የኑርንበርጉ ነዋሪ የኤሌክትሪካል ኢንጅነር ሳምሶን በቀለ ስኬት
የውጭ ዜጎች እድሉን ካገኙና ከተጣጣሩ በጀርመን ስኬታማ መሆን መቻላቸው ማሳያ የሆኑት አቶ ሳምሶን በአሁኑ ጊዜ ስደተኞች በምርጫ ዘመቻ ወቅት ስማቸው መጉደ?…
የውጭ ዜጎች እድሉን ካገኙና ከተጣጣሩ በጀርመን ስኬታማ መሆን መቻላቸው ማሳያ የሆኑት አቶ ሳምሶን በአሁኑ ጊዜ ስደተኞች በምርጫ ዘመቻ ወቅት ስማቸው መጉደ?…
ተመራጭ ፕሬዝዳንት ትራም እራሳቸውም ሰኞ እለት ለአንድ ሜዲያ በሰጡት አስተያየት ፕሬዝዳንት ፑቲንም ከሳቸው ጋር መገናኛኘቱን እንደሚፈለጉትና ከሰኞው በ?…
የመተግበሪያ አጠቃቀምን በተመለከተ በተለያዩ ድረ ገፆች የወጡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በ2024 ዓ/ም ተጠቃሚዎች አውርደው የተጠቀሙባቸው መተግበሪያዎች የማ?…
በአዋጁ መሠረት “የነዳጅ ውጤቶችን ከተፈቀደው ቦታ ውጪ የሚያከማቹ፣ እና ከግብይት ሥርዓት ውጪ ሲሸጡ የተገኙ” ሰዎች፤ ከሦስት ዓመት እስከ አምስት ዓመት ?…
ዶናልድ ትራምፕ የፓናማ ቦይን፣ ጎረቤታቸውን ካናዳን እና ግሪንላንድ ደሴትን በአሜሪካ ይዞታ ሥር ለማስገባት ፍላጎት እንዳላቸው ባለፉት ሳምንታት በተደጋ?…
ሀዲስ ዓለማየሁ መሰንቆ ተጫዋች ነው። ስለ መሰንቆ አውርቶ አይጠግብም። ዓለም ሙሉ በአንዱ የመሰንቆ ገመድ ቢተሳሰርለት ምኞቱ ነው። ሀዲስ እና መሰንቆን መ?…
በአውስትራሊያ የምትኖር አንዲት ሴት ለማኅበራዊ ሚዲያ ፕራንክ በሚል በጓደኛዋ አማካኝት ሙሽራ ሆና የተወነችበት የሰርግ ሥነ ሥርዓት ኋላ ላይ የእውነት ነ?…
በደቡባዊ ካሊፎርኒያ፣ ሎስ አንጀለስ በከፍተኛ ፍጥነት እየተዛመተ ያለውን የሰደድ እሳት ለመግታት በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞች ተሰማሩ።
ኢትዮጵያ ከ50 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የስቶክ ገበያን ክፍት አድርጋለች። ኢትዮ ቴሌኮም ኢኤስክስን በመቀላቀል የመጀመሪያው የልማት ድርጅት ይሆናል?…
በቻይናዋ ከተማ በጉዋንዡ የልብስ ስፌት ማሽን ድምጽ መስማት የተለመደ ነው። ከጠዋት እስከ ማታ ከፋሪባዎች ድምጹ በመስኮት በኩል ይሰማል።ካናቴራ፣ ሱሪ፣ ?…
ባለፉት ሳምንታት ተመራጩ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአርክቲክ ውቅያኖስ የሚገኘውን እና በዓለማችን ትልቁን የግሪንላንድ ደሴትን ‘ለ?…
የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም ኖርዌይ በዓለማችን ቁንጮ ስፍራ ላይ ተቀምጣለች። ባለፈው ዓመት በአገሪቱ ካሉ አስሩ መኪኖች ዘጠኙ የኤሌክትሪክ መ?…
የባሕረ ሰላጤዋ አገር ኳታር አደራዳራዳሪዎች እንደሚሉት እስራኤል እና ሐማስ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ ከጫፍ ደርሰዋል። እስራኤል በሐማስ የተ…
ተሰናባቹ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ሽብርተኝነትን በመንግሥት ደረጃ ስፖንሰር ታደርጋለች በሚል የተፈረጀችውን ኩባ ከዝርዝሩ ሊያስወጧት እንደሆነ ተናገሩ።
ኢትዮጵያውያን በቤት እና በመሬት ግብር የሚከፍሉበት የንብረት ታክስ በተቃዋሚዎች ትችት ቢገጥመውም ጸድቋል። ተቃዋሚዎች አዲሱ ታክስ በሸማቾች ላይ ጫና እ…
አቶ ኮስሞስ ገብረ ሚካኤል ለወጣት ኢትዮጵያውያን የተስፋይቱ ምድር ተደርጋ በምትታየው በደቡብ አፍሪቃ በደላሎች የሚፈጽምባቸው በደል መክፋቱን ገልጸዋል?…
