Image
የፌደራል አቃቢ ህግ በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በጦማርያኑና በጋዜጠኞቹ ላይ የመሰረተውን የሽብር ክስ እንዲያሻሽል የልደታ ከፍተኛ ችሎት ትዕዛዝ ሰጠ፡፡

ፍርድ ቤቱ ዛሬ ህዳር 3/2007 ዓ.ም በዋለው ችሎት ቀደም ብሎ የተከሳሽ ጠበቆች ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ መርምሮ ብይን በመስጠት በንባብ አሰምቷል፡፡ በዚህ መሰረትም ፍርድ ቤቱ በክስ መቃወሚያው ላይ የቀረቡትን ዝርዝር ነጥቦች መርምሮ በተወሰኑ ነጥቦች ላይ አቃቢ ህግ ክሱን እንዲያሻሽል ትዕዛዝ ሲሰጥ፣ በሁለተኛነት ቀርቦ የነበረው የክስ ይዘት በአንደኛው የክስ ይዘት ላይ መጠቃለል ስለሚችል ሁለተኛውን የክስ ይዘት ፍርድ ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ውድቅ አድርጎታል፡፡

በክስ ዝርዝሩ ላይ ተከሳሾቹ ‹‹ለአመጽ ማነሳሳትና መምራት›› የሚያስችል ስልጠና ወስደዋል በሚል በተጠቀሰው ላይ ስልጠናው መቼ፣ በማን እና በምን ጉዳዮች ላይ ተሰጠ የሚለው ግልጽ ስላልሆነ አቃቢ ህግ ክሱን እንዲያሻሽል ተጠይቋል፡፡
በተጨማሪም ተከሳሾቹ አመጽ ለመምራት የስራ ክፍፍል አድርገዋል በሚል የተጠቀሰባቸው የክሱ ይዘት ‹‹ምን አይነት የስራ ክፍፍል፣ ማን ምን እንዲሰራ ክፍፍሉ ተደረገ›› የሚለውን ስለማያመለክት ይህንንም መሻሻል እንዳለበት ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡

በተጨማሪም በክሱ ዝርዝር ላይ ‹‹ቡድን›› እና ‹‹ድርጅት›› በሚል (ግንቦት 7፣ ኦነግ ወይስ ሌላ የሚለውን ስለማይገልጽ) በደፈናው የቀረቡት ነጥቦች ላይ በዝርዝር መቀመጥ ስላለባቸው አቃቢ ህግ ማሻሻያ እንዲያደርግ ታዝዟል፡፡

በሌላ በኩል የተከሳሽ ጠበቆች ‹‹በኢሳት ሬድዮና ቴሌቪዥን መረጃ በመስጠት›› በሚል ተከሳሾች ላይ የቀረበው የክስ ይዘት ሆን ተብሎ ወደ ሌላ አካል (ግንቦት 7) ጋር ለማገናኘት ነው በሚል ያቀረቡትን መቃወሚያ፣ ‹‹በኢሳትና በግንቦት 7 መካከል ያለው ግንኙነት ወደፊት በማስረጃ የሚታይ ነው በሚል ፍርድ ቤቱ መቃወሚያውን ውድቅ አድርጎታል፡፡

ከተከሳሽ ጠበቆች መካከል የሆኑት አቶ አምሃ መኮንን ከችሎቱ በኋላ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት፣ ፍርድ ቤቱ በተከሳሽ ጠበቆች ላይ የቀረበውን የክስ መቃወሚያ ጊዜ ወስዶ መርምሮ ውሳኔ እንዳሳለፈ ጠቅሰዋል፡፡ ይሻሻላሉ የተባሉት የክሱ ይዘቶች ላይ ጥያቄ የተነሳላቸው አቶ አምሃ የውሳኔው ዝርዝር በጽሑፍ ገና እንዳልደረሳቸው ጠቅሰው፣ ‹‹አቃቢ ህግ በታዘዘው መሰረት ክሱን የማያሻሽል ከሆነ ይሻሻላሉ የተባሉት የክሱ ይዘቶች ውድቅ የሚሆኑበት አሰራር አለ›› ብለዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ክሱ ተሻሽሎ መቅረብ አለመቅረቡን ለማየት ለህዳር 24/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

Image
ኢወጋን – በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ ቦታዎች ላይ የቅስቀሳ መልእከቶችን ለህዝብ እይታ አብቅቷል።
የአትዮጵያ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ (ኢወጋን)አባላት በአዲስ አበባ ዋና ዋና የህዝብ መገናኛ ቦታዎች እና የአውቶብስ መጠበቂያ የገበያ ቦታዎች ላይ የወያኔን ስርአት የሚያወግዙ እና ስርአቱን ለማውረድ ህዝቡ በጋራ እንዲነሳ የሚያደርጉ ጥሪዎችን ያነገኡ መፈክሮችን በመለጠፍ እንዲሁም ለፖሊስ እና ጦር ሰራዊቱ የሚገባውን የአንድነት እና የህዝብህን አድን ጥሪ በማስተላለፍ የተሳካ ስራ መስራታቸውን ከአዲስ አበባ ኢወጋን የደረሰን መረጃ ያመለክታል::በአዲስ አበባ ከተማ በተመረጡ ቦታዎች ላይ የቅስቀሳ መልእከቶችን ለህዝብ እይታ አብቅቷል።
መላው ኢትዮጵያዊ ወጣት ከኢወጋን ጎን እንዲሰለፍ ጥሪውን በአክብሮት ያስተላልፋል።
በቭድዮ የተደገፈ ዝርዝር ዜናውን በኢትዮጱያ ወጣቶች ድምጽ በኩል ይፋ እናደርጋለን።
ያለ መስዋዕትነት ድል የለም !!! – የኢትዮጵያ ወጣቶች የጋራ ንቅናቄ (ኢወጋን)አዲስ አበባ

phpBB [video]

Image

ደካማ የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ምርጫ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም፣ በምርጫ ሥም ጫፍ ላይ የደረሰው ሠላማዊ የነጻነት ትግል ጥያቄ መዳፈን የለበትም፡፡

======================

“ብልህነት የተሞላበት ታላቅ የትግል መርህ ማድረግና መስፋፋት፣ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ፣ጠንካራ ሥራና ሥነ-ሥርዓታዊ አበራታች ትግል ለድል የመብቃቱ ዕድል የሰፋ ነው፡፡” ይህ ፁሑፍ የተወሰደው ከአምባገነን አገዛዝ ወደ ዲሞክራሲ ከሚለው ከ ጄን ሻርፕ መፃሐፍ ነው፡፡ በዙህ አጋጣሚ ይህ መፃፍ እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው፣በተለይ በአገር ውስጥ ለሚንቀሳቁ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ለሚያደርጉት አመፅ አልብ ትግል ብዙ አመላካች መረጃዎችን የሚሰጥ ነው፡፡ ዜጎች በሰላማዊ መንገድ የመሰብሰብና የመንግስትን የፖሊሲ ውሳኔዎች እና አሰራሮች የመቃወም መብታቸው የተጠበቀ ነው፣በሰላማዊ ሰልፍ፣በተቃውሞ የፊርማ ሰነድ ፣ለመንግስት ጥሪ ባለመተባበር፣በሥራ ማቆም አድማና በመሳሰሉት ዘዴዎች ተቃውሞ መግለፅ አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው የዲሞክራሲ መብት ነው፡፡ በዓለም አቀፍ የተባበሩት መግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ጉባሄ ባፀደቀው መግለጫ ኢትዮጵያም በፈረመችው ስለ መሰብሰብ እና መደራጀት መብቶች የሚከተሉትን ብሏል ‹‹ የዜጎች የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ተግባራዊ ሂደት ገደብ በማይጣልበት ሁኔታ መከበር ሲኖርበት ነገር ግን ገደብ ቢደረግ እንኳን ገደቡ የዓለም ዓቀፍ ህግና ሰብአዊ መብቶችን መሰረት ያደረገ እና የእነዚህን መብቶች ሁለንተናዊ ጥበቃ እዉን የሚያደርግ መሆን አለበት፤በተለይም ዜጎች የፖለቲካ እና የአይማኖት ለማስከበር የሚያደርጓቸው ተቃውሞዎች መደገፍ አለባቸው፡፡ ››የሚል ሲሆን ፡፡የኢፌዴሪ ህገ መንስት አንቀፅ 30 ንዑስ አንቀፅ 1 ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዞ በሰላም የመሰብሰብ ፣ሰላማዊ ሠልፍ የማድረግ ነፃነት እና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ በማለት በህገመንግስቱ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን ይህ መብት ምን ያህል በአገራችን ተፈፃሚ ነው ብሎ መጠየቅ እና ምላሹን ማወቅ ብዙ እርቀት መሄድን የማይጠይቅ አይደለም፡፡ ከዚህ ቀደም በተለያየ ወቅት እና ቦታ በሰማያዊ እና በአንድነት ፓርቲ የተደረጉ አመፅ አልባ የአደባባይ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ምን ያህል ፈተኛ እንደነበሩ ለአብዛኞቻችን ግልፅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ሂደቶ የገዥው መንግስት ፍላጎት ከማስጠበቅ አንፃር እንጂ በየትኛውም ሕግ ድጋፍ ሣይኖረው አብዛኛው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ውጤት አልባ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ይህ ማለት ግን የተደረጉ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ሁሉ ውጤት አልነበራቸውም ማለት አይደለም፡፡ መንግሰት የሕግ ድጋፍ ሣይኖረው በራሱ ፍላጎትና ፍራቻ ብቻ የህዝቡን ቅሬታዎች ሁሉ ጫና በመፍጠር አፍኖን እንገኛለን፡፡ እንዲህ አይነቱን ሕገ-ወጥ መንግስታዊ ሥራ፣ አልቀበለም ማለት የማንኛውም ኢትዮጵያዊ ግዴታም ነው፡፡ይህን ደግሞ የማሳውቅ እና የማንቃት ኃላፊነት ስለ-አገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚል ሁሉ የሚመለከተው ሲሆን ፣በተለይ ፓርቲዎች የቀን-በቀን ሥራቸው መሆን አለበት፡፡ይሄንን ኃላፊነታቸውን በአግባቡ የተረዱ፣ ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም ትብብር የመሰረቱት ዘጠኝ ፓርቲዎች “ ነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የሕዝባዊ ትግል ፕሮግራም የመጀመሪያ ዙር እንቅስቃሴ ይፋ አድርገዋል፡፡ በኢትዮጵያ የተቃወሞ እንቅስቃሴ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር የተጠራ አመፅ አልባ የ24 ሰዓት የአዳር የአደባባይ የተቃውሞ ትይንት በታሪክ የመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡እንዲህ አይነቱ የሞራል የበላይነት እና ጥልቀት ያለው ሃሳብን የሚጠይቅ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ጥሪ ላስተላለፉት ፓርቲዎች በሙሉ አድናቆትን በሙሉ ልብ የሚያሰጥ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ሌሎች እውነተኛ የተቃዋሚ የፓርቲዎች በትብብሩ ያልታቀፉ፣ በተለይም በሂደቱ ከጅምሩ እስከ መጨረሻው ተሳትፋው በተለያየ ምክንያት የስምምነቱን ሰነድ ያልፈረሙ፣ የተቃውሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ከጋራ ትግሉ ብትቀላቀሉ ውጤቱ የበለጠ ያማረ ይሆናል፡፡በመሆኑም ከሕግ አግባብ ውጪ በማን-አልብኝ እና ትምክተኝነት የተነጠቅነው “የአደባባይ ተቃውሞ” የምናስመልስበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው፡፡ ይዚህ ጽሑፍ አቅራቢ፣ ከዚህ ቀደም “ኢህአዴግ ለምርጫ አልተዘጋጅም” በሚል ርዕስ፡፡ “ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡” ሲል ግንዛቤውን አቅርቧል፡፡ ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ፣ የተዘጋውን በር ለማስከፈት ይቻል ዘንድ በ9 ፓርቲዎች ትብበር ትግሉን የ ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል የፕሮግራም መርህ የመጀመሪያውን ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ የአንድ ወር ዕቅድ አዘጋጅቷል፡፡ በዕቅዳቸው መሠረት ዝግጅቱ የፕሮግራሙ የአፈጻጸም ስልት ፣የጊዜ ሰሌዳ፣ የቦታ ሽፋን፣የፋይናንስ ምንጭ፣ ዓላማዎች፣ትኩረት የሚደረግባቸው ጉዳዮችና መንግስታዊና የህዝብ ክፍሎች፣ዋና ዋና ተግባራት ፣በተጨማሪም በታሳቢነት በአፈጻጸም ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች/ደንቃራዎችና ሥጋቶች እንዲሁም ለፕሮግራሙን ስኬት አጋዥ ሁኔታዎች እንዲካተቱ አድርገዋል፡፡ይህ ደግሞ ከላይ እንደተገለፀው የፓርቲዎቹ ጥንቃቄ የታከለበት ዕቅድ መንደፋቸው የሚያመላክት ነው ፡፡ዘጠኙ የትብብር ፓርቲዎች በህዳር ወር የሚያተኩሩባቸው የተቃወሞ ተግባራትን እንደሚከተለው ይፋ አድረገዋል፡- 1.በየቤተ እምነቱ ጸሎት ፕሮግራም እንዲደረግ ጥሪ ማድረግና አባላት እንደየእምነታቸው ተሳትፎ ማድረግ፤ 2. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግ፤ 3. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ፤ 4. ለመንግሥታዊ ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት፤ 5. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት፤ 6. የህዝብ ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ፤ ናቸው፡፡ የነዚህ እንቅስቃሴዎች ማጠቃለያ ሕዳር 27 ተጀምሮ ሕዳር 28 የሚያበቃ የ24 ሰዓት የአዳር “የአደባባይ ተቃወሞ” ነው፡፡ በዚህ ፁሑፍ መግቢያ ላይ እንደተገለፀው “ብልህነት የተሞላበት ታላቅ የትግል መርህ ማድረግና መስፋፋት፣ጥንቃቄ የተሞላበት ዕቅድ፣ጠንካራ ሥራና ሥነ-ሥርዓታዊ አበራታች ትግል ለድል የመብቃቱ ዕድል የሰፋ ነው፡፡” እንደተባለው ሁሉ በዘጠኙ የተቃወሚ ፓርቲዎች የተጠራው የሕዳር ወር የተቃውሞ እንቅስቃሴ በስልት የተሞላ ስለሆነ ሂደቱ እና ውጤቱ ታሪካዊ እንደሚሆን ተስፋ የሚጣልበት ነው፡፡ ገዥው ፓርቲ እንዲህ አይነት ገፍቶ የመጣ ሕዝባዊ ጥያቂ ዕድል በመስጠት ፣ለሚጠየቁ ሕጋዊና ሰላማዊ ጥያቄዎች አዎንታዊ ምላሽ መስጠት ይጠበቅበታል፡፡ይህ ደግሞ መንግሰት ደግ ስለሆነ የሚያደርገው ሣይሆን ግዴታውም ጭምር ስለሆነ ነው፡፡ሆኖም ግን ከዚህ በተቃራኒ በጦር መሣሪያ ኃይልና በደህንነት አቅም በመመካት የሕዝብን ጥያቄ ለማፈን በተለመደው መልኩ መሄድ ከባድ ቀውሶች እንዲፈጠሩ መመኘት ነው፡፡ ይሁን እንጂ እንዲህ አይነቱ አሉታዊ ነገር መንግስት እንዲፈጠር ቢፈለግ እንኳን፣ ሕዝብ ከፓርቲዎቹ በሚሰጠው መመሪያ ሥነ-ሥርዓታዊና ደፋር እርምጃ ፣ብልህነት የተሞላበት አካሄድ በመከትል ፤አደባባይ ይዞ የወጣውን ጥያቄ ምላሽ አሰጥቶ፣ ሁሉም ነገር በሠላም እንደሚያበቃ የለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ፍላጎት ነው፡፡ በዚህም መሠረት የጉዳዩ ባለቤት የሆኑት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ‹‹የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧል›› ከሚለው አልፎ ‹‹ ተዘግቷል›› ወደሚል ድምዳሜ መሸጋገራቸውን በተጨባጭ ማስረጃ አረጋግጠዋል፡፡እዚህ ደረጃ ላይ መድረሳችሁንም በጋዜጣዊ መግለጫቸው ለሕዝብ አሳውቀዋል፤ሕዝቡ ደግሞ ወትሮም ቢሆን በአገራችን እየተካሄዱ ባሉ ምርጫዎች ሙሉ በሙሉ እምነት የለውም፡፡ይህ ደግሞ “ሰኔ እና ሰኞ” እንደሚባለው ነው፡፡ አሁን ላይ የእምነት ነጻነት ጠያቂዎች፣ጋዜጠኞች፣ጦማሪያን፣የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና አባላት፣ ከገዢው ፓርቲ የተለየ ሃሳብ ያላቸው ዜጎች በአፋኝ ህጎች፣ በፈጠራ ወንጀል ተከሰው አንድም በወህኒ ወይም በስደት ይገኛሉ፡፡በአገራችን የተረጋጋ የፖለቲካ ሥርዓት የለም፣የኑሮ ውድነት የአብዛኛ ኢትዮጵያዊ ትከሻ ያጎበጠ ነው፣ዜጎች በአገራችን ኢትዮጵያ ከቦታ ቦታ ተዘዋውሮ የመንቀሳቀስ እና ንብረት የማፍራት እንዲሁም የመኖር መብት እየተነፈገ ነው፣ሥራ-አጥነት፣ስደት ፣በአገር ላይ ተስፋ መቁረጥ እና ሌሎች መሰል ችግሮች በመንግሰት አስተዳደር ድክመቶች አማካኝነት የተከሰቱ ናቸው፡፡ ስለዚህም እንዲ አይነቱ ደካማ የመንግስት አስተዳደር ለመለወጥ ምርጫ ያስፈልጋል፡፡ይሁን እንጂ ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ ማካሄድ አይቻልም፣ በምርጫ ሥም ጫፍ ላይ የደረሰው ሠላማዊ የነጻነት ትግል ጥያቄ መዳፈን የለበትም፡፡ በመጨረሻም ለዚህ ጽሑፍ ማጠቃለይ እንዲሆን ሙሉ በሙሉ ከዘጠኙ የፓርቲዎች ትብብር ከሰጡት ጋዜጣዊ መግላጭ ሃሳብ በመዋስ ነው፣የዚህም ፁሑፍ አቅራቢ ከዚህ የተለይ እምነት የለውምና፡፡ “ ገዢው ፓርቲ በጉዳይ ፈጻሚው የምርጫ ቦርድ በኩል በተለመደው መንገድ በምርጫ ሥም ለመሥራት የተያያዘውን ቧልት ራቁቱን በማስቀረት ለ ነጻ፣ፍትሃዊ፣ ተኣማኒና አሳታፊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ፣ የምርጫ ሜዳውን እንዲያስተካክል በሠላማዊ ትግል አዎንታዊ ተጽዕኖ ለማሳረፍ በእኛ በኩል አስፈላጊውን መስዋዕትነት ሁሉ ለመክፈልና እስከ መጨረሻው በጽናት መቆም ” በማለት ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል ፡፡ይበል !!!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !
Image

Image
ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ የብር 20,000(የሃያ ሺህ ብር) ዋስ ተጠይቆበት ወደ ማረፍያ ክፍል መግባቱ ታወቀ፡፡
ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር የጅማ ዩኒቨርሲቲ ባቀረበበት ክስ የፕሬስ ህጉን በሚፃረር መልኩ ለአራት ቀናት በማዕከላዊ ታስሮ የተለቀቀው ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ክሱ እንደ አዲስ እንዲቀሰቀስበት ከተደረገ በኋላ ዛሬ በተለምዶ ገዳም ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ባለው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ሁለተኛ የወንጀል ችሎት ከእንቁ መፅሔት አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን ጋር እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
ችሎቱ በሰጠው ትዕዛዝም ጋዜጠኛ ኤሊያስ ገብሩ እና የእንቁ አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን እያንዳንዳቸው የብር 20,000(የሃያ ሺህ ብር) ዋስ እንዲያቀርቡ እስከዛውም ወደ ማረፊያ እንዲሄዱ አዟል፡፡ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ እና አምደኛ አምሳሉ ገ/ኪዳን በአሁኑ ሰዓት ችሎት መድኃኔዓለም አካባቢ በሚገኘው ወረዳ 8 ጣቢያ እንደሚገኝም ታውቋል፡፡

( …. መርዝን በመርዝነት ስለመርዝ መመረዝ :
የመርዙን ለመርዙ በመርዙ ማስመረዝ …. )
(መርዝ ……. ::) #Ethiopia #EPRP #EthiopiaTeachers #MinilikSalsawi
iframe
የታላቁ ገጣሚ እና ባለቅኔ ሃይሉ ገብረዮሃንስ (ገሞራው) አጭር የሕይወት ታሪክ http://www.debteraw.com/gemoraw/ = ድምጽ ላጣው ሕብረተሰብ ድምጽ ሆኖ በማስተጋባቱ በሶስት መንግስታት ስቃይ ያየ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ሃይሉ ገሞራው – ቨድዮውን ይመልከቱት

phpBB [video]

Image

ኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብቶች ላይ የምትፈጽመውን ጥሰት ካላቆመች የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ከአዲስ አበባ መቀየር አለበት ተባለ። በደቡብ አፍሪካ ዊትስ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደ የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ አንጎላዊው ጋዜጠኛ ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች መፍታት አለበት ብሏል።
Image

ራፋኤል ማርኩዌዝ ደ ሞራይዝ አንጎላዊ ጋዜጠኛ ነው። በሙያው በሃገሩ አንጎላ በርካታ ክስ እና እስር እንደገጠመው ይነገራል። ባለፈው ወር በደቡብ አፍሪካ ዊትስ በተካሄደው የአፍሪካ የምርመራ ጋዜጠኝነት ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽን ጨምሮ በሰብዓዊ መብቶች ላይ ጥሰት በመፈጸም ከአፍሪካ ህብረት ህልም በተቃራኒ ቆማለች በማለት ተችቷል። ”የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ በቀዳሚነት የመላ አፍሪካውያንን ህልም ይወክላል። የሰው ልጅ ክብር እና የሰብዓዊ መብት ክብር ደግሞ የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ህልም ነው። ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ የሰዎችን ሰብዓዊ መብት በመጣስ በተቃራኒው መንገድ እየተጓዘች ነው። ይህ ደግሞ የአፍሪካውያንን ህልም አይወክልም። የኢትዮጵያ መንግስት ያሰራቸውን ጋዜጠኞች በመፍታት ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ነጻነትን እንዲያከብር እና ዜጎች እና ጋዜጠኞች ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን በተግባር እንዲያውሉ እንዲፈቅድ የአፍሪካ ህብረት ጫና ማድረግ ይኖርበታል። ”

ራፋኤል በጉባኤው የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችን እስር እና ክስ እንዲሁም የቀድሞው ፍትህ ጋዜጣ አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝን የሶስት አመት ብያኔ በማሳያነት አንስቷል። አፍሪካውያን ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በኢትዮጵያ ያለውን ሁኔታ በቸልታ አልፈዋል ሲልም ተችቷል። ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብትን ማክበር ካልቻለች የአፍሪካ ህብረት ከአዲስ አበባ መነሳት ይኖርበታል ብሎ ያምናል።

”የተወሰኑ ጋዜጠኞችን አውቃለሁ። በ2005 ተኩስ ሲጀመር እና ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ሲታሰሩ በአዲስ አበባ ነበርኩ። አሁን በሃገሪቱ ስላለው ሁኔታ በቂ ግንዛቤ አለኝ። ከኢትዮጵያውያን ምሁራን እና አሁን ባለው መንግስት የተለያየ ጫና የደረሰባቸውን ሰዎች አገኛለሁ። የአፍሪካ ህብረትን ለመወከል በመጀመሪያ ሰብዓዊ መብትን የሚያከብር ሃገር እንፈልጋለን። ኢትዮጵያ ይህንን ማድረግ ካልቻለች እንደ አፍሪካዊነታችን የአፍሪካ ህብረት መቀመጫውን ዜጎች ራሳቸውን የመግለጽ እና ሰብዓዊ መብት ወደ ተከበረበት ሃገር እንዲዛወር መጠየቅ ይኖርብናል። ምክንያቱም ግለሰቦች የሚከበሩባት መንግስታት የህዝብ አገልጋይ እንጂ ከህግ በላይ ያልሆኑባት አጋርነት የጠነከረባት አፍሪካን እንሻለን። ኢትዮጵያ ደግሞ በአሁኑ ወቅት ይህን እያደረገች አይደለም። ””

ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ባለፈው ሳምንት ባወጣው ዘገባ ባለፈው አመት ብቻ በኢትዮጵያ ስድስት የህትመት ውጤቶች ሲዘጉ ከ ሰላሳ በላይ ጋዜጠኞች መሰደዳቸውን ይፋ አድርጓል። በምህጻሩ ሲፒጄ ተብሎ በሚጠራው የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪ ተቋም መሰረት ደግሞ ቢያንስ 17 ጋዜጠኞች በኢትዮጵያ በእስር ላይ ይገኛሉ። ራፋኤል ማርኩዌዝ በእስር ላይ ያሉ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ አፍሪካውያን ሊተባበሩ ይገባል ሲል ይናገራል።

”አፍሪካውያን በሙሉ በተለይም ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በትብብር ከሰራን የኢትዮጵያ መንግስት ቆም ብሎ ራሱን እንዲፈትሽ ማድረግ እንችላለን። አላማችን ኢትዮጵያን ማግለል አይደለም። አላማችን ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን እንድታከብር ሃሳባቸውን በነጻነት የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀማቸው የታሰሩትንም እንድትፈታ ነው።”

http://www.dw.de/%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1% … a-18051929

– “መኢአድን ለማዳን እንረባረብ::” የጠቅላላ ጉባዬ አባላቱ
– ከድርጅቱ የተባረሩ የወያኔ ቅጥረኞች በእርቅ ስም ወደ ድርጅቱ ተመልሰዋል::(አባላት)
– ጠቅላላ ጉባዬው የተካሄደው ፍጹም አምባገነንነት በሞላበት ሁኔታ ነው::

Minilik Salsawi

በኢትዮጵያ በአንጋፈነቱ የሚታወቀው እና በፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የተመሰረተው መአሕድን የተካው በኢንጂነር ሃይሉ ሻውል ሲመራ ቆይቶ አቶ አበባው መሃሪ የተረከቡት የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ፓርቲ (መኢአድ)ከባድ የመፈረካከስ አደጋ ከፊቱ ተደቅኗል ሲሉ የድርጅቱ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ በላኩት መረጃ ገልጸዋል::

መኢአድ ከአንድነት ፓርቲ ጋር የሚያደርገውን ውህደት ተከትሎ ገዢው ፓርቲ ከድርጅቱ የተባረሩትን እነ አቶ ማሙሸት እና ኮሎኔል ታምሩን አደራጅቶ ውህደቱን በመበጥበጥ በመኢአድ ቢሮ ውስጥ ከዚህ ቀደም በተደረገ ስብሰባ ላይ ደህንነቶችን እና ፖሊሶችን አስከትሎ በመምጣት ከፍተኛ የሆነ ብጥብጥ አንስተው የነበረ ቢሆንም ሳይሳካላቸው ቀርቷል::

ውህደቱ የጉሮሮ ላይ አጥንት የሆነበት የወያኔው መንግስት ምርጫ ቦርድን ተገን በማድረግ መኢአድን በማጉላላት ውህደቱ እንዳይፈጸም ከፍተኛ ደባ ከቅጥረኞቹ ከነማሙሸት ጋር በመሆን ሲፈጽም ቆይቶ በስተመጨረሻ ኢንጂነር ሃይሉን በማስገደድ የተባረሩ አባላትን አቶ አበባው መልሶ እንዲያስገባ ካላስገባ ስልጣኑን እንዲለቅ በሚል ጫና የበላይ ጠባቂነታቸውን ተገን በማድረግ የወያኔ ስራ አስፈጻሚዎች ወደ ድርጅቱ ሰርገው በመግባት ድርጅቱ አደጋ ውስጥ መሆኑን የድርጅቱ አባላት በምሬት ተናግረዋል::

ኢንጂነር ሃይሉ ሻውል ከዚህ ቀደም ከወያኔ ጋር ከድርጅቱ እውቅና ውጪ በራሳቸው ፍቃድ ከሟቹ መለስ ዜናዊ ጋር የምርጫ ደንብ የሚል ስምምነት ተፈራርመው ድርጅቱ እንዲዳከም እና ለወያኔዎች በሩን እንዲከፍት ያደረጉ ሰው ቢሆንም ቀደም ብለው ለትግሉ የከፈሉት አስታውጾ ታይቶ የድርጅቱ የበላይ ጠባቂ እና አማካሪ ቢደረጉም በድርጅቱ ማህተም የተባረሩ ቅጥረኞች ወደ ድርጅቱ እንዲመለሱ አድርገዋል ሲሉ አባሎቹ ተናግረዋል::ኢ/ር ሀይሉ ሻውል በፍጹም አምባገነንነት ጉባኤተኛውን አፍነው እርሳቸው በሚፈልጉት መልኩ በእርቅ ጭምብል አንዱን አስወጥተው አንዱን አስገቡ፡፡ ሲሉ የጠቅላላ ጉባዬ አባላቱ ተናግረዋል::

ከዚህ ጉዳይ ጋር የተያያዘዉን መኢአድን የተመለከተ የአቶ ሸንቁጥ አየለን ጽሁፍ ያንብቡት ::
viewtopic.php?f=2&t=89291

የአቶ ሸንቁጥ አየለን ጽሁፍ ያንብቡት ::
መግቢያ –
——-
“የቱ ይቀድማል?:- በዲክራሲያዊ መርህ ላይ የቆመ ሀገር ወይስ ዲሞክራሲን ሊሸከም የሚችል ባህል ላይ የቆመ ማህበረሰብ ?” በሚለዉ ጽሁፌ የፖለቲካ ፓርቲዎቻችን የዉይይትና የክርክር ባህል አለመዳበርን በማስመልከት የተወሰኑ ፓርቲዎችን እያነሳሁ ወቅሼአቸዉ ነበር:: ፓርቲዎች ዉስጥ በግለሰብ ወይም በቡድን ደረጃ የሀሳብ ክፍፍል ሲነሳ ፓርቲዎች በሀሳብ የመሸናነፍ ባህል እንዳላዳበሩ ምሳሌ አድርጌ ካቀረብኩት ፓርቲ አንዱ የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ነበር:: እንዲህም ስል ፓርቲዉን በሀሳብ ሸንቆጥ አድርጌዉ ነበር:-

“መኢአድ ዉስጥ ችግር ከተፈጠረ አራት አመታት አለፉ:: በርካታ የእርቅ ጥረቶች እንደተደረጉ የኢትዮጵያ ሰዉ አስተዉሏል :: በልዬ ልዩ ሚዲያዎችም ላይ ተደምጧል:: ሆኖም በሃሳብ የተለያዩት ሰዎች አንድም ቀን ቁጭ ብለዉ ተደማምጠዉ በሀሳብ ተፋጭተዉ እና ልዩነታቸዉን አቻችለዉ መፍትሄ ላይ ሲደርሱ አልታዬም:: አንዱ ሌላዉን ይወነጅላል:: አንዱ አንዱን ሰርጎ ገብ ነዉ : ባንዳ ነዉ ሲል ስሙን ያጠፋል:: ደግሞ አንዱ እሱ ብቸኛ የድርጅቱ ተጠሪ ይሆንና ሌላዉን ለማግለል ዳዉላ ሙሉ ከዚያም ዘሎ ከቶንም ስፍር የበለጠ ሀሰትና ዉሸት ይደረድራል:: እናም መደማመጥና መነጋገር ብሎም በሀሳብ መፋጨትና ወደ መቻቻል መድረስ ቦታም አላገኙም:: አስቂኙ ነገር ታዲያ መኢአድ ዉስጥ ተከፋፍለዉ ያሉ ብድኖች ሳያፍሩ ስለ ብሄራዊ እርቅ ጉዳይ ሲናገሩ መስማት የተለመደ ነገር መሆኑ ነዉ:: እራሱን ከራሱ ጋር በሀሳብ ተከራክሮና ተወያይቶ ለማስታረቅ ያልቻለ ቡድን ስለብሄራዊ እርቅ ሲያወራ መስማት እጅግ አስቂኝ ነገር ነዉ::”

ይሄን ወቀሳ ያወረድኩበት በመኢአድ ላይ ብቻ አይደለም ነበር:: ሌሎችም የሀገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎችንም አጣቅሸ ነበር:: ሆኖም ዛሬ ትኩረቴን መኢአድ ላይ አድርጌአለሁ:: ምክንያቱም ዛሬ መኢአድ ማንም ኢትዮጵያዊ ያላሰበዉን እና ያልጠበቀዉ የዲሞክራሲ ማማ ላይ ተፈንጥሮ ወጥቶ ተገኝቷልና::

ለራሱ ሀሳብና ህሊና ብቻ ተገዥ የሆነዉ ደፋሩ : እዉቁና ወጣቱ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ባንድ ወቅት የመኢአድ ሰዎች እርስ በርስ ንክሻ እና አለመግባባት ብቻ ሳይሆን በፕሮፌሰር አስራት የሙት አመት ላይ እንኳን ሲጣሉ ቢያስተዉል ” ዛሬ የፕሮፌሰር አስራት ሙት አመት ብቻ ሳይሆን የመኢአድም ሙት አመት ነዉ” ሲል መጻፉን አስታዉሳለሁ::

እኔም ሆንኩ ተመስገን ደሳለኝ በመኢአድ ላይ ትችቶችን ያወረድንበት ወደን ሳይሆን በሚጠበቅበት ስፍርና ቁመት ልክ ሆኖ አልገኝ ስላለን ነበር:: መኢአድ ከ2003 ዓም እስከ አሁኑ ጥቅምት 30/ 2007 ዓም ድረስ ለአራት አመታታ ያሳለፈዉ ዉጣ ዉረድ እና አባላቱም በአምስት ቡድን ተከፋፍለዉ ያደረጉት ሽኩቻ ጉድ የሚያስብል ብቻ ሳይሆን ወይ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚያሰኝ ነበር:: አንድ ፓርቲ አምስት ቡድን ተከፋፍሎ መልሶ ሊድን የሚችለዉ እንዴት ነዉ?

የመላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ወደ ዲሞክራሲ የከፍታ ጉዞ ?
========================================

ለአራት አመታት በአምስት ቡድኖች ተከፋፍለዉ የማያቋርጥ አሉባልታ: ስድብ ወቀሳና ክስ ላይ ተጠምደዉ የነበሩ ሀይሎችን ወደ አንድ ማምጣትና በዉይይት ችግራቸዉን ፈትተዉ እርቅ ወርዶ አንድ የፖለቲካ ሀይል ሆነዉ እንዲቀጥሉ ማድረግ ይቻላል? ለአራት አመታት ያስተዋልነዉ ነገር አይቻልም የሚል ፍጹም አስተማማኝ ድምዳሜ ላይ መድረስ ነበር:: ለዚህም ነዉ ከንግዲህ የመኢአድ ነገር አከተመለት የተባለዉ ነበር::

የሆኖ ሆኖ በጠንካራ ሽማግሌዎች እረዳትነት እያንዳንዱን አምስት የተለያዬ ቡድን በማነጋገር : በተለያዬ ወቅት አመራር በመሆን የተመረጡትን ሀይሎች ሁሉ በማካተት እንዲሁም አንድንም ወገንን ያላገለለ : ከገጠር እስከ ከተማ ያለዉን አመራር በማካተት ጠቅላላ ጉባኤ በማድረግ አስገራሚ ዉጤት ላይ የደረሰ ፓርቲ ሆኖ ወጥቷል:: ዉጤቱን አስገራሚ ያደረገዉም የጠቅላላ ጉባዔዉ ሂደት እጅግ ጠንካራ: በበርካታ ሙግቶች : ክርክሮች : ፊት ለፊት በሚነሱ የተፋጠጥ አካሄዶች እዲሁም አንድም እዉነት ሳይቀር እዚችዉ እህዝብ ፊት ትፋት የሚል አካሄድ የታጀበ መሆኑ ነበር::

እያንዳንዱ ቅሬታ አለኝ የሚል ቡድን ከስድስት መቶ ተሰብሳቢ በላይ ባለበት እዉነት ስትሞግተዉ ወይ ያቀረቅራል ወይም እዉነትን ተርትሮ ለተሰብሳቢዉ ያስረዳል;: ተሰብሳቢዉ ያደምጣል: አፋጣጭ ጥያቄን ይጠይቃል ብሎም ደግሞ ብይንን ይበይናል:: መሸወድ አይቻልም:: ብዙሃን እዉነትን እሰዉ ፊት ላይ ያነባታል: ብዙሃን እዉነትን ከሰዉ ኪስ ዉስጥ በርብሮ ያወጣታል:: አሉባልታ ተናግሮ ማምለጥ አይቻልም:: ፊት ለፊት ላሉባልታዉ መልስ የሚሰጥ ወገን አለና:: ከሁሉም በላይ ደግሞ አይኑን እና ጆሮዉን አንቅቶ የሚያስተዉል ከስድስት መቶ በላይ ህዝብ አለና:: የትም መደበቅ አይቻልም:: የዲሞክራሲ ዉበቱ ህዝብ ፊት እራቁትን ስለሚያስቆም ነዉ::

እናም እያንዳንዱ ቡድን ከጥቅምት 28 እስከ ጥቅምት 30/2007 ዓም በተደረገዉ እልህ አስጨራሽ ግን ደግሞ የዲሞክራሲ የከፍታ ማማ ላይ የረገጠ ሊባል በሚችል የጠቅላላ ጉባዔ ሂደት ዉስጥ ያለዉ አማራጭ ወደ አንድ መምጣትና በጋራ ለዲሞክራሲ መታገል መሆኑን በደንብ የተማረበት: እያንዳንዱንም ለሌላው ወገን ያስተማረበት ወቅት ሆኖ አልፏል:: ለሶስት ቀናት በዘለቀዉ የስብሰባ ሂደት ዉስጥ እስከ ለሊቱ ስድስት ሰዓት ድረስ በማምሸት የተደረገዉ የዲሞክራሲ ከፍታ ላይ የደረሰ የሀሳብ ፍጭት: ክርክር: እና ዉይይት እጅግ ገንቢና ለወደፊት የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች ጥሩ ልምድ ጥሎ ያለፈ አስተምህሮት ይመስላል:: እዚህች ጋ በተለያዩ ፓርቲዎች ስር የታቀፉ ፖለቲከኞቻችን ፈገግ ሲሉ ይታዩኛል:: እኛማ የዲሞክራሲዋን ቁልፍ ጨብጠናታል ሲሉ ፈገግ ማለታቸዉ አንዱ የዲሞክራሲ ድቀት መገለጫ መሆኑን እናጣቅስና እንለፈዉ::

ሀይሉ ሻዉል ከ28-30/3007 ዓም ባሉት መጨረሻ የፖለቲካ ቀኖቻቸዉ ዉስጥ የሰጡት አመራርም ብዙዎቹን አስገርሟል:: “ከንግዲህ እኔ ከማንም ጋር ጸብ የለኝም:: እያንዳንዳችሁም እርስ በርሳችሁ መታረቅና በመሃከላችሁ ያለዉን ጸብ ንዳችሁ አብራችሁ መስራት አለባችሁ::” ይሄን አቋማቸዉን የተፈታተኑ አንዳንድ ወገኖች ቢኖሩም የብዙሃኑም ተሰብሳቢ ዋና ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ሂደትን ማዬት እንጅ ብጥብጥ ስላልነበረ ነገሮች ሁሉ በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቅ ችለዋል:: በዉነቱ ሂደቱ እጅግ አስጨናቂ እንደነበረ ከ20 በላይ ተሰብሳቢዎችን አንድ ባንድ ቃለ መጠይቅ በማድረግ ተረድቻለሁ:: ብዙዎች እንዳሉትም በመጀመሪያ አካባቢ ሂደቱ ከመክበዱ የተነሳ አንድ አጀንዳ ላይ አንድ ቀን የመዋል አካሄድ እንደነበርም አብራርተዉልኛል::

አቶ ማሙሸት አማረ :- አዲሱ የመኢአድ ፕሬዝዳንት ተስፋና ተግዳሮት
=================================================
ማሙሸት አማረ የመኢአድ አዲስ ፕሬዝዳንት ሆኖ በከፍተኛ ድምጽ ተመርጧል:: ማሙሸት አማረ ገና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲት የአንደኛ አመት ተማሪ ሆኖ ዩኒቨርስቲ እንደ ገባ ወገን ሀገርህ አይደለም ተብሎ ካባቶቹ ሀገር ሲባረርና ገደል ሲገፈተር የምን ትምህርት ነዉ ሲል ከፕሮፈሴር አስራት ጋር የፖለቲካ የትግል አዉድማ በወጣት እድሜዉ የተቀላቀለ ሰዉ ነዉ:: አቶ ማሙሸት በፖለቲካ ሂወት ዉስጥ እየተመላለሰም በርካታ የትምህርት ዘርፎችን በማጥናት እራሱን ለአመራር ብቁ ያደረገ ሰዉ ነዉ :: በማርኬቲን ዲፕሎማ: በሊደርሽፕ/አመራር/ ዲፕሎማ እንዲሁም በማኔጅመንት ዲግሪዉን አጠናቋል:: በአሁኑ ሰዓት ደግሞ በፖለቲካ ሳይንስ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ትምህርቱን የቀጠለ ብርቱ የሰላማዊ ትግል መሪ ነዉ::

ለአስራ ሁለት አመታት የታሰረ ሰዉ ቢሆንም በኢትዮጵያ ፖለቲካ የማይማረር : በዲሞክራሲ ሂደት የሚያምን እና የሚያምንበትን ሀሳብ ፊት ለፊት የሚያራምድ ፖለቲከኛ ነዉ:: በቅርበት የሚያቁትም እንደሚገልጹት ለሚያምንበት ነገር ብቻ የሚኖር ሰዉ ሲሉ ይገልጹታል::

ማሙሸት በሀሳብ ልዩነት ያምናል:: በክርክር ያምናል:: ሰዉ አክባሪ እንደሆነ የሚነገርለት ማሙሸት ተናግሮ የማሳመን አቅሙን አብረዉት የሰሩ ሁሉ ይመሰክሩለታል:: ከ28-30/2007 ዓም በተደረገዉ ጠቅላላ ጉባዔ ላይም ይሄንኑ ተናግሮ የማሳመን ችሎታዉን እንዳስመሰከረ ብዙዎች ተስማምተዉለታል:: ሆኖም ማሙሸት አንድ ነገር አይሆንለትም:: ይሄዉም እዉሸትና መስሎ ማደር:: ይሄ ነገር ለፖለቲካ ሂወቱ ዋናዉ ተግዳሮትም አዎንታዊ ገጽታም ሆኖ ከፊቱ የተደነቀረ ይመስላል::

ለአራት አመታት ከማሙሸት አማረ ጋር በሀሳብ ተለያይተዉ የከረሙትና በማሙሸት ላይ ክፉኛ ቂም ይዘዉ የነበሩት ኢ/ር ሀይሉ ሻዉል ከማሙሸት ጋር ሲታረቁ ማሙሸት ለአቶ ሀይሉ በሽማግሌዎች ፊት ያቀረበላቸዉ አንዱ ጥያቄ “ለመሆኑ እኔ እርስዎን ሰድቤዎታለሁ?” የሚል ጥያቄ ነበር:: ሀይሉም ” እረ በፍጹም” ሲሉ መለሱ:: ማሙሸትም በማስከተል ” ታዲያ ሚዲያዉ ሁሉ ማሙሸት አማረ አቶ ሀይሉን ሰደባቸዉ እያለ ሲያናፍስ እርስዎ ዝምታን የመረጡት ለምን ነበር?” ሲል ጠየቀ:: ሀይሉም መለሱ “እኔ ለያንዳንዱ ሚዲያ ያሉባልታ ወሬ ምላሽ ልሰጥ የምችልበት እድሜ ላይ አይደለሁም” ሲሉ መለሱ::

“እኔና አንተ የተጣላንዉ አንተ ለእኔ አልታዘዝም ስላልክ ብቻ ነዉ” ሲሉ አስከትለዉ ሀይሉ ተናገሩ:: ማሙሸትም ለአቶ ሀይሉ ሲመልስ ” እኔ ለእርስዎም ሆነ ለማንም ህገወጥ በሆነ መንገድ የምታዘዝ ሰዉ አይደለሁም:: ከእርስዎም የተጣላንዉ እርስዎ የድርጅቱን ህገ ደንብ ጥሰዉ ያለስልጣንዎት የማይገቡ ዉሳኔዎችን ስለወሰኑ ነዉ::አሁንም ሆነ ወደፊት የድርጅትን ህገ ደንብ የሚጥስ መሪ አምባገነን መሪ ነዉ:: የተጣላንዉም እርስዎ ህግ ስለጣሱ ነዉ:: አሁን ያለዉን አምባ ገነን ስርዓት እየታገልን በተቃዋሚ ፓርቲዎች ዉስጥ ደግሞ የፓርቲ አምባ ገነንነትን አናበረታታም:: ማንኛዉንም አይነት አንባገነንነትን እንታገለዋለን እንጅ:: ” ሲል ቁርጥ ያለ መልስ መለሰ::

ማሙሸት በማስከተል እንዲህ አለ “አባቴ ገና ዩኒቨርስቲ አንደኛ አመት ተማሪ እያለሁ ጠርቶ “ወገን እያለቀ ዝም የምትሉት ምንድን ነዉ? ከፕሮፌሰር አስራት ጋር ተነስታችሁ ታገሉ:: ለእዉነት ሙት” ሲል ለእዉነት ብቻ እንድኖር መመሪያ ሰጥቶኛል:: እዉነትን ማንም ከጣሳት ከዚያ ሀይል ጋር በሀሳብ ሙግት መግጠሜ አይቀርም:: ከርስዎም ጋር የሆነዉ ይሄዉ ነዉ::” ሲል አስገራሚዉን ያባቱን ታሪክ ተናገረ:: ግን በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት አባቶች አሉ እንዴ የሚያስብል ነገር ነዉ::

እናም ሀይሉ ሻዉል ጠቅላላ ጉባዔዉ በተደረገበት ቀን አንድ አስገራሚ ነገር ተናገሩ ” እናንተ ይሄን ማሙሸትን አታቁትም:: እሱ የሚለዉ እዉነት ብቻ ትዉጣ ነዉ:: እንደ ፖለቲከኛ የሚያድበሰብሰዉ ነገር የለም:: የሚፈልገዉ እዉነቷን ብቻ ነዉ:: በአንደበቱ ሁለት ወይም አንድ ነገር አይናገርም:: አንድ ነገር ብቻ ይናገራል:: እሱም እዉነት ብቻ::”

የጠቅላላ ጉባዔዉ ተሰብሳቢ በአቶ ሀይሉ ንግግር እየተገረመ እያለ ድርጅቱን ለተወሰነ ጊዜ በፕሬዝዳንትነት የመሩት አቶ አበባዉ ደግሞ (ከማሙሸት ጋር ጸብ የነበሩ ናቸዉ) ብድግ ብለዉ ” አቶ ማሙሸት ድርጅትን በመክዳት ወይም በገንዘብ ወይም በሌላ በምንም መጥፎ ባህሪ አይታማም :: የሱ ችግር ሀይለኝነት ብቻ ነዉ:: ተጋፋጭ ነዉ:: እልህኛ ነዉ” ሲሉ ስለ ማሙሸት አማረ ያላቸዉን አመለካከት አካፈሉ::

እንግዲህ እነዚህና ከሌሎችም በርካታ ምንጮች የሰበሰብኋቸዉ መረጃዎችን ስተነትናቸዉ ማሙሸት አማረ አሁን በተረከበዉ የፕሬዝዳንትነት ሀላፊነት ቦታ ላይ የሚያሳካቸዉ በርካታ አዎንታዊ ጉዳዮች እንደሚኖሩ መገመት ይቻላል:: እንዲሁም የሚገጥሙት ተግዳሮቶች ቀላል የሚሆኑ አይመስለኝም::

እነዚህ አሉታዊና አዎንታዊ ፈተናዎች ከኢትዮጵያ ባህላዊ ጽንፍ ዉስጥ መንጭተዉ የሚዎጡ ጭብጦች ናቸዉ:: በኢትዮጵያ እዉነት ወዳዱ ሰዉ ፍጹም እዉነት ወዳድ ነዉ:: ሸፍጠኛዉ ደግሞ ጽንፈኛ ሸፍጠኛ ነዉ:: ፕሮፌሰር ሰባስኪ የተባለ የጣሊያን ፕሮፌሰር የኢትዮጵያ ታሪክ በፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ወቅት በሚለዉ መጽሀፉ (እምሻዉ አለማዬሁ ወደ አማርኛ ተርጉሞታል ) አንድ አስገራሚ መረጃን አካፍሎናል:: ጣሊያኖች ስለ ሀበሻ ስነ ልቦና ጥናት አደረጉ:: በርግጥ ጥናቱ ወታደራዊ ጥናት ስለነበረ ያተኮረዉ የሀበሻን ሰዉ ስነልቦና ከወታደራዊ ጭብጥ አንጽር የመተንተን ስራ ላይ ነበር::

እናም የጥናቱ ዉጤት አስገራሚ ነበር:: አጭር የጥናቱ ድምዳሜም ሀበሻ ጀግና ከሆነ ፍጹም ጀግና ነዉ:: ከአፍሪካ ምድር የጀርመንን ጦር ጠራርገህ ለማስወጣት ከፈለግህ ጀግኖቹን የሀብሻ ወታደሮችን መልምል:: ሆኖም ደግሞ አበሻ ፈሪ ከሆነም ፍጹም ፈሪና አድር ባይ ነዉ:: ስለዚህ ምልመላችን ለመለዬት ከባድ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል የሚል ነበር::

ልክ እንደ ጣሊያኖቹ ጥናት ሁሉ ኢትዮጵያ ባህል ዉስጥ እዉነተኛ ሰዎች ሁለት አይነት ጽንፈ ላይ የተንጠለጠለ ቦታ አላቸዉ:: አንድኛዉ ማማቸዉ የጀግናና የተወዳጅነት ማማ ሲሆን ሁለተኛዉ ማማ ደግሞ የተጠላ ማማ ነዉ:: ገትጋታ ተብለዉ የመጠላታቸዉ እድልም የዚያኑ ያህል ሰፊ ነዉ::

ለዚህ እንግዲህ ብቸኛዉ መፍትሄ ሁል አቀፍ የሆነ የጋራ አመራር እንዲኖር ማድረግ እንዲሁም የተለያዩ ሀሳቦች የሚያንጸባርቁ ቡድኖችን ማበረታታት ወሳኝ ነዉ:: ማሙሸት አማረ ትልቁ የቤት ስራዉ የሚሆነዉም ይሄዉ ነዉ:: እርግጥ ነዉ ባዋቀረዉ ካቤኔ ዉስጥ አካታች ስራን እንደሰራ ብዙዎች መስክረዉለታል:: በተለያዩ ጎራ ተከፋፍለዉ የነበሩትን ልዩ ልዩ አመራሮች ሁሉ ጥሩ አድርጎ በካቢኔዉ ዉስጥ ማካተቱም ለወደፊት ሰፊ የሀሳብ ምንጭ ያለዉ አመራርን በድርጅቱ ዉስጥ እንዲፈጠር ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እንዳሰበ እንዲሁም ሁሉም አካላት በትክክል እንዲታቀፉ መፈለጉን አመላካች ነዉ:: የሆነ ሆኖ ግን ወደፊትም ሰፊ መሰረት ላይ የቆመ ሰፊ ማህበረሰብን የሚያካትት የአመራር ሀይል የመመስረት ጠንካራ ጥረት የሚጠበቅበት ይመስለኛል::

ከዚህ በተጨማሪም ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በትብብር የመስራት እና የላቀ ሀገራዊ የዲሞክራሲ እሴት ላይ መስራት ሌላዉ ትልቁ የቤት ስራዉ የሚሆን ጉዳይ ይሆናል:: በተለይም የኢትዮጵያ ሰዉ እፊት ጀምሮ ፓርቲዎች ወይ ተባበሩ አለዚያ ተሰባበሩ የሚለዉ አቋሙ ወደፊት እየጠነከረ እንደሚመጣ ይጠበቃል:: እናም መኢአድ ለዚህ የህዝብ የልብ ትርታ የሚሰጠዉ ምላሽ የማሙሸት አማረ ያመራር ብቃትን ከሚፈትኑ ጥቂት ጉዳዮች ዉስጥ አንዱ የሚሆን ይመስላል::

ሌሎች ፓርቲዎች ከመኢአድ ተሞክሮ ምን ሊቀስሙ ይገባል?
==============================
መኢአድ ለአራት አመታት በተለያዩ ቡድኖች ተከፋፍሎ የዳከረዉን መዳከር ከቶ እንዳይደገም ደግሞም እንዳይታሰብ ብለዉ ሌሎች ፓርቲዎች ተሞክሮ ሊሆናቸዉ የሚችል አስተምህሮት መርምረዉ ማዉጣት ያለባቸዉ ይመስለኛል:: እኛ ሀገር የፖለቲካ ትንታኔ ማድረግ: ከአንድ ሂደት ምን ተማርን ብሎ መወያዬት : ሀሳብ ለሀሳስብ ለመለዋወጥ መነሳሰት ፈጽሞ ባህላችን አይደለም:: በተለያዩ ፓርቲዎች ጥላ ስር ታቅፈዉ ያሉ ሀይሎች በተለይም አሁን በተለያዩ ብድኖች ተከፋፍለዉ ያሉ ሀይሎች ቁጭ ብለዉ ትንታኔ መስሪያ ግዜአቸዉ ይመስለኛል::

ህጋዊ መፈንቅለ ስልጣን ተደረገ ብሎ አንዱ ወገን ሲጮ አንድኛዉ ወገን አትንጫጫ ብሎ አፍ ለማሲያዝ ከመሄድ የመኢአድ ተሞክሮ ምን ይመስላል ብሎ መጠዬቅና መወያዬት ብልህነት ይመስለኛል:: ጠንካራ ዉይይትና ክርክር ሁሉንም የሀሳብ ልዩነቶች ባይፈታቸዉም ዲሞክራሲያዊ ከፍታ ላይ መዉጣት ግን ያስችላል:: ዲሞክራሲ ከፍታ ላይ የወጣ ሀይል ደግሞ ሀሳቦችን ዲሞክራሲያዊ በሆነ አካሄድ ወደ ጋራ ስምምነት ያመጣቸዋል:: ከመኢአድ መማር የሚቻለዉ ይሄን ነዉ::

በዚህ አጋጣሚ እግዚአብሄር በሰጠን ጥቂት የጽሁፍ ጸጋ ሀሳባችንን የምናካፍል ሁሉ በኢትዮጵያ ያለዉ የፖለቲካ ባህላዊ እሴት ያብብ ዘንድ እያንዳንዱ ወገን ወደ ዲሞክራሲ ከፍታ ይራመድ ዘንድ የምንጽፈዉ ጽሁፍ : የምንሰነዝረዉ ሀሳብ ዋጋ ያገኝ ዘንድ ለሚመለከተዉ ሁሉ እናሳስባን:: ሆኖም ማንንም አንማጸንም::

Image

-በሰሞኑ የሰራዊቱ ግምገማ የወያኔው መከላከያ ሰራዊቱ እንደ ደርግ ሰራዊት ሊበተን ይችላል ተባለ::
-በአዲስ አበባ የለውጥ ሃይሎች በመተባበር የሕዝባዊ እንቢተኝነት ጥሪዎችን ለማድረግ ዝግጅት ላይ ናቸው::
-በአስመራ አርብ ቀን ሰው አልባ ተቃውሞ ከቤት ባለመውጣት ሓርነት አርቢ የተሰኘ ንቅናቄ ተጀምሯል::
Minilik Salsawi

ላለፉት 23 አመታት በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ሕዝቦች ላይ ከፍተኛ የቀውስ ማእበል ያስከተሉት ሕዝቦቻቸን ለስደት እና ለእስር እንዲሁም ለሞት የዳረጉት የገደሉት የሻእቢያ እና ወያኔ መንግስታት እስከዛሬ ድረስ ተደጋግፈው እዚህ የደረሱ ቢሆንም ከአሁን በኋላ ያላቸው ሃይል እየተሟጠጠ ህዝባዊ እምቢተኝነት እና አመጽ እየተፈጠረባቸው በውስጣቸውም እየተቦጠቦጡ በመፍረክረክ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል::

የሻእቢያ እና ወያኔ ባለስልጣናት በመጭው ጊዜ ማድረግ የሚገባቸውን ጉዳይ እየተገናኙ እንደሚወያዩ እና በመደጋገፍ ቀሪውን ጊዜያት በስልጣን ለመቀጠል የሚያደርጉት ሙከራ የለውጥ ሃይሎች ህዝቡን በማስተማር እያከሸፉባቸው መሆኑ ተሰምቷል::በዚህም መሰረት በአስመራ ሐርነተ አርቢ ወይንም የአርብ ነጻነት የተባለ የለውጥ ንቅናቄ የተጀመረ ሲሆን ከኤርትራውያን ዲያስፖራዎች ጋር በተቀናጀ መልኩ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ንቅናቄው ትልቅ ዉጤት አምጥቶ በአስመራ ከተማ ኢሳያስን የሚቃወም ወረቀት በብዛት ሲበተን የደህንነት አባላትና ፖሊሶችም ወረቀቶችን ሳይሰበስቡ ጥሪው ሕዝቡ ዘንድ እንዲደርስ መተባበራቸው ታውቋል። እንዲሁም በአዲስ አበባ የሚገኙ ዋና ዋና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ትንንሽ ፓርቲዎችን በትብብር በማቀፍ እንዲሁም በተናጠል በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የሃገሪቱ ከተሞች ታላላቅ ሰልፎችን እና ተቃውሞዎችን በማድረግ ህዝባዊ እምቢተኝነት እንዲፈጠር ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን የኢትዮጵያውያን የዲያስፖራ የለውጥ ግብረሃይልም ከባዱን ሚና በመጫወት ትግሉ እንዲፋፋም አስታውጾ እያበረከተ ነው::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ይህን ሰሞን በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ እየተደረገ ባለ ግምገማ ላይ የመከላከያ ሰራዊቱ የአሸባሪ ሃይሎችን መቆጣጠር ካልቻለ እጣው እንደ ደርግ ሰራዊት መበተን ነው ሲሉ የግምገማው መሪዎች መናገራቸው ታውቋል:: በምድር ጦር መምሪያ ስር ባሉ የሰራዊት ክፍሎች በተደረገ ግምገማ በሁሉም አደራሾች ይህ አይነት የመበታተን አደጋ እንዳለ በይፋ ተገልጿል::የአሸባሪ ሃይሎች የተባሉት በሃገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የዲያስፖራ ጽንፈኞች እንደሆኑ የተገለጸ ሲሆን የዲያስፖራ ጽንፈኞች በሃገር ቤት የሚገኙሃይሎችን በመርዳት አመጽ ሊቀሰቅሱ ሕገመንግስቱን ሊያፈርሱ ምናምን የሚል ዛቻ እና ሃይል የተቀላቀለበት መመሪያ ሲሰጥ የነበረ ሲሆን ከፍተኛ የጦር መኮንኖች የብሄራቸው ስም እየተጠራ እና እየተለየ ሲተቹ እና ሲገመገሙ እንደነበር ታውቋል::

