ሻለቃ ኃይሌ ገ/ሥላሴ የዛሬ 8 ዓመት ገደማ፣ በመስከረም ወር 2003ቱ የኢሕአዴግ ጉባዔ ላይ ተገኝቶ ንግግር አድርጎ ነበር። እናም “እናንተ ፖለቲካውን ሥሩ፣ ንግዱን ለኛ ተዉልን” የሚል ንግግር አድርጓል። ንግዱን አልተዉለትም። ሆኖም ምንጩ በሚታወቀው ሀብቱ እየተፎካከራቸው ነው። እነርሱ በወቅቱ የፈለጉት በሕዝቡ የሚወደደውን ሰው ወደ መድረካቸው በማምጣት ከሕዝባዊ መውደዱ መሻማት/መፎካከር ነበር። ከዚያ ቀጥሎ ለመጀመሪያ ግዜ ክብረወሰን ሲሰብር የለበሰውን ቲሸርት ለወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በሥጦታ አበረከተላቸው። መብቱ ነው ግን ይህም አልበቃው፣ በአትሌቲክስ ሜዳ ክብረወሰን ሲሰብር ከተሰማው ደስታ ይልቅ እዚያ መድረክ ላይ በመገኘቱ የተሰማው ደስታ እንደሚበልጥ ተናገረ። ይሁን። ዞሮ ዞሮ ግን ኃይሌ ለዚህ ሙገሳው በምላሹ የጠየቀው ‘ውለታ’ “ንግዱን ተዉልን” የሚል ብቻ ነበር። በርግጥ ከዚያ በፊት “የአገር መሪነት ማን ይጠላል?” የሚል ቃል ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፤ የግንባሩ አባል ቢሆን የሆነ የአመራር ቦታ የሚከለክሉት አይመስለኝም። ሆኖም ከዚያ በፊት የነበረው የፖለቲካ ልምድ ግን የቅንጅት አመራሮችን በሽምግልና ሥም ይቅርታ ያስፈረመው የአገር ሽማግሌዎች አባልነት ብቻ ነበር። 
ኃይሌ ገብረሥላሴን በመተቸት ለመጻፍ ስንጀምር “ኃይሌ ለአገር ውለታ የዋለ፣ ከአትሌቲክስ ጡረታ ቢወጣም በኢኮኖሚው መስክ ብዙ ሰው ለመቅጠር የበቁ ኢንቨስትመንቶች ላይ የተሠማራ” የሚሉ ማባበያዎችን ማስቀመጥ እንደ ደንብ ተቆጥሯል። እኔ ይህን አላደርግም። ለትችት የሚቀርቡት ሰዎች ስለአገር ምንም ውለታ ያልዋሉ ሰዎች ናቸው ማለት አይደለም። ሁሉም የአቅሙን አዋጥቷል። ኃይሌም ቢሆን በፍትሕ ዓይን ከማንም አይበልጥም። አሁን በኢትዮጵያ ያለው ተቃውሞ ደግሞ የፍትሓዊነት ጥያቄ ነው። የፍትሓዊ አስተዳደር፣ የፍትሓዊ ውክልና፣ የፍትሓዊ የሀብት ክፍፍል፣ የፍትሓዊ ዳኝነት፣ ወዘተ።
ከሁለት ዓመት በፊተ፣ በሕዳር ወር 2008 ቢቢሲ ሬድዮ ላይ ቀርቦ የነበረው ኃይሌ “ዴሞክራሲ ለአፍሪካውያን ቅንጦት ነው” ብሏል። ‘ዳቦ ይቅደም’ ማለቱ ነው። ሆዱን ያልሞላ ሰው ነጻነት አያስፈልገውም ከሚለው “የባርነት ለዳቦ” አስተሳሰብ ጋር የተስተካከለ አባባል ነው። አንድም በድሃ መሳለቅ ሲሆን፣ አንድም ደግሞ በዘር መፈረጅ ነው። ኃይሌ ለመናገር ያለው ድፍረት መልካም ነበር። የሚያሳዝነው ለሚናገረው ነገር ይዘት እና ውጤት ቅንጣት አለመጨነቁ ነው። ብዙ ሰዎች በሱ ንግግር የሚበሳጩት ካለው ሕዝባዊ ተቀባይነት አንፃር ንግግሩ ተፅዕኖ ስለሚያሳድር ነው። ‘ከነጻነት ዳቦ ይቀድማል’ የሚል መልዕክት ያለው ንግግር ሲያደርግ፣ ለሕዝቡ ጭቆናውን ለልማት ሲባል ቻሉት ማለቱ ነው፤ ለመንግሥቱ ደግሞ ሕዝባችሁን ዳቦ እየሰጣችሁ፣ ብትረግጧቸው ምንም አይለይም እያለ ነው። ነገሩ ከዘረኛ ነጮች አመለካከት ጋርም ይሠምራል። ለቅኝ አገዛዝ የተሰጠው አስተያየት (ማብራሪያ) ተመሳሳይ ነው። አፍሪካውያን ድህነት ይዘው እንጂ የምዕራባውያኑን ልብስ ቢያጌጡበት ያምርባቸዋል። የተመጣጠነ ምግብ ቢበሉ ይስማማቸዋል። እንደ ሕዝብ ሉዓላዊነታቸው ቢከበርላቸው ደስ ይላቸዋል። አፍሪካዊ ስለሆኑ የቅንጦት አይሆንባቸውም። ልማትና ዴሞክራሲም የሚጣረሱ ነገሮች አይደሉም። ሁለቱንም ባንዴ ማቅረብ ይቻላል። አፍሪካውያንም እንደሌላው ሁለቱንም ባንዴ ቢያገኙ አይጠሉም።
ከሰሞኑም በድጋሚ ኃይሌ አወዛጋቢ መልዕክቱን በድጋሚ አስተላልፏል። በኢቢሲ ከፓስተር ዳንኤል ጋር ቀርቦ የተናገረው ንግግር ውስጥ የሚያስቆጣ ይዘት ያላቸው ንግግሮች ደንቅሯል። ለምሳሌ “የውጭ እንትን ያለበት… የሚታይበት ነገር” በማለት የገለጸው እና በኋላ ሲተነትነው የግብጽ ስፖንሰርነት አለበት ለማለት እንደፈለገ የሚያስታውቀው ንግግሩ አንዱ ነው። ኢትዮጵያውያን በቂ ብሶት የሌላቸው ይመስል የመንግሥትን ፕሮፓጋንዳ ሰምቶ የውጭ ተልዕኮ አስፈፃሚዎች ሥራ ማስመሰል ተገቢ አይደለም። የውጪ ኃይሎች ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ተቃውሞ ሊደግፉ ይችላሉ እንጂ ሊፈጥሩት አይችሉም። አለቀ። 
ሲቀጥል ደግሞ “ቤት በመዝጋት፣ ትራንስፖርት በመዝጋት” መቃወም “የትም አገር የሌለ” ነገር ነው። ብሎ አጣጥሎታል። በመሠረቱ ኃይሌ ብዙ አገራት መሔዱ እውነት ነው። ነገር በሔደባቸው አገሮች ውስጥ ያለውን የፖለቲካ ስርዓት፣ ለተቃዋሚዎች ተሳትፎ የሚሰጡትን ቦታ እና የሕዝብን ጥያቄ የሚያስተናግዱበትን መንገድ ያጠና ወይም ለማጥናት ግዜ ያገኘ አይመስለኝም። 
ሕዝቦች ወይም የሕዝብ ክፍሎች ጥያቄ ወይም ቅሬታ ሲኖራቸው፣ ሲያሻቸው በመሾምና በመሻር፣ ሲያሻቸው ፖሊሲ በማስወጣት እና በማስከለስ የሚኖሩበት ዘመን ላይ ነን። የኛው መንግሥት ደግሞ መጀመሪያ በነፍጥ ራሱን ሾመ፣ በመቀጠል ፍትሓዊ ባልሆኑ የምርጫ ሒደቶች ሥልጣኑን አስቀጠለ። የሕዝብ ወኪል ማኅበራትን እና ሚድያዎችን አደከመ። በዚህ መንገድ ተናጋሪ እራሱ፣ ፖሊሲ ቀራጭ እራሱ፣ ሁሉ ነገር ራሱ ከመሆኑ የተነሳ የተቃውሞ መንስዔዎቻችሁን ሳይቀር እኔ ራሴ ነኝ የምነግራችሁ አለ። ሕዝቦች በድርጅት የጀመሩትን ተቃውሞ አደናቀፈ። ድርጅቶች ፈርሰውና ተዳክመው ዜጎች በየፊናቸው መቃወም ቀጠሉ። 
ኃይሌ የተቃወመው የሠላማዊ ትግል መንገዶችን ነው። በመሠረቱ በሠላማዊ ትግል ሦስት ደረጃዎች አሉ። የመጀመሪያው ማግባባት ነው፤ በጽሑፍ፣ በሠልፍ… ብዙ ተሞክሮ ሰሚ አልተገኘም። ሁለተኛው፣ አለመተባበር ነው፤ መንግሥት መር ጥፋቶች ሲፈፀሙ የነዚያ ተግባራት አካል ላለመሆን ብዙ ተሞክሯል፣ እየተሞከረም ነው። ግን ሦስተኛውም ተጀምሯል። ጣልቃ መግባት፤ መንግሥት ለጥያቄዎች መልስ አልሰጥም ሲል እና ችግሮች ከድጡ ወደማጡ እየገቡ ሲያስቸግሩ ጣልቃ ገብቶ ይበቃል እንደማለት። ይህ ደረጃ ችግሩ እነርሱን ስለማይነካቸው ብቻ ሠላማዊ ትግሉን የሚቃወሙት ሰዎች የችግሩ ጥልቀት ባይገባቸውም ጫፍ ጫፉ እንዲታያቸው ማድረግ ነው። ችግሩ ከማይገባቸው ሰዎች መካከል የናጠጡ ሀብታሞች ይገኙበታል። 
በመሠረቱ የኃይሌ ችግር የብቻው አይደለም። የሙለር ሪል ኢስቴት ባለቤት አቶ ሙሉጌታ ተስፋኪሮስ ከአንድ ታዋቂ የጀርመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ “ኢትዮጵያ ለዴሞክራሲ ዝግጁ አይደለችም” ብለዋል። የሚገባቸው መልስ ከላይ ለኃይሌ ከተሰጠው የተለየ ሊሆን አይችልም። ጥያቄው ‘ሀብታሞችን ከሕዝባዊ ተቃውሞዎች ተፃራሪ የሚያቆማቸው ምንድን ነው?’ የሚል ነው። 
ለመልሱ ደጋግሜ ወደጠቀስኩት የአሴሞግሉ እና ሮቢንሰን ‘Economic Origin of Democracy and Dictatorship’ የሚል መጽሐፍ ላይ ያገኘሁት ኅልዮትን ልዋስ። የኢኮኖሚ ልኂቃን ሁሌም የአምባገነንነት ደጋፊዎች ናቸው። የሀብት ክፍፍል በሰፋ ቁጥር ሕዝቦች ያምፃሉ። ይህ ዴሞክራሲ በግዚያዊነት ለውጥ ሊያመጣ ይችላል። ነገር ግን አሁንም የኢኮኖሚ ልኂቃኑ የመንግሥት ግልበጣ ደግፈው በኢኮኖሚ የብቻ የበላይ የሚያደርጋቸውን አምባገነናዊ ስርዓት ያቆማሉ። ማለትም ከድሀው ብዙኃን እጅግ የራቀ ሀብት ያላቸው ባለፀጎች ባሉበት አገር ዴሞክራሲ አይፈጠርም፤ ቢፈጠርም አይፀናም። ኃይሌ ገ/ሥላሴ እና ሌሎቹም ባለፀጎች ኢትዮጵያ እና አፍሪካ ለዴሞክራሲ እንዳልተዘጋጁ የሚናገሩት ወይም እንዳይዘጋጁ የሚፈልጉት የኢኮኖሚ ልኂቅነት ጥቅማቸውን (privileges) ለማካፈል ስለሚቸግራቸው ነው። 
አሁን ኃይሌ በይፋ ፖለቲከኛ መሆን እንደሚፈልግ እየተናገረ ነው። ፖለቲከኝነት የሕዝብን ውክልና አግኝቶ ጥቅማቸውን ለማስከበር የሚሠራበት መሆኑን ተረድቶ፣ ይህን የኢኮኖሚ ልኂቅነት ቦታውን እስከመታገል መድረስ መቻል እንዳለበት ከአሁኑ በይፋ ያስብበት ዘንድ ጊዜው አሁን ነው። 

