መጋቢት ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በውጭ ጉዳይ ሚንስቴር የፐብሊክ ዲፕሎማሲና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ጄኔራል አቶ ጌታቸው አረዳ እንደተናገሩት ” የኤርትራ መንግስት ሃሳቡን ቀይሮ ወደ ሰላም ቢመጣ የኢትዮጵያ መንግስት ችግር የለበትም። የኤርትራ ተቃዋሚዎች ከጉያችን ስላሉ ምን እንሆናለን የሚል ስጋት የለብንም” በማለት ተናግረዋል።

የታጠቁ የኤርትራ ሃይሎች እርምጃ የማይወስዱት በድንበር አካባቢ የኤርትራ ሰራዊት በብዛት ስላለ መሆኑን የገለጹት ጄኔራል ዳይሬክተሩ፣ የኤርትራ መንግስት ከእኛ ጋር ለመስማማት ከፈለገ ምንም ቂምና ቁርሾ የምንይዝበት ነገር አይኖርም ሲሉ አክለዋል።

ኢትዮጵያ 20 ሺ ኤርትራውያን ስደተኞችን ታስተምራለች የተባለውም የተጋነነና ቁጥሩ ከ1800 እንደማይበልጥ የተናገሩት አቶ ጌታቸው፣ እነዚህ ተማሪዎች የጸጥታ ስጋት እንደማይሆኑና አስፈላጊው ምርመራ ተካሂዶባቸው ትምህርት እንደጀመሩ ገልጸዋል።

ከኤርትራ ስደተኞች ይልቅ የጸጥታ ስጋት የሚፈጥረው የኢትዮጵያ ተስፋ የቆረጠው ወጣት ነው ያሉት አቶ ጌታቸው፣ ይህን ወጣት መከታተል የጸጥታ ችግሮችን እንደሚቀርፍ ገልጸዋል።

በንግግራቸው መሃል ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ባይከብርም የመክፈር ፍላጎት እንዲኖረው በማድረጋችን ጸጥአየትኩረት አቅጣጫውን ለማስቀየር ችለናል ብለዋል።

የጅቡቲ ወደብን በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ደግሞ፣ ለጅቡቲ ወደብ የምንከፍለውን ኪራይ የጅቡቲ መሪዎች ቤተሰቦች የሚቀራመቱት በመሆኑ አገሪቱ ወደብ ትከለክለናለች ብለን አንሰጋም ሲሉ መልሰዋል።

የመንግስት ባለስልጣናት የሙስና መንገዳቸውን ለማሳካት ሲሉ በመንግሥት ፖሊሲ፣ አሠራርና መመርያ ላይ ጫና እየፈጠሩ እንደሚመቻቸው ተደርጎ እንዲወጣ በማድረግ ላይ ናቸው ሲል ሙስና ኮሚሽን አማሯል።

ኢትየጵያ ውስጥ አሁን ያለው የሙስና መጠን ትናንትና ከነበረው እጥፍና ከእጥፍ በላይ አሻቅቧል፡፡ አሁን አገሪቷ ውስጥ ያለው የኑሮ ውድነት ወደላይ እንዲያሻቅብ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱም የሙስና ጣርያ መንካት ነው፡፡ በዚህ ደረጃ ላይ አሳሳቢ መሆኑን መግለጽ ቀርቶ የእገሌን አገር ደረጃ አያክልም የሚለውን አባባል የኢትዮጵያ ሕዝብን እንደመናቅ ይቆጠራል፡፡በአሁኑ ወቅት ሙስና በኢትዮጵያ ውስጥ ተንሰራፍቷል፡፡ ባለጉዳይም ጉቦ ካልሰጠ ጉዳዩን እንደማያስጨርስ፤ ጉዳይ ፈጻሚም ገንዘብ ካላገኘ ጉዳይን ማስጨረስ የማይቻልበት ደረጃ መድረሱን በገሃድ በሚታይበት ደረጃ ላይ ነን፡፡ በቀበሌ፣ በወረዳ፣ በክፍለ ከተማ፣ በአዲስ አበባ መስተዳድር፣ በፖሊስ፣ በፍርድ ቤት፣ በአገር ውስጥ ገቢ፣ በጉምሩክ፣ በመንገድ ትራንስፖርት፣ በሆስፒታሎች፣ በኢሚግሬሽን፣ ወዘተ ጉዳይን ለማስጨረስ ጉቦ መስጠት የተለመደ ሆኗል፡፡

ጉቦ መስጠትም ሆነ መቀበል እንደ ብቃትና እንደ ሥልጡንነት እየታየ ነው፡፡ ጉቦ የማይቀበል የማይረባና የማይጠቅም ተብሎ የሚሰየምበት ደረጃ ላይ መድረሳችንን እያንዳንዱ ሰው በሚገባ ያውቀዋል፡፡ እንደዚህ በመሰለ አስፈሪ ሁኔታ ውስጥ ባለንበት ወቅት ሙስና ኢትዮጵያ ውስጥ አሳሳቢ ደረጃ ላይ አይደለም ሲባል ምን ማለት ነው? መረጃው የተገኘውስ ከየት ነው? ከተበዳይ ወይስ ከበዳይ?

ኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄዱ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ግዢዎች አነስተኛም ይሁኑ ትላልቅ የፕሮጀክት ጨረታዎች ያለኮሚሽን ክፍያ የተፈጸሙ ናቸው የሚል ጥናት ፍፁም ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም፡፡ ምንልክሳልሳዊበአሁኑ ወቅት በተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ የሚካሄዱ ግዢዎችና ጨረታዎች ሕጋዊነትን ለማስያዝ ብቻ የሚካሄዱ ካልሆነ በስተቀር፣ አስቀድሞ ከታቀደውና ከታለመው ሰው ወይም ድርጅት ውጭ ማንም እንዲገባ በማይፈቀድበት ደረጃ ላይ መድረሳችንን የዋህ ሰው ሳይቀር በሚገባ የሚረዳበት ደረጃ ላይ እኮ ነን ያለነው፡፡ ግዢዎች ሲፈጸሙ ወይም ጨረታ በሚወጣበት ጊዜ የሚደረገውን ለአብነት እንይ፡፡

እጅግ የሚያስፈራው ደግሞ ሙስና ከመስፋፋቱም በላይ ሙስናን የሚዋጋና እውነታው ገሃድ እንዲሆን ጥረት የሚያደርግ ወገን ያለአግባብ እየተበደለ ነው፡፡ ሙሰኞች በያዙት የሕዝብና የመንግሥት ሥልጣን ሀቅን ለመቅበር የሚችሉትን ያህል ማድረግ የሚችሉበት ደረጃ ላይ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ አገሪቷን እጅና እግሯን አስሮ ለጅብ እንደመስጠት ይቆጠራል፡፡

የጨረታ ዶክመንት ለሚፈለገው ድርጅት ወይም ሰው ከሳምንታት ወይም ወራት በፊት አስቀድሞ እንዲሰጥ ይደረጋል፡፡ የጨረታ ዶክመንቱ (ቴክኒካል ስፔስፊኬሽኑ) በአጫራቹ ድርጅት አማካይነት በተመረጡና በታመኑ ሰዎች እንዲሠራ ይደረጋል፡፡ ይህ በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ግዥ በሚፈጽሙ ተቋማት ውስጥ በግልጽ እንደሚደረግ ግልጽ ነው፡፡ ፀሐይ የሞቀውም ነው፡፡ ለጨረታ ወይም ለግዥው የተዘጋጀው ወይም የተመደበው ገንዘብ ለሚፈለገው ድርጅት ወይም ግለሰብ አስቀድሞ እንዲሰጥ ይደረጋል፡፡ ለጨረታ የተዘጋጀው ወይም የተመደበው ገንዘብ አስቀድሞ ለሚፈለገው ድርጅት ወይም ግለሰብ ከተሰጠ በኋላ፣ በሚያቀርበው ዋጋ ላይ ምንም ዓይነት ልዩነት ሳይኖረው ተፈላጊው ድርጅት ወይም ግለሰብ እንዲያቀርብ ተደርጎ ተመራጭ እንዲሆን ይደረጋል፡፡ ምንልክሳልሳዊበአንዳንድ ግዥዎች አሸናፊ እንዲሆን የሚፈለግ የተጫራች ድርጅት ስፔስፊኬሽን እንዳለ የጨረታ ዶክመንት ሆኖ እንደሚቀርብ በግልጽ በሚታወቅበት ደረጃ ላይ ነን፡፡

በአሁኑ ወቅት እየተካሄዱ ያሉ ግዥዎችና ጨረታዎች ከፍተኛ ሙስና እየተፈጸመባቸው የሚካሄዱ መሆኑ ቢታይም፣ ሕጋዊነትን ተከትለው እንደተፈጸሙ ስለሚቀመጡ (በወረቀት፣ በአካሄድና በአሠራር) እጅግ የረቀቁና ሥር እየሰደዱ የመጡ ሙስናዎችን ለማየት ግን አዳጋች አይደለም፡፡ ምንልክሳልሳዊአንድ ድርጅት ከሁለት በላይ የተለያዩ ስም የያዙ የድርጅት ስሞችን ይዞ በመቅረብ አንዱ አሸናፊ ሌሎች አጃቢዎች ሁነው እንደሚቀርቡ በግልጽ ይታወቃል፡፡ የጨረታ ጊዜዎችን እጅግ በማሳጠር አሸናፊ እንዲሆን ለሚፈለገው ድርጅት ወይም ግለሰብ ግን አስቀድሞ መረጃውን በመንገርና ተዘጋጅቶ እንዲቆይ በሚደረግ፣ የሌሎች ተጫራቾችን ጊዜ በማሳጠርና የዝግጅት ጊዜ እንዲያጡ በማድረግ የሚፈጸሙ ግዥዎችና ጨረታዎች ናቸው እየተካሄዱ ያሉት፡፡ምንልክሳልሳዊ

አንዳንድ ቦታ ጨረታ በሚዘጋጅበት ወይም በሚካሄድበት ጊዜ ተጫራቾቹ በአጫራቹ ድርጅት ግለሰቦች ስም የሚጠሩበት አጋጣሚ እንዳለም በግልጽ የሚታወቅ ነው፡፡ ማን አሸነፈ ሲባል የአጫራቹ ግለሰብ ስም እየተጠራ እገሌ አሸነፈ ተብሎ በሚነገርበት ደረጃ ላይ እንዳለን ለማንም ባልተሰወረበት ሁኔታ ላይ ነን፡፡ እጅግ በጣም የሚገርመው ደግሞ ከጨረታ በኋላ አሸናፊው ድርጅት በፕሮጀክቶች ክትትልና በዕቃ ርክክብ ከሚፈለገው ደረጃና ብቃት በታች አፈጻጸም ያሳያል፡፡ ከሚፈለገው ዕቃ ውጭ አቅርቦቶች ሲካሄዱ ዝም እየተባለ የሚፈጸሙ የፕሮጀክቶች ግዥዎች ከበስተጀርባቸው ትልቅ ሙስና እንደሚካሄድባቸው ብዙዎች ያውቁታል፡፡ ምንልክሳልሳዊ

ለዚህ ትልቅ ማሳያ ሊሆኑ የሚችሉ በመንገድ ግንባታ፣ በትላልቅ ግድቦች ግንባታ፣ በውኃ ሥራዎች፣ በቴሌኮም ፕሮጀክቶች፣ በቤቶች ግንባታና ማጠናቀቂያ ላይ ችግሮች ጎልተው እንደሚታዩ በእጅጉ ይታወቃል፡፡ እንደ ምሳሌ ለማቅረብ ከኤርፖርት እስከ መስቀል አደባባይ እየተሠራ ያለው መንገድ ቀደም ብሎ ለሌላ ድርጅት ተሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ኋላ ግን ተቀይሮ ለሲአርቢሲ ተሰጥቷል፡፡ የመጀመርያው ተጫራችና አሸናፊ ድርጅት አቅም ሲመዘን እንኳን በዚህ ትልቅና አስቸጋሪ መንገድ እንዲሳተፍ በገጠር መንገድም ለማሳተፍ የሚያስችል ብቃት እንደሌለው ግልጽ ነበር፡፡ ታዲያ ይህ ድርጅት አሸናፊ እንዲሆን ተመርጦ የነበረው አላስፈላጊ ግንኙነት በመመሥረቱ ነበር፡፡ የዚህ ዓይነት መሰል ገጠመኞች ደግሞ እጅግ በጣም ብዙ ናቸው፡፡ ባንኮች ብድርና የውጭ ምንዛሪ ለመስጠት በግልጽ ኮሚሽን በሚቀበሉበት አገር ላይ ሙስና ኢትዮጵያ ውስጥ አሳሳቢ ደረጃ አይደለም እንዴት ይባላል?

የፀረ ሙስና ኮሚሽን አንዳንድ ሰዎች አሳሳቢ የሚባል የሙስና መረጃ ሲያገኙ፣ በተለይ ከሀብታም ነጋዴዎች ጋር የሚያያዝ ከሆነ ቀድመው ችግሩን ለማወቅና ለመፍታት ከሚጥሩ ይልቅ ለግልግል በሚሯሯጡበት አገር ላይ እያለን፣ ሙስና ኢትዮጵያ ውስጥ ዝቅተኛ ነው እንዴት ይባላል? በአሁኑ ወቅት ከከፍተኛ እስከ ዝቅተኛ የመንግሥት አመራሮች ድረስ በሀብታም ተፅዕኖ ሥር በወደቁበት፣ ጉቦ በመቀበል የአገራቸውን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈው በሚሰጡበት፣ ሀቅን በገንዘብ በሚለውጡበት፣ በጠራራ ፀሐይ ብሉ ሌብልና ቪኤስኦፒ በካርቶን በሚጫንበት፣ የሰው ሕይወት በገንዘብ አደጋ ላይ በሚወድቅበት፣ ዓይን ያወጡ ሙሰኞች በሰፊው ሕዝብ ፊት ደረታቸውን ነፍተው ጉራቸውን በሚነፉበትና ኃይላቸውን የሚያሳዩበት ወቅት መሆናችን እየታወቀ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሙስና አሳሳቢ ደረጃ ላይ አይደለም እንዴት ይባላል?

ትናንትና ለሀቅ፣ ለዲሞክራሲና ለአገራቸው ብልጽግና ሲሉ የወጣትነት ዕድሜያቸውን በረሃ የወጡ ወንድሞቻቸውን፣ እህቶቻቸውንና ጓደኞቻቸውን ቀብረው እዚህ ደረጃ ላይ የደረሱ ጀግኖች በሙስና ተነክረው ሀብታም ሥር በተንበረከኩበት ወቅት፣ የተለያዩ ድርጅቶች ቅጥረኛ በሆኑበት ወቅት፣ አሠራርና መመርያዎችን ጥሰው በኔትወርክ በተሳሰሩበት ወቅት፣ እርስ በራሳቸው እሳትና ጭድ ሁነው በማይተማመኑበት ወቅት፣ ለሕዝብ ህልውና ዋስትና በታጣበት ወቅት፣ሙስና ኢትዮጵያ ውስጥ ሊያሳስብ አይገባም ተብሎ እንዴት ይነገራል?

ከምንም ጊዜ በላይ እጅግ አሳሳቢ፣ ከአሳሳቢነቱ በላይም ጊዜ የማይሰጠውና ወረርሽኝ በሆነበት ደረጃ ላይ ነው ያለነው፡፡ አንዳንድ ቦታ ላይም ሙሰኞች የሙስና መንገዳቸውን ለማሳካት ሲሉ በመንግሥት ፖሊሲ፣ አሠራርና መመርያ ላይ ጫና እየፈጠሩ እንደሚመቻቸው ተደርጎ እንዲወጣ በማድረግ ላይ እንደሆኑ ወሬዎች በሚናፈሱበት ደረጃ ላይ ነው ያለነው፡፡ አንዳንዱ ቅንጣት ጥፋት የሌለው ይመስል ከራባቱን አስሮ ‹‹ሙስናን እንዋጋ›› የሚለው ከበስተጀርባው ትልቅ ጥፋት ተሸክሞ ነው፡፡

እጅግ የሚያስፈራው ደግሞ ሙስና ከመስፋፋቱም በላይ ሙስናን የሚዋጋና እውነታው ገሃድ እንዲሆን ጥረት የሚያደርግ ወገን ያለአግባብ እየተበደለ ነው፡፡ ሙሰኞች በያዙት የሕዝብና የመንግሥት ሥልጣን ሀቅን ለመቅበር የሚችሉትን ያህል ማድረግ የሚችሉበት ደረጃ ላይ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ አገሪቷን እጅና እግሯን አስሮ ለጅብ እንደመስጠት ይቆጠራል፡፡ምንልክሳልሳዊ

Image

ቅሬታቸውን ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሓላፊዎች ገልጸዋል:

(አዲስ አድማስ መጋቢት 20 2006 ዓ.ም)

የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ በኾኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የቤተ ክርስቲያኒቱን እምነትና ሥርዐት እንዲማሩ፣ ዕውቀታቸውንና ገንዘባቸውን በማቀናጀት ሞያዊ ድጋፍ እንዲያበረክቱ በማስተባበር ላይ የሚገኘውን ማኅበረ ቅዱሳንን በአሸባሪነት በመፈረጅ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ አማካይነት ጠቅላላ ሀብቱና ንብረቱ የሚታገድበት ውሳኔ እንዲተላለፍ በመንግሥትም በኩል እርምትና ርምጃ እንዲወሰድበት የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የአድባራት አስተዳዳሪዎች መግለጫ አውጥተውበታል በተባለው ስብሰባ ጉዳይ ኹለት የቅ/ሲኖዶስ አባላት ለከፍተኛ የመንግሥት ሓላፊዎች ቅሬታቸውን ማሰማታቸው ተገለጸ፡፡

የቅ/ሲኖዶሱን ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሉቃስንና በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስና የጅማ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን በስም የጠቀሱት የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ምንጮች፣ ሊቃነ ጳጳሳቱ ቅሬታቸውን ያቀረቡት ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሓላፊዎች እንደኾነ ቢገልጹም የሓላፊዎቹን ስም ከማሳወቅ ተቆጥበዋል።

ቤተ ክርስቲያኒቱ በፀረ ሙስናና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ከመንግሥት ጋራ የተጠናከረ ሥራ ለመሥራት በቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መወሰኗን ሊቃነ ጳጳሳቱ አስታውሰው፣ በዚህም መሠረት ለሙስናና ብክነት የተጋለጡ አሠራሮችን ለማረምና ለማስተካከል ጥረት እያደረገች ቢኾንም ባለሥልጣናቱ ከማን ጋር መሥራት እንዳለባቸው በትክክል አለመለየታቸውንና ግንኙነቱም ሙሰኞችን በአይዟችኹ ባይነት የሚያበረታታ እንደኾነ መናገራቸው ተጠቅሷል፡፡

ሊቃነ ጳጳሳቱ ቅሬታቸውን በዚህ መልኩ ለባለሥልጣናቱ ለማቅረብ ያስገደዳቸው የአድባራት አስተዳዳሪዎቹ፣ ‹‹ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ምእመናንንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶችን ለአድማ ያነሣሣል፤ በሀገርና በቤተ ክርስቲያን ላይ ሁከትና ሽብር እንዲፈጠርና ሰላም እንዲደፈርስ ያደርጋል›› ባሉት በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የሚወሰደው አስተዳደራዊ ርምጃ በፀረ ሽብር ሕጉ መሠረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የጠየቁበት መግለጫቸው ነው፡፡

የመንግሥት የተለመደ እገዛ እንዳላቸው በአጽንዖት የጠቀሱት አስተዳዳሪዎቹ በዚሁ መግለጫቸው፣ መንግሥት በፀረ ሽብር ሕጉ ታሳቢነት ገለልተኛ ኦዲተር መድቦ በማኅበሩ ላይ የሀብትና ንብረት ቁጥጥር የማካሔድ ድጋፉ እንዳይለያቸው ያስተላለፉት ጥሪ በሌላቸው ሕጋዊነትና ውክልና የቀረበ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ በራስዋ መንገድ ማከናወን በሚገባት ተግባር ላይ አላስፈላጊ ጣልቃ ገብነትን የሚጋብዝና ለውጭ ተጽዕኖ አሳልፎ የሚሰጥ እንደኾነ ተመልክቷል፡፡

በመንበረ ፓትርያርኩ ከተገኙት የመንግሥት ሓላፊዎች ጋራ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እንደተካሔደ በተገለጸው የኹለትዮሽ ውይይት፣ ማኅበረ ቅዱሳንን በመቃወም ሰበብ የወጣው የአስተዳዳሪዎቹ መግለጫ ዋነኛ ዓላማ፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃ ወስና የምታካሒደውን የአደረጃጀትና የአሠራር ለውጥ ሒደት መጋፋት ነው ተብሏል፡፡ መላውን የሀገረ ስብከቱን አድባራት አገልጋዮች ለመወከል የማይበቁ ጥቂት ግለሰቦችን በመያዝ ይደረጋል የተባለው ይኸው እንቅስቃሴም ‹‹የት እንደሚያደርስ እናየዋለን›› የሚሉ ንግግሮች ጭምር ከሊቃነ ጳጳሳቱ የተሰሙበት እንደነበር ምንጮቹ አስታውቀዋል፤ ጉዳዩም በመጪው ግንቦት በሚካሔደው የቅ/ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዓቢይ መነጋገርያ መኾኑ እንደማይቀር ተጠቁሟል፡፡

ከሀገረ ስብከቱ አድባራት የተውጣጡ ናቸው የተባሉ አስተዳዳሪዎች ያደረጉት ስብሰባ፣ አስተባባሪዎቹ ከፓትርያርኩ ተሰጥቶናል ከሚሉት ፈቃድ በቀር በሀገረ ስብከቱ የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስና በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ዘንድ በይፋ የታወቀና የተፈቀደ እንዳልነበረ ምንጮቹ ለአዲስ አድማስ ገልጸዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳንን በሁከትና ሽብር ለሚከሱ በቂ ሕጋዊነትና ውክልና የላቸውም ለተባሉ አካላት ፓትርያርኩ የሰጡትን የስብሰባ ፈቃድ፣ በቅርቡ ማኀበሩ አገር አቀፍ የአብነት መምህራን የምክክር ጉባኤ እንዳያካሒድ ከተጣለበት እገዳ ጋር ያነፃፀሩ ታዛቢዎች፣ ሁኔታው የፓትርያርኩን ርምጃዎች መርሕ አልባነት የሚያጋልጥ ነው ይላሉ፡፡ ከዚህም ባሻገር መተዳደርያ ደንብ ያለውና ግልጽ ተልእኮ ይዞ የሚንቀሳቀሰው ማኅበር፣ህልውናና አገልግሎት በግልጽ አስተዳደራዊ ጫና ውስጥ መግባቱን እንደሚያመለክት ታዛቢዎቹ ያምናሉ፡፡

ከመዋቅር፣ ከሀብትና ንብረት ቁጥጥር ጋራ በተያያዘ በማኅበሩ ላይ የሚቀርቡት ውንጀላዎች፣ በፀረ አክራሪነት ስም የሚናፈስበትን ፕሮፓጋንዳ በማጠናከር ፖሊቲካዊ ርምጃ እንዲወሰድበት ፍላጎት ያላቸውን አካላት ምኞት በጉልሕ እንደሚያሳይ አስረድተዋል፡፡ ማኅበሩ ሃይማኖቱን የሚጠብቅ፣ ቤተ ክርስቲያኑን የሚከባከብና ሀገሩን የሚወድ ብቁ ዜጋ ለማፍራት ያለውን ዓላማ የሚረዱ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ካህናት፣ ምእመናንና የመንግሥት አካላትም የተቃዋሚዎቹን አቋምና መግለጫ በጥንቃቄ እንዲመለከቱትም አሳስበዋል፡፡

በሌላ በኩል፣ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖናና ትውፊት ውጭ ነው በተባለ የሌላ እምነት አስተምህሮ የተነሳ በኮሌጁ ደቀ መዛሙርት መካከልና በደቀ መዛሙርቱ ምክር ቤት አባላት ውስጥ ያለው ግንኙነት ውጥረት ውስጥ እንደገባ እየተገለጸ ነው፡፡

ከኮሌጁ ውጭ ከሚገኙና በቅ/ሲኖዶስ ከተወገዙ ግለሰቦችና ቡድኖች ጋር የዓላማና የጥቅም ግንኙነት መሥርተዋል በተባሉ ጥቂት ደቀ መዛሙርት አማካይነት በኮሌጁ ውስጥ ከመንጸባረቅ አልፎ እንደ ሰደድ እሳት እየተቀጣጠለ ነው የተባለው ይኸው አስተምህሮ፣ አስተዳደራዊ መፍትሔ እንዲበጅለት የደቀ መዛሙርቱ ምክር ቤት ጥር 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ለኮሌጁ አስተዳደር ያቀረበው ጥያቄ እስከ አሁን ምላሽ አለማግኘቱ ውጥረቱን የበለጠ እንዳባባሰው ለአዲስ አድማስ የደረሰው መረጃ አመልክቷል፡፡

የአስተምህሮው ውዝግብ አፋጣኝ መፍትሔ አለማግኘቱ ከደቀ መዛሙርቱ አልፎ የምክር ቤት አባላትን ለሁለት እንደከፈለ ተገልጧል፡፡ ኮሌጁንና ደቀ መዛሙርቱን በቅንነትና በትጋት ለማገልገል በደቀ መዛሙርቱ ጠቅላላ ጉባኤ የተመረጠውና ከፍተኛ ሓላፊነት የተጣለበት የደቀ መዛሙርቱ ምክር ቤት፣ ‹‹ከልማቱ ጥፋቱ አመዝኗል›› ያሉት ጸሐፊውና አንድ የአመራር አባሉም ራሳቸውን ማግለላቸው ታውቋል፡፡

‹‹ከቤተ ክርስቲያኒቱ ቀኖናና ትውፊት ውጭ የኾነ የኑፋቄ ትምህርት ሲዘራ ድምፀ ተዓቅቦ ከማድረግ ባሻገር ችግር አለባቸው ከሚባሉት ደቀ መዛሙርት ጎን ተሰልፈው ኮሌጁንም ኾነ ሓላፊነት የሰጠንን ደቀ መዝሙር በቅንነት እንዳናገለግል የአንዳንድ መማክርት አባላት ተግባር አውኮናል›› ያሉት ሁለቱ አባላት፤ በዚህ ሳምንት ለኮሌጁ ዋና ዲን ጽ/ቤት በጻፉት ደብዳቤ፣ ምክር ቤቱ የችግሩ ተባባሪ በመኾኑ ከሓላፊነቱ ታግዶ ጉዳዩ እንዲጣራና እምነታቸውና ሥነ ምግባራቸው በተመሰከረላቸው ደቀ መዛሙርት እንዲተካ ጠይቀዋል፡፡

‹‹የቤተ ክርስቲያንን እንጀራ እየበሉ፣ በጀቷን አውጥታ እያስተማረቻቸው የሌላ እምነት የሚያራምዱ›› ያሏቸውን ወገኖች አጥብቀው እንደሚቃወሙ የገለጹ የደቀ መዛሙርት ተወካዮች በበኩላቸው፣ ኮሌጁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖናና ትውፊት ለመጠበቅና ለማስፋፋት የቆመ በመኾኑ አስተዳደሩ፣ በቃል፣ በድምፅና በጽሑፍ የሚቀርቡለትን ማስረጃዎች መርምሮ አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጣቸው አሳስበዋል፡፡

የአሜሪካን ባለስልጣናት ኢህአዴግን በተመለከተ የሚጠቀሙት ቃልና የድምጻቸው ቃና ተቀይሯል::

ጎልጉል ፦ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላም ብቸኛ ተዋናይና ፊት አውራሪ አድርጎ ራሱን የሾመው ኢህአዴግ ለቀጠናው ስጋት እንደሚሆን ተጠቆመ። አልሸባብንና አልቃይዳን ከምንጩ እናጠፋለን በሚል ስትራቴጂ መለስ ከቆፈሩት ጉድጓድ ውስጥ ሰምጣ የነበረችው አሜሪካ ከጉድጓዱ ለመውጣት ወስናለች። ኢትዮጵያዊያን የሚያምኑትና የሚቀበሉትን መሪ በድፍረት አደባባይ የማውጣት ሃላፊነቱ “አገር ወዳድ” በሚሉ ዜጎችና የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጫንቃ ላይ ነው።

ህወሃት ያቋቋማቸው ጥቃቅን መንግስታት ከህዝብ ይልቅ ለህወሃት የወደፊት እቅድ ታማኝ በመሆን መጓዛቸው ከቀን ወደቅን የፈጠረው ስሜት ኢህአዴግን እየበላው እንደሆነ የጠቆሙ የዜናው ምንጮች፣ ኢህአዴግ የምስራቅ አፍሪቃ የሰላም አባት ሊሆን ቀርቶ የራሱንም ችግር መፍታት ወደማይችልበት የቁርሾ ማሳ ውስጥ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

ህወሃት “በነጻ አውጪነት” ያሰላውና፣ ይህንኑ ዓላማውን በፈለገበት ቀን ተግባራዊ ለማድረግ ያመቸው ዘንድ በየክልሉ ለጣጥፎ ያቋቋማቸውን ፓርቲዎች ሲመሩ የነበሩት አቶ መለስ በድንገት ካለፉ በኋላ ኢህአዴግ ውስጣዊ ሰላሙ መናጋቱ በተደጋጋሚ እየተገለጸ ነው። ኢህአዴግ በበኩሉ “የጓድ መለስን ውርስና ራዕይ ያለማዛነፍ እናስቀጥላለን” እያለ አገሪቱን በደቦ እንድተመራ ማድረጉ የሚታወስ ነው።

አቶ መለስ በጓዶቻቸው ቋንቋ “ተሰው” ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ ምክትል ጠ/ሚኒስትር የነበሩትን አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝን ለመተካት ተቸግሮ ነበር። ደህንነቱን፣ መከላከያውን፣ ፖሊስና ዋንኛ የአገሪቱን ተቋማት ጠቅልሎ የያዘው ህወሃት በቀጥታ አሜሪካ ባደረገችው ጫና ሳይወድ በግዱ አቶ ሃይለማርያምን በጠ/ሚኒስትርነት ለመሰየም ተገደደ። የስልጣን ክፍተቱን በተመለከተ አቻ ድርጅቶችና ህወሃት ውስጥ አለመግባባት ተፈጥሮ ስለነበር “ምደባ” በሚል ኢትዮጵያ በደቦ የሚመሯት አራት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ተሰየሙላት።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የአሜሪካ ዲፕሎማት እንዳሉት አሜሪካ ስጋት የገባት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ነበር። መለስ እንዳለፉ ልዩ ልዑክ ወደ አዲስ አበባ በመላክ ሁኔታውን በመገምገም ስራ የጀመረችው አሜሪካ አሁን አሁን በህወሃት ስትራቴጂ የተሰራው ኢህአዴግ የምስራቅ አፍሪካ ቀንድ ዋንኛ የችግር ምንጭ ስለመሆኑ ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል። በዚህም የተነሳ የአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየመከሩበትና የመፍትሔ ስትራቴጂ እየነደፉ ነው።

“We cannot afford to lose Ethiopia” አሜሪካ ኢትዮጵያን ልታጣት አይገባም በማለት ለጎልጉል የዋሽንግቶን ዘጋቢ የተናገሩት የዲፕሎማት ምንጭ “የአሜሪካን ባለስልጣናት ኢህአዴግን በተመለከተ የሚጠቀሙት ቃልና የድምጻቸው ቃና ተቀይሯል” ሲሉ የጉዳዩን ክብደት አመላክተዋል።

በዋሽንግቶን የአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች፣ የምክር ቤት አባላት እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታቸው ኢህአዴግን አስመልክቶ ተደጋጋሚ ስብሰባ መቀመጣቸው ታውቋል። አዲስ አበባም ተወካይ በመላክ ከሚመለከታቸው ባለስልጣናት ጋር በግል እየተነጋገሩ ነው። በያዝነው ሳምንትም ለተመሳሳይ ስራ አዲስ አበባ የተጓዙ አሉ። እንደ ዲፕሎማቱ ገለጻ የህወሃት ሰዎች ውስጣዊ ችግር እንዳለ አይቀበሉም። በግል ያነጋገሯቸው የሌሎች ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ግን ኢህአዴግ ውስጡ አለመረጋጋትና ስጋት የተሞላው ስለመሆኑ ማረጋገጫ ሰጥተዋል።

በኢትዮጵያ አንድ ችግር ቢፈጠር ለማረጋጋት አስቸጋሪ እንደሚሆን፣ ህዝቡ በተለይ በህወሃቶች ላይ የሚያሳየው ጥላቻ እየተካረረ መምጣቱ፣ በአገሪቱ የሚፈጸመው ያልተመጣጠነ የሃብት ስርጭት፣ አፈናውና ሌሎች የህወሃት/ኢህአዴግ ተግባራት ተዳምረው ህዝቡን ክፉኛ ማስቀየሙ ያልታሰበ ችግር ሊቀሰቅስ እንደሚችል አሜሪካ መገንዘቧን ያወሱት ዲፕሎማት፣ “ህወሀቶች የቀጠናው የሰላም ምንጮች ስለመሆናቸው ለራሳቸው ምስክርነት ለመስጠት ቢሞክሩም በተግባር የሚታየው ግልባጩ ነው” ብለዋል።

ኢትዮጵያ ላይ የተተከለው የጎሳ አገዛዝ እንደሆነ ያመለከቱት እኚሁ ዲፕሎማት “በጎሳ አስተሳሰብ የተዋቀረው ኢህአዴግ ችግሩ ከገነፈለ ሊቆጣጠረው የሚችል ባለስልጣንና መሪ የለውም። አስተዳዳራዊ ማዕከላዊነት አይታይበትም። በግል የሚወስን ባለስልጣንና ርምጃ የሚወስድ አካል የለውም” ሲሉ የስጋቱን ግዝፈት ያሳያሉ። በዚህ ሂደት ውስጥ ችግሩ ቢከሰት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማሰቡ አዳጋች እንደማይሆን ይጠቁማሉ። አያይዘውም “አሜሪካ ቸል ብላ ስትመለከተው የነበረውን ጉዳይ አጽንኦት ብትሰጠው አይገርምም” ብለዋል። አሜሪካ ይህንን የምታደርገው ለራሷ ስትል እንደሆነ ያልሸሸጉት ዲፕሎማት አንድ ጥያቄም ጠይቀዋል። “እናንተስ ለራሳችሁ ስትሉ ምን እየሰራችሁ ነው?” ከረጅም ፈገግታ ጋር።

አልቃይዳን ከምንጩ ማድረቅ በሚለው የመለስ ስትራቴጂ ለኢህአዴግ ግብር ስታስገባ የነበረችው አሜሪካ ግብሯን ስትገብር የኖረችው በፔንታጎን ወታደራዊ ውሳኔ መሰረት ነበር። ኢህአዴግም ግብሩ እንዳይቆምበት በአዲስ አበባ ታክሲ ላይና ህዝብ በሚያዘወትርባቸው ቦታዎች ፈንጂ በማፈንዳት ሲጫወተው የነበረውን ድራማ ዊኪሊክስ (ሹልክ ዓምድ) አምባሳደር ያማማቶን ጠቅሶ ማጋለጡ አይዘነጋም። በዚሁ መነሻ ይመስላል ኢህአዴግ የቀድሞውን ጨዋታ የመጫወት እድሉ እንዳከተመ እንደራሴ ክሪስ ስሚዝ ባደባባይ የመለስን ስብዕና በመዝለፍ ባልተለመደ መልኩ ተናግረው ነበር።

ለጎልጉል መረጃ የሰጡት ዲፕሎማት “እናንተስ” በሚል ለሰነዘሩት ጥያቄ ማብራሪያ ተጠይቀው “እኔ ኢትዮጵያዊ ብሆን አገሬን አስቀድማለሁ” የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል። አሜሪካ አማራጭ ማጣቷንም እንደ አንድ ችግር አንስተዋል።

በዲፕሎማቱ አስተያየት ላይ ገለልተኛ ወገኖችን አነጋግረናል። ያሰባሰባንቸው አስተያየቶች “አሜሪካ እዚህ ደረጃ ከደረሰች፣ ኢህአዴግም በዚህ ደረጃ ከተመደበ ተቃዋሚዎች የግል ጉዳያቸውንና ፕሮግራማቸውን ለህዝብ ውሳኔ በመተው ለመጪው ትውልድና ለአገር ሲሉ ከመቧደን በሽታ ሊፈወሱ ይገባል” የሚል ይገኝበታል።

የተቃዋሚ ፓርቲዎች ተቀናጅቶ መበተን፣ ተደራጅቶ መፍረክረክ፣ ተደላድለው መስለል በተለያዩ ወቅቶች ህዝብ ተስፋ እንዲቆርጥ አድርገዋል። የሚፎካከሩትን ፓርቲ ትተው እርስ በርሳቸው ለተራ ጉዳይ ሲሻኮቱ ዓመታት አሳልፈዋል። በዚህም የተነሳ “አማራጭ የለም” በሚል ኢህአዴግን ማንገስ ግድ እንደሆነ የጠቆሙት አስተያየት ሰጪዎች “የተቃዋሚ ፓርቲዎች ይህንን አስተሳሰብ ሰብረው አገር መምራት እንደሚችሉ የሚያረጋግጥ ህብረት መፍጠር ይገባቸዋል። ይህም ካልሆነ የርስ በርስ ውዝግባቸውን ማቆምና የራሳቸውን የቤት ስራ መስራት ላይ ማተኮር ግዳጃቸው ይሆናል” ብለዋል።

ምሁራን ከተደበቁበት ሊወጡ እንደሚገቡም ያሳሰቡ አሉ። አገር የመምራት፣ በህዝብ የመታመን፣ የህዝብን ይሁንታ ማግኘት እንችላለን የሚሉ ከፊት ለፊት፣ አሁን ከፊት ያለውን ችግር በመጥረግ የወደፊቷን ኢትዮጵያ በመገንባትና መጪውን ትውልድ በማዳኑ ስራ አጋዥ ሃይል ለመሆን መወሰን እንደሚገባቸው በመግለጽ ጥሪ አቅርበዋል። ከሁሉም በላይ ግን “አሁን ካለው ህዝብን ካገለለ ዘመናዊ የመሳፍንት ስርዓት ኢትዮጵያንና ህዝቧን ማሻገር የሚችል ሞገሰ ሙሉ፣ ቅን፣ ከጥላቻ የጸዳ፣ ከሥልጣን ይልቅ የወደፊቷን ኢትዮጵያ አሻግሮ መመልከት የሚችል መሪ ወደ ፊት ወጥቶ በግልጽ ለህዝብ የሚተዋወቅበትን መንገድ የማህበራዊ ሚዲያዎች፣ ድረገጾች፣ ሬዲዮኖች አገር ወዳድ የመገናኛ አውታሮች አጀንዳ አድርገው ሊወያዩበት ይገባል” የሚለው አስተያየት ሚዛኑን የደፋ ሆኗል።

“…የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄውን አልተቀበኩትም::” የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር

ምላሹን አልቀበልም በማለቱም በፖስታ ቤት ተልኮለታል ህገ መንግስቱ እውቅና የቸረው ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት ሳይሸራረፍ መተግበሩን እንዲከታተል በአዋጅ የተቋቋመው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ መጋቢት 28/2006 ዓ.ም መነሻውን ፓርቲው ከሚገኝበት ቀበና በማድረግ በአራት ኪሎ አደባባይ በመዞር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ፊት ለፊት የሚጠናቀቅ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ በመግለጽ ለኦፊሰሩ ደብዳቤ አስገብቶ የነበረ ቢሆንም መስተዳድሩ በአዋጅ የተሰጠውን ጊዜ ገደብ አሳልፎ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ኦፊሰሩ በደብዳቤያቸው ‹‹በርካታ ትምህርት ቤቶች ዩኒቨርስቲና ፣የመንግስት ተቋማት በሚገኙበት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የማይቻል በመሆኑ የተጠየቀውን የሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መሆኑን እንገልጻለን፡፡››ብሏል፡፡ የአገሪቱ ፓርላማ ‹‹ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ስነ ስርዓት ባወጣው አዋጅ ‹‹የከተማው ወይም የአውራጃው አስተዳደር ጽ/ቤት ሰላማዊ ሰልፉ ወይም ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባው ምን ግዜም በየትኛውም ቦታ ሊካሄድ አይችልም ማለት አይችልም››(አዋጅ ቁጥር 3/1983 )በማለት ያወጀውን በአዋጁ ስር የተቋቋመው ጽ/ቤት በማን አለብኝነት በመሻር የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄውን አልተቀበኩትም ብሏል፡፡

