ ልባዊ ምኞቴ ነው፡፡
Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
(ይህ “ኑ! እንዋቀስ” የሚለው ስር ነቀል የለውጥ ጥሪ ቀጥታ የሚያነጣጥረው በኢህአዴግ አባላት ላይ ብቻ ነው፤ አመራሩን በፍፁም አይመለከትም) ኢህአዴግ ራሱ በይፋ ሲናገር እንደተደመጠው፣ በአሁኑ ጊዜ የአባላቱ ቁጥር ወደ ሰባት ሚሊዮን ገደማ ደርሷል። ይህም የአገሪቱ ቁጥር አንድ ግዙፍ የፖለቲካ ፓርቲ ያደርገዋል። በርግጥ ግዙፍ እንጂ ጠንካራ እንዳላልኩ ልብ ይሏል። ምክንያቱም ጥንካሬ የሚለካው በአባላት ቁጥር ሳይሆን በድርጅት ፍቅር፣ በዓላማ ፅናትና በሚሰጡት ልባዊ አበርክቶ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በሕዝብ ብዛት ቁጥር ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሁለተኛ ከአለም ደግሞ አሥራ አምስተኛ ናት። ወደ ሰማኒያ ሚሊዮን ሕዝብ ሲኖራት፣ ያን ያህል ሕዝብ ኖሯት የባህር በር የሌላት ብቸኛ አገር ናት። ከኢትዮጵያ ቀጥሎ ብዙ ሕዝብ ኖርቷት የባህር በር የሌላት አገር፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድ ሶስተኛ የሚሆን ሕዝብ ያላት ዩጋንዳ ናት። የቀድሞ ጥቅላ ሚኒስተር አቶ መለስ ዜናዊ፣ በባህር ወደብ ዙሪያ ሲጠየቁ «ለእድገት […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ዖባማ፤ ዛሬ ኔድርላንድ እንደገቡ በሰጡት መግለጫ ፣ አውሮፓውያንን ዩናይትድ ስቴትስ ሩሲያ በክሪሚያ በወሰደችው እርምጃ ሳቢያ ዋጋ የሚያስከፍላትን የማዕቀብ ርምጃ በመተባበር ወስደናል አሉ። ሰፊ የጦር ኃይል አንቀሳቅሶ

በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ፣ ባለፈው ቅዳሜ ከቀትር በኋላ በደረሰው የአሳት ቃጠሎ፣ በዋናው ህንጻና ማሺኖች ላይ የደረሰ ጉዳት ባለመኖሩ፤ የማተሚያ ቤቱ መደበኛ ሥራ አለመተጓጎሉን ማተሚያ ድርጅቱ ገለጠ። በቃጠሎው የወደሙት በጓሮ በኩል የነበሩ ትርፈ

የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ፍርንክ ባልተር ሽታይንማየር በአፍሪቃ የሦስት ቀናት ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ አዲስ አበባ ገቡ። ጀርመናዊው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ከኢትዮጵያ ፕሬዚደንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ እና

በሮም አደባባይ ኢትዮጵያውያኑ ጀግኖች አትሌቶች ትናንት ድርብ ድል ተጎናፅፈዋል። በወንዶችም፣ በሴቶችም ማንም ከፊታቸው ደፍሮ መቆም አልቻለም። በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ መድፈኞቹን ሰማያዊ ለባሾቹ በገዛ መድፋቸው አፈር ድሜ አብልተዋል። ማን ዩናይትድን ያሳፈረው ባቡር ግን እየተንገታገተ ነው። ሊቨርፑል እና ቸልሲ ተናንቀዋል።

ሸዋ በር እና አከባቢው ስጋት ነጋደው ጭንቀት እንዳጠላበት ነው።”…አዘናግቶ ሊያጋየን ነው::”
የእሳት ማጥፊያ አዘጋጁ እሳት ሊነሳ ይችላል የሚለውን ወያኔያዊ ሽብር በነጋዴዎች ዘንድ ጥርጣሬ አጭሯል::

ምንሊክ ሳልሳዊ:-በሃረር ለረዥም ጊዜ ታፍኖ የቆየው ብሶት ባለፈው ሰሞን የተነሳውን የእሳት ቃጠሎ ተከትሎ ሕዝቡ አደባባይ እስከመውጣት ደርሶ ነበር::የወያኔው መንግስት ካለፉት አመታቶች ጀምሮ በተለያየ ጊዜ የሃረር ነጋዴዎችን መደብሮች ሲያቃጥል እንደ ዋናው ምክንያት ተደርጎ የተወሰደው አከባቢው ለልማት ስለሚፈለግ ከቦታው ተነሱ የሚለው የቅድመ ማስጠንቀቂያ ነጋዴዎቹ በምትኩ ቦታ ይሰጠን የሚሉትን አስታኮ የሚመጣ ቃጠሎ መሆኑ እና ከቃጠሎ በፊት ወደ መደብሮች መጋዘን የሚገቡ ነዳጅ የተሞሉ ጀሪካኖች ሕዝቡ ጣቶቹን በወያኔ ላይ እንዲጠቁም አድርጎታል::

ወያኔ የሃረር ህዝብ ላይ ያደረሰውን ሰቆቃ እና በደል ለመሸፈን ሰላማዊ ሰልፍ በመጥራት ነገሮችን በሙሉ አሸባሪ ብሎ በሚጠራቸው በመላከክ ህዝቡን ለመሸወድ ቢሞክርም አልተሳካለትም:: በየመንገዱ ቢያፍስ ቢያባርር ቢደበድብ ቢያስር ስብሰባ ቢጠራ ያልተሳካለት ወያኔ ከዚህ በመቀጠል ምን ሊያመጣ እንደሚችል እስካሁን የታወቀ ነገር የለም:: ምናልባት ይላሉ የሸዋ በር እና አከባቢው ነጋዴዎች ስጋታችንን እና ጭንቀታችን መደብሮቻችንን እንዳያቃጥልብን ነው ሲሉ ሃሳባቸውን አካፍለውናል::

በውሃ እጥረት እና በሌሎች የአገልግሎት አቅርቦት የምትታመሰው ሃረር በሕወሓት ሰራሾች ደባ እየተደረገባት ያለው የሰብኣዊ መብት ገፈፋ እና በደል እየጨመረ እንዲ እየቀነሰ አለመሆኑ የሰሞኑ ምስክር ሂደት ምስክር ነው::በዚህ ሰሞን ከክልሉ ምክር ቤት እስከ ቀበሌ ካድሬዎች ስብሰባ ከሕዝቡ እስከ ነጋዴው ቢሰበሰብም በሰብሳቢዎች እና በተሰብሳቢው ሕዝብ መካከል አለመተማመን እንደነገሰ ተበትኗል:: በትላንትናው እለት በሸዋ በር አከባቢ ጀጎል ግንቡን አስታኮ ያሉ ባለመደብሮች ስብሰባ ተጠርተው እንዲሁም የእህል እና የቅመማ ቅመም ነጋዴዎች በስብሰባው ተጋብዘው የተገኙ እና በተሰብሳቢው እና በሰብሳቢዎች ሕወሓት ሰራሽ የከተማው ባለስልታናት መካከል ስጋት እና ሽንቀት ወጥሮት የተካሄደ እንደነበር ነጋዴዎቹ ጠቁመዋል::

የሸዋ በር አከባቢ ነጋዴዎች ባለፈው በመብራት ሃይል እና በሲጃራ ተራ አከባቢ የደረሰውን የእሳት ቃጠሎ ከተመለከቱ በኋላ ነግ በኔን በማሰብ ንብረታቸውን ከአከባቢው በማሸሽ ስጋታቸውን በተግባር ለወያኔ ሰራሽ አካላቱ ያሳዩ ሲሆን ይህንን የተመለከተው መንግስታዊ አካል ነኝ ያለ ክፍል ነጋዴው እቃውን ከማውጣት ከመንግስት ጋር በጠረጰዛ ዙሪያ እንሰብሰብ እቃችሁን አታሽሹ ቢልም ነጋዴዎቹ አዘናግቶ ሊያጋየን ነው በሚል እቃቸውን ወደቤታቸው ጭነው ወስደዋል::

ንብረታችን ቤታችን እንዳለ ስብሰባ እንቀመጣለን ብለው የቆረጡት ነጋዴዎች በተጠሩበት ስብሰባ በመሄድ ዋና ዋና የተባሉ ነጥቦችን አንስተዋል::ከተነሱት ነጥቦች በእሁድ ቀን ማንም ሰው በገበያ ቦታዎች ውስጥ መገኘት እንደማይኖርበት;እሁድ ቀን ጠቅላላ መደብሮች ዝግ መሆን እንዳለባቸው:የዘበኞች ቁጥር መጨመር እንዳለበት:ወዛደሮች መታወቂያ እና ባጅ ሊኖረው እንደሚገባ እና መቆጣጠር አስፈላጊ መሆኑን:በንግዱ አከባቢ ዳር ዳሩን የመኪና መንገድ ላይ ያሉ በረንዳዎች እና መደቦች መጽዳት እንዳለበት በገበያ ውስጥ እሳት ማጥፊያዎች እና የውሃ ታንከሮች እንዲዘጋጁ ተወያይተውባቸዋል:; በዚህም መሰረት ነጋዴዎቹ የመተማመን መንፈስ ባይታይባቸውም ወኪሎቻቸውን መርጠው ስራውን ሊሰሩ የተስማሙ ሲሆን እስከዛሬ ያልታሰበ የእሳት ማጥፊያ እና የውሃ ታንከር አዘጋጁ እሳት ሊነሳ ይችላል የሚለውን ወያኔያዊ ሽብር በጥርጣሬ ተመልክተውታል::ምንሊክ ሳልሳዊ

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከታች በአስተያየት መስጫ ውስጥ የምትመለከቱት ምስል ከሶስት አመት በፊት ቦታው ለኢንቨስትመት ይፈለጋል ተነሱ የተባሉ ነጋዴዎች ምትክ ቦታ ይሰጠን እያሉ ሲከራከሩ የወያነ ሰራሽ የክልሉ ባለስልጣናት በድንገት የነጋዴዎችን መደብሮች ያቃተሉት ቦታ ሲሆን ይህ ቦታ ወደ መብራት ሃይል ሂደው ባለፈው ሱቆቻቸው የተቃተሉባቸው ነጋዴዎች ቦታ የነበረ ነው:: መንግስታዊ እሳት እየተከተለን ነው የሚሉ የመብራት ሃይል መደብር ባለቤቶች እና ተጎጂዎች ከ3 አመት በፊት የተቃጠለባቸው ቦታ ሕንጻ ለማሰራት ለአንድ ኢንቨስተር ተሰቶት ጥናት ተካሂዶ ቦታው ለኮንስትራክሽን አመቺ እንዳልሆነ እና አከባቢው ውሃ የሞላበት እና ሕንሳ ሊያሰራ የማይችል አፈሩም ለሕንሳ ግንባታ ተስማሚ እንዳልሆነ ይህ ቦታ ላይ ህንጻ ለማስገንባት ከፍተኛ ወጪ እና ዲዛይን የሚጠይቅ በመሆኑ ቦታው በዚህ ምክንያታዊ ጉዳዮች ለ3 አመት ያህል በምስሉ እንደምታዮት ታጥሮ የነበረ ሲሆን በአሁን ሰአት የተቃጠለው የሲጃራ ተራ እና የመብራት ሃይል ከቃጠሎ የተረፉ ቆርቆሮዎች እና ሌሎች ማቴሪያሎች መከመሪያ እየሆነ ነው::ምንሊክ ሳልሳዊ