On 11th of October 2017, the State-run Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) has written the long awaited report of its investigation of rights violation against Qilinto Fire defendants as per the request of the 19th Bench of Federal High Court at Lideta. On the five pages of report, EHRC revealed scars left after tortures during investigation against 16 defendants among 38 people charged under the same case. The report also revealed flogging marks left on the defendants’ backs, breaking of fingers, scars left after nail-pierced body parts and uprooted finger nails of multiple defendants. Here below I will jot down the torture scars listed in the report and will follow what the defendants have written in response:

  1. Kebede Chemeda – a scar on his right hand; breaking in his right hand thumb
  2. Ibrahim Khamil – a scar on his right leg; a scar on his left hand; scar-marked left from handcuffs
  3. Agbaw Setegn – large scar on his left leg thigh; a scar on his right leg; a sign of nail piercing on his left leg; sign of flogging on his back
  4. Tofik Shikur – a scar on his right hand; uprooting of both thumbs of his legs’ nails; a scar on his left hand
  5. Shemsu Seid – signs that look like remains of flogging at his back
  6. Misbah Kedir – Scar-marks left from handcuffs; a large scar on his right hand; a small scar on his left hand; scars on both of his right and left legs thighs; breaking of his right hand’s pointing finger
  7. Fitsum Getachew – Right hand injury
  8. Temesgen Markos – breaking of his right hand and a scar; large scars on both of his legs
  9. Ashenafi Melese – scars on both of his right and left legs; breaking of his right hand’s ring-finger
  10. Kassa Mohammed – deep scar on his right hand; injury on his head
  11. Sisay Batu – a scar on his right hand
  12. Abduldafar Asrat – uprooting of both of his legs’ thumbs’ nails
  13. Dereje Merga – six scars on his left leg; scar-marks left from handcuffs on both of his legs
  14. Tofik Ferha – a scar on his left hand; scar-marks left from handcuffs
  15. Omar Hassan – uprooting of right leg thumb’s nail; uprooting of nail of next to thumb in his left leg
  16. Seifu Girma – a scar after nail piercing on his left back shoulder; scars on both of his legs

Victims’ Responses

In a five pages of letter smuggled out of prison, the defendants have drafted their opinions on their case, complaints on their current treatment by prison admins and also their response to EHRC’s investigative report. Their response to EHRC’s report is mixed with feelings: they are partly glad EHRC didn’t deny it all as it is a culture in state institutions (at least in perceptions of citizens), on one hand; and, they think it revealed only a small part of what was done against them, on the other hand. Here is what they said:

  1. EHRC didn’t include all human rights violations perpetrated against us
  2. EHRC didn’t request for the accountability of perpetrators of the violations apart from forwarding ‘proposals’ of further investigations in obvious fear of the executive powers
  3. EHRC’s proposal for Addis Ababa Police Commission and Medical Center to further investigate the violations is like giving the violators of our rights an exit from being held accountable
  4. Regardless of all these, we are GRATEFUL to EHRC because it gave us a document that proves our confession to police according to Criminal Code Procedure 27/2 was forced and that it was not genuine confession
Screenshot of from the letters by the victims.

The victims also made calls to all media, human rights organizations, activists, diplomats and every citizen who is concerned about justice to follow their case. 

We less often discuss personalities that are fertile grounds either to be ruled by authoritarians or to be one of them. But, I think, it is important to look what is in them as it looks like we dont basically change from the way our parents have raised us. Our ancestors were either members of the oppressors or the majority (the oppressed) in the past, so are we. It happens to be we use that same privilege inherited from our parents to advance others; or, to remain underprivileged. History proves it is most probable that off springs follow their ancestors footsteps. Chances are big that children of the poor will remain poor; children of farmers remain farmer; children of democratic societies will remain democrat and etc. And, all this is until the quagmire breaks at some point. What’s keeping us a conformist? And, how can we break it?
I was reading a book titled “Between the World and Me” authored by Ta-Nehisi Coates and found some childhood experiences were shared between his world and mine. He wrote his father used to beat him out of fear, “My father was so very afraid. I felt it in the sting of his black leather belt, my father who beat me as if someone might steal me away, because that’s exactly what was happening all around us. Everyone had lost a child, somehow, to the streets, to jail, to drugs, to guns.” Thousands of miles away to Coates’ place, my mother had felt similar fear. My mother used to mention youngsters from my neighborhood and say I should not be like  them. By beating me, she thought she was protecting me. 
Until the age of 11, our father used to live far from us. Therefore, all the burden of raising us (the children) was laid on our mother’s shoulders. And, she was always worried that we may be called woman’s children”, negatively perceived saying to mean ‘undisciplined’. As a child, all I remember was that she always beat me for every little mistakes I made and sometimes to the possible mistakes I could have done. Our mother still believe she has done right and makes pride out of it claiming that we (her children) are well disciplined because she shaped us in terms of physical punishment. 
I was also beaten in Maekelawi, Ethiopia’s torture chamber for the past three regimes. I have always asked what the people who do tortures (as a job) there feel about it. I’m sure they tell themselves an excuse to do that. They may be feeling they have to do it for the wellbeing of the country, or of the people. Basically, the excuses do not have essential difference as to why our parents and teachers beat us while we were children. They want to protect us from ourselves, from our environment and from the world we live in. 
The discovery of ‘Authoritarian Personality’
Based on nature-nurture influence, psychologists define personalities in many categories. But, the so-called ‘Authoritarian Personality’ is discovered following the holocaust in the Second World War. Psychologists asked how a lot of people could accept it, and a group of American based social scientists, led by Theodor Adorno, came up with a researched answer in a book titled  ‘Authoritarian Personality’ (published in 1950). According to their findings, people with an ‘Authoritarian Personality’ tended to be:
  • Hostile to those who are of inferior status, but obedient of people with high status;
  • Fairly rigid in their opinions and beliefs;
  • Conventional, upholding traditional values.
In Ethiopia, especially in urban life, it used to be a common practice to beat children in an excuse of raising them well disciplined. It is still not stopped totally. Children are beaten by their parents, by their teachers and almost by everyone who is an elderly. 
Psychologist Theodor Adorno and his team found in a study that “people with ‘Authoritarian Personalities’ were more likely to categorize people into us and them groups, seeing their own group as superior”; and also that “individuals with a very strict upbringing by critical and harsh parents were most likely to develop an authoritarian personality.” This maybe a reason why most people in Ethiopia appear ethnocentrist and justify authoritarianism. 
People with ‘Authoritarian Personality’ are said to show these characteristics:
  • Ethnocentrism, i.e. the tendency to favor one’s own ethnic group;
  • Obsession with rank and status;
  • Respect for and submissiveness to authority figures;
  • Preoccupation with power and toughness.
Saying No to the Way We Were Made
Fortunately, individuals can beat social norms and learn to see out of box. Trends get broken. People change. 
In addition, ‘Authoritarian Personalities’ are not absolute. In critical evaluation of Adorno’s analysis of ‘Authoritarian Personality’, there are many points psychologists raise in response to his explanation of prejudice:
  • Harsh parenting style does not always produce prejudice children/individuals;
  • Some prejudice people do not conform to the ‘Authoritarian Personality’ type; and
  • Doesnt explain why people are prejudiced against certain groups and not others.
Similar experiences affect different people differently. Ta-Nehisi was not stolen by either of the streets, drugs or guns like his father was afraid. The same happened to me. But, I don’t say the beating worked. Because, when I grow up I have, one by one, dropped the norms my parents valued most. Religion is one of the most valued norms in our family. To declare that I don’t anymore believe in Christianity nor existence of a creator is something my mother would never want to hear. But, it happened. So many things happened different to my parents expectation. I do believe I stopped categorizing myself into ‘us’ and ‘them’. I hope and guess my deviation is also in terms of respect to liberty of myself and of others. I hope I have also deviated from the ‘Authoritarian Personality’ that I was raised into because, eventually, the choice is mine. It is by beating fear, not our children nor people whom we thought are dangerous, that we can win authoritarianism, consequence of fear itself.  

ከዓመታት በፊት አንድነት ፓርቲ በሕይወት ሳለ፣ የቀድሞዎቹ የኢሕአዴግ ባለሥልጣናት አቶ ስዬ ኣብርሓ እና ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ፓርቲውን ሊቀላቀሉ ሲሉ ትልቅ ፌሽታ ሆኖ ነበር። እንዲያውም ‘መርሕ ይከበር’ በሚል የተገነጠለው ቡድን፣ እነርሱን ለመቀበል የተዘጋጀውን ድግስ በአመፅ እስከማደናቀፍ ደርሷል(?)። ቅራኔው “እነርሱ የተለየ አቀባበል የሚደረግላቸው የገዢው ፓርቲ የቀድሞ አባል ስለሆኑ ነወይ?” የሚል ነበር። ተቃዋሚው የቀድሞ የኢሕአዴግ አባል ለቅቆ ሲወጣ ማግነን ያውቅበታል። በአንድ በኩል ሳስበው፣ መቃወማቸው ትክክል መሆኑን የገዢው አባላት መልቀቅ ለተቃዋሚዎቹ ስለሚያረጋግጥላቸው ይመስለኛል። በሌላ በኩል ደግሞ፣ ከጥቅም ባሕር ውስጥ መውጣት ስለሚከብድ ያንን እያሰቡ ይመስለኛል። የኋለኛውን እንዳላምን እንደ ዶ/ር ነጋሶ፣ ከጥቂቶቹ በቀር ብዙዎቹ ተገፍተው ነው ከገዢው የሚወጡት።

የሆነ ሆኖ፣ አናንያ ሶሪ በስላቅ እንደተናገረው፣ ‘ብለን ብለን ኦሕዴድ እና ብአዴን ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ ዛሚ እና ENN ነጻ ሚድያዎች የሆኑበት ዘመን ላይ ደርሰናል’። ለማንኛውም በምናገባኝ ነገሩን ከመታዘብ ይልቅ የኦሕዴድ (እንዲሁም የብአዴን) የሰሞኑ እምቢተኝነት እውነት ወይስ የሕወሓት ሴራ? ተቃዋሚው (በፓርቲ የታቀፈውም ያልታቀፈውም) ጉዳዩን እንዴት ነው ማስተናገድ ያለበት? የሚሉትን ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት እንሞክር።

የጠላቴ ጠላት ለኔ ምኔ?

