በሰሜን ወሎ በከፍተኛ የምግብ እጥረት ህፃናትን ጨምሮ ሰዎች መሞታቸውን የዳሰሳ ጥናት አመለከተ
በግጭት እና በድርቅ ምክንያት ለረጅም ጊዜ ችግር በቆየው የአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ ውስጥ ባጋጠመው ከፍተኛ የምግብ እጥረት ምክንያት የሰዎች ሕይወት መጥፋቱን በወረዳው ያጋጠመውን የምግብ እጥረት የተደረገው ዳሰሳ ጥናት አመለከተ። የወረዳው ባለሥልጣናትም ሰዎች ስለመሞታቸው ከመስማታቸው ውጪ የተረጋገጠ መረጃ እንደሌላቸው ተናግረዋል።