ሌላው አስተያየት ሰጪ ተሽከርካሪውን ከባንክ ብድር ወስዶ መግዛቱን ጠቅሶ በቤንዚን እጥረቱ ምክንያት ሰርቶ ብድር መመለስ እንዳልቻለ ገልጧል፣ አንዴ ነዳጅ…
የትናንትናውን ጨምሮ ባለፉት ሳምንታት ውስጥ አዲስ አበባ ድረስ ዘልቆ በተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ሳቢያ ከእልቅልፋችን እየቀሰቀሰን ሰላም አሳጥ?…
ወደ ባሕር ለመጥለቅ ጥቅም ላይ የሚውል ጀልባ በግብፅ መገልበጡን ተከትሎ ከአደጋው የተረፉ ሰዎች የግብፅ ባለሥልጣናትን ከሰዋል። ጀልባው የተገለበጠው ቀይ…
የአዲስ አበባ ከተማ አውቶብስ አገልግሎት ድርጅት “በድልድል እና ምደባ” 400 የሚሆኑ ሠራተኞችን ከጥር ጀምሮ ከሥራ ማሰናበቱን ሠራተኞች እና ድርጅቱ ተናገሩ።…
ናይጄሪያውያን የፍቅር ጓደኛዋ ነው በተባለ ዘማሪ አንገቶ ተቀልቶ ለተገደለችው ሴት ሐዘናቸውን በማኅበራዊ ሚዲያ እየገለጹ ነው።
የዩናይትድ ኪንግደም የግምጃ ቤት ሚኒስትር ቱሊፕ ሲዲቅ በባንግላዴሽ እየተካካሄደባቸው ባለው የሙስና ምርመራ ጋር በተያያዘ በደረሰባቸው ጫና ከሥልጣናቸ…
የደቡብ ኮሪያ ባለስልጣናት ወታደራዊ አገዛዝን ካወጁ በኋላ አመጽ አነሳስተዋል የተባሉትን ፕሬዚዳንት ዮን ሱክ ዮልን ከጠባቂዎቻቸው ጋር ለሰዓታት ከቆየ አ…
በካሊፎርኒያ ሰደድ እሳት እስካሁን 24 ሰዎች ሞተዋል። በሎስ አንጀለስ የምትኖረው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ትዕግስት ፈረደ በዚህ ሰደድ እሳት የተነሳ ለተጎዱ ነ…
በኢትዮጵያ አረጋውያን ከቤተሰባቸው ጋር እስከ መጨረሻው ሞኖራቸውን አውሮፓውያኑም ሊወርሱት የሚገባ ባህል ነው የምትለው ቱቱ መላኩ በእንግሊዟ ሬዲንግ ከ?…
ኢትዮጵያን ጨምሮ ስለጎረቤት አገራት አወዛጋቢ መልዕክት የሚለጥፉት የኡጋንዳው ፕሬዝደንት ልጅ ራሳቸውን ከኤክስ አገለሉ።
በግጭት እና በድርቅ ምክንያት ለረጅም ጊዜ ችግር በቆየው የአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ ውስጥ ባጋጠመው ከፍተኛ የምግብ እጥረት ምክንያት የሰዎች…
በጥዋቱ ቡና የሚጠጡ ሰዎች ከልብ በሽታ ጋር በተያያዘ የመሞት ዕድላቸው ዝቅተኛ መሆኑን አንድ ጥናት ጠቁሟል።
ይህ ቫይረስ በትንኝ የሚተላለፍ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1930ዎቹ ኡጋንዳ ውስጥ የተገኘ በሽታ ነው። ቫይረሱ በአውሮፓውያኑ 1999 ነው ወደ ምዕራቡ ዓለም የገባው። በአ?…
ስሙ ለዚህ ፅሑፍ ሲባል የተቀየረው የ25 ዓመቱ ሞሐመድ በአውሮፓውያኑ 2028 ጫት ከታገደ ከአራት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሞከረው ለቢቢሲ ይናገራል።
በቄሮ ምንነት እና “ድርጊቶች” ላይ በርካታ ውዝግቦች እየተነሱ ነው። ውዝግቦቹ የሚነሱት በሁለት ፅንፎች ነው፦ ፩ኛው ፅንፍ ያሉት ሰዎች “ቄሮ ቅዱስ ነው” ሲሉ፣ ፪ኛው ፅንፍ ያሉት ሰዎች ደግሞ “ቄሮ እርኩስ ነው” ይላሉ። እኔ ደግሞ ቄሮ እኛ ነህ የምንለውን ይሆናል ባይ ነኝ።
እንደኔ እንደኔ የውዝግቡ ሁሉ መንስዔ የቄሮን ምንነት እና የንቅናቄውን ዓይነት፣ እንዲሁም “የትግሉን” ወይም ደግሞ “የድሉን” ባለቤት ካለመረዳት የመጣ ነገር ይሆን ይሆናል በማለት ነው ይህንን ጽሑፍ ለአማራጭ አስረጅነት ያዘጋጀሁት። እግረመንገዴንም ለውዝግቡም ይሁን ለውዝግቡ መንስዔ የሆኑ ተቃርኖዎችን እዳስሳለሁ። ዓላማዬ ከፅንፉ እና ከፅንፉ ወዲህ ዓለም እንዳለ ለማሳየት እንጂ መሞከር ብቻ ሳይሆን ፍረጃችን ተፅዕኖ እንዳለው ማስታወስም ጭምር ነው።
ቄሮ – ሥያሜው ምን ይነግረናል?