Image
Eritrean refugees in North Ethiopia

በአውሮፓና በአሜሪካ፣ በአፍሪካና መካከለኛው ምሥራቅ፣ በሩቅ ምስራቅና በአውስትራልያ ሳይቀር እያደር
ኤርትራና ስደት ተወራራሽ ቃላት (synonymous) እየሆኑ መጥተዋል። እገሌ/ እገሊት እኮ ኤርትራዊ
ነው/ነች ሲባል ስደተኛ ነው/ነች እንዴ? – ብሎ መጠየቅ የተለመደ አነጋገር ሆኗል። እዚህ አገር ስደተኞች
በዝተዋል ሲባል ሱማሌና ኤርትራውያን በዝተዋል የሚል – ድምዳሜ ላይ ይደረሳል። ኢትዮጵያውኖችም
በዝተዋል ሊባል ትንሽ ቀርቷል።
በቅርብ ዘመናት የነበሩት የኢትዮጵያ ነገስታት ከአውሮጵውያኖች ዘመናዊ መሳርያና ጥቅማጥቅሞችን
ይፈልጉ ነበርና ከባህረ ነጋሹ መሬት (ቦገስ፣ሠሃጢን) ቆንጠር እያደረጉ ለባእዳኑ ኃይላት እንደ መወዳጃነት
ይሰጡ ነበር። የስዊዝ ቦይ ሲከፈት ታድያ የቀይ ባህር ቀጠናነቱ እየጎላ በመሄዱ የአውሮጳ ቅኝ ገዝዎችን
ቀልብ እየሳበ መጣ። በመሆኑም እንግሊዝ ግብጽን – ነጭ አባይን ራሷ መቆጣጠር ፈልጋ ለጥቁር አባይ
ቃፊር በመፈለጓ ይህንኑ ኃላፊነት ኢጣልያ ላይ ወረወረች። ኢጣልያ ይህንኑ ተልዕኮ ተግባራዊ ለማድረግ
ስትቅበዘበዝ የአድዋው ጦርነት ተከስቶ የውርደት ሸማ ተከናነበች። ይሁንና ግን በወቅቱ በነበረው
አስቸጋሪ ነባራዊ ሁኔታ ኢጣልያ ከመረብ ወድያ ያለውን የኢትዮጵያ መሬት በቁጥጥሯ ሥር አደረገች።
በመሆኑም ባህረ ነጋሽን – ኤርትራ የሚል መጠርያ ሰጥተዋት ከእናት ሀገርዋ ነጠሏት።
ኤርትራውያን ከስድሣ ዓመታት በላይ በእጣልያ አገዛዝ በነበሩበት ወቅት የኢጣልያን ስልጣኔ እጅግ
ቀስመዋል። በእጃቸው ከመብላት ይልቅ ሹካና ማንኪያን መጠቀምን ለምደዋል። የቤት ቁሳቁሶችን
አጠቃቀምና በንጽህና አያያዝን ያውቁበታል። አለባበሳቸው ይማርካል። አነጋገራቸውና ዘበናይነታቸው ደስ
ያሰኛል። ጓደኝነታቸው በወረት አይደለም፣ በችግርም ይሁን በደስታ ጊዜ ከወደዱት አይለዩም።
ኤርትራውያን በክልልላቸው ጉዳይ ላይ ድብቅ ቢሆኑም እንኳን በተለያዩ ቁምነገሮች ላይ ለወዳጆቻቸው
ግልጽ ናቸው። ብዙውን ጊዜ ከሸጋዋ ኤርትራዊ ቆንጆ ጋር የተፈጸመ ትዳር እንደ አበባ የፈካ ነው።
ከትዳር አክባሪዋ ኤርትራዊ ጋር የሚመሰረት ጋብቻ ጽናትን ይወልዳል።
ኤርትራውያን ወንድምና እህቶቻችን “ኤርትራን” እንደማትታየዋ “ሠማያዊዋ ሀገራቸው” ሲያመልኳት
ሌሎቹን የአለም አሕጉራት ደግሞ እንደ “ምድራዊ ሀገራቸው” ይቆጥራሉ። ብዙዎች ኤርትራን በሩቅ ሆነው
እንደ መካና መዲና ያከብሯታል፣ ይጨፍሩላታል፣ የጀግኖች ሀገር እያሉ ያወድሷታል እንጂ ጎጇቸውን
ከእሷ ዘንድ መቀለሱን አይመርጡም። በእድሚአቸው የገፉት እንኳን ሳይቀሩ ሀገራቸውን ትተው በውጭ
ሀገር መኖር አይከብዳቸውም። መሰደዱ አላንገሸገሻቸውም። ይህን አስመልክቶ አቶ መለስ
“ኤርትራውያን እግር እንጂ ሀገር የላቸው” – አሉ እየተባለ ይቀለዳል።
ኤርትራውያን አስመራን ንጹሂቷ ትንሿ ሮማ ይሏታል። ሥዕሏ እንደ መላዓከ ሚካኤል ሥዕል ከቢታቸው
ግድግዳ ተለጥፋለች። ነግደው ያተረፉባትን – ተምረው የከበሩባትን አዲስ አበባ ግን ቆሻሻ ይበዛባታል ሲሉ
ያንቋሽሿታል። አፋቤትን፣ ምጽዋን፣ ከረንን፣ ደቀመሀሪን ያንቆላጵሷቸዋል – ረብጣ ነዋይ የዛቁባቸውን
ድሬዳዋን፣ ናዝሬትን፣ አዋሳንና ጅማን አያስታውሷቸውም።
የኤርትራና ስደት መወደጃጀት እክልላቸው መኖር ካለመፈለግ ምክንያት የመነጨ ይመስላል። ስደት
ይቀናቸዋል – ያሳምራቸዋልም። ስለ መሪያቸው አቶ ኢሳይያስ አንዳች ክፉ ነገር ለመናገር የማይፈልጉት
እነዚሁ ኤርትራውያን ይልቁንም በሳቸው ፈላጭ ቆራጭ ባላባታዊ አገዛዝ ምክንያት የመሰደዱ በር ዳግም
ክፍት ስለሆነላቸው በውስጣቸው ያከብሯቸዋል። አቶ ኢሳያስም ቢሆን በበረኸኝነት እልሃቸው ፈረንጆቹን
መናቃቸውና ፊት መንሳታቸው በሌላ በኩል ለኤርትራውያኑ የምዕራቡ ሀገር የመግቢያ ቪዛ መገኛ ስልት
ሆነ።
የኤርትራ የነጻነት ትግል – “ሕዝቡን ነጻ የማውጣት ትግል” – ወይንስ – “መሬቱን ነጻ አውጥቶ ለአቶ
ኢሳይያስ መሸለም”? – የሚለው ጥያቄ አዲስ የማህበራዊ ሳይንስ ንድፈ ሃሳብን ፈንጥቋል። ብዙ ሰዎች
ምትክ የሌላት ሕይወታቸውን ሰውተውላቸው፣ በመድፍና በታንክ እየተታኮሱላቸው የትልቅ ጋሻ መሬት
ብቸኛ ባለቤት እንዲሆኑ በማድረግ – ባለርስቱ ፕሬሲደንት ኢሳያስ በጣት ከሚቆጠሩት የዓለም ሰዎች
አንዱ ናቸው። ግናስ ሕዝቡ አካባቢውን እንደ ኒውክለር ራድየሽን ብክለት እየፈራ የሚፈረጥጠው ለምን
ይሆን? ይህም ጥያቄ አዲስ የማህበራዊ ሳይንስ ምርምርን መፈንጠቁ አልቀረም።
በቅርቡ ሃያ አንድ ዓመት የነጻነታቸውን በዓል ያከበሩት ኤርትራውያን ታሪክ በቅጡ የመዘገበው የግማሽ
ምዕት ዓመት የጦርነትና የስደት ታሪክ አላቸው። ከሃያ አንድ ዓመት በፊት የተጎናጸፉት ነጻነት በየሀገሩ
በስደት የወጡትን ዜጎች ሊመልስ አልቻለም። ይህ ከናቅፋ የተተኮሰው የፋኖ መራዒው የነጻነት ጥይት –
“የመንፈሱን ነጻነት” – ማምጣት አልቻለም። ይልቁንም ከነጻነቱ ማግስት ጀምሮ የሚሰደደውን ሕዝብ
ብዛት ባለፈው ሰላሳ ዓመት ከተሰደደው በመብለጥ ኤርትራውያን ከሶማሌያ ቀጥሎ ምዕራቡን ዓለም
ኢትዮጵያን ጨምሮ እንዲያጨናንቁ አድርጓል። ከባለእርስቱ አቶ ኢሳይያስ ጋር የውስኪ ብርጭቆ
የሚያነሱት የግል አውሮፕላን ነጂዎቻቸው ሳይቀሩ በቅርቡ አውሮፕላኑን ሰርቀው ወደ ሳውዲ
መኮብላላቸው ራሱ አቶ ኢሳይያስ ወዳጅ አልባ መሆናቸውን ያስመሰክራል።
ኤርትራውያኖችን የስደቱ ሰለባ ያደረገው የብሔር ብሔረሰቦችን ጥያቄ አስመልክቶ ንድፈሀሳባዊ ግንዛቤን
ለማግኘት የማርክስንና ኤንግልስን ሥራዎች በጥሞናና ስነምግባራዊ በሆነ መንገድ መረዳትን ይጠይቃል።
በተጨማሪም የራሽያ የጥቅምቱ አብዮት ክስተትንና ተያይዞ የመጣውን የብሔር ጥያቄ ጽንሶችን በጽሞና
መመርመርም ከውዥንብር ያድናል። በእርግጥ የብሔር ብሔረሰብ ጥያቄ አቀንቃኞች ማርክስና ኤንግልስክ
ብቻ ሳይሆኑ ቦልሸቪኮች፣ ሮዛ ሉክሰምበርግና ካርል ካውትስኪም ተጠቃሾች ናቸው።
ማርክስ እ/ኤ/አ በ 1848 ዓ/ም ወደ ተሻለ ማህበራዊ ብልጽግና ደረጃ የሚያሸጋግሩት የምርት ኃይሎች
እድገት (productive forces) ወሳኝ እንደሆኑ አትቶ ይኸው ሂደት በተለያዩ የብሔር ጥያቄዎች ላይ
እንኳን ቢሆን ተጽዕኖ እንደሚያሳርፍ ገልጿል። በመሆኑም በሰራተኛው መደብ (working class) ትግል
ውስጥ የብሔር ጥያቄ የሞተ ነው ሲል ማርክስ ጨምሮ አብራርቷል። የሰራተኛው ትግል መደቦችንና
(classes) ብሔሮችን (nationalities) ስለሚያጠፋ የብሔሮች ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ ቦታ
አያገኝም ብሎ ነበር። የማርክስ ዋነኛ መፈክር የዓለም ሠራተኞች ሁሉ ተባበሩ ነበር። (workers of all
countries unite)
ማርክስና ኤንግልስክ ከ እ/ኤ/አ 1850 በፊት ስለ ብሔር ጥያቄ በቂ ንድፈሃሳቦችን ያልቀረጹ ቢሆንም ቅሉ
እ/ኤ/አ – በ 1863 በተከሰተው የፖላንድ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ብሔራዊ ጥያቄ ላይ
አስተሳሰባቸውን በመለወጥ አየርላንድ ከእንግሊዝ ተገንጥላ ራሷን ማስተዳደር ትችላለች የሚል ጠበቅ
ያላለ፣ ብዥታዊ መደምደምያ ላይ ሊደርሱ ቻሉ። ሌኒንም በተመሳሳይ በሠራተኛው መደብ ልዕልና ላይ
በማተኮር የአርመንያኑ ሶሻል ደሞክራሲ የመገንጠልን ጥያቄ በሠራተኛው መደብ ነጻ መውጣት ይፈታል
ቢልም ቅሉ ሀሳቡን በመለወጥ የተጨቆነ ብሒረ እስከ መገንጠል ሊያደርስ የሚችል መብት አለው ሲል
ድንብርብር ያለ ጽሁፍ ሞነጫጭሯል። በሌላ በኩል ደግሞ ስታሊን – ሌኒንን መሠረት በማድረግ አንድ
ሕዝብ ተመሳሳይ ቋንቋ ከተናገር፣ ባንድ አካባቢ ሳይነጣጠሉ የሚኖሩ ከሆኑ፣ አካባቢአቸው ድንበር
ሊበጅለት የሚችል ከሆነ፣ ሕዝቡ በቂ የምጣኔ ኃብት ክምችት ካለው፣ ተመሳሳይ ስነልቦናዊ አመለካከት
እንዲሁም ተመሳሳይ ባህላዊ ትስስር ካለው ብሔር ሊባል የሚያስችለውን መስፈርት ስለሚያሟላ
የመገንጠል ጥያቄ ሊያቀርብ ይችላል የሚል መደምደምያ ሰጠ። ሆኖም ግን ስታሊን ከነዚህ ስድስቱ
መስፈሮቶች አንድ እንኳን ለተጓደለ ብሔር ስለማይባል መገንጠል እንደማይቻል አስጠንቅቋል።
ይህ ከላይ የተመለከትነው የፈረንጆቹ አኳኋን፣ ፖለቲካ፣ ፍልስፍና፣ ርዕዮተ ዓለም፣ ብዥታ፣ አመለካከትና
ነባራዊ ሁኔታን ያላገናዘበ ትምህርት ወደ ኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ውስጥ ዘልቆ በመግባት –
“የብሔረሰቦች ስታሊናዊ ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል” – በሚል አጉል ሀሳብ ተቀሽሮ ቀረበ።
ሻዕቢያ ከዚህ ንድፈሃሳብ በመነሳት – “አረብ ነኝ” – የሚለውን ጀብሃ ካስወገደ በኋዋላ በመገንጠሉ ጥያቄ
ጸንቶ ሲያበቃ ኦነግን በራሱ አምሳያ በመፍጠር መከረኛይቱን ኢትዮጵያ በእርስ በእርስ ጦርነት አናውጦ
ሲያበቃ ተገነጠለ።
ሻዕቢያ አስቀድሞም ቢሆን ኤርትራን ለመገንጠል ያመቸው ዘንድ በንጉሡ ዘመን የተሰነዘሩትን
የኢትዮጵያን ጭቁን ሕዝብ ጥያቄዎች በራሳቸው ስውር ዓላማ ሥር ሸሽገው ላይ ላዩን ኢትዮጵያዊ
ተቆርቋሪዎች መስለው በደጋፊዎቻቸው በመታገዝ በጥንቃቄ ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል። ከቀዝቃዛው ጦርነት
ማክተም በኋላ የማርክሲዝም ሌኒኒዝም ሃሳቦች በሚካኤል ጎርባቾቭ ፔሪስትሮይካና ግላስኖስት ተሀድሶ
አዲስ መልክ ቢይዝም ቅሉ ሻዕቢያ፣ ሕወሀትና ኦነግ በመገንጠሉ ርዕዮት ላይ ጽናታቸውን አሳዩ።
ሻዕቢያ በገሀድ፣ ሕወሀት በዘዴ ኦነግ በተቀጽላነት። እንዴት?
የኃይለሥላሴ ንጉሳዊ መንግስት በድንገት መገርሰሱ “ለማርኪሲዝም ሌኒኒዝም” ርዕዮተ ዓለም መስፋፋት
ጥርጊያ መንገድ እንዳዘጋጀ ሁሉ፣ የደርግ በራሱ የውስጡ ቅራኔ ምክንያት መፈረካከሱ ደግሞ
ለብሔረሰቦቹ “የራስን በራስ መወሰን እስከመገንጠል” ዓላማ ተግባራዊነት እጅግ ምቹ ሆነ። ድንገት
ሳይታሰብ የሚኒልክ ቤተ መንግስቱን የተቆጣጠሩት በሕወሀቱ ውስጥ የነበሩት ታጋዮች – “የታላቋ ትግራይ”
– ምስረታን መርሀ ግብር ለጊዜው ወደ ጎን ቢተዉም ቅሉ በወቅቱ ለተከሰተው ድንገተኛና አስቸጋሪ ነባራዊ
ሁኔታ ተጋለጡ። ኢሕአዲጎቹ አባቱ ሻዕቢያን ተከትሎ ኦሮምያን ለማስገንጠል ያሰፈሰፈውን ኦነግ
ለማዘናጋት እንዲሁም አዲስ አበባ ድረስ አብሯቸው የመጣውን የጦር አጋራቸውን ሻዕቢያ ላለማስቀየም
መላ በመዘየድ የብሔረሰቦች ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል የሚለውን የማርክሲዝም ሌኒኒዝም
ጽንሰሃሳብ አንቀጽ 39 በህገመንግስቱ ውስጥ ለማካተት ተገደዱ። ቀስ በቀስ ግን ኢሕአዲግ የኦነግን
ሠራዊት ከቦ ከማረከና መሪዎቹን ከምክር ቤቱ ሲያስወግድ ” አንቀጽ 39″ ለይስሙላ የተቀመጠች አንቀጽ
መሆኗ ገሀድ ወጣ። የሕወሃቶቹ ትግራይዋዎቹ፣ ከተወሰኑ ዓመታት ቆይታ በኋላ፣ ኤርትራውያን ቀድሞ
ያካበቱት ሃብት ንብረታቸው ተቀምቶ ባዷቸውን እንዲባረሩ ሲያደርጉ መገንጠል ፋይዳ ቢስ የእልኸኞች
ፖለቲካ መሆኑን በማሳየት ከመቶ ሃምሳ ዓመት በፊት ማርክስና ኤንግልስን ውዥንብር ውስጥ ከቶ
የነበረውን የብሄረሰቦች እስከመገንጠል ጥያቄን ውጤት አልባነትን በተግባር በማሳየት ለሲሪላንካ ታሚል
ተገንጣዮች አዲስ ትምሕርት አስገኙ። ኢሕአዲግ በሌላ በኩል ደግሞ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጭ
ግንባርን (ኦብነግ) በመፋለም ላይ ሲገኝ የመገንጠሉ ጥያቄ ከስታሊን ጋር አብሮ ለመቀበሩ ገለጻ ለማድረግ
ናይሮቢ ውስጥ ስብሰባ ጠርተዋቸዋል።
በመሆኑም ከስታሊናዊው – “የብሔር ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመንገንጠል” – ጽንስ የተወለደችዋ
ኤርትራ ውርዴ ስትሆን አንቀጽ 39 የእንግዴው ልጅ ነው። በዚህም በዚያም ሰበብ ግን ገናናዋና ጥንታዊዋ
ኢትዮጵያ ወደብ አልባ ሀገር እንድትሆን ክፉ ደባ ተሸረበባት።
የመገንጠሉ ሰለባ የሆነው የኤርትራ ሀገር ሕዝብ እንደ ግለሰብ እጅግ መልካሞች ናቸው። ከሚወዷት
እናት ሀገራቸው የነጠላቸው ዘመናዊው የፈረንጆቹ ፖለቲካ ነው። ይኸው የትዕቢትና የማናህሎኝነት
ማኦኢስት ፖለቲካዊ አስተሳሰብ በተማሪዎች ንቅናቄ ዘመን ከነበሩት ተማሪዎችና የዛሬው መሪዎች
አዕምሮ ውስጥ ፈጽሞ እስካልተነቀለ ድረስ ሕዝቡ በራሱ ፈቃድ መኖር አይችልም። ፖለቲካ በማስተዋል
ካልታገዘ መከራን ይወልዳል። ፖለቲካ በጥበብ፣ በትዕግስት፣ በሥነምግባርና በጨዋነት ካልተመራ ሕዝብን
ያሸብራል። ከንቱ እልህና ጀብደኝነት ደሀውን ያሰቃያል። በምስኪኑ ሕዝብ ስቃይ የሚደሰቱ ደግሞ የኋላ
ኋላ የመከራውን ጽዋ ይጨልጡታል። የእቴጌ ጣይቱ ፍርሀት እውን ሆኖ ኢትዮጵያ ራሷ ዘመናዊ
ትምህርት ያስጨበጠቻቸው ልጆችዋ ተረከዛቸውን አነሱባት። በእርግጥ እግዚአብሔር ታሪክ ሠሪ ነው።
ኢትዮጵያን እየጠበቀ ዘመን ከዘመን አሻግሯታል። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ፈጽሞ አይተዋትም።
የሻዕቢያው ባለሥልጣናትና በርከት ያሉ ኤርትራውያን ደጋፊዎቻቸው ኤርትራ ከእናት ሀገርዋ ኢትዮጵያ
መሬት ጋር ዳግም እንድትዋሀድ አይፈልጉም። ኤርትራን የጀግንነት ምሳሌአቸው፣ የስልጣኔ ምንጫቸውና
የቀይ ባህር በራቸው አድርገው ይቆጥሯታል። ማንም እንዲነካባቸው አይፈልጉም። የሕወሀቶቹ
ኤርትራውያኖቹም ቢሆን ባለርስቱ ፕሬዚደንት ኢሳይያስን ማስቀየም አይፈልጉም። ከዚህ ቀደም ሥልጣን
ላይ በነበሩት የሕወሀቱ ትግራዋዮች የተፈጸመውን ኤርትራን የኢትዮጵያ ኤኮኖምያዊ ድጋፍ ያሳጣውን
ርምጃ ለመካስ በሚቻለው ይሞክራሉ። ላንዳንዶቹ ንግዳቸውንና ቤታቸውን እየመለሱላቸው ነው።
አንዳንዶቹም የተጀጋጀውን ቅጽ እየሞሉ ኢትዮጵያው ውስጥ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ፈቅደውላቸዋል።
“ጠርጥር ከገንፎም አይጠፋ ስንጥር” – ያሉ ደግሞ ነገ ምን እንደሚፈጠር ስለማይታወቅ መጠንቀቁ
ይበጃል በሚል አርፈው እተሰደዱበት ሀገር ሆነው አድፍጠዋል።
የሻዕቢያውም ሆነ የሕወሀቱ ቀን የሰጣቸው ኤርትራውያኖች በክፉም በደጉም ጊዜ አብረውት የኖሩትን
የየዋሁን ኢትዮጵያ ሕዝብ ስነልቦናዊ አመለካከት ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ማናከሱን፣ ማከፋፈሉንና
ማጠላለፉን እንደ በቀል ዱላ ይጠቀሙበታል። የግፍ ሥራዎችንም የሥልጣን ዘመናቸው ማራዘምያ
ምትሀት አድርገው ሊጠቀሙበት ይሞክራሉ። “የቤት ሥራ” – የሚሏቸውን እነዚህኑ የርኩስ መንፈስ
ሕዋሳት በየፖለቲካ ማህበሮች፣ ትምህርት ቤቶች፤ ሕዝባዊ ስብስቦችና በየመዝናኛ ቦታዎቹ ሳይቀር እንደ
አንደ አንደ መተት እያሰሩ የዋሁን ኢትዮጵያዊ ያደነዝዛሉ። ታድያ ይህን እያወቁ አንዳንድ ተቃዋሚዎች
ከሻዕቢያ ጋር የመሞዳሞዳቸው ጥፋት – “የፖለቲካ ቂልነት” ወይም “የፖለቲካ ንዝህላልነት” – ተብሎ ብቻ
ሊታለፍ የሚችል አይደለም። ማን ይሙት ማን ሻዕቢያ የወያኔን መውደቅ ይሻል? ወያኔም ቢሆን ልብን
በፕሮፖጋንዳ እያደረቀ እግዚአብሄር በቃ እስከሚለው ቀን ድረስ ያሾፋል እንጂ ከኤርትራ ጫፍ እንኳንስ
ጦር ሣር እንደማይመዘዝ ያውቃል።
እግዚአብሄር በቃ ሲል ኤርትራውያን ወንድምና እህቶቻችን በበጎና በንጹህ ፍላጎት ወደ እናት ሀገራቸው
ጉያ ይመጣሉ። ተንኮል – ተንኮልን መውለዱን ያቆማል። መሠሪነት፣ ሸርና ደባ ወደ ጥልቁ ይወረወራሉ።
ጊዜው ይቅረብም ይራቅም እግዚአብሔር ይህንንም መስራት አይሳነውም።
ኢትዮጵያ ስትበደል እግዚአብሔር ዝም አይልም። ሰላምና ብልጽግና – ፍቅርና አንድነት ለመላው ሕዝብ
ይሁን።
ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሄር ትዘረጋለች። አሜን
ከሀበሻ አበበ (ኖርዌ)

Image

-በውሳኔው የማይስማማ ከሆነ በሱና በቤተሰቡ በወዳጆቹ ስም የተመዘገበው ሃብት እንዲጣራ ተብሏል::
-ሳያገግሙ ስብሰባ እንዲመራ እና ሚዲያ ላይ እንዲቀርብ ታዟል::
Minilik Salsawi

የብአዲን/ኢሕአዲግ ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት አቶ በረከት ስምኦን ያቀረቡት የስልጣን መልቀቂያ ለጊዜው በሚል ውድቅ መደረጉን ሆኖም በቅርቡ መልስ ይሰጥበታል ሲሉ የሕወሓት ባለስልጣናት መመለሳቸውን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል::

አብዛኛውን ጊዜ ራሳቸውን ከቤት በማስቀመጥ እና በማዝናናት ያሳልፋሉ የተባሉት አቶ በረከት ስምኦን በልባቸው ላይ በተገጠመላቸው አርቴፊሻል መሳሪያ በጤንነታቸው ላይ ከባድ እክል እንደፈጠረባቸው እና ከወራት በፊት ሳኡድ አረቢያ ታክመው ቢመጡም ሊሻላቸው እንዳልቻለ እንዲሁም ባለፈው ሳምንት በድጋሚ ቢሄዱም ሆስፒታሉ ተስፋ እንዳስቆረጣቸው ሲታወቅ ከሕክምና መልስ ወደ ቢሯቸው የገቡት በጣት የሚቆጠር ቀናት እንደሆነ ታውቋል::

ይህን ሰሞን ስብሰባ መምራት አለብህ በሚዲያ መታየት አለብህ የሚል ግዳጅ ከሕወሓት ባለስልጣናት ወርዶላቸው የተደናበሩት አቶ በረከት ማገገም እንኳን ሳይችሉ በስራ መደራረብ እንዲሞቱ እየተደረገ ነው ሲሉ ከቤተሰባቸው አንዱ የሆኑት ሲናገሩ ተሰምቷል::አቶ በረከት በከፍተኛ ህመም ውስጥ እንዳሉ ሲታወቅ የሕወሓት ባለስልጣኖች የአዜብን ቡድን እንደመቱት ወዲያው በረከትንም ከጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ አሽቀንጥረው ካሳንቺስ አዲስ ቢሮ እንደሰጡት ሲታወቅ መገፋቱ እያንገበገበው በሽታውን እንዳባባሰበት ታውቋል::

የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች የአሁኑ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ሰመጉ ባወጣው 132ኛ ልዩ መግለጫ በክልሉ በመንገሽና ጎደሬ ወረዳዎች ተፈጥሮ በነበረው ግጭት የተገደሉ የ60 ሰዎች ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
በሪፖርቱ እንደቀረበው 27 የአማራ፣ 27 የመዠንገር፣ 2 የከፋና 4 የኦሮሞ ተወላጆች ተገድለዋል። እንዲሁም 16 የአማራና 6 የመዠንገር ተወላጆች የአካል ጉዳት ሲደርስባቸው፣ 36 የአማራ ተወላጆች ተፈናቅለዋል። 4 የአማራ ተወላጆችም የደረሱበት አለመታወቁ በሪፖርቱ ተጠቅሷል።
ከተገደሉት ሰዎች መካከል የዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ የመዠንገር ተወላጅ የሆኑት ዳኛ ፀጋዬ ጌታሁን ሲገኙበት፣ መካሻ መንግስቱ የተባሉ ሰው ደግሞ እስከነባለቤታቸው ተገድለዋል።
ሰመጉ በግጭቱ መነሻ ዙሪያ የተናገረው ነገር ባይኖርም፣ በተለያዩ አካባቢዎች የብሄረሰቦች ግችት እየተስፋፋ ቢመጣም መንግስት ይህን አሳሳቢ ጉዳይ በዘላቂነት ለመፍታት እያደረገ ያለው ጥረት ከችግሩ ክብደትና እየደረሰ ካለው ጉዳት አንጻር ሲታይ ጨርሶ የሚመጣጠን አይደለም ብሎአል። መንግስት ተመሳሳይ ግጭቶች እንዳይፈጠሩ ዘላቂ መፍትሄ ማበጀት ለነገ የማይባል አንገብጋቢ ጉዳይ ነው የሚለው ሰመጉ፣ በመዠንገር ዞን ለተፈጠረው ሰብአዊ እልቂትና መንስኤ የሆኑ ምክንያቶችንና ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ግልሰቦችንና ቡድኖችን አጣርቶ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል።
ሰመጉ ባወጣው መግለጫ ላይ መንግስት የሰጠው አስተያየት የለም። መኢአድ የተገደሉ ዜጎችን ቁጥር ከ540 በላይ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል።

Image

Image

Image

Image

በኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ ታሪክ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት በህገ መንግስት እውቅና ያገኘውና በይፋ ፓርቲ መመስረት የተቻለው በኢህአዴግ ዘመን ነው፡፡ ይህ መቸም እንደ ጅምር ሊያስመሰግን የሚገባ ተግባር ነው፡፡ ምንም እንኳ ኢህአዲግ ለነፍሱ ብሎ ባያደርገውም፡፡ ሁኔታዎች አስገድደውት ያደረገው እንደሆነ ቢታወቅም በይፋ መደራጀት መቻልን እንደ ትልቅ ለውጥ ነው የምወስደው፡፡
ቁም ነገሩ ግን ኢህአዲግ የፈቀደልንን ህገ መንግስታዊ (ከጫካ ስለሆነ የመጣው ያለመፍቀድ እድልም ነበረው) የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ተጠቅመን ለውጥ ለማምጣት ተንቀሳቅሰናል ወይ? የሚለው ነው፡፡ ለእኔ መልሱ አይደለም የሚል ይሆናል፡፡ ከአዛውንቱ ዶክተር አስራት ወልደዬስ በቀር አንድም እንኳ ህዝብ አስተባብሮ መሬት ያረፈ ትግል ያደረገ እና ኢህአዲግን የተገዳደረ ፓርቲ ፈጽሞ የለም፡፡ ከጠብ-መንጃ ጋር ፊት ለፊት በባዶ እጅ የተጋፈጡት ቆፍጣናው ምሁር አስራት ውልደዬስ እድሜያቸውና ክብራቸውን በማይመጥን ሁኔታ ለእስር ተዳርገው ለሞት ቢበቁም ከእርሳቸው በኋላ ለምልክት እንኳ የተንቀሳቀሰ የፓርቲ መሪም ሆነ ፓርቲ አላየሁም፡፡
ለዚህም እንደ ማሳያ የሚሆነው አንድም እንኳ የፓርቲ መሪ ለእስርም ሆነ ለሞት ሲዳረግ ታይቶ አለመታቁ ነው፡፡ በአካልም ሆነ በመንፈስ አንዳች ጉዳት ደርሶባቸው አለማወቁ ነው፡፡ በነገራችን ላይ የግድ ለምን አልታሰሩም ወይም አልሞቱም የሚል መንቻካ ሀሳብ ለማንሳት ሳይሆን ከኢህአዲግ አምባገነንነት አንጻር ምንም አይነት እርምጃ ያለመውሰዱ የመሪዎቹን ልክ ያሳያል ለማለት ነው፡፡ ሁሉንም የግፍ ገፈት የሚጨልጡት አባላትና ዜጋው ነው፡፡ ቆፍጣናዋን እንስት ብርቱካን ሚዴቅሳን ግን መርሳት ከቶ አይቻልም፡፡
በኢህአዲግ ክፍተት ወይም እንዝላልነት በአጋጣሚ የተገኘው የ1997 ዓ.ም ተሞክሮም ቢሆን በፖለቲከኞች ልፋት ያልመጣ መሆኑ ለክርክር የሚቀርብ አይደለም፡፡ የመለስ ዜናዊ ‹‹እንከን አልባ ምርጫ እንደርጋለን›› ፉከራን ተከትሎ ገርበብ ያውን በር ነጻነት የተጠማው ህዝብ በርግዶት ከመግባቱ በቀር ይህን አስተዋጽኦ አደርጌያለው የሚል ካለ ለክርክር ፈቃደኛ ነኝ፡፡
ምን ይሻል???
እስካሁን የነበረውን ‹‹የእናቴ ቀሚስ ጠለፈኝ›› ማስተባበያ ወደ ጎን ብለን ህዝቡ ድረስ በመውረድ ማደራጀት፤ የነጻነትን ጣዕም እንዲያውቅ ማንቃት፤ ዲሞክራሲን በተግባር ማለማመድ፤ ህዝቡ የሥነ ልቦና ለውጥ እንዲያመጣ ማድረግ ይኖርብናል፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለውድቀታችን ሁሉ ኢህአዲግን መክሰስ ግን እንደ ቋንጣ የደረቀና አዋጭ ቢዝነስ አይደለም፡፡ በነገራችን ላይ ለፖለቲካችን መበላሸት ኢህአዲግ ሰፊ መዳፍ የለውም የሚል የሞኝ አስተሳሰብ የለኝም፡፡ የእኔ መከራከሪያ የኢህአዲግ ባህሪ የታወቀ ስለሆነ እርሱን ወደ ጎን ትተን እና እረስተን ህዝቡ ጋር መድረስና ህዝባችን ማንቃት የሚል ነው፡፡ ምክንያቱም የነቃ ህዝብ ለጭቆና ስለማይች፡፡ በተቃራኒው ያልሰለጠነና ያልነቃ ህዝብ ‹‹ቢጭኑት አህያ ቢጋቡት ፈረስ›› ከመሆን አያልፍምና፡፡
‹‹መንግስት የቆመጠው ቆማጣ አይባልም›› ብሎ የሚተርትን ህዝብ መንግስት መቁመጥ መብቱ አለመሆኑን ማስረዳት ይኖርብናል፡፡ በተቃራኒው ህዝብ በመንግስት ላይ ያለውን የበላይነት አንጽሮ መንገርና ሀሳብ ማስታጠቅ ይጠበቃል፡፡ ነገር ግን አብዛኛዎቹ የሀገራችን ፖለቲከኞች ኢህአዲግን ከመክሰስ እና ሰሞነኛ ነገር ከማራገብ ያለፈ ስር ነቀል ለውጥ የምንፈልግ አይመስለኝም፡፡
‹‹ኢህአዲግ ገዳይ ነው፤ ኢህአዲግ ያስራል ፤ ያፈናቅላል፤ ያሰድዳል፤ የመንግስትን በጀት ለድርጅት ይጠቀማል፤ ይዋሻል…..ብላ ብላ ከሚል ማላዘን ያለፈ ተጨባጭ አማራጭ የለንም፡፡ አለን የምንለው እንኳ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ አይደለም ሀገርን ያክል ትልቅ ነገር ይቅርና መንደር ለመምራት የሚያስችል አቅም ያለው ፓርቲ ማግኘት ጨረቃ ላይ እንደመውጣት ያለ ከባድ ነው፡፡
‹‹የኢህአዲግ የትምህርት ፖሊሲ የተሳሳተ ነው›› የሚል ተቃዋሚ አማራጭ የማቅረብ ግዴታ አይኖርበትም፡፡ እውነታ ግን ባ ተቃውሞ ብቻ ነው፡፡ የእያንዳንዱን ፓርቲ ገመና ቀርባችሁ ስታዩት ከበርሜል ጩኸት አይለይም፡፡ ባዶ ‹‹የእንዲህ ሆነብን›› ጩኸት!! ታዲያ በዚህ ሁኔታ እንዴት ለውጥ ማምጣት ይቻለል?? በነገራችን ላይ ‹‹ኢዴፓ›› መስተካከል ያለበት እንዳለ ሆኖ ማንም ፓርቲ ሊስተካከለው የማይችል ዝርዝር የትንታኔ ሰነድ ባለቤት ነው፡፡
መፍትሄው
መፍትሄው እራሳቸውን በሸንበቆ አጥር ከልለው በጸጉር ስንጠቃ አባዜ የተበታተኑ ፓርቲዎችን ወደ አንድ ጎራ እንዲፈሱ በማድረግ ግዙፍ የሆነ እና አማራጮችን ማቅረብ የሚችል የተቃውሞ ጎራ መፍጠር ብቻ ነው፡፡ ደግሞም ይህን ለማድረግ የሚያግድ አንዳች እንኳ ምክንያት የለም፡፡ ምን አልባት እንደ ዘመነ መሳፍንት ሁሉ በዬ መንደሩ አለቃ ሆነው የከረሙት የፓርቲ አመራሮች ይህ እንዳይሆን አይታገሉም ማለት አይደለም፡፡
ነገር ግን ኢህአዲግን ከመታገላችን በፊት እነዚህን ‹‹የመንደር አውራዎች›› ልክ ማስገባት ለነገ የማይባል ስራ መሆን ይኖርበታል፡፡ መነጋገሪያችን መሆን ያለበትም ፍትህ የተጠማውን ህዝባችን መታደግ የሚችል ፋና ወጊ ፓርቲ እንዴት መመስረት ይቻላል የሚል መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህ ደግሞ ለዛሬ እንጅ ለነገ መባል አይገባውም፡፡

በተባበረ ክንድ ወደ ነጻነት የምንጓዝበት ቀን ሩቅ አይሆንም!!
…………….እናቸንፋለን……!!!