Image

Image

Image

መኢአድ እና አንድነት መጋቢት 11 ቀን የቅድመ ዉህደት ፊርማ ይፈረማሉ ተብሎ ሲጠበቅ ፣ ከመኢአድ ፕሬዘዳንት አቶ አበባው መሃሪ በተጻፈ ደብዳቤ፣ ላልተወሰነ ጊዜ ፊርማው እንዲዘገይ መደረጉ በስፋት ተዘግቧል። አቶ አበባዉ የቅደመ ዉህደቱን ፊርማ ላለመፈረም ሶስት ያልተፈቱ ነጥቦች የሚሏቸውን ያቀርባሉ። ነጥቦቹም የዉህድ ፓርቲው ስያሜን፣ የመሪዎች መመዘኛን እና አንድነት ከመድረክ ጋር ያለዉን ግንኙነት የሚመለከቱ ናቸው። አቶ አበባዉ ባቀረቧቸው […]

Image

March 24, 2014 08:11

ለግልጽነትና ለተጠያቂነት ብሎም ለህዝቦች ጥቅም ቅድሚያ እንደሚሰጥ ህግ ደንግጎ የተቋቋመው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ ያቀረበውን የይግባኝ ማመልከቻ ተቀብሎ ማጽደቁ አነጋጋሪ ሆኗል። በ2009 ኢህአዴግን “ያወጣሁትን መስፈርት አታሟላም” በማለት እውቅና የከለከለው ይህ ተቋም፣ ኢህአዴግ በሚከሰስባቸው ዋና ጉዳዮች ለውጥ ሳያደርግ የራሱን ውሳኔ የገለበጠበት አካሄድ እየተመረመረ እንደሆነ የጎልጉል ምንጮች ጠቁመዋል።

የኢህአዴግን የእውቅና ይግባኝ ጥያቄ ተቀብሎ ያጸደቀው የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) የሚባለው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ነው። ተቋሙ ኢህአዴግ በ2009 አቅርቦት የነበረውን የእውቅና ጥያቄ ውድቅ ሲያደርግ የሰጠው ምክንያት “የመያዶች ህግ የተሰኘው” አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆንና በአገሪቱ የተተከሉት አፋኝ ህጎች እስካልተወገዱ ድረስ ማመልከቻው እንደማይታይ በማሳወቅ ነበር።

በ2009 ጠ/ሚኒስትር የነበሩት አቶ መለስ “መሰዋት” በስተቀር ኢህአዴግ አንዳችም ለውጥ ባላደረገበት ሁኔታ ባለፈው ረቡዕ መጋቢት 19፤2006 (March 19፤2014) ይኸው እውቅና ሰጪ ተቋም የራሱን ውሳኔ ቀልብሶ ለኢህአዴግ እውቅና መስጠቱ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። ከውሳኔው ቀናት በፊት በጓሮ የሚወጠን ድርጊት እንዳለ መረጃ ደርሶት የማሳሰቢያ ተቃውሞ ያሰራጨው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘውየሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት እንዳለው ከሆነ ከተገለበጠው ውሳኔ በስተጀርባ ሚስ ክሌር ሾርት ከፊት ረድፍ ተቀምጠዋል።

ማመልከቻው እንደገና እንዲታይና የቦርዱ የቀድሞ ውሳኔ እንዲገለብጥ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የቀድሞ የእንግሊዝ ዓለምአቀፍ ትብብር ሚ/ር የሆኑት ክሌር ሾርት መሆናቸውን የድርጅቱ መግለጫው ይፋ አድርጓል። እኚህ ግለሰብ የአፍሪካ አምባገነኖችን በመደገፍ የሚታወቁ ሲሆን ይህ ከጥቅማቸው ጋር የተሳሰረው ግንኙነታቸው አሁንም ኢህአዴግን እንዲደግፉ እንዳደረጋቸው ይነገራል፡፡ እንዲሁም በሌሎች ኢህአዴግ ባቋቋማቸው ዓለምአቀፋዊነት ሽፋን በተላበሱ ድርጅቶች ውስጥ የአመራር አባል በመሆን ሚስ ሾርት እንደሚያገለግሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የእንግሊዝ ፓርላማ አባል በነበሩበት ወቅትም ያላወጡትን ወጪ አውጥቻለሁ በማለት በብዙ ሺዎች የሚገመት ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉ መሆናቸው በወቅቱ ዴይሊ ቴሌግራፍ ባወጣው መረጃ አጋልጦ ነበር፡፡ የተወሰነውን ገንዘብ የመለሱ ቢሆንም ጋዜጣው በወቅቱ ያወጣው መረጃ ግለሰቧ የሕዝብን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው የተጠቀሙ “ሙሰኛ” መሆናቸውን ያስረዳል፡፡

ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንደሚሉት ከሆነ ባለፈው ረቡዕ ኦስሎ፤ ኖርዌይ ላይ ውሳኔው በተላለፈበት ወቅት ሚስ ሾርት በግልጽ የኢህአዴግ ደጋፊ በመሆን ተጽዕኖ በማድረግ ወደ ውሳኔ እንዲደረስ ግፊት አድርገዋል፡፡ ግለሰቧ ባላቸው ኃላፊነት በመጠቀም (የEITI የቦርድ ኃላፊ ናቸው) እንዲህ ዓይነቱ ግልጽና ወገናዊነት የታየበት ድጋፍ በማድረግ ከድርጅቱ አሠራር ውጪ ውሳኔ እንዲሰጥ ማድረጋቸው ለወደፊት በሚቀርቡ ማመልከቻዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የአሠራር ችግር እንደሚያስከትል ካሁኑ እየተጠቆመ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ከማዕድን ኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ ማህበራዊ ቀውስ የደረሰባቸው አካባቢዎች እንዳሉ የሚታወቅ ነው። በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱት አካባቢዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ባልጸዳ የሽያጭ ሂደት ሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ የገዙት ሻኪሶ የወርቅ ማዕድን በህዝብ ላይ እያደረሰ ችግር የሚዘገንን ነው። በየጊዜው ግልጽ ባልሆነ የማስፋፊያ ውል የሚፈናቀሉና ከፋብሪካው በሚወጣው ዝቃጭ ለከፍተኛ ብክለት የተጋለጡ ዜጎች ድምጻቸውን ሲያሰሙ መታሰራቸው፣ መገረፋቸው፣ ለይስሙላ በተቋቋሙ ፍርድ ቤቶች የተፈረደባቸው እንዳሉ ታዛቢዎች ያስታውሳሉ።

በጋምቤላ ኢንቨስትመንት ህዝብን እየበላ እንደሆነ የሚጠቁሙት ክፍሎች “ኢንቨስትመንት በከፍተኛ ደረጃ የሚደገፍና የሚበረታታ ተግባር ቢሆንም፣ ኢህአዴግ ፍትሃዊ በሆነ ደረጃ መጠቀም፣ ማስተዳደር፣ መምራትና ኢንቨስትመንቱን ህዝብ “የኔ” ብሎ በመቀበል እንክብካቤ እንዲያደርግ የሚያስችል ስርዓት አለማበጀቱን እንደ ዋንኛ ችግር ያነሳሉ። ኢህአዴግን ያዘጋጀው ህወሃት በራሱ ሰዎች አማካይነት ከውጪ ሰዎች ጋር እየተሻረከ ለህዝብ ጥቅም ሊውል የሚገባውን ሃብት ወደ ውስን ቋት እንደሚያግዝ የሚገልጹት እነዚሁ ክፍሎች” ይህ ዓለም የሚያውቀውን፣ ራሳቸው ህወሃቶችም የማይክዱትን እውነት ነው ብለዋል። ዜጎች የአገራቸው ሃብት ተጠቃሚ ከመሆን ይልቅ አካባቢያቸው ባደላቸው የተፈጥሮ ሃብት ሳቢያ መከራ ሲደርስባቸው፣ ሲሰቃዩ፣ ሲገረፉና፣ ሲገደሉ ማየት በተለመደባት ኢትዮጵያ ውስጥ ለኢህአዴግ የማይገባውን ካባ መደረብ ውሎ አድሮ የሚጋለጥ ክፉ ተግባር እንደሆነም አመልክተዋል።

አነስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙና ኢህአዴግ “ልማታዊ” የሚላቸው ኢንቨስተሮች ሳይሆኑ በከፍተኛ ደረጃ የሚመደብ መዋዕለ ንዋይ የሚያፈሱ ባለሃብቶች ኢንቨስት የሚያደርጉበትን አገር ለመምረጥ የመጀመሪያው መለያቸው የEITI ድረገጽ የአባል አገራት ዝርዝር እንደሆነ ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ። ኢህአዴግም አስፈላጊውን የምዝገባና የማመልከቻ መስፈርት በማሟላት የተቋሙን እውቅና የጠየቀው በድርጅቱ ድረገጽ ላይ ለመመዝገብ ነበር። የሁለት ጊዜ ሙከራው ቢከሽፋም በመጨረሻ ተሳክቶለታል። ስኬቱንና የስኬቱን መንገድ፣ በተለይም የዳይሬክተሯ ክሌር ሾርት ጉዳይና የተዘጋውን ፋይል በማንሳት ውሳኔው የተገለበጠበት አካሄድ ኦስሎ በሚገኘው ሃያ የቦርድ አባላት ባሉበት ተቋም ውስጥም ግራ ያጋባቸው እንዳሉ መረጃዎች አሉ።

ኢህአዴግ አጓድለሃል ተብሎ የሚከሰስባቸውን የዴሞክራሲ ግባቶችና የሰው ልጆች የተፈጥሮ መብቶች፣ አንዲሆም አፋኝ የተባሉትን ህጎች አጠናክሮ ተግባር ላይ ባዋለበት ሁኔታ፣ የዚሁ የአፈናው ሰለባዎች በተለያዩ ማጎሪያዎች ውስጥ ሆነው ድምጻቸውን በሚያስተጋቡበት ወቅት፣ EITI ከተቋቋመበት ዓላማና “መሰረቴ” ከሚለው የግልጽነትና ተጠያቂነት መርህ በተጻራሪ ግልጽነትና ተጠያቂነት በጎደለው መልኩ ለኢህአዴግ የደረበው ብሉኮ ጉዳይ እየተመረመረ አንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። ጉዳዩን የሚከታተሉ “ግልጽነትና ተጠያቂነት በኦስሎ ተፈረደባቸው” ሲሉ ምጸት ሰጥተዋል፤ የክሌር ሾርትንም አካሄድ በEITI የህወሃት/ኢህአዴግ ተወካይ በማለት ተችተዋል። ይህንኑ ጉዳይ እመልክቶ ከሳምንት በፊት ለሪፖርተር አጭር መልስ የሰጡት የማዕድን ሚኒስትሩ EITI ውሳኔውን ያነሳል የሚል ጥርጣሬ እንዳለባቸው የሚያሳብቅባቸው መልስ ሰጥተው እንደነበር ይታወሳል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ዳያስፖራው እንደሚገባው አለመንቀሳቀሱ እንደ ሽንፈትና አቅጣጫ መሳት እንደሚቆጠር ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ጠቁመዋል፡፡ ዳያስፖራው ከጥቃቅንና ስሜታዊ ጉዳዮች በማለፍ በከፍተኛና አገራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የማድረግ አመለካከቱን ማስፋት እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡ አለበለዚያ ኢህአዴግ እንደዚህ ዓይነቱን አጋጣሚ በመጠቀም የራሱን ገጽታ በዓለምአቀፍ መድረኮች እየወለወለ በማቅረብ የሥልጣን ዘመኑን እንደሚያራዝም ጠቁመዋል፡፡

golgul
http://raheltakele.wordpress.com/2014/0 … %E1%89%A0/


16th of March 2014 marks the 1000thday since Reeyot Alemu, a newspaper columnist and teacher, was arrested for working to ethiopianreview.comnews website which the Ethiopian State/court called ‘supporting terrorism’. On the same day, a twitter discussion focused on what happened to weaken the Ethiopian Press. Soleyana Shimeles, an activist for human rights and constitutional order, commented that the State ‘blames the victim after deliberately weakened the Press’. However, a twitter discussionfollowing her tweet revealed that it is not only the State that blames the victim. Many ‘activists’ do. 

