የናይጀርያ ገዥዉ ፓርቲ የህዝባዊ ዲሞክራቲክ ፓርቲ በእንጊሊዘኛ አፅህሮቱ PDP አዲስ የፖለቲካ ፈተና ገጥሞታል። የገዥዉ ፓርቲ አባላት የነበሩ ሰባት ሀገረ ገዥዎች ከፓርቲያቸዉ አፈንግጠዉ፤ All Progressives Congress (APC በእንግሊዝኛ ምሕፃሩ) ከተሰኘዉ ዋና ተቃዋሚ ፓርቲ ጋር የጋራ ፓርቲ መስርተዋል።

ህዳር ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሳውድ አረቢያ የሚታየው ሁኔታ እጅግ አስፈሪ ነው ይላሉ ያነጋገርናቸው ዜጎች። ከ40 ሺ በላይ ኢትዮጵያን በእስር ቤቶች ውስጥ ይገኛሉ። ወደ አገራቸው ለመመለስ የሚፈልጉ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ቀናቸውን ይጠባባቃሉ። የኢትዮጵያ መንግስት በመቶ ሺ የሚቆጠረውን ስደተኛ ለማስተናገድ የመደበው የሰው ሀይል 40 ብቻ ነው። የሳውድ አረቢያ መንግስት ደግሞ በተዘዋዋሪ መንገድ ኢትዮጵያውያን ከአገሪቱ …

ህዳር ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአውሮፓ ህብረት የፓርላማ አባል እና የኢትዮጵያን የ1997 ምርጫ የታዘቡት ወ/ሮ አና ጎሜዝ ይህን የተናገሩት አዲስ ስታንዳርድ ለተባለ የእንግሊዝኛ ጋዜጣ ነው። በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ባለው የአውሮፓ፣ አፍሪካና ካረቢያን አገሮች የፓርላማ ጉባኤ ላይ የተገኙት ወ/ሮ አና የአምባገነን ምንጭ የሆነው መለስ ዜናዊ ቢሞትም፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ፖለቲካዊ ለውጥ አለመምጣቱን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ተለውጣለች …

የሶማልያው ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ ሙሐመድ ጠ/ሚንስትር አብዲ ፋራህ ሺርዶን ሥልጣን እንዲለቁ በመጠየቃቸው ገና በሁለት እግሮችዋ መቆም ያልቻለችውን ሀገር ለሌላ ዙር ቀውስ እንዳይዳርጋት አሥጋቷል። የሁለቱ መሪዎች አለመጣጣም ሰበብ ምን እንደሆነ በትክክል

ባለፈው አንድ ዩኒቨርሲቲ ሄጄ አንድ ጓደኛዬ የነገረኝ አሳዛኝ ነገር ነበር፡፡ የአማርኛ መምህር ለመቅጠር የተሰጠው ፈተና ዩ፣ ዪ፣ ዬ እና ዮ ን መጻፍ ነበር፡፡ በጣም የሚገርመው ግን ከተፈተኑት አምስት የሁለተኛ ዲግሪ ያላቸው መምህራን አንዱ ብቻ አሟልቶ ጽፏቸዋል፡፡ ወደፊት አማርኛን ማንበብና መጻፍ የሚችል ሰው ለማግኘት ሥዕለት ሳያስፈልግ አይቀርም፡፡ እስኪ ይኼንን ማስታወቂያ ተመልከቱት ‹ይከላከላል› ወይስ ‹ይከሳከሳል› – ተከላካይ ነው ቦክሰኛ?

ከአስተዳዳሪው ጋራ የጥቅም ግንኙነት ያላቸው የቅ/ላሊበላ ደብር ሰበካ ጉባኤ አባላትና የአስተዳደር ሠራተኞች፣ ለመኪና ‹ሽልማቱ› ከግማሽ ሚልዮን ብር በላይ (በአንዳንድ ምንጮች መረጃ እስከ ብር 800,000) ከደብሩ ካዝና ወጪ ማድረጋቸው ተጠቁሟል፡፡ ‹‹መነኩሴ ቢሸለም መስቀል እንጂ መኪና ምን ያደርግለታል?›› የሚሉ የቅ/ላሊበላ ደብር ካህናትና ምእመናን፣ ‹‹አባ ገብረ ኢየሱስ በሕግ መጠየቅ እንጂ ሽልማት አይገባቸውም›› በሚል ኅዳር ፲፮ ቀን ፳፻፮ ከቀትር …

እስካሁን ባሉት አመልካች ሁኔታዎች ከተሄደ ኢትዮጵያ በመጪው አስር ዓመታት ጊዜ ዉስጥ መካከለኛ ገቢ ያላት አገር የመሆን ግባቸው እንደሚሳካ የኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ።

አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ዛሬ አዲስ አበባ ዉስጥ በተከፈተዉ የአፍሪቃ ንግድና ኢንዱስትሪ ምክር ቤቶች ስብሰባ ላይ ባደረጉት የመክፈኛ ንግግር ነው አገራቸው በፍጥነት በማደግ ላይ ካሉ ነዳጅ አምራች ያልሆኑ አገሮች አንዷ መሆኗን የተናገሩት።

“ፖሊሲዎቻችንና ስታራቴጂዎቻችን ብቃትና ጥራታቸዉን አረጋግጠዋል። እናም አሁን ያሉትን አመልካቾች ከተከተልን፥ ኢትዮጵያ በመጪዎቹ አስር ዓመታት ጊዜ ዉስጥ መካከለኛ ገቢ ያላት አገር የመሆን ግባችንን እናሳካለን፤” ሲሉ ጠቅላይ ሚንስትሩ እምነታቸውን ገልጠዋል። የዛሬውን ጉባኤ ያዘጋጀዉ ከአርባ በላይ አገሮች ብሔራዊ ምክር ቤቶች አባል የሆኑበት የፓን…

ህዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን እንደገለጹት ስትርሀ እየተባሉ በሚጠሩ የማጎሪያ ካምፖች ውስጥ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ችግር ላይ ይገኛሉ። በውሀ እና በምግብ እጥረት የሚሰቃዩ እርጉዝ ሴቶች፣ ህጻናትና እናቶች አሁንም የድረሱልን ጥሪያቸውን እያሰሙ ነው። በማጎሪያ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያዊን ምግብ እና ውሀ ለመግዛት ወጣ ሲሉ እንደሚገደሉ ጓደኞቻቸው የተገደሉባቸው ኢትዮጵያውያን …

ህዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ግለሰቡ የተገደለው ባለፈው ሳምንት ሲሆን፣ ገዳዮችም ከመንግስት ጋር ባላቸው ቅራኔ የተነሳ ጫካ የገቡ ሰዎች ናቸው ተብሎአል። ከአካባቢው ነዋሪዎች ባገኘነው መረጃ መሰረት በጅማ ዞን ኪሼ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው በለጣ ጫካ ውስጥ በመደበቅ አልፎ አልፎ ጥቃት የሚሰነዝሩ የአኮረፉ ነዋሪዎች ቻይናዊውን የገደሉት ፎቶ ግራፍ ለማንሳት በሚሞክረበት ወቅት ነው። ቻይናዊው …

ህዳር ፲፱(አስራ ዘጠኝ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ጅጅጋን በማስመልከት በተላለፉ ዜናዎች ላይ አንዳንድ ማስተካከያዎች እንድናደርግ የከተማዋ ነዋሪዎች ጠይቀውናል። ኢሳት በብሄር ብሄረሰቦች በአል ምክንያት የጅጅጋ ዩኒቨርስቲ እንደተዘጋ አድርጎ ያስተላለፈው ዜና ስህተት ያለበት ሲሆን የተዘጉት የጅጅጋ ነርሲንግ ማሰልጠኛኮሌጅ እና የጅጅጋ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም እንጅ ዩኒቨርስቲው አለመሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን። የአቶ መለስ ዜናዊ ሀውልት እንደፈረሰ ተደርጎ በቀረበው …

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕግ አገልግሎት መምሪያ ዋና አማካሪ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኰንን የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ኾነው ተሾሙ፡፡ በዛሬው ዕለት የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኾነው የተሾሙት ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ÷ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት ከ፲፱፻፺፫ …

ባለፈዉ ሳምንት ዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ የተገደሉበትን 50ኛ ዓመት ዘክራ ዉላለች። እንደ ጎርጎረሳዉያኑ ህዳር 22 ፤ 1963 ዓ,ም ቀትር ላይ በደቡብ ቴክሳስ ዳላስ ከተማ፤ በጥይት የተገደሉት ፕሬዚደንት ኬኔዲ ሰለባ የሆኑት ስልጣን ላይ ከወጤ ሶስተኛ ዓመታቸ ን ሊይዙ ትንሽ ወራቶች እንደቀራቸዉ መሆኑን ዘገባዎች ያሳያሉ።

ባለፈው መስከረም በኬንያ መዲና በናይሮቢ ፤ የሶማልያው አክራሪ እስላማዊ ድርጅት (አሸባብ)WESGATE በተሰኘው ዐቢይ የገበያ አዳራሽ፣ አደጋ በመጣል ከ 60 በላይ ሲቭሎች መግደሉ የሚታወስ ነው። እ ጎ አ በ 2006 የሶማልያ የሸሪያ ፍርድ ቤቶች ሕብረት