በተቃዋሚዎች ዘንድ “የሕወሓት የበላይነት” መኖሩ እምብዛም አጠራጣሪ አይደለም። ማኅበራዊ ሚድያ አሁን (ከተዳራሽነቱ በላይ) በኢትዮጵያ ፖለቲካ የሐሳብ አቅጣጫ አስማሪ እንደመሆኑ ይህንን እምነት የበለጠ በማስረፅም ሆነ በመታገል ረገድ የጉዞ ካርታ (road map) አስቀማጭ ነው። ይህንን ብዙዎች መረዳታቸው ሽሚያ ፈጥሯል። መጀመሪያ ታሪክን፣ ከዚያ ድልን፣ አሁን ደግሞ ሟችና ገዳይን መሻማት ደረጃ ላይ ተደርሷል። በዚህ መሐል የሕወሓት ደጋፊ/ካድሬዎችም የራሳቸውን ትርክት ይፈጥራሉ። ተቃዋሚው ደግሞ እነርሱ የወደዱትን መጥላት፣ እነርሱ የጠሉትን መውደድን እንደ ምላሽ ይገብራል። አንዳንዴ ሳስበው የሕወሓት ካድሬዎች ተቃዋሚው የሚፈልጉትን እንዲያደርግላቸው ከፈለጉ፣ ያንን ነገር እንዳያደርገው መቀስቀስ ብቻ የሚበቃቸው ይመስለኛል። “ገዱን የምወደው ሕወሓት ስለምትጠላው ነው” የሚል መፈክር ሰምቻለሁ። አቶ ገዱ በሕወሓት ካድሬዎች ፌስቡክ ላይ ከመተቸታቸው በቀር ፓርቲያቸው (ብአዴን) በሕወሓት እልቅና የሚተዳደረው ኢሕአዴግ አባል ነው። የኦሕዴድ የሰሞኑ ነገርም ያው ነው። ይህ ዓይነቱ ምክንያት ለብአዴንም ይሁን ለኦሕዴድ የድጋፍ መሠረት ሊሆኑ አይችሉም።

ኦሕዴድ እና ብአዴን እውን ሕወሓት ላይ አምፀዋል?

ከአስቸኳይ ግዜ አዋጁ በፊት ፌዴራል ፖሊስ የኦሮምያ ከተሞችን መናኻሪያው ሲያደርገው፣ በአማራ ከተሞች ግን (ቢያንስ ተቃውሞዎችን ለመበተን) አልገባም ነበር። የአስቸኳይ ግዜ አዋጁ በታወጀበት ወቅት የሚበዙት እስረኞች የታፈሱት ከኦሮሚያ አካባቢ ነበር። ሌላው ደግሞ እነ ኮሎኔል ደመቀን ለፌዴራል መንግሥቱ አሳልፎ ባለመስጠቱ፣ በዚያ ላይ ብአዴን በላዕላይ ደረጃ ሹም ሽረት ባለማድረጉ፣ በተወሰነ ደረጃ ብአዴን የክልሉን ነጻነት (autonomy) እያስከበረ ነው ማለት ነው በሚል ወስጄው ነበር። ይሁን እንጂ የኋላ ኋላ በአስቸኳይ ግዜ አዋጁ ወቅት የክልሉን ነዋሪዎች ትጥቅ የማስፈታቱ ሥራ በፌዴራሉ የፀጥታ ኃይሎች በዝምታ እንደተሠራ ሰማሁ። እንዲሁም ከክልሉ ታፍሰው መቐለ፣ ባዶ ሽድሽት ታስረው የተፈቱ የተቃዋሚ ፓርቲ አባሎች አግኝቼ የክልሉ ነጻነት (ወይም የአቶ ገዱ እና ፓርቲያቸው እምቢተኝነት) ላይ ያለኝ የማመን ዝንባሌ ቀስ በቀስ ተገፈፈ። በርግጥም አሁን፣ የሕወሓት ካድሬዎች ስሞታቸውን ከብአዴን ላይ አንስተው ወደ ኦሕዴድ አዙረዋል። ኦሕዴድም በተራው ደጋፊ እየጎረፈለት ነው።

ኦሕዴድ በተቃዋሚዎች ዘንድ ሳይቀር ተአማኒነት እንዲያገኝ ያደረገው በኦሮሚያ ሶማሊ ክልሎች ድንበር ነዋሪዎች ዘንድ በተደረገው ግጭት ላይ፣ የክልሉ መንግሥት ባሳየው ለክልሉ ነዋሪዎች ያደላ ተቆርቋሪነት ነው። በዚህ ላይ የሶማሊ ክልል መንግሥት ያንፀባረቀው ብስለት የጎደለው ምላሽ ግጭቱን በማባባስ፣ የኦሕዴድን ተቀባይነት ጨምሮታል። የሶማሊ ክልል ገዢ ፓርቲ (መንግሥት) የ2008ቱን ሕዝባዊ አመፅ ከመቃወም ጀምሮ፣ ያሳየው ዝንባሌ በሕወሓት ወዳጅነት አስፈርጆታል።
ስለዚህ ከሶማሊ መንግሥት ጋር የኦሮሚያ መንግሥት መጋጨቱ፣ ኦሕዴድ ሕወሓትን እንደደፈረ ተደርጎ ተተርጉሟል። በተለይ እኔ ራሴ ቢሾፍቱ ተገኝቼ ባየሁት የኢሬቻ በዓል ላይ እና ከዚያ በኋላ በተካሔዱ ተቃውሞዎች ላይ የክልሉ ፖሊስ አንድም እርምጃ አለመውሰዱ፣ ቀድሞም እነጃዋር “ገዳያችን አግኣዚ ነው” የሚሉትን ተአማኒ አድርጎታል። ለኦሕዴድም ግርማ አላብሶታል።

የኢሕአዴግ አባሎች እንቢታ ምን ፋይዳ አለው?

“የሕወሓት የበላይነት” በፌዴራል መንግሥቱ ብቻ ሳይሆን በኢሕአዴግ ውስጥም አለ። ይህ የሚጀምረው ከአመሠራረታቸው ነው። የኢሕአዴግ አባል ፓርቲዎች፣ በሕወሓት ፍላጎትና ርዕዮተዓለም ተጠርበው፣ ለሕወሓት በኦሮሚያ፣ አማራ እና ደቡብ ክልሎች ቅቡልነት ለማስገኘት የተፈጠሩ ቡድኖች ናቸው። ‘እነዚህ የግንባሩ አባላት የሚያደርጉት ‘መፈንቅለ ሕወሓት’ ተረኛ ጨቋኝ ከማምጣት ውጪ ምን ያመጣሉ?’ የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም።

አምባገነን ገዢን ለመጣል የሚደረገው ትግል ብዙ ፈርጅ አለው። አንዱ አማራጭ ቡድን አቅርቦ ሕዝቡ እንዲመርጠው ማድረግ ነው። ሌላው፣ ገዢው ፓርቲን ሕዝቡ እንዳይቀበለው ማድረግ  ነው። ኢሕአዴግ አማራጭ ኃይሎችን በሚችለው መንገድ ሁሉ ያዳክማል። ተቃዋሚዎች ግን የማዳከም ዕድሉን ለማግኘት እንኳን ሲሞክሩ አይታዩም። በ2008ቱ የኦሮሞ ሕዝብ አመፅ ወቅት ግን የኦሮሞ አክቲቪስቶች ለደረሰው ጥፋት ሁሉ የክልሉን መንግሥት በመውቀስ ፈንታ አግኣዚ እና ሕወሓትን ላይ በማሳበብ በስተመጨረሻ፣ በከፊልም ቢሆን የታችኛው የኦሕዴድ ካድሬዎችን ልብ ከሕወሓት መነጠል ችለዋል። ኦሕዴድን ከሕወሓት መነጠል፣ ወይም ውስጣዊ ነጻነቱን እንዲያስከብር መቻል ለተቃዋሚው የራሱን ዕድል ይሰጣል። ስለዚህ ተቃዋሚው ከዶግማዊ ተቃውሞ ወይም ድጋፍ ይልቅ፣ ስልታዊ ድጋፍ እና ተቃውሞ ማድረግ ለድል ያበቃዋል የሚል እምነት አለኝ። ጥያቄው መሆን ያለበት፣ ‘ድጋፉ ከስልት አልፎ ሙሉ እምነት ዕድሜ ልካቸውን ሲጨቁኑ ወይም ለጨቋኝ አሳልፈው ሲሰጡ የነበሩት ላይ መጣል ደረጃ ተደርሷል ወይ?’ የሚለው መሆን አለበት።

በፌስቡክና ትዊተር ላይ ለኦሕዴድ የቀረበለትን ድጋፍ እየተመለከትኩ ነበር። ለድጋፍ የሚቀርቡትን ምክንያቶች እንደሚከተለው አዋቅሬያቸዋለሁ፦

፩ኛ፣ ኦሕዴድ በአሁን ይዞታው የኦሮሞን ጥቅም ለማስጠበቅ ብቁ ነው በሚል፤
፪ኛ፣ የግንባሩ ውስጥ-ለውስጥ ትግል ኢሕአዴግን ያፈርሰዋል/ያዳክመዋል (በዚህም ተቃዋሚው የመጠናከር ዕድል ያገኛል) በሚል፤
፫ኛ፣ በፓርቲ ውስጥ ያለው የሕወሓት የበላይነት መቀረፍ፣ በፌዴራል መንግሥቱ ውስጥ ያለውን የበላይነትም ይቀርፈዋል በሚል፤
፬ኛ፣ ታሪካዊ ብሶት የሌለበት አናሳ ቡድን ከሚጨቁነኝ፣ ታሪካዊ ብሶት ያለበት ብዙኃን ቡድን ቢጨቁነኝ ይሻላል በሚል፤
፭ኛ፣ ኦሕዴድ “የኛው” (የኦሮሞዎች) ስለሆነ ከቀናው ተረኛ መሪ እንዲሆን ዕድሉን እንስጠው በሚል፤
፮ኛ፣ ሌሎች…

በተመሳሳይ፣ የኦሕዴድን ማፈንገጥ (ያፈነገጠ መምሰል) ያልተቀበሉት፦

፩ኛ፣ የኦሕዴድ (የብአዴንም ሊሆን ይችላል) ‘ያፈነገጠ መምሰል’ የሕወሓት የፖለቲካ ሴራ ነው ብለው ያመኑ፤
፪ኛ፣ የኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች በተፈጥሯቸው ሊለወጡ የማይችሉ ናቸው የሚሉ፣
፫ኛ፣ የግንባሩ አባላት የፈለገ ቢለወጡ ምንም ዓይነት ይቅርታ ሊደረግላቸው አይገባም የሚሉ፣
፬ኛ፣ ሕወሓት በመከላከያ እና ደኅንነት መሥሪያ ቤቱ ያለው ቁጥጥር የእነኦሕዴድን መፍጨርጨር የትም አያደርሰውም እና ጉልበት እነርሱ ላይ ማባከን አያስፈልግም የሚሉ፤ እና፣
፭ኛ፣ የተለያየ ምክንያቶች የሚሰጡ ናቸው።

አፈንጋጭ የተባሉትን ምንም ዕድል ለመስጠት ፈቃደኛ የማይሆኑት በፖለቲካ ዓለም ቋሚ ወዳጅ ወይም ቋሚ ጠላት የሚባል እንደሌለ የዘነጉ ይመስላሉ። ግዚያዊ ወዳጅነቶች/ጠላትነቶች ለሚያራምዱት ርዕዮተ ዓለም ካለው ፋይዳ አንፃር ነው መገምገም የሚኖርባቸው። ሁሉን ነገር የሕወሓት ሴራ ነው ብሎ ማሰብ ሕወሓት የገዘፈ ብልሐተኛ የማድረግ አባዜ ይመስለኛል። ኢሕአዴግ ብልሕ እየሆነ ከሆነም ከሱ በላይ ብልሕ ሆኖ መገኘት ያስፈልጋል። ይህ ሕወሓትን የተወሳሰበ የፖለቲካ ጫወታ ባለቤት ማድረግም ይሁን የገዢው ፓርቲ አባላትን ሲለቅቁ እልል ብሎ መቀበል፣ ከራስ ይልቅ ለኢሕአዴግ ያለን የተደበቀ እምነት አሳባቂ ይመስላል።

ሕወሓት ለምን ዝም አለ?