‘ቄሮ’ ቃሉ ‘ያላገባ፣ ያልወለደ’ ወጣትን ይወክላል። ነገር ግን ወጣት የሚለውን ቃል የሚተኩ ሌሎች የኦሮምኛ ቃላት አሉ። እነዚህም ‘ደርደሩማ’፣ ‘ደርገጌሳ’ እና ‘ጎሮምሳ’ የሚሉት ቃላት ምሳሌ ይሆናሉ። ቄሮ የሚለው ቃል ምንጩ ‘ቄረንሳ’ ከሚለው እና ነብር የሚል ትርጉም ካለው ቃል የተቀዳ እንደሆነ ይነገራል። ስለዚህ ቄሮ ማለት እንደነብር ያለ ብርቱ ወጣት ማለት ነው፣ ማለት እንችላለን። ይሁን እንጂ አሁን በተለይ በኦሮሞ ፖለቲከኞች ዘንድ ‘ቄሮ የሚለው ቃል ፍቺ ‘አብዮተኛ ወጣት’ የሚል ትርጉም አለው።
“የቄሮ ንቅናቄ” ውልደት እና ዕድገት
ቄሮ የሚለው ቃል የፖለቲካ መድረኩ ውስጥ የገባው እ.ኤ.አ. በ2011 የአረቡ አብዮት በፈነዳበት ወቅት ነበር። መቀመጫውን ዳያስፖራ ያደረገው ንቅናቄ ከዩንቨርስቲ ተማሪዎች ጋር ግንኙነት በመመሥረት ‘ቄሮ ቢሊሱማ ኦሮሞ’ የሚባል ኢመደበኛ ማኅበር ፈጠረ። የዚህ ማኅበር አባላት መረጃዎችን በኢሜይል እና በድረገጻቸው እየተለዋወጡ በርካታ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ ቀጠሉ። ሥማቸው በይፋ የተነሳው ግን በ2006 የአዲስ አበባ ከተማ ማስተር ፕላንን ተከትሎ በተነሳው እና ዩኒቨርስቲዎችን ባዳረሰው የተቃውሞ ሰልፍ ወቅት ነው።
ከዚያ በኋላ የተጋጋለው የተቃውሞ ሰልፍ መላው ኦሮሚያን ሲያዳርስ በየአካባቢው ያሉ ወጣቶች ራሳቸውን ቄሮ ብለው መጥራት ጀመሩ። የመጀመሪያው የቄሮ አደራጅ የነበረው (qeerroo.org የተባለ) ድረአምባም ይሁን የፌስቡክ ገጹ አሁን እምብዛም ተከታታይ የላቸውም። ይልቁንም የወጣቶቹ ኅብረት መሪ ተደርጎ በዘልማድ የሚወሰደው የኦኤምኤን ቴሌቪዥን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጃዋር መሐመድ ነው።
ከዚያ በኋላ በኦሮሚያ ክልል፣ በየአካባቢው የሚነሱት ተቃውሞዎች ውስጥ የሚሳተፉ የተደራጁም ይሁኑ ያልተደራጁ ወጣቶች በሙሉ – ራሳቸውን ሲገልጹም ይሁን ሌሎች ሲገልጿቸው – ቄሮ በሚል ሥያሜ ሆነ። ቄሮ በዚህ አካሔድ በማንም ግለሰብ ወይም ቡድን ቁጥጥር ሥር ያልሆነ፣ ነጻ ነገር ግን በኦሮሙማ (ኦሮሞነት) የተሰባሰበ ኢመደበኛ ቡድን ሆነ። ይህ ማለት ግን ወጣቶቹ በፖለቲካ ፍልስፈፍናቸውም ይሁን ብስለታቸው፣ በኢትዮጵያ እና ኦሮሚያ ታሪክም ይሁን ፖለቲካ አረዳዳቸው ወጥ አቋም አላቸው ማለት አይደለም።
ይህ በእንዲህ እያለ በአማራ ክልል የነበረው ሕዝባዊ ተቃውሞ ላይ የሚሳተፉትን ወጣቶች ሥም ለመስጠት ተሞከረ። ‘ፋኖ’ የሚለው ሥያሜ ‘ቄሮ’ ከሚለው ጎን ለጎን መጠቀሱ የተለመደ ነገር ሆነ። ያን ጊዜ በቄሮ ሥምም ሆነ በፋኖ ሥም የሚደረገው ነገር በሙሉ፣ ማዕከላዊ መንግሥቱን እስካስጨነቀ ድረስ “ትክክል” ነበር። ይሁን እንጂ መሬት ላይ “ቄሮ ነኝ” የሚሉትን ያክል፥ “ፋኖ ነኝ” የሚሉ ወጣቶች እምብዛም አልነበሩም። እንዲያውም ‘ፋኖ’ የግንቦት ሰባት ፈጠራ ነው የሚሉ የአማራ ብሔርተኞች ገጥመውኛል። ይሁንና የመንግሥት ባለሥልጣናት ሳይቀሩ አሁን ለምናየው የለውጥ አዝማሚያ አስተዋፅዖ ያበረከቱ ወጣቶችን ሲጠሩ “ቄሮ፣ ፋኖ፣ ዘርማ…” እያሉ መጥራትን ‘ፕሮቶኮል’ አድርገውታል።