አንድነት አዋጁን የጣሰውን ደብዳቤ እንደማይቀበል በመግለጽ ለኦፊሰሩ ደብዳቤ በመጻፍ በአካል ቢሯቸው በመገኘት ለመስጠት ቢሞክርም በአስገራሚ ሁኔታ ኦፊሰሩ ደብዳቤውን አልቀበልም ብለዋል፡፡
የኦፊሰሩ ድርጊት ህገ ወጥ መሆኑን የተገነዘበው ፓርቲያችን ደብዳቤውን ቢሯቸው ጠረጴዛ ላይ ትቶ ከመውጣቱም በላይ በሪኮማንዴ እንዲደርሳቸው አድርጓል፡፡ ኦፊሰሩ እየሰሩ የሚገኙት ነገር ህገ ወጥ መሆኑን እንዲገነዘቡም ለፌደራል ፖሊስ፣ለአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ በግልባጭ ደብዳቤው እንዲደርሳቸው መደረጉን የአንድነት የአዲስ አበባ ዋና ጸሐፊ አቶ ነብዩ ባዘዘው ተናግረዋል፡፡ በህገ ወጥ ደብዳቤ የሚሰረዝ ሰላማዊ የህዝብ ጥያቄ ባለመኖሩም ሰላማዊ ሰልፉ በተያዘለት ቀነ ገደብ እንደሚደረግ አቶ ነብዩ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ Finotenetsanet
Image

Image

ሺህ ዘመናት በኢትዮጵያዊነቱ የኖረውን የትግራይ ህዝብን፤ከተፈጠረ 40 አመት ያልሞላው ህወሐት እኔ ከሌለሁ ትጠፋላችሁ ይላል፡፡ የትግራይ ተወላጅ ሺህ ዘመናትን የኖረው በኢትዮጵያዊነቱ እንጂ በህወሐት አባልነቱ አይደለም፡፡ ዘረኝነት ባታራምዱ የተሻለ ነው የኢትዮጵያ ህዝብ ጠላቶች የትግራይ ተወላጆች ሳይሆኑ / ሕወሓት/ ነው፡፤ ዋናው ትግላችንም ሕወሓትን ማስወገድ ነው። እናንተ የትግራይ ህዝብ ላይ አተኩራችሁ አቃቂር ስታወጡ ሕወሓት እናንተን እንደማስረጃ እየተቀሰ በትግራይ ውስጥ ጥላቻን እየዘራ ነው። ስለዚህ ዘር እየጠሩ ዘመቻ አያዛልቅም ለህዝቦች አንድነት እና ፍቅር ተባብረን ብንነሳ መልካም ነው።

በቅኝ አገዛዝ ታሪክ ብቻ ሳይሆን በአምባገነን ስር አት ውስጥም ባንዳዎች ይፈለፈላሉ ። ይህ የታወቀ ነገር ንው። ውዴታዊ ባንዳነት እንዳለ ሁሉ ግዴታዊ ባንዳነት ከዛ መላመድም እንዳለ ታሪክ ስናገላብጥ አንብበናል። ቢሆንም መልካም የህዝቦችን ታሪክ እየያዝን ለክፉው ታሪክ መቃብር እየማስን እየቀበርን በትግል ወደፊት በመገስገስ በኢትዮጵያ ላይ የተጫነውን የሕወሓት አምባገነናዊ ጁንታ መንግለን መጣል አለብን ።

እደግመዋለሁ !!! ሺህ ዘመናት በኢትዮጵያዊነቱ የኖረውን የትግራይ ህዝብን፤ከተፈጠረ 40 አመት ያልሞላው ህወሐት እኔ ከሌለሁ ትጠፋላችሁ ይላል፡፡ የትግራይ ተወላጅ ሺህ ዘመናትን የኖረው በኢትዮጵያዊነቱ እንጂ በህወሐት አባልነቱ አይደለም፡፡ ድርጅት ይወልዳል ያድጋል ይሞታል፣ህዝብ ግን ለዘላልም ይኖራል፡፡ ፍቅር ያሸንፋል!!!ምንሊክ ሳልሳዊ

ኢህአዴግ የእምነት ተቋማትን በጥብቅ የሚቆጣጠርበት ህግ ሊያጸድቅ ነው።
ህጉ ጣጣ እንዳያመጣ የሰጉ ኢህአዴግን እየመከሩ ነው። ጎልጉል

ኢትዮጵያን ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ እየገዛ ያለው ኢህአዴግ የሃይማኖት ተቋማትንና ምዕመናኑን በጥብቅ የሚቆጣጠርበትን ህግ ለማጽደቅ በዝግጅት ላይ መሆኑ ተሰማ። የህጉ ረቂቅ የደረሳቸው ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ኢህአዴግን አበክረው እየመከሩና በሚያመጣው አጠቃላይ መዘዝ ዙሪያ እያስጠነቀቁ ነው።

ጎልጉል ከዲፕሎማት ምንጮቹ ባገኘው መረጃ መሰረት ኢህአዴግ በእምነት ተቋማት ላይ ቁጥጥሩን የሚያጠብቅበትንና ከሃይማኖት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውጭ መሰብሰብን፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግንና የተቃውሞ ድምጽ ማሰማትን የሚከለክል ህግ አዘጋጅቷል።

የዜናው ምንጮች ዝርዝር ህጉን ለጊዜው ይፋ ከማድረግ እንደሚቆጠቡ አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ የሚደነገገውን አዲስ ህግ ጥሰዋል በሚል የሚከሰሱ ምዕመኖች እስከ እድሜ ልክ በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ የሚያዝ አንቀጽ አለበት። አዲሱ ህግ ከሽብርተኞች ህግ ጋር የሚጣቀስ እንደሆነም የጠቆሙት ክፍሎች ኢህአዴግ “ከእምነት ነጻነት” ጥያቄ ጋር በተያያዘና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ውስጥ ውስጡን እየነደደ ያለው ችግር ስላስጨነቀው ይህንን ህግ ለማውጣት መገደዱን አስረድተዋል። በሌላ በኩልም እስካሁን መፍትሔ ያላገኘው የሙስሊሞች ጥያቄ ከዚያም ጋር ተከትሎ የተከሰተው ደም መፋሰስ ወደፊት ሊያመጣ በሚችለው ጉዳይ ላይ ኢህአዴግን በብርቱ አሳስቦታል፡፡

ኢህአዴግ ከቀን ወደ ቀን ቀውስ እየተደራረበት እንደሆነ የተረዳችው አሜሪካ በከፍተኛ ባለስልጣኖቿ አማካይነት ኢህአዴግን እየመከረች እንደሆነ ከዲፕሎማቶች የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ከፖለቲካው ቀውስና በቀጠናው ካለው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ አሜሪካ በተደጋጋሚ የህወሃትን ሰዎች በተናጠል እያነጋገረች እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል። ዲፕሎማቶቹ እንደሚሉት አሜሪካ መለስ “ከተሰዉ” በኋላ አገሪቱን ማን እየመራት እንደሆነ በቅጡ ለመረዳት በሚያስቸግር ሁኔታ የስልጣን መዛነፍና ደረጃን የጠበቀ የስልጣን ተዋረድ አለመኖሩም አሳስቧታል። ኢህአዴግ ለህልውናዬ ያሰጋኛል በሚል መንግሥታዊ ባልሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች /መያዶች/ ላይ ያወጣውን አፋኝ ህግም ጠቅሰዋል። ዲፕሎማቶቹ በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት ወቅቱ አሁን እንዳልሆነ አመልክተዋል። ጎልጉል

የበደለ፣ የአገር ሀብት ያባከነ፣ ሕገ የረገጠ ግለሰብ ማጥፋቱ እየታወቀ ይቀጣል ወይስ አይቀጣም ለሚለው ጥያቄ ወሳኙ ማስረጃ መሆኑ እየቀረ ነው፡፡ የፖለቲካ ገጠመኝ ሆኗል፡፡ ይታሰራል የተባለው ሊሾም፣ ተጠያቂ ይሆናል የተባለው ጠያቂ የሚሆንበት ሁኔታ አለ፡፡

መልካም አስተዳደር በሕግና በመርህ ደረጃ መከበር አለበት ተብሎ የታወጀ፣ የተነገረ፣ የተለፈፈለት ነው፡፡ በተግባር ደግሞ አቤት ብዬ ሰሚ አገኛለሁ፣ ቅሬታ አቅርቤ ይፈታልኛል የሚል ዜጋ የለም!!!! በዚህ ዙሪያም ጉቦና ጥቅማ ጥቅም የበላይነት እየያዙ ነው፡፡ የአቅም ማነስ ችግር ትልቅ እንቅፋት ነው፡፡ ስብሰባዎችና ሥልጠናዎች የችግር መፍቻ መድረኮች መሆናቸው ቀርቶ መደበቂያ እየሆኑ ነው፡፡ ‹‹በስብሰባና በሥልጠና ምክንያት ኃላፊ የለም›› የሚል ማስታወቂያ መለጠፍ ነው የቀረው፡፡ ኃላፊ ቢሮው ገብቶ አቤቱታ አንብቦ ችግር መፍታት መርህና ግዴታው መሆኑ ቀርቶ የፖለቲካ ገጠመኝ እየሆነ ነው፡፡

የሕግ የበላይነት እንዲኖር፣ ሰብዓዊ መብት እንዲከበር፣ የፕሬስ ነፃነት እንዲረጋገጥ፣ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን እንዲሆን የሚያደርጉ ሕገ መንግሥትና ሕጎች አሉን ????????? ከድህነት የሚያላቅቅ፣ መካከለኛ ገቢ ወዳላት አገር የሚያሸጋግር፣ የቤት፣ የጤና፣ የትምህርት፣ የትራንስፖርት፣ ወዘተ ችግሮችን የሚፈታ ዕቅድም አለን ???????????

እነዚህ አሉ ማለት ግን ዲሞክራሲ ተረጋገጠ፣ ልማት እውን ሆነ ማለት አይደለም፡፡ በመርህ ደረጃ ተግባር ላይ ካዋልናቸው ይጠቅማሉ፡፡ ካላከበርናቸው፣ ከረገጥናቸውና ከጣልናቸው ደግሞ ገጠመኝ ይሆናሉ፡፡ ፍትሕ ገጠመኝ እየሆነ ነው፡፡ምንሊክሳልሳዊ የፍትሕ መጓደል በሚያሳስብ ሁኔታ እየታየ ነው፡፡ በፍትሕ አካላት ውስጥ በአቅምና በአመለካከት ድክመት አለ፡፡ የሥነ ምግባር ጉድለት በትልቁ እየታየ ነው፡፡ በጠበቆች፣ በዳኞችና በዓቃቢያነ ሕግ በኩል አሳሳቢ የሥነ ምግባርና የአቅም ችግር እየተስተዋለ ነው፡፡

በአጠቃላይ የፍትሕ አካላት መጠናከር እያሳዩ ከመጓዝ ይልቅ እየተልፈሰፈሱና እየተንገዳገዱ ናቸው፡፡ በዚህ ምክንያት ፍትሕ ማግኘት መርህ መሆኑ ቀርቶ ገጠመኝ እየሆነ ነው፡፡ ጉቦ የአንቀጾች ሁሉ የበላይ አንቀጽ እየሆነ መጥቷል፡፡ሰላማችን፣ ሉዓላዊነታችን፣ አንድነታችንና ህልውናችን በመርህ ደረጃ ዋስትና ያላቸው መሆናቸው ቀርቶ የፖለቲካ ገጠመኝ ሆነዋል፡፡ የአገር እና የህዝብ ህልውና ገጠመኝ በመሆኑ ወያነ ደግሞ የዛፍ ላይ እንቅልፍ ተኝቷል፡፡ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም በጋራ የዛፍ ላይ እንቅልፉን የሚለጥጠውን ወያነን በማውረድ ህዝባዊ የበላይነትን መቀናጀት የዜግነት ግደታችንን መወጣት አለብን::ምንሊክሳልሳዊ

መብራት ውሃ የስልክና የኢንተርኔት ኔትወርክ አገልግሎቶች መብቶች የህዝብ ናቸው!!!!!
ምንሊክ ሳልሳዊ

Image

አቤቱታችን ከፖለቲካ ነጻነት እና ዲሞክራሲያዊነት ጎን ለጎን የመሰረታዊ አገልግሎቶች ጥያቄ ነው …ይህ ደሞ ለየት ባለ መልኩ አብዮታዊ ነው::እኛ በሰው አገር የምንኖር ዲያስፖራዎች በወገናችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ከማውራት እና መኖሪያ ፍቃዳችን ሲታደስ ከመቀዝቀዝ ዉጪ በወያኔ ላይ የምናሳድረው ጫና እምብዛም ጉልፍ ስፍራ የለውም:: እርስ በርሳቸው የሚላተሙ የጆተኒ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች በላም አለኝ ተስፋ ህዝባችንን አረንቋ ውስጥ እየጨመሩት ነው::

ለጋች አገራት የሚያወጧቸው ሃሰተኛ ጸረ አፍሪካ ሪፖርቶች በተለይ የምስራቅ አፍሪካን ተገን አድርጎ የተመቻቸው የብሄራዊ ጥቅማቸው ፎርሙላ ስኬት የአምባገነኖችን እድሜ በማስረዘም ህዝብ እንዲጭበረበር የህዝብ ጥያቄዎች እንዲደናቀፉ ለገዢዎቻችን የልብ ልብ ሰቷቸዋል:: ለብሄራዊ ጥቅም አስጊ ይሆናሉ የተባሉ የፖለቲካ ድርጅቶችን እስከማጨማደድ እየዘለቀ በኢጅ አዙህ ህዝባዊ ጥያቄዎች እንዲታፈኑ እየተደረገ አምባገነናዊ አገዛዝን አፍልተውብናል እንሱ ለጋሽ አገራት::

መሰረታዊ ፍላጎቶች እና የአገልግሎት ፍጆታችን በበቂ ሁኔታ ባልተሟላበት አገር መንግስት ፕሮጀክት ለመጨረስ የገንዘብ እጥረት ገጠመኝ በሚልበት አገር ብሄራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሬ የለኝም በሚልበት እና የመንግስት ካዝና ባዶ ሆኖ በዕቃ ግምጃ ቤት ሰነድ ጨረታ ከቱጃሮች መንግስት በሚበደርባት አገር ጥቂት ፖለቲካው የወለዳቸው ሃብታሞች እጅግ ብዙ የኢኮኖሚ ድቀት ያፈራቸው ደሃዎች በፈሉበት አገር ምን አይነት የኢኮኖሚ እድገት እንደተመዘገበ አነጋጋሪ ነው:; እስከመቼ የአምባገነኖችን ደጋፊዎች ዉሸት ተሸክመን እንዘልቃለን::

መብራት ውሃ ስልክ ሀገሪቷ ተሰርቶ እና ተበድራ ሳይሆን በተፈጥሮ የታደለችው ጸጋዋ እንደሆነም ያለን ሃብት ይመሰክራል ህዝቡ ያለውን ቴክኖሎጂ ከተፈጥሮ ሃብቱ ጋር አደባልቆ እንዳይጠቀም እኛ እናውቅላቹዋለን የሚሉ የወያኔ አውሬዎች ቀፍድደው ይዘውታል::
በቀላል ሊፈታ የሚችል ችግርን በፖለቲካዋ ሳንካ መተብተብ ምንም የሚጠቅም ስላልሆነ ህዝቡ አስፈላጊውን የአገልግሎቶች አቅርቦት እንዲያገኝ መደረግ አለበት ብለን ካሁን በፊት ብንጮህም ከቀድሞ በባሰ መልኩ ብሶበት ይገኛል::

በአለማችን በረሃ በተባሉት አገሮች የውሃ አቅርቦት በሰፊው ለህዝባቸው እየሰጡ ሲሆን የተጣሩ ውሃዎች ሳይቀር በርካሽ ዋጋ እየተሸጡ ነው::በኢትዮጵያችን ግን በተፈጥሮ የታደልነውን ውሃ በፖለቲካ ሹማምንት ልፍስፍስነት ልንጠቀምበት አልቻልንም ትልልቅ እና ገባር እንዲሁም ትንንሽ ወንዞች እና የተፈጥሮ ውሃ ምንጮች በሞሉባት ሃገራችን ህዝብ ውሃ ተጠማሁ ሲል መመልከት አስደንጋጭ ነው::ሃገሪቱ በውሃ ችግር ተውጣልች::የውሃ እጥረት ኖሮን ሳይሆን በአግባቡ አለመጠቀም እና ችግሩን የመፍታት ባህል ስላሌለን ነው::ለጎረቤት አገሮች ውሃ እንሰጣለን እየተባለ ባለበት የፕሮፓጋንዳ ጡዘት ውስጥ እኛ በጥማት ማለቃችን አሳፋሪ ነው::

ወድ መብራት ስንመጣ ደሞ መንግስት ያለ እንኳን ተደርጎ ማሰብ ይከብዳል:: የኢትዮጵያ ዲሞክራሲ መብራት ጠፍቶ ሲመጣ መብራት መጣ ብሎ መጮህ ነው ተብሎ በሰው ሃገር ጋዜጦች እስኪቀለድብን ድረስ ወያኔ በህዝብ ጭንቅላት ጢባጢቦ እየተጫወተች ነው::ይህ እንደገጠመኝ እና እድል የሚታየው የመብራት እቃቃ ጨዋታ በአግባቡ መፍታት እየተቻለ ችግሩንም ማድረቅ እየተቻለ ለምን መዘናጋት እንደሚፈጠር ማስረዳት የሚችል ባለስልጣን አልተገኘም::በኤሌክትሪክ መጥፋትና ሥርዓት አልበኝነት ምክንያት በርካታ ኢንዱስትሪዎች ሥራቸውን እያቆሙ ናቸው፡፡ በርካታ ማሽኖች ከጥቅም ውጭ እየሆኑ ናቸው፡፡ በመኖሪያ ቤቶች ቴሌቪዥኖች፣ ፍሪጆችና ሌሎች የኤሌክትሪክ ዕቃዎች እየፈነዱና እየተቃጠሉ ነው፡፡ በመብራት መጥፋት ምክንያትም የየዕለቱ ኑሮ ይዘቱም ገጽታውም እየተበላሸ ነው፡፡ ከመኖሪያ ቤቶች አልፎ ካፌዎችም በመብራት መጥፋት ምክንያት ‹‹ተረኛ መድኃኒት ቤት›› እየመሰሉ ነው፡፡ ሻይ ታዞ ‹‹ይቅርታ መብራት የለም›› የሚል መልስ መስማት የተለመደ እየሆነ ነው፡፡ እውነት ኢትዮጵያ ለዜጎቿ፣ ለኢንዱስትሪዎቿም ሆነ ለሁሉም ዓይነት እንቅስቃሴዎቿ የሚሆን በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል የላትም? አይኖራትም? አላትም ይኖራታልም፡፡ በቂ የውኃ ኃይል ማመንጫዎች የንፋስ የኃይል ማመንጫዎች የፀሐይ የኃይል ማመንጫ አቅም የጂኦ ተርማል የኃይል ማመንጫ አቅምም አለ፡፡ እንኳን ለራስዋ ለሌሎች አገሮችም የሚሆን የኤሌክትሪክ አቅርቦት ዕምቅ ሀብት አላት፡፡ ኦኖም ግን በአግባቡ የሚያዳርስ እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች አጣብቂኝ ውስጥ ስለከተቷት ህዝቧ አስፈላጊውን የአገልግሎት መብቶች እና አቅርቦቶች ሊያገኝ አልቻለም::በሃይል ግንባታ ሰበብ በህዝብ ላይ መንግስታዊ አሻጥር እየተፈፀመ ነው::ምንሊክ ሳልሳዊ

ወደ ስልክ እና ኢንተርኔት ኔትወርክ ስንመጣ በጸሎች የሚገኝ ያውም ተለቅሶ መፍትሄም የጠፋለት ጉዳይ ከሆነ ቆይቷል:: በአለማችን በስፋት ይህን የኔትዎርክ ችግር ተቀርፎ ባለበት ሰአት የወያኔ ባለስልጣናት ግን በአደናባሪዎቻቸው በኩል በፋይበር ቅንጠሳ እና በህንጻ መብዛት ቢያሳስቡም ከነሱ ቀድሞ ንቃተ ህሊናው ያደገውን ህዝብ ግን ሊሸውዱት አልቻሉም:: ያው እንደለመዱት በጠበንጃ እና ሽብር በመንዛት ዝም አሰኝተውታል:: የወያኔ መንግስት የህዝብን የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች መፍታት እየቻለ እንዳይፈቱ በማድረግ በሚፈጸም አሻጥር እራሱ አጣብቂኝ ውስጥ እንደገባ ሊገነዘበው አልደፈረም:: የመልካም አስተዳደር ብልሃት የሞላበት አመራር ህግ አክባሪ እና አስከባሪ ባለስልጣንትን ለማግኘት ሁላችንም በትግሉ ላይ እንረባረብ።ምንሊክ ሳልሳዊ

Image

የጋምቤላ ክልልን ሲመሩ ቆይተው ባለመስማማት የኮበለሉት የቀድሞው የክልሉ ፕሬዚዳንት ደቡብ ሱዳን ከሆቴል ውስጥ ታፍነው መወሰዳቸው ተጠቆመ። ዜናው በገለልተኛ ወገን ባይገለጽም ኖርዌይ በስደት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩት አቶ ኦኬሎ አኳይ በኢህአዴግ በጥብቅ የሚፈለጉ ሰው ነበሩ።

በመለስ ዜናዊ ውሳኔ በአኙዋክ ተወላጆች ላይ በጅምላ የተከናወነውን ጭፍጨፋ አስመልከቶ ተቃውሞ በማሰማት የኮበለሉት አቶ ኦኬሎ ወደ ደቡብ ሱዳን ከማምራታቸው በፊት ኬንያ እንደነበሩ፣ ከኬንያ ወደ ደቡብ ሱዳን ለምን እንደተጓዙ የዜናው ምንጮች በይፋ ከመናገር ተቆጥበዋል። ስማቸው እንዲደበቅላቸው የጠየቁ የጋምቤላ አስተዳደር ባልደረባ ለጎልጉል የአካባቢው ዘጋቢ እንደተናገሩት አቶ ኦኬሎ ደቡብ ሱዳን ሆቴል በተቀመጡበት መታፈናቸውን አረጋግጠዋል።

“ወያኔ እጅ ገብቷል” ሲሉ ያከሉት እኚሁ ሰው “አቶ ኦኬሎ ብረት በማንሳት ወያኔን ለመታገል ከተነሱ ጋር ተቀላቅለዋል በሚል ስማቸው መመዝገቡንና ወደ ደቡብ ሱዳን ማቅናታቸው በመታወቁ ህወሃቶች እጅ ሊወድቁ ችለዋል” ብለዋል። ምንጩ ይህንን ይበሉ እንጂ አቶ ኦኬሎ አክዋይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያቀኑበትን ምክንያት በርግጠኛነት ሃላፊነት ወስዶ የገለጸ ወገን አልተደመጠም። ኢህአዴግም ቢሆን የቀድሞውን ሹመኛ ስለመያዙ ይፋ ያደረገው ነገር የለም። ከደቡብ ሱዳን ቀውስ ጋር በተያያዘ የኑዌር ተወላጅ ከሆኑት ሬክ ማቻር ጦር ጋር በመሰለፍ የሳልቫ ኪርን ሃይል ሲወጉ ከተገደሉ ወታደሮች መካከል የኢህአዴግን ሰራዊት መለያ የለበሱ ኑዌሮች መገኘታቸው ውዝግብ አስነስቶ እንደነበር ያመለከቱት ምንጭ “ደቡብ ሱዳን እየወጋት ካለው ኢህአዴግ ጋር አብራ የቀድሞውን የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳደር ከምድሯ ላይ እንዲታፈኑ መፍቀዷ ቅሬታ ያስነሳል” ብለዋል።

ከቤተሰባቸው ተነጥለው በስደት ከሚኖሩበት ኖርዌይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያመሩት የቀድሞው የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳድር ደቡብ ሱዳን በህወሃት ሙሉ ቁጥጥርና ፈቃድ የምትንቀሳቀስ አገር መሆኗን እያወቁ ወደዛ ማቅናታቸውን ባሥልጣኑ “ታላቅ ጥፋት” ብለውታል። ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። በቅርቡ አቶ ኦሞት ኦባንግ መኮብለላቸውና በብዙዎች ዘንድ አውሮጳ እንዳሉ ቢነገርም በትክክል ያሉበት አገር በይፋ አለመታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።
goolgule.com/

ስብሓት የንግግራቸው መነሻ ያደረጓቸውና ወጣት ሲሉ የጠሯቸው መነኩሴ ማን ናቸው?

Image

‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የሚያስተኛ አይደለም›› /አቶ ስብሓት ነጋ/
(ኢትዮ-ምኅዳር ቅጽ 01 ቁጥር 34፤ ረቡዕ ነሐሴ ፳፱ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም.)

የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋራ በመተባበር በአዲስ አበባ በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ ከነሐሴ ፳፩ – ፳፪ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም. ‹‹የሃይማኖቶች በሰላም አብሮ የመኖር እሴት በማጎልበትና ሕገ መንግሥታዊ ድንጋጌዎችን በማክበር የሀገራችንን የሕዳሴ ጉዞ ለማሳካት እንረባረባለን›› በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ጉባኤ ላይ ‹አቦይ› ስብሐት ነጋ በመገኘት አነጋጋሪ ሐሳቦችን ሰንዝረዋል፡፡ አንጋፋው የህወሓት/ኢሕአዴግ መሥራችና የጀርባ ሰው የሚገልጹት ሐሳብ የመንግሥትን ቀጣይ ርምጃ ያመላክታል በሚል በአጭሩ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡

አክራሪነት ይዘቱ ሃይማኖታዊ እንዳልኾነ ሕዝቡም የተገነዘበው ጉዳይ መኾኑ ተደጋግሞ ተገልጧል፡፡ ሃይማኖትን የፖሊቲካ መድረክ የሚያደርጉት የሽብርተኝነት ተግባር ለመፈጸም መኾኑ ግልጽ የኾነልን ይመስለኛል፡፡

አክራሪነትና ጽንፈኝነት በሃይማኖት ውስጥ ማስገባት የመጀመሪያው አደጋ ሲኾን በዚህ ኹኔታ ሃይማኖቱም ሃይማኖት አይኾንም፡፡ አማኞች፣ አክራሪነትና ጽንፈኝነት በየሃይማኖታቸው ውስጥ ሲታይ ሃይማኖታቸው አደጋ ላይ እንደወደቀ መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡

አቶ ካሳ ተክለ ብርሃን (የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ) እንዳለውም፣ በጣም አስደናቂ የኾነውን የኢትዮጵያ ዕድገት ማደናቀፍ ከማንኛውም ወንጀል በላይ በሕዝብ ላይ ከባድ ወንጀል መፈጸም ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለብዙ ዓመታት ሲሠቃይ የነበረ በመኾኑ አሁንም ሕዝቡን ለሥቃይ መዳረግ ተወዳዳሪ የሌለው ወንጀል ነው፡፡

በማንኛውም ሃይማኖታዊ አክራሪነት እና ጽንፈኝነት፣ በምንም ዐይነት ኹኔታ አንድም ሰው ለአንድ ደቂቃ እንኳ ተዘናግቶ መተኛት የሌለበት ሲኾን በተለይ ይህን ነገር በጥብቅ በሁሉም መንገድ መታገል አለብን፡፡

አሁን በኢትዮጵያ ያለውን ዕድገት የሚቀናቀነው የውጭ ተቀናቃኝ ነው፡፡ የእነዚህን ተቀናቃኞች ዓላማ በመያዝ በአክራሪነትና በጽንፈኝነት መልክ ታላቅ ክሕደት መፈጸም ከባድ አገራዊ ክሕደት ነው፡፡ የውጭ ጠላት ቀላል ስላልኾነ አንድም ሰው ሳይቀር በጣም ተጠናክረን መመከት ይገባል፡፡ ሕገ መንግሥቱን መሠረት ያደረገ የፖሊቲካ ልዩነት ሊኖር ይችላል፤ ሕገ መንግሥቱን የመጣስ ዝንባሌ ግን እጅግ በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ መንግሥቱ ብዙ ዋጋ ተከፍሎበታል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያጸደቀው የራሱ ሕገ መንግሥት ስለኾነ ሕዝብ በመራራ ትግል ያጸደቀውን ሕገ መንግሥት መጣስ የወንጀሎች ሁሉ ወንጀል ነው፡፡

በዚህ ስብሰባ ከፍተኛ ግንዛቤ መያዙ በጣም የሚያስደስት ነው፤ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቅ ተስፋ ነው፡፡ ለውጭ ጠላት ደግሞ ሲጠብቀው የነበረ ብጥብጥ መቅረቱ ሕዝብን የሚያስደስት፣ ጠላትን ደግሞ የሚያሳፍር ነው፡፡

ሌላው ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተነሣ ነበር፡፡ አንድ አባታችን ካነሧቸው ብዙ ነገሮች አንዱ፣ ‹‹መንግሥት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እጁን ያስገባል›› የሚል ነው፡፡ መንግሥት በሃይማኖት ውስጥ በእስልምናም ይኹን በኦርቶዶክስ እጁን አያስገባም፡፡ በዚህ ጉዳይ የመጀመሪያ ተጠያቂው እምነቱ ነው፡፡ ሕገ መንግሥት የሰጠው መብት ሲጣስ፣ መንግሥት እጁን ሲያስገባ ለምን ዝም አለ? ለሕገ መንግሥታዊ መብቱ ለምን አልታገለም? ሁለተኛው ተጠያቂ ደግሞ መንግሥት ይኾናል፡፡

ስለዚህ በሩን ከፍቶ ሲያንቀላፋ መንግሥት እጁን ካስገባበት እምነቱ ይጠየቃል፡፡ ይኹን እንጂ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መንግሥት እጁን እንዳላስገባ መቶ በመቶ አምናለኹ፡፡ አንዳንድ የመንግሥት ሰዎች ግን እጃቸውን አስገብተው ሊኾን ይችላል፡፡ ስለዚህ እነዚህን መመከት ነበረበት፡፡ በመጀመሪያ ተጠያቂው ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ራሱ ሲኾን እጃቸውን ያስገቡ ሰዎች ደግሞ በሁለተኛ ደረጃ ተጠያቂ ይኾናሉ፡፡

ሁለተኛ፣ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በአንድ ወጣት*የተነሣ ሐሳብ አለ፡፡ አክራሪነት አደጋ ነው ብሏል፡፡ በኋላ በእስልምና ሃይማኖት አካባቢ በአንዳንድ ሰዎች የሚታየው አክራሪነት አደጋ ነው፤ ዋናው ግን በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተቀበረው ፈንጅ ነው ትልቁ የአክራሪነት አደጋ ብሏል፡፡ አክራሪነት ማለት እምነቱን ለፖሊቲካ ጥቅም ማዋል፣ እምነቱን ለፖሊቲካ ጥቅም ክፍት ማድረግ ማለት ነው፡፡

አንዳንድ ማኅበራት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን የፖሊቲካ መድረክ እያደረጓት ነው፤ ማኅበሩ** እንኳ ባይኾን አንዳንድ ሰዎች ብሎ ጠቅሷል፡፡ ይህን ተጠንቅቆ ያቀረበው ይመስለኛል፡፡ ማኅበሩ ነው አክራሪ ወይስ በማኅበሩ ያሉ አንዳንድ ሰዎች ናቸው? መጣራት ያለበት ጉዳይ ነው፡፡

በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ማኅበር ያሉ አንዳንድ ሰዎች ማኅበሩ ጤናው የተበከለ እንዳይኾን ማጣራት፣ ተጠንቅቆ መያዙ፣ እንደተባለው ፈንጅ ከኾነ አስቸጋሪ ነው፡፡ ወጣቱ* እና ዶክተር ሽፈራው ተክለ ማርያም (የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር) ሁለቱም ከባድ የጥንቃቄ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

እንደተባለው፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በእውነት የፖሊቲካ መድረክ እየኾነች ከኾነ፣ በዚህ አገር የትኛው አክራሪነት ነው ከተባለ፣ ትልቁ አደጋ ያለው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ነው የተባለው ትክክል ነው ወይስ ትክክል አይደለም የሚለው መጣራት የሚኖርበት ቢኾንም በሁለቱ ሰዎች የተጠቆመው ግን የሚያስተኛ አይደለም፡፡ ከእምነቱ ቦታ የኾንም መተኛት የለብንም፤ የሌሎች እምነት አማኞችም መተኛት የለባቸውም፡፡

* * *

ሐራዊ ማስታወሻ፡-

*አቶ ስብሓት ወጣቱ ሲሉ የጠሯቸው የስብሰባው ተሳታፊ ከከምባታ ሐዲያ ጉራጌና ስልጤ አህጉረ ስብከት ከሚገኘው ሃላባ ወረዳ ቤተ ክህነት ጽ/ቤትና ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የመጡ አባ ዮናስ የተባሉ መነኩሴን ነው፡፡ እኒህ ስመ መነኮስ እንደ በጋሻው ደሳለኝ ላሉ ሕገ ወጥ ሰባክያን ዐውደ ምሕረት በመፍቀድና ምእመኑን ሰላም በመንሳት በወረዳው የማኅበሩ ጽ/ቤት እንዲዘጋ ያደረጉ፣ ከትምህርቱም ከግብረ ገቡም የሌሉበት ግለሰብ ናቸው፡፡

መንግሥት አካሂደዋለኹ በሚለው የፀረ አክራሪነት ትግል አጋር መስለው የተጠጉ ግለሰቦች [የደብር አስተዳዳሪ ለማሾም 60,000 ብር ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ በመያዛቸው 60 ጎራሽ የተባሉትንና ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ምክትል ሥራ አስኪያጅነት ተነሥተው ወደ መ/ፓ/ጠ/ቤተ ክህነት የትምህርትና ሥልጠና መምሪያ ምክትል ሓላፊነት የተዛወሩትን የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢን ርእሰ ደብር በሪሁ አርኣያን ይጨምራል] ያላቸውን አግባብነትና የሚሰጡትን መረጃ ትክክለኛነት (ቅንነት) ማጤን ይገባዋል፡፡

አቶ ስብሓት በቤተ ክርስቲያናችን ላይ የሚያራምዱትና በልዩ ልዩ ዘገባዎች ሲገለጽ የቆየው አቋማቸው በተለይ ከ፳፻፩ ዓ.ም ጀምሮ በሚገባ ይታወቃል፡፡ ‹‹ሕገ መንግሥት የሰጠው መብት ሲጣስ፣ መንግሥት እጁን ሲያስገባ ለምን ዝም አለ? ለሕገ መንግሥታዊ መብቱ ለምን አልታገለም?›› ማለታቸው በአባባል ደረጃ ተገቢ ቢኾንም እርሳቸው የጠቀሱትን ሕገ መንግሥታዊ መብት ለማስከበር ቢያንስ በግንቦት ፳፻፩ ዓ.ም በመጠኑ የሞከሩ ብፁዓን አባቶች ምን እንደደረሰባቸው የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን የምንለው ሊቃነ ጳጳሳቱን ልናመሰግናቸው ፈልገን ወይም አቶ ስብሓት እንዳሉት ‹‹በሩን ከፍቶ ያንቀላፋ የለም›› ለማለት አይደለም፡፡ በሌላ መድረክ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ስለ ኹኔታው ምሬታቸውን በገለጹበት ወቅት ‹‹ብትሰየፉስ!›› ያሏቸው የመከራቸው ፍጻሜ ገና መኾኑን ስለሚያሳይ፡፡

አቶ ስብሓት ለቤተ ክርስቲያናችን ተቋማዊ ለውጥ በቅ/ሲኖዶሱና በቀድሞው ፓትርያርክ መካከል የተደረገው የውስጥ ትግል በተጧጧፈበት ወራትና ከዚያም ወዲህ በእጅጉ ይጠሏቸው ነበር የሚባሉትን የቀድሞውን ፓትርያርክ ከመንበራቸው ለማስወገድ ማኅበሩ በቅ/ሲኖዶስ ዕውቅና ካገኘበት የአገልግሎት ዓላማና ስልት ውጭ ሚና ለመስጠትና መሣርያ ለማድረግ የገፋፉበት ኹኔታ በማኅበሩ ቀጣይ ህልውና ላይ ያላቸውን ፍላጎት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ እንደነበር ይነገራል፡፡

ግፊታቸው በወቅቱ በማኅበሩ ጥቂት አመራሮች መካከል ልዩነት ፈጥሮ እንደነበር የሚገለጽ ቢኾንም ተቀባይነት ያገኘ ግን አልነበረም፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን ‹‹የቤተ ክህነት ዕዳ ነው›› በማለት ‹‹የተቃዋሚ ፖሊቲካ መድረክነት›› እንደሚታይበት ወዘተ ባለፈው ዓመት የፍትሕ ጋዜጣ ጽሑፋቸው የሰነዘሩበት ሒስም የዚያ ማወራረጃ እንደኾነ ይታሰባል፡፡

ማኅበሩ ከተመሠረተበት ዓላማና ከሚፈለግበት አገልግሎት አኳያ በድክመት የሚተችበትና ገና ብዙ እንደሚቀረው የብዙዎች እምነት ቢኾንም በሰሞኑ ስብሰባ አቶ ስብሓት ወጣቱ ባሏቸው አባ ዮናስ ጥቆማ በኩል አልፈውና የአባ ዮናስን ንግግር አጉነው ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሰጡት አስተያየት ወይ አቅጣጫ መነሻው ጥላቻ የወለደውና ቅንነት የጎደለው መረጃ እንደኾነ የመረጃው ጠቋሚ ሰው ስለ ማኅበሩ ባላቸው አቋምና በወረዳቸው ከማኅበሩ አባላት ጋራ ባላቸው ግንኙነት መረዳት አያዳግትም፡፡

መንበረ ፓትርያርኩን በመወከል በስብሰባው እንዲገኙ ጥሪ ከተደረገላቸው 50 ተሳታፊዎች መካከል ማኅበረ ቅዱሳን በዋና ጽ/ቤቱ ደረጃ እንደማኅበር እንዳልተጋበዘና ይህም በአክራሪነት ከተካሄደው ፍረጃ ጀምሮ የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰጡበት እንደሚገኝ ተሰምቷል፡፡

አባ ዮናስ ከእውነት የራቀ ጥቆማቸውን፣ አቶ ስብሓትም በዚሁ ላይ የተመሠረተ አስተያየታቸውን/አቅጣጫቸውን በሰጡበት መድረክ ሊቃነ ጳጳሳቱ አቡነ ገብርኤል፣ አቡነ ናትናአል ፣ አቡነ ኄኖክ፣ አቡነ ጎርጎሬዎስ በአጸፋ የመናገርና ምላሽ የመስጠት ዕድል ተነፍገዋል፡፡ ይኸው የስብሰባው አካሄድ ከአዳራሹ ውጭ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱና በፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሓላፊዎች መካከል በከፍተኛ ደረጃ አጠያይቆ እንደነበር ተዘግቧል፡፡ በውይይቱ ቤተ ክርስቲያን ከአክራሪነት አንጻር የተገለጸችበትንና ማኅበሩን አስመልክቶ የተሰነዘሩ ሐሳቦችን መንበረ ፓትርያርኩ በቀላሉ እንደማይመለከተውና በጥብቅ እንደሚነጋገርበት ሊቃነ ጳጳሳቱ ለሚኒስቴሩ ሓላፊዎች እንዳሳሰቧቸውም ተገልጧል፡፡

Hara tewahdo

የወያኔ መንግሥት አክራሪነትን እና ሽብርተኝነትን በመዋጋት ሽፋን ከተከተለው የኢትዮዽያን ህዝብ የማሸበር ዒላማ ያደረገ ፖሊሲና ይህን ፖሊሲ ለማስፈፀም ከሚሠራቸው በርካታ ፀረ ህዝብ ስራዎች አንድ ነገር መናገር ይቻላል፡፡ ገዢው ፓርቲ ኢትዮጵያውያን ወደ ሁከትና ብጥብጥ፣ ብሎም ወደ ለስልጣኑ የሚያሰጋው ከሆነ እስከ መበታተን የሚደርስ እንደ እስሥት እራሱን እየቀያየረ የዘረኛ መርዙን ለ22 ዓመት ሲረጭብት ኖርዋል፡፡ ይህ የፀረ ሽብር አዋጅ ( ነፃነቱንና መብቱን የሚጠይቅ የሚታፈንበት ህግ) በህዝበ ላይ እንዲፈጠር በማድረግና በማስፈራራት “የዓለም አቀፉ ፀረ ሽብር ጦርነት” አጋርነቱን ማደስ፣ በዚህም ከአሜሪካና ከምዕራብ አውሮፓ አገራት የማያቋርጥ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የዲፕሎማሲ ድጋፎችን ማግኘት ይፈልጋል፡፡ ያለፉት 22 ዓመታት ታሪክ የሚያሳየው፣ ገዥው ህወሓት/ኢህአዴግ ስለመብት መከበር የቆሙትን ሁሉ በየተራ ለማንበርከክ በፈጠራ ክሰ መወንጀል፣ ማሰርና ማሳደድ ብሎም መግደል ዋነኛ ስልቶቹ ሆነው መቆየታቸውን ነው። ይህንን የጥፋት አካሄድ ህጋዊ ለማስመሰልም ሰፊ የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ሥራ መስራቱ የተለመደ ነው። በአገር ውስጥ ለሚወስዳቸው ዴሞክራሲን የማቀጨጭ፣ነፃነትን የመገደብ፣ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ያለመቻል ችግሮች፣ በአጠቃላይም በአገሪቱ ውስጥ የሕግ የበላይነት አለመኖርን “በፀረ ሽብር ትግሉ አስገዳጅነት የተፈጠሩ” አስመስሎ ለማቅረብ ይፈልጋል፡፡ የሰብአዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶች እና የነፃነት ገደቦችን ሁሉ “የህዝብን ሰላም ለመጠበቅ ሲባል በህጋዊ መንገድ የተጣሉ ገደቦች” የማስመሰል ፍላጎት እንዳለው ባለፉት ዓመታት ከወሰዳቸው ፖለቲካዊ እርምጃዎች እና እርምጃዎቹን ተገቢ ለማድረግ ካቀረባቸው ምክንያቶች መገንዘብ ይቻላል፡፡
… ምንም እንኳ ኢህአዴግ ኢትዮጵያውያን ያነሷቸውን የነፃነት ጥያቄዎች ለማፈን የ“ሽብርተኝነት” አቧራ ለማስነሳት እጅግ ቢደክምም፣ ራሱ መንግሥት ለህጋዊ እና ሰላማዊ የህዝቦች የመብት ጥያቄ ምላሽ እየሰጠ ያለው የ“ሽብርተኝነት” ተግባር በመፈፀምነው፡፡ በዚህም መሠረት በመጀመርያ የሞከረው፣ “አንድ ግደል፤ አሥር ሺህዎችን አሸብር” የሚለውን የቻይኖች አባባል ተግባራዊ ማድረግ ነበር፡፡
ኢትዮጵያውያን ወያኔ ሊገባው በማይችል ጠንካራ የአንድነት ገመድ ተሳስረዋል ፡፡ በወንጀለኛ የፌደራል ፖሊሶች የሚተኮሱ ጥይቶችና ከብረት የተሰሩ የግፈኛ በትሮች ጭቁኑን ህዝብ ለበለጠ ሰላማዊ ትግልና መስዋዕትነት ያዘጋጁታል እንጂ ከቶውኑም ከትግሉ አያሸሹትም፡፡

ከጭቆና በላይ ሽብር የለም። ምክንያቱም ጭቆና ማስፈራራት፣ ግድያ ……… ምናምን (ሰው ፈርቶና ተሸብሮ ሳይቃወም እንዲገዛ ለማድረግ የሚደረጉ ጥረቶች የሽብር ተግባራት ናቸው)። “ሽብር” ማለት’ኮ ኣንድ ኣካል ራሱ የሚፈልገውን ተግባር በሌሎች ሃይል በመጠቀም ወይ በማስፈራራት ለመጫን ሲሞክር ነው። ሌሎችን እያስፈራራ ያለው ማነው?ማነው ንፁሃን ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን በየመንገዱ የገደለ ? ኣሸባሪ ማነው? ማነው ሰለማዊ ዜጎችን በማፈን እያሸበረ ያለው?