ብአዴን ሲተብት፣ ኦሕዴድ ሲያፈነግጥ – አለቃ ተብዬው ሕወሓት ለምን ዝም አለ? እስኪ ማን ማን እንደሚያፈነግጥ ልያቸው እና ለቃቅሜ ልክ አስገባቸዋለሁ ብሎ ነው? ወይስ፣ የራሱ ሴራ ስለሆነ (በዚህ አጋጣሚ ተቃውሞው ስለታገሰለት፤ እንዲሁም ዳያስፖራው ከጫወታ ውጪ ስለሆነ) ደስ ብሎት ነው? እነዚህን ጥያቄዎች በአሻጥር ትንተና ሳይሆን በተጨባጭ ማስረጃዎች መገምግም ያስፈልጋል። በመልሱ ላይ ተመሥርቶ ስልታዊ ድጋፍ/ተቃውሞ ማድረግ ይከተላል። የአሁኑ ግን ጭፍንነት ይበዛዋል ባይ ነኝ።

የኦሕዴድ ኅብረ ዝማሬ ምንጩ ምንድን ነው?

የኦሮሞ ፖለቲከኞች ‘በአንድነት ኃይሎች’ በጠባብነት እና በተገንጣይነት የመፈረጃቸው ነገር ያደባባይ ምሥጢር ነው። ነገር ግን የምር ኢሕአዴግ ውስጥ ሕወሓትን ለመቀናቀን ከፈለጉ አንድ አጋር ያስፈልጋቸዋል። ፈዛዛው ደኢሕዴን የሕወሓት ካርድነቱ አሁንም እንደቀጠለ ነው። ስለዚህ ከብአዴን ጋር መተባበሩ የግድ ነው። ኦሕዴዶች ጉባኤያቸው ላይ ባሳለፉት አቋም፣ በሚሰጧቸው መግለጫዎች ለኢትዮጵያዊ ኅብረት ያላቸው ታማኝነት ጥያቄ ውስጥ መግባት እንደሌለበት በመሐላ እያረጋገጡ ነው። 7ኛ መደበኛ ጉባዔያቸው ላይ አቋም ከወሰዱባቸው ነጥቦች አንዱ “የኢትዮጵያ ፌዴራሊዝም እና የኢትዮጵያውያንን ኅብረት ጉዳይ የማይደራደሩበት” መሆኑን ገልጸዋል። የጥቅምት 25-27ቱ የምክክር መድረክ ዓላማም ይኸው ይመስለኛል። (ከታች ሶልያና ሽመልስ በትዊተር ላይ የኦሕዴድ-ብአዴንን የሰሞኑን ኅብረት የሚደግፉት ሰዎች ለምን እንደሚደግፉት የጠየቀችበትን ፖል ውጤት አስቀምጣለሁ፤ ብዙዎቹ “ለኢትዮጵያ አንድነት ይጠቅማል” በሚል ተስፋ ነው ድጋፋቸውን የሰጡት።)

ብዙዎቹ መልስ ሰጪዎች የሁለቱን ድርጅቶች
ኅብረት የሚደግፉት ኢትዮጵያዊ አንድነትን ተስፋ
አድርገው ነው። የኦሮምኛ እና እንግሊዝኛው
ፖልም ተመሳሳይ ውጤት ነው ያላቸው።

ከመደምደሜ በፊት ግን የኦሕዴድ-ብአዴን ጥምረትን ለሚደግፉ ሁለት ማስጠንቀቂያዎችን አኖራለሁ፦ አንደኛ፣ የሁለቱ ቡድኖች ጥምረት ከሠመረ ዴሞክራሲ ሊያመጣ የሚችል የመሆኑን ያክል፣ የብዙኃን ገነንነት (majority dictatorship) ሊያመጣ የሚችል እንደሆነ እንዲያስቡበት፤ ሁለተኛ፣ ተቃዋሚዎች ድጋፍ ወይም ተቃውሟቸው ሙሉ ለሙሉ በሁለቱ ፓርቲዎች ላይ ጥገኛ አድርጎ እንዳያስቀራቸው እና መርሕ-መር መሆን እንደሚኖርበት ሁሌ ራሳቸውን ማስታወስ እንዳይዘነጉ ነው።

ከሁሉም በላይ ግን ይህ በሕዝብ አመፅ የተገኘ ዕድል ለኦሕዴድ እና ብአዴን የሥልጣን መወጣጫ እርካብ ብቻ ሆኖ እንዳይቀር መትጋት ያስፈልጋል።

አግባብ ያልሆኑ እስሮች፣ ያልተጠበቁ ፍቺዎች እና የማይታመኑ የፍቺ ክልከላዎች ደጋግመው ቢከሰቱም ሁሌ እንደ አዲስ የሚያወያዩን አጀንዳዎች ናቸው። ኦቦ በቀለ ገርባ የታሰሩት የኦሮሞ ሕዝብን ጥያቄ ያለ ፍርሐት ስላስተጋቡ ብቻ ነው። ይህን የምለው ለይስሙላ አይደለም፤ የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ያቀረበባቸውን ማስረጃ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ አራተኛ ወንጀል ችሎት ተገኝቼ አድምጬያለሁ። ችሎቱ ክሳቸውን ከሽብር ወደ ‘በንግግር አመፅ ማነሳሳት’ (የወንጀል ሕጉ አንቀፅ 257/ሀ) ዝቅ ሲያደርገው ዋስትና እንደሚያሰጣቸው ግልጽ ነበር። ችሎቱ በዋስትና ጉዳይ ውሳኔ ለመስጠት ከአንድ ቀጠሮ በላይ ሲወስድ አይቼ አላውቅም። እርሳቸውን ግን ደጋግሞ ቀጠሮ ሲሰጣቸው፣ ዳኞች ዋስትናውን መከልከልም ሆነ መፍቀድ የፈሩ ይመስል ነበር። በመጨረሻ የሞት ሞታቸውን ከለከሏቸው እና አረፉ። ይግባኝ ተባለ፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በ30 ሺሕ ብር የስር ፍርድ ቤት የከለከለውን ፈቀደ። ቂሊንጦ እስረኛ ማቆያ ቤት እስረኛውን በመፍታት ፈንታ ደብዳቤው ላይ የተጻፈው ቁጥር አደናገረኝ በሚል ሰበብ ሁለት ቀን አሳደራቸው። በመሐል ፋና ሬዲዮ የኦቦ በቀለ ፍቺ በዐቃቤ ሕግ ይግባኝ ባይነት፣ በሰበር ሰሚ ችሎት ታገደ የሚል ዜና ይዞ ወጣ። Déjà vu. 
ሐምሌ ወር 2007፣ በእነዘላለም ወርቅአገኘሁ መዝገብ ሀብታሙ አያሌው፣ አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ዳንኤል ሺበሺ እና አብርሃም ሰለሞን ነጻ ከተባሉ በኋላ የተከሰተው ይሄንኑ ይመስል ነበር። ቤተሰቦቻቸው ሲፈቱ ለመቀበል ቂሊንጦ በር ላይ ሲመላለሱ፣ ማረሚያ ቤቱ ሰበብ ሲፈጥር አቆያቸው፤ በመሐል፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፍቺያቸውን እንዳገደው ተሰማ። ከዚያ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ በዞን ዘጠኝ ጉዳይ ከታሰሩት አምስቱ ድንገት ስማቸው ተጠርቶ ከቂሊንጦ እስረኛ ማቆያ ቤት ተጠርተው ውጡ ተብለው ነበር። ለቀሪዎቹም ሆነ ለወጪዎቹ በጣም አስደንጋጭ ገጠመኝ ነበር። ዐቃቤ ሕግ የነዚህን አምስቱን ክስ አንስቷል ተባለ። ከሁለት ሳምንት በኋላ ቀሪዎቻችን ፍርድ ቤት ቀረብን፣ ያኔ “ተከላከሉ ወይም በነጻ ተሰናበቱ” መባል ነበረብን። ቀጠሮ ተሰጠን፣ ተደገምን፣ 5 ጊዜ። ጥቅምት የሞት ሞታቸውን ቀሪዎቻችን ፈቱን። የነ ሀብታሙ ጉዳይ በጠበቃቸው ይግባኝ ባይነት ዓመት ያክል ተንዘላዝሎ፣ እነርሱም ተፈቱ። 
ማነው አሳሪ?
ለዚህ ጥያቄ እርግጠኛ መልስ ማግኘት ይከብዳል። ከልምድ ግን መገመት ይቻላል። እኔና ጓደኞቼ ማዕከላዊ በነበርንበት ጊዜ ማዕከላዊ የነበሩት (በቁጥጥር ሥር ያዋሉን) መርማሪ ፖሊሶች ስለኛ የሚያውቁት ጥቂት ነገር ነበር። ወረቀታቸውን እያገላበጡ ሲጠይቁን፣ የሆነ ከጀርባቸው ያለ ሰው እነዚህን ጥያቄዎች ጠይቋቸው ብሎ እንደላካቸው ያስታውቅባቸው ነበር። በሰጠናቸው መልሶች የረኩ መስለው ከሔዱ በኋላ፣ እሳት ለብሰው እሳት ጎርሰው ይመለሳሉ። መልሳችን የላኳቸውን ሰዎች አላረካም ማለት ነው። ይሔ ነገር ለኔ ያመላከተኝ ቢኖር ከኋላቸው አለቆቻቸው መኖራቸውን ሳይሆን፣ የአለቆቻቸውም አለቆች መኖራቸውን ነው። በኔ ግምት ‘የመረጃ እና ደኅንነት ቢሮ’ (ደኅንነቶች) ከሁሉም የሽብር ነክ እስሮች ጀርባ ናቸው። 
ጠበቆች አዲስ ክሶች በተመሠረቱ ቁጥር ‘የሕግ ባለሙያ እንዴት እንዲህ ዓይነት ክስ ያዘጋጃል?’ እያሉ ይገረማሉ። ዐቃቤ ሕጎች፣ ለችሎት ‘ክሱን አላየሁትም አሁን ነው የደረሰኝ’ ሲሉ ሰምቼ አውቃለሁ። የሚሰጡት ሰበብ ‘ዐቃቤ ሕግ ተቋም ነው፤ አንዱ ያዘጋጀውን ክስ ሌላው ያስቀጥለዋል’ የሚል ቢሆንም አያሳምነኝም። የሽብር ክሶቹን የሚጽፋቸው ረዥም እጅ ያለ ይመስለኛል – ይኸውም ሊሆን የሚችለው የደኅንነት መሥሪያ ቤቱ ብቻ ነው። 
የዳኞች መለማመድ
የሽብር ችሎትን መዳኘት ሕሊና ላለው የሚያሰቃይ ነገር ነው። አብዛኞቹ ተከሳሾች የአሰቃቂ ጥቃት ሰለባ ናቸው። ያንንም ሰሚ ባገኝ በሚል ተስፋ በችሎት ይተነፍሱታል። ክሱ ዝርክርክ ነው። ማስረጃዎቹ አይረቡም። ተከሳሾቹ በችሎቱ ነጻነት አያምኑም። ዳኞቹ በተለያዩ ጊዜዎች የተለያዩ ስሜቶችን ሲያስተናግዱ ይቆዩና ወደኋላ ላይ የተከሳሾቹን ሕመም መረዳት፣ ማባበል፣ ለውሳኔያቸው ረዥም ማብራሪያ መስጠት እና ፈራ ተባ እያሉ አንዳንድ እስረኞችን መፍታት ይጀምራሉ። ወዲያው ግን ይቀየራሉ።  የሽብር ችሎቶች ዳኞች በጣም ቶሎ፣ ቶሎ ከመቀያየራቸው የተነሳ አንዱ የጀመረውን ጉዳይ ሌላ የመጨረሱ ዕድል ሰፊ ነው። 
በገዢዎቻችን እና በዳኞች መካከል ያለውን ግንኙነት ከውጭ ምልከታ ለመመዘን ሞክሬያለሁ። በቀጥታ ‘እከሌን ይሄን ያክል ፍረድበት፣ እከሌን ፍታው’ የሚባሉ አይመስለኝም። ነገር ግን ዳኞቹ ሲሾሙ መጀመሪያ ለስርዓቱ ያላቸው ታማኝነት ጥያቄ ውስጥ መግባት የለበትም። አንዳንዶቹ ለገዢው ቡድን ጥብቅና ይሰማቸዋል። በዚያ ላይ ሹመቶች አሉ። በታማኝነታቸው ልክ ነው ቀደምቶቹ የተሾሙት።  በሌላ በኩል፣ በተለይ በሽብር ጉዳይ፣ ተከሳሾች የሚመሠረትባቸው የክስ አንቀፅ በራሱ መልዕክት ነው። አሳሪው ተከሳሹን ምን ያህል ማሰር እንደሚፈልግ በክሱ ያመለክታል። በዚያ ላይ የግል ፍርሐታቸው አለ፤ ‘መንግሥት በዚህ የጠረጠረውን እኔ እንዴት ማስረጃ የለም ብዬ እፈታዋለሁ?’ ከዚያም ውጪ ምናልባት በውስጥ ስብሰባቸው ላይ ‘ጉዳዩ ሲሪዬስ ነው’ ይባሉ ይሆናል። ለዚህም ይመስለኛል፣ ዳኞች ከእስረኞቹ ጋር ሲለማመዱ፣ ሐዘኔታ ሲሰማቸው፣ መተዋወቅ ጥርጣሬያቸውን እያጠፋ የመፍታት ድፍረታቸው ሲጨምር አስተዳደሩ የሚፐውዛቸው። አሁን ለምሳሌ የአራተኛው ወንጀል ችሎት ሦስቱም ዳኞቹ ከዚህ ወር ጀምሮ ተቀይረዋል። የ19ኛው ችሎት ዳኞችም በቅርቡ ተቀያይረዋል።
ከዚያ ውጪ ያለው ጫወታ በዐቃቤ ሕግ ሥም ነው። ሲያሻቸው ክሱን ያከብዱታል፤ ሲያሻቸው ያቀሉታል። ሲያሻቸው ክሱን ያቋርጡታል። ሲያሻቸው ምስክሮችን በማፈላለግ ሥም የችሎቱን መደመጥ (እስኞቹ ወኅኒ ተጥለው) ያራዝሙታል (ለዚህ ተባባሪያቸው ምስክሮቹን ማቅረብ ያለበት ፖሊስ ነው)። ሲያሻቸው ፍቺውን በይግባኝ ያሳግዱታል (ለዚህ ደግሞ ተባባሪዎቻቸው የማረሚያ ቤት አስተዳደሮች ናቸው)። 
ማረሚያ ቤቶች ውስጥ የፍቺ ወረቀት መጥቶለት እንዲቆይ የሚፈልጉት ሰው ላይ ሰበብ ይፈጥራሉ። ማረሚያ ቤቶች ውስጥ “ደኅንነት” የሚባሉ ሠራተኞች አሉ። የሥራ ድርሻቸው ምን እንደሆነ አይታወቅም፤ ግን ፈላጭ ቆራጭ ናቸው። እንደሚመስለኝ፣ ዐቃቤ ሕጎች ይግባኝ እንዲሉ (ደኅንነት መሥሪያ ቤቱ) ሲወስን፣ በቀጥታ ለማረሚያ ቤቶቹ የደኅንነት ሠራተኞች፣ እስረኞቹ በሰበብ እንዲቆዩ ትዕዛዝ ይሰጧቸዋል። በዚህ ግዜ ከላይ ፍርድ ቤት ጉዳዩ ይፈፀማል። ዐቃቤ ሕጎች ይህንን በራሳቸው አይፈፅሙትም ብዬ የምገምተው በምክንያት ነው። አብዛኛዎቹ ወጣቶች ናቸው። ካልታዘዙ በቀር በሥራው ላይ እስከ ይግባኝ ለመሔድ የተዘጋጀ ምንም የሥራ መነቃቃት አይታይባቸውም። እንዲሁ ሥራ አጥተው የገቡ ስልቹዎች ናቸው። ብዙውን ክስ አያውቁትም፤ እንዲያውም ችሎት ውስጥ ሲነበብ ከታዳሚው ጋር እየሰሙ የትየባ ስህተት ገጥሞ እንዲያርሙት ሲጠየቁ ግራ ይጋባሉ።
ታዲያ ማነው ፈቺ?
ድንገት ክሳቸው ተቋርጦ የተፈቱ ሰዎች፤ የሞት ፍርድ፣ የ22 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸው በ6 ወይም በ3 ዓመታቸው የተፈቱ ሰዎች አሉ። ይቅርታ ጠይቀው ያልተፈቱ አሉ፤ ይቅርታ ጠይቀው የተፈቱ አሉ። ይቅርታ ሳይጠይቁ የተፈቱ አሉ። መታሰራቸውም አግባብ ስላልነበር፣ መፈታታቸው ብዙዎቻችንን ያስደስተናል። ግን ማነው የሚፈታቸው? በምን መመዘኛ?  የማረሚያ ቤቱ ሥልጣን፣ ከፍርድ ቤቱ ይለያል። ነገር ግን ፍርድ ቤት “የእስረኞችን መብት አትጣስ” ሲባል ጆሮ ዳባ ልበስ የሚለው እና ባለፈው ዓመት የአራተኛው ወንጀል ችሎት ዳኞች “እኛን አትሰሙንም” ብለው ያማረሩት ማረሚያ ቤት ሥልጣን አለው እንዳይባል፤ የለውም። በቀድሞ ታጋዮች የሚመራው ማረሚያ ቤት ለሽብር እስረኞች ከፍተኛ ጥላቻ አለው። ሥልጣን ቢኖረው ስንቶቹ የሙስና እስረኞች (ከቀድሞ ታጋዮችም አሉበት) ለአስተዳደሮቹ በሚሰጡት መደለያ ብዛት ቀዳሚው ተፈቺ ይሆኑ ነበር። ስለዚህ ፈቺ አሁንም የደኅንነት መሥሪያ ቤቱ ነው። መፈታትም የነጻነት፣ ወይም የእስር ዘመንን ማረጋገጫ ሳይሆን የፖለቲካ ጫወታ ነው። አንዳንዴ እየከፋፈሉ እያሰሩ፣ እየከፋፈሉ መፍታት። ሌላ ግዜ ስጋት የሆነውን አቆይቶ፣ ስጋት ያልሆነውን  በመፍታት መደለል። ሌላም፣ ሌላም…
ከዚህ ውጪ ያለው ግምት ብዙም አይስማማኝም። ምክንያቱም፣ አሳሪም የደኅንነቱ ቢሮ፣ ፈቺውም የደኅንነት ቢሮ።