የትግሉ እንዲሁም የድሉ “ባለቤቶች”
የያኔዎቹ ኦሕዴድ እና ብአዴን ተባብሮ ትሕነግ ላይ ማበይ፥ ከወጣቶቹ አመፅ ባልተናነሰ (ወይም በበለጠ መልኩ) ኢሕአዴግን ነቀነቀው። የፓርቲዎቹ ከወጣቶቹ ጋር ያልተጻፈ መግባባት ላይ መድረስ ደግሞ የቀድሞውን ኢሕአዴግን ገድሎ፣ አዲሱን ኢሕአዴግ ወለደ። አሁን ከትሕነግ/ኢሕአዴግ ወደ ኦዴፓ/አዴፓ/ኢሕአዴግ አገዛዝ ተሸጋግረናል። ይሁንና ገና አመፁ አልሰከነም። የትግሉ ባለቤት ተቃዋሚዎች በሙሉ፣ በተለይም አደባባይ የወጡት የኢትዮጵያ ወጣት አመፀኞች ናቸው፤ የድሉ ባለቤቶች ግን የኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች፣ በተለይም ኦዴፓ እና አዴፓ ናቸው። ያለእነሱ ከቀድሞ አቋማቸው መቀልበስ፣ እንዲሁም ለማበር መወሰን በኢሕአዴግ ቤት አሁን ያለው ወደ ዴሞክራሲ የመሸጋገር ዕድል ፈፅሞ አይመጣም ነበር ብዬ እገምታለሁ።
ይሁንና ወጣቶቹ የልኂቃን ተቃዋሚዎችን ጥያቄ ከማስተጋባት ባሻገር ለእንዲህ ያለ ነፍስን አሳልፎ እስከመስጠት የሚደርስ ብሶት የዳረጋቸው ሥራ አጥነት እና ‘የሪከግኒሽን’ ጥያቄ መልስ ቢሰጠው ኖሮ፥ ድሉን የጋራ ድል አድርገን መቁጠር የምንችልበት ዕድል ይኖር ነበር።
አሁን ባለው ሁኔታ ብዙኃን ሥራ አጦች በየአደባባዩ በከፈሉት መስዋዕትነት፥ ‘እነዚህ ሥራ ፈቶች ደግሞ መረበሽ ጀመሩ’ እያሉ ይበሳጩባቸው የነበሩ ልኂቃን በአንድ በኩል፣ እንዲሁም በሌላ በኩል ደግሞ ‘እስከመቼ እንዲህ ተዋርዳችሁ ትኖራላችሁ፣ ታግላችሁ ነጻ ውጡ እንጂ’ እያሉ ሲቆሰቁሷቸው የነበሩ ልኂቃን ሥልጣን እየተቆጣጠሩ ሲመጡ ወጣቶቹ ችላ መባላቸው ሐቅ ነው።
ይህ ነገር ምናልባትም የትግሉ “ባለቤቶች” እና የድሉ “ባለቤቶች” ወይም “ተጠቃሚዎች” መካከል መቃቃር ሳያስከትል አይቀርም። ይህ ጉዳይ አዲስ ብሶት የሚወልድ መሆኑም የጊዜ ጉዳይ ነው።
“ጀግኖች” የነበሩ “ፅንፈኞች”
(የውክልና ጦርነት መሣሪያዎች)
በየአካባቢው በሥራ አጥነታቸው ምክንያት ዋጋ አጥተው፣ በአደገኛ ቦዘኔነት ተፈርጀው ከፊሉ ስደት እየበላቸው፣ ከፊሉ ሱስ እየዋጣቸው የነበሩ ወጣቶች ድንገት የተቀጣጠለው ሕዝባዊ አመፅ ማገዶ ነበሩ። ያኔ “ጀግኖች” ተብለዋል። ምክንያቱም ለልኂቃኑ ፖለቲካ ሁነኛ መሣሪያ ነበሩ። ወጣቶቹ ምናልባትም አእምሮ ከሚያላሽቅ የሥራ አጥነት ስሜት ወጥተው፥ ለራሳቸው ያላቸው ዋጋ እና ግምት የጨመረው በዚህ አመፅ ባደረጉት ተሳትፎ ይሆናል። ሕዝባዊ አመፁ ቆሞ ድንገት አገር መረጋጋት ሲጀምር ግን ወደ “መንደር ያሰለቹ አደገኛ ቦዘኔነት” መመለሳቸው ሆነ። ከተሰጣቸው ሥም መውረድ ከባድ ነው። ስለሆነም የአብዮታቸው ጠባቂ ሆኑ – ከሳሽ፣ ፈራጅ እና ቀጪ። የደቦ ፍርድ፤ በዚህ ወቅት ነው በፅንፈኝነት መፈረጅ የጀመሩት።
በዕውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የምትመራው ‘ኢትዮጲስ’ ጋዜጣ (በጥቅምት 24, 2011 እትሟ) በርዕሰ አንቀፅዋ ቄሮዎችን ለዘብተኛ እና ፅንፈኛ በሚል ከለያየቻቸው በኋላ ፅንፈኞቹን የማስቆም ሥራ መሠራት እንደሚገባ ጠቁማለች። የኢትዮጲስ ስህተት ምናልባት (አንድም) በአገሪቱ የደቦ ፍርዶች እና ወደ ስርዓት አልበኝነት የሚወስዱ እንቅስቃሴዎችን ለቄሮ ብቻ ለይታ መስጠቷ ነው። መቼም በድንጋይ ወግሮ መግደል እና በእንጨት ላይ ዘቅዝቆ መስቀልን የመሳሰሉ የደቦ ፍርዶች አንዱ ከሌላው የሚሻሉበት መንገድ አለ ተብሎ አይታመንም። በዚህ ረገድ ጉዳዩ ‘ወጣት ፅንፈኞች’ በሚል ሊጠቃለል ይችል ነበር ብዬ አምናለሁ። (ሁለትም) ቄሮ የተጻፈ ፕሮግራም የሌለው፣ አባላቱ በዝርዝር የማይታወቁ፣ አንድ ስትራቴጂ እና ግብ የሌለው የግፉአን ማኅበር መሆኑን ከግምት ውስጥ ያላስገባ መደምደሚያ መሆኑ ስህተት ያደርገዋል። ይህም ማለት ማንም ተነስቶ ቄሮ ነኝ ብሎ ማወጅ እና በዚያ ሥም ወንጀልም ይሁን መልካም ጀብዱ መፈፀም ያስችለዋል ማለት ነው። ብዙኃን መገናኛዎች ግን ቡድኑን ግልጽ ቅርፅ እና መዋቅር እንዳለው እንዲሁም “ተግባሩን” አቅዶ እንደፈፀመ ማኅበር ተመልክቶ “እንዲህ ነው” ወይም “እንዲያ ነው” ማለት የተሳሳተ ትርጉም ይሰጣል። (ሦስትም) የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎች – ለምሳሌ የጃዋር “የቄሮ መንግሥት” እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ “ፀጉረ ልውጦችን መቆጣጠር” የመሳሰሉ – ንግግሮች ወጣቶቹን የውክልና ጦርነት ውስጥ እንደከተታቸው ከግንዛቤ ያላስገባ መደምደሚያ መሆኑ ነው።
ፍረጃ እና ተፅዕኖው፤
እስመ ሥሙ ይመርሖ ሀበ ግብሩ
(nomen est omen)
ቄሮንም ይሁን ፋኖን ወይም ሌላ የፖለቲካ ቡድኖችን በተመለከተ ለምናደርጋቸው ፍረጃዎች ማድረግ የሚገባን ጥንቃቄ አለ። ፍረጃ (labeling) በሥነ-ልቦና ግንባታ የሚያሳድረው ተፅዕኖ እንዳለ በርካታ ጥናቶች ያሳያሉ። «እነ እከሌ ይህን አያደርጉም»፣ «እንትን ሆኜ እንዲህ አላደርግም» የሚሉ አባባሎች የሚያስረዱን ቁምነገር ቢኖር የሆኑ ሰዎች ስብስብን የሚገልጽ ማንነትን የምንበይንበት (labeling/defining) መንገድ መልሶ የአባላቱን ድርጊት እንደሚወስን መረዳት እንደሚያሻን ነው። “ቄሮ አብዮተኛ ወጣት ነው” በተባለ ጊዜ አደባባዮችን በተቃውሞ ሰልፎች ንጧል። የለውጥ ጀምበር ሲከፈት “ለውጡን ጠብቁ” ሲባል እንደዚያው ለማድረግ እየሞከረ ነው። ወጣቶቹ በልኂቃኑ የሚሰጣቸውን ሥያሜ ለመመጠን እየተፍጨረጨሩ ነው። “ቄሮ መንግሥት ነው” ብለን ከአቅሙ በላይ ሥራ ከምናሸክመው፣ “ቄሮ የዴሞክራሲ እና የሥልጡን ፖለቲካ ጠበቃ ነው” ብለን በዚህ አቅጣጫ እንዲተጋ ብናደርገው ይመረጣል። “ቄሮ ፅንፈኛ ነው” እያልን ወደዚያ ከምንገፋው “ቄሮ ይህንን አያደርግም” ብለን ብንገስፀው ይሻላል።
ቺርስ ለጥንቃቄ!