ወያኔ፣ ዓመታትን ባሰቆጠረው ግፍና የመብት ረገጣው፣ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በስነልቦና ሽብር አፍኖ፣ አንዱን የህብረተሰብ ክፍል በሌላው ላይ እንዲነሳ በማድረግ፣ የከፋፍለህ ግዛ መንገዱን በማጠናከር፣ የአምባገነን የስልጣን ዘመኑን ለማራዘም እየጣረ መሆኑ ግልጥ ነው። ዛሬ በሀገራችን ውሰጥ፣ በወያኔ መብቱ ያልተረገጠ፣ የጥቃቱ ስለባ ያልሆነ የህብረተሰብ ክፍልን ማግኘት አይቻልም። ይህን መጠን የለሽ ረገጣ ለማስቆምና ዴሞክራሲያዊና ስብዓዊ መብቶችን ለማስከበር የሚቻለው ደግሞ ሁሉም ዜጋ፣ በግልም ሆነ በጋራ፣ ለመብቱ መከበር “እምቢ አልገዛም” ብሎ ሲነሳ ብቻ ነው።
by Lemlem Kebede from Oslo Norway

[/imgwrap][/imgwrap]

Image

በኢትዮጵያ የውጭ እርዳታ ይጎርፋል፤ በግርድፉ ከ40-50 ቢሊዮን ዶላር ባለፉት 22 አመታት ተለግሷል። ወደ 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብም ተበድረናል፡፡ የውጭ ኢንቨስትመንትም ይፈሳል፤ ግንባታዎችም ይካሄዳሉ። በእነዚህ ፈንድሻ ዜናዎች መሃከል ግን ብዙ ችግሮችም አሉ። ውሃ ፣ መብራት፣ ስኳር እና ዘይት በፈረቃ ይከፋፈላሉ፤ ትራንስፖርት ችግር ነው፤ በቀን ሶስት ጊዜ ለመብላት ጭንቅ ነው፤ ነጻነት፣ ፍትህ፣ ሰብዓዊ መብት የሚባሉት ነገሮች ከመንግስት መዝገበ-ቃላት ተሰርዘዋል።

የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አንድ ልዩ ባህሪ አለው። እንደሚታወቀው ልማትና ድህነት ተጻራሪ ሃይሎች ናቸው። ሁለቱ ሃይሎች በአንድ አቅጣጫ መጓዝ አይችሉም። ልማት ወደ ግራ ከሄደ ድህነት የግድ ወደ ቀኝ መጓዝ አለበት። በሃይማኖታዊ ቋንቋ ሰይጣንና መላዕክ ማለት ናቸው። አንዱ ባለበት ቦታ ሌላው ድርሽ አይልም። ይሄ ህግ ተዛብቶ “ልማትና ድህነት በአንድ ላይ ተቃቅፈው ታንጎ የሚጨፍሩበት አገር የት ነው? ” ከተባለ ያች አገር ኢትዮጵያ ናት። ልማቱ አደገ ሲባል፣ ድህነቱም በዚያው ልክ ያድጋል።

አገሪቱ ለ10 ዓመታት በ11 በመቶ እንዳደገች ከተነገረ በሁዋላ እንኳ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ( ምግብ፣ መጠለያና ልብስ) ማሟላት ጭንቅ ሆኗል። የልማቱን ኬክ ጥቂቶች ይበሉታል፣ ብዙዎች ፍርፋሪውን እንኳ አጥተው በረሃብ ያሸልባሉ። ቀኑ ይርዘም እንጅ የባስቲሌ አመጽ በአራት ኪሎ መደገሙ አይቀሬ ነው፤ ድህነትና ልማት ተጣምረው ታንጎ በሚደንሱባቸው አገሮች ማህበራዊ ምስቅልቅል የመጨረሻው ምርት ይሆናል።

የገዚው ፓርቲ ካድሬ ኢኮኖሚስቶች “ልማቱ ጤነኛ አይደለም” ተብሎ ሲነገራቸው አይቀበሉም፤ ክርክር ሲነሳም ብዙውን ጊዜ የሚሰጡት መልስ ” የሚቀጥለው ትውልድ ያልፍለት ዘንድ ይህኛው ትውልድ መስዋትነት መክፈል አለበት” የሚል ሆኖ ይገኛል። በካድሬው አስተሳሰብ ይሄ ትውልድ ጨለማ ውስጥ ቢኖር፣ የሚቀጥለው ትውልድ መብራት እንደልቡ ያገኛል፣ ይሄ ትውልድ ውሃ ቢጠማው ፣ መጪው ትውልድ በጁስ ይራጫል፣ ይሄ ትውልድ ትራንስፖርት ቢቸግረው፣ መጪው ትውልድ በቤት መኪና ይንበሻበሻል ።

የካድሬ ኢኮኖሚስቶች ዋና አላማ ይሄ ትውልድ የመብትና የማህበራዊ ግልጋሎት ጥያቄዎችን እንዳያነሳ የተስፋ ዳቦ እየመገቡ ማዘናጋት ነው፤ አንዳንዴ የሚገነቡ መንገዶችን እያሳዩ ” የወደፊቱ ልጅህ መኪናውን የሚያሽከረክርበት ነው፣ ዘመናዊ ህንጻዎችን እያሳዩ ” የወደፊቱ ልጅህ የሚኖርበት ቤት ነው” እያሉ ያማልሉታል። ይሄ ትውልድ የውሃና የመብራት ጥያቄ ይሟላልኝ ብሎ እስካልተነሳ ድረስ የዛሬው ካድሬ ጭንቀት የለበትም፤ ለመጪው ጊዜማ የመጪው ትውልድ ካድሬ ይጨነቅበታል። “ለመሆኑ መጪው ትውልድ የሚባለው ስንተኛው ትውልድ ነው? የሚቀጥለው ትውልድ እንደሚያልፍለትስ ማረጋገጫው ምንድነው?” እንዲህ አይነት ጥያቄዎች ለካድሬ ኢኮኖሚስቶች መጠየቅ የሌለባቸው” ነውር ” ናቸው።

“ይሄ ትውልድ ለመጪው ትውልድ ሲል መስዋትነት መክፈል አለበት” የሚለውን የካድሬ ቅስቀሳ አምነው የተቀበሉ ሰዎች አጋጥመውኛል። እነዚህም ሰዎች በፊናቸው”ልማትና ዲሞክራሲ በአንድ ጀምበር አይመጣምና ታገሱ ” ሲሉ ከካድሬው የሰሙትን ስብከት መልሰው ለሌሎች ሰዎች ለማስረዳት ሲሞክሩ አይቻለሁ። እንዲህ አይነቱ ስብከት ዜጎች ለመብታቸው እንዳይነሱ በማድረግ በኩል የራሱ አስተዋጽዎ አለው። መሰረታዊ ለውጥ በአገራችን እንዲመጣ የሚፈልጉ ሃይሎች እንዲህ አይነቱን የማዘናጊያ ቅስቀሳ ፣ በእውቀት ላይ በተመሰረተ ክርክር ሊመክቱት ይገባል። በኢትዮጵያ ስላለው ልማትና ድህነት የጠራ ግንዛቤ መያዝ ለዲሞክራሲያዊ ለውጥ የሚደረገውን ትግል ያግዛልና ሁሉም አስተያየቱን ሊሰጥበት ግድ ይላል።

በቀድሞው የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ፣ ሊ ኩዋን ስም የተሰየመ “የሊ ንድፈ ሃሳብ” የሚባል በፖለቲካ ኢኮኖሚ ትምህርት ውስጥ የሚገኝ አስተሳሰብ አለ። ይህ አስተሳሰብ ዜጎችን ከብዙ ጊዜያዊ መብቶቻቸው በመገደብ ልማትን ለማምጣት የሚያልም ሲሆን፣ ዳቦን ከመብት እንዲሁም አምባገነንነትን ከዲሞክራሲ ያስቀድማል ። በዚህ አስተሳሰብ መነሻነት ኢኮኖሚያቸውን የመሩ የእስያ ነብሮች የሚባሉ አገሮች ድህነትን “ቻው” ለማለት እንደቻሉ ይነገራል ። ኢህዴግም የዚህ አስተሳሰብ ተከታይና አራማጅ ነው። አስተሳሰቡ ለብዙ አምባገነን መንግስታት የሚጥም፣ ያለ ገደብ በስልጣን ላይ ለመቆየትም እንደምክንያት ሆኖ የሚያገለግል ” ተወዳጅ” አስተሳሰብ ሆኖ ተገኝቷል- በአንባገነኖች ዘንድ። አቶ መለስም ይህን ሃሳብ መነሻ አድርገው ” ዲሞክራሲና ልማት ግንኙነት የላቸውም” የሚል የመመረቂያ ጽሁፍ መጻፋቸውን ሰምቻለሁ፣ ባላነበውም። የኖቤል ተሸላሚው አማርትያ ሴን የነጻነትና የልማት ግንኙነቶችን የሚያሳይ ውብ መጽሃፍ ባይጽፉ ኖሮ ፣ “ልማት ያለነጻነት ዋጋ የለውም” እያልን የምንጮኸውን ጩኸት ትንሽም ቢሆን የሚሰማን አናገኝም ነበር። እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በዘር ተደራጅተው አገር ከሚመሩት መንግስታት በስተቀር ዛሬ አብዛኛው አለም፣ ነጻነት ለልማት አስፈላጊ መሆኑን ይቀበላል። የእስያ ነብሮች ያደጉት ከነጻነት በፊት ልማትን ስላስቀደሙ ነው የሚለው መከራከሪያም ብዙ አሳማኝ ሆኖ አልተገኘም፤ የእስያ ነብሮች እድገት የራሱ የሆኑ ብዙ ፖለቲካዊና ስትራቴጂካዊ ምክንያቶች አሉት። በተለይ ስለ ቀጣይ እደገት (sustainable development) ስናስብ፣ ነጻነት እጅግ አስፈላጊ ነገር መሆኑን ከአረብ አገራት አብዮትና ውድመት ተምረናል። ነጻነት ከሌለ ዘላቂና ለትውልድ የሚተላለፍ ልማት አይኖርም፤ ዛሬ የተጀመረው ልማት ነገ ለነጻነት በሚደረግ ትግል የሚወድምበት አጋጣሚ ከፍተኛ ነው። ለዚህ ደግሞ ሊቢያ፣ ሶሪያና ግብጽ ምስክሮች ናቸው። ቻይናም ቢሆን ፖለቲካዊ ለውጥ ካላደረገች እጣፋንታዋ መስቅልቅ ነው።

“ከነጻነት በፊት ልማትን እናስቀድም” የሚሉ አምባገነን መንግስታት፣ ልማት በእነሱ ብቻ እንደሚመጣና እነሱ ከሌሉ ልማቱ እንደሚደናቀፍ በማስወራት እድሜ ልክ በዙፋኑ ላይ ለመቀመጥ ያልማሉ። ይህን ህልማቸውን እውን ለማድረግም ” አሳማኝ የሚመስሉ” የኢኮኖሚ ትንተናዎችንም ያቀርባሉ። ከእነዚህ ትንተናዎች አንዱ ይህን ይመስላል ፦ “የካፒታሊዝም ስርአት ለሰዎች ኑሮ መሻሻል አስፈላጊ ነው። ስርአቱ እውን ይሆን ዘንድ ደግሞ ካፒታሊስቶችን በብዛት ማፍራት አስፈላጊ ነው። ካፒታሊስቶች ሀብት እንዲያጠራቅሙ ደግሞ ሰራተኛው የደሞዝና ሌሎች ጥቅማጥቅሞችን መጠየቅ የለበትም። ባለሀብቱ ሃብት ማጠራቀም ከቻለ፣ አዳዲስ ግንባታዎች ይካሄዳሉ፣ ብዙ ሰራተኞችም ይቀጠራሉ። እድገትም ይኖራል፣ ሁሉም ተያይዞ ያልፍለታል። መንግስትም ቢሆን የህዝቡን ፍላጎት አሟላለሁ ብሎ ባለሃብቶች ብዙ ቀረጥ እንዲከፍሉ ማስገደድ የለበትም። የህዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ሲል ባለሀብቱን ብዙ ግብር ማስገበሩ አይቀርምና የህዝቡን ጥያቄ ለጊዜው ገሸሽ ያድርግ።” አስተሳሰቡ በአጭሩ “ታገሱ፣ ይህኛው ትውልድ ባያልፍለት የሚቀጥለው ትውልድ ያልፍለታል።” የሚል ነው።

በዚህ ንድፈ-ሀሳብ መሰረት የመብትና የኢኮኖሚ ጥያቄዎችን “ያለጊዜው” መጠየቅ ጎጂ ነው፤ ህዝቡ በችግር ብዛት ቢያልቅም የሚጠበቅ ነው። መንግስት የስራ ማቆም አድማዎችንና ሌሎች የመብት ጥያቄዎችን በሃይል ለመጨፍለቅ ጦሩን ቢሰብቅና ዜጎች ቢሞቱ ለካፒታሊዝም ግንባታ እስከሆነ ድረስ የተቀደሰ እርምጃ ነው። አስተሳሰቡ ኢኮኖሚውን ነጻ ፖለቲካውን እዝ የሚያደርግ፣ “ፖለቲካው ኮሚኒዝም- ኢኮኖሚው ካፒታሊዝም” ነው።

ይህን አስተሳሰብ ወደ አገራችን ነባራዊ ሁኔታ እናምጣ እንየው። “ባለሀብቱ ሀብት ያጠራቅም ዘንድ መታገስ አስፈላጊ ነው” የሚለው ምክር አሳማኝ ነው እንበል። ይሄ ትውልድ ተበድሎ የሚቀጥለው ትውልድ ይለፍለት የሚለውም አርበኝነት ነው እንበልና እንቀበለው። ነገር ግን ይህን አስተሳሰብ በአገራችን ተግባራዊ ብናደርገው የሚፈለገውን ውጤት እናመጣለን ወይ? ብለን ስንጠይቅ ፣ የምናገኘው መልስ አሉታዊ ይሆናል። እነሆ ምክንያቶቹ-

በቅድሚያ በእኛ አገር ሃብት እንዲያጠራቅሙ ስርአቱ የሚንከባከባቸው አዲስ-ሰዎች በአብዛኛው ከአንድ አካባቢ የመጡ ወይም የአንድ ብሄር አባላት ናቸው። እነሱ ሃብት እስኪያጠራቅሙ ሌላው ህዝብ እንዲሞት መፍረድ ከሞራል አኳያ ተቀባይነት አይኖረውም። እነሱ ብቻ ካፒታሊስቶች እንዲሆኑና ኢኮኖሚውን እንዲቆጣጠሩት ከፈቀድን ሌላው ህዝብ በባርነት ስር እንዲኖር እየፈረድንበት ነው። ኢኮኖሚውን እነሱ ብቻ ከተቆጣጠሩት ፖለቲካውንም መቆጣጠር አይሳናቸውም። ደቡብ አፍሪካ በኢትዮጵያችን ትመሰረታለች፤ ልዩነት ቢኖር የካፒታሊስቶቹ ቀለም ብቻ ነው።

“ግደየለም እነሱም የእኛው ሰዎች ናቸው” ብለን ብንተዋቸው እንኳ ፣ የአገር ፍቅር ስሜት አልባነታቸው ፈቅደን እንዳንገዛላቸው ያደርገናል። እነዚህ አዳዲስ ካፒታሊስቶች ገንዘባቸውን በአገር ውስጥ ባንክ አያስቀምጡም፣ ፋብሪካ ከሚገነቡ ህንጻ ቢቀጣጥሉ ይመርጣሉ፤ ህንጻ ሲሰራ እንጅ ከተጠናቀቀ በሁዋላ ብዙ ሰው አይቀጥርም። ግሎባል ፋይናንሻል ኢንቴግሪቲ 11 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የአገሪቱ ገንዘብ በውጭ ባንኮች መቀመጡን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ይህ ሃብት የማን ነው? ተከድኖ ይብሰል። ነገር ግን እነዚህ ባለሃብቶች የአገር ፍቅር ስሜት እንደሌላቸው በደንብ ያሳያል።

የእኛ አዲሶቹ ባለሃብቶች ጉራና ልታይ ልታይ ማለትን ይወዳሉ። ደሃው እየደማ በሚያገኙት ገንዘብ አንድ ጠርሙስ ውስኪ እስከ 30 ሺ ብር እየገዙ ይራጬቡታል፤ ፈረንጆች እንኳ ለመያዝ የማይደፍሩትን ዘመናዊ መኪኖችን እያሽከረከሩ በሚሞትላቸው ህዝብ ላይ ይንደላቀቁበታል። ለጎራ ካልሆነ ሃመር መኪና በእግሩ በሚሄድ ህዝብ መሃል ምን ይሰራል? የሆላንድ ባለሀብት እኩል እንደ ነዋሪው ቅናሽ ሱቅ ውስጥ ገብቶ እቃ ይገዛል፣ ሚሊኒየሩን ከሌላው ህዝብ መለየት አይቻልም። የእኛን አዳዲስ ባለሀብቶች ለመለየት በጣም ቀላል ነው። እነዚህ ባለሀብቶች ናቸው የነገውን ትውልድ ያሳልፉለታል ተብሎ የሚጠበቀው።
ከሁሉም በላይ እነዚህ አዳዲስ ባለሀብቶች ገንዘብ የሚያጠራቅሙት የመንግስትን ስልጣን ይዘው እንጅ ሰርተው፣ ለፍተው፣ በእኩልና በፍትሃዊ መንገድ ተወዳድረው አይደለም። የሃብት ምንጭ የሆነውን መሬት እንደልብ እያገኙ፣ ከታክስ ነጻ እቃዎችን እያስገቡ፣ ተቀናቃኞቻቸውን በተንኮል ከገበያ እያስወጡ ነው የከበሩት።

ከእነዚህ ባለሀብቶች ውጭ ያለው ዋና ካፒታሊስት ( ባለሀብት) ደግሞ መንግስት ነው። በኢትዮጵያ እንዲያውም ዋናው ኢንቨስተር መንግስት ነው። መንግስት መሬትና ፋብሪካዎችን እየጨሸ የሚሰበስበውን ገንዘብ ከላይ ያሉት ቁንጮዎች ይመዘብሩታል። ከዝርፍያ የተረፈው ገንዘብ ለድሃው የኑሮ መደጎሚያ ይዋል ሲባልም ጦርነት ይሰበቃል። መንግስት ሃብት እስኪያጠራቅም ጥያቄዎችን ከመጠየቅ ታገሱ የሚባል ነገር ተቀባይነት የለውም ። መንግስት ሲደኸይና ዜጎች ሲበለጽጉ እንጅ ተቀራኒው ከተፈጠረ አደጋ ይኖራል።

አሁን ያሉት አዲሶቹ ባለሀብቶችም ሆኑ አሁን ያለው መንግስት የሚቀጥለውን ትውልድ ህይወት መለወጥ የሚችሉ አይደሉም። ባለሀብቶች ሃብት ሲያጠራቅሙ ለድሃው ተንጠባጥቦ ይደርሰዋል የሚለው የ trickle-down የኢኮኖሚ አስተሳሰብ ለአሁኑዋ አገራችን አይሰራም፤ ምክንያቱም ያሉን ባለሀብቶችና መንግስት በድሃው ላይ የሚዘምቱ እንጅ ለድሃው የሚቆሙ አይደሉም። ጤነኛ ካፒታሊዝም በጤነኛ ከፒታሊስቶች ይገነባል፣ ጤነኛ ካፒታሊስት ባይኖርም፣ አገር ወዳድ ካፒታሊስት ግን አለ። የእኛዎቹ፣ ከመንግስት ጀምሮ ጤነኞችም አገር ወዳዶችም አይደሉም።
ደሃው ኢትዮጵያዊ ዛሬ ለመብቱእና ለማህበራዊ አግልግሎት መሻሻል ካልተነሳ፣ ነገ በህይወትም ላይኖር ይችላል።

ስደመድመው – “የዛሬው ትውልድ ተበድሎ የነገው ትውልድ ይለፍለት” የሚለው አስተሳሰብ አሁን ባለው የአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ፈጽሞ የማይሰራ ፣ ሰዎች ለነጻነታቸውና ለመብታቸው እንዳይነሱ የሚያዘናጋ እንዲሁም የአንድን በዘር ላይ የተመሰረተ ስርዓት ቀጣይ ህልውና ለማረጋገጥ ተብሎ የሚነዛ አደገኛ አስተሳሰብ በመሆኑ፣ ዜጎች በዚህ አስተሳሰብ ሳይዘናጉ ዛሬውኑ ለመብታቸው መከበር መነሳት አለባቸው- ነገን ስንጠብቅ ዛሬ እንዳንሞት እንጠንቀቅ።

Image

ታላቁን ገመና የደበቀው የ“የንጉሡ ገመና”
የመጽሐፉ ርዕስ – የንጉሡ ገመና
የገጽ ብዛት – የ172
የታተመበት ዘመን – 2006 ዓ.ም
የሽፋን ዋጋ – ብር 49.75
አሳታሚ – ግርማ ለማ
የመጽሐፉ ይዘት ከታሪክ ዘውግ የሚመደብ ሆኖ አሳታሚው ሁለት ምንጮችን ተጠቅመው ነው ያሳተሙት፤ እነሱም ለ14 ዓመታት በንጉሥ አሽከርነት ያገለገሉት የአቶ ሥዩም ጣሰው መንዜው የግል ማስታወሻና የልዩ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ጽ/ቤት ቀይ ሽብርን አስመልክቶ ያሳተመው “ደም ያዘለ ዶሴ” የተሰኙ መፃሕፍት ናቸው፡፡
በተለይ አቶ ሥዩም ከልጅነታቸው ጀምረው በቤተመንግሥት ያደጉና ለድፍን 14 ዓመታት በንጉሡ አሽከርነትና አልባሽነት ያገለገሉ በመሆናቸው የንጉሠ ነገሥቱን ጓዳ ጐድጓዳ፤ የአሽከሮችን፣ የደንገጡሮችንና የወቅቱን ባለሥልጣናት ጠቅላላ ሁኔታ የማየት ብቻ ሳይሆን የማወቅ ዕድሉ ስለነበራቸው ማስታወሻቸው ተአማኒነት ይኖረዋል። አቶ ሥዩም ንጉሠ ነገሥቱ ሥልጣናቸውን ተቀምተው መጀመሪያ በቤተመንግሥታቸው ቀጥሎም በ4ኛ ክፍለ ጦር እስረኛ እስከሆኑበት ድረስ ንጉሡን በታማኝነት አገልግለዋል፤ በደርግ ዘመን እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ኖረው ኢህአዴግ ሲገባ በቁጥጥር ስር መዋላቸውና ከጠባቂዎች አምልጠው ራሳቸውን ማጥፋታቸው ይነገራል፡፡ ወደ መጽሐፉ እንመለስ፡፡
አሳታሚው ግርማ ለማ፤ በምስጋና ገጹ ላይ የጽሑፉን ዋና ቅጅ (ኦሪጅናል) የሰጠው “በያን ናስር” የተባለ ሰው መሆኑን ጠቅሷል፤ ግን በያን የሥዩምን ጽሑፍ እንዴት እንዳገኘው ወይም የሥዩም ወኪል ይሁን፤ የገለጠልን ነገር የለም፤ የተገኘበት መንገድ ቢጠቀስ በጣም ጥሩ ነበር፡፡ ምክንያቱም ሥዩም የሞተው በድንገት ነው፤ የተያዘውም ሳያስበው ቤቱ በታጣቂዎች ተከቦ ነው፡፡ ስለዚህ ሃሳባችንን ወደአልተፈለገ ጥርጣሬ እንዳያመራን ግርማ ረቂቁን እንዴት እንዳገኘው ቢገልጥልን መልካም ነበር፡፡ የተጻፈልን ታሪክ ነዋ! ታሪክ ያለአስተማማኝ ማስረጃ ሊታሰብም ሊጻፍም እጅግ ይከብዳል፡፡
መጽሐፉ የምስጋናና የመግቢያ ገጾችን ሳይጨምር፣ በዘጠኝ ምዕራፎች የተዋቀረ ነው፡፡ ስምንቱ ከስዩም ጣሰው ማስታወሻ የተወሰዱ ሲሆን ዘጠነኛው ምዕራፍ “ደም ያዘለ ዶሴ” ከተባለው መጽሐፍ የተገለበጠ ነው፡፡
የመጽሐፉ ጠንካራ ጐኖች
መጽሐፉ በንጉሡ ጓዳና ቢሮ ውስጥ ስለነበረው እውነት የገለጠልን በመሆኑ፣ የንጉሠ ነገሥቱን አጠቃላይ ሰብዕና ለሚያጠና ሰው ትልቅ የታሪክ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ ንጉሡ በካህናትና ባለሥልጣናት ዘንድ ተፈርተው ይከበሩ ስለነበር፣ ድምሩ ህዝብም አባቱን እየተወ “ኃይለሥላሴ ይሙት” በማለት በስማቸው ይምልና ይገዘት ነበር፡፡ ግን እንደ ሥዩም ጣሰው ጓዳቸውን ገብቶ የማየት ዕድል ቢገጥመው ኖሮ ምን ያህል ሲታለል እንደኖረ ይገባውና ከልቡ ይቆጭ ነበር ያሰኛል፡፡ ለማንኛውም የመጽሐፉን ጠንካራ ጐኖች በአምስት ከፍያቸዋለሁ፡፡
ገመና አንድ
ንጉሡ ተደባዳቢ ነበሩ
ንጉሡ አሽከሮቻቸውን ይደበድቡ ነበር፤ “…የፀጉር ቅባት ፓንተን ሳቀርብላቸው ቀና አሉ፤ አዩኝ፡፡ አሰቡ አሰቡና ‘ማታ ማነው ፍራፍሬውን የደገሰው’ ብለው ጠየቁኝ፡፡ እኔም ራሴ መሆኔን ነገርኋቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ብድግ አሉና ተያያዙኝ፡፡ እስከሚደክማቸው ድረስ ደበደቡኝና ቁጭ ብለው ፀጉራቸውን አበጠሩ፡፡ ክራባታቸውን አሰሩና ተነሱ። ልብሳቸውን ለብሰው ሲጨርሱ ጠሩኝ፡፡ እኔም አቀርቅሬ ተጠጋሁ፡፡ አስጐነበሱና እስከሚበቃቸው ወገሩኝና እየተሳደቡ ወደ ቁርሳቸው ሄዱ” (ገፅ 11-12)
ይህን አይነት እርግጫና ጥፊ ለሥዩም አዲስ አልነበረም፤ በየጊዜው ይገረፋል፤ የስድብ ውርጅብኝ ይዘንብበታል፡፡ ሁለት ቀን ብቻ ከተገረፈ በኋላ ብር እንዲሰጠው አድርገዋል፤ ይህ አንድም ምሥጢራቸው እንዳይወጣ ማባባያ ነው፡፡ አለዚያም ካሣ ነው ማለት ይቻላል፡፡
ሆኖም የሥዩም (አሽከርና የታሪኩ ፀሐፊ መሆኑን አንዘንጋ) ትልቁ ፈተና ከንጉሡ ዱላ ይልቅ የሴት አሽከሮች በእሱ ላይ ማደምና ከባለሥልጣናት ጥርስ ውስጥ ማስገባት ነበር ትልቁ ፈተና የሆነው። ለዚያ ሁሉ እርግጫ፣ ጥፊና ዱላ ሰበቡ ንጉሡ የገረዶችንና የአሽከሮችን ወሬ ስለሚሰሙ ነው፡፡ (ገፅ 14)
ንጉሡ ወሬ ይወዳሉ፤ የሆነ ያልሆነን ሁሉ የሚቀላምድላቸውን ሰው ያስጠሩትና ምንም ሳያጣሩ የተወራበትን ሰው ራሳቸው ይገርፋሉ፤ ካስፈለገም ግዞት ይልካሉ፡፡ (ገፅ 21 እና 24)
ገመና ሁለት
ንጉሡ ሴሰኛ ነበሩ
ንጉሡ ሴት በጣም አብዝተው ይወዱ ነበር፤ በዚህ የተነሳ ከጽዳት ሠራተኞች፤ ከአበሻ ወጥ ቤቶች፣ ከእንጀራ ጋጋሪዎች፣ ከቅንጬ ቤቶች፣ ከሴተኛ አዳሪዎች፣ ከሆስተስና ከባለ ትዳር ሴቶች ጋር ይቀብጡ ነበር፡፡ “ሴቶቹ አብዛኛውን ጊዜ የሚገቡት ቀን ከምሳ መልስ እረፍት በሚያደርጉበት ጊዜ ከ8-10፡30 ባለው ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ ጃንሆይ ገብተው ከተኙ በኋላ ትንሽ ቆይተው ደወል ይደውላሉ፡፡ በዚያ ጊዜ በዚህ ነገር የተለየ ባለሟል የሆኑ አሽከሮች በተራቸው ይገቡና “ዕገሊትን ጥራ” ሲባል ይጠራል፡፡ ምን አልባት እርሱ ከተጠራችው ሴት ጋር ሽርክና ከሌለው ወይም ከምትወስደው ገንዘብ በብዛት ካላካፈለችው “እርሷ አሁን የለችም” በማለት የርሱ ሽርክ በየጊዜው ብዙ ገንዘብ የምትሰጠውን ሴት “ዕገሊት አለች፤ እርሷ ከሥራዋ ላይ አትጠፋም” በማለት ይቀላምድና ይጠራል፡፡ ሲገቡና ሲወጡ የተለየ ጥንቃቄ ይደረጋል፡፡ ነገር ግን ሴቶቹ በሚያሳዩት መለዋወጥ የተቀረው ሰው እዚያ ቦታ እንደደረሰች ይገባዋል” (ገፅ 51)
“ቢሮ የሚደረገው ደሞ ሌላ ነው፤ ቢሮ በሚሠሩበት ጊዜ ረፈድ ሲልና አንዳንድ ባለሥልጣኖችን ካነጋገሩ በኋላ ገለል ብለው ቢሮ አጠገብ ካለው መኝታ ቤት ጐራ ይላሉ፡፡ ከዚያም በዚያ አካባቢ ከሚሠሩት ሴቶች ውስጥ የፈለጓትን አስጠርተው ትንሽ ከተጨዋወቱ በኋላ ወደ ቢሮአቸው ይገባሉ፡፡ …ሆስቴሶችንና ሌሎችን ደግሞ እምድር ቤት ካለው ቢሮ ነው የሚያገኙአቸው” (ገፅ 51)
ይህ ሁሉ ሲሆን እንደየሴቶቹ የንቃት መጠን ዛቅ ያለ ገንዘብ ይከፈላቸዋል፤ ከሥራ ቤት፣ እንጀራ ቤትና ወጥ ቤት ለሚመጡት ሴቶች የሚከፈላቸው አነስተኛ ገንዘብ ሲሆን ለጽዳት ሠራተኞችና ለሌሎች ሴቶች ግን ከ70-80 ሺህ ብር ይከፍሉ ነበር፡፡ ሴቶቹ ደግሞ ወደ ንጉሡ ላቀረባቸው ሰው (ደላላው) ከ5-10 ሺህ ብር ቀረጥ የመክፈል ግዴታ ነበረባቸው። በዚህ የተነሳ ከንጉሡ ጋር የተገናኙ ሴቶች ሁሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ቆንጆ ቪላና ዘመናዊ መኪና ይገዙ ነበር፡፡ ቀስ በቀስ እንዲያውም ፖለቲካዊ ሥልጣኑን ተቆጣጥረው የፈለጉትን ያስሾሙ ያስሸልሙ፤ የጠሉትን ደግሞ ያሰቃዩት ነበር (ገፅ 51)
አንዳንድ የንጉሡ ውሽሞች በጣም ቀበጦች ስለነበሩ በመንግሥት ወጭ፣ አስተርጓሚ ጭምር ተመድቦላቸው ለሽርሽር ፈረንጅ አገር ይሄዱ ነበር። በጣም የሚያሳዝነው ግን ንጉሡ የባለቤታቸውን የዕቴጌ መነን አስፋውን ጌጣጌጥ ሳይቀር ለውሽሞቻቸው መስጠታቸው ነው፡፡ ለአንዳንድ ውሽሞቻቸውም ቋሚ ደሞዝ ተቆርጦላቸው የቤተ መንግሥት አሽከሮች በየወሩ እቤታቸው ድረስ እየሄዱ ይከፍሉ ነበር፡፡ (ገፅ 56)
ይህ ድርጊት ያንገበገበው ሥዩም “ኢትዮጵያ በተለይ ከ1960 ዓ.ም ጀምሮ ስትገዛ የኖረችው በንጉሠ ነገሥቱ ሳይሆን በእልፍኝ አስከልካዮች፣ በጥቂት የእልፍኝ አሽከሮችና በገረዶች ነበር፡፡ …ቤተመንግሥቱ ቤተመንግሥት መሆኑ ቀርቶ ፍጹም የሰይጣን ቤት ሆኖ ነበረ” ሲል ትዝብቱን አስፍሯል። (ገፅ 20)
ገመና ሶስት
ንጉሡ አይጾሙም ነበር
ንጉሡ አክሱም ጽዮንንና ሌሎች አብያተ ክርስቲያናትን ስለአሠሩ ካህናት ያወድሷቸዋል፤ ይሰግዱላቸዋል፡፡ “አቤቱ ፍርድን ለንጉሣችን ስጠው” እያሉም ዘወትር ይፀልያሉ፤ እንደ ጻድቃንና ሰማዕታት በመቁጠርም መልክአ ኃይለሥላሴ ደርሰውላቸው ነበር፡፡ ሆኖም ንጉሡ የክርስቲያንን ህግና ሥርዓት በመጣስ፣ አርብና ረቡዕን እንዲሁም ሌሎች አጽዋማትን አይጾሙም ነበር፡፡ (ገጽ 25 እና 34)
ገመና አራት
ንጉሡ ጠንካራ ሰራተኞችንና ታማኞችን አይወዱም ነበር
“ግርማዊነታቸው የሚወዱት ሰው ፈጣን፣ አጭበርባሪ፣ አሳባቂ፣ በዕውቀት ያልበሰለ፣ እርሳቸውን አምታቶ የሚያታልላቸውን ሰው በጣም ይወዱታል፡፡ የጥቅም ተካፋዮቻቸው በሙሉ በዕውቀት ያልበሰሉ፣ የሰውን መብት በፍጹም ያልተረዱ፣ ሰውን ሸጠው ለመክበር ብቻ ጽኑዕ ዓላማ ያላቸው፣ ለኔ እንጂ ለኛ የሚል መንፈስ ፈጽሞ የሌላቸው ጨካኞች፣ ሰው በችግር ሲሰቃይ ሲያዩ ከማዘን ይልቅ መደሰትን የሚመርጡ ከንቱዎች ናቸው፡፡
“ግርማዊነታቸው አጥብቀው የሚጠሉት ሰው እውነትን በጣም አድርጐ የሚወድ፣ ዘወትር የሚከራከራቸው፣ በእውነት ፍጹም በሆነ መንገድ የሚወዳቸው፣ ሲዋሹ የሚያስተባብላቸው፣ የሚታሙበትን ነገር እንዲተው የሚነግራቸው፣ የማይንቀዠቀዥ፣ አዋቂ ሰው በፍጹም አይወዱም” (ገፅ 31) ይለናል፤ ሥዩም በ14 ዓመት የአሽከርነት ዘመኑ የታዘበውን ሲያካፍለን፡፡
ገመና አምስት
ንጉሡ ስስታም ነበሩ
ንጉሠ ነገሥቱ ኢትዮጵያን የምታክል ታላቅ አገርና እጅግ ብዙ ህዝብ የመግዛታቸውን ያህል ስስታቸውም ያን ያህል አሳፋሪ እንደነበር በመጽሐፉ ላይ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል፡፡ በልጅነት ዘመናችን የምናውቃቸው ንጉሥ፤ በየቦታው ሲዘዋወሩ ብር እንደጥሬ እየበተኑ የሚሄዱ መሆናቸውን ነበር፡፡
ሥዩም የሚያውቀውን እውነት ሲነግረን ግን ስስታቸው በጣም የወረደና ለማመን የሚያስቸግር ሆኖ እናገኘዋለን “…በተለይ ከኬኩ ትንሽ በቄንጠኛ አኳኋን ቆርሰው ከበሉ በኋላ በምልክት አድርገው በጥንቃቄ እንዲቀመጥ ይናገራሉ፡፡ በማግስቱ ሲመጣ ትንሽ ለውጥ ከታየበት “ማነው የተጫወተበት” በማለት ማሰቃየት ነው፡፡ አንድ ኬክ ከሶስት እስከ አምስት ቀን ድረስ እየተመላለሰ ይቀርባል፡፡ ለምሳሌ ሐሙስ ቀን ተጀምሮ እንደሆነና ቅዳሜ ደብረዘይት ቢሄዱ አብሮ ይሄዳል፤ ማሩንም በጣም አድርገው ይቆጣጠራሉ፡፡ ከማስቀመጫው ብልቃጥ ውስጥ ትንሽ ጐድሎ ያገኙት እንደሆነ “እንደፈለጋችሁ ትጫወቱበታላችሁ” ብለው መለብለብ ነው” (ገፅ 33) ሲል ያየውን ትዝብት ያካፍለናል፡፡
ከዚህ ሌላ መኝታ ቤታቸው በስጦታ ዕቃዎች፣ በቸኮላት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ስለሚሞላ ዕቃ ቤት ይመስል ነበር፤ እንዲያውም አትክልትና ፍራፍሬው፤ እንዲሁም ቸኮላትና ኬኩ እየተበላሸ የመኝታ ቤታቸውን ሽታ ያበላሸው ነበር፡፡ (47፣ 116፣ 117)
ከመጽሐፉ ውስጥ በጣም የገረመኝ ቢኖር (ገፅ 149) ቀኛዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ ከ1963 ዓ.ም ጀምሮ ለንጉሡ ልክ “ልዩ ካቢኔ” ይባል እንደነበረው የስለላ ተቋም፣ በየቀኑ ለንጉሡ ደብዳቤ ይልኩ የነበሩ መሆናቸው ነው፤ ለመሆኑ ቀኛዝማች ተሥፋን ከንጉሡ ጋር ያውም በየቀኑ የሚያገናኛቸው ምን ብርቱ ምሥጢር ነበር ይሆን እንድል አድርጐኛል፡፡
የመጽሐፉ ድክመት
መጽሐፉ ከላይ በመጠኑም ቢሆን የነካካኋቸውን ጉዳዮች የዓይን ዕማኙን ሥዩም ጣሰውን ዋቢ አድርጐ የመቅረቡን ያህል ሌላ ድክመት እንዳለበትም መዘንጋት አያሻም፡፡
አሳታሚው በመግቢያው ላይ “አሽከር ሥዩም (አፈሩን ገለባ ያድርግለትና) በሰነዱ ውስጥ ጽሑፉን ለንባብ ሳያበቃው እንዳይሞት አምላኩን የተማጸነበት ፀሎት አለ” ብሎናል፡፡ ግን ይህንን ከሰነዱ ውስጥ አናገኘውም፡፡ ይህ የሚያሳየን የሥዩም ሰነድ የተነካካ ወይም የተቆራረጠ ፍሬ ነገር አለው ማለት ነው፤ ይህ ከሆነ ደግሞ ፍጹም ስህተት ነው፡፡ አንድ አካል ሲቆረጥ ሌላውን ምሉዕ እንደማያደርገው ሁሉ የሥዩም ጽሑፍም የቋንቋ አርትኦት ብቻ ተደርጐለት መታተም ነበረበት፡፡
ሌላው ከወሲብ፣ ከንዋይና ከሃይማኖታዊ ገመናቸው ይልቅ የንጉሱ ፖለቲካዊ ገመና ቢታከል ኖሮ ጽሑፉን ተወዳጅ ያደርገው ነበር፤ ሰዎችን በምሥጢር መግደልና ማስገደል፣ በፍርድ አካባቢ የነበረው ሸር ሁሉ ሊገለጽ በተገባ ነበር፡፡ ይህን አይነቱን ታላቅ ገመና ሥዩም ሳይነካካው አልቀረም፤ ግን በመጽሐፉ ላይ አናገኘውም፡፡ ይህ ደግሞ ታላቁንና ለ44 ዓመታት የኖሩበትን ገመና ምስጢር አድርጐብናል፡፡ ከገጽ 141 ጀምሮ እስከ ገጽ 172 ያለውና “ደም ያዘለ ዶሴ” ከሚለው መጽሐፍ እንዳለ ተገልብጦ የቀረበልንም የመጽሐፉ ትልቅ ድክመት ነው፡፡ እንደ ትርፍ አንጀት የተለጠፈውን 32 ገጽ ከዋናው መጽሐፍ “ደም ያዘለ ዶሴ” ላይ አንብበነዋል፤ እዚህ ላይ መደረቱ ለምን አስፈለገ?
addis admass newspaper