አቶ ሀብታሙ አያሌው ግራ እግሩ ላይ ጉዳት ስለደረሰበት ችሎቱን ተቀምጦ ለመከታተል መገደዱንም ለማወቅ ተችሏል፡፡በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ተከሳሾች ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው ::
7 ሙስሊም ወንድሞች እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም ተሳትፈዋል›› የተባሉ ተከሰዋል ::

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በሽብር የተከሰሱት አራቱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ዛሬ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት የዋስትና ጉዳያቸውን ለማየት ለህዳር 2/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ሀብታሙ አያሌው፣ የሽዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታና ዳንኤል ሺበሺን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ላይ የፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ከቀናት በፊት መመስረቱ የሚታወስ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ የዋስትና ጉዳያቸውን አይቶ ብይን ይሰጣል ቢባልም የተከሳሽ ጠበቆች አጭር የጊዜ ቀጠሮ በጠየቁት መሰረት ለህዳር 2/2007 በአምስት ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ከ1-5ኛ እና የ9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ የተከሳሾች የዋስትና ጉዳይ ከመታየቱ በፊት በተከሳሾች ላይ የቀረበው ማስረጃ የገጽ ብዛት ተጠቅሶ ለጠበቃዎቹ እንዲደርሳቸውና የአቃቢ ህጎቹ ስም እንዲጠቀስ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡
ጠበቃው የዋስትና ጉዳዩን በተመለከተ በቃል ጥያቄውን ማድረስ እንደሚችሉ ገልጸው፣ ነገር ግን ጊዜ ተሰጥቷቸው በጽሑፍ ለዳኞቹም ለአቃቤ ህጎቹም ማቅረብ እንደሚችሉ ለችሎቱ በጠየቁት መሰረት ለቀጣይ ቀጠሮ በጽሑፍ አዘጋጅተው እንዲቀርቡ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ አቃቤ ህግ በበኩሉ ያለውን የሰነድ ማስረጃ ከክሱ ጋር አያይዞ ማቅረቡን በመግለጽ የሰው ማስረጃዎችም እንዳሉት አስረድቷል፡፡
አቶ ሀብታሙ አያሌው ግራ እግሩ ላይ ጉዳት ስለደረሰበት ችሎቱን ተቀምጦ ለመከታተል መገደዱንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ አቶ ሀብታሙ አያሌው 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ሌሎች ተከሳሾች ደግሞ 1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ፣ 3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ፣ 4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ፣ 5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ፣ 6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ፣ 7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን፣ 8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ፣ 9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ፣ እና 10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ 7 ሙስሊም ወንድሞች እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም በዋና ወንጀል አድራጊነት ተሳትፈዋል በሚል አቃቤ ህግ ዛሬ ክስ እንደመሰረተባቸው ታውቋል፡፡
ተከሳሾቹም፡-
1ኛ. ተከሳሽ ጃፋር መሀመድ
2ኛ. መሀመድ ኑሩ
3ኛ. መሐመድ ሰሊም
4ኛ. ኑረዲን ጀማል
5ኛ. መሀመድ አባብያ
6ኛ. አኑዋር ጃኒ
7ኛ. ጀማል አብዱ ናቸው፡፡
= በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርት =

ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡

እንደ መግቢያ፡- በመዝገበ ቃላት አተረጓጎም መሠረት “ዲሞክራሲ ማላት በሕዝብ የተመረጠ መንግሥት ማለት ሲሆን የመጨረሻውም ሥልጣን በሕዝብ ቁጥጥር ስር ያለ፣በቀጥታ በራሳቸው ወይም እነርሱ በወከሉት ወገን ብቻ በሥራ የሚተረጐምና በነፃ ምርጫ ስርዓት የተመረኮዘ ነው” ይላል፡፡ በአብርሃም ሊንከን አባባል “ዲሞክራሲ ከሕዝብ የወጣ ፣በሕዝብ የተመረጠና ለሕዝብ የሚያገልግል መንግስት ነው፡፡”በማለት የሰጠው ትርጓሜ በአብዛኛው ተቀባይነት ያገኝ ሃሳብ ነው፡ሦስቱ መሠረታዊ የመንግስት ምሶሶዎች ተብለው የሚታወቁት ማለትም ሕግ አውጪ፣ሕግ አስፈጻሚ እና ሕግ ተርጓሚ በሁለት መንገድ ሥራቸውን ያከናውናሉ፡፡እነኚኽም አካሄዶች ቀጥተኛ እና የተወካይ ዲሞክራሲ ተብለው ተለይተው ይታወቃሉ ፡፡
ቀጥተኛ ዲሞክራሲ ዜጎች የሚመርጧቸው ምንም ዓይነት ተወካይ አይኖራቸውም፡፡ይህ ማላት ግን አስተዳዳሪ ወይም መሪ የላቸውም ማለት አይደለም፡፡በማናቸውም ጉዳዮች ውሳኔ የሚወስነው በቀጥተኛ የህዝብ ተሳትፎ ነው፡፡ለየትኛውም የህዝበ ውሳኔ ጉዳዮች ፣ዜጎች በጋራ ተሰባስበው በመመክር በአንድ ዓይነት ስምምነት፣ ውይም በድምፅ ብልጫ ውሳኔ የሚያስተላልፉበት ስርዓት ነው፡፡የዲሞክራሲ እናት በመባል የምትታውቀው አቴንስ ከ4 ሺህ እስከ 7ሺህ የሚደርሱ ሰዎች ስብሰባ በማካሄድ ነበር ቀጥተኛ የሆነ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን ተግባራዊ ታደርግ የነበረችው፡፡ይሁን እንጂ ከሕብረተሰብ ብዛት እና ከውስብስብነቱ አኳያ ለቀጥተኛ ዲሞክራሲ ተግባራዊነት የሚሰጠው ጥቅም ውስን በመሆኑ ብዙም ሳይጓዝ እንዲቀር ተደርጓል፡፡በአሁን ወቅት በዓለማችን በአብዛኛው ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የዲሞክራሲ ዓይነት የተወካዮች ዲሞክራሲ ነው፡፡እንዲህ ዓይነቱ ዲሞክራሲ ዜጎች የፖለቲካ ውሳኔዎችን የሚወስንላቸው ተወካዮቻቸውን በመምረጥ ነው፡፡ተመራጮችሁም በበኩላቸው የመረጣቸውን ሕዝብ ወክለው ውስብስብ መንግስታዊ ሥራዎችን እውቀታቸውን፣ጊዜያቸውን እና ጎልበታቸውን ሰውተው ግልጋሎት ይሰጣሉ፡፡
በአገራችን ኢትዮጵያ፡- ከቀጥተኛ ዲሞክራሲ ይልቅ የተወካዮች ዲሞክራሲ ውጤቱ አጥጋቢ ባይሆንም፣ ተግባራዊ ለማድረግ ሙከራዎች ከዚህ ቀደም ተደርጓአል፡፡በተለይ በቀዳማዊ ንጉሳችን ኃይለ ስላሴ የተወካዮች ዲሞክራሲ ወደ አገራችን በማስገባት የዲሞክራሲ በዓላችን እንዲዳብር የተደረገው ጥረት እና ውጤት በታሪክ በአውንታዊ ጎን ተፅፎ የሚኖር ነው፡፡ይሁን እንጂ የተወካዮቹ አመራረጥ እና የሥራ ሂደታቸው ሲለካ ውጤቱ ምን እንደነበር ለታሪክ አዋቂዎች ቢተዉ የተሻለ ይሆናል፡፡ከዚህ ባለፈ በደርግ የተካሄደው የብሔራዊ ሸንጎ እና የኢሕአዴግ የ4 ዙር አገር አቀፍ ምርጫ ለዜጎች ከሰጠው ፋይዳ ይልቅ የአምባገነን ሥርዓት ለማስቀጠል የሰጠው ጥቅም የበዛ ነው፡፡
ከምርጫ 1997 ዓ.ም ወዲህ፣ ገዥው መንግሰት የምርጫን መቃረብ ተከትሎ መንገዶችን ይሰራል፣ የጋራ መኖራይ ቤት ገንብቶ በዱቢ እና በረጅም ወራት ክፍያ ለተጠቃሚዎች ያስተላልፋል፣ለመንግሰት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ያደርጋል፣በአንድ ለአምስት አደረጃጀት በመጠቀም የምረጡኝ ዘመቻ ይጀምራል፣አብዮታዊ ዲሞክራሲ ስልጠናና ጥምቀትን ያካሂዳል፣ዘላቂነት የሌላቸው ጊዚያዊ የሥራ እድሎችን በመፍጠር የሥራ አጦችን ካርድ ይነጥቃል፤ይህ ሣይሆን ሲቀር ኢ-ፍህታዊ ጥቅማ-ጥቅምን በመስጠት ደጋፊን ያበዛል፡፡ በተጨማሪም መቼም የማይፈፀሙ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በየቦታው የመሠረት ድንጋይ በመጣል ዳንኪራ ያስጨፍራል፣ከዚህም በላይ የሆነበትን ደግሞ ቃል ይገባል ፡፡እነዚህና መሰል የሆኑ ሁሉ ነገሮችን ማከናወኑ ለምርጫ ካርድ እንጂ ለዘለቂታዊ ልማት አይደልም፡፡የምርጫ ወቅት ሲቃረብ መንግስት ደፋ ቀና ደፈ ቀና የሚለበት ሥራ ሁሉ ለይስሙላ እንጂ ዘለቄታዊ ጠቀሜታ እንደሌለው ላለፉት አራት ዙር በተደረጉ ምርጫዎች ለማረጋገጥ ይቻላል ፡፡ በይበልጥ ደግሞ የፊታችን ግንቦት ወር ይካሄዳል የሚባለው ምርጭ በገዥው መንግሰት ቀጥተኛ ተፅኖ ስር በወደቀው ምርጫ ቦርድ እና ፣በመንግስት በኩል መንገስት ስል ኢሕአዴግ ወይም ወያኔ ለማለት እንደተፈለገ ግንዛቤ ይወሰድልኝ፡፡ምክንያቱ ደግሞ ገዥው ፓርቲ እና መንግስት ባልተለያዩበት ሥርዓት ውስጥ በመሆናችን ነው፡፡ስለሀኖም በእነዚህ ሁለት ሃይሎች ተፎካካሪ ወይንም አማራጭ በሆኑ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ ይህ-ቀረሽ የማይባል ጫና እየደረሰባቸው ይገኛል፡፡ችግሩ ደግሞ ቀጥተኛ በሆነ መንግድ የሚፈፀም ስለመሆኑ ከዚህ በታች በመጠኑ ለማመላከት ይሞከራል፡፡
የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በፓርቲዎች፡-
በዓለም አቀፍ የተባበሩት መግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ጉባሄ ባፀደቀው መግለጫ ኢትዮጵያም በፈረመችው ስለ መሰብሰብ እና መደራጀት መብቶች በሚከተሉው መልኩ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ “ የዜጎች የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች ተግባራዊ ሂደት ገደብ በማይጣልበት ሁኔታ መከበር ሲኖርበት ነገር ግን ገደብ ቢደረግ እንኳን ገደቡ የዓለም ዓቀፍ ህግና ሰብዓዊ መብቶችን መሰረት ያደረገ እና የእነዚህን መብቶች ሁለንተናዊ ጥበቃ እዉን የሚያደርግ መሆን አለበት፡፡በተለይም ዜጎች የፖለቲካ እና የአይማኖት ለማስከበር የሚያደርጓቸው ተቃውሞዎች መደገፍ አለባቸው፡፡”የሚል ነው ፡፡
ይህ እጅግ በጣም ጠንካራ የሆነ ዜጎች በፖለቲካ የመደራጀት መብታቸውን የሚያስከበር ዓለም አቀፍ ሕግ ነው፡፡አሁን በሥራ ላይ ያለው ሕገመንገስት ይህን ህግ በመቀበል አካቶ ይገኛል፡፡እርግጥ ነው ህገመንግስቱ በራሱ ማሻሻይን የሚፈልጉ በርካታ አንቀፆች አሉት፡፡በዚህ አጋጣሚ ሰማያዊ ፓርቲ ዜጎችን በጋራ አግባብቶ በዘላቂነት ሊያገለግል የሚችል እና ለሕገመንግሰት መሠረት ወይም ምሶሶ የሚሆን “የዜጎች ቃል-ኪዳን ሰነድ ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ”የተሰኘ ሠነድ በማዘጋጀት ለህዝብ ይፋ ማድረጉ የሚታወቅ ነው፡፡ለዚህም መልካም ጅማሮ ለሰማያዊ ፓርቲ አድናቆት ሊቸረው ይገባል፡፡ወደጉዳያችን ስንመለስ በዓለም አቀፍ እዲሁም በኢትዮጵያ ሕግ የፖለቲካን ዓላማ ለማስፈፀም ሕግን መሠረት ያደረገ አደረጃጀት የተፈቀደ ነው፡፡ይሁን እንጂ ይህን መሰረት ያደረገ አደረጃጀት ኖራቸው በአገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የተቃወሚ ፓርቲዎች፤ ሰብዓዊና ዲሞክራሳዊ መብቶች ይከበሩ፣የሕግ የበላይነት ይረጋገጥ፣ህዛባዊ መንግሰት ይመስረት በማለታቸው እና ለተግባራዊነቱ በመንቀሳቀሳቸው ብቻ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ለሞት፣ለእስራት፣ለስደት እና ለእንግልት እየተዳረጉ ይገኛሉ፡፡
ይህም በመሆኑ አብዛኛው የተቃዋሚ ፓርቲ አባላቶቺ ታስረዋል፣የመንግሰት ታጣቂ ሃይሎች በግልፅ እና በስውር በፓርቲ አባላት ወከባና እንግልት እየፈፀሙ ይገኛሉ፣ጠንካራ የሚባሉ የተቃዋሚ ሃይሎች የቀን-ተቀን ሥራቸውን የሚያከናውኑበት ቢሮ መከራየት እንዳይችሉ አከራዩች በቀበሌ ካድሬዎች ማስፈራሪያ እና ዛቻ ይደርስባቸዋል፣ከብዙ ልፋት እና እንግልት በኋላ በሚያገኙት ቢሮ የፓርቲ አባላቶች ወደ ቢሮ ሲገብ እና ሲወጡ እየጠበቁ የመንግሰት ደንነቶች ወከባ ከፍ ሲልም ትንኮስ እየፈፀሙ ይገኛሉ፣ ፓርቲዎች ዋንኛ የተቋቋሙለትን ዓላማ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችላቸውን ማናቸውም እንቅስቃሴዎች ከደጋፊዎቻቸው ጋር በመሆን በነፃነት አደባባይ ወጥተው ቅስቀሳ እንዲሁም ተቃውሞ ማድረግ የሞት ሽረት ትግል ነው፡፡በተለይ ደግሞ አዲስ ተመዝጋቢ አባላት የአባልነታው የእጩ ቀናት መቁጠር ከመጀመራቸው በፊት በመንግሰት ታጣቂ እና በካድሬዎች የሚደርስባቸው ማስፈራሪያ እና ዛቻ ልጉድ ነው፡፡ከምንም በላይ ደግሞ የአባላትን ወራዊ መዋጮ እና ድጋፍ የፓርቲዎች የፋይናስ አቅም አይነተኛ መንግድ ነው፡፡ሆኖም ግን ይህ ገንዘብ በራሱ በቂ አይደለም፡፡ይህም በመሆኑ የፓርቲ አባላት ሣይሆኑ ደግፍ መስጠት ለሚፈልግ ለማንኛውም ኢትዮጵያዊ በልብ ሙሉነት ገንዘባቸውን እንዳይለግሱ ጫና ይደረግባቸዋል፡፡የጉዳዩ አሳሳቢነት ምን ያኸል እነደሆነ ለማሳያ አነድ ምሣሌ መጥቀስ ይቻልል፤አቶ የሺዋስ አሰፋ፣አቶ አብታሙ አያሌው፣አቶ ደንኤል ሽበሺ እና አቶ አብርሃ ደስታ በማእከላዊ እስር ቤት በዋንኛነት የሚደረግባቸው ምርመራ “የፓርቲያችሁ የገንዘብ ምንጭ ምንድነው ? ማነው በቋሚነት ድጋፍ የሚያደርግላችሁ ?ገንዘቡ የት ነው የሚቀመጠው” የሚሉት ዘወትር የተለያየ የምርመራ ዘዴዎች በመጠቀም የሚጠየቁት ጥያቄ ነው፡፡ነገሩን ይበልጥ አስገራሚ የሚያደርገው ከላይ የተገለፁት የፓርቲ አባለት የተያዙት “በሽብር ወንጀል በመጠርጠር ነው”በማለት ገዥው መንግስት ገልፆአል ሆኖም በምርመራ ወቅት ግን የሚጠየቁት የፓርቲ ገንዘብ ወጪና ገቢ ነው፡፡ በአጠቃላይ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል በመሆን ብቻ ነጋዴው ከንግዱ፣ተማሪው ከት/ት፣ሰራተኛው ከስራው፣ገበሬው ከእርሻው፣አርብቶ አደሩ ከከብቶችሁ እየተፈናቀለ ይገኛል፡፡
ስለዚህም ተፈካካሪን የተቃወሚ ፓርቲን በእንዲህ መልኩ እያዳከመ እና አንዳንዶችን በጭራሽ ከወደቁበት እንዳይነሱ እያደረገ ይገኛል፡፡በእንዲህ መልኩ ከሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ጋር ኢሕአዴግ ተፎካካሪ በመሆን ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው እንዴት ሊባል ይቻላል ?
የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በምርጫ ቦርድ ፡-
በየደረጃው ትክክለኛ ምርጫ እንዲካሄድ ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ይቋቋማል፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 102 ላይ ይገኛል፡፡ይሁን እንጂ የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች ሹመታቸው ከመንግስት መልካም ፍቃድ የመነጨ ሲሆን አሰራራቸውም ለገዥው መንግስ በእጅጉ በጣም ያደላ ነው፡፡ስለዚህም ምርጫ ቦርድ ህገመንግስቱን መሠረት አድርጎ ነጻ እና ገለልተኛ ነው ለማለት ከበድ ድፍረትን የሚጠይቅ ነው፡፡የስከዛሬውም የምርጫ ቦርድ የሥራ አንቅስቃሴ ለገዥው መንግስት ያለው ታማኝነት እና አገልጋይነት በድብቅ ሣይሆን በአደባባይ “እዩልኝ፣ስሙልኝ” እያለ በራሱ ላይ መስክሮ የእኛን መስክርነት ከሰጠን አመታት ተቆጠሩ፡፡ከወረዳ የምርጫ አስፈፃሚ ጀምሮ እስከላይ ያለው የምርጫ ቦርድ ሃላፊ፣ በገዥው መንግሰት ቀጥተኛ ተፅእኖ ስር መሆናቸው ግልፅ እና አሻሚ ያልሆነ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ ላይ ከዘህ በላይ ማሣያዎችን ለማመላከት መሄድ ዉሃ ቅዳ ዉሃ መልስ ይሆናል ነገሩ፡፡
በመሆኑም ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ በአገራችን የለም፡፡ ሃቁ ይህ ሆኖ ሣለ ከተፈካካሪ የተቃወሚ ፓርቲዎች ጋር ኢሕአዴግ ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው ማለት እንዴት ይቻላል ?
የገዥው መንገስት ቀጥተኛ ጫና በነፃ በጋዜጠኛ ላይ ፡-
ማንኛውም ሰው ያለማንም ጣልቃ ገብነት የአመለካከት እና ሐሳብን በነፃ የመያዝና በማንኛውም የማሰራጫ ዘዴ የመግለፅ ነፃነት አለው፡፡የሚለው በህገመንግስቱ አንቀፅ 29 ተፅፎ ይገኛል፡፡ በእርግጥ ይህ መብት ገደብ ሊጣልበት እንደሚችል በህገ መንግስቱ ላይ ተገልፆ የተቀመጠ ሲሆን ገደብ ግን መሠረታዊ የሆነውን መረጃን የመስጠት እና የማግኘት እንዲሁም አስተሳሰብ ላይ ወይም አመለካከት ላይ ውጤት እንደማይኖረው በህገመንግስቱ ተገልፆ ይገኛል፡፡
ይሁን እንጂ አሳብን በነፃ ማሰብና ማንሸራሸር በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ እጅግ አዳጋች ነው፡፡ አሳብን ለመግለፅ ይቅርና ከገዥው መንግስት ፍላጎት እና አሳብ ውጪ ማሰብ በራሱ ለእስራት እና ለእንግልት ይዳርጋል፡፡ጋዜጠኞችን በማሰቃየት፣በማሰር እና እንዲሰደዱ በማደረግ ኢትዮጵያ በዓለማችን መጥፎ ሪከረድ አስመዝግባለች፡፡በአሁን ወቅት ከ17 የማያንሱ ጋዜጠኞች በእስር ቤት እየተሰቃዩ ይገኛሉ፡፡21 የሚሆኑ ጋዜጠኖች በስደት መከራን እየተቀበሉ ነው፡፡መንግስትን ተችቶ የፃፈና ፁሁፉ የወጣበት ጋዜጣ ወይም መፅሔት ጨምሮ ሁሉም ተጠራርጎ ቃሊቲ የሚገባበት ወይም አደገኛ ዛቻና መስጠንቀቂያ የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡በውጪ አገር የሚገኙ የተለያዩ ሚዲያዎችም ቢሆኑ፣በአገር ውስጥ ተደማጭ እና ተነባቢ እንዳይሆኑ ከፍተኛ ገንዘብ በመመደብ አፈና እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡
ስለዚህም ነፃ አሳብ የሚንሸራሸርባቸው ነፃ ጋዜጦችና መፅሔቶች ምን ያህል አሉ ? በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሄደው አገራዊ ምርጫ ተፈካካሪ ፓርቲዎች የምረጡኝ ዘመቻ ቅስቀሳ የሚያደርጉት በይትኛው ነፃ ጋዜጣ እና መፅሔት ነው ? ህሊናውን እና ሙያውን ብቻ መሠረት አድርጎ የሚሰራ ጋዜጠኛ ምን ያህል አለ ? እርግጥ ይህ ፁሑፍ የቀረበበት ሚዲያ ጋዜጣ በቀጣይ የሌሎች ጋዜጣ እና ጋዜጠኞች እጣ ፈንታ እንደማይደረሰው በምንም እርግጠኛ መሆን ይቻላል፡፡በምንም!!
እናም ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ጋዜጠኛ እና የእትመት ውጤት ሣይኖር መርጫ እንዴት ይታሰባል፡፡አገራችን በጋዜጠኛ ድርቅ እንድትመታ ገዥው መንግሰት ሆነ ብሎ ያደረገው መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ይህ በሆነበት ሁኔታ ኢሕአዴግ ለመርጫ እራሱን እያዘጋጀ ነው ማለት በራስ ላይ እንደመተኮስ ይቆጠራል ፡፡

ከላይ በመጠኑ የዚህ ፁሑፍ አቅራቢ ለመዳሰስ የሞከራቸው እና ሌሎች ተመሳሳይ ምክንያቶችን ግምት ውስጥ በማስገባት፣ ኢሕአዴግ በጭራሽ እራሱን ነፃ ለሆነ የምርጫ ውድድር እያዘጋጀ አይደለም !የፖለቲካ ሊቃውንት እንደሚያስገነዝቡት እና ዓለም አቀፍ ነባሪዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ለምርጫ መሰረታዊ ከሆኑት ውስጥ ፤በእኩል ደረጃ ባይወንም እንኳን በአንፃራዊነት የተወዳዳሪ ፓርቲዎች ነፃነት እና እኩል ተሣትፎ ሊኖር ይገባል፣ፓርቲዎችን ሊያወዳደሩ የሚችል ከማንኛውም ተጽእኖ ነፃ የሆነ ምርጫ ቦርድ እና ጉዳዩን ሙያዊ ስነምግባር መሠረት በማድረግ ለህዝብ መረጃ የሚያደርስ ነፃ ሚዲያ ያስፈልጋል፡፡እነዚህ መሰል ዋንኛ መስፈርቶች ባልተሟሉበት በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ፣ በመጪው ግንቦት ወር ነፃ ምርጫ ማካሄድ የሚታሰብ አይደለም፡፡

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !

ጎንደር ፦ የህዝቦችን መብቶች የማይወክሉ የወያኔ ሰንደቅ አላማዎች ከሚውለበለቡበት ወረዱ ::
#Ethiopia #Gonder #Kimant #ESAT #MinilikSalsawi #Freedom

– በሰሜን ጎንደር ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ተዘጉ:: ESAT
– በሰሜን ጎንደር ዞን 130 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው አልተገኙም።
– በአድማው የመንግስት መስሪያ ቤቶች ይካተታሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የቅማንት ተወላጆች ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ በተጠራ የስራ ማቆም አድማ በዞኑ የሚገኙ ከ80 በላይ ትምህርት ቤቶች ካለፈው አርብ ጀምሮ የተዘጉ ሲሆን፣ መንግስት እስከ መስከረም 30 መልስ የማይሰጥ ከሆነ፣ ተቃውሞው ግብር ባለመክፈል እንደሚቀጥል አስተባባሪዎቹ ለኢሳት ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በርካታ አስተባባሪዎች ተይዘው የታሰሩ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን መንግስት ለጥያቄው እስከ መስከረም መጨረሻ መልስ እንደሚሰጥ አስታውቆ ነበር።

እስካሁን ከ130 ሺ ያላናሱ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው የቀሩ ሲሆን፣ ሌሎች ትምህርት ቤቶችና የመንግስት መስሪያ ቤቶችም በአድማው ይቀጥላሉተብሎ ይጠበቃል። በተዘጉት ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚውለበለቡ ሰንደቃላማዎች እንዲወርዱ ተደርጓል። ሰንደቃላማዎች እንዲወርዱ የተደረገበት ምክንያት የህዝቦችን መብቶች የሚወክሉ አይደሉም በሚል ነው።

Image

ትናንትና ምሽት አካባቢ ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍኖ የተወሰደው የዞኑ አስተባባሪ እስከአሁን ሰዓት ድረስ ያለበትን ቦታ ማወቅ አልተቻለም፡፡ ትናንት ማምሻውን በሲቪል እና መሳሪያ በታጠቁ የገዢው ፓርቲ ሀይሎች ቤቱ ተበርብሮ ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍኖ መወሰዱን በዞኑ ያሉ የፓርቲው አካላት አረጋግጠዋል፡፡

ከሰማያዊ ፓርቲ የጎንደር ዞን አስተባባሪ አቶ አግባው ሰጠኝ በተጨማሪም ወደ ስድስት(6) የሚደርሱ የአንድነት እና መኢአድ ፓርቲ አባላትም ወደ አልታወቀ ቦታ ታፍነው መወሰዳቸው ተረጋግጧል፡፡

በሌላ በኩል በጎንደር ባሉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ከፍተኛ ክትትልና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሆነ የዞኑ ተጠሪዎች አመልክተዋል፡፡

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር – ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡
‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ›› እንዳዘጋጀ ያሳወቀው ትብብሩ የትግሉ ዓላማ ፍትሃዊ ምርጫ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጾአል፡፡
‹‹ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ ያለውን ወገናዊነትና ጉዳይ አስፈጻሚነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል›› ያለው መግለጫው በመጀመሪያ ዙር የአንድ ወር ፕሮግራሙ 6 ዋና ዋና ተግባራትን ለመፈጸም ዝርዝር እቅዶችን አውጥቶ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡

phpBB [video]

በህዳር ወር የሚያከናውናቸው ተግባራትም፡-
1. በቤተ እምነት ጸሎት እንዲደረግና ጥሪ ማቅረብና አማኞች እንደየ እምነታቸው ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማድረግ
2. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ
3. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት (ሰላማዊ ሰልፍ)
4. ለመንግስት ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት
5. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግና
6. የህዝብን ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ እንደሆኑ በመግለጫው አሳውቋል፡፡
ከእቅዶቹ መካከልም በሶስት ተከታታይ እሁዶች በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች 3 የአደባባይ ስብሰባዎች እንደሚኖሩ፣ በመጨረሻው መርሃ ግብርም ህዳር 27ና 28 በፕሮግራሙ ማጠቃለያነት የ24 ሰዓት (የውሎና የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚደረግ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡

በገዥው ፓርቲና በምርጫ ቦርድ ጥምረት ይፈጸማል ያለውን ህገ ወጥ ተግባር በመታገል ለሰላማዊ ትግሉ አወንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት እስከመጨረሻው በፅናት ለመቆም መዘጋጀቱን የገለጸው ትብብሩ በአገር ቤትና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ በትብብሩ ሂደት ቆይተው እስካሁን ያልፈረሙና ሌሎች ፓርቲዎች እና የዓለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡
Image
Image
Image
Image

የበፍቃዱ ሃይሉ ወንድም በፎቶ ማንሳት ሙከራ ተይዟል።የዋስትና ጉዳይ ለነገ ተቀጥሯል።
Minilik Salsawi

193 ቀናት ካለምንም ማስረጃ ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው ብቻ ለእስር የተዳረጉት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሶስት ጋዜጠኞች በዛሬው እለት በልደታ ፍርድ ቤት ተገኝተዋል ። ነጭ በመልበስ ሰላማዊነታቸውን ያሳዩት ጦማርያኑ እና ጋዜጠኞቹ በልደታ ፍርድ ቤት ሲደርሱ ፎቶግራፍ ለማንሳት ሞክሯል የተባለ የጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ወንድም በወያኔ ፖሊሶች ቁጥጥር ስር ውሏል።

ፍርድ ቤቱ ለህዳር 3 2007 ቀጠሮ የሰጠ ሲሆን ማህሌት እና ኤዶም ያቀረቡትን የማረሚያ ቤቱ የሚደርስባቸውን በደል በተመለከተ ሃላፊዎቹ ቀርበው እንዲያስረዱ ት እዛዝ ሰቷል።ዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ለ10ኛ ጊዜ ችሎት የቀረቡት የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ሶስቱ ጋዜጠኞች ለሳምንት (ህዳር 3/2007 ዓ.ም) ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው፡፡
ፍርድ ቤቱ ዛሬ በጦማርያንና በጋዜጠኞቹ ቀደም ሲል የቀረበውን የክስ ማሻሻያ አቤቱታ መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ የተጠበቀ ቢሆንም፣ ምርመራው አላለቀም በሚል ምክንያት አጭር ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በዛሬው ችሎት ላይ ከተሰየሙት ዳኞች መካከል ሁለቱ አዲሶች በመሆናቸው ምክንያት ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ጠበቃ አምሃ መኮንን ገልጸዋል፡፡ ዳኞች ብቻ ሳይሆን ችሎት ክፍሉም በመቀየሩ ክፍሉ ጠባብ ነው በሚል፣ የተከሳሽ ቤተሰቦችና ጋዜጠኞች ችሎት መግባት አለመቻላቸውም ታውቋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በነገው ዕለት ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተከሳሾች ዋስትና ጉዳይ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ መያዙን አቶ አምሃ ጨምረው አስረድተዋል፡፡
በተከሳሾች በኩል ደግሞ፣ ሁለቱ ሴት ተከሳሾች (ኤዶም ካሳዬ እና ማህሌት ፋንታሁን) በቃሊቲ ማረሚያ ላይ ያነሱትን የመብት ጥሰት አቤቱታ በተመለከተ የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር በቀጣይ ቀጠሮ ድጋሚ ቀርቦ እንዲያስረዳ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ ሁለቱ ተከሳሾች በቀን ለ10 ደቂቃ ብቻ ስማቸው ቀድሞ በተመዘገቡ ሰዎች ብቻ እየተጎበኙ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡

– የወያኔ ልማታዊ ዲሞክራሲ የህዝብን መጉላላት እንደጨመረ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች አማረሩ።
– አዳማ ናዝሬት ውጥረቱ የነገሰ ሲሆን ሕዝባዊ ተቃውሞ ይፈነዳል ተብሎ ተፈርቷል።
– ሕዝቡ ለታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ በመተባበር ለህግ የበላይነት እና ልእልና እንዲነሳ ተጠይቋል ።
– በአዳማ ናዝሬት የባጃጅ ባለቤቶች ሊያደርጉት የነበረው የስራ ማቆም አድማ አስተላለፉት። – የታክሲ ባለንብረቶች ከትላንትና ጀምረው ቁጣቸውን እየገለጹ ነው።
Minilik Salsawi

በወያኔው መንግስት አዲሱ የልማት ስታራቴጂ በሚል በታክሲዎች እና በሕብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ እንግልት እየደረሰ እንደሆን ነዋሪዎች በመግለጽ ላይ መሆናቸው ታወቀ ። ከትላንትና ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ላይ በከተማው ትራፊኮች እየተካሄዱ ያሉ ድርጊቶች በከፍተኛ ሁኔታ ህዝብን ወደ ተቃውሞ የታክሲ ባለንብረቶችንም ወደ ስራ ማቆም አድማ የሚመራ ነው ሲሉ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ ልንጠራ እንችላለን ሲሉ አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የታክሲዎች ባለንብረቶች ማህበር አባል የገለጹ ሲሆን የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ ከበፊትም የታሰበበትና በሂደት የጊዜ ሰሌዳ ወጥቶበት እንደሚካሄድ ሲገልጹ ሕዝቡም ለዚሁ ያለውን ትብብር እንዲገልጽ በማለት ሲናገሩ ሕዝቡ ለታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ በመተባበር ለህግ የበላይነት እና ልእልና እንዲነሳ ጠይቀዋል ።

የታክሲዎች የስራ ማቆም አድማ መታየት አለበት በሚለው ሃሳብ የሚስማሙ ሹፌሮች እንዳሉት ከዚህ ቀደም በተለያዩ የከተማዋ ቦታዎች የነበሩት የታክሲ መጫኛዎች እንዲቀሩ የተደረጉ ሲሆን ወደተለያዩ ቦታዎች በመበታተናቸው የህዝቡ እንግልት ከመጨመሩም በላይ ሹፌሮችም ይህንን ተከትሎ በመንገድ ላይ እንዳይጭኑ ከጫኑ ከባድ ቅጣት እየተጣለባቸው ስለሆነ ከልማታዊው የትራፊክ ህግ ጋር ተስማምተው ሊሄዱ እንዳልቻሉ ገልጸዋል። የታክሲ ባለንብረቶችም ይሁኑ ሹፌሮች እና ረዳቶቻቸው በልማታዊው የትራፊክ እኩይ ህግ የተበሳጩ ሲሆን ቁጣቸውን በመግለጽ ወደ ስራ ማቆም አድማ ጥሪ ለማድርግ እያመሩ መሆኑን ታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአዳማ ከትላንትና ጀምሮ ከፍተኛ ውጥረት እንደተከሰተ ነዋሪዎች ተናግረዋል። ሕዝባዊ ተቃውሞ ይፈነዳል በሚል በነገሰው ውጥረት የባጃጅ ባለንብረቶች ባጃጆቻቸው ወደ ከተማው እንዳይወጡ ይዘዋቸው የነበረ ቢሆንም ፖሊስ ውጥረት እንዳሌለ እና ስራwቸን እንዲጀምሩ ሲያስገዲዳቸው ውሏል።

ስራቸውን እንዲጀምሩ ቢያስገድዳቸውም የባጃጅ ሹፌሮች ስራ ለማቆም ያስነሱት ተቃውሞ በፖሊስ የከሸ መሆኑንም ተያይዞ የመጣው ዜና ይገልጻል። ሹፌሮቹ በመንግስት ትራፊኮች ከፍተኛ የአስተዳደር በደል እና ዘረፋ ይፈጸምብናል በማለት ሲናገሩ የነበረ ሲሆን ከትላንት ጀምረው አዳማን ፖሊሶች በአጥለቅልቀዋታል ሲሉ ምንጮቹ ገልጸዋል።በአዳማ ናዝሬት ከሁለት አመት በፊት በተደረገ የስራ ማቆም አድማ ባጃጆች እና ሹፌሮቻቸው በመንግስት ላይ ተቃውሞ አሰምተው እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው ሲሉ ምንጮቹ አስታውስዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዜና በቅርብ ቀናቶች ውስጥ ህዝቡ በንቃት እንዲከታተል እና በአዳማ ናዝሪት የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሁሉ የስራ ማቆም ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲሉ የባጃጅ ሹፌሮች በላኩት ቃላቸው ገልጸዋል።