A Short Story of the Press

It is the same regime, the current regime, which created the Free Press and then tried to kill it. It is not dead yet; but it is also hardly possible to say it is alive. Researchers (Terje and Hallelujah, 2009) put the history of the Free Press in the past two decades in three overlapping periods:  

“…Tafari and others draw three periods of the private press in Ethiopia. The first period was the chaotic period from 1991 to 1997 with a blooming of new newspapers and anarchy journalism. The second period, 1997-2005 saw the establishment of professionally and ethically integrated newspapers like Reporter, Addis Admas, Fortune and Capital. The last period goes from 2005 when press freedom again came under threat after editors and journalists were imprisoned and persecuted after alleged transgressions following the May 2005 elections…” 

If the paper, from which the above excerpt was taken, was written now there would be a fourth period too – we may call it a counter-attack period! The current Press, however is mostly led by different people from the media leaders who existed pre-2005, it is now trying to counter attack (in becoming too critical of the State in its own way) past the self-defense time that followed its threat after the contested election in 2005.

Elections have become nightmares of the independent media. Even though the Press tried to recover from its wound of post 2005 election, the Ethiopian State planned to narrow the sphere to clear way for the 2010 election: the penal code was revised in relation to Free Press issues; the anti-terrorism bill, which clearly puts Freedom of Expression in danger, passed; the highly emerging Addis Neger newspaper journalists were intimidated to have eventually exiled; other journalists and bloggers were prosecuted in relation to terrorism; a few media houses such as Addis Admass took measures to toned down choosing existence over professional integrity. 


What Went Wrong?

There are still a lot of independent magazines coming out on Saturdays monthly, fortnightly or weekly and a dozen of weekly newspapers. Nevertheless, their maximum circulation is not more than 10,000 of copies. Most of the publications lack original stories, they are full of opinions rather than news and features, opinion columns are full of ‘hateful insults’. Some of the publications copy contents from social media; some others write their opinions based on what the social media set; and, only a few strive to write original and researched stories – and these ones are not preferred by the State.

This severely discouraged the ethical and professionalism needs to publish a news outlet. The market is apparently dominated by ‘market-driven’ news publications regardless of their content. However, the debate about these news outlets ranged from the question of professionalism to ‘the requirement of balancing stories’ as a must.

Ethics and professionalism are not the only things that Ethiopian independent media are criticized for. Keeping balance between two sides of stories (especially while covering politics) is mentioned as a precondition to blossom a media industry that promotes plurality of ideas. In additon, some believe this isn’t achieved due to mere lack of the media performance while others argue that this incompetent and less diverse media was created after continuous intimidation of the Press by the State.  

Along with the above legitimate arguments are there also confusions by critiques of the Press: (1) criticizing the State has been labeled as ‘hate speech’ (which is also referred as ‘lack of ethics’; however, Zami FM and Ethio-channel newspaper, for example, were never criticized by State officials however they are not different (except for they are affiliated to the ruling party) from those criticized in lack of ethics); (2) upholding specific values has been considered as lack of balance to alternative sides of stories; and (3) the Press is generally considered as irresponsible unless the State highly regulated it.  
  

In the rush to criticize the media, no one remembered to ask the real causes of these problems. It is inevitable that every country of the world would have tabloids that focus on rumors and individuals stories. Countries would also have quality news outlets that do their jobs professionally and Ethiopia is not an exception. However, the latter needs to have freedom as a prerequisite. 

The State has labeled whatever comes out from the independent news outlets as lies and hates; so, officials cooperate least when the Press needs to access official information. This opens door for listening rumors and making speculations. The laws and intimidation against media houses and critical journalists drive professionals away and those “heroes” who militantly engage with State views dominated the sphere.  

What went wrong is the cause, not the consequence. The cause is lack of freedom to do the job. 

The Tale of Two Magazines: Lomi and AddisGuday

These (Lomi and AddisGuday) are two weekly magazines that have competing numbers of circulation while both being critical of the government. Yet, they are very different in any ethical standard.

The Deputy Minister in the Government Communication Affairs, Ato Shimeles Kemal, commented in a symposium that it’s ridiculous to say ‘there is no press freedom in Ethiopia’ where news outlets like Lomi magazine are published without a problem. The infamous Lomi magazine has the highest weekly circulation followed by AddisGuday, recent report from Ethiopian Broadcast Authority indicated. Lomi, in contrary, is not dearly loved by its own readers. Lomi barely writes an original content except in a couple of columns left for “Beteley lelomi” (“Exclusive to Lomi) and the editorial message. Its number of staff is very limited and the entire job is done on what is gathered from the Social Media. This magazine has no role other than disappointing public officials. 

On the other hand, AddisGuday publishes full content of original stories with an excellent layout design and serious concern to brand the news outlet. It has four-fold number of staff than Lomi has; its office size and weekly expenditures are also that fold. This is the kind of competition that discourages professional news outlets to be committed in doing for the best. The only way AddisGuday could survive from such competition is its brand – which brought it high value and number of advertisements. 

The State never took any measures on whatever Lomi publishes because it would rather encourage such incredible news outlets which it would be advantaged from for two purposes: (1) to show ‘we give freedom to even those who insult us’ card (knowing the fact that these outlets do not do any bad to the regime in a long term due to lack of credibility); (2) to prove the news outlets don’t do any good other than compiling angry comments from Social Media (by letting us see all the news outlets in the same eye). 

These rules of the State (its patience to Lomi) are not applicable for AddisGuday and the like. Since May 2013, the infamous ‘agenda’ column of another State-owned and poorly professional Addis Zemen newspaper (on page 4) is busy condemning AddisGuday for being a voice of oppositions and alleged terrorists; the page even went worse claiming the magazine has received money from Ginbot 7, a convicted terrorist group. In addition, in a so-called ‘study’ conducted jointly by Ethiopian Press Agency and Ethiopian News Agency, Addis Zemen claimed that AddisGuday, Lomi and other five magazines are voices of extremist political groups. The target of the ‘study’ gets clearer not only when one see that Lomi and AddisGuday are evaluated in the same criteria and found to be functioning similarly but also when one discovers that AddisGuday is put on top of the list of the ‘study’. It’s like accusing AddisGuday for Lomi’s fault. 

In Conclusion

The Press Freedom was a good thing in the beginning. The constitution gives the best it has. The very challenge is the ruling party – which has a long term dream in power. All the intimidations of the Press, prosecutions of journalists, unfair competition opportunities for preferred media houses, unfavorable investment ground for media business and etcetera happened to bring this dream of the incumbent true. There is no distinguishing line between the State and the ruling party, EPRDF. The ruling party wants the media to work in favor of it or it won’t exist; so does the State. 

Lack of freedom decreases creativity; but, that’s not the only challenge the Press is experiencing in the industry. The press, like any other private sector, it has to face being disfavored for State investments. There are no enough private publishers; even those existed do not risk their business involving themselves in printing news outlets. It has been criminalized for publishers to publish stories that might incite public protests. This is how the media business, we argue, is forced to face double-fated challenges than any other investment to primarily bother about ethics and professionalism. Currently, those who invest in the industry are not those who value professionalism most, they are those who love to play it hard – who take greater risks. 

Emphasizing freedom’s role in creating good Media, Tracy J. Ross opens and concludes her paper ‘Test of Democracy: Ethiopia’s Mass Media and Freedom of Information Proclamation (2010)’ in the following two paragraphs:

“David Ben-Gurion once said, ‘The test of democracy is freedom of criticism.’ Freedom of criticism has long been recognized as an essential, inalienable human right; a right that is thought to transcend political and geographical borders and applies regardless of culture, language, and national origin. In Ethiopia, as democracy begins to grow despite a history of corruption and totalitarianism, freedom of expression has proven to be an unsteady notion […] 

 “If Ethiopia hopes to move toward a more democratic State, it is critical to open the lines of communication between the government, media, and citizens. Freedom of expression is the only way to achieve an accountable and transparent government free from corruption and tyranny, while developing a professional and unbiased press. The press, in other words, must have the freedom to criticize the government.”

—-

Edited by: Soleyana Shimeles

መጭው ምርጫ ያሰጋው ወያኔ ሕዝቡን ለማደናበር እና ለማጭበርበር ሊረዳኝ ይችላል ያለውን አዲስ የልማታዊ ዲሞክራሲ ሰነድ እያዘጋጀ ሲሆን የባለራእዩ የሚሉት የመለስ ዜናዊ ትራንስፎርሜሽን እቅድ በዝግታ ለማስቀረት እና ሕዝቡ አኩርፎበታል ያለውን የማንፌስቶ ሰነድ ለማዘጋጀት በአቶ በረከት የሚመራው ቡድን ስራውን መጀመሩ ታውቋል::

ተቃዋሚዎች ከፍተኛውን ድምጽ አግኝተው ከጨዋታ ውጪ ያደርጉኛል የሚል ስጋት ያደረበት ወያኔ በ1997 የተከሰተው አይነት ሽንፈት እንዳይደርስበት ከሰነዱ ዝግጅት ጎን ለጎን ስብሰባዎችን በማካሄድ ተቃዋሚዎች ከምርጫ የሚወጡበትን እና ምርጫውን የሚያጭበረብርበትን አዲስ ስልት እየነደፈ መሆኑንም ምንጮች አክለው ገልጸዋል::የህዝቡ ብሶት እንደበረታ ያወቀው ሕወሃት መራሹ መንግስት በጭንቀት እና በምእራባውያን ጫና ተወጥሮ እንደሚገኝ ይታወቃል::