Image

በአሜሪካ፣ በፈረንሳይና ቤልጂየም ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ነበራቸው
የ25 ሚሊዮን ዶላር ባለፀጋ ነበሩ – ወደ ቢሊዬነርነት ተጠግተዋል
ቤተ-መፅሃፋቸው ራሳቸው ባሰባሰቡት 10ሺ መፃህፍት የተሞላ ነበር

በሳምንቱ ማጠናቀቂያ ግድም “ጮማ” የሆነ መረጃ እጄ ገባ፡፡ አንድ ወዳጅ ነው መረጃውን ከባህር ማዶ በኢሜይል ያሻገረልን፡፡ The New York Times የዛሬ 105 ዓመት፣ አፄ ምኒልክ ሲሞቱ ነው ዘገባውን ያወጣው – ኖቨምበር 7 ቀን 1909 ዓ.ም፡፡ “ንጉስ ምኒልክ እዚህ ኢንቨስትመንት አላቸው” በሚል ርዕስ የቀረበው ፅሁፍ፤ከአቢሲኒያ የተመለሰውን የቤልጂየም አሳሽ ባሮን ዲ ጃርልስበርግ ቃለመጠይቅ በማድረግ የተጠናቀረ እንደሆነ ኒውዮርክ ታይምስ ይገልፃል፡፡ የሚታወቁትን ታሪኮች እየዘለልኩ “ጮማ ጮማ” የሆኑትን መረጃዎች ነው የማቀብላችሁ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል ከመዘጋቱ በፊት በዚህ በአዲሱ የአፄ ምኒልክ ታሪክ ላይ ትንሽ ጥናትና ምርምር ቢያካሂድ ትክክለኛው ታሪክ (ያልተጭበረበረው ማለቴ ነው!) ለትውልድ ይሸጋገራል የሚል እምነት አለኝ፡፡ “የለም! የአፄ ምኒልክን ጉዳይ አጥንቼ ፋይሉን ዘግቻለሁ” የሚል ከሆነም እንዳሻው፡፡ የኒውዮርክ ታይምስ መረጃ ግን የሚያወላዳ ዓይነት አደለም፡፡ ለመሆኑ እኚህ የጥቁር ህዝብ ኩራት፣የአድዋ ጀግና—–አዳዲስ ገድሎች ምን ይሆኑ? (የተጭበረበርነው ታሪክ ማለት ነው!)
ባሮን ዲ ጃርልስበርግ ለጋዜጣው እንደተናገረው፤ ምኒልክ ከሌሎች የአህጉሪቱ ነገስታት ጨርሶ የተለዩ መሪ ነበሩ፡፡ በዲፕሎማትነት፣ በኢንቨስተርነት (ፋይናንሰር)፣ በተዋጊነት የሚስተካከላቸው አልነበረም፡፡ በተዋጊነትና በዲፕሎማትነት ያላቸውን ብቃትና ዋጋ ያስመሰከሩት ጣልያን በአቢሲኒያዎች ድል በተነሳች ወቅት ነበር ይላል – ጃርልስበርግ። በመጨረሻዎቹ የንግስና ዘመናቸው ግን ምኒልክ ይበልጥ በኢንቨስትመንት እንቅስቃሴያቸው እንደታወቁ ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል፡፡
የንግስና ዘውድ ከመድፋታቸው ቀደም ብሎ በወጣትነት ዘመናቸው የኢንቨስትመንት ዝንባሌ እንደነበራቸው የሚያስታውሰው ዘገባው፤በዚያ እድሜያቸው በፈረንሳይና ቤልጂየም የማዕድን ማምረቻዎች ውስጥ ቀላል የማይባል መዋዕለ ንዋይ አፍስሰው ነበር ይለናል፡፡ ከንግስናቸው በኋላ ግን አገር በማስተዳደር ሥራ በመወጠራቸው ከኢንቨስትመንቱ ተስተጓጉለው እንደነበር የኒውዮርክ ታይምስ ዘገባ ያመለክታል፡፡
“ዛሬ የአቢሲኒያው ገዢ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴያቸውን ወደ ዩናይትድ ስቴትስ በማስፋፋት በአሜሪካ የባቡር ሃዲድ ሥራ ላይ ከፍተኛ የአክስዮን ድርሻ አላቸው” ሲል አሳሹ የንጉሱን ወቅታዊ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ገልጿል፡፡
አፄ ምኒልክ በአሜሪካ እንዲሁም በፈረንሳይና ቤልጂየም ያላቸው አክስዮንና ኢንቨስትመንት ሲደማመር ከ25 ሚሊዮን ዶላር የማያንስ የግል ሃብት እንደነበራቸው ይገመታል ብሏል- አሳሹን ጠቅሶ የዘገበው ጋዜጣው፡፡
“እኚህን ጥቁር የአቢሲኒያ ገዢ በተመለከተ በእጅጉ የሚያስደንቀው ጉዳይ ሁለ-ገብነታቸው ነው” ሲል የሚያደንቀው የቤልጂየሙ አሳሽ፤ንጉሱ የተዋጣላቸው ቋንቋ አዋቂ ነበሩ ይላል – ፈረንሳይኛ፣ እንግሊዝኛና ጣልያንኛ አቀላጥፈው ይናገሩ እንደነበር በመጥቀስ፡፡ ሁለመናቸውን ለአገራዊ ጉዳዮች ለመስጠት ቢገደዱም አዲስ የወጡ የአውሮፓ የስነጽሑፍ ስራዎችን ለመቃኘት ግን ጊዜ አያጡም የሚለው ጃርልስበርግ፤ ብዙ ጊዜ አዲስ የአውሮፓ ደራሲ ስም ሲጠቀስ እምብዛም አይደናገራቸውም ነበር ብሏል፡፡
እሳቸውን ከሁሉም በላይ የሚያኮራቸው ራሳቸው ባሰባሰቧቸው 10ሺ መፃሕፍት የተደራጀው ቤተመፅሃፋቸው ሲሆን መፃህፍትን በተመለከተ ዋነኛ ትኩረታቸው በአፍሪካና በእስያ ጥንታዊ ስልጣኔዎች ላይ የሚያጠነጥኑ ሥራዎች ነበሩ ይላል – ለኒውዮርክ ታይምስ ምስክርነቱን የሰጠው ባሮን ዲ ጃርልስበርግ፡፡ ለካስ ምኒልክ ወደው አይደለም– ትምህርት፣ ቴክኖሎጂ፣ ሥልጣኔ፣ ዘመናዊ አስተዳደር ወዘተ—-ሲሉ የኖሩት፡፡ (የንጉሱን ታሪክ ተጭበርብረናል!?)

addis admass amharic newspaper

ምንሊክ ሳልሳዊ:- ሃገራችን ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢና አስጊ ስለሆነ ሕወሓት መራሹ ገዥው ፓርቲና አማካሪዎቹ ባለስልጣኖቹ ችግሩን ዓይተው መፍትሔ ካላስቀመጡ፣ አገርንና ሕዝብን በማስቀደምና በማሳተፍ ካልተንቀሳቀሱ አደጋ አለ፡፡ ያልታሰበና ያልተጠበቀ ግጭትና ችግር በአገራችን ውስጥ ብቅ ጥልቅ እያለ ነው::ኢትዮጵያ ደሃ አገር ናት ተብላ ትጠቀሳለች እንጂ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮች ተከፋፈሉ ተጣሉ፣ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ተከፋፈሉ ተጋጩ፣ የእስልምናና የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ተባሉ፣ ወዘተ የሚል አንሰማም ነበር፡፡

አሁን በዘመን ወያኔ በመስጊድም በቤተክርስቲያንም አካባቢ ይህን እየሰማን ነው፡፡ የህዝብን አንድነት ለመናድ የሚፈልገው ገዢው ኢህኣዴግ በሃይማኖቶች መካከል ግጭት እና መተራመስን ለመፍጠር ፕሮፓጋንዳውን በስፋት እየነዛ ይገኛል::በምእራብ ኢትዮጵያ ያልተሳካውን በምስራቅ ኢትዮጵያ ለመድገም አዲስ ዘመቻ ተጀምሯል::ይህ መንግስታዊ ሽብር አደጋ አለው::ድሮ እንዲህ ዓይነት ችግር ሲፈጠር ለማስታረቅ ሩጫ ነበር፡፡ አሁን ለማባባስ የሚሯሯጥ ወያኔያዊ ኃይል እንዳለም በግልጽ እየታየ ነው፡፡ መፍትሔ ከማስገኘት ይልቅ የበለጠ ብጥብጥ እንዲከሰት የመንግስታዊ አካላት ስውር እጆች ግፊት እየበዛ ነው፡፡

የኑሮ ውድነት በህዝቡ ላይ ተደራርቦ ከጭነት ልክ በላይ እየሆነ ነው፡፡ ብር እየመነመነችና እየከሳች በመሞት በየቀኑ የቀብሯ ጥሩንባ እንደተነፋ ነው፡፡ የሃገራሽን ገንዝብ ብር በራሷ ግሽበቱ ተሽኖባት አትክልትና ፍራፍሬን ፣ ስንዴና ጤፍን፣ ትራንስፖርትና ልብስን፣ የላስኪት ቤትን እና የቤት ኪራይን፣ የተማሪውን ደብተርና ስክሪፕቶን መጋፈጥ ተስኗታል፡፡ የኑሮ ውድነት የሚያስከትለው የወንጀል ድርጊት አለ፡፡ ኑሮ ውድነቱ ወንጀልን ወልዷል::ሴቶች እህቶቻችን እድሜ እና የስራ ሁኔታ ሳይለይ ስጋቸው በመሸጥ ስራ ላይ ሲሰማሪ ከተማሪ እስከ ባለትዳር ከሕጻናት እስከ አዛውንት የሚያቀርቡ የወሲብ ደላሎች በሃገሪቱ ከትመዋል::ይህም ዋነኛ አደጋ ነው::

ለፖለቲካው እና ለስልጣኑ አትኩሮት የሚሰጠው ኢህኣዴግ ተቋማትን በሚገባ አለመገንባቱና ሥርዓቱን በሁሉም ዘርፍና መስክ አለመሞከሩን ብዙ ቀዳዳዎችን እንዲፈጠሩ ከማድረጉም በላይ፣ ለችግርና ለአደጋ የሚዳርግ ሁኔታ መኖሩ በገሃድ እየተስተዋለ ነው፡፡ የሃገሪቱ የተፈጥሮ ሃብት በስራ ላይ ሊውል ነው ከሚለው ዘገባ ጀምሮ እስከ ማዕድን በመገኘቱ ሀብት ተፈጠረ ብለን በሰማን ማግስት ፖታሽና ወርቅ ፍለጋው ዩራኒየም ፍተሻው ተቋረጠ:ነዳጅ የሚፈልግ ኩባንያ ሥራ እንዲያቆም ተደረገ መባሉን ስንሰማ ያሳስበናል፡፡ ሃገሪቱ ወደ አደጋ ውስጥ ሰተት ብላ መግባቷን እና እንደማትወጣውም ይጠቁመናል::

ወያኔ በፖለቲካ ታማኝነት ያደራጃቸው እውቀት እና ልምድ የሌላቸው በሙስና እና በዝምድና የተሳሰሩ አትኮሮታቸው በሰው አገር ንብረት እና ገንዘብ ማከማቸት በሆኑ ባለስልታናት የተዋቀሩ መሥርያ ቤቶች ሲልፈሰፍሱና ውሳኔ መስጠት ሲያቅታቸው ማየቱም ወዴት እየሄድን ነው የሚያሰኝ ሆኗል፡፡ ይህም ከባድ እና እስካሁን ሊፈታ ያልቻለ አደጋ ነው::

በዳያስፖራው ያለው ዘረኝነት፣ ጐሰኝነት፣ መከፋፈል፣ መራራቅ፣ ሃይማኖትን መጠቀሚያ ማድረግ፣ ከጠላት ጋር ወግኖ መሟገት፣ አገርንና የአገርን ክብር አሳልፎ መስጠትና ፖለቲካን ቢዝነስ በማድረግ ለአትራፊነት መወራጨት፣ አስፈሪ የሆነ አቋምና እንቅስቃሴ ማድረግ አሳሳቢ ነው፡፡ይህም እንዲፈጠር ከባድ ሚና የሚጫወተው ከሃገር ቤት የሚራመደው አሳዛኝ የፖለቲካ ፖሊሲ ሲሆን እንዲሁም ወያኔ እያሰለጠነ የሚያሰማራቸው የበግ ለምድ የለበሱ ቀበሮዎች የሚረጩት መርዝ ነው ይህም ሌላኛው በሃገር ላይ የተደቀና አደጋ ነው::

አንድነታችንን የሚፈታተኑ የጠባብ ጐሰኝነትና አካባቢያዊ ስሜት የተላበሱ አስተሳሰቦች እዚህም እዚያም ሲሰሙና በቦታው መሟሟቂያ ሲሆኑ ማስተዋልም የተለመደ ሆኗል፡፡ የረዥም ዘመናት አንድነት ያለውን በፍር የተሞላውን በማህበርዊ እሴቱ እና ጉዞው አለም ያደነቀውን ኢትዮጵያዊነት የሚሸረሽሩ መንግስታዊ የማፊያ እጆች ሕዝብን በማፈናቀል እና ጎሰኝነትን እና ስልጣንን የማስረዘሚያ ስልት በማድረግ ከህዝብ አናት ላይ የሚሸኑ ትናንሽ የመንደር መንግስታት እንዲፈጠሩ በማድረግ የአብሮነት ፍቅርን እና አንድነትን በማደፍረስ በስፋት እየሰሩ ነው::ይህ ደግሞ እያየነው ያለነውን ከባድ አደጋ በሃገሪቱ ላይ እንዲሰራፋ አድርጓል::

እደግመዋለሁ::ሃገራችን ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢና አስጊ ስለሆነ ሕወሓት መራሹ ገዥው ፓርቲና አማካሪዎቹ እና ባለስልታኖቹ ችግሩን ዓይተው መፍትሔ ካላስቀመጡ፣ አገርንና ሕዝብን በማስቀደምና በማሳተፍ ካልተንቀሳቀሱ አደጋ አለ፡፡ ሃገራችን እና ህዝቧ ሊወጡበት የማይችሉት ከባድ አደጋ ከፊታችን መደቀኑን ልብ ብለን በአንድነት እና በጋራ ከላይ የተቀመጡትን አደገኛ ሽብሮች የፈጠረውን በስልታን ላይ ያለውን መንግስት በአንድነት በመታገል ወደ ከርሰ መቃብሩ ከተን ዳግም እንዳያንሰራራ ማድረግ የኢያንዳንዳችን የዜግነት ግዴታ ነው::

በሕወሓት/ኢሕአደግም ይሁን በተቃዋሚዎች በረት እና ማደሪያ …….
እየከፋ ያለን ጉዳይ እየተሻሻለ ነው ማለት = እያወቁ ማለቅ ……. ‪

= ሥልጣንህን አድን = ኢሕአደጋዊ አጀንዳ ወደ = አገርህን አድን = ሕዝባዊ አጀንዳ ይቀልበስ።
እየተሻለኝ ነው እያለ ከሚሞት፣ በጣም ጥሩ ምልክት ነው እያለ ከሚገድል ያድነን ፡፡ ደግ ደጉን ማውራት የተሻለ ዓለም ለማየት ይጠቅማል የሚለው ብሂል እንደተጠበቀ ሆኖ፤ እየከፋ ያለን ጉዳይ እየተሻሻለ ነው ማለት ግን እያወቁ ማለቅ ዓይነት ነው፡፡

ምንሊክ ሳልሳዊ ዕውነቱን ተናግሮ የመሸበት ማደር ለአገርና ህዝብ ይበጃል እንጂ ጐጂ አይደም፡፡ የማይሰጋ ተስፋ የሌለው ሰው ነው ፡፡ አይመጣምን ትተሽ ይመጣልን ጨምሪበት” የሚሉት ዓይነት::
በየኑሮ መስኩ ያለውን ህመም፣ በየሙያ መስኩ ያለውን ተወሳክ፣ በየፖለቲካ መስኩ ያለውን ወረርሽኝ በጊዜ መመርመር ዋና ነገር ነው፡፡ እኛ የወደድነውን እያጐላን በየሚዲያው ብንለፍፍ ለሀገርና ለህዝብ ፋይዳ አይኖርም።

ለምርጫ እወዳደራለሁ የሚል ፓርቲም ይሁን ፕሮፓጋንዳ የሚረጭ ሚዲያ ፍትሐዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕዝባዊ ሥርዓት ለመገንባትና በዚህ መንገድ ለመምራት ከፈለገ፣ ሕዝብን ማክበርና ማዳመጥ ጥበብ መሆኑን፣ አማራጭና ተለዋጭ የሌለው መርህ መሆኑን ለመግለጽና አፅንኦት ለመስጠት ነው፡፡
የሕዝብን ብሶት ማዳመጥና ለሕዝብ ከበሬታ የመስጠት ጉዳይ ጥበብ መሆን ብቻ ሳይሆን፣ ጊዜ የማይሰጥና በእጅጉ አንገብጋቢ ሕዝብ አድን እና አገር አድን አጀንዳ እየሆነ ነው፡፡ሥልጣንህን አድን ከሚለው ኢሕአደጋዊ አጀንዳ በላይ፡፡

በኢትዮጵያችንም እንደዚሁ ሕዝብን የማክበርና የማዳመጥ ጉዳይ ተገቢና አስፈላጊ ተብሎ ብቻ የሚታለፍ ሳይሆን፣ አንገብጋቢ ሆኖ የተግባር ያለህ እያለ በመጮህ ላይ ያለ አጀንዳ ነው፡፡ ላለው ችግር ብቸኛው ፍቱን መድኃኒትና ጥበብ ሕዝቡን ማክበርና ማዳመጥ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ እየጠየቀ ነው፡፡ አቤት እያለ ነው፡፡ እየጮኸ ነው፡፡ ጥያቄው ማነው ሕዝቡን እያከበረና እያዳመጠ ያለው ? የሚል ነው፡፡ ምንሊክ ሳልሳዊ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

በአገራችን ኢትዮጵያ ሁሉም መብቶች ያለምንም ገደብ የሚከበሩበትን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ላለፉት ዓመታት በርካታ መስዋዕትነቶች ተከፍለዋል፡፡ ዜጎች የመደራጀትና ሀሳባቸውን የመግለጽ ህገ-መንግሥታዊ መብት እንዳላቸው ጧት ማታ በመንግሥት ብዙሀን መገናኛዎች ቢለፈፍም፤ ሁሉም ነገር የይምሰልና የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ስልት እንደሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልፅ ነው፡፡

ከሕግ በላይ የሆነ አገዛዝ ባለበት አገር በየስፍራውና በየክልሉ የሚገኙ ካድሬዎችና የስርዓቱ ባለሟሎች እራሳቸውን ከህግ በላይ አድርገው ቢቆጥሩ የሚገርም አይደለም፡፡ በዚሁም ምክንያት በገዢው ፓርቲ ተቋማት፣ ኃላፊዎችና ባለስልጣናት የሚፈፀመው ኢ-ሰብአዊና ኢ-ዴሞክራሲያዊ ድርጊቶች እጅግ እየከፋ መጥቷል፡፡

ባሳለፍነው ሳምንት በፓርቲያችን በአንድነት የተሰጣቸውን የተለያዩ ተልዕኮዎችን ለለማስፈፀም ወደ ደቡብ ክልል በተንቀሳቀሱት የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራና ም/ኃላፊው አቶ ዳንኤል ሽበሺ ላይ እና ከ32 በሚበልጡ የወላይታ ዞን አመራሮች ላይ መጋቢት 13 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም መንግስታዊ ውንብድና ተፈፅሞባቸዋል፡፡ በወላይታ ዞን ፖሊስ አዛዥ ሻለቃ ላሊሼ ኦሌ የሚመሩና የደህንነት ሰዎችን ጨምሮ ከ8-1ዐ የሚሆኑ መንግስታዊ ወሮበሎች የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን ምክር ቤት አባላት የተሰበሰቡበትን ግቢ በሀይል ሰብረው በመግባት የፓርቲ ሰነዶችን፣ ሁለት ሳምሰንግ ጋላክሲ ስልኮችን ጨምር በድምሩ ከ2ዐ የሚበልጡ የሞባይል ስልኮችን ዘርፈው ሄደዋል፡፡

ወሮበሎቹ ታርጋ የሌላቸው ሞተር ሳይክሎችን በመጠቀም አመራሮቻችንን ወደ ፖሊስ ጣቢያ አስገድደው ወስደዋል፡፡ ከፓርቲያችን አመራሮቻችን የተነጠቁ ስልኮች በዞኑ ፖሊስ አዛዥ ቢሮ ውስጥ ፈሳሽ ውስጥ በመጨመር ከጥቅም ውጭ በማድረግ ሁለቱ ከፍተኛ አመራሮችና የዞኑን ም/ቤት አመራሮች ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳይኖራቸው አድርገዋል፡፡ አመራሮቹን አፀያፊ በሆነ ማጎሪያ ውስጥ ከቀኑ 5፡00 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 6፡30 አስረው ማደሪያ ሊያገኙ በማይችሉበት ሰዓት ለቀዋዋቸዋል፡፡ ይህ አይነቱ ከመንግስታዊ አካል የማይጠበቅ ውንብድና በሚሊዮኖች ድምጽ የመጀመሪያው እንቅስቃሴ ወቅት ሐምሌ 5 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም በዚሁ ዞን ተፈፅሞ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ በወቅቱ የጠራነውን ሕዝባዊ ስብሰባ ለማደናቀፍ ታርጋ የሌላቸውን ሞተር ሳይክሎች በመጠቀም በቅስቀሳ ላይ የነበሩ አባላትን በመደብደብና በመዝረፍ እንዲሁም የተከራየነውን አዳራሽ ጥበቃዎች ዘግተው እንዲሄዱ ከመደረጉም ባሻገር ከግለሰብ የተከራየነውን ሞንታርቮ ዘርፈው እስከ ዛሬም አልመለሱም፡፡

ምንም እንኳ የአንድነት ከፍተኛ አመራርና አባላት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መስፈን በሚካሄደው ትግል ውስጥ መንገላታት፣ መደብደብ፣ መታሰርና ሞትም ካለ አይናቸውን ሳይጨፍኑ አፍጠው ለመቀበል ዝግጁ ቢሆኑም ይህን አሳፋሪ ድርጊት በቸልታ የማንመለከተውና አስፈላጊውን ነገሮች አጣርተን ተገቢውን ፖለቲካዊና ሕጋዊ እርምጃ የምንወስድበት ጉዳይ መሆኑን መግለጽ እንወዳለን፡፡

ሕገ መንግሥቱ ላይ የሠፈረውን የመደራጀት መብትና እና በተሻሻለው በፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2ዐዐዐ አንቀጽ 46 ንዑስ አንቀጽ‹2› የፖለቲካ ፓርቲዎች የዕለት ከዕለት ተግባሮችን ስር ፤ የሕዝቡን ፖለቲካዊ ግንዛቤ ማዳበር፣ የፓርቲውን ዓላማ ለሕዝቡ ማስረጽ፤ ዜጎች በአገሪቱ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው መቀስቀስ፣ በሕዝቡና በመንግሥት ተቋማት መካከል ግንኙነት እንዲጠናከር ማድረግ የሚሉ ግልጽ ድንጋጌዎች ሰፍረዋል፡፡ በአንፃሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከገዛ አባሎቻቸው ጋር በማንኛውም ጊዜ መሰብሰብ እንደሚችሉ እየታወቀ በመንግስትና በገዢው ፓርቲ የሚፈፀሙ ሕገ ወጥ ተግባሮች በየእለቱ ተጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ ሕግ ማክበርም ማስከበርም ያልቻለው ኢህአዴግ ሠላማዊ ትግሉን የሚደፈጥጡ ድርጊቶች ፈፃሚና አስፈፃሚ ካድሬዎች እና ሕገ አስከባሪ የተባለው የወላይታ ዞን ፖሊስ አዛዥ አይነት ግለሰቦችን በማበረታታት ሕጋዊና ሠላማዊ ትግሉን ወደ ጠርዝ እየገፋ ይገኛል፡፡

በዚህ አጋጣሚ ለፓርቲያችን ከፍተኛ አመራሮችና ለወላይታ ዞን የወረዳ አመራሮችና አባላት ያለንን ክብር እየገለፅን፣ በወላይታ ሶዶ በአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና የፓርቲያችን የዞኑ ምክር ቤት አባላት ላይ የተፈፀመው መንግስታዊ ውንብድና ስርአቱ የወረደበትን የዝቅጠት ደረጃ አመላካች እንደሆነ ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

ድል የሕዝብ ነው!
መጋቢት 16 ቀን 2ዐዐ6 ዓም
አዲስ አበባ

ሸዋ በር እና አከባቢው ስጋት ነጋደው ጭንቀት እንዳጠላበት ነው።”…አዘናግቶ ሊያጋየን ነው::”
የእሳት ማጥፊያ አዘጋጁ እሳት ሊነሳ ይችላል የሚለውን ወያኔያዊ ሽብር በነጋዴዎች ዘንድ ጥርጣሬ አጭሯል::

ምንሊክ ሳልሳዊ:-በሃረር ለረዥም ጊዜ ታፍኖ የቆየው ብሶት ባለፈው ሰሞን የተነሳውን የእሳት ቃጠሎ ተከትሎ ሕዝቡ አደባባይ እስከመውጣት ደርሶ ነበር::የወያኔው መንግስት ካለፉት አመታቶች ጀምሮ በተለያየ ጊዜ የሃረር ነጋዴዎችን መደብሮች ሲያቃጥል እንደ ዋናው ምክንያት ተደርጎ የተወሰደው አከባቢው ለልማት ስለሚፈለግ ከቦታው ተነሱ የሚለው የቅድመ ማስጠንቀቂያ ነጋዴዎቹ በምትኩ ቦታ ይሰጠን የሚሉትን አስታኮ የሚመጣ ቃጠሎ መሆኑ እና ከቃጠሎ በፊት ወደ መደብሮች መጋዘን የሚገቡ ነዳጅ የተሞሉ ጀሪካኖች ሕዝቡ ጣቶቹን በወያኔ ላይ እንዲጠቁም አድርጎታል::

ወያኔ የሃረር ህዝብ ላይ ያደረሰውን ሰቆቃ እና በደል ለመሸፈን ሰላማዊ ሰልፍ በመጥራት ነገሮችን በሙሉ አሸባሪ ብሎ በሚጠራቸው በመላከክ ህዝቡን ለመሸወድ ቢሞክርም አልተሳካለትም:: በየመንገዱ ቢያፍስ ቢያባርር ቢደበድብ ቢያስር ስብሰባ ቢጠራ ያልተሳካለት ወያኔ ከዚህ በመቀጠል ምን ሊያመጣ እንደሚችል እስካሁን የታወቀ ነገር የለም:: ምናልባት ይላሉ የሸዋ በር እና አከባቢው ነጋዴዎች ስጋታችንን እና ጭንቀታችን መደብሮቻችንን እንዳያቃጥልብን ነው ሲሉ ሃሳባቸውን አካፍለውናል::

በውሃ እጥረት እና በሌሎች የአገልግሎት አቅርቦት የምትታመሰው ሃረር በሕወሓት ሰራሾች ደባ እየተደረገባት ያለው የሰብኣዊ መብት ገፈፋ እና በደል እየጨመረ እንዲ እየቀነሰ አለመሆኑ የሰሞኑ ምስክር ሂደት ምስክር ነው::በዚህ ሰሞን ከክልሉ ምክር ቤት እስከ ቀበሌ ካድሬዎች ስብሰባ ከሕዝቡ እስከ ነጋዴው ቢሰበሰብም በሰብሳቢዎች እና በተሰብሳቢው ሕዝብ መካከል አለመተማመን እንደነገሰ ተበትኗል:: በትላንትናው እለት በሸዋ በር አከባቢ ጀጎል ግንቡን አስታኮ ያሉ ባለመደብሮች ስብሰባ ተጠርተው እንዲሁም የእህል እና የቅመማ ቅመም ነጋዴዎች በስብሰባው ተጋብዘው የተገኙ እና በተሰብሳቢው እና በሰብሳቢዎች ሕወሓት ሰራሽ የከተማው ባለስልታናት መካከል ስጋት እና ሽንቀት ወጥሮት የተካሄደ እንደነበር ነጋዴዎቹ ጠቁመዋል::

የሸዋ በር አከባቢ ነጋዴዎች ባለፈው በመብራት ሃይል እና በሲጃራ ተራ አከባቢ የደረሰውን የእሳት ቃጠሎ ከተመለከቱ በኋላ ነግ በኔን በማሰብ ንብረታቸውን ከአከባቢው በማሸሽ ስጋታቸውን በተግባር ለወያኔ ሰራሽ አካላቱ ያሳዩ ሲሆን ይህንን የተመለከተው መንግስታዊ አካል ነኝ ያለ ክፍል ነጋዴው እቃውን ከማውጣት ከመንግስት ጋር በጠረጰዛ ዙሪያ እንሰብሰብ እቃችሁን አታሽሹ ቢልም ነጋዴዎቹ አዘናግቶ ሊያጋየን ነው በሚል እቃቸውን ወደቤታቸው ጭነው ወስደዋል::

ንብረታችን ቤታችን እንዳለ ስብሰባ እንቀመጣለን ብለው የቆረጡት ነጋዴዎች በተጠሩበት ስብሰባ በመሄድ ዋና ዋና የተባሉ ነጥቦችን አንስተዋል::ከተነሱት ነጥቦች በእሁድ ቀን ማንም ሰው በገበያ ቦታዎች ውስጥ መገኘት እንደማይኖርበት;እሁድ ቀን ጠቅላላ መደብሮች ዝግ መሆን እንዳለባቸው:የዘበኞች ቁጥር መጨመር እንዳለበት:ወዛደሮች መታወቂያ እና ባጅ ሊኖረው እንደሚገባ እና መቆጣጠር አስፈላጊ መሆኑን:በንግዱ አከባቢ ዳር ዳሩን የመኪና መንገድ ላይ ያሉ በረንዳዎች እና መደቦች መጽዳት እንዳለበት በገበያ ውስጥ እሳት ማጥፊያዎች እና የውሃ ታንከሮች እንዲዘጋጁ ተወያይተውባቸዋል:; በዚህም መሰረት ነጋዴዎቹ የመተማመን መንፈስ ባይታይባቸውም ወኪሎቻቸውን መርጠው ስራውን ሊሰሩ የተስማሙ ሲሆን እስከዛሬ ያልታሰበ የእሳት ማጥፊያ እና የውሃ ታንከር አዘጋጁ እሳት ሊነሳ ይችላል የሚለውን ወያኔያዊ ሽብር በጥርጣሬ ተመልክተውታል::ምንሊክ ሳልሳዊ

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከታች በአስተያየት መስጫ ውስጥ የምትመለከቱት ምስል ከሶስት አመት በፊት ቦታው ለኢንቨስትመት ይፈለጋል ተነሱ የተባሉ ነጋዴዎች ምትክ ቦታ ይሰጠን እያሉ ሲከራከሩ የወያነ ሰራሽ የክልሉ ባለስልጣናት በድንገት የነጋዴዎችን መደብሮች ያቃተሉት ቦታ ሲሆን ይህ ቦታ ወደ መብራት ሃይል ሂደው ባለፈው ሱቆቻቸው የተቃተሉባቸው ነጋዴዎች ቦታ የነበረ ነው:: መንግስታዊ እሳት እየተከተለን ነው የሚሉ የመብራት ሃይል መደብር ባለቤቶች እና ተጎጂዎች ከ3 አመት በፊት የተቃጠለባቸው ቦታ ሕንጻ ለማሰራት ለአንድ ኢንቨስተር ተሰቶት ጥናት ተካሂዶ ቦታው ለኮንስትራክሽን አመቺ እንዳልሆነ እና አከባቢው ውሃ የሞላበት እና ሕንሳ ሊያሰራ የማይችል አፈሩም ለሕንሳ ግንባታ ተስማሚ እንዳልሆነ ይህ ቦታ ላይ ህንጻ ለማስገንባት ከፍተኛ ወጪ እና ዲዛይን የሚጠይቅ በመሆኑ ቦታው በዚህ ምክንያታዊ ጉዳዮች ለ3 አመት ያህል በምስሉ እንደምታዮት ታጥሮ የነበረ ሲሆን በአሁን ሰአት የተቃጠለው የሲጃራ ተራ እና የመብራት ሃይል ከቃጠሎ የተረፉ ቆርቆሮዎች እና ሌሎች ማቴሪያሎች መከመሪያ እየሆነ ነው::ምንሊክ ሳልሳዊ

Image

Image

Image

Image

March 24, 2014 08:11

ለግልጽነትና ለተጠያቂነት ብሎም ለህዝቦች ጥቅም ቅድሚያ እንደሚሰጥ ህግ ደንግጎ የተቋቋመው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ ያቀረበውን የይግባኝ ማመልከቻ ተቀብሎ ማጽደቁ አነጋጋሪ ሆኗል። በ2009 ኢህአዴግን “ያወጣሁትን መስፈርት አታሟላም” በማለት እውቅና የከለከለው ይህ ተቋም፣ ኢህአዴግ በሚከሰስባቸው ዋና ጉዳዮች ለውጥ ሳያደርግ የራሱን ውሳኔ የገለበጠበት አካሄድ እየተመረመረ እንደሆነ የጎልጉል ምንጮች ጠቁመዋል።

የኢህአዴግን የእውቅና ይግባኝ ጥያቄ ተቀብሎ ያጸደቀው የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) የሚባለው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ነው። ተቋሙ ኢህአዴግ በ2009 አቅርቦት የነበረውን የእውቅና ጥያቄ ውድቅ ሲያደርግ የሰጠው ምክንያት “የመያዶች ህግ የተሰኘው” አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆንና በአገሪቱ የተተከሉት አፋኝ ህጎች እስካልተወገዱ ድረስ ማመልከቻው እንደማይታይ በማሳወቅ ነበር።

በ2009 ጠ/ሚኒስትር የነበሩት አቶ መለስ “መሰዋት” በስተቀር ኢህአዴግ አንዳችም ለውጥ ባላደረገበት ሁኔታ ባለፈው ረቡዕ መጋቢት 19፤2006 (March 19፤2014) ይኸው እውቅና ሰጪ ተቋም የራሱን ውሳኔ ቀልብሶ ለኢህአዴግ እውቅና መስጠቱ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። ከውሳኔው ቀናት በፊት በጓሮ የሚወጠን ድርጊት እንዳለ መረጃ ደርሶት የማሳሰቢያ ተቃውሞ ያሰራጨው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘውየሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት እንዳለው ከሆነ ከተገለበጠው ውሳኔ በስተጀርባ ሚስ ክሌር ሾርት ከፊት ረድፍ ተቀምጠዋል።

ማመልከቻው እንደገና እንዲታይና የቦርዱ የቀድሞ ውሳኔ እንዲገለብጥ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙት የቀድሞ የእንግሊዝ ዓለምአቀፍ ትብብር ሚ/ር የሆኑት ክሌር ሾርት መሆናቸውን የድርጅቱ መግለጫው ይፋ አድርጓል። እኚህ ግለሰብ የአፍሪካ አምባገነኖችን በመደገፍ የሚታወቁ ሲሆን ይህ ከጥቅማቸው ጋር የተሳሰረው ግንኙነታቸው አሁንም ኢህአዴግን እንዲደግፉ እንዳደረጋቸው ይነገራል፡፡ እንዲሁም በሌሎች ኢህአዴግ ባቋቋማቸው ዓለምአቀፋዊነት ሽፋን በተላበሱ ድርጅቶች ውስጥ የአመራር አባል በመሆን ሚስ ሾርት እንደሚያገለግሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ የእንግሊዝ ፓርላማ አባል በነበሩበት ወቅትም ያላወጡትን ወጪ አውጥቻለሁ በማለት በብዙ ሺዎች የሚገመት ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉ መሆናቸው በወቅቱ ዴይሊ ቴሌግራፍ ባወጣው መረጃ አጋልጦ ነበር፡፡ የተወሰነውን ገንዘብ የመለሱ ቢሆንም ጋዜጣው በወቅቱ ያወጣው መረጃ ግለሰቧ የሕዝብን ገንዘብ ለግል ጥቅማቸው የተጠቀሙ “ሙሰኛ” መሆናቸውን ያስረዳል፡፡

ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው እንደሚሉት ከሆነ ባለፈው ረቡዕ ኦስሎ፤ ኖርዌይ ላይ ውሳኔው በተላለፈበት ወቅት ሚስ ሾርት በግልጽ የኢህአዴግ ደጋፊ በመሆን ተጽዕኖ በማድረግ ወደ ውሳኔ እንዲደረስ ግፊት አድርገዋል፡፡ ግለሰቧ ባላቸው ኃላፊነት በመጠቀም (የEITI የቦርድ ኃላፊ ናቸው) እንዲህ ዓይነቱ ግልጽና ወገናዊነት የታየበት ድጋፍ በማድረግ ከድርጅቱ አሠራር ውጪ ውሳኔ እንዲሰጥ ማድረጋቸው ለወደፊት በሚቀርቡ ማመልከቻዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የአሠራር ችግር እንደሚያስከትል ካሁኑ እየተጠቆመ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ከማዕድን ኢንቨስትመንት ጋር በተያያዘ ማህበራዊ ቀውስ የደረሰባቸው አካባቢዎች እንዳሉ የሚታወቅ ነው። በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱት አካባቢዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ባልጸዳ የሽያጭ ሂደት ሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲ የገዙት ሻኪሶ የወርቅ ማዕድን በህዝብ ላይ እያደረሰ ችግር የሚዘገንን ነው። በየጊዜው ግልጽ ባልሆነ የማስፋፊያ ውል የሚፈናቀሉና ከፋብሪካው በሚወጣው ዝቃጭ ለከፍተኛ ብክለት የተጋለጡ ዜጎች ድምጻቸውን ሲያሰሙ መታሰራቸው፣ መገረፋቸው፣ ለይስሙላ በተቋቋሙ ፍርድ ቤቶች የተፈረደባቸው እንዳሉ ታዛቢዎች ያስታውሳሉ።

በጋምቤላ ኢንቨስትመንት ህዝብን እየበላ እንደሆነ የሚጠቁሙት ክፍሎች “ኢንቨስትመንት በከፍተኛ ደረጃ የሚደገፍና የሚበረታታ ተግባር ቢሆንም፣ ኢህአዴግ ፍትሃዊ በሆነ ደረጃ መጠቀም፣ ማስተዳደር፣ መምራትና ኢንቨስትመንቱን ህዝብ “የኔ” ብሎ በመቀበል እንክብካቤ እንዲያደርግ የሚያስችል ስርዓት አለማበጀቱን እንደ ዋንኛ ችግር ያነሳሉ። ኢህአዴግን ያዘጋጀው ህወሃት በራሱ ሰዎች አማካይነት ከውጪ ሰዎች ጋር እየተሻረከ ለህዝብ ጥቅም ሊውል የሚገባውን ሃብት ወደ ውስን ቋት እንደሚያግዝ የሚገልጹት እነዚሁ ክፍሎች” ይህ ዓለም የሚያውቀውን፣ ራሳቸው ህወሃቶችም የማይክዱትን እውነት ነው ብለዋል። ዜጎች የአገራቸው ሃብት ተጠቃሚ ከመሆን ይልቅ አካባቢያቸው ባደላቸው የተፈጥሮ ሃብት ሳቢያ መከራ ሲደርስባቸው፣ ሲሰቃዩ፣ ሲገረፉና፣ ሲገደሉ ማየት በተለመደባት ኢትዮጵያ ውስጥ ለኢህአዴግ የማይገባውን ካባ መደረብ ውሎ አድሮ የሚጋለጥ ክፉ ተግባር እንደሆነም አመልክተዋል።

አነስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙና ኢህአዴግ “ልማታዊ” የሚላቸው ኢንቨስተሮች ሳይሆኑ በከፍተኛ ደረጃ የሚመደብ መዋዕለ ንዋይ የሚያፈሱ ባለሃብቶች ኢንቨስት የሚያደርጉበትን አገር ለመምረጥ የመጀመሪያው መለያቸው የEITI ድረገጽ የአባል አገራት ዝርዝር እንደሆነ ስለ አሰራሩ የሚያውቁ ይናገራሉ። ኢህአዴግም አስፈላጊውን የምዝገባና የማመልከቻ መስፈርት በማሟላት የተቋሙን እውቅና የጠየቀው በድርጅቱ ድረገጽ ላይ ለመመዝገብ ነበር። የሁለት ጊዜ ሙከራው ቢከሽፋም በመጨረሻ ተሳክቶለታል። ስኬቱንና የስኬቱን መንገድ፣ በተለይም የዳይሬክተሯ ክሌር ሾርት ጉዳይና የተዘጋውን ፋይል በማንሳት ውሳኔው የተገለበጠበት አካሄድ ኦስሎ በሚገኘው ሃያ የቦርድ አባላት ባሉበት ተቋም ውስጥም ግራ ያጋባቸው እንዳሉ መረጃዎች አሉ።

ኢህአዴግ አጓድለሃል ተብሎ የሚከሰስባቸውን የዴሞክራሲ ግባቶችና የሰው ልጆች የተፈጥሮ መብቶች፣ አንዲሆም አፋኝ የተባሉትን ህጎች አጠናክሮ ተግባር ላይ ባዋለበት ሁኔታ፣ የዚሁ የአፈናው ሰለባዎች በተለያዩ ማጎሪያዎች ውስጥ ሆነው ድምጻቸውን በሚያስተጋቡበት ወቅት፣ EITI ከተቋቋመበት ዓላማና “መሰረቴ” ከሚለው የግልጽነትና ተጠያቂነት መርህ በተጻራሪ ግልጽነትና ተጠያቂነት በጎደለው መልኩ ለኢህአዴግ የደረበው ብሉኮ ጉዳይ እየተመረመረ አንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። ጉዳዩን የሚከታተሉ “ግልጽነትና ተጠያቂነት በኦስሎ ተፈረደባቸው” ሲሉ ምጸት ሰጥተዋል፤ የክሌር ሾርትንም አካሄድ በEITI የህወሃት/ኢህአዴግ ተወካይ በማለት ተችተዋል። ይህንኑ ጉዳይ እመልክቶ ከሳምንት በፊት ለሪፖርተር አጭር መልስ የሰጡት የማዕድን ሚኒስትሩ EITI ውሳኔውን ያነሳል የሚል ጥርጣሬ እንዳለባቸው የሚያሳብቅባቸው መልስ ሰጥተው እንደነበር ይታወሳል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ዳያስፖራው እንደሚገባው አለመንቀሳቀሱ እንደ ሽንፈትና አቅጣጫ መሳት እንደሚቆጠር ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ጠቁመዋል፡፡ ዳያስፖራው ከጥቃቅንና ስሜታዊ ጉዳዮች በማለፍ በከፍተኛና አገራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት የማድረግ አመለካከቱን ማስፋት እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡ አለበለዚያ ኢህአዴግ እንደዚህ ዓይነቱን አጋጣሚ በመጠቀም የራሱን ገጽታ በዓለምአቀፍ መድረኮች እየወለወለ በማቅረብ የሥልጣን ዘመኑን እንደሚያራዝም ጠቁመዋል፡፡

golgul
http://raheltakele.wordpress.com/2014/0 … %E1%89%A0/

መጭው ምርጫ ያሰጋው ወያኔ ሕዝቡን ለማደናበር እና ለማጭበርበር ሊረዳኝ ይችላል ያለውን አዲስ የልማታዊ ዲሞክራሲ ሰነድ እያዘጋጀ ሲሆን የባለራእዩ የሚሉት የመለስ ዜናዊ ትራንስፎርሜሽን እቅድ በዝግታ ለማስቀረት እና ሕዝቡ አኩርፎበታል ያለውን የማንፌስቶ ሰነድ ለማዘጋጀት በአቶ በረከት የሚመራው ቡድን ስራውን መጀመሩ ታውቋል::

ተቃዋሚዎች ከፍተኛውን ድምጽ አግኝተው ከጨዋታ ውጪ ያደርጉኛል የሚል ስጋት ያደረበት ወያኔ በ1997 የተከሰተው አይነት ሽንፈት እንዳይደርስበት ከሰነዱ ዝግጅት ጎን ለጎን ስብሰባዎችን በማካሄድ ተቃዋሚዎች ከምርጫ የሚወጡበትን እና ምርጫውን የሚያጭበረብርበትን አዲስ ስልት እየነደፈ መሆኑንም ምንጮች አክለው ገልጸዋል::የህዝቡ ብሶት እንደበረታ ያወቀው ሕወሃት መራሹ መንግስት በጭንቀት እና በምእራባውያን ጫና ተወጥሮ እንደሚገኝ ይታወቃል::

የመለስ ዜናዊ የትራንስፎርሜሽን እቅድ በሃገሪቱ የአገልግሎት አቅርቦት ማጣትን:ሙስናን :ድህነትን:የዜጎች ስደትን :ስራ አጥነትን የኑሮ ውድነትን ወዘት ከማስፋፋቱም በተጨማሪ ምንም አይነት ውጠት እንዳልታየበት እና እስካሁን የተተገበረው የተጠበቀውን ያህል ባለመሆኑ ከፕሮፓጋንዳ ያለፈ ምንም የፈየደው ነገር እንዳሌለ ኢሕኣዴግ በራሱ ድርጅታዊ ጉባዬ እና ስብሰባዎች መናገር ከጀመረ ሰነባብቷል::ምንሊክ ሳልሳዊ

ዛሬ መጋቢት 14 ቀን ነው፡፡ የኢህአፓው መሪ ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ከደርግ ዋና ጽ/ቤት ለተላኩ ወታደሮች እጄን አልሰጥም ብሎ ከኪዳኔ በየነ ህንጻ (በድሮው አጠራር ፊሊፕስ ህንጻ) ላይ ራሱን ወርውሮ ህይወቱን ያጠፋው ልክ በዛሬዋ እለት በ1969 ዓ.ል. ነው፡፡ ኢህአፓዎች ተስፋዬ ደበሳይ ራሱን ያጠፋበትን ያንቺን ቅጽበት የቆራጥነትና የጽናት ተምሳሌት አድርገው ይዘክሯታል፡፡

Image

በእርግጥም ተስፋዬ ደበሳይ ቆራጥ ነበር፡፡ ላመነበት ዓላማ ሺዎችን አንቀሳቅሷል፡፡ ለጠላቶቹ ሳይንበረከክ ህይወቱን ሰውቷል፡፡ በርሱ ሞት ያዘኑት ኢህአፓዎች “ተስፋዬን ከምናጣ ሌሎች የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቶቻችን በሙሉ ቢጠፉ ይሻለን ነበር” በማለት መሪር ሐዘናቸውን አሰምተዋል፡፡ የደርግ መንግሥት እርሱ በሞተበት ዕለት ባወጣው መግለጫ አንድ ክፍለ ጦር ሰራዊት የተደመሰሰ ያህል ነበር የፎከረው፡፡
ተስፋዬ ደበሳይ ማን ነው? በኢህአፓ ውስጥ የነበረው ሚና ምን ይመስል ነበር?… ህይወቱ የተፈጸመው እንዴት ነው? እስቲ በጥቂቱ እንየው፡፡
*****
ኢሮብ በትግራይ ክፍለ ሀገር፣ [deleted] አውራጃ ውስጥ የምትገኝ ወረዳ ናት (በአሁኑ የአስተዳደር አወቃቀር በትግራይ ክልል፣ ምስራቃዊ ዞን ውስጥ ነው የምትገኘው)፡፡ በዚህች ወረዳ ከትግርኛ ተናጋሪው ብሄረ-ትግራይ በተጨማሪ ኢሮብ የሚባለው አነስተኛ ብሄረሰብ ይኖራል፡፡ ይህ ህዝብ በውስጡ ሶስት ዐይነት ማህበረሰቦች አሉት፡፡ አንደኛው ደመክኒቶ ይባላል፡፡ የዚህ ማህበረሰብ አባላት የካቶሊክ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ሁለተኛው ማህበረሰብ “ሀሳበላ” የሚባል ሲሆን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ይበዙበታል፡፡ ሶስተኛው ማህበረሰብ “ዳልገዳ” ይባላል፡፡ እነዚህኛዎቹ ደግሞ ሙስሊሞች ናቸው፡፡ እነዚህ ማህበረሰቦች የሚናገሩት ቋንቋ በኤርትራ ምድር ከሚነገረው የሳሆ ቋንቋ ጋር ተመሳሳይነት አለው፡፡ ሆኖም ኢሮብ እና ሳሆ በኢኮኖሚ ስምሪታቸው ይለያያሉ፡፡ የሳሆ ህዝብ ሙሉ በሙሉ አርብቶ አደር ነው፡፡ ኢሮቦች ግን በእርሻ ስራና በአነስተኛ ዕደ-ጥበባት ነው የሚተዳደሩት፡፡ የኢሮብ ወረዳ ተራራና ሸንተረር ይበዛዋል፡፡ በአካባቢው ካሉት ተራሮች መካከል “አሲምባ” እና “አይጋ” ትልልቆቹ ናቸው፡፡

በዚህች የኢሮብ ወረዳ ውስጥ አሊቴና የምትባል አነስተኛ መንደር አለች፡፡ ይህች መንደር የአጋሜ አውራጃ ርዕሰ ከተማ ከሆነችው አዲግራት 35 ኪሎ ሜትር ያህል ትርቃለች፡፡ የመንደሪቷ ነዋሪዎች በአብዛኛው ካቶሊክ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ተሰፋዬ ደበሳይ በዚያች አነስተኛ መንደር ውስጥ ነው በ1933 የተወለደው፡፡ ወላጅ አባቱ አቶ ደበሳይ ካህሳይ ይባላሉ፡፡ እናቱ ደግሞ ወ/ሮ ምህረታ ዓዶ-ዑማር ነበሩ፡፡ ተስፋዬ የቤተሰቡ የበኩር እና ብቸኛ ወንድ ልጅ ነው፡፡ ከርሱ በኋላ የተወለዱት ስድስት ልጆች በሙሉ ሴቶች ናቸው (ለዚህ ጽሑፍ የመረጃ ምንጭ ከሆነው የመጋቢት ወር/2005 የኢህአፓ ዘገባ ለመረዳት እንደተቻለው ከስድስት እህቶቹ መካከል አምስቱ በህይወት ይገኛሉ፤ ወላጅ አባቱም በህይወት አሉ)፡፡

አሊቴና በዚያ ዘመን ትምህርት ቤት አልነበራትም፡፡ ስለዚህ ህጻኑ ተስፋዬ የትምህርት ጉጉት ቢኖረውም እድሜው አስር ዓመት እስኪሆነው ድረስ ትምህርት ቤት ለመግባት አልታደለም፡፡ በ1943 ግን አዲግራት ከሚኖሩት አክስቱ ዘንድ ሄደና ትምህርት ቤት እንዲያስገቡት ለመናቸው፡፡ አክስቱም በከተማዋ ከሚገኝ ታዋቂ የካቶሊክ ሚሽን ትምህርት ቤት አስገቡት፡፡ ተስፋዬም እስከ ስምንተኛ ክፍል በዚሁ ት/ቤት ከተማረ በኋላ ዘጠኛ ክፍልን መቀሌ በሚገኘው አጼ ዮሐንስ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አጠናቀቀ፡፡ ይሁንና በወቅቱ የትምህርት ወጪውን በራሱ ሸፍኖ መማር እንደማይችል በመረዳቱ ፊት ወደ ነበረበት የካቶሊክ ት/ቤት ተመለሰ፡፡ እዚያም እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል ከተማረ በኋላ ለከፍተኛ ትምህርት ወደ ጣሊያን ሀገር ተላከ፡፡ በሀገረ ኢጣሊያ ሮም ከተማ ካለው Urbaniana University በፍልስፍና ትምህርት የዶክትሬት ዲግሪውን ተቀበለ፡፡

ተስፋዬ በስራው ዓለም ሲሰማራ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰራበት መስሪያ ቤት የማስታወቂያና መርሐ ብሄር ሚኒስቴር ነበር፡፡ በዚህ መስሪያ ቤት የምርምር ክፍል ሃላፊ ሆኖ እየሰራ በማታው ክፍል የአባዲና ፖሊስ ኮሌጅ አስተማሪ ለመሆን በቅቷል፡፡ በ1964 ለተጨማሪ ስልጠና ወደ አውሮጳ (ስዊዘርላንድ) ተልኳል፡፡ በዚያ እያለም በመቀጣጠል ላይ የነበረው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ልቡን ስለወሰደው ትምህርቱን ትቶ ሙሉ በሙሉ ወደዚያው ገብቷል፡፡

ታዲያ እርሱ ወደ ስዊዘርላንድ በሄደበት ወቅት በአውሮጳው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማህበር እና በአሜሪካው የተማሪዎች ማህበር መካከል ከፍተኛ ውዝግብ ይካሄድ ነበር፡፡ ሁለቱ ማህበሮች የተወዛገቡት የድርጅት ምስረታና አደረጃጀት፣ የኤርትራ ጥያቄ፣ የብሄረሰቦች መብት፣ የትጥቅ ትግል አስፈላጊነት በመሳሰሉ አርዕስተ ነገሮች ዙሪያ ነበር፡፡ በጊዜው የድርጅት አስኳል ለመመስረት ጥረት ያደርግ የነበረው የአልጄሪያው የስደተኛ ተማሪዎች ቡድን ከአሜሪካው ማህበር ጋር ተቀራራቢ አቋም አሳየ፡፡ የአውሮጳው ማህበር መሪዎች በሀገር ቤት ከነበሩ ጥቂት ተማሪዎች ጋር አንድ ዓይነት አቋም ላይ ደረሱ፡፡ ተስፋዬ ደበሳይ ግን የአውሮጳው ማህበር መሪዎችን ውሳኔ በመቃወም ከአልጄሪያው ቡድን ጋር ወገነ፡፡ በዚህም መሰረት የአልጄሪያው ቡድን፣ የአሜሪካው ቡድንና አውሮጳ የነበሩት ጥቂት ተማሪዎች በድርጅት ምስረታ ሂደት ላይ መነጋገር ጀመሩ፡፡ ውይይቱ ለወራት ሲብላላ ከቆየ በኋላ በዓለም ዙሪያ ተበታትነው የነበሩ ሌሎች ኢትዮጵያዊ ተማሪዎችንም ማካለል ጀመረ፡፡ በስተመጨረሻም በሚያዚያ ወር 1964 “የኢትዮጵያ ህዝቦች አርነት ድርጅት” (ኢህአድ) ተወለደ፡፡ ተስፋዬ ደበሳይም ለድርጅቱ አመራር ከተመረጡ ሰባት የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት አንዱ ሆነ፡፡
*****
ኢህአድ የተወለደው በውጪ ሀገር ነው፡፡ ከ1964-1966 በነበሩት ዓመታት ዋነኛ ስራው ድርጅቱን ማስተዋወቅና አባላትን ማሰባሰብ ነበር፡፡ ከፍልስጥኤም ነጻ አውጪ ድርጅትና ከኤርትራ ግንባሮች የተሰጠውን ድጋፍ በመጠቀም የትጥቅ ትግል የመጀመር እንቅስቃሴ ሲያደርግም ቆይቷል፡፡ የድርጅቱ ቀዳሚ ዓላማ ከገጠር በሚጀመር የትጥቅ ትግል በረጅም ጊዜ የስርዓት ለውጥ ማምጣት ነበር፡፡ የኢህአድ መሪዎችም ድርጅቱ ቀዳሚ ሰራዊቱን ሊያሰማራበት ወዳሰበው የአሲምባ ተራራ በመሄድ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራር እንዲሰጡ ለማድረግ ታስቧል፡፡ ይሁንና በ1966 የፈነዳው የኢትዮጵያ አብዮት የትግሉን አቅጣጫ ሙሉ በሙሉ ቀየረው፡፡ የአሮጌው ስርዓት መውደቅ አይቀሬ እንደሆነ ሁሉም በየፊናው አወቀ፡፡ “በርሱ ቦታ ተተክቶ ሀገሪቱን የሚመራው ማን ነው?” የሚለው ጥያቄ ግን አነጋጋሪ ሆነ፡፡ በዚህም በተራማጅ አብዮተኞች መካከል ከፍተኛ ውይይት ተቀሰቀሰ፡፡ በመደምደሚያውም የፓርቲ ቅርጽ የነበራቸው ቡድኖች በከተሞች አካባቢ የፖለቲካ ትግል ቢያደርጉ ጠቀሜታው ከፍ ያለ እንደሚሆን ከስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ በመሆኑም በውጪ ሀገር የነበረው የኢህአድ አመራር ወደ ሀገሪቷ ለመግባት ወሰነ፡፡

ከኢህአድ ከፍተኛ መሪዎች መካከል በቅድሚያ ወደ አዲስ አበባ የገባው ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ነው፡፡ ጊዜውም ሰኔ 1966 ነበር፡፡ በወቅቱ የወታደሮች ቡድን የሆነው ደርግ ተመስርቶ የአጼውን መንግሥት ለመጣል እያኮበኮበ ነበር፡፡ በሀምሌ ወር አጋማሽ ላይ ደርግ የልጅ እንዳልካቸውን ካቢኔ በመሻር ልጅ ሚካኤል እምሩ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ መረጣቸው፡፡ ልጅ ሚካኤልም ካቢኔአቸውን ሲያቋቁሙ በስዊዘርላንድ የሚያውቁትን ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይን የመሬት ይዞታ ሚኒስትር እንዲሆን ጠየቁት፡፡ እርሱ ግን ከውጪ የመጣው ለዚያ አልነበረምና አንዳች ምክንያት ፈጥሮ አሉታዊ መልስ ሰጣቸው፡፡ በምትኩ በመስሪያ ቤቱ በኤክስፐርትነት ቢቀጠር ለመስራት ፈቃደኛ እንደሆነ ገለጸላቸው፡፡ በዚህም መሰረት ከነሐሴ 1966 ጀምሮ የመስሪያ ቤቱ ሰራተኛ ሆነ፡፡

ተስፋዬ ወደ ሀገር ቤት ከተመለሰ በኋላ ድርጅቱን በማስፋፋትና አባላትን በማደራጀት ስራ ላይ ነበር የተጠመደው፡፡ የድርጅቱ ልሳን የሆነችውን “ዲሞክራሲያ” ጋዜጣ ከሚያወጡ አርታኢያን መካከልም አንዱ ነበር፡፡ በድርጅቱ የመጀመሪያ ጉባኤ ዋና ጸሐፊ ሆኖ የተመረጠው ብርሃነ መስቀል ረዳ ከሰራዊቱ ጋር ስለነበር በርሱ ቦታ በጊዜያዊነት አመራር የሚሰጠውም ተስፋዬ ደበሳይ ነበር፡፡ በወቅቱ በድርጅቱ አመራር ላይ ከነበሩትም መካከል በዕድሜም ሆነ በትምህርት ደረጃ የሚበልጠው እርሱ ነበር፡፡

ተስፋዬ እስከ ታህሳስ 1967 በአዲስ አበባ ከተማ ከቆየ በኋላ ከመሬት ይዞታ ጋር ለተያያዘ የመስክ ስራ ወደ ትግራይ ተጓዘ፡፡ እግረ መንገዱንም አሲምባ የሚገኘውን የድርጅቱን ጀማሪ ሰራዊት ለመጎብኘት ወደዚያው ጎራ አለ፡፡ በጊዜው የነበረውን የሀገሪቱን የፖለቲካ ሁኔታ ለሰራዊቱ ካብራራ በኋላ ግን ያልተጠበቀ ችግር ተከሰተ፡፡ ስምንት ያህል የሰራዊቱ አባላት ከጀማሪ ሰራዊቱ በመነጠል ለደርግ እጃቸውን ሰጡ (እጃቸውን የሰጡት ሰዎች ተስፋዬ መኮንን፣ ኃይለ እየሱስ ወልደ ሰንበት፣ አበበ በየነ፣ ዘከሪያ መሐመድ፣ አያሌው ከበደ፣ ጋሻው መንግሥቱ፣ ሀይሌ ወልደ ጊዮርጊስና ዳዊት አሰፋ ነበሩ፤ እነዚህ ሰዎች በ1968 መጀመሪያ ላይ “ማሌሪድ”፣ ማለትም “የማርክሲስት ሌኒኒስት ሪቮሉሽናሪ ድርጅት”ን መስርተዋል)፡፡ ታዲያ የነዚህ ሰዎች ከኢህአፓ አፈንግጦ መውጣት የዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይን ማንነት አጋለጠው፡፡ በመሆኑም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህቡዕ ለመግባት ተገደደ፡፡
*****
ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ህቡዕ ከገባ በኋላ የሙሉ ጊዜ አብዮታዊ ሆኗል፡፡ ኢህአድን በሙሉ አቅሙ አገልግሏል፡፡ በነሃሴ ወር 1967 ድርጅቱ ስሙን ቀይሮ “ኢህአፓ” (የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ) የተሰኘውን ዝነኛ መጠሪያውን የያዘበትን ጉባኤ በዋናነት ያዘጋጀውም እርሱ ነው፡፡ የድርጅቱ የፍልስፍና ሊቅ (ideologue) ሆኖ የሚያገለግለውም እርሱ ነበር፡፡ በኢህአፓ መስራች ጉባኤ “ዋና ጸሐፊ” የሚባል የስልጣን ተዋረድ ሲሻር በቀዳሚነት የማዕከላዊ ኮሚቴ ጸሐፊ ሆኖ ማገልገል የጀመረው እርሱ ነበር (ይህ የጸሐፊነት ቦታ በየጊዜው ይለዋወጥ ነበር፤ ጸሐፊው የሚመረጠውም በፓርቲው ጉባኤ ሳይሆን በፖሊት ቢሮው ነው)፡፡

እስከ 1968 አጋማሽ ድረስ በነበረው ጊዜ የኢህአፓ አመራሮች ማንነት በግልጽ አይታወቅም፡፡ በዚያን ጊዜ ህቡዕ ለመግባት የተገደዱት ብርሃነ መስቀል ረዳ እና ተስፋዬ ደበሳይ ብቻ ናቸው፡፡ በመሆኑም አብዛኛው የፓርቲው ስራ የሚከወነው በተስፋዬ ነበር (ብርሃነ መስቀል ለፖሊት ቢሮው ስላልተመረጠ ከፍተኛ ሃላፊነት አልተሰጠውም፤ በተጨማሪም ከሌሎች መሪዎች ጋር መነታረክ ጀምሮ ነበር) ፡፡

የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዜያዊ ጽ/ቤት ከተመሰረተ በኋላ ግን አመራሩን ለአደጋ የሚያጋልጥ ሁኔታ ተከሰተ፡፡ በጽ/ቤቱ የተመረጡት ከፍተኛ ካድሬዎች የኢህአፓ መሪዎችን ስለሚያውቋቸው ለደርግ አሳልፈው ይሰጡአቸዋል የሚል ስጋት ሰፈነ፡፡ በመሆኑም በ1968 መጨረሻ ገደማ ሁሉም መሪዎች ህቡዕ ለመግባት ተገደዱ፡፡ ታዲያ የኢህአፓ የትግል ስትራቴጂም መለወጥ የጀመረው ከዚህ ወቅት ጀምሮ ነው፡፡ ከ1968 ክረምት ወራት በፊት በከተሞች አካባቢ የፖለቲካ ትግል ብቻ ያደርግ የነበረው ኢህአፓ የደርግ ፋሺስትነትን ለመከላከል በሚል የከተማ ትጥቅ ትግል የጀመረው ያኔ ነው፡፡

አንዳንድ ወገኖች የትጥቅ ትግሉ በዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ግፊት የመጣ ነው ይላሉ፡፡ ከሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማሪያም ጀምሮ መገደል ያለባቸውን ከፍተኛ የደርግና የመኢሶን ባለስልጣናት ዝርዝር እያዘጋጀ የሞት ፍርድ ያስወስን የነበረው ተስፋዬ ደበሳይ ነው በማለት ይሞግታሉ፡፡ ከዚህ እልፍ ሲል ደግሞ የተስፋዬን ትግሬነት በመጥቀስ ብቻ ሻዕቢያ በአዲስ አበባ ከተማ ሽብር ለመቀስቀስ የመደበው የጥፋት ወኪል ነው የሚል መረጃ የሚያስነብቡ ጽሁፎችን ማየት የተለመደ ሆኗል (ለነገሩ ተስፋዬ የኢሮብ ተወላጅ ነው እንጂ ትግሬ አልነበረም)፡፡ ይሁንና እንዲህ ዓይነቱን የተናጥል ክስ በተስፋዬ ላይ የሚያጠናክር ማስረጃ የለም፡፡ ኢህአፓ የከተማ ትጥቅ ትግል እንዲጀምር የወሰኑት ብዙሃኑ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ናቸው እንጂ ተስፋዬ ደበሳይ ብቻ አልነበረም፤ ውሳኔውን የተቃወሙት ጌታቸው ማሩ እና ብርሃነ መስቀል ረዳ ብቻ ነበሩ (በጊዜው የኢህአፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት የነበሩት ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ፣ ዮሐንስ ብርሃኔ፣ ዮሴፍ አዳነ፣ ክፍሉ ታደሰ፣ ክፍሉ ተፈራ፣ ዘርዑ ክህሸን፣ ኢያሱ አለማየሁ፣ ሳሙኤል አለማየሁ፣ አበራ ዋቅጅራ፣ ፍቅሬ ዘርጋው፣ ጸጋዬ ገብረመድህን፣ ብርሃነ መስቀል ረዳ፣ ጌታቸው ማሩ እና ጸሎተ ህዝቅያስ ነበሩ)፡፡

*****
መስከረም 13 ቀን 1969፡፡ በዚህች ዕለት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያምን ለመግደል ያልተሳካ ሙከራ ተደረገ፡፡ በዚህም የተነሳ ኮሎኔሉ ኢህአፓን ለማጥፋት ቆርጠው ተነሱ፡፡ በስውር የሚያካሄዱትን ርሸና ይፋ ማውጣት ጀመሩ፡፡ በታህሳስ ወር የኮሎኔሉን እርምጃ የሚቃወሙ መኮንኖች በደርግ ውስጥ መዋቅራዊ ለውጥ አካሄዱ፡፡ ይሁን እንጂ ከአንድ ወር በኋላ (ጥር 25/1969) ኮሎኔል መንግስቱ ማንም ባላሰበው መንገድ ጠላቶቻቸውን በማጥፋት “ለምሳሌ ያሰቡንን ቁርስ አደረግናቸው” በማለት አወጁ፡፡ “አብዮቱ ከተከላካይነት ወደ አጥቂነት ተሸጋግሯል” ተባለ፡፡ “ቀይ ሽብር” በይፋ ታወጀ፡፡ “ነጻ እርምጃ” ተፈቀደ፡፡

በወቅቱ የኢህአፓው ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ አዲስ አበባ ውስጥ እንደነበረ ደርጎች ያውቁ ነበር፡፡ ነገር ግን አድራሻውን በትክክል ማወቅ አልቻሉም፡፡ ኢህአፓም ከጥር ወር መጨረሻ ጀምሮ እየተባባሰ በመሄድ ላይ የነበረውን የደርግ እርምጃ ለመቀልበስ እንደማይችል አውቆታል፡፡ ይሁንና የከተማውን የትጥቅ አመጽ አላቋረጠም፡፡ ደግሞም ዋና መሪውን ከደርግ አፍንጫ ስር አውጥቶ ከደህና ቦታ ለማድረስ አልሞከረም፡፡

ታዲያ ኢህአፓዎች መሪአቸው ከከተማው ወጥቶ ለደህንነቱ አስተማማኝ በሆነ ቦታ ቢደበቅ ይፈልጉ ነበር፡፡ በተለይ በመጋቢት ወር አጋማሽ (1969) ከሚካሄደው የቤት ለቤት አሰሳ ነፍሱን እንዲታደግ ይመኙ ነበር፡፡ ይሁንና መሪው ከከተማው ለመውጣት ምንም ዓይነት ፍላጎት አልነበረውም፡፡ “በዚህ ክፉ ቀን ተከታዮቼን ጥዬ ከከተማ አልሰደድም” በማለት ቆርጧል፡፡ አሰሳው ከመጀመሩ አስቀድሞ በነበሩት ቀናት ራሱ ሸኝ ሆኖ በልዩ ልዩ እርከን ላይ ያሉ ኢህአፓዎችን ከከተማው ወደ ገጠር ይሸኝ ነበር፡፡ ለምሳሌ የቤት ለቤት አሰሳው ከሚካሄድበት ዕለት በፊት በነበሩት ቀናት (ከመጋቢት 10-13 ባሉት ቀናት) ተስፋዬ ደበሳይ በርካታ የኢህአፓ አባላትን ከከተማ እያስወጣ ወደ ገጠር መሸኘቱ ተመዝግቧል፡፡ በነዚያ ቀናት በርካቶች ወደ አሲምባና ሰሜን ሸዋ አካባቢዎች ሄደዋል፡፡ እርሱ ግን እዚያው ሆኖ አሰሳው የሚያመጣውን ውጤት ለማየት ይጠባበቅ ነበር፡፡
*****
ዕለቱ መጋቢት አስራ 15/1969 ነው፡፡ ደርግ የቤት ለቤት አሰሳውን እያካሄደ ነው፡፡ እያንዳንዱ ቤት እየተከፈተ ይፈተሻል፡፡ “አናርኪስት” ተብሎ የተጠረጠረ ሰው እየተያዘ ወደ ማዕከላዊ ምርመራና የቀበሌ እስር ቤቶች ይጋዛል፡፡ ከእስራቱ ለማምለጥ የሞከረ ያለ ምንም ጥያቄ ይገደላል፡፡ ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ያረፈበት የበሪሁን ማሪዬ ቤትም እንደሚፈተሽ መረጃው ለኢህአፓ አሀዶች ደርሷል፡፡ በመሆኑም የተስፋዬን ህይወት ለመታደግ ቀኑን በመንግሥት ቢሮ ውስጥ ተደብቆ ማሳለፍ አስፈላጊ እንደሆነ ታምኖበታል (በወቅቱ ቢሮዎች አይፈተሹም ነበር)፡፡ በዚህ መሰረት ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይና በሪሁን ማሪዬ አምባሳደር ቴአትር አካባቢ ባለው ኪዳኔ በየነ ህንጻ ውስጥ በሚገኘው የበሪሁን ሚስት ቢሮ ለመደበቅ ወሰኑ፡፡ በበሪሁን ማሪዬ ሾፌርነትም ከመርካቶ አካባቢ ወደ አምባሳደር ቴአትር እንቅስቃሴ ጀመሩ፡፡ ተክለ ሀይማኖት አካባቢ ሲደርሱ ግን ተስፋዬን በሚያውቅ ሰው እይታ ውስጥ ገቡ፡፡ ያ ሰው ወዲያኑ ለደርግ ጸጥታ ሀይሎች በመደወል የተስፋዬን መገኘት አበሰራቸው፡፡ ለራሱ ደግሞ በቀስታ (እነርሱ ሳያዩት) ከኋላ እየነዳ ተከተላቸው፡፡ ደርጎች ለወራት ሲፈልጉት የነበረው አውራ ጠላታቸው ዱካ መገኘቱን ሲሰሙ በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ተባለው ስፍራ አሳሽ ጦር ላኩ፡፡

ተስፋዬ ደበሳይና በሪሁን ማሪዬ ወደ ኪዳኔ በየነ ህንጻ ገቡ፡፡ ሆኖም ህንጻው እንደጠበቁት ነጻ ሆኖ ስላላገኙት ወደ መጡበት ለመመለስ ወሰኑ፡፡ ፈጠን ባለ እርምጃ ከህንጻው መውጫ በር ላይ ሲደርሱ ግን ለነርሱ የተላከው አሳሽ ጦር ህንጻውን ከቦ አገኙት፡፡ በዚህን ጊዜም ወደ ህንጻው ለመመለስ ሩጫ ጀመሩ፡፡ ሆኖም በቅርብ ርቀት ላይ የነበሩት አሳሾች ተኮሱባቸው፡፡ በሪሁን ማሪዬ ወዲያውኑ ተገደለ፡፡ ተስፋዬ ደበሳይ ደግሞ ግንባሩ ላይ ቆሰለ፡፡ እርሱ ግን አልቆመም፡፡ የህንጻውን ፎቆች በትጋት ወጣ፡፡ ከስድስተኛው ፎቅ ላይ ሲደርስ አንድ ክፍት ቢሮ አየ፡፡ ከቢሮው በመግባት በመስኮቱ በኩል ወደ ውጪ ተወረወረ፡፡ ከሰከንዶች በኋላም መሬት ላይ ተፈጠፈጠ፡፡ የኢህአፓው መሪ እንዲህ ባለ አሳዛኝ ትራጄዲ ከምድር ላይ ተሰናበተ፡፡
*****
ስለዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ በኢህአፓ ወገን በይፋ የተጻፈው ታሪክ ይህ ነው፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ አንዳንድ ጸሐፊዎች አሟሟቱን በሚመለከት አወዛጋቢ ታሪኮችን ማስነበብ ጀምረዋል፡፡ ውዝግቡ ለጊዜው አይጠቅመንም፡፡ የታሪክ ጸሐፊዎች ሐቁን እስከሚያወጡት ድረስ አወዛጋቢውን ታሪክ ብንዘለው ይሻላል፡፡ በጣም የምንስማማበት ጉዳይ ቢኖር ሀይሌ ፊዳ የመኢሶን ግርማ እና ኩራት እንደነበረው ሁሉ ተስፋዬ ደበሳይም የኢህአፓ አውራ የነበረ መሆኑን ነው፡፡ መኢሶንን ያለ ሀይሌ ፊዳ፣ ኢህአፓንም ያለ ተስፋዬ ደበሳይ ማሰብ አይቻልም፡፡ ሁለቱም የአንድ ትውልድ ፈርጦች ነበሩ፡፡ ሁለቱም በተሳሳተ ስሌት እርስ በርስ ተዋጉ፡፡ ሁለቱም በጨካኙ ስርዓት ተበሉ፡፡

የዶ/ር ተስፋዬ ታሪክን የማሳርገው በሚከተለው ታዋቂ የኢህአፓ መዝሙር ነው፡፡
“ቢወቀጥ አጥንቴ ቢንቆረቆር ደሜ
ለአዲስ ሥርዓት ልምላሜ
ፍጹም ነው እምነቴ
ትግሉ ነው ሕይወቴ”
*****
አፈንዲ ሙተቂ
መጋቢት 14/2006

(የትረካ ምንጮች)
1. ባቢሌ ቶላ፣ የትውልድ እልቂት፣ 1985፣ አዲስ አበባ
2. ክፍሉ ታደሰ፣ “ያ ትውልድ” ቅጽ 1፣ 1987፣ አዲስ አበባ
3. ክፍሉ ታደሰ፣ “ያ ትውልድ” ቅጽ 2፣ 1990፣ አዲስ አበባ
4. የያ ትውልድ ተቋም፣ “ዝክረ ተስፋዬ ደበሳይ”፣ መጋቢት 2005፣ ከኢንተርኔት የተገኘ
5. ገነት አየለ አንበሴ፣ የሌተና ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማሪያም ትዝታዎች፣ 1994፣ አዲስ አበባ
(አፈንዲ ሙተቂ)
The writer, Afendi Muteki, is a researcher of the Ethnography and History of the peoples of East Ethiopia. He is an author of “Harar Gey”, an Ethnography book about the historical city of Harar. You can read some of his articles on his blog and his facebook page.