ብዙ ሰው ችላ ብሎታል። የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ግን “መደራደራቸውን” ቀጥለዋል። ከኢሕአዴግ ጋር እየተደራደሩ ያሉት ፓርቲዎች ምንም ሕዝባዊ ቅቡልነት/ውክልና የላቸውም ማለት ይቻላል። ለዚያ ነው “ድርድሩ” ጆሮ ያጣው። ዞሮ ዞሮ ኢሕአዴግ “ድርድሩን” ሲጠራ በተነሳበት ዓላማ ሊጠናቀቅ ተዳርሷል። የምርጫ ስርዓቱን ማሻሻል። ኢሕአዴግ ውጤቱን “በድርድር” የተገኘ ለማስመሰል ስለፈለገ እንጂ ቀድሞውንም ስርዓቱን ለማሻሻል ወስኗል። ለምን እና እንዴት?

፩) ቀዳሚ አሳላፊ (First Past The Post /FPTP) የተባለው የአሁኑ ስርዓት ድምፅ አባካኝ ነው። ነገሩን በምሳሌ ለማስረዳት የምርጫ 2002 የአዲስ አበባ ውጤትን እናመጣለን። በወቅቱ ከመረጡ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ውስጥ 54% ኢሕአዴግን መረጡ፣ 37% መድረክን መረጡ፣ 9% ሌሎች ተቃዋሚዎችን መረጡ። ነገር ግን ከአንድ ተቃዋሚ በስተቀር ፓርላማ ባለመግባቱ በጥቅሉ የ46% የአዲስ አበባ መራጮች ድምፅ ባክኖ ቀርቷል።

፪) ብዙ መራጭ ባላቸው የምርጫ ክልሎች ብዙ ድምፅ ያገኙ ተወዳዳሪዎች ሲወድቁ፣ ትንሽ መራጭ ባለባቸው የምርጫ ክልሎች ያሉ ተወዳዳሪዎች ባነሰ ድምፅ አልፈዋል። ለምሳሌ በዚያው የ2002 ምርጫ ወቅት በአንድ የምርጫ ክልል 42,555 ድምፅ ያገኙት የመድረክ ተወዳዳሪ አቶ ዑርጌሳ ዋኬኔ ፓርላማ አልገቡም፤ ነገር ግን በሌላ ምርጫ ክልል 12,753 ድምፅ ያገኙት የኢሕአዴግ ተወዳዳሪ ዶ/ር እልፍነሽ ኃይሌ ፓርላማ ገብተው ነበር።

፫) የምርጫ ስርዓቱ ተመጣጣኝ ውክልና (proportional representation /PR/) ቢሆን ኖሮ ለአዲስ አበባ ከተተዉት 23 የምክር ቤት ወንበሮች ውስጥ 12ቱ በኢሕአዴግ፣ 9ኙ በመድረክ እና ቀሪዎቹ ሁለቱ ለሌሎች ተቃዋሚዎች ይሔዱ ነበር። (በዚያው በ2002ቱ ምርጫ)

ይሔ ቅሬታ ሲነሳ ሰንብቶ ነበር። ኢሕአዴግ ግን ባለፉት ሁለት ምርጫዎች ወቅት ባገኘው ድምፅ መሠረት ስርዓቱ ተመጣጣኝ ውክልና ቢሆንም ኖሮ ማለፉ አይቀርም ነበር። ምክንያቱም፣

ሀ) ከምርጫ 97 ወዲህ መራጩ ሕዝብ በምርጫው ስርዓት ዴሞክራሲያዊነት ተስፋ ቆርጧል። ለመምረጥ የሚሔዱትም ወይ የቀበሌ ባለሥልጣናትን የሚፈሩ ተቃዋሚዎች፣ ወይም የኢሕአዴግ ደጋፊዎች፣ ወይም ጥቂት በምርጫ ፖለቲካ መቁረጥ ያቃታቸው መራጮች ብቻ ናቸው።

ለ) ኢሕአዴግ ምርጫው አንድ ዓመት ሲቀረው ገለልተኛ ሚዲያዎችን ከበፊቱ የበለጠ በማፈን ወይም በማገድ፣ ጋዜጠኞች እና ፖለቲከኞችን በማሰር፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን በመሰንጠቅ እና የመንግሥት ሚድያዎችን እና የመንግሥት ተቋማትን ለቅስቀሳ በመጠቀም ራሱን ብቸኛ ተወዳዳሪ አድርጎ ያቀርባል።