በ1997 ኢትዮጵያ ዉስጥ የምርጫ ሒደት የተከታተለዉ የአዉሮጳ ሕብረት የታዛቢዎች ቡድንን የመሩት እና የኢትዮጵያ መንግሥትን አጥብቀዉ የሚተቹት የአዉሮጳ ሕብረት እንደራሴ ወይዘሮ አና ጎሜሽ በትናንቱ ጉባኤ በነበረዉ ክርክር ዋና ተሳታፊ ነበሩ

ባህር ዉስጥ ከመስጠም የተረፉ ሶስት ኢትዮጵያዉን ተገን ጠያቂዎች ከትናንት በስተያ የቤልጂየም ጦር ሠራዊት ላይ ክስ መሠረቱ። ከሁለት ዓመታት በፊት በጀልባ የተጫኑ አፍሪቃዉያን ስደተኞች ወደጣሊያን ሲጓዙ ለአደጋ መጋለጣቸዉን ከተመለከቱ በአካባቢዉ ከነበሩ ኃይሎች ርዳታ ባለማግኘታቸዉ 63ቱ ህይወታቸዉ አልፏል።

ቴዎድሮስ አድሃኖም Tewodros Adhanomኤፍሬም ማዴቦ
የኢትዮጵያ ህዝብና እናስተዳድረዋለን የሚሉት አምባገነን ገዢዎቹ ተስማምተውና አንዱ ሌላውን አክብሮ የኖረበት አንድም የታሪክ አጋጣሚ የለም። የእስከዛሬው ታሪካችን ምዕራፍ በጥቅሉ ሲታይ ታሪካችን የሚቋጨው ህዝብ ተረገጠ፤ ተጋዘ፤ ገዢዎች ደግሞ ረገጡ፤ ገዙ፤ አሰሩ፤ አጋዙ እየተባለ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አሸናፊ ንጋቱ
በስልጣን ላይ ያለው የወያኔ መንግስት የዛሬ 22 ዓመት አንግቦት የነበረውን የዲሞክራሲ መፈክር በማየት ዲሞክራሲ የጠማው የኢትዮጵያ ህዝብ የደስታ ጮቤ በመርገጥ ነበር የተቀበለው። ነገር ግን ይህ መፈክር ድራማ መሆኑ እየዋል እያደረ ነበር እየተጋለጠ የመጣው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም፣ ትርጉም፦ ነጻነት ለሀገሬ

ባለፉት አስርት ዓመታት በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች በአገራቸው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አህጉር በተለየ መልኩ ተንሰራፍቶ እየተፈጸመ ካለው ጭካኔና ርህራሄ የጎደለው አምባገነናዊ ስርዓት ለማምለጥ ሲሉ እግራቸው ወዳመራቸው አገር በመሰደድ ላይ ይገኛሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አበራ ሽፈራው ከጀርመን
በተለይም ባለፉት 22 ዓመታት በሀገራችን ለተከናውኑት አበይት ችግሮች ሁላችንም እጆቻችንን ወደ ህወሓት እየቀሰርን ለችግሮቻችን መፍትሔ መስጠት አቅቶን ይባሱኑ ለከፍተኛ ስቃይና መከራ መዳረጋችንና፤ መፍትሔውን ከህወሓት እየጠበቅን ለችግራችን መባባስ አስተዋጽኦ በማድረጋችን ችግራችን እየተባባሰ ቀጥሏል። በምን መልኩ ነው አስተዋጽኦ አደረግነው?

ሙሉውን አስነብበኝ …

ህዳር ፲፰(አስራ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በርካታ ተስፋ የቆረጡ ኢትዮጵያውያን መዲናህ ከተባለው መጠለያቸው  ግንብ እየዘለሉ  ወደ ታይባን ዩኒቨርስቲ ካምፓስ እንደገቡ የአገሪቱ ፖሊስ አስታውቋል። ብርጋዴር ፋህድ ቢን አሚር አል ጋናም እንደገለጹት 15 ኢትዮጵያውያን ወደ ዩኒቨርስቲው ግቢ የገቡ ሲሆን የጸጥታ ሀይሎች ኢትዮጵያውያኑን በመያዝ ወደ ማጎሪያ ካምፓቸው ልከዋቸዋል። ኢትዮጵያውያኑ በሰዎች፣  በመኪኖች ወይም ህንጻዎች ላይ ጉዳት እንዳላደረሱ …