ህወሓቶች በዓረና እንቅስቃሴና በትግራይ ህዝብ የተቃውሞ መንፈስ በጣም ደንግጠዋል። የዓረና ተከታታይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ተከትሎ ህወሓትም ተከታታይ ህዝባዊ ኮንፈረንስ ለማድረግ ወስኗል፤ ጀምሯልም። የህዝብ ተወካዮች ተብለው የተመረጡ የየአከባቢያቸው ህዝብ እንዲሰበስቡ መመርያ ተሰጥቷል። ይቅርታ የህዝብ ተወካዮች ሳይሆኑ የፓርቲ ተወካዮች መባል አለባቸው፤ ምክንያቱም የተመረጡት በህዝብ ሳይሆን በህወሓት ነው። የሚያገለግሉትም ለህዝብ ሳይሆን ለህወሓት ነው። ምክንያቱም በህዝብ ተመርጠው ተብለው የህዝብ ችግር ከመናገር ይልቅ የህወሓት አጀንዳ ደግፈው የሚያጨበጭቡ ናቸው። እስካሁን የመረጠውን ህዝብ ችግር የተናገረ የህዝብ ተወካይ የህወሓት አባል አላገኘሁም። በህወሓት የፖለቲካ ፍልስፍና የተማእከለ ዴሞክራሲ መሰረት አንድ አባል ከፓርቲው አስተሳሰብ ወጥቶ የፓርቲው ብልሹ አሰራሮች ባደባብይ ወይ በፓርላማ ማጋለጥ አይችልም። ካጋለጠ ከፓርቲው ይባረራል። ለዚህም ነው የህዝብ ተወካዮች ተብለው ፓርላማ ይገቡና የፓርቲው ተወካዮች ሁነው የሚቀሩ።

የህዝብ ወይም የህወሓት ተወካዮች ህዝብ ሲሰበስቡ ፈተና እያጋጠማቸው ነው። የሽረ ተወካይ ህዝቡ ሰድቦ አባሯታል። ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ በዓድዋ ህዝብ ተሰድባለች። የዓድዋ ህዝብ ለቅዱሳን “እናንተ ቤተሰቦቻቹ ለመርዳት እንጂ መቼ ለህዝብ ደህንነት ሰርታቹ ታውቃላቹ?” የሚል አስተያየት ሰጥቷል። በመቐለም አዲሳለም ባሌማ ህዝብ (ይቅርታ በመቐለ ህዝብ ተብለው የተሰበሰቡ ካድሬዎች ነበሩ) ሰብስቦ እርዱን ማለቱ ታውቋል። የመቐለ ዉሃ በ2007 ዓም ፕሮጀክት ቀርፀን እንፈተዋለን፤ ብቻ እኛን ምረጡ ብሎ ተማፅኗል። የመቐለ ነጋዴዎች ሰብስቦ ችግሮቻቹ ለመፍታት ተዘጋጅተናል ብሎዋል።

አጠቃላይ የህወሓት ስትራተጂ ህዝብን ለመሸወድ ያለመ ሲሆን የሚያጠነጥነውም “ህወሓት ካልተመረጠ የትግራይ ማንነት ይጠፋል” የሚል ነው። “ጠላቶቻችን እየመጡ ናቸው፤ ከህወሓት ጎን ተሰለፉ! ጦርነት ሊከፈትና ልጆቻችሁ አደጋ ላይ ሊወድቁ ይችላሉ” እያሉ ይገኛሉ።

ግን የትግራይ ማንነት በህወሓት ህልውና የተንጠለጠለ አይደለም። እንኳን የህዝብ ማንነት የአንድ ግለሰብ ማንነትም ሊጠፋ አይችልም። ምክንያቱም የህዝብ ማንነት ቀርቶ የአንድ ሰው ማንነት ከጠፋ የሰውየው መብትና ነፃነት ተጥሷል ማለት ነው። መብቱ ወይ ነፃነቱ ከተጣሰ ደግሞ አዲስ የመጣ ስርዓት ልክ እንደ ህወሓት አምባገነናዊ ስርዓት ነው ማለት ነው። የህውሓትን ያህል አምባገነን ስርዓት ከመሰረትን ደግሞ ህወሓት አልተቀየረም ማለት ነው። ህወሓት ካልተቀየረ የፖለቲካ ለውጥ አልመጣም ማለት ነው። የፖለቲካ ለውጥ ካልመጣ ደግሞ ትግላችን ይቀጥላል (ለውጥ እስኪመጣ ድረስ)። ስለዚህ እኛ የምንታገለው ከህወሓት የተሻለ ስርዓት ለመመስረት እንጂ ህወሓትን በሌላ አምባገነን ስርዓት ለመተካት አይደለም። ስለዚህ ላረጋግጥላቹ የምፈልገው ነገር ቢኖር የማንም ህዝብ ወይ ግለሰብ ማንነት ይከበራል እንጂ አይጠፋም።

“ጠላቶቻችን እየመጡ ነው” የሚለው ዉንጀላ ግዜው ያለፈበት ፕሮፓጋንዳ ነው። የህዝብ ጠላት ጨቋኝ ስርዓት ነው። ህዝብ ከጨቋኝ ስርዓት ዉጭ ሌላ ጠላት የለውም። ጨቋኝ ስርዓት የህዝብ ጠላት እስከሆነ ድረስ እንታገለዋለን። ጨቋኝ ስርዓት ምን ግዜም አንቀበልም። ጨቋኝ ስርዓት ስለማንቀበል ነው አሁን ህወሓትን የምንቃወመው። ስለዚህ ዓላማችን የስርዓት ለውጥ ማምጣት እስከሆነ ድረስ ለጨቋኞች ቦታ የለንም፤ ህወሓትም ሌሎችም። እኛ የምንቀበለው ዴሞክራሲያዊ የህዝብ መንግስት ብቻ ነው።

ህወሓቶች በዓረና አጀንዳዎች በመስጋታቸው ምክንያት የዓረና ሐሳቦችን ለመቀበል እየተገደዱ ነው። በቅርቡ በህዝብ ፊት እየቀረቡ የመሬት ይዞታ ጉዳይ በዓረና እየቀረበ ያለውን ሐሳብ እንደሚደግፉ እየገለፁ ነው። (የዓረና ሐሳብ እንደግፋለን እያሉ ሳይሆን የህዝብን ፍላጎት ለማሟላት እንሞክራለን በሚል ነው። የህዝቡ ፍላጎት ደግሞ የዓረና የመሬት ፖሊሲ ነው)። የዓሰብ ወደብም በሰለማዊ መንገድ ለማስመለስ እንሞክራለን በማለት እየተመፃደቁ ነው። ለነጋዴዎችም ግብር እንቀንሳለን በሚል ምክንያት ለመጀንጀን እየሞከሩ ነው።

አሁን ግራ ሲገባቸው ስራ የሌላቸው ወጣቶች ለውትድርና ለመመልመል እየሞከሩ ሲሆን ማንም ወጣት ፍቃደኛ ሊሆን አልቻለም። በወጣቶቹ ዉሳኔ የተደናገጡ ህወሓቶች የጎዳና ተዳዳሪ የነበሩ ህፃናት ልጆች አታለው (ስራ እንሰጣቸዋለን በሚል ምክንያት) ለዉትድርና መመልመላቸው ታውቋል። ለምሳሌ በመቐለ ከተማ የነበሩ ብዙ የጎዳና ተዳዳሪ ህፃናት ተወስደዋል (ማረጋገጥ ይቻላል፤ አሁን በመቐለ ከነበሩ ህፃናት አንድ የቀረ የለም)። ግን አብዛኞቹ ህፃናት ከ16 ዓመት በታች ናቸው። ከ16 ዓመት በታች ህፃናት ለውትድርና የሚመለምል የቸኛ ሕገወጥ መንግስት ኢህአዴግ መሆኑ አይቀርም። ምክንያቱም በማንኛውም ሕግ ከ16 ዓመት በታች ህፃናት ለውትድርና መመልመል ሕጋዊ ሊሆን አይችልም። ጉዳዩ የሚከታተለው ካገኘ በዓለም አቀፍ ሕግ ወንጀል ሊሆን ይችላል።

በዓዲግራት የፈፀሙብንን ድብደባ በጣም አክስሮባቸዋል። የትግራይ ህዝብ ሙሉበሙሉ እንዲጠላቸው ሁነዋል። እናም በጣም ሰግተዋል። በቅርቡ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሊጀምሩ ይችላሉ። በወታድሩም ቢሆን ህወሓቶች ድጋፍ የላቸውም።

It is so!!!
አብረሃ ደስታ

Image

መለስ በመጀመሪያው የኤርትራውያን ነፃነት ቀን ዝግጅት ላይ ለኤርትራውያን እንዲ ብሎ ነበር። «ቁስል እንዳለባችሁ አውቃለው። ለምን? ብትሉ ጀርባችሁ ላይ ያለው ቁስል በእኔ ጀርባ ላይም አለ። ይህንን ያለፈ ምህራፍ እርሱት አልላችሁም። ነገር ግን ቁስላችንን ማከክ የለብንም አሁን ሁሉ ነገር አልቋል (ተውዲኡ ኣሎ)ክፉ፣ ክፉውን ቀብረነዋል!!» ነበር ያለው።

ይህንን የመለስ ዜናዊ አነጋገር አንድምታ ስናይ «ይኸው ደረስንላችሁ! ጠላት ተቀበረ! መቀበር ብቻ አይደለም አስተሳሰቡንም አዛብተነዋል! ያለበት ነበር። እንግዲህ ማነው ጠላት? ኢትዮጵያ? የማን አስተሳሰብ ነው? የኢትዮጵያ! ምን አይነት አስተሳሰብ? እንግዲህ እንደምናውቀው በተለየ ጊዜ የኢትዮጵያን ሳይኮሎጂ የሚያዛቡ ነገሮችን ሲናገሩ ነበር። ለምሳሌ፦ «ባንዲራ እኮ ጨርቅ ነው!» ይሄ አባባልን ለሚያይ ሌላ ሰው በቀላሉ የአፍ ወለምታ ሊመስለው ይችላል።ነገር ግን ሆን ተብሎ የኢትዮጵያውያንን አስተሳሰብ ለማዛባትና ለማሽመድመድ የሚደረግ ሴራ ነው።

በባንዲራችን እንደምንኮራ ያውቃሉ! የሶስት ሺህ አመት ታሪክ አለን ብለን እንደምንኮራ ያውቃሉ! ነገር ግን ይህንንም ታሪካችንን ወደ መቶ አመት ዝቅ ለማድረግ ይጥራሉ፤ ባለፉት መሪዎቻችን በአጼ ምንሊክ ፣ በነ አጼ ቴዎድሮስ፣ በነ አጼ ዩሐንስ፣ በነ አሉላ እንደምንኮራና እንደምንወዳቸው ከእነሱ ጋርም ያለንን ትስስር ያውቃሉ! ወያኔዎቹ ባንዳዎች ግን በየጊዜው ቴሌቭዥን ላይ እየወጡ «የኢትዮጵያ አጼዎች እኮ ጊዜያቸውን ያሳለፉት በጦርነት ነበር።» ይላሉ። ይሄን መናገር በተለይ አቶ መለስ እንደሆቢ ነበር የወሰዱት የሚመስለው። እንግዲህ የኢትዮጵያ ህዝብ መሪዎቹ «ለካ እንዲህ ነበሩ» ብሎ እንዲያፍር! የዛሬውም ቅጥ ያጣ ድህነት «እነሱ ያመጡት ጣጣ ነው!» ብለውም ለመናገር ይሞክራሉ።

እንደዚህ አይነት ቀጣይ ነገሮችን አምጥተን አገጣጥመን «ባንዲራ ጨርቅ ነው!» ካሉበት ጊዜ ጀምሮ ያሉትን ሰብስበን ብናያቸው መለስ የተያያዘው ኢትዮጵያዊ አንገቱን ደፍቶ፣ በኢትዮጵያዊነቱ አፍሮ፣ ድህነትን እንዲቀበል፣ ከኋላ ቀርነት ጋር ተቆራኝቶ እንዲኖርና የበታችነት ስሜት እንዲኖረው አድርገዋል እየተደረገም ነው»

Image

በቅርቡ ባህርዳር ላይ በተካሄደው የኢትዮጵያ ስፖርት በአል ሼኽ አልሙዲ በክብር እንግድነት ተጋብዘው ነበር። የበአሉን መክፈቻ በቲቪ ስከታተል አንድ ጥያቄ ወደ በአእምሮዬ መጣ። አልሙዲንን የክብር እንግዳ አድርጐ መጋበዙ ለምን አስፈለገ?..ብዙ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ። “የገዢው ፓርቲና የባለስልጣናቱ ታማኝ ወዳጅ ስለሆኑ፣ በባህርዳሩ ስታዲየም ግንባታ ድርጅታቸው ስለተሳተፈ ወይም ሼኹ ለስፖርት ያላቸውን ፍቅር በማየት..” የሚሉ ነገሮችን መደርደር ይቻላል።

በእኔ ግምት አልሙዲ በባህርዳሩ በአል በእንግድነት የተጋበዙት በሰሜን አሜሪካ ስፖርት በአል ላይ ስለተዋረዱ የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት የፈጠርዋት ማፅናኛ ትመስለኛለች። ባለፈው አመት እዚህ ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በአንድ ሳምንት ሁለት የኢትዮጵያ ስፖርት በአል ተከበሮዋል። አንድኛው በሼኽ አልሙዲና የዳይስፖራውን ማንነትና ፍላጐት ባልተገነዘቡ ወዳጆቻቸው የተዘጋጀ ነበር። በነዚህ ወገኖች ግምት “ዳያስፖራው በተወሰኑ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት ካድሬዎች የሚሽከረከር የዋህ ህዝብ” አድርገው ይወስዱታል።

አሜሪካ ሀገር ከኅይለስላሴ ጀምሮ በደርግ ጊዜ ከዛም በኋላ የመጣው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ (በምንም መንገድ አሜሪካ ይምጣ) ለዘሩ፣ ለጐሳው ሳይሆን ለኢትዮጵያዊነቱ ጥልቅ የሆነ ፍቅርና ክብር አለው። በዚህ ምክንያት የኢህአዴግን የዘር ፖለቲካ አይደግፍም። ከደጋፊዎቹም ጋር የማይታረቅ ቅራኔ ውስጥ የገባው በዚህ አገር ወዳድ አቋሙ ነው። ይህ እውነት ያለገባቸው አልሙዲና ተከታዮቻቸው በስፖርቱ አስታከው ዳያስፖራውን እንቆጣጠራለን በማለት በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ቢከሰክሱም አልተሳካላቸውም። ባዶ ስታዲየም ታቅፈው ነው የቀሩት። ሁለተኛው ኢ.ኤስ.ኤፍ.ኤን የሚባለው ኢትዮጵያዊ ፌዴሬሽን የነሱን ያክል ገንዘብ ሳይኖረው በርካታ ህዝብ ከጎኖ ማሰለፍ ችሎዋል። እንዲያውም ስታዲየሙ ሞልቶ ሰው እስኪመለስ ድረስ። በዚህ በአል ከፍተኛ የሆነ የአንድነትና የአገር ፍቅር ስሜት የታየበት፣ የኢትዮጵያ ባንዲራ ከፍ ብሎ በብዛት የተውለበለበበትና ያሸበረቀበት፣ ሰዎች ከብሄራቸው ይልቅ ኢትዮጵያዊነታቸውን ያገነኑበት ትልቅ በአል ነበር።

ባዶ ስታድየም የታቀፉትና አፍረው በውርደት ለተመለሱት አልሙዲ የባህርዳሩ እድል በማፅናኛነት ተሰጣቸው። ኢትዮጵያዊያን በነፃነት በሚኖሩበት አሜሪካ ግን አልሙዲ በገንዘባቸው የህዝብን ድጋፍ መግዛት አይችሉም። በገንዘብ ምንም ማድረግ እንደማይችሉም ሊያውቁት ይገባል።

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ዛሬ በጽ/ቤቱ መግለጫ ሰጠ ፡፡
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

ከአዲስ አበባ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ!

ኢህአዴግ አገር የመምራት ብቃት እንደሌለው አዲስ አበባ ማሳያ ናት!!

Image
ሌሎች አገሮች ለዋና ከተሞቻቸው ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የየአገሮቻቸው ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ማሳያ በማድረግ አለም አቀፍ ተቋማትንና ጎብኝዎችን በመጋበዝ የከተሞቻቸውን ነዋሪዎች ተጠቃሚ ያደርጋሉ፡፡

እንዳለመታደል ሆኖ ግን በብዙዎች የአፍሪካ አገራት የአህጉሪቱ መዲና ተደርጋ የምትጠቀሰው አዲስ አበበባችን ከጊዜ ወደ ጊዜ ወደ ኋላ አየተጎተተች ለኑሮ ምቹ ከሆኑ ከተሞች ምድብ መቀላቀለ ተስኗት ለነዋሪዎቿ የማትመች የፈተና ምድር ሆናለች፡፡

ኢህአዴግ ራሱን ልማታዊ መንግሥት በማድረግ ከሰየመበት ቅጽበት አንስቶ በልማት ሰበብ ዜጎች ከመኖሪያቸውና ቤተሰቦቻቸውን ከሚያስተዳድሩበት የንግድ ቦታ እንዲፈናቀሉ ተደርገዋል፡፡ በከተማይቱ እንዲነሱ የተደረጉት የንግድ ሱቆች በአብዛኛው በኪራይ ቤቶችና በቀበሌ ስም የተመዘገቡ በመሆናቸውም በሱቆቹ በመነገድ ይተዳደሩ የነበሩ ቤተሰቦች ባዶ አጃቸውን እንዲቀሩ ተደርገዋል፡፡

በአዲስ አበባ እየተካሄደ ያለውን የመንገድ ዝርጋታ የተነሳ የተጠና ሥራ ባለመሰራቱ ከፍተኛ የህዝብ ገንዘብ የወጣባቸው መንገዶች ለምረቃ በበቁ በጥቂት ቀናት ልዩነት እንዲፈርሱ ተደርገዋል፡፡ የከተማው ነዋሪ ለሚጠቀምባቸው የመጓጓዣ አውታሮች ተለዋጭ መንገድ ባመዘጋጀቱም ለተጨማሪ ወጪ ተዳርጓል፡፡ ትራንስፖርት ማግኘት በሁሉም አካባቢዎች አስቸጋሪ በመሆኑ የከተማይቱ የሥራ እንቃስቃሴ ተዳክሟል፡፡ መንግሥት ‹‹የምትታለብ ላም›› በማለት የሚጠራው የኢትዮ ቴሌ ኮም አገልግሎት የለም የሚባልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ ጭምር በኢትዮጵ ቴሌኮም የተንቀራፈፈ አገልግሎተ የተነሳ ባንኮችና የተለያዩ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ለደምበኞቻቸው ተገቢውን ግልጋሎተ ማበርከት አልቻሉም፡፡
የከተማይቱ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር የተወሰኑ ሠራተኞች ችግር እንደሆነ ተጠቁሞ ሠራተኞች ለስንብት ቢዳረጉም የኤሌክትሪክ መቆራረጥና ለረጅም ግዜ መጥፋት የከተማይቱ ኢንዱስትሪዎች ፤ንግድ ተቋማትንና ነዋሪውን እያማረረና ህይወቱን እያመሰቃቀለ ከመሄድ ውጭ ምንም አይነት ለውጥ አልታየበትም፡፡ በከተማይቱ ውሃ ማግኘት እንደ ትልቅ እድል መቆጠር ጀምሯል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ የከተማይቱ 75% ነዋሪ ውሃ እንደሚያገኝ ቢናገሩም መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን በተቃራኒው ሆኗል፡፡ ጊዜያቸውን በትምሀርት ገበታቸው ላይ በመገኘት ማሳለፍ ይገባቸው የነበሩ ተማሪዎች ውሃ ለመቅዳት ረዥም መንገድ ለመጓዝ በመገደዳቸው የትምህርት ጊዜአቸው እየተበደለ ይገኛል፡፡

በአጠቃላይ ከተማይቱን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ የከተማይቱ ነዋሪ ለሚገፋው አስቸጋሪ ህይወት ተጠያቂ ነው፡፡ ድርጅቱ አገሪቱን የመምራት ብቃት እንደሌለውም የወቅቱ የአዲስ አበባ ሁኔታ አይነተኛ ማሳያ ነው፡፡

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የከተማይቱ ነዋሪ እየገፋው የሚገኘውን ፈታኝ ህይወት በማጥናት ህዝቡን በተለይም የከተማውን እና የዙሪያ አካባቢዋን ነዋሪ በማደራጀት በቅርቡ ‹‹የእሪታ ቀን›› በማለት ሰይሞ በ1ወር ጊዜ ውስጥ ሠላማዊ ሠልፍ ለማድረግ የወሰንን መሆኑን እየገለፅን የአዲስ አበባና አካባቢዋ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፉ በሚደረግበት ቀን በነቂስ በመውጣት በስርዓቱ ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ለመግለፅ እንዲዘጋጁ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
ድል የህዝብ ነው
መጋቢት 11 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም
አዲስ አበባ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

በመኢአድ በኩል የቀረበው ቅድመ ውህደት ያለመፈረም ሰበብ አሳዛኝና የሕዝቡን ጥያቄ ያኮሰሰ ነው!!

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ መግለጫ
Image
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ለረዥም ዓመታት የሕዝብ ፍላጎትና አንገብጋቢ የሆነውን ተቃዋሚዎች ‹‹ተባበሩ ወይ ተሰባበሩ›› ጥያቄ ለመመለስ በስትራቴጂና አምስት ዓመት ዕቅድ ውስጥ በማካተት መንቀሳቀስ ከጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ የውህደት ጉዳይ ለአንድነት ፓርቲ የአንድ ሰሞን ጥያቄ ሳይሆን ስትራቴጂክ ግብ ነው፡፡ የዚሁ አካል የሆነ እንቅስቃሴ በመኢአድና አንድነት ፓርቲዎች መሐከል መካሄድ ከጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ሂደቱን ለመቋጨት በርካታ ድርድሮችና የደብዳቤ ልውውጦችም ቢከናወንም እነሆ አሁንም ተጨባጭ ውጤት በተግባር አለመታየቱ የሁለቱም ፓርቲ አባላት በእጅጉ እያሳዘነ ነው፡፡
Image
በተለይ በቅርቡ እየተካሄደ ከነበረው ተግባር መካከል ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) መጋቢት 1 ቀን 2ዐዐ6 ዓም የተፃፈልንን ደብዳቤ መሠረት በማድረግ የሁለቱ ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች እንዲገናኙ የተጠየቀውን ጥያቄ በደስታና በላቀ መንፈስ ተቀብለነዋል፡፡ በዚሁ መሠረት መጋቢት 4 ቀን 2ዐዐ6 ዓም በሰጠነው የደብዳቤ መልስ ላይ እንደገለጽነው በአንድነት ፓርቲ እይታ አመራሩ የፊት ለፊት ውይይት የምንፈልገውና ወሳኝ ጉዳይ በመሆኑ መጋቢት 7 ቀን 2006 ዓ.ም በመኢአድ ጽ/ቤት በተጠራውና የሁለቱ ፓርቲዎች የብ/ም/ቤት አባላትና የላዕላይ ም/ቤት አባላት በተገኙበት ለታሪክ በተቀረፀ ወሳኝ ስብሰባ ሠፊ የኃሳብ ልውውጦች ተካሂደው የፓርቲዎቹ ከፍተኛ አመራሮች የሚከተሉትን አስገዳጅ የውሳኔ ሃሳብ አቅርበው ነበር፡፡
በዚሁም መሠረት፡-
የሁለቱም ፓርቲዎች አባላት አላስፈላጊ ጥቃቅን ጉዳዮችን በማንሳት ውህደቱን አታጓቱ ውህደት የማትፈፅሙ ከሆነ እኛ አባላት በራሳችን ውህደት እንፈፅማለን የሚል ጥብቅ ተማፅኖና ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል፡፡
በአጠቃላይ የሁለቱ ፓርቲዎች ፕሬዚደንቶችና አደራዳሪ ሽማግሌዎች በገቡት ቃል መሠረት ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም ቅድመ ውህደት የመግባቢያ ሰነድ እንዲፈረም ከስምምነት ተደርሶ ነበር፡፡
የሁለቱ ፓርቲዎች ከፍተኛ አመራሮች የውህደት አስፈፃሚውን ጠቅላላ ጉባኤ ጠሪ ኮሚቴ አባላት የሚሆኑትን የስም ዝርዝር፣ የፊርማው ስነ ሥርዓት በሚከናወንበት እለት እንዲያመጡ ተስማምተን ነበር፡፡
በከፍተኛ አመራሮችና በሁለቱ ሥራ አስፈፃሚዎች ውሳኔ መሠረት የሁለቱ ፓርቲ ፕሬዝደንቶች ተስማምተው፣ የቅድመ ውህደት መግባቢያ ሰነድ በሁለቱ ፓርቲዎች የድርድር ኮሚቴ አባላት መካከል ተፈራርመን፤ ሆቴል ተከራይተንና ከአዲስ አበባ አስተዳደር የሕዝባዊ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል የዕውቅና ሠነድ አግኝተን የመጨረሻ የስነ-ስርዓቱን መርሃ-ግብር በመጠባበቅ ላይ እያለን በድንገት በመኢአድ ፕሬዝደንት በኩል በቁጥር መ/ኢ/አ/ድ 278/06 መጋቢት 9 ቀን 2006 ዓ.ም በእለቱ የቅድመ ውህደት ፊርማውን መፈረም እንዳማይችሉ የሚገልጽ ደብዳቤ ለፓርቲያችን መድረሱ በእጅጉ አሳዝኖናል፡፡ ከደብዳቤው እንደተረዳነው መጋቢት 7 ቀን 2006 ዓ.ም የፓርቲዎቹ ከፍተኛ አመራሮች ከበርካታ የሃሳብ ልውውጥ በኋላ የደረሱበትን ውሳኔ የሚቀለብስ፣ የሁለቱ ፓርቲዎች ተደራዳሪዎች እየተስማሙ በቃለ ጉባኤ ያፀደቁትንና ከሁሉም በላይ የሁለቱ ፓርቲ ተደራዳሪዎች ለቅድመ ውህደት ባዘጋጁትና ባፀደቁት የመግባቢያ ሰነዶች ላይ የሰፈሩ ነጥቦችን እንደ አዲስ በማንሳትና በጥቃቅን ጉዳዮች በመጠመድ የቅድመ ውህደቱ እንዳይፈረም ተደርጓል፡፡ ለዚህ ታሪካዊና የሕዝብ ጥያቄ መደናቀፍ ምክንያቱ የመኢአድ ፕሬዚንት ሲሆኑ ይህን ሁኔታ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ለሚገኙ ለሁለቱ ፓርቲዎች አባላት፣ ደጋፊዎች፣ በግል ተነሳሽነትና በሀገር ተቆርቋሪነት ስሜት ሁለቱን ፓርቲዎች ለማደራደር ሲደክሙ ለነበሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎችና ለሕዝቡ ጥሩ ዜና ባይሆንም ላለመፈረሙ ኃላፊነቱን የሚወስዱት የመኢአድ አመራሮች በተለይም ፕሬዝደቱ መሆናቸውን ማሳወቅ እንወዳለን፡፡
በዚህ አጋጣሚ ለውህደቱ መሳካት የመኢአድ አባላትና ከፊል አመራሩ እያሳዩ ለሚገኘው ፍላጎትና ጥረት ፓርቲያችን መልካም አክብሮቱን መግለፅ ይወዳል፡፡
መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም

ይህ ትዉልድ ትክክለኛዉን መላ እስኪያገኝ ፋታ ስጡን እንላለን!

http://www.eaglewingss.com/%e1%8b%ad%e1 … %e1%8a%9d/

መላ ያጣ የጊዜአችን ሰሞንተኛ መካሪ ያጣ የቀንም የጭለማም አስማተኛ ፡፡ ደግሞ የተካነ ቶሎ የሚላመድ የሚያላምድ፣እባብን ከርግቡ ምላስን ከሆዱ፤ ደግሞ አዋኪም ኣዋቂም የምላስ ዳንኪረኛ፡፡

አንዳንዴ አበሻ የዋሁ ያዳምና የ ሔዋን ጠላት እባብ ነው ብሎ የራሱን ምላስ ትቶ የባቢቱን ሲጠነቀቅ ይኖራል ፡፡ አሁን አሁን እኮ ተናዳፊዉ ሰዉ ነዉ፡፡ ተናዳፊዉ እባብ ቀረና ሰዉ መርዘኛ እባብ ሆኖዋል ሂዩማን ቬኖም (human venom)፡፡ እናም ታዲያ የሰሞንተኛዉ አስማተኛ ምላስ ነገረ ስራዉ ሁሉ በምላሱ መርዝ የዋሁንም የሱንም አጫፋሪም ተቃዋሚም በራሱ መርዝ በክሎ አንድ ላይ ወደ ራሱ የሆድ ከርስ አንጦርጦስ ለመክተት የተነሳ ይመስላል፡፡

የምላስና የሆድ አስማተኛ ይቅርታም ይሉኝታም የሌለዉ ብቻ የሱ ስራ በነዛ በረጂም ለሁለት በተሰነጠቁ መርዛማ ምላሶቹ አሳስቶም አሞኝቶም ፤አግባብቶም አቆላምጦም፤አባብሎም ያ ካልሆነም ደግሞ እንደግዜው መስሎም ከዚህም ከዚያም ያገኘዉን ወደዚያ መዉጪያ ወደሌለዉ የከርስ ዎይንም የሆድ አንጦርጦስ መክተት ነው የሱ ዓላማ፡፡

ዛሬ እዚህ ያለንበት የፈረንጆቹ ማህበረሰብ ዉስጥ በተመስጦ እሚወያዩት ስለ ምህዋር ጠፈር ብላክ ሆል ስለሚሉት የስበትን ሚስጥር ሰለማወቅ ነዉ ሚስጥሩን ሳይንሳቸዉ ገና ትክክለኛዉን መልስ ባያገኝም፡፡ ዛሬ ዛሬ ግን የዕኛን የፖለቲካ አዙሪትና ስበት ብንፈልገዉ ደግሞ የሰዉ ሆድ ዉስጥ ሆኖዋል እምናገኘዉ ፡፡ሆድም ብላክ ሆል (black hole) ሆነ ላበሻ ፡፡ትዉልዱ ለፖለቲካ ለዉጥና ለመልካም አስተዳደር ለፋትሕና ለዲሞክራሲያዊ ለዉጥ ይታገላል ፣ነገር ግን ደግሞ ትግሉ በሆድ ዎይንም በከርስ ስበት ምክንያት ተኮላሽቶ ይኸዉ የዚህ ትዉልድ ስቃይና መከራ እንደ ዓዲስ እየትራዘመ ይገኛል፡፡

ባሁኑ ዎቅት ኢትዮጽያና ኢትዮጵያዉያንን ስላለባቸዉ የማህበራዊ የምጣኔ ሃብታዊ ፖለቲካዊ ችግሮች ተስታከዉ በሚካሄዱ ባስመሳዮችና ባላዋቂዎች ፖለቲከኛ ነን ባዮች ምክንያት የትግሉ አቅጣጫ ላይ ደንቃራ ሆነዉ ይታያሉ፡፡እነዚህ መርዛማ አስመሳዮች በዘመናዊ አዳራሾች በዘመናዊ የመገናኛ መረቦች የመላዕክትም የፃዲቅም የሴይጣንም ፤የታዋቂ ሰዉ ስምም የጅግናም ሰዉ ስምና ክብር ፤በምላሳቸዉና በባዶ እራሳቸዉም ላይ እየጫኑ ፡ቡድን እያበጁ በመዋገን በፖለቲካ ዕምነት፥ በፖለቲካ አመለካከት ዎይንም ደግሞ በምክንያታዊነት ሳይሆን፡ እንዳዉ ብቻ ለጥቅም አሊያም በመንደርተኝንትና በጥላቻ ባዶ ኢትዮጵያዊኛ ከበሮ ዕየተደለቀ እርስ በርስ ሲቆለማመጡ ሲካካቡ እና የኮሚቴ ሹምና የቴሌቭዥን የክብር ዕንግዳ እየተደራረጉ ሲካካቡ ከርመዉ ዛሬ ደግሞ አንዱ አስማተኛ ድንገት ከጉያቸዉ አፈትልኮ ወጥቶ የጥንት የጠዋቱን ከነጉዲት በፊት ያመልክ የነበረዉን ዋናዉን ሴይጣን መልሶ ተቀላቅሎ ዛሬ ሌላ ዙር ነጋሪት በተቃዋሚዉ ፓርቲና ማህበረሰቡ ላይ ዕየተጎሸመ ያለኛ በቀር የፖለቲካ መንገድም እዉነትም ሐርነትም የለም እየተባልን ነዉ፡፡

ዛሬ በሁለቱም ጎራ የሚታየዉ የባዶ ዓርበኝነት ድራማ የብዙሃኑን ህዝብ የለዉጥ ጥያቄና የዚህን ወጣት ትዉልድ ትግል እያጓተተና እየጎዳዉ ይታያል፡፡ለዚህም የሚታዩት ምክንያቶች ያላዋቂ ሳሚ መብዛትና ፥ያመራር ችግር፤ተጠያቂነት የሌለዉ የባለሞያና የፖለቲካ አናርኪዝም (anarchism) ዋናዎቹ ችግሮች ቢሆኑም እነዚህን ችግሮች ተንተርሰዉ ዘመኑ ባፈራዉ የሜድያ መረቦች የመስኮት (window )አስመሳይ ፖለቲከኞች ማን እንደኛ ለ ኢትዮጵያ የሚሉ ስግብግቦችና ራስ አድናቂ (narcissist) በ ኢትዮጵያ ህዝብ የለዉጥ ትግል ላይና በዚህ ዓዲስ ወጣት ትዉልድ የለዉጥና የዲሞክራሲያዊ ጥያቄ ላይ ትልቅ የተህዋስ ወረርሽኝ (virus epidemic) ሆነዉበት ይገኛል፡፡

ከድሮ ጀምሮ አንድ የለመድነዉና ያደግንበት አጉል ባህል አለ፡፡ ወቅታዊ ያልሆነ ዘመንተኝነት አብሮን አድጎ ይኸዉ ይኼን ኮተታችንን እዚህም እሰዉ አገር አምጥተን እርስ በርስ መደናቆር ይዘናል፡፡ ባንድ ዎቅት ንዋይ ደበበ የ ጥቅምት አበባ ነሽ አሉ ብሎ ዘፍኖ ጠዋትም ማታም በበጋም በክረምትም ትንሹም ትልቁም የዘፍነዉ ነበረ ከዛም ደግሞ ሐይልዬ ታደሰ የተባለ ድምጻዊ ይሞታል ዎይ ታዲያ ( Link )እምትለዉን ዘፈን አዉጥቶ በማህበረሰቡ ዉስጥ በጣም ከመደጋገሙ የተነሳ በግዜዉ የነበረዉን ማህበረሰባዊ ነዉር ማህበረሰባዊ የሞራል ዝቅጠት ራሱ ኪነትና ስነጥበብ አብረዉ ዓብረዉ ቡሄራዊ ነዉራችንን አንድ ላይ ስንዘፍነዉና ዳንኪራዉም ሲመታ ነበረ፡፡ ታድያ በግዜው የነበረዉ ማህበረሰባዊ ነዉር ከመደጋገም (cliches) ከመሆን አልፎ ግቦ ስጭም ግቦ ተቀባይም ራሱ ተጎጂዉም ማህበረሰብ ነዉሩን አብሮ ይዘፍነዉ ነበር፡፡ ዛሬም ያለዉ የሆድ ዎይንም የከርስ ነዉራችንን በትንሿ መስኮት (window) ዳንኪራዉ እየተመታልን ጠዋትና ማታ የግዜዉን ተደጋጋሚ ቃላቶች መስማት ግድ ይሏል፡፡የዘንድሮ የፓልቶክ አድማጭ እና እራሱ ፓልቶክ (paltalk) ክፍሉም እዛዉ አገራችን እንዳሉት የነ መላዉያኑ ሰፈር የመርካቶ ሙዚቃ ቤቶች ሲመስል ሰዉም ደግሞ ሙዚቃ ቤቶቹን ከቦ እሚዉለዉን መስሎኣል ፡፡

እዚህ በዳያስፖራዉ የዕለት ተዕለት ኑሮ ዉስጥ ለኑሮ ማደላደያና ለእንቶ ፈንቶ የፖለቲካ ፍጆታ መገልገያ ተደርገዉ የተያዙ የዘመኑ ተደጋጋሚ ቁልፍ ቃላቶች (cliches) ሆነዉ የቀሩ አሉ፤ለምሳሌ ብንወስድ፣ ኢትዮጵያዊ ዓርበኛ፤ ዎያኔ ሻዕቢያ ፤ግንቦት ሰባት አሸባሪ አዋኪ፤ዎይንም (terrorist) ባንዳ ሆዳም፤ ቅጥረኛ ሰላይ፤ እነዚህ ክሊሸስ (cliches) በገዢዉ መደብም ሆነ በተቃዋሚዉ ጎራ ሲያስፈልጋቸዉ ማዕረግ መስጫ ካስፈለገም ማዉገዢያና ማጥቂያም ማሰሪያም ሆነዉ ያገለግላሉ፡፡ማናቸዉም ነፃ የሆኑ አስተያየቶችና አመለካከቶች በነዚህ የዘመኑ የዳያስፖራ ፖለቲከኞች ዘንድ የስም ተቀፅላ ዎይንም ታፔላ እየተለጠፈላቸዉ በቀጥታ የነሱን የፖለቲካ ገበያና ህልዉና እንዲያስጠብቁ አርገዉ የጠቀሙባቸዋል፡፡

ዛሬ እየሰማን ያለነዉ የፖለቲካ ዓመለካከት ልዩነትን ዎይንም የፖለቲካ ዕምነትን ሳይሆን ይልቁንስ የግለሰቦችን የሆድ እና የዓመል ዥዋዥዌ እንደትልቅ የፖለቲካ አጀንዳ በየመገናኛ መረቡ ላይ ሲያራግቡት ነዉ፡፡ ዛሬ ይህ ትዉልድ እነሱ ባጨማለቁትና ባመሳቀሉት አሁን ድረስ እየተሰቃየበት ነዉ ፡፡ማህበረሰቦች በግለሰቦች ምላስና ሆድ ዋጋ እየወጣላቸዉ ማንም ባተሌ እየተነሳ የፈለገዉን ስም በራሱ ላይ እየጫነ በስደት ያለዉን ነፃ ማህበረሰብ እያመሱት ይገኛሉ፡፡እሚገርመን ደግሞ ከመላዉያን ሰሞንተኛ አስማተኛ ሰሞኑን የወሰደዉ በቀል አይሉት ክህደት፣ ቅጥፈት አይሉት ስሕተት፣ ርካሽ የፖለቲካ ኮተት፤ተዓማኒነት ዎይንም ደሞ ተቀባይነት እንዲያገኝና የነፃዉን ህብረተሰብ ድጋፍና ቀልብ ለመሳብ የብዙሃኑን የልብ ትርታ አፈንፍኜ አግኝቻለዉ በማለት ባዶ ዲስኩር ሲያረግ ከርሞአል ፡፡

ዛሬ ባብዛኛዉ ኢትዮጵያዊ በዝምታ የሁለቱን የውሸት ዓርበኞች ዳር ሁኖ የቆመበትን ምክንያቶች ይኸዉ ተዓምረኛ አስማተኛ ለከርሱ ፍጆታ ሲል እንደፖለቲካ አቝዋምና በዝምታ ላለዉ ህብረተሰብ ደርሶ አሳቢ ሆኖ ይህንኑ ማህበረሰብ እንደ አንድ ዕምቅ የተፈጥሮ ሃብት የፖለቲካ ገፀ በረከት አድርጎ እዛዉ ላለዉ የገዢ መደብ ለማቅረብ ባዶ የዓርበኝነት ዕምቢልታ እየተነፋ ይገኛል።ይብላኝልኝ ግን በደመቀበት ሲደምቁ ለነበሩ አዋቂ ነን ባዮች ፣በዘር በሃይማኖት ፣በእከክልኝ ልከክልህ ፣ በሰዉ ያንገት ስፋት ፣በከርሱ ስፋት ፣ወርድና ቁመት ማዕረግ እየሰጡ ሆይ ሆይ ሲሉ ለነበሩ ይብላኝልኝ።

በነዚህ አስመሳዮች ከርስ እዚህም እዚያም አሁንም ድረስ እንደትንሿ የጠረጴዛ ኳስ ሲመቱና እየተመቱ ላሉ ፣እነሆ ከያለንበት እንዲህ እንላለን፡፡ ዛሬ የምናያቸዉ የመድረክ ተዋንያን በትንሽዋ መስኮት (window) እየተወኑ ያሉት የፖለቲካ ተዉኔት በራሳቸዉ ድርሰት እራሳቸዉንና ቡችሎቻቸዉን እየተውኑ መሆኑን እንዲያዉቁት ። መላ ያጣዉ ይህ ትዉልድ ግን ትክክለኛዉን መላ እስኪያገኝ ፋታ ስጡን እንላለን።

ምንሊክ ሳልሳዊ :- በዚህ ሳምንት አትክሮት ማግኘት ከሚፈልጉ ወገኖቻችን በዋነኝነት በኩዌት የሚኖሩ እና በስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ናቸው:: ባሳለፍነው ቀናት በዋና ዜናነት በአገሪቱ የስፖርት ሚኒስትር መኖሪያ ቤት ውስጥ የምትሰራ ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ የአሰሪዋን ሴት ልጅ ገላለች ተብሎ የተዘገበውን ዜና ተከትሎ ኢትዮጵያውያን በስጋት ላይ ሲሆኑ እንዲሁም ተከራካሪ የዜግነት መብታቸውን የሚያስከብር ኤምባሲ መጥፋቱ እና በኤምባሲው የሚፈጸመውን ደባ በከፊል ለማየት እንሞክራለን::

የዚህ ዘገባ ምንጮች በኩዌት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ተጨማሪ መረጃ ያላቸው ሊልኩልን የሚችሉ መሆኑን ለመግለጽ እወዳለሁ:: መረጃውን ላደረሱን ወገኖች ምስጋና አቀርባለሁ::
ምንሊክ ሳልሳዊ
በአሁኑ ወቅት በኩዌት ለኢትዮጵያውያን ነገሮች ሁሉ አስቀያሚ እና አስቸጋሪ እየሆኑ እንደሆን ለኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ቅርብ የሆነ ኢትዮጵያዊ ገልጿል::ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደረጉ በደሎች ተከራካሪ የመንግስት አካል እና የኤምባሲ ሰው መጥፋቱ ለአሁኑ ወንጀል መፈጸም እና ስጋት መንስኤ እንደሆነ ጠቁሟል::በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሱ በደሎች እና ከአሰሪዎቻቸው እና ከቀጣሪ ድርጅቶች ጠፍተው የሚመጡ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሃገራቸው መመለስ ሲገባው ከደላሎች ጋር በመመሳጠር ሌላ ስራ በማስገባት ችግሩ እንዲሰፋ ያደረገው እምባሲው እና ሆዳም ዲፕሎማቶቹ ናቸው ሲል ይኸው የኮሚኒቲው ሰው ገልጿል::

ኢትዮጵያውያን በኩዌት እስር ቤት እየተሰቃዩ ከፍተኛ ወጪ ከኤምባሲው እና ከኮሚኒቲው በማውጣት ደግሰው በመጨፈር ላይ በነበሩበት ሰአት ከኢህ ቀደም ከፍተኛ ተቃውሞ የገጠማቸው ሲሆን ወገኖቻችን በእስር ቤት እየተሰቃዩ ለምን እንዲህ አይነት ድግስ ይደገሳል:: አስፈላጊውን ወጪ በማድረግ ወደ ሃገራቸው የሚመለሱ ይመለሱ ያሉ ወገኖችን የተለያየ የኤምባሲ ትብብር በመከልከል ወደኤምባሲው በር እንዳይደርሱ በማገድ ከፍተኛ የሆነ የግል ጥቅምን ያማከለ በደል እየተፈጸመ መሆኑን የኮሚኒቲው ሰው አጫውቶናል::ለማንም ተደግሶ የማያውቅ ኮሚኒቲው የኢትዮጵያ ሆኖ እያለ ለሌሎች ኢትዮጵያውያን እና ግለሰቦች ሳያገለግል የትግራይ ልማት ማህበር አላማን ሲያስተምር ይውላል ሲሉ አባላቱ ይተቹታል:: የታሰሩትን ለጊዜው ተወት አድርጓቸው እና የሃገራችንን መልካም ገጽታ እናስተዋውቅ እያሉ ለዜጎች አትኩሮት በመንፈግ አሁን ላለንበት ስጋት አብቅተውናል ሲሉ ኢትዮጵያውያን በማማረር ይናገራሉ::

ኮሚኒቲው ሲቋቋም ለታሰሩ እና ለተቸገሩ መፍትሄ ይሆናል ተብሎ የነበረ ቢሆንም በስሙ መካከል ህዳሴ የሚል ቃል በመጨመር ቢሮውን ከነበረበት ቦታ ወደ ኤምባሲው ውስጥ በማዘዋወር ፖለቲካ እየሰበከ ኢትዮጵያውያንን ረስቷል ሲሉ ይናገራሉ::ሌላው ነገር ይላሉ ኢትዮጵያውያኑ ማንኛውንም ደብዳቤ በኤምባሲውም ይሁን በኮሚኒቲው ማህተም ተደግፎ ቢጻፍ በኩዌት ውስጥ ተቀባይነት የለውም ሲሉ ይገልጻሉ::የመኖሪያ ፈቃድ ለማሳደስ በእጃችን ፓስፖርት እያለ ፓስፖርቱን ለመቀበል የኩዌት መኖሪያ ፈቃድ የሚያድሰው አካል ብዙ መጉላላት እና ወከባ እንደሚፈጽምባቸው እና ይህንንም ለኤምባሲው ሪፖርት ቢደረግ የራሳችሁ ጉዳይ የሚል ዘለፋ አዘል መልስ እንደሚሰጡ ታውቋል::

በግድያ ወንጀል ተጠርጥራ የተያዘችው ኢትዮጵያዊት ተከትሎ የመኖሪያ መታወቂያዎች እንዲታደሱ መደረግ የጀመረ ሲሆን ካሁን በፊት NON KUWAITI የሚል ሲጻፍ የነበረ ሲሆን በኣሁን ሰአት ለኢትዮጵያውያን በተለየ መልኩ Ethiopian ኢትዮጵያዊ የሚል መጻፍ የተጀመረ መሆኑ ታውቋል::

የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ምንም መከራከር የማይችል እና በመኪና ተገጭተው የሞቱ ታንቀው ራሳቸውን ከፎቅ ወርውረው የሞቱ ኢትዮጵያውያን ደብዛቸው እና የሞት ጉዳያቸው እንዳይነሳ ኮሚኒቴው በመሸፋፈን ለችግር እየዳረገን ነው ሲሉ በኮሚኒው ላይ አማረዋል::በ17 አመቷ ወደ ኩዌት የገባችው እና በአሁን ሰአት የ22 አመት ወጣት የሆነችው በግድያ ተጠርጥራ የተያዘችው ኢትዮጵያዊት በአሰሪዎቿ ልጆች የተደፈረች መሆኗን ለኤምባሲው ቅርብ የሆነ ግለሰብ ተናግሯል::ግድያውን ከመፈጸሟ በፊት በልጁ የተደፈረች እና ይህንን ጉዳይ ለሴት ልጂቷ ብትናገር የሚሰማት ያጣት እና የደበደቧት መሆኗን እና ይህንን ተከትሎ ወንጀሉን ፈጽማው ይሆናል የሚሉ ግምቶች በስፋት ይነገራል::

በኢምባሲው ውስጥ የሚደረገው ከፍተኛ በደል በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ሲሆን በኤምባሲው ውስጥ ከ400 እስከ 500 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን የሚገኙ ሲሆን: ከፍተኛ የሆነ መጉላላት እየደረሰባቸው ለኣእምሮ ጉዳት ለጭንቀት ለድብርት እና ለእብደት መዳረጋቸውን የገለጹ ሲሆን በኤምባሲው ውስጥ ከፍተኛ የምግብ እጥረት ያለ ሲሆን ኤምባሲው ግን በድግስ እየተንበሸበሸ ኮሚኒቲው በየድህረገጹ የፌሽታ ፎቶዎችን በመርጨት ከፌሽታው ጀርባ ግን የኢትዮጵያውያን ሞት እና ሰቆቃ ለእይታ እንዳይበቃ እያደረገ ሲሆን አንድም ቀን የሞቱ እና የተበደሉ ኢትዮጵያንን ቦታ ሳይሰጥ የኢትዮጵያውያን መብት እና ነጻነት ሳያስከብሩ በአደባባይ ስንገላታ እያዩን ያላግጡብናል ያመናጭቁናል ከፖሊስ ጋር ይተባበሩብናል በማለት አቤቱታቸውን የሚሰማ አካል እንዳላገኙ እና በስጋት አጣብቂኝ ውስጥ መግባታቸውን ኢትዮጵያውያን ተናግረዋል:: ተጨማሪ ዘገባዎች ካሉ እንመለሳለን:: ምንሊክሳልሳዊ

በማስመሰል ታጥሮ መሆን በጠፋበት
ምን አገባኝ የሚል በተከማቸበት
የባይተዋር መንፈስ ከሞላ ባገሩ
ዘመኑን ማወቂያ ይሄ ነው ሚስጥሩ
ይሄን ጊዜ ጠርጥር እንደጠፋ ዘሩ፡፡
(ገጣሚ ደምሰው መርሻ/ያልታተመ)

አዎን፣ ገጣሚ ደምሰው እንዳለው እኔም በዚህ ዘመን “ዘሩ እንደጠፋ” አሊያም ሊጠፋ እንደተቃረበ እጠረጥራለሁ፡፡
ስለምን? ቢሉ …በኢትዮጵያችን ለህሊናው፣ ለሕዝብና ለሀገሩ የሚቆረቆር፣ የእውነት ተሟጋችና የሞራል ልዕልናን የተቀዳጀ ሙሉ ሰው ፈልጎ ማግኘት እጅግ አተካች ሆኗልና፡፡ የግል ጥቅም አሳዳጅ፣ አፋሽ-አጎንባሽ በሞላበት፣ እንደ ቴዎድሮስ ለሀገር ቤዛ መሆን፤ እንደ ግርማሜዎቹ እና ወርቅነህ የራስን ምቾት ወዲያ ጥሎ በጠገበ ሆድ ከወገን ጋር መራብና ከጎኑ መቆም፤ እንደ አቶ ሽፈራው ደሳለኝ አስፈሪ ሞት ከከበበው ሸለቆ ውስጥ በህይወት ለመውጣት ሲባል የጠላትን ጫማ ከመላስና ያላመኑበትን ተናግሮ ምህረት ከመጠየቅ ይልቅ በድፍረት ሞትን ፊት ለፊት መጋፈጥ ወይም ግንባርን ለአረር መስጠት እንደ ተረታ-ተረት ከተቆጠረ ዘመናት አልፏል (አቶ ሽፈራው ደሳለኝ ማን ናቸው? ለሚለኝ አንባቢዬ ‹‹የታኀሣሡ ግርግር እና መዘዙ›› የተሰኘውን የብርሃኑ አስረስ መጽሐፍ ገፅ 302ን እንዲያነብ እጋብዘዋለሁ) አሊያም ደግሞ የሰው ዘር በመሆን ብቻ የሚገኘውን የሞራል ልዕልና ከትውልድና ሀገር ጥቅም አኳያ ለማጠየቅ በዚህ አውድ ለማነሳው ተጠየቅ በአንፅሮ ለማፍታታት ይጠቅመኝ ዘንድ እኔው ራሴ እዚሁ ጠቅሼው አልፋለሁ፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ‹‹በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ጊዜ የድጋፍ ንግግር አድርጋችኋል በማለት በመንግስት ተይዘው ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ከተላኩት አንዱ የሆኑት…›› ብለው ከአቶ ሽፈራው ደሳለኝ ጋር ከአስተዋወቁን በኋላ እንዲህ በማለት ትርክታቸውን ይቀጥላሉ፡- ‹‹…አቶ ሽፈራው ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ ተልከው ለፖሊስ ቃላቸውን ሰጥተው ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ የእምነት ክህደት ቃል ሲጠየቁ ዳኛው ‹ሠርተሃል ለተባለው ወንጀል ጥፋተኛ ነህ፣ አይደለህም?› ይላቸዋል፡፡ ‹የቱን ወንጀል?› ሲሉ አቶ ሽፈራው ዳኛውን ይጠይቃሉ፡፡ ዳኛው አቶ ሽፈራው ሠርተዋል የተባለውን የወንጀል ቃል ሊናገሩት አልወደዱም አልደፈሩምምና ‹አንተ የሠራኸውን?› ብለው ጠየቁ፡፡ አቶ ሽፈራው ‹እስቲ ወንጀል የተባለው ይነበብልኝ› ብለው አጥብቀው ይጠይቃሉ፡፡ ይሄን ጊዜ ዳኛው ሳይወዱ ‹ይህን ጣሳ እግዚአብሔር ገላገለን፣ አወረደልን ማለትህን፤ …ለዚህ ጥፋተኛ ነህ አይደለህም?› ይሏቸዋል፡፡ ‹የለም ተስተካክሎ ይጻፍልኝና እምነት ክህደቴን ልናገር› ይላሉ፡፡ ‹የለም በዚህ ላይ ጥፋተኛ ነኝ በል› ይሏቸዋል፡፡ ‹ትክክለኛ ቃሌ ይጻፍና ነው እንጂ እንዲሁ ጥፋተኛ ነኝ፤ አይደለሁም፤ አልልም› ብለው ይመልሳሉ፡፡ ‹እሺ ምን ተብሎ ይስተካከል› ሲሏቸው፤ ‹ይህን የበሰበሰ የተጠረማመሰ አሮጌ ጣሳ እግዚአብሔር ገላገለን ነው ያልኩት› ሲሉ ዳኞቹ የተባለውን አልሰማንም ለማለት ራሳቸውን ጠረጴዛ ስር አግብተው ተደበቁ፡፡››
በዚህ ዘመን ራሳቸውን ጠረጴዛ ስር አግብተው እንደ ሰጎን አንገታቸውን ቀብረው በፍርሃት የሚኖሩ አድር፣ እበላ-ባይ፣ ፈሪ ሰዎች የአቶ ሽፈራውን ባመኑበት መቆም እንደ አጎል ጀብደኝነትና ሞኝነት ቢቆጥሩት አስገራሚ አይሆንም፡፡ የሆነው ሆኖ እንደ ብልህነት አሊያም ብልጥነት ተደርጎ የሚወሰደውን የአድርባይነት ‹‹ስልት›› ለማሳየት አንዲት ሀገርኛ ምሳሌ እዚህ ጋ ለንፅፅር ላቅርብና እንደ ፕሮፌሰር መስፍን ለራሴ ጽሑፍ ‹‹F›› ከመስጠቴ በፊት ወደ አጀንዳዬ ልዝለቅ፡፡
ታሪኩ ዝናው በስፋት የናኘ ሽፍታ የመሸገበትን (ግዛቱ ያደረገ) ጥቅጥቅ ያለ ጫካ አቋርጦ ስለሚያልፍ መንገደኛ ገጠመኝ ነው፡፡ መንገደኛው ለሰዓታት ከተጓዘ በኋላ ድንገት ሽፍታው እጅ ይወድቅና ስንቅ የቋጠረበትን ስልቻ ጨምሮ ከላይ እስከታች ይበረበራል፤ ሆኖም ሰባራ ሳንቲም ሊያገኝበት ባለመቻሉ ከመጠን በላይ የተበሳጨው አያ ሽፍታ ሆዬ ንዴቱን ለማብረድ ሲል ‹‹ውዳሴ ዜማ አቅርብልኝ!›› በማለት ቀጭን ትዕዛዝ ይሰጠዋል፤ በፍርሃት ነፍሱ እጉሮሮው የተወተፈችበት መንገደኛም ተንፈስ ብሎ ለመረጋጋት እየሞከረ እንዲህ ሲል አቀነቀነለት ይባላል፡-
‹‹አይኑ የተኳለ ጠላት የሚጋረፍ
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ 2
ጠብ-መንጃ ገስጋሽ ጉብታ ተሻግሮ
ከዘብጥ የሚናደፍ
እንደሚካኤል ነህ ጠላትህም አይተርፍ!››
እነሆም የሀገሬ ምድር እንዲህ ባሉ ሀሞተ-ቢስ አወዳሾችና አስመሳዮች ተጥለቅልቃ እጆቿን ወደ ሰማይ ከዘረጋች (ሱባኤ ለመግባት) ሰነበተች፡፡ በርግጥም ከብዙሀኑ በተሻለ ማንሰላሰል ይሳናቸዋል ተብለው የማይታሰቡ ‹‹ምሁራን››ም ሆኑ ‹‹መንፈሳዊ››ነታቸው የበዛ የኃይማኖት መሪዎች በግል ጥቅመኝነት ታውረው ከስርዓቱ ጋር እጅና ጓንት በመሆን የጭቆና አገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም በሀሰት መስካሪነት የቅጥፈት ምላሳቸውን ሲያንበለብሉ መስማት ‹እግዚኦ› የሚያስብል አስደንጋጭ መናፍቅነት መሆኑ ቀርቶ እንደ ተራ ነጋዴ ንግግር፣ ተራ የዕለት ተዕለት አጋጣሚ ከሆነ ዘመናት ተቆጠሩ፡፡ ‹‹መንፈሳዊያን›› አባቶች በተከበረው ቤተ-መቅደስ ምኩራብ ላይ ከመእምናኑ ፊት ለፊት ቆመው ቃየልን ‹‹አቤል››፣ በርባንን ‹‹መሲህ›› በማለት ሲሰብኩም ለአመል እንኳ ድንቅፍ አያደርጋቸውም፤ ከግላዊ ጥቅማቸው አሻግረው የግፉአንን የስቃይ እሮሮ ማድመጥም ሆነ ለሌላው ማሳወቅ ጭራሹንም አይሞክሩትም፡፡ ‹‹ምሁራን›› ተብዬዎቹም አርቲስት ሰለሞን ተካልኝ ‹‹ውበት ከቅንድቡ የሚፈስ›› እንዲል፤ ‹አይኑ የተኳለ› እያሉ በሕፃናት ደም ሳይቀር የጨቀየውን ኢህአዴግ መራሹን መንግስት እንዴት እንዴት ‹ብፁእ› አድርገው የውዳሴ ከበሮ ሲመቱለት እንደሚያድሩ እዚህ ጋ ዘርዝሮ ለማቅረብ ማሰብ አባይን በጭልፋ አጋብቶ ለመጨረስ እንደመሞከር ያለ ዕብደት ያስቆጥራል፡፡
ወጣም ወረደ እንዲህ አይነቱ የሞራል ዝቅጠት በትላንት ወይም በዛሬ የእድሜ ገደብ የሚለካ አለመሆኑን በድፍረት መናገር ይቻላል፤ ምክንያቱም በነገሥታቱ የአገዛዝ ዘመን የጀመረና በጣሊያን የአምስት ዓመቱ የወረራ ወቅት እንደወረርሽኝ የተስፋፋ ስለመሆኑ በቂ ማሳያዎች አሉ፡፡ ይህ እንግዲህ ‹‹ሀገር›› ለተሰኘ ማህተም መስዋዕት የሆኑትን አቡነ ጴጥሮስን የመሳሰሉ ታሪክ በታላቅ አክብሮት የሚዘክራቸውን ቀዳማይ አባቶችና እናቶችን ሳንዘነጋ ነው፡፡ እናም የሩቁን ትተን ከ1983ቱ የመንግስት ለውጥ ወዲህ ያለውን እንኳ ብንመለከት ይህን መሰሉ ክስረት ዙሪያችንን ከቦ ሊውጠን የቀረው ስንዝር ታህል ርቀት ብቻ መሆኑን ለመረዳት የማሕበራዊ ሳይንስ ምሁራን ትንታኔን ማገላበጥ አይጠይቅም፡፡ ያኔ ገና በለውጡ ማግስት ህወሓት እና ሻዕቢያ በአንድ አንቀልባ ካልታዘልን በሚሉበት የ‹‹ጫጉላ›› ዘመን፣ ከኤርትራ ምድር የወርቅ ጥርሳቸው ሳይቀር በጭካኔ ወልቆ ባዶ እጃቸውን የተባረሩ ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ በጉምቱው ምሁር ፕሮፌሰር እንድሪያስ እሸቴ የተመራው አጣሪ ቡድን ‹‹ውሸት ነው! ይህ አይነቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ኤርትራ ይኖሩ
በነበሩ ኢትዮጵያውያን ላይ አልተፈፀመም!!›› በማለት አይኑን በጨው አጥቦ በድፍረት ሲያስተባብል፣ አንጀታችን እያረረ ‹‹ይሁና!›› ብለን በትዝብት ማለፋችን እውነት ቢሆንም፤ የዝምታችን ውስጠ-መልዕክት ያልገባው ፕሮፌሰሩ ግን ያረረው አንጀታችን ይበልጥ እርር ይል ዘንድ በተለመደው ቅጥፈቱ ታላቁ የዐድዋ ድል ባለቤትነትን ከሀገር ከፍታ፣ ቁልቁል ወደ ጎጥ ለማውረድ ያልፈነቀለው ቋጥኝ፣ ያልማሰው ስር አልነበረም (በነገራችን ላይ ህወሓት ዛሬም ከዐድዋ ድል ጀግኖች ጋር ጥቁር ደም እንደተቃባ በግላጭ የሚያመላክተው በዘንድሮው 118ኛው ክብረ በዓል ላይ የተስተዋለው አሳፋሪ ትእይንት ነው፡፡ ይኸውም በታሪካዊቷ ዐድዋ ከተማ በሚገኘው ሶሎዳ ተራራ ስር ‹ድሉን ለመዘከር› ከተሰቀሉት የእቴጌ ጣይቱ፣ የራስ አሉላ አባነጋ፣ የባልቻ አባነፍሶ እና የባሻ አውዓሎም ግዙፍ ምስሎች መሀል የተሸናፊው ሀገር ህዝብ ሳይቀር በድሉ ዕለት ሮማ በተሰኘው አደባባዩ ‹‹ቪቫ ምኒሊክ›› እያለ በታላቅ ጩኸት ያወደሰው የታላቁ ንጉሠ ነገሥት ምስል አለመካተቱ ነው፡፡ …መቼም ይህ ለምን ሆነ? ብለን የክልሉን አስተዳዳሪ ጓድ አባይ ወልዱን ብንጠይቀው ‹‹በጦርነቱ ወቅት ምኒሊክ መሸሽ ጀምሮ ነበር›› የሚለውን ዝነኛ ህወሓታዊ ትርክት ገልብጦ፣ ‹‹በስራ መደራረብ በተፈጠረ ስህተት ነው›› ብሎ በክፍለ ዘመኑ ታላቅ ሽርደዳ አንጀታችንን ይበልጥ ድብን እንደሚያደርገው ቅንጣት ታህል አትጠራጠሩ)
ለማንኛውም እንደ ፕሮፌሰር እንድሪያስ ያሉ በድሃው ሕዝብ ጥሪት የከፍተኛ ደረጃ የትምህርት ዕድል ማግኘት የቻሉ በርካታ እበላ-ባይ ‹‹ምሁራን›› ስርዓቱ የሥልጣን ዘመኑን ለማራዘም የሚያምታታበትን ‹‹የሁለት ዲጂት የኢኮኖሚ ዕድገት›› የፈረንጅ ጥናቶችን በጥራዝ-ነጠቅነት እያጣቀሱ ምክንያታዊ መስለው ሊያሳምኑን በከንቱ ብዙ ደክመዋል፡፡ በአናቱም የመከላከያ ሠራዊቱ ለባዕድ ሀገር ጥቅም ሲባል ሶማሊያን በወረረበት ወቅት አንዳንድ የዩንቨርስቲ መምህራን እና ‹‹የፖለቲካ ተንታኞች›› በመሬት ያለውን ተጨባጭ እውነታ ይሁነኝ ብለው ወደጎን ገፍተው አገዛዙ ቀን ከሌት ‹‹እመኑኝ!›› በሚል ጩኸት ያሰለቸንን ሰበብ፣ በጥናት እንደተረጋገጠ አስመስለው ለመተንተን ያደርጉት የነበረው እሽቅድምድም ሁሌም በሀዘን የምናስታውሰው ነው፡፡
የኃይማኖት መሪዎችም ምንም እንኳ በነቢብ የአገልግሎታቸው ዋጋ በፈጣሪ መንግስት መሆኑን ደጋግመው ቢነግሩንም፣ በሀልዮ የሚታየው የአሸርጋጅነት ግብራቸው ግን ምድራዊውን ጨቋኝ ስርዓት ደግፎ የሚይዝ ምሰሶና አቅፎ የሚያሞቅ ክንድ ከሆነ በርካታ አስርታት ተቆጥረዋል፡፡ የእስልምና እምነት የበላይ ወሳኝ አካል የሆነው መጅሊስ መእምናኑ ያነሱት ፍትሃዊው የመብት ጥያቄ ተቀልብሶ፣ ሕዝባዊ ውክልና የተሰጣቸው የኮሚቴ አባላት ለአስከፊው የቃሊቲ ማረሚያ ቤት የተዳረጉበትን መንግስታዊ ሽብርተኝነት ለመሸፋፈን ከመተባበርም አልፎ ቅዱስ ቁራንን አዛብቶ እስከመጥቀስ መድረሱ በትዝብት ያሳለፍነው የትላንት ኩነት ነው፡፡ የክርስትና እምነት መሪዎችም በተመሳሳይ ሁናቴ የስርዓቱን የጭካኔ እርምጃዎች እንደ ቅዱስ ተግባር ለማፅደቅ ያልረጩት ጠበል፣ ያልጠቀሱት የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል አልነበረም፡፡ ሌላ ሌላውን እንኳን ትተን በቅርቡ ህይወቱ ያለፈው የኦሮሚያ ክልል አስተዳዳሪ የአለማየሁ አቱምሳ ስርዓተ ቀብር ላይ ፓትርያርክ ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ‹ዲሞክራሲን ለማስፈን መስዋዕትነት የከፈለ፤ ሩጫውን የጨረሰ፤ ተጋድሎውን
በብቃትና በንቃት የተወጣ…› እያሉ አፋቸውን ሞልተው የምስክርነት ቃላቸውን ሲሰጡ ሀፍረት ብሎ ነገር ለቅፅበት እንኳን ዝር 3 አላለባቸውም፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ በሰውየው ህልፈት እጃቸው እንዳለበት የሀሜት ወሬ የሚናፈስባቸው እነዚያ ጲላጦሳውያን ጓዶቹ እንዳሻቸው ቢያንቆለጳጵሱት መቼስ የፕሮፓጋንዳ ስራ ነው ብሎ በቸልታ ማለፍ ይቻል ይሆናል፡፡ ነገር ግን የሰማዩን መንግስት ብቻ ያገለግሉ ዘንድ በቃሉ እንዲመላለሱ ግድ የሚላቸው ‹‹መንፈሳውያን››፣ እንዲያ የገዛ ወገኑን ‹‹ኦነግ!›› በሚል የሀሰት ውንጀላ በጥይት ሲደበድብና ሲያስደበድብ፤ መከራን በሕዝብ ላይ እንደምርጊት ሲለስን፤ አምባገነን ስርዓቱን በታማኝነት ሲያገለግል… ያለፈን ሰው ‹‹ዲሞክራት›› እያሉ በአደባባይ ማወደስ በቤተ-ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ ራሱ የተነቀፈውን ለእግዚአብሔርና ለቄሳር ዕኩል መገዛትን እንደትክክለኛ ተግባር አምኖ መቀበል ነው ወደሚል ጠርዝ መገፋታችን አይቀርም፡፡
በግልባጩ በሁሉም እምነት ያሉ ‹‹መንፈሳዊ›› መሪዎች ስርዓቱ በድህረ-ምርጫ 97ም ሆነ በተከታዮቹ ዓመታት የተቃዋሚ ፓርቲ የአመራር አባላትን እና ጋዜጠኞችን እንደ ጥጃ እያሰረ በግፍ ሲያሰቃይ ድርጊቱን ለመንቀፍም ሆነ ዘላቂ ዕርቅ እንዲወርድ ለመማለድ አንዳች ሙከራ አለማድረጋቸው በታሪክ ጥቁር መዝገብ በጉልህ ቀለማት ሰፍሮ የሚኖር ሀጢያታቸው ነው (የቅንጅት እስረኞችን ለማስፈታት የተሄደበት የ‹‹ሽምግልና›› መንገድ የአቶ መለስ ዜናዊ ቧልት ስለመሆኑ ከቶም ማንም ሊጠራጠረው አይችልምና እዚህ መጥቀሱ አስፈላጊ አይመስለኝም)
ሌላው የማሕበረሰባችን የሞራል እሴት በእጅጉ መዝቀጡን የሚያስረግጥልን ብዙሀኑ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች በተዘፈነበት ለመደነስ፣ በተደገሰበት አሳላፊ ለመሆን የሚያደርጉትን መገፋፋት ስናስተውል ነው፡፡ ስርዓቱ ከሚያራምደው ‹‹አብዮታዊ ዲሞክራሲ›› ርዕዮተ-አለም የተቀመረውን ‹‹ፌደራሊዝም አወቃቀር››ን ተንተርሶ ሀገሪቱን በዘውግ ከፋፍሎ እና በሕዝብ መካከል የጥርጣሬ መንፈስ አንብሮ የሥልጣን ዕድሜ ማራዘሙን በግጥምና ዜማ ማወደስ የእህል-ውሃ ጥያቄ ካደረጉት በርካታ ዓመታት ነጉደዋል፡፡ እንዲህ አይነት የሙዚቃ ስራ በአንዳንድ ክልሎች መሬት የሚያሸልም ፈጣን አዋጪ አድርባይትመንት (ኢንቨስትመንት ላለማለት ነው) እስከ መሆን መድረሱ ከታፊና ነጋዴ አርቲስቶች በዘውጉ ዙሪያ ይረባረቡ ዘንድ ታላቅ ልማታዊ አብነት ሆኗቸዋል፡፡ ይህ ሁናቴም በኢትዮጵያ ኪነ-ጥበብን የንፁሃን መታጣት ከድንጋይ ወገራ የታደጋትን የኦሪቷ ዘማዊት ከማስመሰልም አልፎ እንደ ነገሥታቱ ዘመን የአዝማሪ ጨዋታ፤ የቤተ-መንግስቱ መዝናኛ እና አጀንዳ ማራገቢያነት እስከ መሆን ሞዴል ተሸላሚ አድርጓታል፡፡ ይሁንና ቁጥራቸው ጥቂት ቢሆንም ቴዎድሮስ
ካሳሁንን (ቴዲ አፍሮን) የመሳሰሉ መክሊታቸውን እንደ ጉሊት ሽንኩርት ለሽያጭ ያላቀረቡ ከያኒያን፣ ደራሲያን፣ ገጣሚያን… የመኖራቸውን እውነታ ሳንዘነጋ፤ ሀገሪቱ ‹‹ሰው አይብቀልብሽ!›› ተብላ የተረገመች እስኪመስል ድረስ ብሔራዊ ጥቅም፣ ህሊና፣ ሞራል፣ እውነት የረከሱበትና የተዋረዱበት ዘመን ላይ መድረሷን የሚያስረግጡልን በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡
ከጥቂት ወራት በፊት በብአዴኑ ካሳ ተክለብርሃን ፊት-አውራሪነት የሶማሌ ክልልን የጎበኙት አርቲስቶቻችን፣ ገና ድሮ ጆርጅ ኦርዌል ‹‹Animal Farm›› ብሎ በሰየመው መጽሐፉ ‹‹አራት እግር ጥሩ፤ ሁለት እግር መጥፎ›› እያሉ በመንጫጫት ስብሰባን ለመረበሽና ተቃውሞን ለማጨናገፍ አሳማው ናፖሊዮን እንዳሰለጠናቸው አይነት በጎች፤ ኢህአዴግ በጎጥ የካፋፈለውን ሕዝብ ‹‹በታሪኩ ከመቼውም ጊዜ በላይ አሁን አንድ ሆኗል!!›› በማለት በሬ ወለደ የሀሰት ምስክርነታቸውን አምነን እንድንቀበል ለማድረግ ለሳምንታት ተንጫጭተው ሊያደነቁሩን ሞክረዋል፡፡ እነዚህ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች የክልሉ ነዋሪዎች ገና ዛሬ (በኢህአዴግ እፁብ ድንቅ እና ፍትሀዊ አስተዳደር) ኢትዮጵያዊነት እንደተሰማቸው፤ ገና ዛሬ በፍቃደኝነት ኢትዮጵያውያን እንደሆኑ አስመስለው ለማሳመን የሄዱበት የቁልቁለት መንገድ አጥንት ድረስ በሚዘልቅ ሀዘን እንዳኮራመተን እነርሱም ይጠፋቸዋል ብዬ አላስብም፡፡ ጉዳዩ ሆድ ሌላ፣ እውነት ሌላ ሆኖባቸው እንጂ፡፡ ግና፣ የቄሳሩ ጲላጦስም ‹‹እውነት ምንድር ነች?›› እንዲል፣ እውነት ለእነርሱ ዋጋዋ ስንት ነው? መቼም ከእውነት ይልቅ ግድ የሚሰጣቸው የሆድ ነገር ነው፤ እበላ አዳሪዎች ናቸውና፡፡
በጥቅሉ በኢትዮጵያችን ከምሁር እስከ ተርታው፤ ከጳጳሳት (ፓስተራት) እና ሼሆች እስከ መናፍቃውያን፤ ከልሂቅ እስከ ደቂቅ፤ ከጄነራል እስከ ወታደር፤ ከከያኒ እስከ ጽሑፍ ገልባጭ፤ ከቱጃር እስከ ጥሮ-ግሮ አዳሪ፤ ከመምህር እስከ ተማሪ… ስር የሰደደ አድርባይነት እና የሞራል ክስረት ለመንሰራፋቱ አይነተኛ ማሳያው አምባገነኑ ኢህአዴግ እንዲህ ሚሊዮኖችን ረግጦ እየጨፈለቀ፣ አስሮ እያንገላታ፣ ከሀገር እያሰደደና እየገደለ… ከሁለት አስርት በላይ መቆየት የመቻሉ ምስጢር ነው፡፡ ግና፣ የሕዝብን መከራ በማራዘም ኪስን ማደለብ፣ ግላዊ ፍላጎትን ማርካት ሁሌም አትራፊ ሊሆን እንደማይቻል መዘንጋት የለበትም፡፡ ማን ነበር ‹የተከፋፋለና አድርባይ ሕዝብን ከጭቆና ማላቀቅ፣ ሰማይን የማረስ ያህል አዳጋች ነው!› ያለው?
አዎን፣ ከ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ ጀምሮ በጉልበታም ስርዓታት የጭካኔ መዳፍም ሆነ በግላዊ ጥቅመኝነት እየተናዱ የመጡት የባህል እና የሞራል እሴቶች ትውልዱን ዛሬ ላይ ለደረሰበት አስከፊ ማሕበራዊ ቀውስ መዳረጋቸው አሌ የማይባል ነው፡፡ ርግጥ ነው የችግሩ ስፋትና ጥልቀት እንደ ስርዓቱ የፖለቲካ ፍልስፍና በዘውግ የተከፋፈለ አይደለም፤ ብዙሀን እና ህዳጣን የሚል መስፈርትንም የተከተለ አይደለም፤ ኃይማኖታዊ መለያም የለውም፤ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች አለቅጥ መንሰራፋቱ በግላጭ ይታያልና፡፡ ይህም ነው መፍትሔውን ስር ነቀል የማሕበራዊ አብዮት (ለውጥ) ብቻ እንዲሆን ያስገድደው፡፡
የቀደሙት ሁለት አብዮቶች በዋናነት ያነሷቸው የብሔር እና የመሬት ጥያቄ መክሸፋቸው (መቀልበሳቸው) ዛሬም ሶስተኛ አብዮትን የማይቀር ዕዳ አድርጎ የመውሰዱ ሁነት እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ሥራ-አጥነት፣ ከነባሩ ባህል ማፈንገጥ፣ ሙስና፣ በሕብረተሰቡ ዘንድ አክብሮትና 4 ተሰሚነት ያላቸው ታላላቆችን አለማደመጥ፣ አድርባይነት፣ ደንታቢስነት፣ ዶሮ ሳይጮኽ ደጋግሞ መክዳት፣ የ‹‹ስቀሎ፣ ስቀሎ…›› ሀሰተኛ ድምፅ መበራከት፣ ኢ-ሞራላዊ ድርጊቶች እና የመሳሳሉት ትውልድና ሀገር ገዳይ ደዌዎችን ለመፈወስ ከማሕበራዊ አብዮት ያነሰ መፍትሔ እንደሌለ ከተለያዩ ሀገራት ታሪክ መረዳት ይቻላል፡፡ በነገራችን ላይ ኢህአዴግ በየትኛውም የዓለማችን ሀገራት የተከሰተ ሕዝባዊ አብዮት እንቅልፍ እንደሚነሳው በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ለተከታታይ ቀናት ‹‹ተንታኝ›› ጭምር በመጋበዝ፣ ምስራቅ አውሮፓ ድረስ ተጉዞ የተሳካውን የዩክሬን አብዮት ከቀለም ጋር በማያያዝ ለማውገዝ ያቀረባቸው ፕሮግራሞች የፍርሃቱ መጠን አንዱ ማሳያ ተደርገው ሊወሰዱ ይችላል፡፡ ግና፣ እውነት እውነት እልሀለሁ በመቶ ሺህ የሚቆጠር የታጠቀ ኃይል ቢሰለፍ፣ እልፍ አእላፍ ፊርማቶሪዎች በሕዝብ መሀል ቢሰገሰጉ፣ ሚሊዮናት ካድሬዎች ሀገር-ምድሩን ቢያጥለቀልቁ፤ አገዛዛዊ ጭቆና እና ማሕበራዊ ክስረት እስካለ ድረስ የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ፣ የትኛውም ምድራዊ ኃይል ሊያመክነው የማይችል አብዮት መቀጣጠሉ የማይቀር ጉዳይ ነው፡፡ በመጨረሻም ይህንን ጽሑፍ ጄነራል መንግስቱ ነዋይ በተለምዶ ‹‹የታሕሳስ ግርግር›› እየተባለ የሚጠራውን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መክሸፍ ተከትሎ ፍርድ ቤት በቀረበበት ወቅት በሰጠው ቃል እቋጨዋለሁ፡-
‹‹…ዋ! ዋ! ዋ! ለእናንተም ለግዥአችሁ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሀሳቤ በዝርዝር ገብቶት በአንድነት በሚነሳበት ጊዜ የሚደርስባችሁ መዓት የሚያሳቅቅ ይሆናል፡፡››
ትንቢቱ ከ13 ዓመት በኋላ ከእጥፍ በላይ መፈፀሙን ስናስታውስ፣ በጥቅመኝነት ስሌት ከስርዓቱ ጋር ተወዳጅተው የግፉአንን የመከራ ዕድሜ የሚያራዝሙ አድርባዮችም ሆኑ የአገዛዙ ልሂቃን ሕዝቡ ‹‹ሆ!›› ብሎ በአንድነት የተነሳ ዕለት ከመዓቱ ያመልጡ ዘንድ አይቻላቸውምና ዛሬውኑ ‹ንሰሀ ግቡ!› ብሎ ማሳሰብ ግድ ይላል፡፡ …ዋ! ዋ!! ዋ!!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

ይድነቃቸው ከበደ

Image

ሰብአዊ መብቶች እያንዳንዳችን ሰው በመሆናችን ብቻ የሚገቡን ከሰብአዊነታችን ተለይተው ሊታዩ የማያችሉ መብቶች ናቸው፡፡ መንግስታት እነዚህን በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና የተሰጣቸውን ሰብአዊ መብቶች ለማክበር ለማስከበርና ለማሟላት በቀዳሚነት ኃላፊነት አለባቸው፡፡ በዚህም መሰረት ኃላፊነት ከፈረሙ ቀደምት አገራት መካከል ኢትዩጵያ ትገኝበታላች፡፡

ይሁን እንጂ የሴቶች ሰብአዊ መብቶች በሚፈለገው መልኩ ተግባራዊ ካለመሆኑ ባሻገር ኢ-ፍትሃዊነት እጅግ የበዛ ነው፡፡ ይህም በመሆኑም እ.ኤ.አ. በ1908 በአሜሪካ ኒወርክ ከተማ በጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ይሰሩ የነበሩ ላብአደር ሴቶች ‹‹ለእኩል ሥራ እኩል ክፍያና የተመቻቸ የሥራ ሰዓት ለሴቶች›› በሚል መፈክር የሥራ ማቆም አድማ በማካሄድ የሴቶች ድምፅ እንዲስተጋባ አድርገዋል፡፡ ይህን ተከትሎ የዓለም ሴቶች በማህበር በመደራጀት ትግላቸውን በማጠናከራቸው የዓለም መንግስታትን አስተሳሰብ በመለወጥ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አባል አገሮች የሴቶች መብት ስምምነት/ኮንቪክሽን/ እንዲፈራረሙ እብይ ምክንያት ሆነዋል፡፡
እ.ኤ.አ. በ1910 በኮፕን አገር ከተማ በተደረገው ሁለተኛው ዓለም አቀፍ የሴቶች ጉባሄ ላይ የመነሻ ሃሳብ በማቅረብ ማርች 8 በየዓመቱ እንዲከበር ያደረጉት ሴቶች ለመብታቸው ያደረጉትን አስታውጾ ለመዘከር ዓለም አቀፍ መድረክ ለማመቻቸት በመቻላቸው ስማቸው በአክብሮት ይነሳል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓሉን ያከበሩት ጀርመን፣አውስትራሊያ፣ሲውዘርላንድ እና ዴንማርክ ለመሆናቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ከዚሁ የአንድነት ተምሳሌትነት በመነሳት በዓለማ አቀፍ ደረጃ ማርች 8 የሴቶች ቀን በማድረግ ዓለም አቀፍ ስያሜዎችን በመስጠት አገራችን ኢትዮጵያ ጨምሮ በተለያየ መልክ ሲከበር አመታትን እቆጥሯል፡፡ የዘንድሮዉም ማርች 8 አለም አቀፍ የሴቶች ቀን እስከ ዛሬ በአገራችን በተከታታይ የኢትዮጵያ ሴቶች ካከበሩት በዓላት የሚለየው ሁሌም የምኮራባቸው የሰማያዊ ፓርቲ ሠላማዊ ታጋይ ሴቶች የፈፀሙት ገድል ነው፡፡
በአገራችን ኢትዮጵያ የዜጎች መብት በእኩልነት ተጠብቆ በሴቶች ላይ አጥልቶ የኖረው የጾታ ጭቆና እስከዛሬ ምላሽ ያላገኘ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡በተለይ በወያኔ/ኢህአዴግ መንግስት የስልጣን ዘመን የሴቶች ጭቆና እና የመብት እረገጣ በህግ ማቀፍ ውስጥ መሆኑ ይብልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡ ይህን ለማለት የሚያስደፍረው የህጎች ሁሉ የበላይ ህግ ነው በሚባለው ህገመንግሰት የፆታን አድልዎ የሚቀርፍ እና የሴቶችን መብት የሚያመላክት ድንጋጌዎች በውስጡ አካቶ የያዘ ቢሆንም ተግባሪዊነቱ ፕ/ር መስፍን እንዳሉት ‹‹የተፃፈበትን ወረቀት ያህል ዋጋ የማያወጣ ነው››፡፡ ዋጋ አለው እንኳን ከተባለ የትርፉ ተካፋይ የሆኑት የገዥው መንግሰት አጨብጫቢዎች እና የጡት ልጆች ብቻ ናቸው፡፡
በአገራችን መከበር ከጀመረ ከሦት አስርታት በላይ ያስቆጠረው ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ለሴቶች በሴትነታቸው ከሚደርስባቸው ጾታዊ በደል እና የሰብአዊ መብት ጥሰት ያስቀረላቸው አንድም ነገር የለም፡፡ በተለይ ከላይ እንደተገለፀው በወያኔ/ኢህአዴግ መንግሰት ሴቶች በህግ እና በመብት ጥላ ስር ከፍተኛ የሰብአዊና የዲሞክራሲ ጥሰት እየተፈፀመባቸው ይገኛል፡፡
እጅግ አስገራሚው ክስተት ደግሞ የኢህአዲግ ሴቶች ሊግ ፣ የሴቶች ፎረም ኢህአዲግ የሚያዘው እና አገዛዙ ያስተባበራቸው በርካታ የሴት ማህበራት ተጠሪነታቸው በቀጥታ ለወያኔ መንግስት ስርአት ነው፡፡ ስርአቱ ደግሞ የመላው ኢትዮጵያዊያን ድጋፍ እና ይሁንታ ያላገኘ መሆኑ ነው፡፡ ነገሩን ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርገው ደግሞ ኢትዮጵያዊያን ሴቶች ከመንግስት ድጋፍ ውጪ በራሳቸው ፍቃድና አቅም አንድም የተደራጀ ማህብር የሌላቸው መሆኑ ነው፡፡ እርግጥ ነው የሴቶች የፅዋ እና የእድር እንዲሁም የዕቁብ ማህበራት በአገራችን ለቁጥር የሚታክቱ ነው፤ግን እነዚህ ማህበራት የሴቶችን ሁለንተናዊ ችግሮችን የሚቀርፉ አይደለም፡፡
ለመደራጀት ሳይሆን ለማደራጀት ትኩረት እና ድጋፍ የሚሰጠው መንግሰት በሴቶች ላይ ማላገጥን ስራዬ ብሎ ተያይዞታል፡፡ለዚህም እንደማሳያ ከታችኛው የቀበሌ ባለስልጣን ጀምሮ እስከላይኛው የአገር መሪ የሴቶች እኩልነት እና የመደራጀት መብት በህግ የተጠበቀ እንደሆነ ሳይታክቱ የሚገልፁት ነገር ነው፡፡ይሁን እንጂ የሴቶች እኩልነት እና የመደራጀት መብት ለኢህአዴግ አባልነት እና ቤት ለቤት ቡና እያጣጡ የተነገራቸው መልሰው ከማውራት ከቅያስ ወይም ከጎሮ ከድሬነት ያለፍ ተሳትፎ ከተደራጁበት ሳይሆን ከደራጃቸው አካል ያተረፉት ነገር የለም፡፡ ከላይ የተጠቀሰው አሳብ ለመረዳት እና ለመታዘብ ብዙ መራቅ አያስፈልግም በህገመንግስቱ መሰረት ተደራጅተዋል የተባሉ ማናቸውም እንዲሁም በየትኛውም ቦታ የሚገኙ የሴት ማህበራት ከመንግሰት ተፅኖ ውጪ ላለመሆናቸው ከማህበራቸው የስም አወጣጥ ጀምሮ ተግባራቸው በመመልከት በቀላሉ ማህበሩ እና ማህበርተኞችን እነማን እንደሆኑ ለመረዳት ይቻላል፡፡
ለዚህ ፁሑፍ መነሻ የሆነው አሳብ ዘንድሮ ተከብሮ ሳይሆን ተደፍሮ ለማለት በሚያስችል ሁኔታ ማርች 8 መሰረት ያደረግ ነው፡፡ እንደሚታወቀው የባለፈው እሁድ ማርች 8 አስመልክቶ የሴቶች 5 ሺህ ኪ.ሜ ሩጫ ውድድር ተካሂዶአል፡፡ በውድድሩ ላይ ቁጥራቸው የበዛ ሴቶች ተሳትፈዋል ፤ከተሳታፊዎቹ ብዛት ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ በአነስተኛ እና ጥቃቅን መንግስት ያደራጃቸው ሴቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ሴቶች አደባባይ ይዘው የወጡት አሳብ ጥቃቅን መሆኑ በእርግጥም ማህበርተኞቹ ምን ያህል አንድ ለአምስት ‹‹እደተጠረነፉ›› የሚያሳይ ነው፡፡ የጉዳዩ አሳሳቢነት የሚጀምረው እነኚህ ጢቂት ‹‹የተጠረነፉ›› ሴቶች በነፃነት ቀናቸው ነፃነት የተነፈጋቸው መሆኑ ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ እሩጫው ላይ የተሳተፉት በራሳቸው ፍቃድ ሳይሆን በድረጅታቸው ትዕዛዝ ነው ሊያስብል የሚያስችል የተለያየ ‹‹ልማታዊ›› የሆነ መፈክሮችን ሲያሰሙ ተደምጠዋል፡፡በመንግሰት ልዩ ድጋፋ የተደረገላቸው እነኚህ ሴቶች ለሚደግፉት ሳይሆን ለተገደዱበት ዓላማ የመሰላቸውን መፈክር እና ቀረርቶ በማሰማት እንዲሁም የተለያዩ ፖስተሮችን በመያዝ በዕለቱ ሲንቀሳቀሱ ታይተዋል፡፡
ይሁን እንጂ ለመንግስት ደጋፊዎች የተፈቀደው ለሌሎች ለመንግሰት ተቃዎሚ ሴቶች ፖሊስ ያደረገው ክልከላ እና እስራት ክስተቱን አስገራሚ ብቻ ሳይሆን አሳሳቢያ ደርገዋል፡፡ እንደሚታወቀው ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ነው፤ ይህ ቀን ሴቶች ተሰባስበው ከበሮ ይዘው የሚደልቁበት ቀን ሳይሆን ለነፃነታቸው ቀደምት ሴቶች ያደረጉትን ተጋድሎ በመዘከር ያሁኖቹ ሴቶች ለበለጠ እኩልነት እና ነፃነት በጋራ የሚቆሙበት የቃል ኪዳን ቀን ነው፡፡ ይህም እንደሆነ የተረዱ ሴቶች በነፃነት ቀናቸው ስለነፃነታቸው ከፍ ባለ ድምፅ ሲዘምሩ ማየት ምንኛ መታደል ነው ! ይህን በድፍረት ላደረጉት የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች አድናቆት ሊቸራቸው እና ድጋፍ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ሴቶች በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ በአደባባይ ታፍሰው ለእስር የበቁት በእኔ ዘመን ይህ የመጀመሪያ ነው ፡፡የኔ ዘመን ደግሞ 23 ዓመት ሙሉ የሴቶች የፖለቲካ ተሳትፎ የበላው ጅብ አልጮው ብሎ ተቸግረን የከረምንበት ወቅት ነው፡፡ እርግጥ ነው ይህ የሆነበት ምክንያት ለማወቅ እና ለመዘርዘር ሰፊ ጥናት ያስፈልጋል፡፡ የችግሩ አሳሳቢነት እንደተጠበቀ ሆኖ እንቢ ለነፃነቴ በማላት አደባባይ በመውጣት የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች ‹‹ እኔ የጣይቱ ልጅ ነኝ ! እስክንድር ይፈታ ! እርዮት ትፈታ ! አብበከር ይፈታ ! አንዱአለም ይፈታ ! መብራት እና ውሃ ናፈቀን ! ፍትህ እንፈልጋለን ! ›› እና የመሳሰሉትን መፈክር በልበ ሙሉነት በማሰማት ያሳዩት ቆራጥነት ታሪክ መቼም የሚዘነጋው አይደለም፡፡ በይበልጥ ደግም በዚሁ የፖለቲካ አመለካከታቸው ምክንያት ብቻ ለእስር መዳረጋቸው የመንግስት ስርዓት ምን ያህል አምባገነን እና ጨቋኝ እንደሆን በግልፅ የሚያሳይ ነው፡፡

ፀረ ሰላም ሃይሎች
የፀረ ዲሞክራሲ ሃይሎች
የፀረ ልማት ሃይሎች
ኣሸባሪዎች
ነውጠኞች
ነጭ ለባሾች
የደርግ ርዝራዦች
ያለፉት ስርዓት ቅሪቶች
የኣፄው ስርዓት ናፋቂዎች
ኣደገኛ ቦዘኔዎች
ኪራይ ሰብሳቢዎች
የግል ጥቅም ኣሳዳጆች
ጥገኞች
ትምክህተኞች
ነፍጠኞች
የስልጣን ጥመኞች
ተስፈኞች
ጠባቦች
እንክርዳዶች/ጉርዶች
መሃል ሰፋሪዎች
ኣድሃሪያን
የቀለም ኣብዮተኞች
የሻዕቢያ ቅጥረኞች/ ጋሻጃግሬዎች
ኣክራሪ ቡድኖች
የሰለፊ/ወሀቢ እምነት ኣራማጆች
ፅንፈኞች
ቆ… ሻሻ (እደግመዋለሁ ቆ… ሻሻ!)
የበከተ/የገማ/የበሰበሰ ኣስተሳሰብ ያላቸው ሰዎች
ዝቃጮች
ሁከተኞች
ፀብ ኣጫሪዎች
ተቸካዮች
ተንበርካኪዎች
ጥራዝ ነጠቆች
ስግብግብ ነጋዴዎች
ተለጣፊዎች/ተነጣፊዎች
የኢንተርሃምዌ ኣራማጆች
ሗላቀር ኣስተሳሰብ የተጠናወታቸው ሃይሎች
ህገ መንግስቱን በጉልበት ለመናድ የሚዶልቱ ሃይሎች
ኣንዳንድ ኣርቆ ማሰብ የተሳናቸው ዜጎች (ዘገምተኞች )




(ደከመኝ በነጠብጣብ ልለፈው )
*****

የቀረ የለም። ምሁር ነሽ፡ ፖለቲካ ኣያገባኝም የምትይ መሃል ሰፋሪ ነሽ፤ የእምነት ሰው ነሽ፡ ነጋዴ ነሽ፡ ምንድነሽ ሁልሽም ቅጥያ ኣለሽ!