– የመከላከያ እና ፖሊስ ሰራዊቱ ላይ አለመተማመኑ እየጨመረ መጥቷል።
– የደህንነት አባላቱ መረጃን በግል ጥቅም በመለወጥ እየሰሩ ነው የሚል ግምገማ ቀርቦባቸው ተንጠዋል።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
– የሃገሪቱን ጉዳይ በተመለከተ ለበታች “ተከታይ ” ባለስልጣናት መረጃ መስጠት ቆሟል።
– የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑሮ ተነስተው ለመሸሽ እንጂ ታጥቀው ደም ለመፋሰስ ዝግጁ አይደሉም ።

በኢትዮጵያ ውስጥ መጭው ጊዜ በህዝቡ ዝምታ ተከትሎ በስርአቱ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ይከተላል የሚል መረጃ መሰማት ከጀመረ ጀምሮ በወያኔ ባለስልጣናት እና በቅርብ ሰዎቻቸው ዘንድ ከፍተኛ የሆነ ድንጋጤ መኖሩን ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል።የአስመራ ተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ ሪሞት ኮንትሮል ወያኔ እጅ ነው ስለዚህ የትጥቅ ትግል ወያኔን አያስፈራውም ያሉት ምንጮች የሃገር ውስጥ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና ወያኔ ልሙጥ የሚላቸው የተቃዋሚ ፓርቲዎቹ አጋር ዲያስፖራዎች በለውጥ እንቅስቃሴ ውስጥ ህዝቡን በማንቃት ረገድ እያደረጉት ያለው ርብርብ ትልቅ ስጋት እንደፈጠረባቸው እንዳስደነገጣቸው ሲታወቅ በድንጋጤ የመጣ ለኢሕአዴግ አንዳንድ ወቅታዊ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ያሉ ባለስልጣናት ከሃገር እንዳይወጡ እና ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ፓስፖርታቸውን ከመነጠቅ ጀምሮ በአይነቁራኛ እንደሚጠበቁ ታውቋል። የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑሮ ተነስተው ለመሸሽ እንጂ ታጥቀው ደም ለመፋሰስ ዝግጁ እንዳልሆኑ ከምንጮቹ ተሰምቷል።
Image
በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ አዳዲስ የሆኑ ውስጣዊ እርምጃዎችን በመውሰድ በተጠናከረ መልኩ በሰራዊቱ መካከል እየተከሰተ ያለውን አለመተማመን ለመቆጣተር የሚረዱ ስብሰባዎች በስፋት ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ መካሄድ የጀመሩ ሲሆን በፖሊስ ሰራዊቱም ውስጥ በተለይ በቡድን የሚያሴሩ ሰዎች አሉ እየተባለ ስለሚነገር የወያኔ አንድ ብሄር ሰዎችን በስፋት በመመደብ እንዲሁም ከዚህ ቀደም እንደተሰረገው የቢሮ ሰራተኛውን ከደህንነት ቢሮ በሚመደቡ የሕወሓት ደህንነቶች ለመተካት የታቀደ ሲሆን ቀሪውን ከቢሮ ውጭ የሚሰራውን የፖሊስ አካል ለመቆጣጠር አዲስ ሃይል እንደሚመደብ ታውቋል።የመከላከያ እና የፖሊስ ሰራዊቱ ከሃገሪቱ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር በማበር አደጋ ሊፈጥር ይችላል ሲል መፈራቱ እንዲሁም ሰራዊቱን እየከዱ የሚሄዱ መበራከታቸው አለመተማመኑን ከማስፋቱም በላይ ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርጓል።

በኢትዮጵያ ውስጥ እየተደረገ ያለውን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መንግስት አቀፍ እንቅስቃሴ በተመለከተ ከሕወሓት ባለስልጣናት ውጪ ለበታች ተከታይ ባለስልጣናት ምንም አይነት መረጃ መስጠት እንደቆመ ሲታወቅ ማንኛውም ሃገራዊ ጉዳይ አልቆ እና በአፈጻጸም ደረጃ ላይ ሆኖ እንደማንኛውም ሰራተኛ እንደሚሰሙ ባለስልጣኖቹ በመናገር ላይ መሆናቸው ታውቋል ። በደህንነት ቢሮ ውስጥ በተደረገ ግምገማ የደህንነት አባላት መረጃዎችን በግል ጥቅም በመለወጥ አሳልፋቹ እየሸጣችሁ ናቸው በሚል መገምገማቸውን የውስጥ ምንጮች ተናግረዋል።እንደ ምንጮቹ ከሆነ መረጃን ያለምንም ርሕራሔ መረጃው በአምስት ደኢቃ ውስጥ ጠላት እጅ ገብቶ ያገኘነው ነው ሲሉ የአዲስ አበባው ደህንነት ሹም አቶ ጸጋዬ ተናግረዋል።በዚህ ግምገማ የተከፉት የደህንነት አባላት በመንግስት ባለስልጣናቱ እየተናጡ ቢወረፉም ዝምታን መርጠዋል።#ምንሊክሳልሳዊ

ፍትህ ! ፍትህ ! ፍትህ ! በሰላማዊ ጥያቄ ፍትህን ለማረጋገጥ ባለመቻሉ በህዝባዊ እምቢተኝነት ይረጋገጣል!!!
Minilik Salsawi

እኛ ኢትዮጵያዊያንን በላያችን ላይ እየነቀዙ ያሉትን ነቀዝ አምባገነኖች ለማስወገድና ፍትህ ዲሞክራሲ ነጻነት እና ሰላም ለመቀናጀት ካደቀቀን የኑሮ አለንጋ ለመላቀቅ በጋራ አደባባይ በመውጣት ስርአቱን የምንገረስስበት ወሳኝ ጊዜ ላይ መሆናችንን አውቀን የተነፈግነውን ፍትህ በሃቀኝነት ማረጋገጥ አለብን።

የበሃገራችን የተንሰራፋው የኢሕአዴግ መራሹ መንግስት የፍትህ ስርአቱ እንዲቀበር እና በፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እንዲሞት በማድረግ ህዝቦች በፍትህ አካላት ላይያላቸው እምነት ተስፋ እንዲያጣ አድርጓል::የፍትህ አካላት ለሃገሪቱ ዜጎች ማገልገል ሲገባቸው ለጥቂት ባለስልጣናት እና ለጥቅማ ጥቅም በመገዛት ህጎች እንዲፋለሱ በማድረግ ላይ ይገኛሉ :;ሊሻሻል እና ሊለወጥ በማይችልበት ደረጃ ላይ የደረሰው ይህ የፍትህ አካላቱ ንቅዘት አለኝታነቱን እና ታማኝነቱን በማጉደል ከፍተኛውን ወንጀል በመፈጸም ላይ ይገኛል::

በጥቅም የነቀዙት የፍትህ አካላቱ በሙስና ላይ እርምጃ እንዲወስዱ መቀመጣቸውን ዘንግተው በፓርቲ ካድሬነት ብቻ የሰለጠኑ እና ታማኝነታቸው ለአንድ አካል እና ተጠሪነታቸውም ለገዢው በመሆኑ ህዝብ ትክክለኛ ፍትህ እንዳያገኝ በማድረግ ላይ ሲገኙ ይህንንም ላላቸው የፓርቲ ቀረቤታ በማናለብኝነት በሙስና ተዘፍቀው ፍትህ በማጓደል ህገመንግስቱን እና ተከታይ ህጎችን እያጣመሙ በመተርጎም የዜጎች መንፈስ እንዲበላች እና በፍትህ ሂደት ላይ እምነት እንዳይጣል እያደረጉ ይገኛል:: የፖለቲካ ታማኝነታቸውን መከታ በማድረግ ከፍትህ ማጓደል በተጨማሪ በጉቦ ቅሌት ላይ ተሰማርተው የሙስና ሰለባ የሆኑት የፍትህ አካላቱ በሚያገኙት ጥቅማጥቅም መዝገቦችን በመዝጋት እና ሰነዶችን በማጥፋት በተዘዋዋሪ ፍትህ ፈላጊዎችን በህገወጥ መንገድ በሃይል በማስደንገጥ በአጭሩ ሊፈቱ የሚችሉ እና ውስኔ የሚገባቸውን ጉዳዮች ቀጠሮ በማስረዘም እና የፍርድ ውሳኔዎችን በማዛባት ፍትህ ከቁጥጥር ውጪ ወቶ ህገወጥነት እንዲስፋፋ አድርገዋል::

በዳኝነት ወንበር ላይ መቀመጥ የፖለቲካ ደላልነት የሚመስላቸው የእሕኣዴግ ካድረዎች ካለምንም በቂ የህግ እውቀት በፖለቲካ ፓርቲ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ፕሮግራም ተገርተው የገረፍ ገረፍ ህግን ሰልጥነው በህግ ባለመብሰል ካለ አቅማቸው ወንበሩን ስለያዙት ከፍተኛ የፍትህ መበላቸት በመስፋፋቱ ህዝቦች ላይ ከፍተኛ የስነ ልቦና ችግር እያደረሱ ነው:: እነዚህ በህግ እውቀት የአቅም ማነስ የተጠለፉ የፖለቲካ አገልጋዮች ተቆጣጣሪ አካል ሳይሆን ፍርድ እንዲያዛቡ ያስቀመጣቸው አካል የስልታን እድሜው እንዲረዝም ምንም አይነት እርምጃ ባለመውሰዱ ዜጎችን እያስለቀሱ ይገኛሉ::

ለፍትህ አረም የሆኑት የኢሕኣዴግ ባለስልጣናት እጅግ በወረደ መልኩ ከአንድ ህዝብ አስተዳድራለሁ ከሚል አካል በማይጠበቅ አካሄድ በፍትህ ስርኣቱ ላይ ጣልቃ በመግባት ሕግ አውጪው፣ ሕግ አስፈጻሚውና ሕግ ተርጓሚው ነፃ ሆነው እንዳይንቀሳቀሱ እንዳይሰሩ በየፍርድ ቤቱ ዳኞች ላይ በስልክ እና በተለያዩ ዘደዎች ትእዛዝ በማስተላለፍ አደገኛ ሽብር እየፈጸሙ ይገኛሉ::የፖለቲካ ጣልቃ ገብነትን እና ጫና በመሸሽ ሽብር ስጋት እና ፍርሃት ስለተፈጠረባቸው ቁጥራቸው ብዙ የሆነ እና በቂ የህግ እውቀት ያላቸው ዳኞች ተሰደዋል-ከስራ ተባረዋል-በገዛፍቃዳቸው ስራ ለቀዋል-ታስረዋል..::

ይህ ማስፈራራት እና ሽብር በፍትህ አካላት ላይ የሚፈጠረው በባለስልታናት ብቻ ሳይሆን ባለስልጣናቱን መከታ ባደረጉ ሰዎችም ጭምር ነው::ባለስልጣናቱ በየፍርድ ቤቱ ዳኛ አድርገው የመደቧቸውን ካድሬዎቻቸውን በማዘዝ በህሊና እና በፖለቲካ እስረኞች ላይ ካለምንም ማስረጃ እንዲፈረድ የወዳጅ ዘመዶቻቸው መዝገብ እንዲዘጋ ሰነድ እንዲበላሽ እንዲቃጠል በማድረግ ጫና እየፈጠሩ የፍትህ ስርኣቱ እንዲነቅዝ አድርገውታል:: ይህንን የነቀዘ ስር አት እና የፍትህ ሂደት ለመገርሰስ በጋር ተያይዘን አደባባይ በመውጣት ሕዝባዊ ሃይላችንን ተጠቅመን ድላችንን ማረጋገጥ አለብን።#ምንሊክሳልሳዊ

የወያኔ መንግስት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ገጥሞታል

• ‹‹የወያኔ መንግስት የብርን ዋጋ በቅርቡ ‹ዲቫሊዌት› ሊያደርግ ይችላል››
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) ነገረ ኢትዮጵያ
Image
ነገረ ኢትዮጵያ እንዳለው የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደገጠመው የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ አንድ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የብሄራዊ ባንክ ከፍተኛ የኢኮኖሚ አጥኚ እጥረቱ መኖሩን አረጋግጠዋል፡፡ከ20 ቀናት በፊት እያንዳንዱ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የውጭ ምንዛሬ ይሸጥ እንደነበር የተናገሩት ምንጮች፣ ከ20 ቀን ወዲህ ግን በሁሉም የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ማንኛውም አይነት የውጭ ምንዛሬ እንዳይሸጥ በደብዳቤ (cercular ዞሯል) ተከልክሏል፡፡
በመሆኑም አሁን ላይ ዜጎች በውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደተቸገሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ‹‹በተለየ ሁኔታ የሚሸጥላቸው ሰዎች ከጉዞ ወኪላቸውና ከበላይ አካል ይዘውት በሚመጡት ደብዳቤ መሰረት ብቻ ነው ምንዛሬ ሊያገኙ የሚችሉት፡፡ ከዚህ ውጭ ግን እንደበፊቱ ማንም የውጭ ምንዛሬ ማግኘት አይችልም›› ሲል አንድ የንግድ ባንክ ሰራተኛ ገልጹዋል፡፡
የውጭ ምንዛሬ እጥረቱ የተከሰተው በዶላር ምንዛሬ ብቻ ሳይሆን በሁሉም የውጭ ምንዛሬዎች ላይ መሆኑንም ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡ አሁን ላይ አንድ የአሜሪካ ዶላር በጥቁር ገበያ እስከ 22 ብር እየተሸጠ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡
በሌላ በኩል ከብሄራዊ ባንክ አካባቢ የደረሱት የነገረ ኢትዮጵያ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት መንግስት ቀደም ሲል በIMF የቀረበለትን የ‹ዲቫሊዌሽን› ጥያቄ መቀበሉ እንደማይቀር ታውቋል፡፡ ‹‹አሁን ያለው ሁኔታ እንደሚያሳየን መንግስት የብርን ዋጋ በቅርቡ ‹ዴቫሉዌት› ማድረጉ አይቀሬ መሆኑን ነው፡፡ አንዳንድ ‹አርቲፊሻል› የውጭ ምንዛሬ እጥረቶች ቢኖሩም ዋናው የችግሩ መነሻ ግን የ‹ዴቫሊዌሽኑ› ጉዳይ ነው›› ሲሉ የብሄራዊ ባንክ የኢኮኖሚ አጥኚው ለነገረ ኢትዮጵያ አስረድተዋል፡፡
ሰሞኑን መንግስት ለወራት ተከልክሎ የነበረው የአረብ ሀገራት የስራ ጉዞ እንደገና እንዲጀመር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም መናገራቸው አይዘነጋም፡፡ ይህም ወደ አረብ ሀገራት የሚሄዱ ዜጎች ተጨማሪ ምንዛሬ እንዲያስገኙ ከማሰብ ሳይሆን እንደማይቀር ይገመታል፡፡

Image
ለጥቂቶቹ መልቀቅያቸው የተሰጣቸውም ሲሆን ለአብዛኞቹ ግን ገና አልተሰጣቸውም።
Minilik Salsawi Via ፍሰሃ ደስታ

በመከላከያ ሚኒስተር ውስጥ የሚገኙ የውስጥ ምንጮቼ እንደላኩልኝ የወያኔ መንግሰስት ቀኝ እጁን አጥተዋል። በዘመነ አቶ መለስ አድርግ የተባለውን ያለማወላወል የሚያደርግ : በ97 በአዲስ አበባ ወጣቶች ላይ ከፍተኛ ጥቃት የፈፀመው የኢህአዲግ ታማኙና ፈጥኖ ደራሹ የአጋአዚ ክፍለሰራዊት ከወያኔ መንግስት ጋር የነበረው ቆይታውን በፍቺ ሊፈፅመው መሆኑ ምንጮቼ ገልፀዋል።

እንደ ፍሰሃ ምንጮች ገለፃ በአጋአዚ ክ /ሰራዊት የሚገኙ ሀይሎች ከአቶ መለስ ህልፈት በኋላ ባልታወቀ ምክንያት ከቤተ መንግሰት ወጥተው ወደ ሱማሊና ደቡብ ሱዳን ጸጥታ ለማስከበር በሚል እንደተሰማሩ የሚታወቅ ነው። ከሀገር ውጭ እስከሁለት ዓመት ያክል ቆይተው ሲመለሱ ሊከፈላቸው የጠበቁት: ገንዘብ በተባበሩት መንግስታት ስኬል በመሆኑ ከፍ ያለ ነበር የተሰጣቸው ግን ሀምሳ ሽህ የኢትዮጵያ ብር ብቻ ነው። ለምን ብለው የጠየቁት ደግሞ የርግጫ የምንትሴ እየተባለ ተቆርጦ እንደቀረ ተገልፆላቸዋል።

ተቆርጦ ተገምዶ ሊያገኙ ከጠበቁት ሩቡን እንኩዋ አላገኙም።በዚህም ምክንያት የክፍለ ሰራዊቱ አባላት መንግስት ላይ ኩፍኛ አንዳኮረፉና በተለይ የሁለት ሀይሎች አብዛኛው አባላት መልቀቅያ እንዳስገቡ: መልቀቅያቸው እንዲቀዱ የተለያየ ተስፋ ቢሰጣቸውም: ለመዓርግ እድገት ቢታጩም ፍቃደኛ ሊሆኑ አልቻሉም። ለጥቂቶቹ መልቀቅያቸው የተሰጣቸውም ሲሆን ለአብዛኞቹ ግን ገና አልተሰጣቸውም።በነገራችን ላይ የአጋአዚ ሰራዊት ከውትድርና ውጭ ሌላ ሂወት የለንም ሲሉ እንደነበር ይነገራል ታድያ አሁን ከውትድርና ሂወት ወጥተው ምን ሊሆኑ ነው? ግንቦት ሰባት ጥሪ ሊያደርግላቸው ይችላል የሚል እርግጠኛ ያልሆነ ጥርጣሬ አለኝ።‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

“ይህ አገዛዝ በቃው! አንፈልገውም! 27 ዓመት + 1 አንቀበልም!”

Image
ቡርኪናፋሶን ያለገደብ ሲመሩ የነበሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ ለተጨማሪ ዓመታት ሥልጣናቸውን ለማራዘም ያደረጉት ሙከራ በመክሸፉ ከሥልጣናቸው እንደሚለቁ ገለጹ፤ ለአንድ ዓመት የመሸጋገሪያ መንግሥት ተመስርቶ ምርጫ እስከሚደረግ በሥልጣን እንደሚቀጥሉ አስታወቁ፡፡ ሕዝቡና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ግን ይህንን የሚቀበሉበት ትከሻ እንደሌላቸውና የኮምፓዎሬ አገዛዝ አሁኑኑ መውረድ እንዳለበት በተቃውሟቸው እየገለጹ ነው፡፡ ከ27ዓመት አምባገነናዊ ሥርዓት በኋላ ቡርኪናፋሶ ወደ ሌላ አምባገነናዊ ሥርዓት ልትሄድ እንደምትች ተጠቆመ፡፡

በቀድሞው ፕሬዚዳንት ቶማስ ሳንካራ ዘመን የመንግሥት ባለሥልጣንና የሳንካራ ወዳጅ የነበሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ፤ ቶማስ ሳንካራ ባልታወቀ ሁኔታ በመፈንቅለ መንግሥት ከተገደሉ ከዛሬ 27ዓመት ጀምሮ ቡርኪናፋሶን መግዛት ጀመሩ፡፡ መፈንቅለ መንግሥቱን በመምራት የተሳተፉት ኮምፓዎሬ የሳንካራን መገደል በወቅቱ “ድንገተኛ” በማለት ከመጥቀስ በስተቀር ምርመራ እንዲካሄድ አላዘዙም፤ ምስጢሩም እንዳይወጣ ተደርጎ ቆይቷል፡፡

ቶማስ ሳንካራን ከሥልጣን ካስወገዱ በኋላ ለሦስት ዓስርተ ዓመታት ያህል የዘለቀውን አገዛዛቸውን የጀመሩት ኮምፓዎሬ እኤአ በ1990ዎቹ በተደጋጋሚ የተመረጡት ሲሆን የአገሪቱ ሕገመንግሥት ከተሻሻለ በኋላ በሁለት ሺዎቹም ሁለት ጊዜ ተመርጠዋል፡፡

በአገዛዝ በቆዩበት ዘመን ሁሉ የአውሮጳውያንና የአሜሪካ ወዳጅ በመሆን ሥልጣናቸው ሳይደፈር በአምባገነንነት ለመቆየት ችለዋል፡፡ አክራሪ እስላማዊነትን እዋጋለሁ በማለት የአሜሪካ ወዳጅነታቸውን ያጠናከሩት ኮምፓዎሬ በላይቤሪያና ሴራሊዮን እጅግ አስከፊ ጭፍጨፋ ያካሄዱትን እና በአሁኑ ወቅት 50ዓመት እስራት የተበየነባቸው የቀድሞው የላይቤሪያ መሪ ቻርልስ ቴለር የቅርብ ወዳጅ ነበሩ፡፡ ሳንካራን ለመገልበጥና ለመግደል የቴይለር ጦር እንደተሳተፈና በምላሹ ኮምፓዎሬ ለቴይለር ወደ ሥልጣን መምጣትና ከዚያ ጋር ተያይዞ ለተፈጸመው ወንጀል ተባባሪ ናቸው በማለት ሁኔታዎችን የሚያገናኙ ወገኖች አሉ፡፡

በአገራቸው የሚነሱ ተቃውሞዎችን ስልታዊ በሆነ መንገድና በምዕራባውያን ድጋፍ ሲያከሽፉ የኖሩት ብሌዝ ኮምፓዎሬ በአካባቢው አገራት ዘንድ የሰላም ዘንባባ አቅራቢ፣ አስታራቂ፣ አስማሚ፣ ሸምጋይ፣ … ሆነው ምስላቸውን እና ማንነታቸውን ሲገነቡ ቆይተዋል፡፡ በአምባገነንነት በቆዩባቸው ዓመታት በሙስና በተለይም ከአልማዝ ሽያጭ ከሚገኘው ገንዘብ ያላቸው ተሳታፊነት ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል፡፡

በቀጣዩ የአውሮጳውያን ዓመት 2015 ሥልጣናቸው የሚያበቃው ኮምፓዎሬ “ደህና ሁኑ” ብለው ለመሄድ የተዘጋጁ አልነበሩም፡፡ በመሆኑም የአገሪቱን ሕገመንግሥት በማሻሻል እንደገና ለመመረጥ ደፋ ቀና ማለት ጀመሩ፡፤ ፓርላማቸውን አሰብስበው ሕገመንግሥቱ እንዲሻሻል በማድረግ ሂደት ላይ እያሉ ሕዝቡ “በቃኝ” አለ፡፡

የ27 ዓመታት አገዛዝ የመረራቸው ዜጎች ሐሙስ ዕለት ፓርላማውን ጥሰው በመግባት ድምጽ እንዳይሰጥ ከማድረግ አልፈው በእሣት አጋዩት፡፡ ተቃውሞ በየቦታው ፈነዳ፡፡ ቡርኪናፋሶ መጋየት ጀመረች፡፡ ሁኔታው ያላማራቸው ኮምፓዎሬ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጁ፡፤ ሰሚ ግን አላገኙም፡፡ ሕዝቡ “ይህንን አገዛዝ አንፈልግም፣ በቃን” አለ፡፡ ሕዝባዊ ዓመጽ በየቦታው ተቀጣጠለ፡፡ በተለይ ዋና ከተማዋ ዖጋዱጉ የዓመጹ ዋና ማዕከል ሆነች፡፡

መንግሥት ሥራ አቆመ፣ ፓርላማውም ፈረሰ፡፡ ድህነት ያስመረራቸው ዜጎች አሁንም ተቃውሟቸውን ቀጥሉ፡፡ ኮምፓዎሬን ማየትም ሆነ መስማት በጭራሽ አይፈልጉም፡፡ ወታደሮች በየአካባቢው ሥነሥርዓት ለማስጠበቅ እየጣሩ ቢሆንም ዓመጹ ግን ቀጥሏል፡፡ ንብረት እየወደመ ነው፤ ባንኮችም ተዘርፈዋል፡፡

ዛሬ አርብ ዳግም ለመመረጥ ሲመኙ የነበሩት ኮምፓዎሬ ሥልጣን በቃኝ፤ መንግሥት ፈርሷል፤ ፓርላማውም አይሰራም፤ ከሥልጣኔ እለቃለሁ ነገር ግን በ2015 ምርጫ እስከሚካሄድ የሽግግር አስተዳደር ተመስርቶ ሁሉም ነገር መረጋጋት አለበት በማለት አስቀድሞ በተቀዳ የቴሌቪዥን መልዕክት ቢያስተላልፉም ሰቆቃ የመረራቸው፣ ኑሮ ያቃጠላቸው፣ ነጻነት የጠማቸው ዜጎች ግን አሁንም “አንሰማም” ብለው ተቃውሟቸውን በመቀጠል ፕሬዚዳንቱ ከሥልጣን እንዲወርዱ ጠይቀዋል፡፡

ሰላሳ አራት የሚሆኑ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ፕሬዚዳንቱ ያቀረቡትን ቅደመ ሁኔታ አንቀበልም ብለዋል፡፡ ለኮምፓዎሬ ምላሽ ሲሰጡም “አንድ የምንቀበለው አጭርና ግልጽ ቅድመ ሁኔታ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ብሌዝ ኮምፓዎሬ ከሥልጣን እንዲለቁ ነው” በማለት ተናግረዋል፡፡

ጦሩ ሥልጣኑን የተረከበ እንደሆነ እየተጠቆመ ሲሆን አገሪቱን በበቂ ሁኔታ ለማረጋጋት እንዳልቻለ ከዋና ከተማዋ የሚመጡ ዜናዎች ይጠቁማሉ፡፡ የሕዝቡ ዓመጽም ወደ ሌሎች ከተሞች እየተዛመተ መሆኑን ከተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች እየተሰማ ነው፡፡

በአንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ዘንድ ከአረብ ጸደይ ቀጥሎ የተጀመረ “የአፍሪካ ጸደይ” ሊሆን ይችላል በማለት ግምት የሰጡበት የቡርኪናፋሶ ሕዝባዊ አመጽ ተመልሶ በአምባገነናዊ አገዛዝ እንዳይወድቅ ስጋት አላቸው፡፡ ለዚህም ጠንካራ ተቋማት መመሥረት አስፈላጊነትን ያሰምሩበታል፡፡ በተለይ ከአምባገነናዊ አገዛዝ ወደ ሕዝባዊ ሥርዓት በሚደረግ ጉዞ በቅድሚያ የሚደረጉ መሰናዶዎች ሳይከናወኑ በጭፍን አምባገነኖችን ከሥልጣን እንዲወርዱ ማድረግ በበርካታ አገራት እንደተደረገው መልኩን የቀየረ አምባገነናዊ ሥርዓት ለመመሥረት እንደሚጋብዝ ይናገራሉ፡፡ ከዚህ አንጻር የሕዝብ ንቃተ ኅሊና መዳበር፣ የእርሰበርስ ውይይት መጀመር፣ የተቋማት መመሥረት፣ … ወሳኝነት ያላቸው ቅድመ ሁኔታዎች እንደሆኑ ያሰምሩበታል፡፡

*********************
“ይህ አገዛዝ በቃው! አንፈልገውም! 27 ዓመት + 1 አንቀበልም!”
ቡርኪናፋሶ ከአምባገነን ወደ አምባገነን?
http://www.goolgule.com/it-is-over-for- … rkinafaso/

Image
ስብሓት ነጋና የኤርትራ ጉዳይ
ስብሓት ነጋ በቪኦኤ የትግርኛ ፕሮግራም ላይ የሚከተለውን ብሏል (ግርድፍ ትርጉም ነው፤ ሙሉ ዝግጅቱ ሲቀርብ ወደ አማርኛ እንመልሰው ይሆናል) ፥
«የኤርትራ ጉዳይ የቅኝ ግዛት ችግር ነው የሚለው አመለካከታችን ዳግም መፈተሽ አለበት። የአገዛዝ ችግር እንጂ የቅኝ ግዛት አልነበረም።»
ለምን አሁን???
«የኤርትራ ህዝብ ለነፃነት ከነበረው ጉጉትና ከደረሰበት ግፍ አንፃር፤ ነፃነቱን «በመረጠው መንገድ» መቀዳጀቱ ባያስቆጨንም፤ ችግሩ «የቅኝ ግዛት ችግር» ነበር የሚለው አመለካከታችን መስተካከል ያለበት ይመስለኛል።»
አሁንም በድጋሚ፤ ለምን አሁን???
የኤርትራ ጉዳይ የቅኝ ግዛት ነበር የሚል አመለካከት የህውሓትና የሻዕቢያ ብቻ እንጂ የማንም እንዳልነበር ግልፅ ነው። (የኤርትራ ህዝብ ሳይቀር ከኢትዮጵያ ጋር በአብሮነት መቀጠል እንደሚፈልግ ቀደም ሲል በጥናት የተረጋገጠ መሆኑን በዘውዴ ረታ መፅሃፍ ላይ «የኤርትራ ጉዳይ» ያነበብኩ መሰለኝ። ) ሟች መለስ እስከ ግብአተ መሬቱ ፍፃሜ ድረስ ኤርትራ የኢትዮጵያ ቅኝ ተገዢ እንደነበረች ሲያውጅ ኖሯል። ችግራቸው የአስተዳደር እንጂ የቅኝ ተገዢነት አይደለም ያሉ ኢትዮጵያውያን ተገድለዋል፤ ታስረዋል፤ ተሳደዋል፤ ወዘተ። ችግሩ የቅኝ ግዛት ነው፤ ጥያቄውም የነፃነት ጥያቄ ተብሎ፤ ያለ ህዝበ ውሳኔ መፍትሄ ተሰጥቶበታል። መፍትሄውም ጦስና ግሳንግሱን በሁለቱ ህዝብ መሃል አራግፎ፤ ኤርትራን ህዝብ አልባ ዋሻ አድርጓታል። ስንት ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን በነሱ ምክንያት አልቀዋል።
ይሄ የአገሪቱ ብቸኛ «ሉዓላዊ ግለሰብ»፤ ይህ አመለካከታቸው ዛሬ መታረም እንዳለበት የሚነግረን ለምን ይሆን? ምን ተንኮል አስቦ ነው??