ትላንት አንድ የስዊድን ጋዜጠኛ “ሐሳብን ከመግለጽ ነፃነት ይልቅ ደኅንነቴን እመርጣለሁ” የሚል አስተያየት አዲስ አበባ ላይ እንደገጠማት ነገረችኝ። ዛሬ ደግሞ በጥዋቱ አንዲት አሜሪካዊ ጓደኛዬ በዋትሳፕ “ብጥብጥ ካለበት ዴሞክራሲ ይልቅ ሠላማዊ አምባገነንነት ይሻላል” የሚል ክርክር እንደገጠማት ነገረችኝ። በጣም ነው ያዘንኩት፤ ምክንያቱም እዚህ ድምዳሜ ላይ እንድንደርስ የሚፈልጉ የፖለቲካ ቡድኖች እንዳሉ አውቃለሁ።
በመሠረቱ ዛሬ በጉዳዩ ላይ በአጭሩ መሞነጫጨር የፈልግኩት በነዚህ ሰዎች ብቻ አስተያየት ተነሳስቼ አይደለም። “ጭቆና ለምደን ነፃነት መሸከም አቃተን” የሚሉ አስተያየቶችን ደጋግሜ እሰማለሁ። ስህተቱ የሚጀምረው ዴሞክራሲም ይሁን ነፃነት ላይ “ደርሰናል” ከሚለው ድምዳሜ ነው። አሁን ያለንበት ሁኔታ ዴሞክራሲያዊ ነፃነት ለማዋለድ በምጥ ላይ ነው ቢባል ይሻላል። እንደ አዋላጆቹ ብቃት ፅንሱ (ዴሞክራሲው) ይወለዳል ወይም ይጨናገፋል። አዋላጆቹ ካላወቁበት ደግሞ ፅንሱ እናትየውን ጨምሮ ይዞ ሊሔድ ይችላል። ስለዚህ ድምዳሜያችን ጥንቃቄ የሚያሻውን ጉዳይ ችላ እንድንለው ሊያደርገን ይችላል። ግን ዋነኛው የአረዳድ ችግር የዚህ ጉዳይ ብቻ አይደለም።
ሠላም በአምባገነንነት እና በዴሞክራሲ ውስጥ
አምባገነንነት ሕዝቡ “በቃኝ” ብሎ ቀና እስከሚል ድረስ ረግጦ የመግዛት ስልተ መንግሥት ነው። አምባገነኖች የበቃኝ ነጥብ ከመድረሷ በፊት ሁሉንም ነገር ስለሚያፍኑ ሠላም ያለ ያስመስላሉ። በአምባገነናዊ ስርዓት ውስጥ ፀጥታ ስላለ ሠላም ያለ ይመስላል። ነገር ግን የታፈነ አመፅ አለ፤ የታፈነ ደም መፋሰስ አለ። ስለ አመፁም ይሁን ስለ ደም መፋሰሱ መነጋገር አይፈቀድም። የመረጃ ምንጮችም ይታፈናሉ። በአምባገነናዊ ስርዓት ውስጥ የአመፁ መሪ መንግሥት ነው።
በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግን ሰዎች ቅሬታቸውን ሁሉ ያጮኻሉ፣ ትንሿም ብሶት ሳትቀር ትሰማለች። ይህ ራሳቸውን እንደሰጎን አሸዋ ውስጥ ቀብረው የሚኖሩትን ብዙዎች ከምቾት ዞናቸው ስለሚያስወጣቸው ሠላም ደፈረሰ ይላሉ። በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ፀጥታው ይደፈርስ ይሆናል እንጂ እንደ አምባገነናዊ ስርዓት ሠላም አይደፈርስበትም። ግጭቶች በዴሞክራሲያዊ ስርዓትም ውስጥ አሉ። ይሁን እንጂ ንግግር ስለማይታፈን ግጭቶችን በአካል ሳይከሰቱ በድርድር መፍትሔ ይፈለግላቸዋል፤ ከተከሰቱም በኋላ በአጭሩ ለመቅጨት ፈጣን መፍትሔ ለመፈለግ ዴሞክራሲ ያስችላል።
በጣም ስኬታማ የሚባሉት አገሮች ውስጥ ልዩነቶቻቸውን በዴሞክራሲያዊ ስርዓት አቻችለው ኖረዋል፤ እኛም እንችላለን!
ሐሳብ እና አመፅ
“እመፅ ማነሳሳት” እና “የጥላቻ ንግግር” የሚባሉ ችግሮች አሉ። ነገር ግን ብዙዎች ቃላቱን የሚጠቀሙባቸው የማይፈልጉትን ሐሳብ ለማፈን ሲሆን ብቻ ነው። በመሠረቱ ዓለም ዐቀፍ ስምምነቶች ላይ ሐሳብን የመግለፅ ነፃነት እንዲከበር ቁርጠኛ አቋም የተወሰደበት አንዱ ምክንያት ሐሳብን የመግለጽ ነፃነት “አመፅ” እና “ለውጥ” መካከል ሚዛን መፍጠር ስለሚችል ነው። ሐሳባቸውን በነፃነት እንዲገልፁ ያልተፈቀደላቸው ሰዎች በአመፅ ያደርጉታል። እንዲናገሩት ሲፈቀድላቸው ግን የሚጋጩ ፍላጎቶቻቸውን ሳይቀር ማስታረቂያ መንገድ በመነጋገር ይፈልጋሉ።