የልማት ሰራዊቱ ከሁሉም ጋር ስለማይስማማ (ከራሱም ጭምር) ለሁሉም ቅጥያ ኣዘጋጅቷል፤ ባንዳች የስድብ ምትሃታዊ ሃይል ነው ስርዓቱ የቆመው ማለት ሳይሻል ኣይቀርም።

Image
ምንሊክ ሳልሳዊ :- ህገመንግስታዊ ጥያቄ ባነሱ ከጄኔራልነት እስከ ሻምበልነት ማእረግ ባላቸው የቀድሞው የኢሕዴን ታጋዮች እና የአሁን የብኣዴን የጦር መኮንኖች እና በሕወሃት ጄኔራሎች መካከል ከፍተኛ የሆነ የመብት ጥያቄዎችን ያማከለ እና ህገመንግስታዊ ስርኣትን ተከትሏል የተባለለት ጥያቄዎችን ተከትሎ ከፍተኛ ውጥረት መከሰቱን የመከላከያ ምንጮቻችን ጠቁመዋል::

ባለፉት ሰሞናት የተደረጉት ስብሰባዎች በከፍተኛ አለመግባባት የተበተኑ ሲሆን በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ በስፋት የፓርቲ ስራዎች እንጂ ሃገራዊ ስራዎች እየተሰሩ አይደለም የሚሉ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊቱ ለህገመንግስቱ መከበር ተገኢ መሆን አለበት በአሁን ወቅት ለአንድ የፓርቲ አመራር እና ለፕሮፓጋንዳ ተገኢ ሆነናል የሚሉ ተመሳሳይ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በሰራዊቱ ውስጥ ያለውን የእድገት የትምህርት እና የደምወዝ መብትን በተመለከተም ከፍተኛ ክርከር ቢደረግም ካለመግባባት መኮንኖቹ ጥርስ እንደተነካከሱ ወደየመጡበት ተበታትነዋል::

የሰራዊት አባላትን ለመቀነስ በተደረገው ጥናት መሰረት ለምን ሁለት ብሄር ላይ አተኮረ የሚሉ ጥያቄ እንዲሁም የስኮላርሺፕ አድሏዊነት በተመለከተ ጠንከር ያሉ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን እንዲሁም ከአንድ ብሄር ለትምህርት ተመርጠው የሚላኩ መኮንኖች በዛው ሳይመለሱ ይቀሩና ነገሩ ይድበሰበሳል የሚሉ አስጨናቂ ጥያቄዎች ተከታትለው ቢነሱም ከመድረኩ መልስ ሳይሰጥባቸው ተድበስብሰው አልፈዋል::ከአንድ ብሄር ብቻ ተመርጠው ለትምሕርት አውሮፓና አሜሪካ ከሄዱት መኮንኖች 80 ከመቶ ያልተመለሱ ሲሆን ይህ ጉዳይ ተድበስብሶ ሌላው ብሄር ስኮላሺፕ እንዳያገኝ ምክንያት እየተፈጠር በዚያው ስለምትከዱ ሃገር ውስጥ በቂ አካዳሚ ስላለ እዚህ እንድንማር ይደረጋል::ስኮላሺፕ የሚሰጣቸው ለማይመለሱ መኮንኖች ነው የሚሉ አቤቱታዎች ተሰምተዋል::ምንሊክ ሳልሳዊ

በሕወሓት ጄኔራሎች እና በብኣዴን ከፍተኛ የጦር መኮንኖች መካከል የተነሳውን ፍጥጫ ተከትሎ ጄኔራል አበባውን ወደ ሲችል ባለስልጣንነት ለማዘዋወር የታቀደ መሆኑን የገለጹት ምንጮሽች በአሁን ሰአት ጄኔራሉ እንደ ቁም እስረኛ አብዛኛው ጊዜያቸውን በመኖሪያ ቤታቸው እንደሚያሳልፉ እና ወደ ቢሯቸው አልፎ አልፎ እንደሚገቡ ታውቋል::

የሳሞራ የኑስን ስልጣን ይረከባሉ ተብሎ የሚጠበቀው ጄኔራል አበባው ጄኔራል ዮሃንስን ወደ ሳሞራ ሕወሓት በሹመት አቅርቦ ካመጣቸው በኋላ ይተለያየ ተጽእኖ እየተደረገባቸው ቢሆንም የብኣዴን ፓርቲ አመራሮች ሁኔታውን በቅርብ እየተከታተሉ ነው ቢባልም ምንም አይፈጥሩም የአሽከርነት ሚና ካልሆነ በስተቀር ሲሉ ምንጮሹ ገልጸዋል::የጄኔራል አበባው ስልጣን ማቆም እና ወደ ሲቭል ባለስልጣንነት መቀየር በሃገሪቱ የፖለቲካ ሂደት ላይ የሚያመጣው ለውጥ እንዳይኖር ሁኔታዎች እየተገመገሙ መሆኑ ታውቋል::ከዚህ ቀደም በተለያየ ወቅት ወደ ውጪ ለእረፍት ለመሄድ ጥያቄ ያቀረቡት ጄኔራል አበባው በተለያየ ምክንያት ሲሰናከልባቸው የቆየ ሲሆን እሳቸውን እና መሰላቸውን ከሰራዊቱ በዘዴ እና በብልሃት ገፍቶ ለማስወጣት በስፋት እየተሰራ መሆኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል::ካሁን ቀደም ሜጄር ጄኔራል የነበሩት አባዱላ ገመዳ አቶ ተብለው ወደ ሲችል ባለስልጣንነት ሲዘዋወሩ ሁለት ከፍተኛ የጦር ጄኔራሎች ደግሞ ወደ እስር ቤት መወርወራቸው አይዘነጋም::ምንሊክ ሳልሳዊ

Image

ከ50 በላይ የሚሆኑ የቅማንት ብሔረሰብ አመራርና አባላት መታሰራቸው ተጠቆመ::
ሕገ መንግሥቱ በሚፈቅደው መሠረት እያቀረበ ባለው የማንነትና የራስ አስተዳዳርነት ጥያቄ ምክንያት፣ ከ50 በላይ የሚሆኑ አባላትና አመራሮቹ መታሰራቸውን የቅማንት ብሔረሰብ አመራር ኮሚቴ አስታወቀ፡፡

የካቲት 9 ቀን 2006 ዓ.ም. ‹‹ቅማንት የሚባል ሕዝብ የለም ያለ አካል ባይኖርም የራስ አስተዳደር ግን ሊፈቀድ አይችልም›› በሚል የክልሉ መንግሥት ተወካዮች ምክር ቤት ነሐሴ 30 ቀን 2005 ዓ.ም. ያስተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም፣ በጎንደር ከተማ እስከ 300 ሺሕ የሚደርሱ ተወላጆች በተገኙበት ሰላማዊ ሠልፍ https://www.facebook.com/photo.php?fbid … =3&theater ማድረጉን ተከትሎ፣ በተለይ በአመራር ኮሚቴው ላይ ጫናና ወከባ ሲደርስበት መቆየቱን ገልጿል፡፡

በመሆኑም የክልሉ መንግሥት በተቀናጀ መንገድ በአባላቱና በአመራሩ ላይ በአድማ በታኝና ፖሊስ ሠራዊት በታገዘ ኃይል አማካይነት፣ ከየካቲት 28 ቀን 2006 ዓ.ም. እስከ መጋቢት 1 ቀን 2006 ዓ.ም. ድረስ ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት ድረስ በድምሩ 50 አመራርና አባላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው እንደታሰሩበት ኮሚቴው አስታውቋል፡፡ በመተማ ወረዳ ሰላማዊ ሠልፍ አድርገው በሰላም ካጠናቀቁ በኋላም የታሰሩ አባላት እንዳሉም አክሏል፡፡

የክልሉ መንግሥት በምን ምክንያት እንዳሰራቸው ግልጽ ባያደርግም፣ የታሰሩ አባላቱ በቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዳይጠየቁ፣ ከጎንደር በ80 እና 100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኙ ዳባትና ደባርቅ ወረዳዎች ተወስደው መታተሰራቸው የሰብዓዊ መብት ረገጣ መሆኑን ኮሚቴው አስታውቋል፡፡

የቅማንት ብሔረሰብ ተወካይ ኮሚቴ በአባላቱና አመራሩ ላይ የአማራ ክልል መንግት ፈጽሞብኛል ስለሚለው እስራትና መንገላታት ማብራሪያ እንዲሰጥ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን መምርያ ሲጠየቅ፣ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው ኮማንደር ሰኢድ መሐመድ ምንም መረጃ እንደሌላቸው ገልጸው፣ የሰሜን ጎንደር ዞን ፖሊስ መምርያን ለማብራሪያ ጠቁመዋል፡፡ የሰሜን ጎንደር ፖሊስ መምርያ ፖሊስ ባልደረባ የሆኑትና ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ ፖሊስ፣ ‹‹እኛ ቅማንት የሚባል ብሔረሰብ አናውቅም፤ የምናውቃቸው አማራ መሆናቸውን ነው፤›› ካሉ በኋላ፣ በበኩላቸው የሰሜን ጎደር ዞን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወደ ኮማንደር ዘመነ አመሸ ቢጠቁሙም፣ የቢሮም ሆነ የግል ስልካቸውን ሊያነሱ ባለመቻላቸው የኮማንደሩን ምላሽ ማካተት አልተቻለም፡፡ Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) ምንጭ ረፖርተር ጋዘጣ

Image

የሕወሐት አባል የሆነውና በአሜሪካ የሚኖረው ብስራት አማረ በርካታ ወንጀሎችን እንደፈፀመ የቅርብ ምንጮች አጋለጡ። ሕወሐት በረሃ እያለ የባዶ 6 እስር ቤት ዋና ሃላፊ የነበረው ብስራት አማረ የኢ.ህ.አ.ፓ አባላት የነበሩት እነ ፀጋዬ ገ/መድህን (ደብተራው) ጨምሮ በሕወሐት የተያዙትን በሙሉ ወረኢ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በነበረ እስር ቤት በጅምላ አሰቃይቶ እንደገደላቸው ምንጮቹ አረጋግጠዋል። በሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ ሰዎች « ኢዲዩና ፊውዳል..» በሚል ባዶ 6 ተብሎ ይጠራ በነበረው እስር ቤት ተሰቃይተው እንዲገደሉ የተደረጉት በብስራት አማረ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮቹ ከዚህ በተጨማሪ የድርጅቱን በርካታ አባላት እንዳስገደለ አያይዘው ገልፀዋል። እነተክሉ ሃዋዝ በዚህ ወንጀለኛ ከተገደሉት ይጠቀሳሉ ሲሉ ያክላሉ።

በ1983ዓ.ም ሕወሐት/ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ የሟቹ የደህንነት ሹም ክንፈ ገ/መድህን ምክትል የነበረው ብስራት አማረ ከቤተ መንግስት የጃንሆይ የነበረ ከፍተኛ ወርቅ በመዝረፍ መውሰዱን ያጋለጡት ምንጮቹ በዚህ የዘረፋ ወንጀል ሆለታ እስር ቤት እንዲገባ መደረጉን ያመለክታሉ። በነስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ትእዛዝ እንዲፈታ ተደርጐ ወደ አሜሪካ የተሸኘው ብስራት አሜሪካ ሲጓዝ የዘረፈውን ወርቅ ይዞ እንደነበረ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ምንጮች በግርምት ይገልፃሉ። ብስራት አማረ አሜሪካ ከመጣ በኋላ ቅርስ የሆኑትንና የዘረፋቸውን ወርቆች መሸጡንና አንዲት ሴት ለማሻሻጥ የተቀበለችውን 1ኪሎ ወርቅ ከወሰደች በኋላ እንደካደችው ማወቅ ተችሎዋል። ብስራት አማረ ስለዚሁ ጉዳይ ተበሳጭቶ የነገራቸው ምንጮች ማረጋገጫ ይሰጣሉ።

የብስራት ታናሽ ወንድም የሆነውና በደህንነት ቢሮ ይሰራ የነበረው ታጋይ ጠስሚ (ጠስሚ -ትርጉሙ ቅቤ ማለት ነው) ከስራው በመልቀቅ የአስመጪና ላኪነት ትልቅ ቢዝነስ መክፈቱን የጠቆሙት ምንጮቹ አክለውም፥ ድርጅቱ የተከፈተው ብስራት አሜሪካ ከገባ በኋላ በላከለት ገንዘብ መሆኑን አስታውቀዋል። (ስለዚሁ ጉዳይ በ1995 ዓ.ም በኢትኦጵ ጋዜጣ መረጃው ይፋ መደረጉና የብስራት ወንድም ቅቤ ኢትኦጵ ቢሮ ድረስ በመምጣት የጋዜጣውን አዘጋጅ በድንጋጤ ተውጦ “የራሴን ቢዝነስ ተቋም ነው፤ እነማን መረጃ እንደሚሰጧችሁ አውቃለሁ። እባካችሁ የእኔንም፣ የወንድሜንም ስም አታንሱ?” በማለት ተማጽኖ አቅርቦ ነበር።)

ብስራት አማረ ከሽማግሌው ስብሃት ነጋ ጋር ባለው የጠበቀ ግንኙነት ወደ ኢትዮጵያ ሲመላለስ መቆየቱን ያወሱት ምንጮቹ፣ ወንጀለኛውና ዘራፊው መቀሌ ሄዶ አስገደ ገ/ስላሴን እንደከሰሰ አስታውቀዋል። የደርግ ወንጀለኞች ከአሜሪካ በገዢው ፓርቲ እየተወሰዱ ነገር ግን የኢ.ህ.አ.ፓ አባላትንና ሌሎች ንጹሃን ዜጎችን በጅምላ የፈጀና የአገር ቅርስ የዘረፈ ወንጀለኛ ጠያቂ ማጣቱ አስገራሚ ነው ብለዋል ምንጮቹ። ጠያቂ አካል ካለ በወንጀለኛው ብስራት አማረ ላይ ለመመስከር ፈቃደኛ መሆናቸውን አክለዋል። ይህን ምስክርነትና ማረጋገጫ ሊሰጡ የሚችሉና በአሜሪካ የሚኖሩ ሶስት የቀድሞ የሕወሐት ሹሞች እንዳሉና የብስራትን ወንጀል ጠንቅቀው የሚያውቁ መኖራቸውን አያይዘው ጠቁመዋል።
===ከኢየሩሳሌም አርአያ ከኢየሩሳሌም አርአያ ከኢየሩሳሌም አርአያ ===

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ግምገማ

በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ያተኮረ ውይይት ጄኔቭ ስዊትዘርላንድ ውስጥ ዛሬ ተካሂዷል ። የተለያዩ ዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ባዘጋጁት በዚሁ ውይይት ላይ በኢትዮጵያ ይፈፀማሉ የተባሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በዝርዝር ቀርበዋል።

Image

መንግሥት የሰብዓዊ መብት አያያዙን እንዲያሻሽል ያግዛሉ የተባሉ ሃሳቦችም ተሰንዝረዋል ። በስበሰባው ላይ የተካፈሉት የኢትዮጵያ መንግሥት ተወካዮች ለተሰነዘሩት ወቀሳዎች የበኩላቸውን መልስ መስጠታቸው ተገልጿል ። በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ያተኮረው ውይይት ዛሬ የተደረገው ከ25,ተኛው የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጉባኤ ጎን ለጎን ነው ። የውይይቱ ዓላማም በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ያተኮረ ዝርዝር ዘገባ ለተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በመጪው ግንቦት ከመቅረቡ አስቀድሞ ስለሃገሪቱ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ግንዛቤ ማስጨበጥ ነው ። ስበስባውን ካዘጋጁት ዓለምዓቀፍ ድርጅቶች አንዱ መቀመጫውን ጆሃንስበርግ ደቡብ አፍሪቃ ያደረገው ሲቪኩስ የተባለው ድርጅት የፖሊሲና የጥብቅና ጉዳዮች መኮንን ቶር ሆድንፌልድ ስብሰባው በተለይ በሶስት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መወያየቱን ለዶቼቬለ ተናግረዋል ።

ከነዚህም እጎአ በ2009 ዓም የወጣው የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራት ህግ አንዱ ነው ። ህጉ ከባድ ተፅዕኖ ማሳደሩና መዘዞቹም በውይይቱ መነሳታቸውን ሆድንፌልድ ገልፀዋል ። « በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ መብት ለሚታገሉ ድርጅቶች በሚለገሰው ዓለም ዓቀፍ የገንዘብ እርዳታ ላይ በተጣሉትን ገደቦች ላይ ተነጋገግረናል በዚህ ህግ ምክንያት በኢትዮጵያ ዓለም ኦቀፍ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች አይሰሩም ። በርካታ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶችም ከሰብዓዊ መብት ጋር የተገናኙ ሥራዎች ማካሄድ አቁመዋል ወይንም ከነጭራሹ ተዘግተዋል »

መድረኩ ትኩረት ሰጥቶ የተወያየበት ሌላው ጉዳይ ደግሞ ሃሳብን በነፃ የመግለፅ መብት ላይ ያደርጋል የተባለው ጫና ነበር ።

«ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ከተገቢው የህግ ሂደት ውጭ እንዲሁም በልዩ ደንቦች ሃሳብን በነፃ የመግለፅ መብት ላይ የተጣሉትን ገደቦችም በውይይቱ ተነስተዋል ። በተለይ ስብሰባው በኢትዮጵያ 12 ጋዜጠኞች በቨረ ሽብሩ ህግ ምክንያት መከሰሰሳቸውኢትዮጵያ ውስጥ በህጋዊ መንገድ የጋዜጠኝነት ተግባራቸውን ሲያከናውኑ ርዕዮት ዓለሙና እስክንድር ነጋ የመታሰራቸውም ጉዳይ ላይም ትኩረት ሰጥቶ ተነጋግሯል ።

ሆድንፌልድ እንደሚሉት በውይይቱ በኢትዮጵያ የነጻ ሚዲያ መገደብም ተነስቷል ። በጎርጎሮሳውያኑ 2012 5 ጋዜጦች መዘጋታቸው በአሁኑ ሰዓትም ኢንተርኔ ት ከሚጠበቀው በላይ ቅድመ ምርመራ ይካሄድበታል ዓለም ዓቀፍ መገናኛ ብዙሃንንና የሰብዓዊ መብት ጉዳዮችን የሚያነሱ ድረገፆች በኢትዮጵያ እንዳይሰሙና እንዳይታዩ በመንግሥት ይታገዳሉ ሲሉ ተወያዮቹ መገለፃቸውን ተናግረዋል ሆድንፌልድ የኢትዮጵያ መንግሥት የሰብዓዊ መብት አያያዙን እንያሽሽልም ሃሳቦች ተሰንዝረዋል ።

« የ2009 ዓም የበጎ አድራጎት ና የሲቪክ ማህበራት መተዳደሪያ ደንብ እንዲሰረዝ ወይም እንዲሻሻል ሁለተኛ የፀረ ሽብር ህግ በደል መፈፀሚያና ጋዜጠኖችን ማፈኛ እንዳይሆን እንዲሰረዝ በፀረ ሽብሩ ሕግ ምክንያት የታሰሩ ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎች በሙሉ እንዲፈቱ እንዲሁም ተቃዋሚዎችና ሰላማዊ ሰልፈኞች ከሚቀጥለው ዓመት ምርጫ በፊት የመሰብሰብ መብታቸውን እንዲጠቀሙ እንዲደረግ ሃሳብ ቀርቧል ።»

ዶቼቬለ ስለ ውይይቱ ና ስለተሰጡት አስተያየቶች የኢትዮጵያ መንግስት ተወካዮችን ለማነጋገር ያደረገው ሙከራ አልተሳካም ። ሆኖም በውይይቱ ላይ የተካፈሉት የሰብዓዊ መብት ተመራማሪው አቶ ያሬድ ኃይለ ማርያም ያኢትዮጵያ መንግሥት ተወካዮችለመድረኩ የሰጡትን አስተያየት አጋርተውናል ።

http://www.dw.de/%E1%8B%A8%E1%8A%A2%E1% … a-17495793

ወያኔ/ኢሕአዴግ ጥሩምባ ነፍቶ የብሔሮች፣ የብሔረሰቦችና የሕዝቦች ነጻነት ብሎ ከአወጀና ሁሉንም ለሃያ ሁለት ዓመታት በተስፋ ከአስፈነደቀ በኋላ ችግር ተፈጠረበት፤ ችግሩ ምንድን ነው? ችግሩ የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች የሚባለው ነው፤ ችግሩ አፍ ከሚችለው በላይ ለመጉረስ ከራስ ጋር መተናነቅ ሆነ፤ ችግሩ የማሰብ ድርቀት ነው፤ ችግሩ ከአሜሪካና ከአውሮፓ መንግሥታት ጀምሮ እስከቀበሌ መዋቅር ያሉትን ሁሉ በአንድ ዘዴ እያባበሉና እያታለሉ ማደናበር ነው፤ ችግሩ በሃያ ሁለት ዓመታት ውስጥ ዘዴው ሻግቶ ዓላማው ደብዛው መጥፋቱ ነው፤ ቸግሩ የዘዴው መሻገትና የዓላማው መክሸፍ መጋለጡ ነው፤ ችግሩ ወያኔ የተቀመጠበት የሥልጣን ወንበር መቆርቆር መጀመሩ ነው።

የግለሰብ ነጻነት ታፍኖ የጎሣ ነጻነት መታወጁ ፋይዳ እንዳላመጣ ታየ፤ የግለሰብን ነጻነት ለመደፍጠጥ ሲባል የጎሣዎች ነጻነትም አብሮ ተደፍጥጦ ነበር፤ ይህንን አስቀድሞ ለማየት ለምን ሳይቻል ቀረ? የሚል ጠያቂ ከመጣ መልሱ ቀላል ነው፤ በሚልዮኖች ብር እየወጣ መንገድ ሲሠራና አስፋልት ሲለብስ ቆይቶ ከጥቂት ወራት በኋላ የባቡር ሀዲድ ለመዘርጋት ተብሎ የተሠራውን አስፋልት የለበሰ መንገድ ማፍረስ እንዳስፈለገ አይተናል፤ የባቡሩ ጉዳይ ለምን አስቀድሞ አልታየም? የጎሣን ነጻነት ለማጉላት ሲባል የግለሰብን ነጻነት መደፍጠጡ ዞሮ ዞሮ የጎሣውንም ነጻነት አንደሚደፈጥጠው ያልታየበት የተለየ ምክንያት የለውም፤ አሰቀድሞ አለማየት የባሕርይ ነው፤ በተጠቀሱት ምሳሌዎች ሁለቱም ዋጋ ያስከፍላሉ፤ ልዩነቱ የአንዱ ዋጋ የሚከፈለው በፖሊቲካ ኪሳራ ሲሆን፣ ሌላው የሚከፈለው በኢኮኖሚ (በሀብት) ኪሳራ ነው፤ ሆኖም የፖሊቲካውም ሆነ የሀብቱ ኪሳራ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ በሙሉ ያለምንም የጎሣ ልዩነት ሲጫንበትና ችጋር ሲያንዣብበት በሥልጣኑ ወንበር ላይና በዙሪያው የሚንሳፈፉት ፈጣሪዎቹ ናቸውና የችግሩ ሸክም ሲያልፍም አይነካቸው! እንኳን ለፖሊቲካና ለሀብት ኪሳራ ለሕይወት ኪሳራም ቢሆን የማይጠየቅ መሆኑን በምክር ቤት በሚባለው ውስጥ በድፍረት የተነገረበት አገዛዝ ነው።

የትግራይ ሕዝብ የአገዛዙ ጉልበትና የጥቅም ተካፋይ ነው እየተባለ እስቲያምመው ድረስ በሐሜት ተለበለበ፤ የሚናገርለት ቡድንና የሚናገርበት መድረክ ሳያገኝ ሃያ ሁለት ዓመታት ያህል ኢትዮጵያዊ ትእግስቱን አሳየ፤ ዛሬ አረና የሚባለው የትግራይ የፖሊቲካ ቡድን ወያኔ ለብቻው በትግራይ ሲቆጣጠረው የቆየውን የፖሊቲካ መድረክ ለመጋራት ፊት ለፊት በሰላማዊ የፖሊቲካ ትግል እየተጋፈጠው ነው፤ ይህ አዲስ ሁኔታ በትግራይ ብቻ ሳይሆን በመላ ኢትዮጵያ የፈጠረውንና ሊፈጥር የሚችለውን የፖሊቲካ እንቅስቃሴ እንኳን ሌሎች በሩቅ የሚከታተሉ ወያኔዎችም ገና አልገባቸውም፤ በፖሊቲካውም ሆነ በኢኮኖሚው አገዛዙ ችግርን አስቀድሞ የማየት ብቃት እንዳላሳየ ከላይ በተጠቀሱት ምሳሌዎች አረጋግጠናል፤ ስለዚህም አገዛዙ በትግራይ የገጠመውን ሰላማዊ ፉክክር ለመቋቋም አዲስ ዘዴ አላገኘም፤ እስካሁን በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች እንደተደረገው ሁሉ በትግራይም ተቀናቃኞቹን በእስርና በዱላ ለማገድ እየሞከረ ነው፤ ሌላ ዘዴ ገና አላገኘም፤ የሚፈልግም አይመስልም፤ በዱላ መጠቀም ሲለመድ አንጎል ይደነድናል፤ ወገንን ጠላት ያደርጋል፤ ወገን ጠላት ከሆነ ማን ወዳጅ ሊሆን ነው? ትልቁ አደጋ ይህ ነው።

መሠረታዊ ችግርም አለበት፤ በእውነተኛ የጎሣ ፖሊቲካ ውስጥ የማይታዩ ነገሮች እየተከሰቱ ነው፤ በአንድ ጎሣ ውስጥ ከባድ የሆነ የአስተሳሰብ ልዩነት፣ የሥልጣን ክፍፍልም ሆነ የሀብት ልዩነት ጎልቶ ሲወጣ የጎሣው ሥርዓት መክሸፉንና መምከኑን ያመለክታል፤ መስታወት ሆኖ የመሠልጠንና የመለወጥ ልዩነት የሚታየው በዚህ ጊዜ ነው፤ መሠልጠን የማይለውጣቸውን ሰዎች መማር ይለውጣቸዋል፤ ከማትጊያ ጋር በሚሰጥ የቡድን መመሪያ የሚሠሩትን ሰዎች በግል ማንበብና ማሰብ ይለውጣቸዋል፤ ይህንን የማይቀርና ሊታገድ የማይችል የለውጥ አቅጣጫ ማየት የማይችሉ ለዛሬ እንጂ ለነገ የሚኖሩ አይደሉም፤ በትግራይ በመታየት ላይ ያለው የነጻ ሰዎችን፣ የነጻ ግለሰቦችን አስተሳሰብ የሚገልጽ አንቅስቃሴ ለትግራይ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ትልቅ ግምት የሚሰጠው ነው፤ የመንጋ አስተሳሰብን ለመረዳት ፌስቡክን ማጥናት ነው፤ የወያኔ የካድሬ ሠራዊት በሻገተው አስተሳሰቡ (መለስ ዜናዊ በጸያፍ ቃላት ገልጾታል፤) እያየው በዚያው በለመደውና ባስለመዱት የዱላና የጉልበት ዘዴ ሊያመክነው እየጣረ ነው፤ ወጣቶቹ ግን እየተደረገ ያለውን በአለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት ከተጫነባቸው የተስፋ ክምር ጋር እያስተያዩ ማን እንደጠገበና ማን እንደተራበ ያያሉ፤ ያመዛዝናሉ፤ አቅዋማቸውንም ያስተካክላሉ፤ የትግራይ ወጣቶች የፖሊቲካ ንቃትና ነጻ አስተሳሰብ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ወጣቶች ላይ ሊኖረው የሚችለውን ተጽእኖ የወያኔ ካድሬዎች አስበው ሊደርሱበት አይችሉም፤ የተለመደው አስቀድሞ አለማየት አወዳደቅን የሚጎዳ፣ የሚያስከፋና የሚያሳፍር ያደርገዋል!

የጭቆና ሠራዊት እንዲሆን የሚሠለጥነው የካድሬ ሠራዊት ጸረ-ማሰብ ነው፤ አስቦ ሳይሆን ለትእዛዝና ለሆዱ የሚገዛ ነው፤ ከላይ እስከታች በአንድ አስተሳሰብ ብቻ የሚንቀሳቀስ በመሆኑ የአገር ጉዳዮችን ለሕዝባዊ ሙግት አይከፍትም፤ ስለዚህም ሀሳቡ አይናፈስም፤ ስለዚህም አስተሳሰቡ የጊዜ መጫወቻ ይሆናል፤ ይሻግታል፤ ጸረ-ማሰብ ሆኖ ከመሻገት መዳን አይቻልም፤ መለስ ዜናዊ ይህንን በደንብ ያውቅ ነበር! ዛሬ እነኮኸንና እነሺን (ኮኸን በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ውስጥ የአፍሪካ ክፍል ኃላፊ የነበረ ሲሆን ሺን ደግሞ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ነበር፤) በዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ የሚናገሩት በኤርትራና በሶማልያ ላይ የተነደፈው መመሪያ አልሠራምና እንደገና መፈተሽ አለበት እያሉ ነው፤ እነዚህ ሰዎች የሚናገሩት የማንን መሠረታዊ ጥቅም ለማራመድ ነው? በጊዜው ጥያቄውን ለመመርመርና በትክክል ለመመለስ ካልተቻለ በሚቀጥሉት ሁለትና ሦስት ዓመታት የአፍሪካ ቀንድ ሁኔታ ሲለዋወጥ የኢትዮጵያ አገዛዝ ይጨማደድና ብዙ ባዶ ቀፎዎችን ይዞ ይቀራል።

“ወደሽ ከተደፋሽ ቢረግጡሽ አይክፋሽ” ማለት ይሄ ነው፡፡
ለጋራ ጥቅማችን ብሎ ለራሱ ከሚጠቀምብን ያድነን፡፡ ከሃዲዎች የዕጣ-ፈንታቸዉን ያገኛሉ::

ተነስ ሲሉት የሚነሳ፣ ተኛ ሲሉት የሚተኛ …” ዞሮ ዞሮ ወዶ-ገባ ያሉትን መፈፀም ግዴታው ነው፡፡ ወዶ-ገባ ዝርያው ብዙ ነው፡፡ የፖለቲካ ወዶ-ገባ አለ፡፡ ፖለቲካው ምንም ይሁን ምንም ለጥቅሜ እገባበታለሁ ይላል፡፡ የኢኮኖሚ ወዶ-ገባ አለ፡፡ ኢኮኖሚው ምንም ይሁን ምን ሆዴን እሞላበታለሁ ይላል፡፡ የማህበራዊ ወዶ-ገባ አለ፡፡ ከማናቸውም ማህበራዊ ቀውስ እኔ ጥቅሜን ካካበትኩ ያሉኝን አደርጋለሁ ባይ ነው፡፡ ብልህ ሰው የውሾቹን ዓይነት ዕጣ-ፈንታ ያስተውላል፡፡ አበሻ፤ “አብዶም ሠግዶም ውሉን አይስትም” የሚል አባባል አለው፡፡ ይሄንንም ልብ-ልንበል፤ የህግ-ወዶ-ገባም አለ፡፡ በፍትሕ ሽፋን ጥቅሙን የማያጋብስ፡፡

አገርን የሚያጠፋ ማንኛውም ጥፋት ጥፋት ነው፡፡ ሚሥማርም አቀበልን ድንጋይ ያው ነው፡፡ በወገናዊነት ላንድ ቡድን መጠቀሚያ አመቻቸንም፣ በሙስና ውስጥ ተዘፈቅንም፤ ዞሮ ዞሮ “ጌታ ተሰቅሏል”፡፡ አገርና ህዝብ በድለናል፡፡ እገሌ አድርግ ብሎኝ ነው እንጂ እኔ በራሴ አላደርገውም ነበር ማለት የኋላ ኋላ ከተጠያቂነት አያድንም፡፡ በሥርዓቱም ማሳሰብ በግልና በቡድን ከሠራነውና አንዱን የእናት ልጅ፣ አንዱን የእንጀራ ልጅ አድርገን ካጠፋነው ጥፋት ተጠያቂነት አያድንም፡፡ ሰው ሰውን መበዝበዙ ነው ሀቁ፡፡ ፊት ለፊቱም ግልባጩም ያው ነው እንደ ማለት ነው፡፡

ስለዚህ ሥርዓት ሰበብ አይሆንም፡፡ ዕውነቱ ሰው ሰውን መበዝበዙ ነው፡፡ ሊበራል፣ ኒዮ ሊበራል፣ አብዮታዊ፣ ኮሙኒስታዊ፣ ፋሽስታዊ፣ ቦናፓርቲዝማዊ፣ ልማታዊ፣ ሉአላዊ፣ ፀረ-ሽብራዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ኢጋዳዊ፣ … ሁሉም የሰውና ሰው ተቃርኖና ፍጭት መልኮች ናቸው፡፡ ዋናው ከህዝብና ከሀገር ጥቅም አኳያ ምን ይመስላሉ ተብሎ መመርመር ያለባቸው ናቸው፡፡ የሰውና ሰው ግንኙነት የጨቋኝና ተጨቋኝ፣ የወገናዊና ኢወገናዊ፣ የፍትሐዊና ኢፍትሐዊ፣ ወይስ ቡድናዊና ኢቡድናዊ? ምን ይመስላል፡፡ የሳንቲሙ ገፅ ምን ዓይነት ነው? ዘውድ? ጎፈር? ወይም በሠያፍ የቆመ? መፈተሽ አለበት፡፡

አንዱ ለአመራሩ ሚሥጥር ቅርብ በመሆኑ አስቀድሞ ኢንፎርሜሽን ያገኛል፡፡ ቤቱን ከውርስ ያድናል፡፡ ሌላው ለኢንፎርሜሽኑ እሩቅ ነውና ላዩ ላይ ይታወጅበታል፡፡ ለብዙሃኑ ጥቅም ሲባል ጥቂቶቹ ቢጎዱም ምንም አይደለም የሚለውም አስተሳሰብ መመርመር ይኖርበታል፡፡ የአብዮቱ ጦስ ይሁን የካፒታሊዝም ጦስ ባልለየበት አገር አዋጆችና መመሪያዎች ሲከለሱ ማየት ቢያንስ ያስገርማል፡፡ አቀንቃኙ Protagonist እና ተቃራኙ antagonist በቀላሉ አይለዩም፡፡ ከሥልጣን ይባረራሉ፡፡ ተባራሪዎቹ ያወጡት ህግና መመሪያ ምን እንደሚሆን ዕጣ-ፈንታው አይታወቅም፡፡ ከሁሉም ይሰውረን! ህዝብ ብቻ ግራ እንደተጋባ ይቀጥላል፡፡ “ሰው ይጫኑብህ ግንድ? ቢሉት፤ ግንድ ከተጫነኝ ሰው ያነሳልኛል፣ ሰው ከተጫነኝ ማን ያነሳልኛል፤ አለ” የሚባለው ግራ-ገብ ዘመንን የሚያመላክተን ነው፡፡ ከዚህም ይሰውረን! ከሚጫነን ይገላግለን፡፡ ከወዶ-ገባነት ይቅር ይበለን!!#MinilikSalsawi