Image
አብርሃ ደስታ የሁለት ድርጅቶች አባል ነው የሚል ክስ ተመስርቶበታል
#Ethiopia #UDJ #Blueparty #Ginbot7 #EPRDF #MinilikSalsawi

– ወደ አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ ታዟል
– እነ የሽዋስን ጨምሮ 10ር ተጠርጣሪዎች በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው

Minilik Salsawi
በልደታ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ምድብ ወንጀል ችሎት ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ በተሰየመው ችሎት 10 ተከሳሾች በፌደራል አቃቢ ህግ በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከ100 ገጽ በላይ የክስ ቻርጅ የተነበበላቸው ሲሆን ከክስ ቻርጁ ጋር ከ300 ገጽ በላይ የምርመራ ሰነድ ቀርቦባቸዋል፡፡

የክሱ መዝገብ የተከፈተው ዘላለም ወርቃገኘሁ በተባለውና ‹‹የግንቦት 7 አመራር ነው፡፡›› ተብሎ ክስ በተመሰረተበት ግለሰብ ሲሆን በዚህ የክስ መዝገብ የተካተቱትም፡-

1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ
2ኛ ተከሳሽ ሀብታሙ አያሌው
3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ
4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ
5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ
6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ
7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን
8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ
9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ
10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው

ለሁሉም ተከሳሾች ከዛሬ በፊት ክስ እንዳልደረሳቸውና ዛሬ ፍርድ ቤት ውስጥ እንደተሰጣቸው ታውቋል፡፡ በችሎቱ 6ኛ ተከሳሽ ከሆነው ዮናታን ወልዴ በስተቀር ሁሉም ያለ ጠበቃ የቀረቡ ሲሆን ጠበቃዎቹ ያልቀረቡበት ምክንያትም ጠበቆቹ ደምበኞቻቸው የሚቀርቡበት ቦታና ጊዜ ስላልተነገራቸው እንዲሁም ቀደም ብለው እንዳይገናኙ በመደረጋቸው መሆኑን አቶ ኃብታሙ አያሌው ችሎቱ ላይ ተናግሯል፡፡

ከሳሹ የፌደራል አቃቢ ህግ በ1996 የወጣው የወንጀል ህግ እና የጸረ ሽብር ህግ ጠቅሶ ክስ ያቀረበ ሲሆን ክሶቹ በሁለት ዋና ዋና ጭብጦች ቀርበዋል፡፡ የመጀመሪያው ጭብጥ ‹‹ከሽብርተኛ ቡድኖች ጋር በጋራ በመስራት›› የሚል ሲሆን ‹‹ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ የመንግስትን መሰረተ ልማት በማፈራረስ፣ ህዝብን ለአመጸ በማነሳሳት መንግስትን መለወጥ አላማው አድርጎ ከሚሰራውና ራሱን ግንቦት 7 ብሎ ከሚጠራው ቡድን ጋር አባል በመሆንና በወንጀል ድርጊቶች በመሳተፍ›› በሚል ቀርቧል፡፡

ሁለተኛው የክስ ጭብጥ ‹‹የሽብር ቡድን አመራር በመሆን›› የሚል ሲሆን በተለይም የአንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ‹‹የሽብር ቡድኑ አመራር በመሆንና አባል በመመልመል›› በሚል የክስ ጭብጥ ቀርቦበታልል፡፡

ከ2-5ኛ የክስ መዝገብ የሚገኙት ማለትም ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሽ፣ አብርሃ ደስታና የሸዋስ አሰፋ ‹‹ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲን ከለላ በማድረግ ግንቦት 7 የተባለውን የሽብር ቡድን አላማ ለማሳካት ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ፋሲል የኔ ዓለምና ሌሎች የሽብር ቡድኑ አባላት ጋር በስልክ በመነጋገርና በማህበራዊ ድህረ ገጸ የተለያዩ መልዕክቶችን ተለዋውጠዋል›› የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ አብርሃ ደስታ ከግንቦት 7 በተጨማሪ ‹‹ደምኢት የተባለ ቡድን አባል ነው፡፡›› የሚል ክስ ቀርቦበታል፡፡

በስተመጨረሻም ፍርድ ቤቱ ሁለት ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ አንደኛው ረቡዕ ጥቅምት 26/2007 ዓ.ም 3 ሰዓት ተከሳሾቹ ዋስትና ይሰጣቸው አይሰጣቸው በሚለው ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤቱ ከተከሳሾቹ ጠበቆች ጋር ተማክሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሏል፡፡ በሁለተኛነት ተጠርጣሪዎቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ቀደም ሲል ለአራት ወራት ወደቆዩበት ማዕከላዊ እስር ቤት እንዳይመለሱ ፍርድ ቤቱን ስለጠየቁ ፍርድ ቤቱ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት (3ኛ) እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

ተከሳሾቹ ትናንት ጥቅምት 20/2007 ዓ.ም አራዳ ምድብ ችሎት ይቀርባሉ ተብሎ የነበር ቢሆንም ሳይቀርቡ ቀርተዋል፡፡ በተመሳሳይ ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ጠዋት ወደ ልደታ ፍርድ ቤት ተወስደው የነበረ ቢሆንም እንደገና ወደማዕከላዊ ተመልሰው ከሰዓት እንዲቀርቡ ተደርገዋል፡፡

ነገም እኛ ከሕዝብ ጥያቄ እንደማናመልጥ ልናውቅ ግድ ይለናል!!!
Minilik Salsawi
እውነትን ብንውጣት ምናለ? በሃሰት ሕዝብን እያታለልን እስከመቼ እንኖራለን ? እስከመቼ ያልሆነ እንደሆነ ያልተደረገ እንደተደረገ እስከመቼ እየተደበቀ እየተሹለከለከ። የሕዝብን የነጻነት እና የመብት ጥማትን ተገን አድርገን በማይረቡ ወንፊቶች ስር ተሸሽገን የተሸሸግን መስሎን እየታየን ለምን ? የማያዛልቅ ጸሎት …. ባለፉት አመታቶች እኮ እያየን ነው ምንም ውጤት የለም አላየንም አልሰማንም የምንልበት ደረጃ ላይ ነን ያለነው። ታዲያ ምንን እንመን ? ማን እውነትን ይዟል እንበል? በፕሮፓጋንዳ አብዮት ተወጥረን እስከመቼ?

ያሌለ ነገር እንዳለ ያልተሰራ እንደተሰራ አይ አንቺ መሬት !! አዎን ያው እውነትን እንያዝ ለህዝብ ከህዝብ በህዝብ የሆነ ስኬታማ ትግል እናድርግ በማለታችን ምናልባት ልንሰደብ ልንዋረድ ልንዘረጥጥ እንችላለን ለምን በፕሮፓጋንዳ የሞሉን እውነትን መዋጥ ስለሚከብዳቸው መግቢያ ሲጠፋ ግለሰቦች ላይ ይዘምታሉ። ግለሰቦችን ከኢትዮጵያዊ ጨዋነት ውጪ ይሳደባሉ ያዋርዳሉ ይወነጅላሉ። ትላንትና ምን አሉ? ዛሬ ምን አሉ? ነገ ምን ይላሉ ? በትግል ላይ ነን እያሉን መስመሩ አያዋጣም ያሉ ሰዎችንስ እንዴት አስዋጡ ? እያንዳንዱን መለስ ቀለስ እያልን በፖለቲካ እና አገራዊ ህዝባዊ ምንዛሬ ላይ ካጤነው መጭውን ጊዜ ለመወሰን አንገታችንን የሚያስደፋን ነገር አፍንጫችን ስር ይወተፋል።

በግልጽ መውጣት ሲገባን ለሌላ የተለመደ ፕሮፓጋንዳ መስመር እና ስልት ቀይረን ስንመጣ ቀን ጠብቆ ከህዝብ ጥያቄ ማምለጥ እንደማይቻል ለመናገር እንደፍራለን። አለማቀፍ ድርጅቶች እና ሚዲያዎች የእሚነግሩን ሌላ መሬት ላይ ያለው ሌላ ፕሮፓጋንዳው የሚነግረን ሌላ ታዲያ የነጻነት ጥማታችንን እንዴት እንወጣ። ያለን የመጨረሻ እድል ሕዝቡ ሆ ብሎ አደባባይ እንዲወጣ ከማድረግ ውጪ አለ አለን በሚሉት ላይ መተማመኑ እንደማያዋጣ ሊሰመርበት ይገባል እኔም እንደ ዜግነቴ የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል አውቅልሃልሁ የሚል የህሰት ፕሮፓጋንዳ አንገሽግሾናል ። ነጻነት በጃችን ነውና ራሳችንን ነጻ እናውጣ ።

Image

የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያው የቅዱስ ሲኖዶሱን ልዕልና በማጽናት ተጠናቀቀ ::

+ የፓትርያርኩ ምሬትና ብስጭት ያሳሰባቸው ብፁዓን አባቶች ሲያረጋጓቸው አመሹ::
+ አቡነ ማትያስ አማካሪዎችን በከፍተኛ ድምፅ ‹‹ውጡልኝ›› በማለት ከፊታቸው አበረሯቸው፡፡

‹‹ከሕዝብ አጋጫችኹኝ፤ ከወንድሞቼ አንድነት ለያችኹኝ፤ ከነገራችኹኝ አንዱንም የተቀበለኝ የለም›› በሚል የተመረሩት አቡነ ማትያስ ምክራቸው ያልሠመረላቸውን ሦስት አማሳኝ አማካሪዎችን በከፍተኛ ድምፅ ‹‹ውጡልኝ›› በማለት ከፊታቸው አበረሯቸው፡፡

ከትላንትናው የስብሰባ ውሎ መጠናቀቅ በኋላ ፓትርያርኩ የነበሩበት የምሬትና የብስጭት ኹኔታ ተነግሯቸው ወደማረፊያቸው የተጠሩት በሹመት ቅድምና ያላቸው ብፁዓን አባቶች÷ አቡነ ማትያስ በተጠሪነት ጉዳይ የተሟገቱለት አቋም የቤተ ክርስቲያን እንዳልኾነ፣ ለአጭር ዕድሜ የኖረው የቤተ ክርስቲያን ሕግ መለወጥ እንደሌለበት ይልቁንም የአማሳኞችንና የባዕዳንን ምክር ከመስማትና ከመቀበል ተጠብቀው ትላንት ከቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ጋራ ኹነው የተከላከሉለትን ሕገ ቤተ ክርስቲያን ማስከበራቸውን ቢቀጥሉ በእርሳቸውና በአባቶች መካከል ያለው ውጥረት ሊረግብና ሊተራረቅ እንደሚችል አመልክተዋቸዋል፡፡

ፓትርያርኩ በትላትናው ምሽት አማሳኞቹን በብስጭትና በምሬትም ቢኾን ከአበረሯቸውና በብፁዓን አባቶች ምክር ከተጽናኑ በኋላ በዛሬው የምልአተ ጉባኤው ውሎ ስብሰባውን በተረጋጋና በመግባባት መንፈስ ሲመሩና ‹‹እናንተ ካላችኁት አልወጣም›› እያሉ በጋራ ሲወስኑ ውለዋል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶሱን የበላይነት(ልዕልና) በማረጋገጥ በተጠናቀቀው የሕገ ቤተ ክርስቲያን ማሻሻያ ረቂቅ አጀንዳ፣ ከፓትርያርኩ ጀምሮ እያንዳንዱ ሊቀ ጳጳስና ኤጲስ ቆጶስ(ጳጳስ) ተጠሪነቱ ለቅዱስ ሲኖዶሱ እንደኾነ ጸንቷል፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት ኾኖ ሲሠራበት የቆየው ልምድ በማሻሻያው ተካትቶ እንዲደነገግ ተወስኗል፡፡ በልዩነት ነጥቦቹ ላይ በተላለፉት ውሳኔዎች መሠረት ረቂቁ ተስተካክሎ ሲቀርብ በምልአተ ጉባኤው አባላት ፊርማ እንደሚጸድቅ ይጠበቃል፡፡

በደቡብ አፍሪቃ በሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብና በምእመናን መካከል ለተፈጠረው አለመግባባት መፍትሔ ለመስጠት በቀረበው የአጣሪ ልኡክ ሪፖርት ላይ የመከረው ምልአተ ጉባኤው÷ ብፁዕነታቸው ለጊዜው መንበረ ጵጵስናቸውን በናይሮቢ አድርገው በኬንያ፣ በጅቡቲና በሱዳን ተወስነው እንዲሠሩ፤ በደቡብ አፍሪቃ ደግሞ አገልግሎቱ በአድባራት አለቆችና በሰባክያነ ወንጌል ላይ ተመሥርቶ እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡ ምልአተ ጉባኤው በሰሜን አሜሪካ በሚገኙት ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ጉዳይ መምከር ጀምሯል፡፡

ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ራሱን የቻለ ሊቀ ጳጳስ ስለመመደብና በሀገረ ስብከቱ የተፈጠሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ዙሪያ በነገው ዕለት በመምከር ውሳኔ እንደሚያሳልፍ ይጠበቃል፡፡

#Ethiopia #SouthSudan #OELF #ExEthiopianArmyOfficers #MinilikSalsawi

ሰው በላው መንግስቱ ሃይለማርያም መሞት ሆነ መኖር ማንችንንም ሊያስጨንቀን ሊያሳስበን አይገባም።
Minilik Salsawi

በስልጣን ላይ ያለውን የወያኔን አምባገነን መንግስት ለማስወገድ በትጥቅ ትግል ውስጥ የገቡ ተቃዋሚ ሃይሎች ከደቡብ ሱዳን የውጪ ጉዳይ ባለስልጣናት እና ዲፕሎማቶች ጋር መገናኘታቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገልጸዋል።ከባለስልጣናቱ ጋር የተገናኙት በኤርትራ ውስጥ እንቅስቃሴ የማያደርጉ ድርጅቶች እና በአስመራ ቢሮ የሌላቸው የፖለቲካ ሰዎች እንደሆኑ ታውቋል።

በመጪው ጊዜያት ሊደረጉ ስለሚችሉ እና ሊከናወኑ ስለሚገባቸው ጉዳዮች እንዲሁም በደቡብ ሱዳን የተቃዋሚ ሃይሎች ከጁባ መንግስት ተጽእኖ ስር ያልወደቀ የራሳቸው መንደርደሪያ መሬት እና ወታደራዊ ቤዝ የሚያገኙበትን ጉዳይ በተመለከተ መወያየታቸው ታውቋል። እንዲሁም አስፈላጊ የሆነ ወታደራዊ እርዳት የሚደረግበትን ሁኔታ ላይ መነጋገራቸው ሲታወቅ በቀድሞ የደርግ መንግስት ከፍተኛ መኮንኖች እንደ ዜግነታቸው ሃገራቸውን ለመካስ በወታደራዊ አማካሪነት ላይ የሚሰሩበትን አስመልክቶ የጁባው መንግስት ስምምነቱን ገልጿል።ምንጮቹ ከዚህ በላይ ዝርዝር ሁኔታ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆኑም።

መንግስቱ ሃይለማርያም የኢትዮጵያን ተቃዋሚ የትጥቅ ትግል የሚፈልጉትን አካላቶች ከደቡብ ሱዳን ባለስልጣናት ጋር ያገናኛል የሚል ፍራቻ የተከሰተ ይመስል ይህን ሰሞን ከባለፈው አመታት በተወራረሰ መልኩ በቀጥታ ግልባጭ መንግስቱ ሃይለማርያም እንደሞተ አድርገው የሻእቢያ አቧራ አጫሽ ድህረገጾች ወሬውን እያቦነኑ ይገኛሉ። በባለፈው ጊዜ እኔ ራሴው መንግስቱ ሃይለማርያም እንደሞተ ተነፋፍሼ ነበር ከዛሬዎቹ አለን ባይ ምንጮቼ ያገኘሁትን ይዤ ።

የሆኖ ሆኖ በየእስር ቤቱ ስለታሰሩብን የፖለቲካ መሪዎቻችን ጋዜጠኞቻችን እና የሃይማኖት ምሁራን መጨነቅ እና ስለመጪው ትግል ሰፋ ያለ ስራ መስራት ይገባናል ። ሻእቢያ ይህን ሰሞን በኤርትራ የተነሳበትን ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በሌላው ዘንድ አትኩሮት እንዳያገኝ ከሚሰራው ስራ ጎን ለጎን የመንግስቱ ሃይለማርያምን መሞት ሊያረዳን ይፈልጋል። ወይ ሻእቢያ እና ወያኔ ለማደናበር ማን ብሏቸው።

ሰማያዊ ፓርቲ ጥቅምት 18/2007 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ የኢትዮጵያ ህዝብ አፋኙን ስርዓት በመቃወምና ከስርዓቱ ጋር ባለመተባበር በብሔራዊ ደረጃ የሚደረገው ትግል አካል እንዲሆን ጥሪ አቀረበ፡፡
ImageImage
‹‹የሀገራችን አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሱና እየከፉ የመምጣታቸውን ያህል ገዢው ፓርቲ ቆም ብሎ ከማሰብ ይልቅ ወደ ማይወጣው አዘቅት ውስጥ ሀገሪቷን ጭምር እያንደረደራት ይገኛል›› ያለው የሰማያዊ ፓርቲ መግለጫ ገዥው ፓርቲ ከዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ሂደት ፍፁም በማይጣጣም መልኩ አፋኝ መዋቅሩን በማናለብኝነት እያስፋፋ እንደሚገኝ አብራርቷል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ለማናቸውም አስተዳደራዊም ይሁን ፖለቲካዊ ጥያቄዎች ሀይልን በመጠቀም ለመደፍጠጥና ለማጥፋት ቆርጦ በመነሳት ፍፁም አምባገነንነቱን ገፍቶበት የበርካቶች ህይወት እየቀጠፈ እንደሆነ ገልጾአል፡፡

መግለጫው ለስርዓቱ አፋኝነት በምሳሌነት ካነሳቸው መካከል በአለፈው ክረምት ወራት ጀምሮ ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የሚሰጠው የግዳጅ ስልጠና የሚገኝበት ሲሆን በስልጠናው ስነ ምግባር በጎደለው መልኩ የጥላቻ ዘመቻ በማካሄድ የሃሳብ ልዩነትን የማስተናገድ ፍላጎቱ ሙሉ ለሙሉ እንደተዳፈነ ያሳየ ነው ብሎታል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ እነዚህን ስልጠናዎች እጅግ በቅርበት ሲከታተላቸው የቆየ መሆኑንና ከጅማሬውም ተቃውሞውን በይፋ መግለጹንም መግለጫው አውስቷል፡፡
ፓርቲው በጋዜጠኞች ላይ የተወሰደው የማሳደድ እርምጃ፣ በነጻው ፕሬስ ላይ የተፈጸመው አፈና የስርዓቱን መበስበስ እና አፋኝ አምባገነንነትን ብቸኛ አማራጭ አድርጎ መቀጠል መምረጡን ግልጽ አመላካች ነው ብሏል፡፡

‹‹እጅግ የከፋውና እየተባባሰ የመጣው ከፍተኛ አደጋ ያዘለ ችግር ያለው አስተዳደራዊ እና ፖለቲካዊ ጥያቄ እያነሱ ያሉ የሕብረተሰብ ክፍሎችን በሀይል ለመግዛት ቆርጦ መነሳቱ ነው›› ያለው መግለጫው በተለይ በኦጋዴን በርካታ ዜጎች በመንግስት ሀይሎች ህይወታቸው መቀጠፉ ሳያንስ ሬሳቸው እንኳን ክብር በሌለው ሁኔታ መሬት ለመሬት እየተጓተተ ባደባባይ ሰብአዊ መብት ሙሉ ለሙሉ መጣሱን አውስቷል፡፡ በተጨማሪም በጋምቤላም የህወሓት ሰዎች መሬት በሕገ-ወጥ መንገድ መቀራመታቸውን የተቃወሙ በርካታ የሰው ህይወት የተቀጠፈበት ሁነት ሀገሪቱ ወደ ከፋ ሁኔታ እያመራች ለመሆኑ አመላካች ነው ሲል ገልጾአል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ገዥው ፓርቲ በህዝብ ላይ የሚፈጽመውን በደል በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን ያስታወቀው መግለጫው ‹‹የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ ከግምት በማስገባት መላው የሀገሪቱ ህዝብ፣ በውጪ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ለሀገር ተቆርቋሪ ተቋማት እንዲሁም በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ስር ሆናችሁ ለውጥን የምትሹ ወገኖች ሀገራችንን ወደ አደጋ እየወሰዳት ያለውን አፋኝ ስርዓት በቻላችሁት ሁሉ በመቃወምና ከስርዓቱ ጋር ባለመተባበር በብሔራዊ ደረጃ የሚደረገው ትግል አካል እንድትሆኑ›› ሲል ጥሪ አቅርቧል፡፡

ለተቃውሞ ሰልፉ ህዝቡ እንዲዘጋጅ ጥሪውን አቅርቧል።
ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት የተቃውሞ ሰልፉን ቀን ይፋ ያደርጋል ተብሎ የሚጠበቀቅ መኢአድ በፋሽሽቱ ወያኔ በጋምቤላ በጉራፈርዳ እና በሱማሌ ክልል እየተካሄደ ያለዉን የዘር ማጥፋት ወንጀል በጋራ ለማስቆም መላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚሳተፍበት ተከታታይ የተቃዉሞ ሰልፍ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ይደረጋል፡፡ ሲል የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ አስታወቀ።

በዉጭም በሃገር ዉስጥም የምትገኙ ኢትዮጵያዊያን ከጎናችን በመቆም ይህን ዘረኛ ስርዓት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ በድሞክራሳዊ ስርዓት እንቀይረዉ፡፡ ያለው መኢአድ አስፈላጊዉን ዝግጅት ሁሉ አጠናቀናል፡፡ ሲል ለተቃውሞ ሰልፉ ህዝቡ እንዲዘጋጅ ጥሪውን አቅርቧል።‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬

Image
አንድነት ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው በገዛ ፍቃዳቸው ሥልጣናቸውን ለቀቁ
አቶ በላይ ፍቃዱ ቀጣዩ ፕሬዚዳንት በመሆን ተመረጡ

Image
የአንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ የተሰበሰበ ሲሆን በስብሰባውም ላይ በፕሬዚዳንቱ ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው ሪፖርት የቀረበ ሲሆን ከውስጥና ከውጭ በተፈጠሩ አንዳንድ የማያሰሩ ችግሮች፣ ካለባቸው የሥራ ጫና እና ፓርቲው ወደፊት አንድነቱን ጠብቆ ለ2007 ምርጫ አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ በማሰብ በራሳቸው ሙሉ ፍቃድ ከፕሬዚዳንትነታቸው በመልቀቅ ለብሔራዊ ም/ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት አሳውቀዋል፡፡
ብሔራዊ ም/ቤቱ የኢ/ር ግዛቸው የሰለጠነ ዲሞክራሲያዊ አካሄድ እጅግ ከፍተኛ በሆነ አክብሮት በመመልከትና በአገር ውስጥ በተቃውሞው ጎራ ለሚንቀሳቀሱና ለራሱ ለገዢው ፓርቲም ጭምር አስተማሪ የሆነ እርምጃ በመውሰዳቸው አክብሮትን ቸሯቸዋል፡፡
በቀጣይም የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ በሚፈቅደው መሰረት በፕሬዚዳንትነት የሚመሩ እጩዎችን በማቅረብ ለማስመረጥ አምስት አባላት በአስመራጭ ኮሚቴነት ተሰይመዋል፡፡
Image
ራሳቸውን ለፕሬዚደንትነት በእጩነት ያቀረቡት
1ኛ. አቶ በላይ ፈቃዱ
2ኛ. አቶ ደረጀ ኃይሉ
3ኛ. አቶ ትዕግስቱ አወሉ ሲሆኑ እነዚህ እጩዎች ራሳቸውን ተራ በተራ ካስተዋወቁ በኋላ የብሔራዊ ም/ቤቱ አባላት
በምስጢር ድምፅ አሰጣጥ ለሚፈልጉት ዕጩ ድምፅ ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም በተደረገው የድምፅ ቆጠራ አቶ በላይ ፍቃዱ ከፍተኛ ድምፅ በማማምጣት አንድነት ፓርቲን በፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ ተመርጠው ቃለ መሃላ ፈፅሟል፡፡
Image
ስብሰባው እጅግ ዲሞክራሲያዊ በሆነ መግባባት ተጠናቋል ሲሉ የአንድነት ፓርቲ ሴክሬታሪያት ለፍኖተ ነፃነት ገልጸዋል፡፡

በእስር ላይ የሚገኘው የሰማያዊ ፓርቲ አመራር የሽዋስ አሰፋ የርሃብ አድማ አደረገ ።
የሽዋስ አሰፋ በርሃብ አድማው ምክንያት ሰውነቱ እንደተዳከመ ባለቤቱ ገልጻለች፡፡

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
በማዕከላዊ ምርመራ ታስሮ የሚገኘውና የሰማያዊ ፓርቲ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ የሆነው አቶ የሽዋስ አሰፋ የአራት ቀን የርሃብ አድማ አደረገ፡፡ የሸዋስ ማክሰኞ ጱግሜ 4 ጀምሮ አዲሱን አመት በርሃብ አድማ ያሳለፈ ሲሆን ቅዳሜ መስከረም 3/2007 ዓ.ም ምግብ እንደቀመሰ ባለቤቱ ወይዘሮ ሙሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻለች፡፡ አቶ የሽዋስ የርሃብ አድማ ያደረገው ከታሰረበት ሐምሌ 1/2006 ዓ.ም ጀምሮ ከጠበቃው ጋር ከአንድ ጊዜ በላይ መገናኘት ባለመቻሉና ዘመድ አዝናድ እንዲሁም የኃይማኖት አባት እንዳይጎበኘው በመከልከሉ ነው፡፡ የሽዋስ አሰፋ በባለቤቱ ብቻ ከሳምንት አንድ ቀን እንዲጎበኝ የተፈቀደለት ሲሆን የርሃብ አድማ ባደረገባቸው ቀናት ባለቤቱ ምግብ ስታስገባ ለየሸዋስ ምግቡ እንደደረሰው ተደርጎ ባዶ ሳህን ሲደርሳት ቆይቷል፡፡

ባለቤቱ የበዓል ቀን ልትጎበኘው በሄደችበት ወቅት ‹‹ወጥቷል›› ተብላ የተመለሰች ሲሆን በማግስቱ ልጆቹን ይዛ ልትጠይቅ ስትሄድም ‹‹ስብሰባ ላይ ናቸው!›› በሚል እንዳታገኘው በመደረጓ ለ15 ቀናት ሳትጠይቀው ቆይታለች፡፡ አቶ የሽዋስ ‹‹የርሃብ አድማውን ያደረኩት ቤተሰብና ጠበቃዬ እንዳይጠይቁኝ በመከልከላቸው ነው፡፡ ለምን እንዲጠይቁኝ አይደረግም? ብዬ ጥያቄ ሳቀርብ ማንም አልመጣም፡፡ ቢመጣ እንድትጠየቅ እናደርግ ነበር፡፡›› የሚል መልስ እንደሚሰጡት ገልጾአል፡፡

በሌላ በኩል ጠበቃው ተማም አባ ቡልጉ የሽዋስን ለማግኘት በተደጋጋሚ ወደ ማዕከላዊ አቅንቶ የተለያየ ምክንያትና መሰናክል እየፈጠሩ ሳያገናኙት እንደቀሩ ገልጾአል፡፡ ጠበቃ ተማም ‹‹ለበርካታ ቀናት አመላልሰውኛል፡፡ ለምሳሌ አንድ ቀን ረቡዕ ጠዋት ሄድኩኝ፡፡ መብትን መለመን ጥሩ ባይሆንም እንዲያገናኙኝ ብለምናቸውም ሊያገናኙኝ አልቻሉም፡፡ ከሰዓት እንድመለስ ነግረውኝ ከሰዓት ብሄድም አሁንም ሊያገናኙኝ አልቻሉም፡፡ ለቀጣይ ረቡዕ ቀጠሩኝ፡፡ አሁንም ረቡዕ ስሄድ የተለያየ ምክንያት እየፈጠሩ ሊያገናኙኝ አልቻሉም፡፡ እንዲያውም ‹‹ምን ታመጣለህ አናገናኝህም!›› አሉኝ፡፡ ብዙ ጥረት ባደርግም ሊያገናኙን አልቻሉም፡፡ የሚገርመው የዳንኤልና የሃብታሙ ጠበቃ የሆኑ ሌሎች ጓደኞች አሉኝ፡፡ አንድ ሰው ከአንድ ጠበቃ በላይ ሊኖረው እንደሚችል እየታወቀና እኔም ደንበኞቼን ማግኘት እንዳልችል ከልክለውኝ እነሱን ግን ‹‹እኛ የምናውቀው ተማምን ነው›› ይሏቸዋል፡፡ እኔ ስሄድ ደግሞ ደንበኞቼን እንዳላገኝ እደረጋለሁ፡፡›› ሲሉ ሁኔታውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የሽዋስ ምግብ ሲገባለት ምግቡን የሚያደርሱለት አካላት መልሰው ለሚስቱ እንዲሰጧት ይነግራቸው እንደነበር የተናገረ ሲሆን የርሃብ አድማ ላይ እንደሆነ እንዳይታወቅ ምግቡን የበላ አስመስለው እቃውን ባዶ አድርገው መመለሳቸው አሳፋሪና ቅጥ ያጣ አፋኝነት መሆኑን መግለጹ ታውቋል፡፡ የሽዋስ አሰፋ በርሃብ አድማው ምክንያት ሰውነቱ እንደተዳከመ ባለቤቱ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻለች፡፡

– የዩንቨርስቲው ስልጠና በግሩፕ እንዲደረግ ቢሞከርም ከፍተኛ አለመግባባት በመፈጠሩ ተበትኗል።
– ሽመልስ ከማል ከለገሃር ሙልሙል ጫት ቤት ተጠርቶ አለቃ ጸጋይ ፊት በመቅረብ ማስጠንቀቂያ ተሰቶታል።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

ለአንድ ሳምንት ያህል ሊሰጥ የታሰበው እና ለሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች መምህራን የተጀመረው የወያኔ የልማታዊ ዲሞክራሲ ስልጠና ገን ክጅምሩ ከፍተኛ ተቃውሞ እንደገጠመው ከተለያዩ መምህራን የተሰበሰቡ መረጃዎች ጠቁመዋል። ገና ስልጠናው ከመጀመሩ መምህራኑ መንግስት ያለብንን ችግር እና የሃገሪቱም ሁኔታ ማገናዘብ እና መፍታት ካልቻለ የስራ ማቆም አድማ እናደርጋለን ሲሉ በጭብጫባ የታጀበ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል። ይህ የግዳጅ ስልጠና በተለያዩ አደራሾች የተጀመረ ሲሆን መምህራኑ እንዳሉት የውይይቱ የመግቢያ ሰነድ ተረስቶ በሃገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ እና በመምህራን ሕይወት ዙሪያ ከባድ የሆነ ንትርክ ተገጥሞ ለወያኔ አሰልጣኞች ከባድ ጋሬጣ ሆነው እንደነበር መምህራኑ ክላኩት መልእክት ለማወቅ ተችሏል። የመምህራኑ ስልጠና በነገው እለትም የሚቀጥል ሲሆን ለወያኔ የእግር እሳት እንደሚሆኑ ይጠበቃል።ምንሊክ ሳልሳዊ

በዛሬው እለት ጠዋት በሽመልስ ከማል ሲመራ የነበረው እና የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የኢንዱስትሪ ካምፓስ ተማሪዎች የግዳጅ ስልጠና በጩኸት ቢበተንም ሽመልስ ከማል ደንግጦ ከስብሰባ አደራሹ በመውጣት ተደብቆ የጠፋ እና ወደ ተለመደው የጫት ሱስ ተግባሩ የሄደ መሆኑን ሁኒታውን ሲከታተሉ የነበሩ እና አብረውት በአስተባባሪነት እና በተባባሪ አሰልጣኝነት የተመደቡ ካድሬዎች ጠቁመዋል። ለአለቆቹ ሪፖርት ሳያደርግ ወደ ጫት ቤት ያቀናው ሽመልስ ከማል በአስቸኳይ የስልክ ጥሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ካለው የአለቃ ጸጋይ ቢሮ ተጠርቶ በመሄድ ከስልጠናው ጋር በተያያዝ ከፍተኛ የሆነ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው ሲሆን ከቢሮው ሲወጣ ፊቱ ተለዋውጦ እና ደንግጦ እንደነበር አስተባባሪዎቹ እና ተባባሪ አሰልጣኞቹ ከሰጡኝ መረጃ ለማወቅ ችያለው።

የስልጠናው አስተባባሪዎች ስልጠናውን ለመቀጠል አቶ ሽመልስ ከማልን ትተውት ወደ አ አ ዩ ኢንዱስትሪ ካምፓስ ቢደርሱም ተማሪው ከተባለበት ሰአት ሁለት ሰአታት ያህል በመዘግየት ከቀኑ 9 ሰአት ላይ በየግሩፑ ቢመጣም የግሩፕ ስልጠና አስተባባሪ እና አሰልጣኝ ካድሬዎች ተማሪውን በፍጹም ሊያሳምኑት ያልቻሉ ሲሆን ተማሬው አቴንዳስ ሲደረግ የታደለውን ኖትቡክ እና ቢክ እስክርቢቶ እንዳልተጠቀመበት ታውቛል።ብዚህ ስልጠና ላይ ተዋት ተማሪው በጩኸት እና በፉጨት ስለረበሸ የውሃ እና የሻይ አቅርቦት ተከልክሏል።ምንሊክ ሳልሳዊ

የከሰአት በኋላ ስልጠና በግሩፕ የተከፋፈለ ሲሆን ይህንን ያደረጉት ተማሪው በጋራ ሆኖ ተቃውሞ እንዳያሰማ እና በግሩፑ ተቃውሞ ቢኖር እንኳን በቀላሉ መቆጣጠር እንዲቻል ተማሪው ጎን ለጎን እንዳያወራ አራርቆ በማስቀመጥ
ተማሪው እርስ በ እርስ እንዳይደጋገፍ ለማድረግ ነው። አሰልጣኞቹ ካድሬዎች ስልጠናውን በተማሪው መሰላቸት በመደናበራቸው 9 ሰአት ስልጠናውን ጀምረው ወዲያው ተማሪው ጥያቄ ካለው ብለው ጥያቄ እንዲጠይቅ ሲያደርጉ ከተጠየቁ ጥያቄዎች መካከል ስልጠናው ጥቅም የለውም?፣ አላማው ምንድነው?፣የቀድሞ ስራቶችን ክፋት ብቻ ለምን ታወራላችሁ ?፣ ራሳችሁን በ21ኛው ክፍለዘመን ለምን ከኋላቀር የቀድሞ ንጉሳውያን አስተዳደር ጋር ትመዝናላችሁ፡? ከናንተ በፊት መንግስታት እንጂ የሚበድሉት በህዝብ መካከል ፍቅር እና የሃይማኖት መቻቻል ነበር ይህን አምናቹሃል አሁን የት ገባ?፤ ወደ ኋላ እየተመለስን ከምናላዝን ለምን አሁን ባሉት እና ወደፊት በሚኖሩት አስቸጋሪ ፈተናዎች እና ጉዳዮች ላይ አናተኩርም ? ወዘተ የሚሉ ጥያቂዎች ቢነሱም ምላሾቻቸው የማያረኩ የተድብሰበሱ እና የሚያደናግሩ ነበሩ ። እንዲሁም በነገው እለት በነጻ ፕሬስ በጋዜጠኞች እና በመንግስት መካከል ስላለው ሁኔታ ለመወያየት ቀጠሮ ተይዞ ስልጠናው በተማሪው መሰላቸት እና ጉርምርምታ 9 ሰአት ጀምሮ 10.30 ተበትኗል።