ሐ) ኢሕአዴግ ለታይታ ያክል ተቃዋሚ የፓርላማ አባል እንዲኖረው ቢፈልግም፣ በየምርጫ ክልሎች የሚያሠማራቸው ካድሬዎች በሙሉ በኋላ ላይ ላለመገምገም ሲሉ በራሳቸውን የምርጫ ክልል ኢሕአዴግን አሸናፊ ለማድረግ የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው ዘዴ ተጠቅመው ያሸንፋሉ። 100% ውጤት የተገኘው በነዚህ ተንኮሎች እና ዘዴዎች ነው።

ስለዚህ (ሐ) ላይ የተጠቀሰው ችግር ሳይፈጠር (ካድሬዎቹ አሉታዊ ግምገማ ሳይቀርብባቸው) ተቃዋሚ ፓርላማ የማስገቢያው መንገድ የ”ተመጣጣኝ ውክልና” በመጠቀም መሆኑን ኢሕአዴግ ተረድቷል። ነገር ግን ደግሞ ድንገት የምርጫ 97 ዓይነት ነገር ተከስቶ በቀላል የተቃዋሚዎች ዳግማዊ መነቃቃት በተመጣጣኝ ውክልና የሚገኘው ውጤት የተቃዋሚዎቹን ድምፅ ድምር ከኢሕአዴግ ሊያስበልጠው እንደሚችል ያውቃል። ለዚህ ነው “ቅይጥ ትይዩ” (Mixed-Parallel) የሚባል የስርዓት ማሻሻያ ይዞ የመጣው።

በጣም የሚያሳዝነው ተቃዋሚዎች “ቅይጥ ትይዩ” የተባለው የምርጫ ስርዓት ምን ዓይነት እንደሆነ አለማወቃቸው ብቻ ሳይሆን፣ ኢሕአዴግ እንዲያስረዳቸው መጠየቃቸውም ጭምር ነው።

በተመጣጣኝ ውክልና ስርዓት ከግል ተወዳዳሪዎች ውጪ ፓርቲዎችን ወክለው የሚቀርቡ ግለሰቦች አይኖሩም። ፓርቲዎቹ ባገኙት ውጤት ልክ ነው ለወንበሮቹ ሰው የሚመድቡት። ቅይጥ ትይዩ የተባለው ስርዓት የተወሰኑ ወንበሮች በቅድሚያ አላፊ ስርዓት፣ የተወሰኑ ወንበሮች ደግሞ በተመጣጣኝ ውክልና የሚገኝበት እና ሁለቱንም የምርጫ ስርዓቶች ጎን ለጎን ማስኬድ የሚቻልበት ስርዓት ነው። ይህ የምርጫ ስርዓት አንድ ፓርቲ ለረዥም ዓመታት የገዛባቸው አገሮች የተከተሉት ስርዓት ነው። በተለይ የምርጫ ክልሎቹን በደጋፊዎቹ አሰፋፈር ማወቀር (gerrymandering) የቻለ ፓርቲ ዘላለም አሸናፊ  የሚሆንበት ስርዓት ነው።

ተቃዋሚዎቹ ስለተጠቆመው የምርጫ ስርዓት ኢሕአዴግ ካብራራላቸው በኋላ ነው “መደራደራቸውን” የቀጠሉት። አሁን 11 ፓርቲዎችን ያቀፈው ቡድን 60:40 (ማለትም 60% ቀዳሚ የሚያልፍበት፣ 40% ተመጣጣኝ ውክልና) እንዲሆን “የመደራደሪያ” ምጥጥን በማቅረብ “ቅይጥ ትይዩ” ስርዓትን ተቀብለዋል።

በበኩሌ፣ ትክክለኛው “ሕዝባዊ ስርዓት” የሚለካው በምርጫው ውጤት ሳይሆን በምርጫዎች መካከል ባለው ሕዝባዊ ተሳትፎ ነው ብዬ ነው የማምነው። ይህ ደግሞ ያለ ሲቪል ማኅበራት፣ ያለ ገለልተኛ ብዙኃን መገናኛና ለሕዝብ ወገንተኛ የሆኑ ተቋማት በሌሉበት ይሳካል ብዬ አላምንም። ሆኖም፣ የምርጫ ስርዓቱም ቀላል ቁም ነገር ነው ብዬ አላስብም። ስለዚህ፣ ለእንደኛ ዓይነቱ አገር ድምፅ አባካኙ ቀድሞ አላፊ ስርዓት አዋጭ ነው ብዬ አላምንም። የተሻለው ተመጣጣኝ ውክልና ነበር። ይህ ግን ቀድሞም የይስሙላ በተባለው ድርድር፣ በፓርቲዎች አላዋቂነት ሳቢያ የማይሆን ሆኗል። ኢሕአዴግ በራሱ ፍላጎት የጀመረውን ድርድር እንደፍላጎቱ እየጨረሰው ነው።


[WARNING: If a personal note bores you, don’t read this.]
I was 11 years old boy when EPRDF took power. As a kid, I had a confused feeling during the time the then ‘Woyane’ controlled Addis on Ginbot 20. During the nights before, we used to listen to ‘Dimtsi Woyane’, radio broadcasted by TPLF from battlefield. I remember the elderlies were very worried however I kind of loved the guys from what they, the Woyanes, spoke on the radio. In addition, my father, despite being a member of the then national guard in the Ethio-Somali border, had said he had wished ‘Derg’ to be defeated, or at least my sister had told me he had said so. Derg’s defeat wasn’t just my father’s dream come true for me. He also retired and reunited with his family.
Even though the ‘Woyanes’ were portrayed like monsters by the time they took control of Addis Ababa, I liked them. I stared at them wondering at their never cut hair, old shorts and sandals. I told a couple of them that ‘I love them’ when they come to our village for disarmament and search for illegal holds of arms.
Soon later, they are worn with good uniforms, and ‘kesikis’ shoes which I had wished to have a pair. Their name became popularly EPRDF and the ‘Woyane’ turned a derogatory term for ‘Derg’ propagandists already associated it with equivalence to ‘separatists’.
EPRDF took control of state owned and widely listened only radio station and preached a lot about democracy, national liberation, equal rights and so on. It was my formative age. Everything I listened to was sweet and persuasive. In contrary, the elderlies in our neighborhood became so critical of the new regime. I didn’t know why but I thought it was only because it is a government that EPRDF is hated and that only because newly formed opposition political parties are not given the governing chance, that they are preferred.
I didn’t know why people became more concerned about their ethnic background. Discussions of the older people seemed always as if there is something to be worried. I couldn’t get the slightest idea of what bothered them until I turned 18 and went with my father to ‘Kebele’ to get an ID. I was asked what my ‘nationality’ (not citizenship) was. I never felt belonging to any ethnic group before. I turned my face toward my father who took almost a minute to respond to. He looked like he lost an internal battle immediately after that. My mother and father are from different regions and it never mattered before. Until now, telling the ‘nationality’ written on my ID is embarrassing to me. I always felt it isn’t representative of my identity. It is like I’m legally forced to feel belonged to one group and not to the rest.

I’m from a very humble background, economically speaking. Some sort of bitterness source of which I didn’t figure out started growing in me against the regime of EPRDF. I worked as a day laborer (‘Gutter maintainer’) when I finished high school. It was when Addis started to boom in construction. I have witnessed buildings and real estates mushrooming. These real estates’ residents lifestyle comparison to the livelihoods in my neighborhood was significantly clear. Then, I stopped working there and joined college. I had needed pocket money and started home tutoring young adults of well to do families. I graduated from college and formed a cooperative association with my college mates. Even though, cooperatives were encouraged by the time we were founding that association, many doors in the offices of the ‘kebeles’ were closed to us because we were not involved as member of any league whose members the regime wants to promote.
It was no surprise that when I first become politically active that my most concerns were of economical. I worry about the ever growing economical gap, the corruption and the marketing system that is over controlled by the regime. Now, years later, these are the least of my worries. It is not because they are improving. They are even worsening. However, by the time I had to thrive, survival became the issue again as I became more endangered beyond my wishes for economic betterment.
Back in the most contested election of 2005, I have supported CUD, participated in its unforgettable mass demonstration in May 2005, voted for it, protested in streets when I believed the election was rigged. But, I never thought EPRDF was collection of people who will let us pay a lot, afterwards, as people for staying in power. In the post 2005 election anti-government protests, the regime’s forces killed my age-mate neighbor Lealem. The regime has made everything difficult to all of hardworking age-mates of mine in the poverty wrecked neighborhood, Ferensay Legasion.
With all the challenges I have faced and the efforts I have done, life isn’t any more difficult to survive but everything in it is meaningless. The family and families in the neighborhood that have raised me are still in that vicious cycle to survive in the poverty that I had grown in. The state rhetoric of economic growth couldn’t be convincing. The construction boom in my city feels like the wealth of the city belongs to someone else. I reflected only a few of my feelings in multiple blogs I have written.
Blogging has helped me think, revise my stances, rethink the sources of problems and engage in more than writing activities. Through blogging, I have come a long way. I’m a person with a developed or even maybe with a different ideology than the person who I was when I started blogging.
My bold activities, including blogging, against the regime’s officials’ impunity, its failing policies and unconstitutional acts cost me a lot already. Everything became personal but again, I did downplay it as if it is not personal. I was detained, tortured and charged with “terrorism” and held in prison for 544 days to finally get acquitted and forced to defend myself of downgraded charges of ‘inciting violence through writing’. The case is still on hearing in two courts: at the Federal High Court in defense of the downgraded charge and at the Supreme court with my colleagues because the Federal prosecutor appealed against our acquittal. To appear before two courts for a single case is against the procedural law of the country.
Life after imprisonment couldn’t be the same as before for my colleagues and myself. I have lost all the trust on the government’s either capacity or willingness to protect its people’s wellbeing. I have read a lot of government sponsored lies written on state-owned Addis Zemen newspaper against the Zone 9 blogging collective to which I am a co-founding member and to which we were targeted of ‘enemies of the government’. My friends and I are living a tragedy. We can’t be anywhere we want for we don’t have the luxury of being considered commoners, but dissidents from whom the government is looking a mistake to throw back to jail.
Some people tell me the countless migration of Ethiopians at risky routes is motivated by economic challenges; I say the economic challenge is the foster child of political failures. The same kind of people tell me prisoners were killed when they try to escape a prison that had caught fire; they also tell me people died in stampede during a protest in a religious festival where government in the country fired tear gas. I disagree because the cause of deaths in either incident is irresponsible acts of government forces. I don’t just blame the helpless victims. The attempt to justify such kind of things drives me emotionally mad. It drives me mad because it could have been me who has drowned in an ocean or who got executed by some terrorists in Sahara desert; it could have been me who has been burned down into ashes or who has been killed in the stampede. I feel the pain because I know it all comes to me yet before a while. And, I don’t hate (even like) my emotionality because it is what makes me human.
I get angry, then sad, then frightened. I became more vulnerable than before and more than an average person. This is the life of mine and my friends. We were raised in a way to end up dissidents. We are emotionally affected. In fact, we can’t have humanity without being emotional.

Now, the government in Ethiopia has declared a ‘state of emergency’ that lasts in six months. As ‘the usual suspects’ because of our dissents, my friends and I are scared more than before. It has always been a risky thing to criticize the government here. Furthermore, this declaration has given the government the right to arrest us even without an excuse. I’m publishing this personal note as a blog because I am afraid I may be arrested sometime soon. If so I want people read me and understand me. I want people to also understand my likes to understand the desperate protests in Ethiopia. It’s an attempt to survive as human with dignity.