የመለስ ዜናዊ የትራንስፎርሜሽን እቅድ በሃገሪቱ የአገልግሎት አቅርቦት ማጣትን:ሙስናን :ድህነትን:የዜጎች ስደትን :ስራ አጥነትን የኑሮ ውድነትን ወዘት ከማስፋፋቱም በተጨማሪ ምንም አይነት ውጠት እንዳልታየበት እና እስካሁን የተተገበረው የተጠበቀውን ያህል ባለመሆኑ ከፕሮፓጋንዳ ያለፈ ምንም የፈየደው ነገር እንዳሌለ ኢሕኣዴግ በራሱ ድርጅታዊ ጉባዬ እና ስብሰባዎች መናገር ከጀመረ ሰነባብቷል::ምንሊክ ሳልሳዊ

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዕድገትና የለውጥ እቅድ ለማሳካት አስፈላጊ ከሆኑት ጉዳዮች መካከል የኤሌክትሪክ አቅርቦት ትልቁን ሚና ይዞዋል። በኢትዮጵያ የኤሌክትሪኩን አገልግሎት ዘርፍ የማስፋፋቱ ስራ ከተጀመረች ብዙ ዓመታት ቢሆነውም ፣ ውጤቱ እስካሁን የሚፈለገው ደረጃ ላይ ገና አልደረሰም።

ዛሬ መጋቢት 14 ቀን ነው፡፡ የኢህአፓው መሪ ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ከደርግ ዋና ጽ/ቤት ለተላኩ ወታደሮች እጄን አልሰጥም ብሎ ከኪዳኔ በየነ ህንጻ (በድሮው አጠራር ፊሊፕስ ህንጻ) ላይ ራሱን ወርውሮ ህይወቱን ያጠፋው ልክ በዛሬዋ እለት በ1969 ዓ.ል. ነው፡፡ ኢህአፓዎች ተስፋዬ ደበሳይ ራሱን ያጠፋበትን ያንቺን ቅጽበት የቆራጥነትና የጽናት ተምሳሌት አድርገው ይዘክሯታል፡፡

Image

በእርግጥም ተስፋዬ ደበሳይ ቆራጥ ነበር፡፡ ላመነበት ዓላማ ሺዎችን አንቀሳቅሷል፡፡ ለጠላቶቹ ሳይንበረከክ ህይወቱን ሰውቷል፡፡ በርሱ ሞት ያዘኑት ኢህአፓዎች “ተስፋዬን ከምናጣ ሌሎች የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቶቻችን በሙሉ ቢጠፉ ይሻለን ነበር” በማለት መሪር ሐዘናቸውን አሰምተዋል፡፡ የደርግ መንግሥት እርሱ በሞተበት ዕለት ባወጣው መግለጫ አንድ ክፍለ ጦር ሰራዊት የተደመሰሰ ያህል ነበር የፎከረው፡፡
ተስፋዬ ደበሳይ ማን ነው? በኢህአፓ ውስጥ የነበረው ሚና ምን ይመስል ነበር?… ህይወቱ የተፈጸመው እንዴት ነው? እስቲ በጥቂቱ እንየው፡፡
*****
ኢሮብ በትግራይ ክፍለ ሀገር፣ [deleted] አውራጃ ውስጥ የምትገኝ ወረዳ ናት (በአሁኑ የአስተዳደር አወቃቀር በትግራይ ክልል፣ ምስራቃዊ ዞን ውስጥ ነው የምትገኘው)፡፡ በዚህች ወረዳ ከትግርኛ ተናጋሪው ብሄረ-ትግራይ በተጨማሪ ኢሮብ የሚባለው አነስተኛ ብሄረሰብ ይኖራል፡፡ ይህ ህዝብ በውስጡ ሶስት ዐይነት ማህበረሰቦች አሉት፡፡ አንደኛው ደመክኒቶ ይባላል፡፡ የዚህ ማህበረሰብ አባላት የካቶሊክ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ሁለተኛው ማህበረሰብ “ሀሳበላ” የሚባል ሲሆን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ይበዙበታል፡፡ ሶስተኛው ማህበረሰብ “ዳልገዳ” ይባላል፡፡ እነዚህኛዎቹ ደግሞ ሙስሊሞች ናቸው፡፡ እነዚህ ማህበረሰቦች የሚናገሩት ቋንቋ በኤርትራ ምድር ከሚነገረው የሳሆ ቋንቋ ጋር ተመሳሳይነት አለው፡፡ ሆኖም ኢሮብ እና ሳሆ በኢኮኖሚ ስምሪታቸው ይለያያሉ፡፡ የሳሆ ህዝብ ሙሉ በሙሉ አርብቶ አደር ነው፡፡ ኢሮቦች ግን በእርሻ ስራና በአነስተኛ ዕደ-ጥበባት ነው የሚተዳደሩት፡፡ የኢሮብ ወረዳ ተራራና ሸንተረር ይበዛዋል፡፡ በአካባቢው ካሉት ተራሮች መካከል “አሲምባ” እና “አይጋ” ትልልቆቹ ናቸው፡፡

በዚህች የኢሮብ ወረዳ ውስጥ አሊቴና የምትባል አነስተኛ መንደር አለች፡፡ ይህች መንደር የአጋሜ አውራጃ ርዕሰ ከተማ ከሆነችው አዲግራት 35 ኪሎ ሜትር ያህል ትርቃለች፡፡ የመንደሪቷ ነዋሪዎች በአብዛኛው ካቶሊክ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ተሰፋዬ ደበሳይ በዚያች አነስተኛ መንደር ውስጥ ነው በ1933 የተወለደው፡፡ ወላጅ አባቱ አቶ ደበሳይ ካህሳይ ይባላሉ፡፡ እናቱ ደግሞ ወ/ሮ ምህረታ ዓዶ-ዑማር ነበሩ፡፡ ተስፋዬ የቤተሰቡ የበኩር እና ብቸኛ ወንድ ልጅ ነው፡፡ ከርሱ በኋላ የተወለዱት ስድስት ልጆች በሙሉ ሴቶች ናቸው (ለዚህ ጽሑፍ የመረጃ ምንጭ ከሆነው የመጋቢት ወር/2005 የኢህአፓ ዘገባ ለመረዳት እንደተቻለው ከስድስት እህቶቹ መካከል አምስቱ በህይወት ይገኛሉ፤ ወላጅ አባቱም በህይወት አሉ)፡፡

አሊቴና በዚያ ዘመን ትምህርት ቤት አልነበራትም፡፡ ስለዚህ ህጻኑ ተስፋዬ የትምህርት ጉጉት ቢኖረውም እድሜው አስር ዓመት እስኪሆነው ድረስ ትምህርት ቤት ለመግባት አልታደለም፡፡ በ1943 ግን አዲግራት ከሚኖሩት አክስቱ ዘንድ ሄደና ትምህርት ቤት እንዲያስገቡት ለመናቸው፡፡ አክስቱም በከተማዋ ከሚገኝ ታዋቂ የካቶሊክ ሚሽን ትምህርት ቤት አስገቡት፡፡ ተስፋዬም እስከ ስምንተኛ ክፍል በዚሁ ት/ቤት ከተማረ በኋላ ዘጠኛ ክፍልን መቀሌ በሚገኘው አጼ ዮሐንስ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አጠናቀቀ፡፡ ይሁንና በወቅቱ የትምህርት ወጪውን በራሱ ሸፍኖ መማር እንደማይችል በመረዳቱ ፊት ወደ ነበረበት የካቶሊክ ት/ቤት ተመለሰ፡፡ እዚያም እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል ከተማረ በኋላ ለከፍተኛ ትምህርት ወደ ጣሊያን ሀገር ተላከ፡፡ በሀገረ ኢጣሊያ ሮም ከተማ ካለው Urbaniana University በፍልስፍና ትምህርት የዶክትሬት ዲግሪውን ተቀበለ፡፡

ተስፋዬ በስራው ዓለም ሲሰማራ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰራበት መስሪያ ቤት የማስታወቂያና መርሐ ብሄር ሚኒስቴር ነበር፡፡ በዚህ መስሪያ ቤት የምርምር ክፍል ሃላፊ ሆኖ እየሰራ በማታው ክፍል የአባዲና ፖሊስ ኮሌጅ አስተማሪ ለመሆን በቅቷል፡፡ በ1964 ለተጨማሪ ስልጠና ወደ አውሮጳ (ስዊዘርላንድ) ተልኳል፡፡ በዚያ እያለም በመቀጣጠል ላይ የነበረው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ልቡን ስለወሰደው ትምህርቱን ትቶ ሙሉ በሙሉ ወደዚያው ገብቷል፡፡

ታዲያ እርሱ ወደ ስዊዘርላንድ በሄደበት ወቅት በአውሮጳው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማህበር እና በአሜሪካው የተማሪዎች ማህበር መካከል ከፍተኛ ውዝግብ ይካሄድ ነበር፡፡ ሁለቱ ማህበሮች የተወዛገቡት የድርጅት ምስረታና አደረጃጀት፣ የኤርትራ ጥያቄ፣ የብሄረሰቦች መብት፣ የትጥቅ ትግል አስፈላጊነት በመሳሰሉ አርዕስተ ነገሮች ዙሪያ ነበር፡፡ በጊዜው የድርጅት አስኳል ለመመስረት ጥረት ያደርግ የነበረው የአልጄሪያው የስደተኛ ተማሪዎች ቡድን ከአሜሪካው ማህበር ጋር ተቀራራቢ አቋም አሳየ፡፡ የአውሮጳው ማህበር መሪዎች በሀገር ቤት ከነበሩ ጥቂት ተማሪዎች ጋር አንድ ዓይነት አቋም ላይ ደረሱ፡፡ ተስፋዬ ደበሳይ ግን የአውሮጳው ማህበር መሪዎችን ውሳኔ በመቃወም ከአልጄሪያው ቡድን ጋር ወገነ፡፡ በዚህም መሰረት የአልጄሪያው ቡድን፣ የአሜሪካው ቡድንና አውሮጳ የነበሩት ጥቂት ተማሪዎች በድርጅት ምስረታ ሂደት ላይ መነጋገር ጀመሩ፡፡ ውይይቱ ለወራት ሲብላላ ከቆየ በኋላ በዓለም ዙሪያ ተበታትነው የነበሩ ሌሎች ኢትዮጵያዊ ተማሪዎችንም ማካለል ጀመረ፡፡ በስተመጨረሻም በሚያዚያ ወር 1964 “የኢትዮጵያ ህዝቦች አርነት ድርጅት” (ኢህአድ) ተወለደ፡፡ ተስፋዬ ደበሳይም ለድርጅቱ አመራር ከተመረጡ ሰባት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት አንዱ ሆነ፡፡
*****
ኢህአድ የተወለደው በውጪ ሀገር ነው፡፡ ከ1964-1966 በነበሩት ዓመታት ዋነኛ ስራው ድርጅቱን ማስተዋወቅና አባላትን ማሰባሰብ ነበር፡፡ ከፍልስጥኤም ነጻ አውጪ ድርጅትና ከኤርትራ ግንባሮች የተሰጠውን ድጋፍ በመጠቀም የትጥቅ ትግል የመጀመር እንቅስቃሴ ሲያደርግም ቆይቷል፡፡ የድርጅቱ ቀዳሚ ዓላማ ከገጠር በሚጀመር የትጥቅ ትግል በረጅም ጊዜ የስርዓት ለውጥ ማምጣት ነበር፡፡ የኢህአድ መሪዎችም ድርጅቱ ቀዳሚ ሰራዊቱን ሊያሰማራበት ወዳሰበው የአሲምባ ተራራ በመሄድ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራር እንዲሰጡ ለማድረግ ታስቧል፡፡ ይሁንና በ1966 የፈነዳው የኢትዮጵያ አብዮት የትግሉን አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ ቀየረው፡፡ የአሮጌው ስርዓት መውደቅ አይቀሬ እንደሆነ ሁሉም በየፊናው አወቀ፡፡ “በርሱ ቦታ ተተክቶ ሀገሪቱን የሚመራው ማን ነው?” የሚለው ጥያቄ ግን አነጋጋሪ ሆነ፡፡ በዚህም በተራማጅ አብዮተኞች መካከል ከፍተኛ ውይይት ተቀሰቀሰ፡፡ በመደምደሚያውም የፓርቲ ቅርጽ የነበራቸው ቡድኖች በከተሞች አካባቢ የፖለቲካ ትግል ቢያደርጉ ጠቀሜታው ከፍ ያለ እንደሚሆን ከስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ በመሆኑም በውጪ ሀገር የነበረው የኢህአድ አመራር ወደ ሀገሪቷ ለመግባት ወሰነ፡፡