ህወሓት ብአዴንም፣ ኦህዴድም፣ ኢህአዴግም ሆኖ ሁሉም የሚጠይቀውን ጥያቄ ይመልሳል፡፡
አዛዡም ናዛዡም ህወሓት ነው:: Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

ከአመታት በፊት የገዥው ፓርቲ አባል ሳይሆን በመንግስት ስራ ላይ ተሰማርቶ ይሰራ ነበር፡፡ 1997 ዓ.ም በኋላ ግን በዚህ አቋሙ አልቀጠለም፡፡ ‹‹አንዴ ቅንጅት ሌላ ጊዜ ደግሞ ኦነግ እያሉ ስም ሲለጥፉብኝ ‹ከዚህ ሁሉ!› ብየ ኦህዴድን ተቀላቀልኩ›› ይላል ካድሬው ለነገረ ኢትዮጵያ፡፡ ከዚህ በኋላ ባሉት ጊዜያት ደመወዝና እድገት በእጥፍ ተጨምሮለታል፡፡ የትምህርት እድል ተሰጥቶታል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ኦህዴድም ሆነ ኢህአዴግ ህዝብ ላይ የሚፈጽሙትን በደል በቅርብ ርቀት ተገኝቶ ተከታትሏል፡፡

ካድሬው እንደሚለው ከእነ አባዱላና መሰል ፖለቲከኞች ውጭ የኦህዴድ ካድሬዎች በፓርቲያቸው እምነት የላቸውም፣ በህወሓት በደል በእጅጉ ተማርረዋል፡፡ የ‹‹ብአዴኖችም ከእኛ የሚለይ ነገር የለውም፡፡ ተመሳሳይ ነው፡፡›› ይላል ካድሬው፡፡

በበርካታ ጉዳዮች ‹‹ፓርቲዬ›› ከሚለው ኢህአዴግ እንደሚለይ ቢገልጽም በአንድ ጉዳይ ግን ይስማማማል፡፡ ‹‹ጥያቄ የሚያቀርብ ካድሬ አንድም ኦነግ አሊያም የድሮው ቅንጅት አካል የነበረ ፓርቲ ወይንም ትምክተኛ ተብሎ ስም ይሰጠዋል፡፡ ኦነግ ወይንም ‹‹ቅንጅትነት/ትምክተኝነት›› ጥያቄ ማንሳት ከሆነ የኦህዴድ ካድሬዎች ሲገለጡ ኦነጎች ናቸው፡፡ ብአዴኖቹ ደግሞ እንደዛው ቅንጅት/ትምክተኛ ናቸው ማለት ነው››፡፡ በዚህ ጉዳይ ካድሬው የድሮው ጠቅላይ ሚኒስትር ‹‹ኦህዴድ ሲገለጥ ኦነግ ነው!›› በሚለው ይስማማል፡፡

ካድሬው ለነገረ ኢትዮጵያ እንደገለጸው በተለይ የብአዴንና የኦህዴድ ካድሬዎች በህወሓት ጫና ከመቼውም በላይ ተማርረዋል፡፡ ‹‹አዛዡም ናዛዡም ህወሓት ነው፡፡ ትጠይቃለህ፡፡ ስም ይሰጥሃል፡፡›› የሚለው የኦህዴድ ካድሬ፤ የኦህዴድና የብአዴን ካድሬዎችም ሆነ ባለስልጣናት ይህ ነው የሚባል ተጽዕኖ እንደሌላቸው ከተሞክሮው ይመሰክራል፡፡ ‹‹ብአዴንና ኦህዴድ ይጠይቃሉ፡፡ ህወሓት ይመልሳል፡፡ የብአዴንና የኦህዴድ ባለስልጣናት ካድሬዎቹ የሚጠይቋቸውን ጥያቄዎች እንኳን በራሳቸው መመለስ አልቻሉም፡፡ ህወሓት ብአዴንም፣ ኦህዴድም፣ ኢህአዴግም ሆኖ ሁሉም የሚጠይቀውን ጥያቄ ይመልሳል፡፡ እንዲያው እድል ተሰጥቷቸው የሁለቱ ፓርቲዎች ፖለቲከኞች ቢመልሱ እንኳ የህወሓት ተራ ካድሬም ቢሆን የሆነ ነገር ያስተካክላል፡፡ ኦህዴድና ብአዴን ብቁ አለመሆናቸውን ለማሳየት የሚያደርገው ነው፡፡››

ካድሬውን ‹‹ኢህአዴግን ምን የሚያሰጋው ይመስልሃል?›› በሚል ከነገረ ኢትዮጵያ ለቀረበለት ጥያቄም የመጀመሪያው ያደረገው ፓርቲው ውስጥ ያለውን ክፍፍል ነው፡፡ ‹‹አብዛኛው የኢህአዴግ ካድሬ እንደ እኔ ፓርቲው ያደርስብኛል ካለው አደጋ ለመዳን አሊያም ለገንዘብ የተቀላቀለ ነው፡፡ አያምንበትም፡፡ ሁሉም ቀን ነው የሚጠብቀው፡፡ ወደ ህዝብ ሲቀርቡ በመካከላቸው ችግር እንደሌለ ያስመስላሉ እንጅ የኢህአዴግ አባል ፓርቲዎች በመካከላቸው ከፍተኛ ቅራኔ አለ፡፡ ለምሳሌ ያህል በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ የተወሰደው እርምጃ የኦህዴድ ካድሬዎችን አስቆጥቷል፡፡ እስካሁን ይመለስላቸው አይመለስላቸው ባላውቅም በወቅቱ እነ አባዱላ ፓስፖርታቸውን እንደተቀሙ ሰምቻለሁ፡፡ ይህ አንድ ቀን የሚፈነዳ ይመስለኛል፡፡››

ሌላው ይላል ካድሬው ‹‹ህዝብ በፓርቲው እምነት እንደሌለው ሁላችንም እናውቃለን፡፡ ህዝብ ገንፍሎ የሚወጣ ይመስለኛል፡፡ በእርግጥ አሁን ህዝቡ ዝምታን መርጧል፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ህዝብን ለማሳመን ወይንም ለማስተማር በሄድኩበት አጋጣሚ ከዝምታው በስተጀርባ ህዝብ ለፓርቲው ጥላቻ እንዳለው ለማየት ችያለሁ፡፡ በቅርቡ በተለያዩ የኦሮሚያ ዩኒቨርሲቲዎች ስልጠና የተሰጣቸው ተማሪዎች ሰነዱን አቃጥለው ስለ ነጻነት ዘምረዋል፣ ፓርቲው አብጠልጥለዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሲደማመር አንድ ቀን ህዝብ ገንፍሎ የሚወጣ ይመስለኛል››

ዘላለማችንን የፖለቲካ የበታችነት የተጠናወተን ጥገኞች ሆነናል:: በባህር ዳር ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እየተካሄደ ያለው የብአዴን ካድሬዎች እና የለውጥ ሃዋርያ ብሎ ራሱን የሚጠራው የወጣት አባላት ቡድን በድርጅቱ ውስጥ ያገረሸውን የለውጥ ጥያቄ ተከትሎ በብኣዴን ውስጥ እየተነሳ ስላለው የፖለቲካ መብት ጥያቄ በሰፊው ውይይት የተደረገበት ሲሆን ብአዴን የኢሕኣዴግን መርሆ እንደጠበቀ ከሌሎች ድርጅቶች የበላይነት እና ጥገኝነት መላቀቅ አለበት በሚሉ እና ወደ […]

ጥያቄው የለውጥና የነጻነት ነው ። ለለውጥ እንትጋ !!! ነፃነታችን በጃችን ላይ ነው፡፤ !!!
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

አዎ የኛ የኢትዮጵያውያን ጥያቄ የግለሰቦች በስልጣን ወንበር ላይ መፈራረቅ ሳይሆን ጥያቂያችን የለውጥ ጥያቄ ነው። የፖለቲካ አስተዳደር ለውጥ የኑሮ ውድነት የሚያላቅቅ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ለውጥ በጋራ ህብረተሰባዊነት ላይ የተመሰረት የማህበራዊ ፍትህ እኩልነት ለውጥ የነጻነት እና የመብት ማግኘት ጥያቄ በሃገራችን ተዘዋውረን በፈለግነው ቦታ የመስራት እና የመኖር ጥያቄ የመሳሰሉት ለውጦች በሃገራችን ላይ የሃገራችን ባለቤቶች ስንሆን የ ሚገኘው ብልጽግና እና እድገት ባለቤት መሆናችንን የሚያረጋግጥልን ለውጥ እንፈልጋለን፡፡

የጉልቻ መለዋወጥ ከሆነ እንደ ለውጥ የሚታየው በኢትዮጵያውያን የ እለት ከእለት የሕይወት ሂደት ውስጥ ድህነት እና ነጻነት ማጣት እንጂ ምንም አይነት የፈየደው ነገር አለመኖሩን ከሃይለስላሴ ጀምሮ ያየነው ነው፤ መንግስቱ ሓ/ማርያም መጣ ሄደ መለስ ዜናዊ መጣ ሄደ አሁንም ጠቅላይ ተብሎ ተሾመልን ይህም ጉልቻውን ለፖለቲካ ማጣፈጫ ሆነ እንጂ እንኳን ሊያስተዳድረን ይቅር እና የገዛ አንገቱን እንኳን ማዘዝ አልቻለም፤ ታዲአ የዜጎችን የለውጥ ጥያቄ ጉልቻ በመለዋወጥ መመለስ እንደማይቻል በይፋ እያየነው ነው፡፡

የኛ የለውጥ ጥያቄ የህዝቦችን የዜግነት መብቶች የሚያረጋግጥ እንጂ በውጭው አለም እና በሃገር ውስጥ ብሄራዊ ውርደት የሚያከናንብ አስተዳደር አይደለም፤ የኛ የለውጥ ጥያቄ በተስኪያናችንን እና መስኪዳችን እንዲሁም ታሪኮቻችንን የሚያረክስ የፖሊስ እና የጦር ሰራዊት ለውጥ ሳይሆን የነጻነት እና የመብት ጥያቂያችንን በህገመንግስት መሰረት የሚያስከብርልን አስተዳድር ነው፤ የኛ የለውጥ ጥያቄ በኑሮ ውድነት አደባይቶን በሙስና ጥቂት ሃብታም ብዙ ደሃ የሚፈጥር ዋሾ አስተዳደር አይደለም፡፤ የኛ የለውጥ ጥያቄ ህዝባዊ መሰረት ያለው ሚዲያ እንጂ በግምት የሚደሰኩር ውሸታም ሚዲያ አይደለም፡፤በአጠቃላይ የለውጥ ጥያቄያችን የባሰ እና የበሰበሰ መንግስት እንዲያስተዳድረን ሳይሆን እንደ ሃገር ባለቤትነታችን መብታችንን አስከብሮ በነጻነታችን እያኖረ ሃገራዊ ሃላፊነት እና ግዴታ እንዲሰማን የሚያደርግ መንግስት እንጂ የጉልቻ ተፈራራቂ አምባገነን ንግስና አይደለም፡፡

ኢትዮጵያውያን ለውጥ እንፈልጋለን ስንል የለውጥ ጥያቂያችንን መከለያ አድርጎ የስልጣን ጥሙን የሚያረካ የፖለቲካ ድርጅት እና የፖለቲካ ወያላ አንፈልግም፡፤ የኛን የለውጥ ጥያቄ ለፖለቲካ አጀንዳቸው ተጠቅመው ነጻነታችንን የሚያስነጥቁን የፖለቲካ ድርጅቶችን አንናፍቅም፡፤እኛ በፈረንጅ ቋንቋ የተገነባ የዲሞክራሲ ንግድ በነጻነታችን ላይ እንዲሰራፋ አንፈልግም። ኢትዮጵያውያን ነጻነታችን ያለው በፈረንጆች ሳይሆን በ እጃችን ላይ ስለሆነ እያንዳንዳችን ነጻነታችንን ለማስመለስ መረባረብ ግድ ይለናል። ጥያቂያችን የምእራብ ዲሞክራሲ ሳይሆን በነጻነት የመኖር ትያቄ ነው፡፤ ለለውጥ አሁንም እንጮሃለን። ፈረንጅ ለራሱ አጽድቆ ያራባውን ዲሞክራሲ ከነጻነት በኋላ እንደርስበታለን።

የዲሞክራሲ ትርጉም ቢገባንም ገዢዎቻችን ግን ለለበታ ስለሚጠቀሙበት በቋንቋችን ነጻነት ለውጥ እያልን እንዘምራለን፡፤ለለውጥ በጋራ በመነሳት ነጻነታችንን በትግላችን መቀናጀት ግድ ይለናል። በሃገራችን እና በነጻንትችን ላይ ባለቤቶች እንደሆንን ሃላፊነት ሊሰማን ስለሚገባ ነጻነታችንን ራሳችን ማረጋገጥ አለብን እንጂ የማንም ችሮታ እንዳልሆነ ተገንዝበን በጋራ ለለውጥ መነሳት ግዲታችን ነው። ነጻነታችን በ እጃችን ስለሆነ ዛሪውኑ ለማስመለስ እንትጋ።

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ተሰደደ።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

በተለያዩ ጋዜጦች፣ መፅሔቶች የራሱ “አዲስሚዲያ” ብሎግን ጨምሮ በተለያዩ ድህረ-ገፆች አዘጋጅ እና ፀሐፊ ጋዜጠኛ ብስራት ወ/ሚካኤል መሰደዱ ታወቀ፡፡ ጋዜጠኛው ቀደም ሲል የፍኖተ-ነፃነት ጋዜጣ አዘጋጅ፣የኢቦኒ መፅሔት ዋና አዘጋጅ፣ በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው ኢሳው መፅሔት ባልደረባና አምደኛ፤ በኢትዮ-ምህዳር ጋዜጣና በቅርቡ ወደህትመት የገባው ቀዳሚ ገፅ ጋዜጣ ላይም የተለያዩ የፖለቲካ፣ ሰብዓዊ መብት ጥሰትና ማኀበራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ በራሱና በብዕር ስም እንደሚፅፍ ይወቃል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የተመሰረተውና በመንግስት ከፍተኛ ቁጥጥርና ጫና ላይ የወደቀው የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) መስራች አባል፤ በኋላም የማኀበሩ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ በመሆን እያገለገለ እንደነበር ይታወቃል፡፡

ጋዜጠኛው ከዚህ በፊትም በመንግስት ደህንነት ኃይሎች በምሽት እገታ እንደገጠመው፣ ከስልክ ጠለፋ እስከ ዛቻና ማስፈራራት ይደርስበት እንደነበር ከዚህ ቀደም የወጡ መረጃዎች ቢያመለክቱም፤በተለይ ከጥቅምት 2006 ዓ.ም. ከአዲሱ ጋዜጠኞች ማኀበር መመስረት ሂደት ጀምሮ እና በሚያዚያ ወር 2006 ዓ.ም. 3 ጋዜጠኞችን እና 6 የዞን 9 ብሎገሮች በመንግስት ከታሰሩ በኋላ የመንግስት ደህንነቶች ክትትል ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉንና ቀጣዩ እስር እሱ ላይም ሊፈፀም እንደሚችል በመረዳት ለቅርብ ጓደኞቹ አሳውቆ ነበር፡፡

ብስራት ባለፈው ነሐሴ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. አርብ ጠዋት አዲስ ባወጣው የስልክ መስመር የማዕከላዊ ስልክ ጥሪ ካስተናገደ በኋላ ለጊዜው ከአዲስ አበባ ውጭ መሆኑን በማሳወቅ ለሰኞ እንደሚቀርብ ምላሽ ከሰጠ በኋላ ባለፈው እሁድ ድንገት ሀገር ጥሎ መሰደዱ ታውቋል፡፡

በቅርቡ ከታሰሩት ጋዜጠኞችና ብሎገሮች የእስር ስም ዝርዝር ውስጥ የማኀበሩ አመራሮች መኖራቸውና በቀጣይም መንግስት በአመራሮቹ ዙሪያ መረጃ እየሰበሰበ መሆኑ ምንጮች አረጋግጠው እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ቀደም ሲል የማኀበሩ ፕሬዘዳንት ጋዜጠኛ በትረ ያዕቆብ፣ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ጋዜጠኛ ዘሪሁን ሙሉጌታ፣ ገንዘብ ያዥ ጋዜጠኛ ሃብታሙ ስዩም እና መስራች አባል ጋዜጠኛ ተሰማ ደሳለኝ መሰደዳቸው አይዘነጋም፡፡ በአጠቃላይ ጋዜጠኛ ብስራት ወ/ሚካኤልን ጨምሮ በ2006 ዓ.ም. ብቻ 25 የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ሲሰደዱ፤3 የውጭ ዜጎች ጋዜጠኞችን ጨምሮ 20 ጋዜጠኞችና ብሎገሮች ደግሞ በእስር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

ኦሕዴድ ከኢህአዴግ ተለይቶ ራሱን የቻለ ፓርቲ እንዲሆን የሚፈልግ ቡድን ተነስቷል።

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
በዚህ በያዝነው ነሃሴ ወር ውስጥ ብቻ የሕወሓት/ብአዴን ከፍተኛ አመራሮች እና አንጋፋ ታጋዮች የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እና የደቡብ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅትን ባገለል እና ባላሳተፈ በተከታታይ የተደረጉ ተደራራቢ ስብሰባዎች በኦሕዴድ አመራሮች ዘንድ ጥያቄን ያጫረ ሲሆን በደሕዴግ አመራርች ዘድ ደሞ የዝምታ ድባብ እንዲያጠላ በማድረጉ በኢሕአዴግ ድርጅቶች መካከል በአዲስ መልኩ የውስጥ ፍጥጫ ማየሉን የድርጅቱ መረጃዎች ጠቁመዋል።

የኦሕዴድ አመራሮች በኢሕአዴግ ውስጥ የሚደረጉ ስብሰባዎች ለምንድነው የድርጅታችንን ሰዎች የሚያገሉት የሚሉ ጥያቄዎች ስእሞኑን ለሙክታር ከድር እና ለአባዱላ ገመዳ የቀረቡ ሲሆን እስከመቼ በሕዝብ ተተፍተን በሃይል ብቻ ለመኖር እንችላለን ኦሕዴድ ከኢህአዴግ ተለይቶ ራሱን የቻለ ፓርቲ በመሆን ተሃድሶ እንዲያደርግ ካልሆነ ድርጅቱ ከአንድ አካል የበላይነት የሚላቀቅበት መፍትሄ እንዲፈለግ ሲሉ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል።

በዚህ ወር ወስጥ ኢሕአዴግን ለማዳን በሚል የተለያዩ ስብሰባዎች በቀድሞ አንጋፋ ታጋዮች በሆኑት እና በሲቪል እና ውታደራዊ ስልጣን ላይ ባሉት የሕወሓት እና የብአዴን አመራሮች ተከታታይ ስብሰባዎች እየተደረጉ ሲሆ የወያኔው ጁንታ ዜጎች እየሰበሰበ በማሰር እና በሕዝቡ ዘንድ በሃሰት ፕሮፓጋንዳ እንድሁም ስም በማጥፋትና በተለያዩ እኩይ ተግባሮቹ በውጪም በውስጥም በደረሰበት የፖለቲካ ኪሳራ ለመጪው አመታት ሕዝቡን እንዴት አታሎ እና አጭበርብሮ መግዛት እንዳለበት እቅድ እያወጣ ሲሆን ለአዲስ አመት መጀመሪያም የኢሕአዴግ አመራሮችን ሰብስቦ መመሪያ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ወያኔ ሲፍረከረክ አጋጣሚዎችን መጠቀም እስካሁን ያልቻሉት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አሁንም በወያኔ ላይ የደረሰውን ኪሳራ ትጠቅመው አፋጣኝ የፖለቲካ ድሎችን በማስመዝገብ የበሰበሰውን ስርአት ወደ መቃብር እንዲወርድ ያላሰለስ ትግል ማድረግ አለባቸው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራል።

‹‹ጠበቆቻቸው በእየዕለቱ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመጣስ በሰፊ የፖለቲካ ዘመቻ የተጠመዱ ናቸው፡፡›› ገጽ 46
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

ባለፈው ሳምንት ለተማሪዎች በሚሰጠው ስልጠና ቴዲ አፍሮና ሰማያዊ አጀንዳ መሆናቸውን መግለጻችን ይታወሳል፡፡ በአሁኑ ወቅት ስልጠናው ወደ ሙስሊሙ እንቅስቃሴና የኮሚቴው ጠበቃዎች መዞሩን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሚሰጠው በዚህ ስልጠና የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊና መንግስት የሙስሊሙ ጉዳይ እልባት እንዲሰጥ የጠየቁ አካላት በአክራሪነት ፈርጇቸዋል፡፡ ‹‹የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ፈተናዎች›› በሚለው ሰነድ የሙስሊሙ ማህረሰብ እንቅስቃሴ ደም ለማፍሳሰስ እየጣረ እንደሚገኝ ይገልጻል፡፡

ከዚህም ባሻገር የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጠበቆች ከጥብቅና ይልቅ የፖለቲካ ስራ እንደሚሰሩ በሰነዱ ላይ ተጠቅሷል፡፡ በሰነዱ ገጽ 46 ላይ ‹‹ጠበቆቻቸው በእየ ዕለቱ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ በመጣስ በሰፊ የፖለቲካ ዘመቻ የተጠመዱ ናቸው፡፡›› ሲል ያትታል፡፡

ሰነዱ ለስርዓት ግንባታ እንቅፋት ናቸው የሚላቸው የሁለቱንም እምነት ተከታዮች ሲሆን ‹‹በክርስትናም ሆነ በእስልምና ሽፋን አገራዊ አጀንዳዎችን አስቀድመው ከሚፈታተኑን ኃይሎች ባልተናነሰ ደረጃ ደግሞ በሚያገኙት የገንዘብ ጥቅማጥቅም ተደልለው አገራችን የጀመረችውን የእኩልነት ጉዞ የሚያጥላሉ፣ ህገ መንግስታዊ ስርዓታችንን ጥላሸት የሚቀቡ ኃይሎች አሉ፡፡›› ሲል የሁለቱን እምነት ተከታዮች ይወቅሳል፡፡

ሰልጣኞቹ የላኩልንን የሰነዱ ክፍል እንደሚከተለው አያይዘነዋል፡፡
Image

A ban comes into force in the UK on Tuesday on the drug, khat, that is traditionally used by Ethiopian, Kenyan, Somali and Yemeni communities.

The British government says outlawing khat brings the UK into line with other European countries where it is a controlled substance.

However in Kenya’s khat-growing region, there is concern about the economic impact of the ban.

The BBC’s Anne Soy reports.
Read more http://betinews.com/?p=1354

Image

በቅርቡ የታጠቁ ግለሰቦች ከዶላር ጋር በተያያዘ በመሃል አዲስ አበባ በጠራራ ጸሃይ ሁለት ሚሊዮን ብር በመዝረፍ መሰወራቸውን ተከትሎ የተገኙ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ዘረፋውን የፈጸሙት ግለሰቦች በአቶ ጌታቸው እና በአቶ ኢሳያስ የሚመራው የደህንነት የማፊያ ቡድን አባላት መሆናቸው ታውቋል። እስካሁን በምርመራ ላይ ተብሎ ሌሎችን በመያዝ ካለወንጀላቸው ያሰረው ፖሊስ ከሳሾች የተባሉትን በመክሰስ እንዲሁም ከሳሾች ዘራፊ ግለሰቦቹ እነዚህ አይደሉም ቢሎም ፖሊስ ለመስማት ፈቃደኛ አልሆነም።

በመከላከያ ሰራዊት የሕወሓት መኮንኖች ስር የሰደደው የሙስና እና የዘረፋ አድራጎት በደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥም ከሹሙ ከአቶ ጌታቸው እና ከባለስልጣኖቻቸው ጀምሮ እስከ ገራፊዎች ድረስ መንሰራፋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል:: እንደውስጥ አዋቂ ምንጮቹ መረጃ ከሆነ የደህንነት ባለስልጣኖቹ የተዘፈቁበት የሙስና ተግባር በተጨማሪ ዘረፋን እና ሴት መድፈርን እንዲሁም የቡድን ወንጀሎችን ያካተተ መሆኑ ተጠቁሟል::በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ባለሃብቶችን በማስፈራራት ከፍርድ ቤት ትእዛዝ ውጪ በማሰር እንዲሁም የሙስና ወንጀል ተገኝቶብሃል ይህን ያህል ገንዘብ አምጣ ካላመጣህ እንገድልሃለን እስከማለት በከመድረሳቸውም በተጨማሪ ይህንን ጉዳይ ለፖሊስ የጠቆመ ባለሃብት በማፈን ንብረቱ ባማገድ እና በተለያዩ ስልቶች የተጠየቀውን ገንዘብ እንዲሰጥ በማስገደድ ላይ መሆናቸውን ምንጮቹ ጠቁመዋል::

ከዚህ ቀደም በሙስና የተከሰሱ የስርኣቱ ባለስልጣናትን ተገን በማደርግ በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ባለሃብቶችን በመከታተል እና ደህንነት ቢሮ ድረስ በመውሰድ በሙስና ከታሰረው ስም እየተጠቀሰ … ከሚባል ባለስልጣን ጋር ግንኙነት አለህ ማስረጃ ተገኝቶብሃል በማለት በፈጠራ ወንጀል ባለሃብቱን በመዝረፍ ስራ ላይ ተሰማርተው የነበረ እና እንዲሁም የአዲስ አበባን ቆነጃጅት ቢሯቸው ድረስ በግብረአበሮቻቸው አፋኝነት እና አስገዳጅነት በመውሰድ ካለፍላጎታቸው አስገድደው በመድፈር ላይ ናቸው ያሉት ምንጮቹ ተራ የደህንነት አባላት ለዚሁ ተልእኮ ተሰማርተው የሚሰሩት ምንም አይነት ወንጀል በቡድን ሲፈጽሙ የሚጠይቃቸው አለመኖሩን የሕዝቡን በደል የከፋ አድርጎታል::

ኢትዮጵያውያን በሕወሓቱ የደህንነት መዋቅር የሚመራ የሽብር ተግባራትን አጥብቆ ስለሚፈራ እና በየጊዜው በሕወሓት ደህንነቶች መሪነት የሚወሰዱ እርምጃዎች በሃገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ ስጋትን በመፍጠራቸው በየእስር ቤቱ የሚካሄዱ ሕገወጥ ጸረ ፍትህ ተግባራት እና የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች የኢትዮጵያውያን የቀን ተቀን አጀንዳ ሆነው መምጣታቸው ገዢው ፓርቲ ሕዝቡን ምን ያህል እንዳሸበረ ይጠቁማል ሲሉ ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል::
#ምንሊክሳልሳዊ

Image

ዜጎችን መታደግ የማይችሉ በአስቸኳይ ቆባቸውን አውልቀው ከተራው ሕዝብ የመቀላቀል ግዴታ አለባቸው።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

ቤተክርስቲያን እና መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ እጅና ጓንት ሆነው በኢትዮጵያውያን ላይ የማያባራ ጭቆና ማካሄድ ከጀመሩ ረዥም ዘመናት ተቆጥረዋል። ይብልጡኑ የመንግስቶች ጎህ ከቀደደ ጀምሮ በተለይ የተዋህዶ ሃይማኖት መሪዎች አስፈሪ እና አስደንጋጭ እንዲሁም አሳዛኝ ደግሞም አሳፋሪ ቃላቶችን በመጠቀም ስጋዊ እና ምድራዊ ስልጣኖችን ለገዢዎች ለማደላደል ይህ ነው የማይባል ግፍ በምእመናኖቻቸው እን በሌሎች አማኞች ላይ ፈጽመዋል አስፈጽመዋል፤ እየፈጸሙ ነው፤ እያስፈጸሙ ነው። ይህ የማይዋጥለት አሊያም የሚክድ ካለ እውነት የማይደላው ብቻ ነው።

የኢትዮጵያ ጨቋኝ መንግስታት የሆኑ ከጥንት እስከ ዛሬ የተንሰራፉ በህዝብ ላይ የሚያደርጉት ጭቆና እና በደል ታሪክ የማይሽረው ጠባሳ በሰው ልጆች የትውልድ ሂደት ላይ መፍጠሩ እንደተጠበቀ ሆኖ የሃይማኖቶች ሚና ግን እጅግ በሚያሳዝን መልኩ ዜጎች በግፍ በጨቋኝ መንግስቶች ሲታረዱ በመባረክ የመንግስታቱን እድሜ አስረዝመዋል አሁንም እያስረዘሙ ነው። የመንግስት እና የሃይማኖት ቁርኝት የሚፈለገው ስልጣንን አደላድሎ ለመያዝ እና ህዝብን ረግጦ ለመግዛት ካለ ምኞት እንጅ ለዜጎች ከመቆርቆር የመነጨ አይደለም። የሃይማኖት አባቶች በሃይማኖታዊ የመንፈስ ጥኡም ሰበካና ዜማ ጋር በማጣፈጥ የጨቋኞችን የበላይነት በመስበክ ማስፈራራት እና ማሸማቀቅ የጳጳሳት እና የሼህዎች አብይ ተግባር ነው።
በኢትዮጵያ ውስጥ ተገዝተው አሊያም አድርባይ ሆነው በመስራት ላይ ያሉ የሁሉም ሃይማኖት መሪዎች እጅግ ጥንቃቄ በጎደለው ሁኔታ በዜጎች ላይ የሚደርሱ ግድያዎች ድብደባዎች እስሮች እና መንገላታቶችን እንደ አንድ መንፈሳዊ የሃይማኖት መሪ እንደ ሰብአዊ ተፈጥሮ አሊያም መጽሃፋቸው እንደሚያዛቸው ለዚጎች ሲደራደሩ ሲከራከሩ ሲዋያዩ ሲሆንም አንተም ተው አንተም ተው ሲሉ አልታዩም ከዚህ በከፋ መልኩ በልማታዊ ዲሞክራሲ የፖለቲካ ፉጨት ስር ተደብቀው በለው በሚል አብዮታዊ ዜማ ዜጎችን እያስፈጁ ይገኛሉ።

አንድ የሃይማኖት አባት የታመመ ሲጠይቅ፤ የሞተ ሲቀብር ፤የተቸገር ሲረዳ ፤የታሰረ ዞሮ በመጎብኘት ሲያጽናና እንጂ ሲፖተልክ አሊያም ሲወሸክት ማየት ያማል። በሃገራችን ምእመናንን እንምራለን የሚሉ ሕዝብን መንፈስ እንመግባለን የሚሉ የለሊት ወፍ የሆኑ የክርስትና እና እስልምና የሃይማኖት መሪዎች ዜጎችን መታደግ የማይችሉ ከሆነ በአስቸኳይ ቆባቸውን አውልቀው ከተራው ሕዝብ መቀላቀል ግዴታ አለባቸው። ይህ ጉዳይ የብዙሃኑ የዜጎች ጉዳይ ስለሆነ ክርስቲያን እስላም የሚባልበት ሳይሆን የኢትዮጵያውያን የጋራ ጉዳይ ነው።

Image

በሃገሪቱ ዜጎች በአለም ላይ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በነጻነት በመጻፋቸው የእኩልነት እና የነጻነት ጥይቄ በማንሳታቸው ብቻ አሸባሪ ተብለው እስር ቤት በታጎሩባት ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስኪ ላስጠናው ላጥናው ያለ የሃይማኖት መሪም ይሁን የሃይማኖት ሃራጥቃ የለም። እንዲሁም በታሰሩ ሰዎች እና በአሳሪዎች መካከል እርቀ ሰላም እንዲወርድ ለወደፊቱ ስህተቶች ካሉ እንዳይደገሙ ነገሮችን ለማግባባት እና ለማቻቻል የፈቀደ አንድም የሃይማኖት መሪ የለም። ይብስኑ የሃይማኖት መሪዎቹ በየስብሰባው እና በየጭብጨባው ዜጎች የመንግስታዊ ሽብር ዱላ ሰለባ እንዲሆኑ እያበረታቱ ይገኛሉ ።

የዜጎች ሁኔታ ያሳሰባቸው የሃይማኖት መሪዎች በከፍተኛ ዛቻ እና ማስፈራራት እንዲሁም በጥቅም በማሰር እንዳይንቀሳቀሱ አሊያም በተዘዋዋሪ ባልሰሩት ወንጀል ለማጥመድ ሴራ በመጎንጎን እያስፈራሩ የህዝቦችን የሰብ አዊ መብት ጥያቄዎች እንዳያነሱ በማስደንገጥ እንዲሁም በጥቅማ ጥቅም እና በገንዘብ በመደለል አባትነታቸውን ለስጋዊ ባለስልጣናት እንዲሸጡ እና የፖለቲካ ምንዝር እንዲፍጽሙ እየተደረገ ሲገኝ ይህንን የምንዝር ጌጥ ከመለማመዳቸው የመጣ የሃይማኖት አባቶች ከጨቋኞች ብሰው በሕዝብ ላይ ከፍተኛ በደል እንዲፈስም ከባዱን ሚና እየተቻውቱ ይገኛሉ ።