ሰማያዊ ፓርቲ 3ኛውን እና አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዶ አቶ የሽዋስ አሰፋን ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ!
መስከረም 28 ቀን 2009 ዓ.ም በተካሄደው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ከተጠበቀው በላይ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት እና የምርጫ ቦርድ ተወካዮች በተገኙበት በተካሄደውው 3ኛው እና አስቸኳይ ጉባኤ የፓርቲው መስራች አባልና ከዓመታት እስር በኋላ በቅርቡ የተፈቱትን አቶ የሺዋስ አሰፋን በአብላጫ ድምጽ ሊቀመንበር በማድረግ መምረጡን ፓርቲው አስታውቋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አዲስ አመራርም በቀጣዮቹ ቀናት ይፋዊ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡

የህብረተሰባዊነት ኢትዮጵያ ጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ብ/ጄኔራል ለገሰ ተፈራ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። ኢሳት (መስከረም 25 ፥ 2009) ሃገራችን ኢትዮጵያ ካፈራቻቸው ብርቅዬ፣ ጀግና እና ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን መካከል በግንባት ቀደምትነት የሚጠቀሱት የህብረተሰባዊነት ኢትዮጵያ ጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ብ/ጄኔራል ለገሰ ተፈራ በአሜሪካ አገር …

የህብረተሰባዊነት ኢትዮጵያ ጀግና ሜዳይ ተሸላሚ ብ/ጄኔራል ለገሰ ተፈራ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። Read more »

“…ኢሕአዲግ ከገባበት የፖለቲካ አጣብቂኝ ውስጥ ለመውጣት የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦችንና ሕዝቦች እርስ በእርስ ለማጋጨት የሚያደርገው ሙከራ በሕዝባችን በተባበረ ትግል ይከሽፋል!…” ======= ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ “…ኢሕአዲግ በ1983 ዓ.ም ከደርግ ስርዓት ውድቀት በኋላ የመንግስት ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ …

ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ Read more »

በውጥረት ላይ ውጥረት መደራረብ ይቁም! (አፈንዲ ሙተቂ) —– ሰሞኑን በኦሮሚያ እና በሰሜን ጎንደር የተከሰተው የተቃውሞ ንቅናቄ ሀገሪቱን ውጥረት ውስጥ ከትቷታል፡፡ አመጹ እየተጋጋለ መሄድ እንጂ የመቀዛቀዝ ባህሪ አላሳይ ብሏል፡፡ አሁንም በልዩ ልዩ አካባቢዎች ቀጥሏል፡፡ በአራቱም አቅጣጫዎች ውጥረት ሰፍኗል፡፡ በህይወት ዘመኔ ይህንን …

በውጥረት ላይ ውጥረት መደራረብ ይቁም! (አፈንዲ ሙተቂ) Read more »

የዞን ዘጠኝ ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ ፣ ፀደቀ ድጋፌ እና አዲስአለም ደስታ በሁከት ማነሳሳት ወንጀል ተጠርጥረው በትላንትናው እለት ታስረዋል፡፡ ትላንት ከስራ ሰዓት በኋላ በላሊበላ ሬስቶራንት ተገናኝተው ሻይ ቡና እያሉ በሚጨዋወቱበት ወቅት ነው ከምሽቱ 1፡30 ላይ እዛው ሬስቶራንት በነበሩ ሲቪል የለበሱ የፓሊስ …

የዞን ዘጠኝ ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ ፣ ፀደቀ ድጋፌ እና አዲስአለም ደስታ በሁከት ማነሳሳት ወንጀል ተጠርጥረው በትላንትናው እለት ታስረዋል፡፡ Read more »

ቆንጂት ስጦታው — የኢትዮጵያ ሕዝብ ስለ ልዩነትና በአንድ ዘር ስለተደራጀ ወታደራዊ ገዳይ ጦር ሊሰማ ሊያይ ኣይገባም። ይህንን የሚመኙለት ካሉ ኣንድም እድገትና ኣንድነት ፍቅርና እኩልነት የማይፈልጉ ሕዝብን ለማናከስ የሚጥሩ ኣልያም ልክ ሕወሓት በኣንድ ዘር ወጥ ምልምል ኣድርጎ በሰራቸው የኣግዓዚ ኮማንዶዎች ኣይነት …

የኢትዮጵያ ሕዝብ ስለ ልዩነትና በአንድ ዘር ስለተደራጀ ወታደራዊ ገዳይ ጦር ሊሰማ ሊያይ ኣይገባም። ቆንጂት ስጦታው Read more »

ወታደራዊ ክንፍ አስፈላጊ ነው ብለዋል ዋዜማ ራዲዮ-ከኦሮሚያ ህዝባዊ አመፅ አስተባባሪዎች ግንባር ቀደሙ ጃዋር መሀመድ በሚኒሶታ በቢሾፍቱ የደረሰውን ጭፍጨፋ አስመልክቶ መስከረም 23 ቀን የኦሮሞ ማህበረሰብ ባደረገው ስብሰባ ላይ እንደጠቆመው የኦሮሞ የመብት ትግል በቅርቡ ወደ አዲስ ምዕራፍ ይሸጋገራል። ከአዳዲስ ዕቅዶቹ መካከል የኦሮሚያን …

የኦሮሞ ተቃውሞ መሪዎች የነፃነት ቻርተርና የሽግግር መንግስት ዝግጅት እያደረጉ ነው Read more »

በኢህአዴግ ውስጥ ድንገተኛ ጊዜ አዋጅ ታውጇል ። አዲስ አበባ ጭር ብላለች። #EthiopiaProtests#AddisAbeba#MinilikSalsawi#DownTPLF Minilik Salsawi – mereja.com – በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ ኢህአዴግን የሚያስተዳድረው የህዋሃት የደህንነት ተቋሙና ወታደራዊው አመራር ነው።የደህንነት ተቋሙና ወታደራዊ ሃይሉ በሙሉ ስልጣን እየተንቀሳቀስ ነው።ድርጅት ውስጥ በድንገተኛ ጊዜ አዋጅ …

በኢህአዴግ ውስጥ ድንገተኛ ጊዜ አዋጅ ታውጇል ። አዲስ አበባ ጭር ብላለች። Read more »

የጎንደሮች የትግል አንድነት ፈጠራ ማስደነቁን ቀጥሏል፤ በእሬቻ በዓል ላይ ለሞቱት ወገኖች ሀዘናችሁ ሀዘናችን ነው ብለው ንፍሮ ቀቅለው ድንኳን ጥለው ተቀምጠው ወጣቱ እየጎረፈ ሲሆን ከታች በፎቶው እንደምትመለከቱት የትህነግ ኣግኣዚ ወታደሮች ህዝቡ ሀዘኑን እንዳይገልፅ ለመከላከል እየሞከሩ ነው።

BBN – እሁድ ዕለት በቢሾፍቱ በንጹኃን ላይ የተፈጸመውን መንግስታዊ ጭፍጨፋ ተከትሎ ተጎጂዎችን ሲያክም የነበረው ቢሾፍቱ ሆስፒታል ሁኔታውን አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ፡፡ መግለጫውን ለጋዜጠኞች የሰጡት በሆስፒታሉ ጠቅላላ ሐኪም የሆኑት ዶክተር ማንደፍሮ ኬሲ እና የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ባይሳ ተገደው በሰጡት በዚህ …

የቢሾፍቱ ሪፈራል ሆስፒታል በተጽዕኖ ሐሰተኛ መግለጫ ሰጠ Read more »

በሰማያዊ ፓርቲ ፅህፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳዬችና በፓርቲው የወደፊት የስራ እንቅስቃሴ ዙርያ ከአባላት ጋር ዉይይት ተካሄደ፡፡ መስከረም 24 2009 ዓ/ም በሰማያዊ ፓርቲ ፅህፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳዬችና በፓርቲው የወደፊት የስራ እንቅስቃሴ ዙርያ ከአባላት ጋር ዉይይት ተካሄደ፡፡ መስከረም 24 2009 ዓ/ም

ወያኔዎች አይናቸው እያየ ታሪክ ሰርተን አይናቸውን እናፈርጠዋለን። #Ethiopia Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) – ህዝቡ ነገ እንቅስቃሴ እንደማይኖር እየተናገረ ነው፤ በኣስጎሪና በሰበታ በርካታ ፋብሪካዎች ጋይተዋል። የወያኔ ውሾች በኣለም ገና ፈሰዋል። በኣቃቂ ቃሊቲ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ እየተሰማ ነው። ወያኔ ጭንቅ ውስጥ ገብቷል …

የኢሬቻውን ጭፍጨፋ ተከትሎ ህዝብ የተቃውሞ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው Read more »

የኢትዮጵያ ምድር ባቡርን በተመለከተ አማራ ክልል ውስጥ በሁለተኛው ዙር ሊሰሩ ከታቀዱ መስመሮች ውስጥ አንዱ የወረታ- አዘዞ-መተማ (መስመር 7) ነው። በዚሁ ዙር በትግራይ በኩል ደግሞ ከመቀሌ-ሽሬ ይገነባል ተብሎ ታቅዱዋል። አንድ ለአማራ እጅግ አንገብጋቢ የሆነ ጉዳይ አለ። በአጭሩ እንደሚከተለው እገልጸዋለሁ። ተስፋኪሮስ አረፈ …

“የመቀሌ-ሸሬ መንገድ ሁመራ ድረስ መሄዱ ተከልሶ ከወረታ-መተማ ድረስ ያለው ጸደቀ” እያሉ በሬ ወለደ ጸረ-አማራ እንቅስቃሴ ጀምረዋል Read more »

ህወኃት የጥፋት ኃይሎች እያሰማራ ነው:: በተለያዩ ወንጀሎች በእስር ቤት የቆዩ ‹ወጣቶችን› በጥቅም በመደለልና በማሰልጠን በዓለም ገና፣ ሰበታ አካባቢ ያሉ የሌላ ክልል ነዋሪዎች ላይ ጥቃት ለማድረስና የኦሮሞ ወጣቶች እንዳደረጉት በማስመሰል የህዝብ ለህዝብ ግጭት እንዳለ ለማሳየት፣ መተማመንና አንድነት እንዳይኖር ፣ ጥርጣሬ እንዲነግስና …

ህወኃት የጥፋት ኃይሎች እያሰማራ ነው:: Read more »

የኬኒያ ባለስልጣኖች በናይሮቢ ኢትዮጵያውያንን አሰሩ በናይሮቢ ኬኒያ የኦሮሞ ብሔረሰብ አባላት የሆኑ ኢትዮጵያውያን የኢሬቻ በዓልን ለማክበር ያደረጉትን ስብሰባ የኬኒያ ፖሊሶች ከመበተናቸው ሌላ 40 የሚሆኑትን ህገ ወጥ ናችሁ በሚል ያሰረ መሆኑ ታውቋል። ፖሊስ ኢትዮጵያውያኑ ስብሰባውን ያደረጉት ያለፈቃድ ነው በማለት ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን …

የኬኒያ ባለስልጣኖች በናይሮቢ ኢትዮጵያውያንን አሰሩ Read more »

ተቃውሞው ኣዲስ ኣበባ ፉሪና ኣለም ገና ገብቷል። #Ethiopia #EthiopiaProtests #AddisAbaba #MinilikSalsawi #Freedom ፉሪ የጀመረው ተቃውሞ ወደ አለምገናም ቀጥሏል። ፉሪ ሱቆች፣ ካፌዎች፣ ባንኮች እና ባጠቃላይ መንገድ ዳር ያሉ ንግድ ቤቶች በጠቅላላ ዝግ ናቸው። ፉሪ መንገዱ ዳር እስከ ጆሞ ድረስ በታጠቁ የፌደራል …

ተቃውሞው ኣዲስ ኣበባ ፉሪና ኣለም ገና ገብቷል። Read more »

አዳማ ተቃውሞ ተነስቷል። ወደ ሶደሬ በሚወስደው መንገድ የሚገኙ ሰፋፊ እርሻዎች እየተቃጠሉ ነው። ፌደራሎች አካባቢውን ወረውታል። የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል። የስልክ አገልግሎትም አስቸጋሪ ነው። የኢንተርኔት አገልግሎት በቢሾፍቱም ከትላንት ማታ ጀምሮ ተቋርጧል። የጂማ ዩኒቨርሲቲ ኦሮሞ እና አማራ ተማሪዎች ከአንድ ሰአት በፊት …