በአገራችን መደራጀትም ይሁን ሐሳብን የመግለጽ ነፃነት ታፍነው መኖራቸው የአደባባይ ምስጢር ነው። ይህ በእንዲህ እያለ የማኅበራዊ ሚድያ መከሰት ተናደው መድረክ ያጡትንም፣ የተስማሙ የሚመስላቸውንም የሚጋጩትንም በአንድ ግንባር አገናኛቸው። በዚህ መሐል ጎራ ለይተው በሐሳብ መቆሳሰላቸው የሚጠበቅ ነው። መሬት ላይ ለመግባባት መነጋገርን፣ የዜግነት መብት እና ግዴታዎችን ማወቅ እና ማክበርን የሚያስተምሩ ሲቪል ማኅበራት ቢያብቡ ኖሮ፥ ሐሳቦች በየጉዳዩ ላይ ዕውቀት ካላቸው ሰዎች አንደበት ተቀብለው የሚያንሸራሽሩ ሚድያዎች ቢያብቡ ኖሮ፥ ዛሬ አላዋቂዎች ባሻቸው ጉዳይ ላይ ደፋር ተንታኝ ሆነው ብዙ ተከታይ እና አድማጭ አያፈሩም ነበር። ለዚህ ያበቃን አምባገነንነት እንጂ ዴሞክራሲ አይደለም።
አሁንም ቢሆን መፍትሔው ማዕቀብ አይደለም፤ ነፃነት ነው። ሁሉም ሰዎች በነፃነት በተነጋገሩ ቁጥር አሸናፊ ሐሳቦች እየተንጓለሉ ይወጣሉ። “እውነት ለሐሰትም ሳይቀር ምስክር ነች” እንደሚባለው፥ የሚዋሹት እውነት በሚናገሩት ይጋለጣሉ፤ ጥላቻ የሚሰብኩት ፍቅር በሚሰብኩት ይሸነፋሉ።
መፍትሔው በሰው ልጅ ማመን ነው
አምባገነናዊነት እና ዴሞክራሲያዊነት በሰው ልጆች ላይ ያለን እምነት መገለጫዎች ናቸው ብዬ አምናለሁ። አምባገነን ስንሆን ሰዎች መጥፎዎች ናቸው። ቁጥጥር፣ እገዳ እና ቅጣት ያስፈልጋቸዋል ብለን እናምናለን። ዴሞክራት ስንሆን ደግሞ በተቃራኒው በሰው ልጆች ቀናነት እምነት ይኖረናል። ሰዎች ሲያጠፉ እንኳን ለክፋት ወይም ክፉ በመሆን ሳይሆን በመሳሳት ነው ያደረጉት ብለን እናምናለን። ስለዚህ ዴሞክራት ስንሆን ለሰዎች ነፃነት፣ ከኃላፊነት እና ተጠያቂነት ጋር እናጎናፅፋለን።
በዴሞክራሲ ተስፋ ቆረጥን ማለት በሰው ልጆች ተስፋ ቆረጥን ማለት ነው።
ታሪካዊቷ ኢትዮጵያ የአማርኛ ተናጋሪዎች እና የትግርኛ ተናጋሪዎች በዋነኝነት የሚዘውሯት ነበረች። በተለይ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ወዲህ ያለችው ኢትዮጵያ በሁለቱ ፉክክር እና ማመቻመች (compromise) ነበር የቆመችው። ዳግማዊ ምኒልክ ደቡቡን እና ምሥራቁን የዛሬዪቱ ኢትዮጵያ አካል ባደረጉበት ወቅት ግን በቁጥር ከትግርኛ ተናጋሪዎቹ እና ከአማርኛ ተናጋሪዎቹ የሚበልጡ ኦሮሞዎች የአገረ መንግሥቱ አካል በመሆናቸው፥ ኦሮምኛ ተናጋሪዎች በፊት ከነበራቸው ተቀናቃኝነት የበለጠ ኃይል አግኝተዋል። ይህ ክስተት ኢትዮጵያን ሦስተኛ የሥልጣን ተፎካካሪ እንድታገኝ አድርጓታል። (ይህ ማለት ግን ከዚያ በፊት ኦሮሞዎች የአገረ መንግሥቱ አካል አልነበሩም ማለት አይደለም፤ ሸዋ ቀድሞውንም ቅይጥ ከመሆኑም ባሻገር፣ በ16ኛው ክፍለ ዘመን ‘ታላቁ የኦሮሞ ፍልሰት’ የኦሮምኛ ተናጋሪዎች ሰሜኑን የኢትዮጵያ ክፍል ተቀላቅለዋል። ይህም የወሎና የጁ ኦሮሞ ፖለቲከኞችን አፍርቷል። በዘመን ወደኋላ በነጎድን ቁጥር ታሪኩ ይለዋወጣል፤ ስለዚህ ርቀን ባንሔድ ጥሩ ነው። የዚህ ጽሑፍ ዓላማም ዛሬን በሚጫኑ የቅርብ ጊዜ ታሪካዊ መቀናቀኖች ላይ ማተኮር ብቻ ነው። እንዲያውም ትግራይን ከተፎካካሪ ሕዝቦች የነጠሉ የታሪክ ኩነቶችን መለየት ነው።)
የኤርትራ (ባሕር ምላሸ) የጣልያን ቅኝ ግዛት መሆን የትግራዋዩን ቁጥር በግማሽ ቢቀንሰውም ትግራይ የመንግሥት መነሻ ማዕከል በመነበሯ ምክንያት የመሐል አገር የሥልጣን ፉክክሩ ውስጥ ተፅዕኖዋ ሳይቀንስ ከርሟል። በዳግማይ ምኒልክ ሰዐት ትልቁ ኃይል እና ሥልጣን ሸዋ ላይ ተከማችቶ የነበረ ቢሆንም፣ ትግራይ እና ደቡቡም በየአካባቢ ንጉሡ የተወሰነ ነጻነት ነበረው። በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ (ቀኃሥ) ግዜ ግን የአካባቢ ነገሥታት ሁሉ ከስመው ማዕከላዊነት ሰፈነ። ቀኃሥ የሥልጣን መስህቡን ሁሉ አዲስ አበባ ላይ – በመዳፋቸው ሥር አኖሩት።