ከኢህአድ ከፍተኛ መሪዎች መካከል በቅድሚያ ወደ አዲስ አበባ የገባው ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ነው፡፡ ጊዜውም ሰኔ 1966 ነበር፡፡ በወቅቱ የወታደሮች ቡድን የሆነው ደርግ ተመስርቶ የአጼውን መንግሥት ለመጣል እያኮበኮበ ነበር፡፡ በሀምሌ ወር አጋማሽ ላይ ደርግ የልጅ እንዳልካቸውን ካቢኔ በመሻር ልጅ ሚካኤል እምሩ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ መረጣቸው፡፡ ልጅ ሚካኤልም ካቢኔአቸውን ሲያቋቁሙ በስዊዘርላንድ የሚያውቁትን ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይን የመሬት ይዞታ ሚኒስትር እንዲሆን ጠየቁት፡፡ እርሱ ግን ከውጪ የመጣው ለዚያ አልነበረምና አንዳች ምክንያት ፈጥሮ አሉታዊ መልስ ሰጣቸው፡፡ በምትኩ በመስሪያ ቤቱ በኤክስፐርትነት ቢቀጠር ለመስራት ፈቃደኛ እንደሆነ ገለጸላቸው፡፡ በዚህም መሰረት ከነሐሴ 1966 ጀምሮ የመስሪያ ቤቱ ሰራተኛ ሆነ፡፡

ተስፋዬ ወደ ሀገር ቤት ከተመለሰ በኋላ ድርጅቱን በማስፋፋትና አባላትን በማደራጀት ስራ ላይ ነበር የተጠመደው፡፡ የድርጅቱ ልሳን የሆነችውን “ዲሞክራሲያ” ጋዜጣ ከሚያወጡ አርታኢያን መካከልም አንዱ ነበር፡፡ በድርጅቱ የመጀመሪያ ጉባኤ ዋና ጸሐፊ ሆኖ የተመረጠው ብርሃነ መስቀል ረዳ ከሰራዊቱ ጋር ስለነበር በርሱ ቦታ በጊዜያዊነት አመራር የሚሰጠውም ተስፋዬ ደበሳይ ነበር፡፡ በወቅቱ በድርጅቱ አመራር ላይ ከነበሩትም መካከል በዕድሜም ሆነ በትምህርት ደረጃ የሚበልጠው እርሱ ነበር፡፡

ተስፋዬ እስከ ታህሳስ 1967 በአዲስ አበባ ከተማ ከቆየ በኋላ ከመሬት ይዞታ ጋር ለተያያዘ የመስክ ስራ ወደ ትግራይ ተጓዘ፡፡ እግረ መንገዱንም አሲምባ የሚገኘውን የድርጅቱን ጀማሪ ሰራዊት ለመጎብኘት ወደዚያው ጎራ አለ፡፡ በጊዜው የነበረውን የሀገሪቱን የፖለቲካ ሁኔታ ለሰራዊቱ ካብራራ በኋላ ግን ያልተጠበቀ ችግር ተከሰተ፡፡ ስምንት ያህል የሰራዊቱ አባላት ከጀማሪ ሰራዊቱ በመነጠል ለደርግ እጃቸውን ሰጡ (እጃቸውን የሰጡት ሰዎች ተስፋዬ መኮንን፣ ኃይለ እየሱስ ወልደ ሰንበት፣ አበበ በየነ፣ ዘከሪያ መሐመድ፣ አያሌው ከበደ፣ ጋሻው መንግሥቱ፣ ሀይሌ ወልደ ጊዮርጊስና ዳዊት አሰፋ ነበሩ፤ እነዚህ ሰዎች በ1968 መጀመሪያ ላይ “ማሌሪድ”፣ ማለትም “የማርክሲስት ሌኒኒስት ሪቮሉሽናሪ ድርጅት”ን መስርተዋል)፡፡ ታዲያ የነዚህ ሰዎች ከኢህአፓ አፈንግጦ መውጣት የዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይን ማንነት አጋለጠው፡፡ በመሆኑም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህቡዕ ለመግባት ተገደደ፡፡
*****
ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ህቡዕ ከገባ በኋላ የሙሉ ጊዜ አብዮታዊ ሆኗል፡፡ ኢህአድን በሙሉ አቅሙ አገልግሏል፡፡ በነሃሴ ወር 1967 ድርጅቱ ስሙን ቀይሮ “ኢህአፓ” (የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ) የተሰኘውን ዝነኛ መጠሪያውን የያዘበትን ጉባኤ በዋናነት ያዘጋጀውም እርሱ ነው፡፡ የድርጅቱ የፍልስፍና ሊቅ (ideologue) ሆኖ የሚያገለግለውም እርሱ ነበር፡፡ በኢህአፓ መስራች ጉባኤ “ዋና ጸሐፊ” የሚባል የስልጣን ተዋረድ ሲሻር በቀዳሚነት የማዕከላዊ ኮሚቴ ጸሐፊ ሆኖ ማገልገል የጀመረው እርሱ ነበር (ይህ የጸሐፊነት ቦታ በየጊዜው ይለዋወጥ ነበር፤ ጸሐፊው የሚመረጠውም በፓርቲው ጉባኤ ሳይሆን በፖሊት ቢሮው ነው)፡፡

እስከ 1968 አጋማሽ ድረስ በነበረው ጊዜ የኢህአፓ አመራሮች ማንነት በግልጽ አይታወቅም፡፡ በዚያን ጊዜ ህቡዕ ለመግባት የተገደዱት ብርሃነ መስቀል ረዳ እና ተስፋዬ ደበሳይ ብቻ ናቸው፡፡ በመሆኑም አብዛኛው የፓርቲው ስራ የሚከወነው በተስፋዬ ነበር (ብርሃነ መስቀል ለፖሊት ቢሮው ስላልተመረጠ ከፍተኛ ሃላፊነት አልተሰጠውም፤ በተጨማሪም ከሌሎች መሪዎች ጋር መነታረክ ጀምሮ ነበር) ፡፡

የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዜያዊ ጽ/ቤት ከተመሰረተ በኋላ ግን አመራሩን ለአደጋ የሚያጋልጥ ሁኔታ ተከሰተ፡፡ በጽ/ቤቱ የተመረጡት ከፍተኛ ካድሬዎች የኢህአፓ መሪዎችን ስለሚያውቋቸው ለደርግ አሳልፈው ይሰጡአቸዋል የሚል ስጋት ሰፈነ፡፡ በመሆኑም በ1968 መጨረሻ ገደማ ሁሉም መሪዎች ህቡዕ ለመግባት ተገደዱ፡፡ ታዲያ የኢህአፓ የትግል ስትራቴጂም መለወጥ የጀመረው ከዚህ ወቅት ጀምሮ ነው፡፡ ከ1968 ክረምት ወራት በፊት በከተሞች አካባቢ የፖለቲካ ትግል ብቻ ያደርግ የነበረው ኢህአፓ የደርግ ፋሺስትነትን ለመከላከል በሚል የከተማ ትጥቅ ትግል የጀመረው ያኔ ነው፡፡

አንዳንድ ወገኖች የትጥቅ ትግሉ በዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ግፊት የመጣ ነው ይላሉ፡፡ ከሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማሪያም ጀምሮ መገደል ያለባቸውን ከፍተኛ የደርግና የመኢሶን ባለስልጣናት ዝርዝር እያዘጋጀ የሞት ፍርድ ያስወስን የነበረው ተስፋዬ ደበሳይ ነው በማለት ይሞግታሉ፡፡ ከዚህ እልፍ ሲል ደግሞ የተስፋዬን ትግሬነት በመጥቀስ ብቻ ሻዕቢያ በአዲስ አበባ ከተማ ሽብር ለመቀስቀስ የመደበው የጥፋት ወኪል ነው የሚል መረጃ የሚያስነብቡ ጽሁፎችን ማየት የተለመደ ሆኗል (ለነገሩ ተስፋዬ የኢሮብ ተወላጅ ነው እንጂ ትግሬ አልነበረም)፡፡ ይሁንና እንዲህ ዓይነቱን የተናጥል ክስ በተስፋዬ ላይ የሚያጠናክር ማስረጃ የለም፡፡ ኢህአፓ የከተማ ትጥቅ ትግል እንዲጀምር የወሰኑት ብዙሃኑ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ናቸው እንጂ ተስፋዬ ደበሳይ ብቻ አልነበረም፤ ውሳኔውን የተቃወሙት ጌታቸው ማሩ እና ብርሃነ መስቀል ረዳ ብቻ ነበሩ (በጊዜው የኢህአፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት የነበሩት ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ፣ ዮሐንስ ብርሃኔ፣ ዮሴፍ አዳነ፣ ክፍሉ ታደሰ፣ ክፍሉ ተፈራ፣ ዘርዑ ክህሸን፣ ኢያሱ አለማየሁ፣ ሳሙኤል አለማየሁ፣ አበራ ዋቅጅራ፣ ፍቅሬ ዘርጋው፣ ጸጋዬ ገብረመድህን፣ ብርሃነ መስቀል ረዳ፣ ጌታቸው ማሩ እና ጸሎተ ህዝቅያስ ነበሩ)፡፡

*****
መስከረም 13 ቀን 1969፡፡ በዚህች ዕለት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያምን ለመግደል ያልተሳካ ሙከራ ተደረገ፡፡ በዚህም የተነሳ ኮሎኔሉ ኢህአፓን ለማጥፋት ቆርጠው ተነሱ፡፡ በስውር የሚያካሄዱትን ርሸና ይፋ ማውጣት ጀመሩ፡፡ በታህሳስ ወር የኮሎኔሉን እርምጃ የሚቃወሙ መኮንኖች በደርግ ውስጥ መዋቅራዊ ለውጥ አካሄዱ፡፡ ይሁን እንጂ ከአንድ ወር በኋላ (ጥር 25/1969) ኮሎኔል መንግስቱ ማንም ባላሰበው መንገድ ጠላቶቻቸውን በማጥፋት “ለምሳሌ ያሰቡንን ቁርስ አደረግናቸው” በማለት አወጁ፡፡ “አብዮቱ ከተከላካይነት ወደ አጥቂነት ተሸጋግሯል” ተባለ፡፡ “ቀይ ሽብር” በይፋ ታወጀ፡፡ “ነጻ እርምጃ” ተፈቀደ፡፡