ህዳር ፲፰(አስራ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሶማሌ ክልል 8ኛውን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ታከብራለች መባሉን ተከትሎ የክልሉን ዋና መቀመጫ ጅጅጋን  አርቲስቶች እና የመንግስት ባለስልጣናት በየጊዜው እየጎበኙዋት ነው። ለበዓሉ ዝግጅት የተመደበለትን 31 ሚልዩን ብር ከዝግጅቱ በፊት ቀድሞ ያጠናቀቀው የሶማሌ ክልል መንግስትን ለበአሉ ማክበሪያ እና ማድመቂያ በማለት ተጨማሪ 14 ሚሊዮን ብር ጠይቋል። ለበዓሉ ማስተናገጃ የሚሆን ስቴዲየም …

ህዳር ፲፰(አስራ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአህጉሪቱ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ተንከባካቢ አካል ነው የተባለው ኮሚሽን፣ ኢትዮጵያ ለስኳር ልማት በሚል በታችኛው ኦሞ አካባቢ የሚገኙ ዜጎችን በማፈናቀል እየፈጸመችው ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በፍጥነት እንድታቆም ጠይቆ፣ በጉዳዩ ላይ ምርመራ እንደሚያደርግም ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት በአካባቢው በሚኖሩ ብሄረሰቦች ላይ ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ግርፋት እና እስራት መፍጠሩን …

ህዳር ፲፰(አስራ ስምንት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዩጵያ የቴሌቪዥን ድራማ ታሪክ በረዥምነቱ ቀዳሚውን ቦታ በመያዝ የሚታውቀው ሰው ለ ሰው ተከታታይ ድራማ 109 ክፍሎች ያህል ከተላለፈ በኃላ፣ ሰዎች በማህበራዊ ድህረ ገጾች የድራማው ተዋንያን የሆነውን በትወና ስሙ አስናቀ የተባለውን  ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለቤት ከወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር  በማመሳስል ገጸባህሪውና ወ/ሮ አዜብ መስፍን ባለስልጣናትን በገንዘብ …

ዓለም አቀፍ የኢንተርኔት መረጃ አገልግሎት ማግኛ ድር (WWW)የተሰኘው ድርጅት መሥራች፣ ብሪታንያዊው ሳይንቲስት፣ ሰር ቲሞቲ በርነርስ ሊ፤ ይኸው በይፋ መረጃ አቅራቢ የሆነው የኢንተርኔት «ድር» ቁጥጥርና ቅድመ ምርመራ እያየለ መምጣቱ ለወደፊቱ

ጥንታዊ ስልጣኔን ለታሪክ ትተን ከድህነት ወለል በታች ከሚፈረጁት የዓለማችን ኣገራት ተርታ ተሰልፋ የምትገኘው ኢትዮጵያ ግን ደግሞ ይህ ነው የማይባል የተፈጥሮ ሀብትም እንዳላት ይታወቃል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከዓለም እጅግ ደሐ የሚባሉ ሐገራትን የምጣኔ ሐብት ይዞታን የገመገመበትን ዘገባ ባለፈዉ ሳምንት ይፋ አድርጓል።ዓለም አቀፉ ድርጅት እጅግ ደሐ ብሎ ከፈረጃቸዉ 49ኝ ሐገራት ዉስጥ 34ቱ የአፍሪቃ ሐገራት ናቸዉ።

የኢትዮጵያ መንግስት ከስዑድ አረቢያ ከሃምሳ ሺህ የሚበልጡ ዜጎች ወደሀገር ቤት መመለሳቸዉን አስታወቀ። የመንግስት ቃል አቀባይ ለዶቼ ቬለ እንደገለፁት ለዚሁ ተግባር በጀት ተመድቦ በሚካሄደዉ ዘመቻም በየዕለቱ ወደስምንት ሺህ ገደማ የሚሆኑት እየገቡ ነዉ።

የለውጡ ቀንደኛ ተገዳዳሪዎች፣ ‹‹ጠላቶች ነበርን፤ ዛሬ የሰማነውና ያየነው ጥናት ግን መልካም ኾኖ አግኝተነዋል፤›› ሲሉ ራሳቸውን ሒስ አድርገዋል፤ ‹‹ቤተ ክርስቲያኒቱ የተወለደችው ዛሬ ነው፤›› ሲሉም የመዋቅርና አሠራር መመሪያ ጥናቱን አድንቀዋል፤ ጥናታዊ ውይይቱ በላቀ የለውጥ መነሣሣት ቀጥሏል፤ ከፍተኛ አመራሩ የተሳተፈበት የቀዳማይ ዙር ጥናታዊ ውይይት መርሐ ግብር ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