ደርግም የቀጠለበት ይህንኑ የቀኃሥ እጅግ የተማከለ መንግሥታዊ ስርዓት ነው። ኢሕአዴግ ሲመጣ ምንም እንኳን በፌዴራል ስርዓት የማዕከላዊ መንግሥቱን ሥልጣን በሕግ (de jure) ለክልሎች ቢያከፋፍልም በተግባር (de facto) ትልቁ ሥልጣን ግን በማዕከላዊ መንግሥቱ ቁጥጥር ሥር ነበር። የኢሕአዴግ ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት በእጅ አዙር የሥልጣኑን ቁጥጥር ለኢሕአዴግ ፈላጭ ቆራጮቹ ትሕነግኦች (TPLFs) ስላጎናፀፈ መቐለን ከአራት ኪሎ ያላነሰ ባለ ሥልጣን አድርጓት ነበር።
የትግራይ ፖለቲከኞች የማዕከላዊ ፖለቲካውን ለመቆጣጠር ባደረጉት ትግል፥ የኤርትራ ትግራዋዮች ድጋፍ አስፈልጓቸው ነበር። ይሁን እንጂ የትሕነግ ፖለቲካ ቢያንስ በሕግ ደረጃ ክልሎችን የሚያጠናክር በመሆኑ መልሶ ራሱን በልቶታል። ቀድሞ ያልነበሩ የኦሮምያ እና የአማራ ክልሎች ባለፉት ሁለት ዐሥርት ዓመታት የራሳቸው መንግሥታዊ መዋቅር፣ የራሳቸውን የፀጥታ ኃይል እና አስተዳደራዊ መዋቅሮች ዘርግተው አንድ ትውልድ ሲያሳልፉ የሕዝብ ቁጥራቸውን የሚያክል ጥያቄ ይዘው ተነሱ። የትሕነግ ሰዎች የፌዴራሊዝሙን ፅንሰ ሐሳብ ሲነድፉ ወቅታዊ የበላይነታቸውን እንጂ ዘላቂ ውጤቱን የጠረጠሩ አይመስለኝም። አሁን ወደ ዳር የመገፋታቸውን ውጤት መቀበል ሲያዳግታቸው በማየቴ ይህንን አልኩ እንጂ፥ ምናልባት ሲጀምሩት አግባብ ነው ብለው አምነውበትም ሊሆን ይችላል። የሆነ ሆኖ አሁን በግልጽ እንደምናስተውለው የኦሮሞ እና አማራ ጥምረት የመንግሥትን ሥልጣን ተቆናጥጧል። ይህንን መቀልበስ የሚችል ኃይል በቅርብ ግዜ የሚመጣ አይመስለኝም።
የታሪካዊቷ ኢትዮጵያ ግዛተ ዐፄ ከተመሠረተበት ግዜ ጀምሮ አሸናፊው ተሸናፊውን እየዋጠ እዚህ የደረሰው የኢትዮጵያ አገረ መንግሥት፥ አሁን አዲስ ምዕራፍ ላይ ነው። በዶናልድ ሌቪን አገላለጽ በአማራው አንብሮ (thesis) እና በኦሮሞው ተፃርሮ (anti-thesis) የተገነባችው ‘ታላቋ ኢትዮጵያ’ (የዛሬዪቱ ኢትዮጵያ ብዬ ነው እኔ የምረዳው) የወትሮ የሥልጣን ተቀናቃኞቹን (የትግርኛ ተናጋሪዎቹን) ከማዕከላዊው መንግሥት ገለል አድርጎ፣ ተረኛ እና ዋነኛ ዘዋሪዎቹ ሁለቱ ድምር ብዙኃን፣ ማለትም የኦሮምኛ እና የአማርኛ ተናጋሪዎችን አንግሧል። ይህ ለጊዜው ቢጨናገፍ እንኳን ለአገራዊ ቀውስ እና አለመረጋጋት ይዳርጋል እንጂ አይፀናም።
![]() |
| ፎቶው ላይ ከግራ ወደቀኝ የሚታዩት፤ የኮንሶ መሪ ካላ ገዛኸኝ እና ወንድማቸው |
In an inaugural speech, Prime Minister Abiy Ahmed Ali turned almost all pessimists in to EPRDF enthusiasts. It is like he has all traits of a leader ‘naturally’. His charisma coupled with his fluency in three local languages of “the competing nationali…
(Recap the Past Decades of EPRDF’s Rule)It all started when the Ethiopian national election ended in crisis 13 years ago. But, it became very interesting when the beginning of an end of an era gives a hint with the resignation of a Prime Minister for t…