በወቅቱ የኢህአፓው ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ አዲስ አበባ ውስጥ እንደነበረ ደርጎች ያውቁ ነበር፡፡ ነገር ግን አድራሻውን በትክክል ማወቅ አልቻሉም፡፡ ኢህአፓም ከጥር ወር መጨረሻ ጀምሮ እየተባባሰ በመሄድ ላይ የነበረውን የደርግ እርምጃ ለመቀልበስ እንደማይችል አውቆታል፡፡ ይሁንና የከተማውን የትጥቅ አመጽ አላቋረጠም፡፡ ደግሞም ዋና መሪውን ከደርግ አፍንጫ ስር አውጥቶ ከደህና ቦታ ለማድረስ አልሞከረም፡፡

ታዲያ ኢህአፓዎች መሪአቸው ከከተማው ወጥቶ ለደህንነቱ አስተማማኝ በሆነ ቦታ ቢደበቅ ይፈልጉ ነበር፡፡ በተለይ በመጋቢት ወር አጋማሽ (1969) ከሚካሄደው የቤት ለቤት አሰሳ ነፍሱን እንዲታደግ ይመኙ ነበር፡፡ ይሁንና መሪው ከከተማው ለመውጣት ምንም ዓይነት ፍላጎት አልነበረውም፡፡ “በዚህ ክፉ ቀን ተከታዮቼን ጥዬ ከከተማ አልሰደድም” በማለት ቆርጧል፡፡ አሰሳው ከመጀመሩ አስቀድሞ በነበሩት ቀናት ራሱ ሸኝ ሆኖ በልዩ ልዩ እርከን ላይ ያሉ ኢህአፓዎችን ከከተማው ወደ ገጠር ይሸኝ ነበር፡፡ ለምሳሌ የቤት ለቤት አሰሳው ከሚካሄድበት ዕለት በፊት በነበሩት ቀናት (ከመጋቢት 10-13 ባሉት ቀናት) ተስፋዬ ደበሳይ በርካታ የኢህአፓ አባላትን ከከተማ እያስወጣ ወደ ገጠር መሸኘቱ ተመዝግቧል፡፡ በነዚያ ቀናት በርካቶች ወደ አሲምባና ሰሜን ሸዋ አካባቢዎች ሄደዋል፡፡ እርሱ ግን እዚያው ሆኖ አሰሳው የሚያመጣውን ውጤት ለማየት ይጠባበቅ ነበር፡፡
*****
ዕለቱ መጋቢት አስራ 15/1969 ነው፡፡ ደርግ የቤት ለቤት አሰሳውን እያካሄደ ነው፡፡ እያንዳንዱ ቤት እየተከፈተ ይፈተሻል፡፡ “አናርኪስት” ተብሎ የተጠረጠረ ሰው እየተያዘ ወደ ማዕከላዊ ምርመራና የቀበሌ እስር ቤቶች ይጋዛል፡፡ ከእስራቱ ለማምለጥ የሞከረ ያለ ምንም ጥያቄ ይገደላል፡፡ ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ያረፈበት የበሪሁን ማሪዬ ቤትም እንደሚፈተሽ መረጃው ለኢህአፓ አሀዶች ደርሷል፡፡ በመሆኑም የተስፋዬን ህይወት ለመታደግ ቀኑን በመንግሥት ቢሮ ውስጥ ተደብቆ ማሳለፍ አስፈላጊ እንደሆነ ታምኖበታል (በወቅቱ ቢሮዎች አይፈተሹም ነበር)፡፡ በዚህ መሰረት ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይና በሪሁን ማሪዬ አምባሳደር ቴአትር አካባቢ ባለው ኪዳኔ በየነ ህንጻ ውስጥ በሚገኘው የበሪሁን ሚስት ቢሮ ለመደበቅ ወሰኑ፡፡ በበሪሁን ማሪዬ ሾፌርነትም ከመርካቶ አካባቢ ወደ አምባሳደር ቴአትር እንቅስቃሴ ጀመሩ፡፡ ተክለ ሀይማኖት አካባቢ ሲደርሱ ግን ተስፋዬን በሚያውቅ ሰው እይታ ውስጥ ገቡ፡፡ ያ ሰው ወዲያኑ ለደርግ ጸጥታ ሀይሎች በመደወል የተስፋዬን መገኘት አበሰራቸው፡፡ ለራሱ ደግሞ በቀስታ (እነርሱ ሳያዩት) ከኋላ እየነዳ ተከተላቸው፡፡ ደርጎች ለወራት ሲፈልጉት የነበረው አውራ ጠላታቸው ዱካ መገኘቱን ሲሰሙ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ተባለው ስፍራ አሳሽ ጦር ላኩ፡፡

ተስፋዬ ደበሳይና በሪሁን ማሪዬ ወደ ኪዳኔ በየነ ህንጻ ገቡ፡፡ ሆኖም ህንጻው እንደጠበቁት ነጻ ሆኖ ስላላገኙት ወደ መጡበት ለመመለስ ወሰኑ፡፡ ፈጠን ባለ እርምጃ ከህንጻው መውጫ በር ላይ ሲደርሱ ግን ለነርሱ የተላከው አሳሽ ጦር ህንጻውን ከቦ አገኙት፡፡ በዚህን ጊዜም ወደ ህንጻው ለመመለስ ሩጫ ጀመሩ፡፡ ሆኖም በቅርብ ርቀት ላይ የነበሩት አሳሾች ተኮሱባቸው፡፡ በሪሁን ማሪዬ ወዲያውኑ ተገደለ፡፡ ተስፋዬ ደበሳይ ደግሞ ግንባሩ ላይ ቆሰለ፡፡ እርሱ ግን አልቆመም፡፡ የህንጻውን ፎቆች በትጋት ወጣ፡፡ ከስድስተኛው ፎቅ ላይ ሲደርስ አንድ ክፍት ቢሮ አየ፡፡ ከቢሮው በመግባት በመስኮቱ በኩል ወደ ውጪ ተወረወረ፡፡ ከሰከንዶች በኋላም መሬት ላይ ተፈጠፈጠ፡፡ የኢህአፓው መሪ እንዲህ ባለ አሳዛኝ ትራጄዲ ከምድር ላይ ተሰናበተ፡፡
*****
ስለዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ በኢህአፓ ወገን በይፋ የተጻፈው ታሪክ ይህ ነው፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ አንዳንድ ጸሐፊዎች አሟሟቱን በሚመለከት አወዛጋቢ ታሪኮችን ማስነበብ ጀምረዋል፡፡ ውዝግቡ ለጊዜው አይጠቅመንም፡፡ የታሪክ ጸሐፊዎች ሐቁን እስከሚያወጡት ድረስ አወዛጋቢውን ታሪክ ብንዘለው ይሻላል፡፡ በጣም የምንስማማበት ጉዳይ ቢኖር ሀይሌ ፊዳ የመኢሶን ግርማ እና ኩራት እንደነበረው ሁሉ ተስፋዬ ደበሳይም የኢህአፓ አውራ የነበረ መሆኑን ነው፡፡ መኢሶንን ያለ ሀይሌ ፊዳ፣ ኢህአፓንም ያለ ተስፋዬ ደበሳይ ማሰብ አይቻልም፡፡ ሁለቱም የአንድ ትውልድ ፈርጦች ነበሩ፡፡ ሁለቱም በተሳሳተ ስሌት እርስ በርስ ተዋጉ፡፡ ሁለቱም በጨካኙ ስርዓት ተበሉ፡፡

የዶ/ር ተስፋዬ ታሪክን የማሳርገው በሚከተለው ታዋቂ የኢህአፓ መዝሙር ነው፡፡
“ቢወቀጥ አጥንቴ ቢንቆረቆር ደሜ
ለአዲስ ሥርዓት ልምላሜ
ፍጹም ነው እምነቴ
ትግሉ ነው ሕይወቴ”
*****
አፈንዲ ሙተቂ
መጋቢት 14/2006

(የትረካ ምንጮች)
1. ባቢሌ ቶላ፣ የትውልድ እልቂት፣ 1985፣ አዲስ አበባ
2. ክፍሉ ታደሰ፣ “ያ ትውልድ” ቅጽ 1፣ 1987፣ አዲስ አበባ
3. ክፍሉ ታደሰ፣ “ያ ትውልድ” ቅጽ 2፣ 1990፣ አዲስ አበባ
4. የያ ትውልድ ተቋም፣ “ዝክረ ተስፋዬ ደበሳይ”፣ መጋቢት 2005፣ ከኢንተርኔት የተገኘ
5. ገነት አየለ አንበሴ፣ የሌተና ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ትዝታዎች፣ 1994፣ አዲስ አበባ
(አፈንዲ ሙተቂ)
The writer, Afendi Muteki, is a researcher of the Ethnography and History of the peoples of East Ethiopia. He is an author of “Harar Gey”, an Ethnography book about the historical city of Harar. You can read some of his articles on his blog and his facebook page.

(አዲስ ጉዳይ፤ ቅጽ ፰ ቁጥር ፳፻፰፤ መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም.) ሃይማኖት ከአስተዳደሩ የተለየ በጣም ጥልቅ ነገር ነው፡፡ ሃይማኖት ማለት ከአንድ ግለሰብ ኾነ ከጥቂት ሰዎች አመራር የተለየና የራሱ የኾነ ዶግማ፣ ቀኖና እና ትውፊት፣ ባህልና ሥርዓት ያለው መኾኑ መታወቅ ይኖርበታል፡፡ በሥነ ምግባር ደረጃ እኔን ጨምሮ ኹሉም ሰው ችግር ሊኖርብን ይችላል፡፡ ይኹንና ይኼ የሥነ ምግባር ጉዳይ ሊፈታ የሚችለው በመነጋገርና …

ከወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች የእስርና እንግልት ማብራሪያ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራና ድርጅት ጉዳይ ም/ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ በደቡብ ቀጠና በወላይታ ዞንና በሲዳማ ዞን አዋሳ ከተማ ያሉ ከፍተኛ አመራሮች ጋር የፓርቲውን የትግል ስትራቴጅክ ዕቅዶች ላይ ማብራሪያ፣ ደንብና ፕሮግራም ለመስጠት እንዲሁም የስራ ጉብኝት ለማድረግ በ 12/07/06 ወደ ወላይታ ዞን ሶዶ […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ልሳን የሆነው ፍኖተ-ነጻነት ጋዜጣ በግማሽ ሚሊዮን ብር የራሱን ማተሚያ ማሽን በመግዛት እና በመትከል በቅርብ ቀን ሕትመቱ ለሕዝብ በገበያ ላይ እንድሚውል ተገልጸ፡፡ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ሐላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ተፈራ እንደገለጹት፤ የአንድነት ፓርቲ እና የፍኖተ ነጻነት የኢዲቶሪያል ቦርድ ባለፈው አመት ያሳትማት የነበረችው ጋዜጣ በ2005 ዓ. ም. በጉልበት እንድትዘጋ በመደረጉ እና የመንግስት […]