አዳማ ተቃውሞ ተነስቷል። Read more »

ጀግናውን የዳባትን ሕዝብ በተልካሻ ምክኒያት በመሸወድ ከዘረኛው እና ሰው በላው ሕወሓት መንግሥት ጎን የቆመ በማስመሰል ታላቅ ሰልፍ በማስወጣት በEBC ሰፊ ሺፋን ተሰጥቶት ዶክመንታሪ ፊልም ሊሠራ መሆኑ ታውቋል። ባንዳው የብአዴን ጽ/ቤት ኃላፊ አገናኘው አስማማው ከዳባት አጅሬ የሚሰራውን መንገድ ምክኒያት በማድረግ የሁሉንም …

በዳባት ሕወሓት ጸረ ሕዝብ ዶክመንተሪ ፊልም ሊሰራ ነው Read more »

ቢሾፍቱ እየተከበረ ባለው የእሬቻ በዓል ላይ የሞቱት ቁጥር ከ500 በላይ እንደሆነ ተዘገበ:: ቁጥሩ በየሰዓቱ እንደሚጨምር የተገለጸ ሲሆን በሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖችም መቁሰላቸውን ከስፍራው ያነጋገርናቸው እማኞች ገልጸዋል። በዚህ የ እሬቻ በዓል ላይ በአብዛኛው ሕይወታቸው የጠፋው ወገኖች ኦሮሞዎች እና አማሮች መሆናቸው ተገልጿል:: የትግራይ …

ወያኔ በቢሾፍቱ የጨፈጨፋቸው ወገኖች ቁጥር ከ500 በላይ ሆነ Read more »

ኢሬቻን ለማክበር የተጓዙ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የደረሰው እልቂት ከተሰማ አንስቶ መቂ፣ ዝዋይ እና ሻሸመኔ ከባድ ተቃውሞ ተቀስቅሷል። ከትላንት ምሽት አንስቶ መንገዶች በተደጋጋሚ እየተዘጉ ነው። ተሽከርካሪዎች እየተቃጠሉ ነው። ህዝብ ወደ ጎዳና ወጥቶ ቁጣውን በምሬት እየገለፀ ነው ። #MinilikSalsawi


በትናንትናው ዕለት በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ሃይቅ ለመከበር በዝግጅት ላይ የነበረውና ከኦሮሞ ክብረ በዓሎች አንዱ የሆነው ኢሬቻ በዓል ላይ ለዘገባ ተገኝተው የነበሩ ጋዜጠኞች የተከታተሉትን በዝርዝር ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። ጽዮን ግርማ የተወሰኑትን አነጋግራ ተከታዩን አጠናቅራለች። ያድምጡ ↓

በተለያዩ ቦታዎች ያሉ ዩኒቨርስቲዎች የመከፈቻ ቀናቸው እንዲዘገይ መመሪያ የተሰጠ መሆኑ ታወቀ በጎንደር፣ በጎጃም፣ በወለጋ፣ በአምቦ፣ በወሊሶ፣ በአዳማ፣ በባሌ፣ በሐረር ወዘተ. የሚገኙ ዩኒቭርሲቲዎች ከመደበኛ የዘመኑ የትምህረት መከፈቻ እንዲዘገይ የውስጥ መመሪያ መተላለፉ እየተነገረ መሆኑን ተረድተናል፡፡ በቅርቡ የተከሰተው ሕዝበዊ አመጽ ተማሪዎች ከክረምቱ መዘጋት …

በተለያዩ ቦታዎች ያሉ ዩኒቨርስቲዎች የመከፈቻ ቀናቸው እንዲዘገይ መመሪያ የተሰጠ መሆኑ ታወቀ Read more »

በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች በግፍ ለተገደሉ ወገኖቻችን መታሰብያ ስነስርዓት ተካሄደ፡፡ ——————————————————————————————– መስከረም 22 ቀን 2009 ዓ/ም ዓመታዊ የእሬቻ በዓል አከባበር ላይና በተለያየ ግዜ በብዙ የሀገራችን ክፍሎች በግፍ ለተገደሉ ወገኖቻችን መታሰብያ የሻማ ማብራትና የፀሎት ስነስርዓት በሰማያዊ ፓርቲ ፅ/ቤት ተደረገ፡፡

በመላው ኦሮሚያ ከባድ ተቃውሞ ተቀስቅሷል። ለኣዲስ ኣበባ ቅርብ በሆነችው ቡራዩ የከባድ መሳሪያ ቶክስ ማምሻውን የጀመረ ሲሆን በሙገር የዳንጎቴ ንብረት የሆነ ከባድ መኪና በሕዝባዊ ንቅናቄው ኣራማጆች ሲጋይ በቡሌ ሆራ ፍርድ ቤቶች ጋይተዋል፤ ሲኤምሲ ልዩ ስሙ መሪ አካባቢ ህዝብ እና የወያኔ ወታደሮች …

በመላው ኦሮሚያ ከባድ ተቃውሞ ተቀስቅሷል። Read more »

#Update what a black day! #በኢሬቻ የተገደሉ ወገኖቻችን ቁጥር 115 ደረሰ:: የቆሰሉ 75 ናቸዉ:: እስካሁን ባለዉ መረጃ:: በተያያዘ ዜናም ከሞትት መካከሎም ባህሉን ከኦሮሞ ወንድሞቻቸዉ ጋር ለማክበር የተገኙ የአማራ ልጆች እንዳሉ ታዉቋል:: በዚህ ሰአት ኔትወርክ የተዘጋ […]

በመተማ፣ ቋራና አርማጭሆ አካባቢዎች ጥቂት በገንዘብ የተገዙ ባንዳዎች ለአማራው ተጋድሎ ከፍተኛ እንቅፋት እየሆኑ ይገኛል፡፡ የሚከተሉት 9 ባንዳዎች በሕወሓት ሰዎች በገንዘብ በመደለል ከአማራው ሕዝብ በተቃራኒ የተሰለፉ የመተማ ገንዳ ውኃ (ሸኽዲ) ከተማ የሚገኙ ናቸው፡፡ መላው የመተማና የአርማጭሆ […]

News Ethiopia Wetatoch Dimts October 3, 2016 መረጃ ሙሉ ያደርጋል ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያ ወጣቶች ድምፅ ሳምንታዊ ዜናዎችን እንዲሁም መጣጥፎችን ለስለስ ካሉ ሙዚቃዎች ጋር ይዘንላችሁ ቀርበናል አብራችሁን ሁኑ [youtube http://www.youtube.com/watch?v=u00yOAwLugE&w=640&h=360]

የጀርመን ሬድዮ ጣቢያ ጋዜጠኛ ከምሽቱ አንድ ሰአት ላይ ስለተከሰተው ነገር ሲናገር ትናንት ማታ የነበረውን እና ዛሬ ጧት ከግርግሩ በፊት የነበረው ሰላም ተቃውሞ የነበረ እንደነበርና ነገር ግን ግርግሩና ቶክሱ ከመጀመሩ በፊት ሁሉንም ጋዜጠኞች ከአካባቢው ለቀው እንዲወጡ […]

“አማራው የራሱ ሬዲዮ ጣቢያ ካቋቋመ ኢሳትን ያዳከማል” የወቅቱ ነጠላ ዘፈን። ለምንድን ነው ኢሳት የሚዳከመው? ኢሳት የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ(OMN) ወይም የእስልምና አማኝ ወገኖቻችን ድምጽ ሬዲዮ ቢላል ብርድካስቲንግ ኔትወርክ (BBN) እና ሌሎችም በመቋቋማቸው ተዳከመ እንዴ? ለምንስ እነሱ ሲቋቋሙ ኢሳት ይዳከማል የሚል እሮሮ …

“አማራው የራሱ ሬዲዮ ጣቢያ ካቋቋመ ኢሳትን ያዳከማል” የወቅቱ ነጠላ ዘፈን Read more »

ከሰለሞን አባ ሰላምታየን እንደ “ያ ትውልድ” የፍቅር ደብዳቤ ሳላስረዝም ወደዋናው ጉዳየ ልግባ ። ክቡርነትዎ ኢሳት የግንቦት ሰባት ልሣን መሆኑን አውቀው በአንዳንድ ነገር ሊያጋድል ይችላል ብለው መጠርጠርዎ መልካም ። ነገር ግን ለፖለቲካል ሰርቫይቫል ተብሎ ድንበር ያልለፈን አካሄድ ደግሞ ሌላው ወገን አይቶ …

ይድረስ ለክቡር አቶ ፈቃደ ሸዋቀና (ከፌስቡክ የተገኘ) Read more »

ጽዮን ግርማ/ VOA በቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ ኃይቅ ሊከበር በዝግጅት ላይ የነበረውና ከኦሮሞ ክብረ በዓሎች አንዱ የሆነው እሬቻ በዓል ተስተጓጉሏል፤ በግጭትና በትርምሱ ወቅት ብዙ ሕይወት መጥፋቱና በአካልም ላይ ብዙ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል፡፡ ዋሽንግተን ዲሲ — በቢሾፍቱ ሆራ […]

ኢትዮሚዲያ በ26/09/2016 ከግደይ ዘርአፅዮን ጋር ያካሄደውን ቃለ ምልልስ አንብቤዋለሁ። ግደይ ዘርአፅዮንን የማውቀው ገና ትግሉ ሳይጀመር በፊት ነው። ግደይ በጥሩ ቤተሰብ ያደገ ግለሰብ ነው። ትገሉ ሳይጀመር በመስከረም 1967 አዲስ አባባ ውስጥ ማገበትን መሰረቱ። የመሰረቱትም አረጋዊ በርሄ፣ […]

ያሳዝናል፤ ያናድዳል፡፡ ለነጻነት በሚደረግ ትግል የንጹሐን ዜጎች ሞት የሚጠበቅ ቢሆንም ባዶ ቄጠማን በእጃቸው ይዘው ከአምላካቸው ለአገራቸው ሰላም ሲለምኑ በነበሩ ሰዎች ላይ ይህን ዓይነት መቅሰፍት ሲወርድ በምን ቃል መግለጽ ይቻላል? በዚህች አገር ላይ በዓልን በፌሽታና በደስታ […]

አሁን ባለው ቁጥር ከ295 በላይ ሰዎች በቢሾፍቱ ተረሽነዋል፡፡ 120 አስክሬኖች ወደ ቢሾፍቱ ሆስፒታል ሲሄዱ 175 የሚሆኑት አስክሬኖች ወደ አዲስ አበባ ተጭነዋል፤ወደ ቢሾፍቱ ሀይቅ ውስጥ ከአስለቃሽ ጪስ እና ከጥይት ሸሽቶ የሰጠመ ህዝብ ቁጥር ብዛት ግን ገና አልታወቀም፡፡ በሻሸመኔ ህዝቡ ለተቃውሞ ወጥቶ …

በሻሸመኔ ህዝቡ ለተቃውሞ ወጥቶ በአደባባይና በየቀበሌው ከታጣቂ ኃይል ጋር ተፋጦ ይገኛል Read more »

በቢሾፍቱ ኢሬቻ በአል ላይ ህዝቡ ያሳየውን ሰላማዊ የተቃውሞ ስነ ስርአት የሚያሳየውን ይህን ቪዲዮ ተመልከቱ። ይህ 200 ሰዎችን ለመግደል ምክኒያት ይሆናል? አሳዛኝ ነው። [youtube http://www.youtube.com/watch?v=UhePpkX_Jp8]