የሃይማኖት አባቶች ሰጥ ለጥ ብለው ስለልማት ብቻ እንዲሰብኩ የእስላሙንም ሆነ የክርስቲያኑን ጥያቄዎች በተገኙበት እንድያስተጋቡ ማስጠንቀቂያ ከተሰጣቸው አባቶች መካከል አቡነ ማትያስ አቡነ ሉቃስ እና ሌሎችም ተጠቃሾች ናቸው እንዲሁም የወያኔ መንግስት በቅርቡ ለሾማቸው የእስልምና ምክር ቢት ሼሆችን ከፍተኛ የሆነ ምክር አዘል ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል። እኔ ስጨፈጭፍ እናንተ አጨብጭቡ የሚለው አሸባሪው የወያኒ መንግስት ሃይማኖቶችን በራሱ አይዲኦሎጂ በመቀጽ ቀሚሳቸውን ያንዥረገጉ ሰላዮችን እና የሃይማኖት ነቅእዞችን በመመደብ ዜጎችን በተመለከተ የሚደርሱ በደሎች እና ገፈፋዎች ጠያቂ እንዳያገኙ አስታራቂ እንዳይሹ አድርጓል። ፓትርያርኩ ተንገላተው ከተለቀቁ በኋላ በማህበራዊ ድህረገጾች ላይ ብዕራቸው ለምን ታቀበ? ከፋሲካ ክብረ በአል በኋላ በትዊተር ላይ እንዳልተገኙ የሚነገርላቸው ፓትርያርኩ ራሳቸውን ከማንኛውም አንደፋዳፊ ንግግር በመቆጠብ በተረጋጋ መልኩ አንገታቸውን እንዲሰብሩ እና በቅርባቸው ለተመደቡላቸው የመንግስት ደህንነቶች /አማካሪዎች ተገዢ እንዲሆኑ ተደርጓል።

ዜጎቹን የማይታደግ የሃይማኖት መሪ ቆቡን አውልቆ ከፖለቲካው ጎላ ልኢቀላቀል አሊያም ገለልተኛ ሰው ሆኖ እንዲቀመጥ ለመምከር እንፈልጋለን ። በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሃይምኖቶች ለመንግስታዊ ሽብር ተገዢ እና ታዛዥ እንዲሁም የሽብር ሰባኪ ሆነው ዜጎችን በአደባባይ እያስግደሉ ዜጎች ከሞቱ በኋላ በሃይማኖታቸው ስር አት እና ደንብ እንዳይቀበሩ ተጽእኖ በማድረግ ለምድራዊው የጨቋኝ ምደብ ተባባሪ እና አስተባባሪ በመሆን ከባድ ወንጀል እየፈጸሙ ይገኛሉ። ስለዚህ በዜጎች ላይ የሚደርሱ በደሎች የማይቆረቁራቸው የሃይማኖት አባቶች ሊወገዱ ይገባል።
http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … st_18.html
ማሳሰቢያ ፦ በዛሬው እለት በኦርቶዶክስ በእስልምና በካቶሊክ እና ከመካነ እየሱስ ቤተክርስቲያን የተዘዋወረው የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ቡድን ያሰባሰበውን ጉድ የያዘ መረጃ በቅርቡ በይፋ እናወጣዋለን ይጠብቁን።

“ሰዎቹ ለፖለቲካ ትርፍ ማስገኛ መጠቀሚያ እየሆኑ ነው::” የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር

ባለፈው ዓመት ለዓመታት ከኖሩበትና ሀብት ንብረት ካፈሩበት መኖሪያቸው እንደተፈናቀሉ በመግለጽ ይህን ተግባር ፈጽመዋል፣ አስፈጽመዋል ባሏቸው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴርና በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ቡለል ወረዳ ላይ ተፈናቃዮቹ በተወካዮቻቸው በኩል ክስ መስርተዋል፡፡

በዚህ መሰረት ዛሬ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ 8ኛ ፍትሃ ብሄር ምድብ በዋለው ችሎት የክስ መዝገቡ ተሰምቷል፡፡ ተፈናቃዮቹ በጠበቃቸው በዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም አማካኝነት እየተመሩ ክሱን እንዲያስኬዱላቸው ቄስ መስፍን አስፋውንና አቶ አቻምየለው ደሴን ወክለው አቤቱታቸውን ለፍርድ ቤቱ አሰምተዋል፡፡

ከሳሾቹ ከ15-20 ዓመታት ከኖሩበት ስፍራ ቤት ንብረታቸውን ጥለው እንዲፈናቀሉ መደረጋቸውንና ይህም ህገ-መንግስታዊ መብታቸውን በመጣስ ወንጀል እንደተፈጸመባቸው አስረድተዋል፡፡ ክሱ የቀረበባቸው የፌደራል ጉዳዮችና የቡለል ወረዳም መልስ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከሳሾቹ ይኖሩበት በነበረው ቦታ ቤት ንብረት አላፈሩም፤ ሰዎቹ ለፖለቲካ ትርፍ ማስገኛ መጠቀሚያ እየሆኑ ነው ሲል ለችሎቱ አስረድቷል፡፡
የቡለል ወረዳ በበኩሉ ከሳሾቹ በወንጀል የሚፈለጉ እንደሆኑ ጠቅሷል፡፡ ችሎቹ ግራ ቀኙን አዳምጦ ሶስቱም አካላት ለክርክር ቀጠሮ ሰኔ 30 ድጋሜ ችሎት ፊት እንዲቀርቡ ወስኗል፡፡

ይህን የፍርድ ሂደት ለማስጀመር ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ላይ ባካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የዜጎችን ከአመታት ከኖሩበት ቀየ መፈናቀል በማውገዝ ጉዳዩን ወደ ህግ ለማቅረብ ቃል በገባው መሰረት የተፈናቃዮችን ሁኔታ ቦታው ድረስ በመሄድና በመከታተል ለአሁኑ የህግ ሂደት እንዲደርስ ማስቻሉን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ገልጸዋል፡፡ አሁንም ፓርቲው አጠቃላይ የፍረድ ሂደቱን በቅርበት እንደሚከታተል አቶ ዮናታን ጨምረው አስረድተዋል፡፡

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

እርስ በርስ መካሰስ፣ መጠላላት፣ መበላላት፣ የሌላውን ታሪክ ማጉደፍ፣ የሌሎችን ሰብዓዊ ክብር መንካትና ማዋረድ እንደ ጀብዱና አሸናፊነት በሚቆጠርበት፣ ጥላቻ፣ ጽንፈኝነትና መለያየት የአገራችን ፖለቲካ ፓርቲዎችና ፖለቲከኞቻችን ልዩ መለያ ሆኖአል፡፡

ኢትዮጵያን ወደ አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ ያሻግራል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት ተማሪ፣ ገበሬ፣ ወታደር፣ ምሑር፣ወዘተ በነቂስ ሆ ብሎ የተሳተፈበት አብዮት በአገራችን ላይ ጥሎት ያለፈው ጠባሳ እጅግ ከባድና መራር ነበር፡፡ እስከ አሁንም ድረስ በዚያን ዘመን ትውልድ አባላት ለውጥ አራማጆች ላይ የፈጠረው የልዩነት ገደል፣ ጥላቻና መራርነት ሳይናድ እዚህ ዘመን ላይ ደርሰናል፡፡

የትናንት ትውልድ አባል የሆኑት አብዛኛው የዛሬዎቹ ፖለቲከኞቻችን የብዙ ወገኖቻቸውን ክቡር ሕይወት የቀጠፈውንና አገሪቷን ወደ አሰቃቂ እልቂትና ፍጅት የመራውን ፖለቲካዊ ቀውስ አስመልክቶ ይቅር ለመባባልና እርቅ ለማውረድ ከወሬ ባለፈ ተግባራዊ የሆነ እንቅስቃሴ ለማድረግ አልደፈሩም፡፡ ዛሬም ቢሆን ትናንት በአገራችን ላይ ለተከሰተው ሰብዓዊ እልቂት፣ ኢኮኖሚያዊ ውድመትና ማኅበራዊ ምስቅልቅል አንዱ አንዱን ተጠያቂ የማድረግ አባዜ ነው ጎልቶ የሚታየው፡፡

የፍቅርን፣ የሰላምንና የዕርቅን ባንዲራ ከፍ አድርጎ በማውለብለብ የኢትዮጵያችንን የዘመናት ፖለቲካዊ ስብራቷንና እያመረቀዘ ያስቸገራትን የቂም በቀልና የጥላቻ ቁስሏ ይሽር ዘንድ የፍቅርንና የይቅርታን ዘይት የሚያፈስላት እንደ ማንዴላ ያለ ብሔራዊ የፍቅር ጀግና ለማግኘት ገና አልታደለችም፡፡ እናም ያልሻረ ቁስሏን፣ ያልተፈወሰ ሕመሟንና ያልተጠገነ ስብሯቷን ይዛ በማንከስ እናት ኢትዮጵያ በእኛም ዘመን ወንድም ወንድሙን ትናንት በተፈጸመ ታሪክ ለበቀልና ለሞት የሚፈላለጉባት ምድር ሆና ዘልቃለች፡፡

በጥላቻ፣ በቂም በቀለኝነትና በጽንፈኝነት እግረ ሙቅ ውስጥ ለወደቀው የአገራችን ፖለቲካ መፍትሔው ከልብ የሆነና ከፍቅር የመነጨ ብሔራዊ እርቅ፣ መግባባትና በግልጽ መነጋገር እንደሆነ በግሌ በእጅጉ አምናለሁ፡፡ ይህን ጹሑፍ ለመጻፍ የተነሳሁበት ዋነኛው ምክንያትም በገዢው ፓርቲም ሆነ በተቃዋሚ ፖለቲከኞቻችን መካከል ተቀራርቦ በመግባባት መነጋገር ይቻል ዘንድ፣የአንድ አገር ልጆች በሐሳብ ልዩነትና ፖለቲካዊ አመለካከት ምክንያት በጠላትነት የምንፈራረጅበት የጨለማው ታሪክ ዘመናችን ያበቃ ዘንድ በመመኘት ነው፡፡

አሁንም ድረስ የአገራችን ፖለቲካ በጥላቻና በጽንፈኝት ሥር ወድቆ የሚማቅቅ መሆኑን ከበቂ በላይ የሆኑ ማሰረጃዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ በዕርቅና በፍቅር መንገድ ሊነሱ ቀና ቀና ያሉትንም ባለ ራዕዮች ከጠላቶቻቸው ቀድመው ወዳጆቻቸው ነን የሚሉት ራዕያቸውን አምክነው፣ ተስፋቸውን አድብዝዘው ከትግሉ መድረክ ገፍተዋቸዋል፡፡ እናም ዛሬም ድረስ የአገራችን የፖለቲካ ሰማይ ካረገዘው ከጥላቻ፣ ከጽንፈኝነትና ከቂም በቀል የጸዳ ለማድረግ ገና ከፊታችን እልህ አስጨራሽ የሆነ ረጅም ጉዞ የሚቀረን ይመስለኛል፡፡

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) :- የመንግስት ሹመኞችና ባለሟሎቹ የሙስናን በሽታውን ወደ ሕዝብ ነዝተውታል፡፡ ነጋዴው ማህበረሰብ እንደወትሮው ወጭ ገቢውን የሚያሰላው ከቀጥተኛ ወጭው ጋር ያተያያዘውን ግዢና ግብር ብቻ አይደለም፡፡ የቀን ጅብ ለሆኑ ሙሰኞች የሚሰጠውን ኮሚሽንና ውጣ ወረዱን ጭምር ነው። ………… ሕዝቡ የኑሮ ውድነት ከበደኝ! የእቃ ዋጋ ንረት አስመረረኝ! ግፍ በዛብኝ! ሸምቶ መቃመስ አቃኝ የሚል ምሬት ሲያሰማ.. ሹመኞች አፍ ለማስያዝንና ለማሸማቀቅ ይሽቀዳደማሉ፡፡ “በገበያ ስርዓት ነው የምንመራው የሚችል ይገዛል፡፡ ያልቻለ አይገዛም” ይባላል፡፡ ገፋ ሲልም “አጭበርባሪ ነጋዴ ስናሳድድ አንገኝም!” የሚል ማበረታቻ አከል መልስ ለሕዝቡ ይሰጣል፡፡
የተረጋጋ የነበረውን የግብይይት ስርዓት ያለበቂ መነሻና ጥናት የዋጋ ጣራ በማወጅ፣ ውቅያኖሱን ደብድቦ አሳውን የሚረብሽ ፖሊሲ ይዘረጋል፡፡ አለመረጋጋቱን ታኮ ነጋዴው እጥረትን፣ የጥራት ችግርን፣ ቅሸባን፣ ሚዛን ማጓደልን አይነተኛ የስራውና የትርፉ መሰረት ያደርገዋል፡፡ ሕዝብ፤ ሙስና እየነዳ ላመጣው ግፍ ለዋጋ ንረት፣ ለኑሮ ውድነት፣ ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውስ ተዳርጓል፡፡
http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … -post.html

መጪው ጊዜ ለወያኔ ጨለማ ሆኖቦታል። መላ ሃገሪቱን በስለላ መረብ አጥሮታል።

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
የሃገሪቱ ግማሽ በጀት ላፓርላማቸው ሳያሳውቁ ለደህንነት እና ለስለላ ተግባር መድበዋል።
በአራት ቡድኖች ተከፍሎ በከፍተኛ የሕወሃት አመራሮች የሚመራ የደህንነት ቡድን በአገሪቱ በአዲስ መዋቅር ስራ መጀመሩን መረጃዎች ጠቁመዋል ፤ ኢሕአዴግ ውስጥ በተነሳው የብሩህ ተስፋ ክሽፈት የመጣ በባለስልጣናቱ ዘንድ ከፍተኛ የሆነ ድንጋጤ መከሰቱን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ውጥረት አመራሮችን አጣብቂኝ ውስጥ ከቷቸዋል። ባለፉት 23 አመታት በህዝብ እና በሃገር ላይ የተደረገው ከፍተኛ የሆነ በደል እና ዘረፋ በሕዝቡ ዘንድ ጥርስ እንዳስነከሰባቸው እና መጪው ጊዜ ይጨልምብናል ብለው ከፍተኛ ስጋት ስላደረባቸው በአራት ቡድኖች የተከፋፈለ በሕወሓት ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ እና በመላው ሃገሪቱ የተበተነ የድህንነት እና የስለላ ሃይል ማሰማራታቸው ታውቋል።

በአራት ቡድኖች ተከፍሎ በከፍተኛ የሕወሃት አመራሮች የሚመራ የደህንነት ቡድን በአገሪቱ በአዲስ መዋቅር ስራ የጀመረው በየአከባቢው ከመንደር እና ቀበሌ ጀምሮ እስከ ከተሞች የገጠር ወረዳዎች ዘልቆ በመግባት በወያኔ ላይ ደባ ይሰራሉ ይፈጸማሉ ይመከራሉ የተባሉ እያንዳንዱን የዜጎች እንቅስቃሴዎች ሪፖርቶችን በትጋት በመሰብሰብ ወደ መሃል አገር በመላክ መታፈን ያለባቸው መገደል ያለባቸው ደብዛቸው መጥፋት ያለባቸውን ሰዎች በተመለከተ ከበላይ በሚተላለፍለት ትእዛዝ መሰረት መፈጸም ዋናው ስራው ነው። ይህ የደህንነት እና የስለላ መዋቅር ከመሃል ሃገር ተነስቶ እስከ ኬንያ ዩጋንዳ የኤርትራ ደጋማ አከባቢዎች ደቡብ ሱዳን እና ሱዳን ጅቡቲ እና ሰሜን ሱማሊያን ያጠቃልላል።

ወያኔ የሚጠራው መጪው ምርጫ ሕዝቡ በ1997 እንዳደረገው አሁንም እንዲሁ ቂሙን በካርድ ይገልጽብናል በማለት የሚሰጋው ወያኔ መጪውን ምርጫ ተከትሎ ሊመጣ የሚችለውን ተቃውሞ ከፍተኛ የሆነ የሃይል እርምጃ በመጠቀም ለማክሸፍ የሚያስችለው በየትኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ሊሆን እንደሚችል ስለላውን ተያይዞታል፡፤

አራቱ የደህንንት እና የስለላ ቡድኖችን የሚመሩት ከፍተኛ የሕወሓት አመራሮች የደህንነት ሹሞቹ ጌታቸው እና ኢሳያስ በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለውን እና በጎረቤት አገሮች ያለውን በደብረጺሆን ገብረሚካኤል የሚመራው ቡድን በደቡብ ኢትዮጵያ በብርጋዴር ጄኔራል ተክለብርሃን የሚመራው ቡድን በምእራብ ኢትዮጵያ እንዲሁም ባለፈው አውስትራሊያ ውስጥ በቡጢ የተዘረሩት አለቃ ጸጋዪ የሰሜኑን ክፍል እና የኤርትራ ደጋማ አከባቢዎችን የደህንነት እና የስለላ መዋቅር ለመምራት ከፍተኛ ገንዘብ ለስልጣን ማቆያቸው በመመደብ የገቡበትን ውጥረት ለማኮላሸት እየሰሩ መሆኑን ታውቋል።

በፓርቲው ውስጥ የሚነሱ ጥያቄዎች የካድሬዎች እንቢተኝነት የውጪ ሃይሎች ጫና የህዝብ እሮሮ እና አቤቱታ አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ወያኔ ማጣፊያው አጥሮት የሃገሪቱን ግማሽ በጀት የሚሆነውን ለደህንነት እና ለስለላ ተግብር በማዋል ከፍተኛ የሆነ አደጋ በሃገር ላይ አውጆ ሕዝብን እያሸበረ ይገኛል።

የመሪዎቻችንን የክስ መከላከያዎች ለማሰራጨት እንረባረብ!

ኡስታዝ አቡበክር አህመድና ዳዒ ያሲን ኑሩ ያቀረቡት የክስ መከላከያ በጽሁፍና በድምጽ ተዘጋጅቶ ከታች በሚገኙት ሊንኮች ቀርቧል

1.የኡስታዝ አቡበክር አህመድ ክስ መከላከያው የፒዲኤፍ ጽሁፍ ሊንክ፡-

http://goo.gl/NRSNki

የኡስታዝ አቡበክር አህመድ ክስ መከላከያው የድምጽ ትረካ ሊንክ፡-

http://goo.gl/RSPs2Q

2.የዳዒ ያሲን ኑሩክስ መከላከያው የፒዲኤፍ ጽሁፍ ሊንክ፡-

http://goo.gl/abVvpS

የዳዒ ያሲን ኑሩ ክስ መከላከያው የድምጽ ትረካ ሊንክ፡-

http://goo.gl/FucbrB

መጋቢት 24 አህመዲን ጀበልና ኡስታዝ ያሲን ኑሩ የቀረቡበት ልዩ ዘገባ
በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ሊንክ

http://goo.gl/7p9z81

መጋቢት 25 ኡስታዝ በድሩ ሁሴንና
ካሚል ሸምሱ የቀረቡበት ቢቢኤን ልዩ
ዘገባ በጣም አነስተኛ መጠን ያለው ሊንክ

http://goo.gl/TpX7ii

የመሪዎቻችንን የክስ መከላከያዎች
ለማሰራጨት እንረባረብ!
የመሪዎቻችንን የክስ መከላከያዎች ለማሰራጨት እንረባረብ!
to be continued ………..

Image

ጌታቸው ሽፈራው እንደጻፈው ፤- የመመረቂያ ጽሁፌን ለመጨረስ ደፋ ቀና እያልኩ ባለሁበት ወቅት ነው አንድ የማላውቀው ስልክ የተደወለልኝ፡፡ ይህ ስልክ አባል ባለመሆኔ ስራ እንደማላገኝ ተስፋ ወደመቁረጥ በተቃረብኩበት ወቅት ለስራ እንደምፈለግ አበሰረኝ፡፡ ስልኩ ከኢመድኤ (INSA) መሆኑ ተነግሮኛል፡፡

ይህን መስሪያ ቤት ስም ፈጽሞ ሰምቼው አላውቅም፡፡ ለጓደኞቼ ሳወራቸው ከእኔ በፊት አብዛኛዎቹ ተደውሎላቸው እንደነበር አጫወቱኝ፡፡ የህወሓት፣ የብአዴን፣ የኦህዴድ፣ የደኢህዴን ልጆች እርስ በእርሳቸው እንደተጠቋቆሙም ወሬ ደረሰኝ፡፡ በስተመጨረሻ እኔም መጠራቴ ነው፡፡ ሌላኛው ግራ የሚያጋባው ወሬ ግን መስሪያ ቤቱ የስለላ ተቋም እንደሆነ መስማቴ ነው፡፡ ሁለት ሆድ ሆንኩ፡፡ የኋላ ኋላ አይቶ መውጣቱ እንደሚሻል ወሰንኩ፡፡ አንድ በጣም የሚቀርበኝ ጓደኛዬ ስለተቋሙ ካጫወተኝ በኋላ እንዲቀጥሩኝ አባል መሆኔን (ሸውጄ) እንድነግራቸው አግባባኝ፡፡ አልፈለኩም፡፡

ለጥያቄ የተቀጠርንበት ቀን ደረሰ፡፡ ለፈተና ቀረብን፡፡ ጥያቄዎቹ ከጠበቅናቸው በላይ ናቸው፡፡ ከጠበቁት በላይ ስለ ኢትዮጵያ አንድነት በርካታ ጥያቄዎች ቀርበውልኛል፡፡ ከዚህ መርህ ያፈነግጣሉ የተባሉ ጓደኞቻችን ሳያልፉ ቀርተዋል፡፡ ፈተናውን አልፈን ለስልጠና በገባንበት ወቅት ደግሞ ሌላ ተስፋ ሰጭ ጉዳይ ተከሰተ፡፡ በነጻነት መከራከር ቻልን፡፡ በአንድ ትምህርት ዘርፍ (ፖለቲካል ሳይንስ) ለቅጥር ያለፍነው 12 ወጣቶች ሌሎቹን እንድናስተባብር በየ ውይይት ክበቡ ተሰባጠርን፡፡ ኢንሳን ብቻ ሳይሆን ፖለቲካውን የሚርቁትን ይቀይራሉ ተብለንም ‹‹12ቱ ሐዋሪያት›› የሚል ስም ወጣልን፡፡ በኋላ አንዷ የውጭ አገር እድል አግኝታ ስትወጣ ‹‹ይሁዳዋ!›› ብለን ተሳልቀንባታል፡፡ ይሁዳ ያወቀው ይህኔ ነው፡፡ ነገር ሳይበላሽና ሳይቆስሉ ቦታ መያዝን የመሰለ ነገር የለም፡፡

ስልጠናውን ጨርሰን ለአንድ አመት ያህል በነጻነት ሰራን፡፡ የማንኛውም ፖለቲካ ፓርቲ አባል መሆን ይቻላል፡፡ ነገር ግን ይህ አቋም ስራ ላይ ማንጸባረቅ አይፈቀድም ተባልን፡፡ ይህ ለእኛ ትልቅ ነገር ነበር፡፡ አሁን አሁን ሳስበው ግን ለኢንሳዎች ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ ማለት ኢዴፓ ብቻ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ምክንያቱም አንዱ ‹‹አለቃ›› ስለጉዳዩ ተናግሮ ሳይጨርስ ‹‹ይህን ስል ግን የኢዴፓን አቋም እዚህ (ስራ) ላይ ማንጸባረቅ ይቻላል ማለት አይደለም፡፡›› ሲል አስታውላለሁ፡፡

ብቻ ያ ጊዜ ለመስሪያ ቤቱ መልካም አመለካከት የነበረን ጊዜ ነው፡፡ ጅራትና ምንድን ነበር ወደኋላ የሚመጣው? በእርግጥ ከዚህ በፊት ኢንሳ ጠለፋና ሌሎቹንም ነገሮች እንደሚሰራ መስማት ጀመረናል፡፡ ስለ ጉዳዩ እርግጠኛ ባንሆንም የት ነው የምትሰራው ተብሎ ‹‹ኢንሳ!›› ለማለት የሚያኮራ አልነበረም፡፡ ብዙዎቹ ጓደኞቻችን ‹‹ሰላይ!›› እንመስላቸው ነበር፡፡ የእኛ አገር ችግር ይህ ነው፡፡ ስለላን ገዥዎች አበላሸተውታል፡፡ ህዝቡም ሆነ ሰላይን መልሶ መሰለል የሚባል ነገር አያውቅም፡፡ ዝም ብሎ መራቅ፡፡ ዝም ብሎ ማማት ብቻ ነው፡፡
አሁን ጅራትና ጉድ ጭራሹን እየፈጠጡ መጡ፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ አባል መሆን አትችሉም ተባለ፡፡ መጀመሪያ የነበረን ተስፋ ሁሉ እንደገና ተስፋ አጣ፡፡ ይህ በሆነበት ወቅት ነው፣ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ እንደ አንዳች ክፉ ነገር የሚጠሉትና የሚጠየፉት አቶ መለስ ሰንደቅ አላማውን ከላይ ወደታች ገለበጡት፡፡

እኔም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ‹‹ሰውዬው ለምን ሰንደቅ አላማውን ገለበጡት?›› የሚል ጥያቄ አነሳሁ፡፡ ከቀናት በኋላ ይህን ሰንደቅ አላማው ላይ የጻፍኩትን ትንሽዬ ነገር ተከትሎ 12 አስቂኝ ከስሶች ቀረቡብኝ፡፡ አብዛኛዎቹ ህገ መንግስቱን ካለመቀበል፣ የፖለቲካ ቡድኖች (እነማን እንደሆኑ እነሱው ይወቁት) አባል ሆነሃል እና ጽንፈኝነት ጋር የተለነቀጡ ናቸው፡፡ በዝርዝር የአሰብ ወደብን የኢትጵያ ነው ብለሃል፣ ኢትዮጵያ የውጭ ብድር አለባት ብለሃል፣ የጋዳፊን ፎቶ ግራፍ አጋርተሃል (ሸር አደርገሃል)፣ ከጉራፈርዳ ስለተባረሩት አርሶ አደሮች ጽፈሃል፣ ኢህአዴግን ግንባራም ብለሃል……የሚሉት ይገኙበታል፡፡

በእነዚህ ክሶች መሰረትም ለ2 ወራት ያህል ከስራ ታገድኩ፡፡ በዚህ ወቅትም ለክሶቼ መልስ እንድሰጥ ታዝዣለሁ፡፡ እናም ክሱ እንዲነሳልኝ የክሶቹን ፍሬ ቢስነት ጠቅሼ ተከራከርኩ፡፡ አይ እኔ ሞኙ! ህግ በሌለበት፡፡ በዚህ ክርክር የዲስሊን ኮሚቴ አባል ናቸው የተባሉ የህወሓት አባላት ልክ እንደ ከሳሽ ‹‹እንዴት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ታንቋሽሻለህ›› የሚል ክስ አቅርበው ተከራክረውኛል፡፡ የብአዴን አባላት ደግሞ እነሱን ተከትለው አስተጋብተዋል፡፡ ያም ሆነ ይህ ‹‹በከፍተኛ ወንጀል›› ተባረርኩ፡፡ በዚህ ወቅት አንድ የብአዴን ካድሬ ያለኝ መቼም ሊረሳኝ አይችልም፡፡ የቅርብ አለቃዬ ስለነበር ስለ ነበረኝ ስነምግባር፣ ስለ ስራ አፈጻጸም፣ ክስ የተባሉት የማያስከስሱኝ መሆኑን ገልጬ መባረሬ አግባብ አለመሆኑን አሳወቁት፡፡ እሱም ‹‹ዋናው ታማኝ መሆን ነው፡፡›› ብሎኝ አረፈው፡፡ ኢህአዴግ ብትሆን አትባረርም ነበር ለማለት ነው፡፡ የሚገርመው ይህ ካድሬ ፌስ ቡክ ላይ እራሱን ፈላስፋ አድርጎ ስለነጻነትና ፍትህ ሲዛላብድ የሚውል መሆኑ ነው፡፡

ከተባረርኩ ከሳምንት በኋላ መሰናዘሪያን ተቀላቀልኩ፡፡ ከወራት በኋላ (ጥቅምት 20) ደግሞ አቶ መለስ የማይወዱት ሰንደቅ አላማ በዓል ተከበረ ተባለ፡፡ በእውኑ ግን ተከብረው የዋሉት ሟቹ ሰውዬ ናቸው፡፡ ጥቅምት 21 መሰናዘሪያ በፊት ገጽ አንድ ጽሁፍ (የእኔው ነው) ይዛ ወጣች፡፡ መለስ የገለበጡትን ሰንደቅ አላማ አንግባ ‹‹እውን ኢህአዴግ ሰንደቅ አላማውን ያከብረዋልን?›› የሚል ነው፡፡ መሰናዘሪያ በሳምንቱ አልተመለሰችም፡፡ አታሚው ኢህአዴጎችን ሰንደቅ አላማው ላይ የተጻፈው ጽሁፍ ስላስቆጣቸው እንዳያትም እንደነገሩት አስታወቀን፡፡ በቃ ዳግም ተባረርኩ ማለት ነው፡፡ አሁን ሌላ ስራ መፈለግ ይጠበቅብኛል፡፡ የኢንሳን ልምድ ሳሳይ ደግሞ በርካቶች ይበረግጋሉ፡፡ በግል ሚዲያው ብጽፍም በቋሚነት ለማሰራት አቅም አልነበራቸውም፡፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ከገዥው ፓርቲም በላይ ለሚዲያውም ሆነ ለሰራተኛው በዝባዥና ገዳዮች ሆነው አግቻቸዋለሁ፡፡

እንዲህ እንዲህ ስል ለሁለት አመት ያህል ቋሚ ስራ መፈለግ ነበረብኝ፡፡ አራት አመት ያህል ደግሞ ከቤተሰብ ጋር ተቆራርጫለሁ፡፡ 18 አመት ያህል አስተምራኝ፣ ስራ ይዠያለሁ ያልኳትን እናቴን እንዴት ተባርሬያለሁ ልበላት? በፖለቲካ አቋሜ ተባረርኩ ብላት ደግሞ ከዚህ ሁሉ የባሰ ይሆናል፡፡ እናም ዝም ብዬ ስራ ፍለጋ መኳተኑን ያዝኩት፡፡ መነኩሴዋን እናቴን አይኗን ሳላያት አራት አመት ሞላ፡፡ ዛሬ ነገ እሄዳለሁ ስል ቀኑ ነጎደ፡፡ ከዛሬ ነገ አግይቼ አይኗን አያታለሁ ያልኳት እናቴም እንደሳሳኋት፣ እሷም እንደሳሳች ለወዲያው ላንገናኝ ተለያየን፡፡ እናቴ አለፈች፡፡ ያለ አግባብ የተፈናቀልኩበትን ስራ ልይዝ፣ ከያዥኩ ከጥቂት ጊዜም በኋላ ‹‹ልረጋጋ!›› ላይ ታች ስል ለረዥም ጊዜ የተለየኋት እናቴ አመለጠችኝ፡፡

በእርግጥ እናቴ ወርቅን በባሌስትራ ከሚቀይሩት ወገን አይደለችም፡፡ መሬት አልሸጠችም፡፡ ህዝብን በጠባብ ማንነት አልከፋፈለችም፡፡ አገር አላስገነጠለችም፡፡ ሰንደቁን አላዋረደችም፣ አልዘቀዘቀችም፡፡ የህዝብ መብት አላፈነችም፡፡ የህዝብ ገንዘብ ወደ ውጭ አላሸሸችም፡፡ ንጹሃንን አልገደለችም፣ አላሰረችም፡፡ አላፈናቀለችም፡፡ እናቴ ንጹህ ነች፡፡ የእሷ ነፍስ የገነት ነፍስ ነች፡፡ ሌሎች ግን የሞት ሞታቸውን ሞተዋል፡፡ ትውልድም አጥንታቸውን እንደረገመ ይኖራል፡፡

እኔም እላለሁ፡፡ ሞት ማለት የሞት ሞት ሲሆን ነው፡፡ ይህን እናቴ አልሞተችውም፡፡ ምስኪኗ ወላጅ እናቴ የክብር ሞቷን ስትሞት አሁን ለእኔ የቀረኝ አንዲት እናት ብቻ ናት፡፡ እናት አገር ኢትዮጵያ! አገር ብትኖር ወላጅ እናቴ ተቀብራበታለች፡፡ እኔም አልቅሸበታለሁ፡፡ አዎ! ወላጅ እናት ባትሞት እጅጉን መልካም ነበር፡፡ ከሞተች ግን ምን ይደረጋል? ብቻ እናት አገር አትሙት!

እናቴ ሆይ! አምባገነኖቹ ፊቴ ላይ የደቀኑብኝን አቀበት ለመውጣት ስጥር አንቺ አምልጠሽኛል፡፡ አሁን ብችል እናት አገርን ለማዳን ከሌሎቹ ጋር ሆኜ ጠጠር ለመጣል፣ ጥረቴ ለዚህ ባይበቃ እንኳ የራሴን መብት ለማስከበር፣ ይህንን ደግሞ ባልችል ሆድ አደር ላለመሆን አቀበቱ ላይ ነኝ፡፡ ሞት አይቀርምና አንድ ቀን እንደምሞት አውቀዋለሁ፡፡ የሞት ሞት መሞት ግን አልፈልግም፡፡ ደግሞም ከአንቺ ጋር ያለያየኝን አቀበቱን ወጥቼ ሜዳው ሳልደርስ ባልከተልሽ ደስ ይለኛል፡፡ በዚህ አንቺም እንደማትቀየሚኝ አውቃለሁ፡፡ እስከዚያው ግን አምላክ ነፍስሽን በገነት ያኑራት!