ከተመሰረተ ከ70 ዓመታት በላይ ዕድሜ እንዳስቆጠረየሚነገርለት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኘው የብርሃንና ሠላም ማተሚያ ቤት ዛሬ ቃጠሎ እንደደረሰበት ወኪላችን ከአዲስ አበባ ዘገበ።

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ሩስያ ክሪሚያን ይፋ የግዛትዋ አካል አድርጋ ከተቀበለች በኋላ ሩስያ በዚያ በይፋ የጦሩ ቁጥጥሯን አጠናከረች። ከዩክሬይን በተገነጠለችው ክሪሚያ ውስጥ ባሉት 147 የዩክሬይን የጦር ሰፈሮች የሩስያ ባንዴራ መውለብለብ መጀመሩን የሩስያ መከላከያ ሚንስቴር አስታውቋል።

የአወሮጳ ህብረት ከአፍሪቃ ጋ በብራስልስ ጉባዔ ሊያደርግ ጥቂት ጊዜ በቀረበት ባሁኑ ጊዜ የጀርመን መንግሥት ለአፍሪቃ ህብረት ተጨማሪ ፊናንስ ርዳታ ለመስጠት ቃል ገባ። እርግጥ ፡ አፍሪቃውያን ለችግሮቻቸው ራሳቸው መፍትሔ ለማፈላለግ ይሻሉ፡ ያም ቢሆን ግን፡ ጀርመን ከጎናቸው መቆሟን የሀገሪቱ የልማት ትብብር ሚንስትር ጌርድ

የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ እና ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ደህንነታቸው አደጋ ላይ ነው፡፡ የሟቹን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የአቶ መለስ ዜናዊ ምስል ያለበት ቲሸርት የለበሱ ከ 10 የሚልቁ የመንግስት ካድሬዎች በወላይታ ሶዶ እየተደረገ የነበረውን አንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን ምክርቤት ስብሰባን በሀይል ማደናቀፋቸውን ከስፍራው ለፍኖተ ነጻነት የደረሰው ዘገባ አመለከተ፡፡ ካድሬዎቹ የስብሰባ […]

ዴሞክራሲ ስርዓት በመገምባት ላይ በሚገኙ ወይንም የዴሞክራሲ በዳበረባቸው አገሮች ውስጥ እጅግ ብዙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና ተቋሞች ከመንግስት ነጻ ሆነው ይመሰረታሉ። በነፃነት ይንቀሳቀሳሉ። የጋዜጠኞች ማህበሮች፣ የጋዜጠኞች መድረኮች፣ የሰራተኛ ማህበሮች፣ የተማሪ ማህበሮች፣ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች፣ የስነጽሑፍ ማህበሮች፣ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ አሳብ አቀንቃኝ ድርጅቶች፣ የፖለቲካ አሳብ አቀንቃኝ ቡድኖች፣ የህዝብ ጤንነት እና ኑሮ ሁኔታ መሻሻል ተቆርቋሪ ድርጅቶች፣ የመንግስት […]

ዶክመንተሪው የ2007 ሀገራዊ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት አካል እንደኾነ ተጠቁሟል ‹‹ማስረጃ አቅርቡና እንነጋገርበት›› ለሚለው የማኅበሩ ጥያቄ ምላሽ አልተሰጠም (ፋክት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፴፰፤ መጋቢት ፳፻፮ ዓ.ም.) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሲኖዶሱን ይኹንታ አግኝቶ በመላው አገሪቱ የሚንቀሳቀሰውን የማኅበረ ቅዱሳንን አመራርና አባላት በአክራሪነት የሚከስ ነው የተባለ ዶክመንተሪ ፊልም ለማዘጋጀት መታቀዱ ተጠቆመ፡፡ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ አንዳንድ ሓላፊዎች …

የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባዉ መሃሪ በደብተራው ፓልቶክ ክፍል ቀርበዉ ባደረጉት ሰፊ ዉይይት፣ በመኢአድ እና በአንድነት መካከል ስላለዉ የዉህደት እንቅስቃሴ ማብራሪያ ሰጥተዋል። «አንድነቶች እኮ ልጆቻችን ናቸው። መኢአድ የነበሩ ናቸው» ያሉት አቶ አበባዉ በመኢአድ እና በአንድነት መካከል የፖለቲካ ፕሮግራም ልዩነቶች እንደሌሉ ተናገረዋል። «ታዲያ የሁለቱም ፓርቲዎች ምክር ቤቶች ከወሰኑ በኋላ ምንድን ነው ምክንያቱ መኢአድ ለመፈረም ያልቻለው ? » […]

የተባበሩት መንግሥታት  የትምህርት፣ የሣይንስና የባህል ድርጅት – ዩኔስኮ ሎሬአል ከሚባል ዓለምአቀፍ የውበትና የሠውነት ጥራት መጠበቂያ አቅርቦቶች አምራች ቡድን ጋር በየዓመቱ የሚያካሂደው ሴቶች በሣይንስ ሽልማት ኢትዮጵያዊቱ ዶ/ር ሰገነት ቀለሙ አሸናፊ ሆኑ፡፡

ሣይንቲስቷ ዶ/ር ሰገነት ቀለሙ ተቀማጭነቱ ናይሮቢ – ኬንያ የሆነው የነፍሣት አካላት እና አካባቢ ጥናት ዓለምአቀፍ ማዕከል /ኢሲፔ/ (International Center for Insect Physiology and Ecology – ICIPE) ዋና ዳይሬክተር ናቸው፡፡

ዶ/ር ሰገነት ከትናንት በስተያ (ረቡዕ) ፈረንሣይ ዋና ከተማ ፓሪስ ላይ በተካሄደው የዓለምአቀፍ ሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ ለዘንድሮው16ኛው የዩኔስኮ እና ሎሬአል ሽልማት በአሸናፊነት ከቀረቡት መካከል አንዷ…

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በስምምነቱ ሰነድ ላይ እንደተገለፀው የበርሊን አስተዳደር ስደተኞቹ ያቀረቡለትን ጥያቄዎች ለመመለስ ቃል ገብቷል ።እርዳታ ሰጭዎች አስፈላጊውን እንክብካቤ እንዲያደርጉላቸውም ፈቃደኝነቱን ገልጿል ።

ህወሓቶች በዓረና እንቅስቃሴና በትግራይ ህዝብ የተቃውሞ መንፈስ በጣም ደንግጠዋል። የዓረና ተከታታይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ተከትሎ ህወሓትም ተከታታይ ህዝባዊ ኮንፈረንስ ለማድረግ ወስኗል፤ ጀምሯልም። የህዝብ ተወካዮች ተብለው የተመረጡ የየአከባቢያቸው ህዝብ እንዲሰበስቡ መመርያ ተሰጥቷል። ይቅርታ የህዝብ ተወካዮች ሳይሆኑ የፓርቲ ተወካዮች መባል አለባቸው፤ ምክንያቱም የተመረጡት በህዝብ ሳይሆን በህወሓት ነው። የሚያገለግሉትም ለህዝብ ሳይሆን ለህወሓት ነው። ምክንያቱም በህዝብ ተመርጠው ተብለው የህዝብ ችግር ከመናገር ይልቅ የህወሓት አጀንዳ ደግፈው የሚያጨበጭቡ ናቸው። እስካሁን የመረጠውን ህዝብ ችግር የተናገረ የህዝብ ተወካይ የህወሓት አባል አላገኘሁም። በህወሓት የፖለቲካ ፍልስፍና የተማእከለ ዴሞክራሲ መሰረት አንድ አባል ከፓርቲው አስተሳሰብ ወጥቶ የፓርቲው ብልሹ አሰራሮች ባደባብይ ወይ በፓርላማ ማጋለጥ አይችልም። ካጋለጠ ከፓርቲው ይባረራል። ለዚህም ነው የህዝብ ተወካዮች ተብለው ፓርላማ ይገቡና የፓርቲው ተወካዮች ሁነው የሚቀሩ።

የህዝብ ወይም የህወሓት ተወካዮች ህዝብ ሲሰበስቡ ፈተና እያጋጠማቸው ነው። የሽረ ተወካይ ህዝቡ ሰድቦ አባሯታል። ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ በዓድዋ ህዝብ ተሰድባለች። የዓድዋ ህዝብ ለቅዱሳን “እናንተ ቤተሰቦቻቹ ለመርዳት እንጂ መቼ ለህዝብ ደህንነት ሰርታቹ ታውቃላቹ?” የሚል አስተያየት ሰጥቷል። በመቐለም አዲሳለም ባሌማ ህዝብ (ይቅርታ በመቐለ ህዝብ ተብለው የተሰበሰቡ ካድሬዎች ነበሩ) ሰብስቦ እርዱን ማለቱ ታውቋል። የመቐለ ዉሃ በ2007 ዓም ፕሮጀክት ቀርፀን እንፈተዋለን፤ ብቻ እኛን ምረጡ ብሎ ተማፅኗል። የመቐለ ነጋዴዎች ሰብስቦ ችግሮቻቹ ለመፍታት ተዘጋጅተናል ብሎዋል።

አጠቃላይ የህወሓት ስትራተጂ ህዝብን ለመሸወድ ያለመ ሲሆን የሚያጠነጥነውም “ህወሓት ካልተመረጠ የትግራይ ማንነት ይጠፋል” የሚል ነው። “ጠላቶቻችን እየመጡ ናቸው፤ ከህወሓት ጎን ተሰለፉ! ጦርነት ሊከፈትና ልጆቻችሁ አደጋ ላይ ሊወድቁ ይችላሉ” እያሉ ይገኛሉ።

ግን የትግራይ ማንነት በህወሓት ህልውና የተንጠለጠለ አይደለም። እንኳን የህዝብ ማንነት የአንድ ግለሰብ ማንነትም ሊጠፋ አይችልም። ምክንያቱም የህዝብ ማንነት ቀርቶ የአንድ ሰው ማንነት ከጠፋ የሰውየው መብትና ነፃነት ተጥሷል ማለት ነው። መብቱ ወይ ነፃነቱ ከተጣሰ ደግሞ አዲስ የመጣ ስርዓት ልክ እንደ ህወሓት አምባገነናዊ ስርዓት ነው ማለት ነው። የህውሓትን ያህል አምባገነን ስርዓት ከመሰረትን ደግሞ ህወሓት አልተቀየረም ማለት ነው። ህወሓት ካልተቀየረ የፖለቲካ ለውጥ አልመጣም ማለት ነው። የፖለቲካ ለውጥ ካልመጣ ደግሞ ትግላችን ይቀጥላል (ለውጥ እስኪመጣ ድረስ)። ስለዚህ እኛ የምንታገለው ከህወሓት የተሻለ ስርዓት ለመመስረት እንጂ ህወሓትን በሌላ አምባገነን ስርዓት ለመተካት አይደለም። ስለዚህ ላረጋግጥላቹ የምፈልገው ነገር ቢኖር የማንም ህዝብ ወይ ግለሰብ ማንነት ይከበራል እንጂ አይጠፋም።

“ጠላቶቻችን እየመጡ ነው” የሚለው ዉንጀላ ግዜው ያለፈበት ፕሮፓጋንዳ ነው። የህዝብ ጠላት ጨቋኝ ስርዓት ነው። ህዝብ ከጨቋኝ ስርዓት ዉጭ ሌላ ጠላት የለውም። ጨቋኝ ስርዓት የህዝብ ጠላት እስከሆነ ድረስ እንታገለዋለን። ጨቋኝ ስርዓት ምን ግዜም አንቀበልም። ጨቋኝ ስርዓት ስለማንቀበል ነው አሁን ህወሓትን የምንቃወመው። ስለዚህ ዓላማችን የስርዓት ለውጥ ማምጣት እስከሆነ ድረስ ለጨቋኞች ቦታ የለንም፤ ህወሓትም ሌሎችም። እኛ የምንቀበለው ዴሞክራሲያዊ የህዝብ መንግስት ብቻ ነው።

ህወሓቶች በዓረና አጀንዳዎች በመስጋታቸው ምክንያት የዓረና ሐሳቦችን ለመቀበል እየተገደዱ ነው። በቅርቡ በህዝብ ፊት እየቀረቡ የመሬት ይዞታ ጉዳይ በዓረና እየቀረበ ያለውን ሐሳብ እንደሚደግፉ እየገለፁ ነው። (የዓረና ሐሳብ እንደግፋለን እያሉ ሳይሆን የህዝብን ፍላጎት ለማሟላት እንሞክራለን በሚል ነው። የህዝቡ ፍላጎት ደግሞ የዓረና የመሬት ፖሊሲ ነው)። የዓሰብ ወደብም በሰለማዊ መንገድ ለማስመለስ እንሞክራለን በማለት እየተመፃደቁ ነው። ለነጋዴዎችም ግብር እንቀንሳለን በሚል ምክንያት ለመጀንጀን እየሞከሩ ነው።

አሁን ግራ ሲገባቸው ስራ የሌላቸው ወጣቶች ለውትድርና ለመመልመል እየሞከሩ ሲሆን ማንም ወጣት ፍቃደኛ ሊሆን አልቻለም። በወጣቶቹ ዉሳኔ የተደናገጡ ህወሓቶች የጎዳና ተዳዳሪ የነበሩ ህፃናት ልጆች አታለው (ስራ እንሰጣቸዋለን በሚል ምክንያት) ለዉትድርና መመልመላቸው ታውቋል። ለምሳሌ በመቐለ ከተማ የነበሩ ብዙ የጎዳና ተዳዳሪ ህፃናት ተወስደዋል (ማረጋገጥ ይቻላል፤ አሁን በመቐለ ከነበሩ ህፃናት አንድ የቀረ የለም)። ግን አብዛኞቹ ህፃናት ከ16 ዓመት በታች ናቸው። ከ16 ዓመት በታች ህፃናት ለውትድርና የሚመለምል የቸኛ ሕገወጥ መንግስት ኢህአዴግ መሆኑ አይቀርም። ምክንያቱም በማንኛውም ሕግ ከ16 ዓመት በታች ህፃናት ለውትድርና መመልመል ሕጋዊ ሊሆን አይችልም። ጉዳዩ የሚከታተለው ካገኘ በዓለም አቀፍ ሕግ ወንጀል ሊሆን ይችላል።

በዓዲግራት የፈፀሙብንን ድብደባ በጣም አክስሮባቸዋል። የትግራይ ህዝብ ሙሉበሙሉ እንዲጠላቸው ሁነዋል። እናም በጣም ሰግተዋል። በቅርቡ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሊጀምሩ ይችላሉ። በወታድሩም ቢሆን ህወሓቶች ድጋፍ የላቸውም።

It is so!!!
አብረሃ ደስታ

Image

መለስ በመጀመሪያው የኤርትራውያን ነፃነት ቀን ዝግጅት ላይ ለኤርትራውያን እንዲ ብሎ ነበር። «ቁስል እንዳለባችሁ አውቃለው። ለምን? ብትሉ ጀርባችሁ ላይ ያለው ቁስል በእኔ ጀርባ ላይም አለ። ይህንን ያለፈ ምህራፍ እርሱት አልላችሁም። ነገር ግን ቁስላችንን ማከክ የለብንም አሁን ሁሉ ነገር አልቋል (ተውዲኡ ኣሎ)ክፉ፣ ክፉውን ቀብረነዋል!!» ነበር ያለው።

ይህንን የመለስ ዜናዊ አነጋገር አንድምታ ስናይ «ይኸው ደረስንላችሁ! ጠላት ተቀበረ! መቀበር ብቻ አይደለም አስተሳሰቡንም አዛብተነዋል! ያለበት ነበር። እንግዲህ ማነው ጠላት? ኢትዮጵያ? የማን አስተሳሰብ ነው? የኢትዮጵያ! ምን አይነት አስተሳሰብ? እንግዲህ እንደምናውቀው በተለየ ጊዜ የኢትዮጵያን ሳይኮሎጂ የሚያዛቡ ነገሮችን ሲናገሩ ነበር። ለምሳሌ፦ «ባንዲራ እኮ ጨርቅ ነው!» ይሄ አባባልን ለሚያይ ሌላ ሰው በቀላሉ የአፍ ወለምታ ሊመስለው ይችላል።ነገር ግን ሆን ተብሎ የኢትዮጵያውያንን አስተሳሰብ ለማዛባትና ለማሽመድመድ የሚደረግ ሴራ ነው።

በባንዲራችን እንደምንኮራ ያውቃሉ! የሶስት ሺህ አመት ታሪክ አለን ብለን እንደምንኮራ ያውቃሉ! ነገር ግን ይህንንም ታሪካችንን ወደ መቶ አመት ዝቅ ለማድረግ ይጥራሉ፤ ባለፉት መሪዎቻችን በአጼ ምንሊክ ፣ በነ አጼ ቴዎድሮስ፣ በነ አጼ ዩሐንስ፣ በነ አሉላ እንደምንኮራና እንደምንወዳቸው ከእነሱ ጋርም ያለንን ትስስር ያውቃሉ! ወያኔዎቹ ባንዳዎች ግን በየጊዜው ቴሌቭዥን ላይ እየወጡ «የኢትዮጵያ አጼዎች እኮ ጊዜያቸውን ያሳለፉት በጦርነት ነበር።» ይላሉ። ይሄን መናገር በተለይ አቶ መለስ እንደሆቢ ነበር የወሰዱት የሚመስለው። እንግዲህ የኢትዮጵያ ህዝብ መሪዎቹ «ለካ እንዲህ ነበሩ» ብሎ እንዲያፍር! የዛሬውም ቅጥ ያጣ ድህነት «እነሱ ያመጡት ጣጣ ነው!» ብለውም ለመናገር ይሞክራሉ።

እንደዚህ አይነት ቀጣይ ነገሮችን አምጥተን አገጣጥመን «ባንዲራ ጨርቅ ነው!» ካሉበት ጊዜ ጀምሮ ያሉትን ሰብስበን ብናያቸው መለስ የተያያዘው ኢትዮጵያዊ አንገቱን ደፍቶ፣ በኢትዮጵያዊነቱ አፍሮ፣ ድህነትን እንዲቀበል፣ ከኋላ ቀርነት ጋር ተቆራኝቶ እንዲኖርና የበታችነት ስሜት እንዲኖረው አድርገዋል እየተደረገም ነው»

Image

በቅርቡ ባህርዳር ላይ በተካሄደው የኢትዮጵያ ስፖርት በአል ሼኽ አልሙዲ በክብር እንግድነት ተጋብዘው ነበር። የበአሉን መክፈቻ በቲቪ ስከታተል አንድ ጥያቄ ወደ በአእምሮዬ መጣ። አልሙዲንን የክብር እንግዳ አድርጐ መጋበዙ ለምን አስፈለገ?..ብዙ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። “የገዢው ፓርቲና የባለስልጣናቱ ታማኝ ወዳጅ ስለሆኑ፣ በባህርዳሩ ስታዲየም ግንባታ ድርጅታቸው ስለተሳተፈ ወይም ሼኹ ለስፖርት ያላቸውን ፍቅር በማየት..” የሚሉ ነገሮችን መደርደር ይቻላል።

በእኔ ግምት አልሙዲ በባህርዳሩ በአል በእንግድነት የተጋበዙት በሰሜን አሜሪካ ስፖርት በአል ላይ ስለተዋረዱ የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት የፈጠርዋት ማፅናኛ ትመስለኛለች። ባለፈው አመት እዚህ ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በአንድ ሳምንት ሁለት የኢትዮጵያ ስፖርት በአል ተከበሮዋል። አንድኛው በሼኽ አልሙዲና የዳይስፖራውን ማንነትና ፍላጐት ባልተገነዘቡ ወዳጆቻቸው የተዘጋጀ ነበር። በነዚህ ወገኖች ግምት “ዳያስፖራው በተወሰኑ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት ካድሬዎች የሚሽከረከር የዋህ ህዝብ” አድርገው ይወስዱታል።

አሜሪካ ሀገር ከኅይለስላሴ ጀምሮ በደርግ ጊዜ ከዛም በኋላ የመጣው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ (በምንም መንገድ አሜሪካ ይምጣ) ለዘሩ፣ ለጐሳው ሳይሆን ለኢትዮጵያዊነቱ ጥልቅ የሆነ ፍቅርና ክብር አለው። በዚህ ምክንያት የኢህአዴግን የዘር ፖለቲካ አይደግፍም። ከደጋፊዎቹም ጋር የማይታረቅ ቅራኔ ውስጥ የገባው በዚህ አገር ወዳድ አቋሙ ነው። ይህ እውነት ያለገባቸው አልሙዲና ተከታዮቻቸው በስፖርቱ አስታከው ዳያስፖራውን እንቆጣጠራለን በማለት በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ቢከሰክሱም አልተሳካላቸውም። ባዶ ስታዲየም ታቅፈው ነው የቀሩት። ሁለተኛው ኢ.ኤስ.ኤፍ.ኤን የሚባለው ኢትዮጵያዊ ፌዴሬሽን የነሱን ያክል ገንዘብ ሳይኖረው በርካታ ህዝብ ከጎኖ ማሰለፍ ችሎዋል። እንዲያውም ስታዲየሙ ሞልቶ ሰው እስኪመለስ ድረስ። በዚህ በአል ከፍተኛ የሆነ የአንድነትና የአገር ፍቅር ስሜት የታየበት፣ የኢትዮጵያ ባንዲራ ከፍ ብሎ በብዛት የተውለበለበበትና ያሸበረቀበት፣ ሰዎች ከብሄራቸው ይልቅ ኢትዮጵያዊነታቸውን ያገነኑበት ትልቅ በአል ነበር።

ባዶ ስታድየም የታቀፉትና አፍረው በውርደት ለተመለሱት አልሙዲ የባህርዳሩ እድል በማፅናኛነት ተሰጣቸው። ኢትዮጵያዊያን በነፃነት በሚኖሩበት አሜሪካ ግን አልሙዲ በገንዘባቸው የህዝብን ድጋፍ መግዛት አይችሉም። በገንዘብ ምንም ማድረግ እንደማይችሉም ሊያውቁት ይገባል።