የማቻርና የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ተደራዳሪ ልዑካኖች አዲስ አበባ ውስጥ በተናጠል ከሸምጋዩ ከምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት በእንግሊዘኛው ምህፃር IGAD ጋር እየተነጋገሩ ነው ። ቀጥተኛው ወይም የፊት ለፊቱ ንግግር ደግሞ ነገ ወይም ከነገ ወዲያ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል ።

የትብብሩ ሊቀመንበር አርቲስት ታማኝ በየነ ማህበሩ የጀመረው የገንዘብ ድጋፍ የማሰባሰብ እንቅስቃሴ በተቀናጀ መልኩ እንደሚቀጥል አስታውቋል ። በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የበኩላቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉም ጥሪ አቅርቧል ።

ወጣት ተዋናይ ነው፤ በተለይ «ቤቶች» በተሰኘው አስቂኝ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ላይ «ይበቃል» የተሰኘውን ገፀባሕሪ ወክሎ በመጫወት ዝናን አትርፏል። ወደ ፊት ዓየር ላይ በሚበቃው የዶቸቬለ ተከታታይ ድራማ ላይም ተሳታፊ ሆኗል።

ሶማሊያ መዲና መቅዲሾ በሚገኝ አንድ ሆቴል አጠገብ ትናንት ምሽት በተከታታይ በደረሱ የቦምብ ፍንዳታዎች የሞቱት ሰዎች ቁጥር ወደ 13 ከፍ ማለቱ ተዘግቧል ። ከሟቾቹ መካከል ፖሊሶችም ይገኙበታል ። የሶማሊያው ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አሸባብ ለጥቃቱ ሃላፊነቱን ወስዷል ።

የሳዉዲ መንግስት የሰጠዉ የምህረት አዋጅ የጊዜ ገደብ ካለቀ በኋላ በሪያድ መንፉአ በኢትዮጵያዉያን ላይ የሞትና የመቁሰል አደጋ ከደረሰ ወዲህ ሕጋዊ ሰነድ የሌላቸዉም ሆነ ካመጣቸዉ አሠሪ ጋ የማይሠሩ ማናቸዉም ዜጎች እንደህገወጥ እንደሚቆጠሩ በማሳሰብ፤

የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ተደራዳሪዎች ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ የሰላም ንግግር ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል ። አደራዳሪዎቹና ተደራዳሪዎቹ ግን ድርድር የሚጀምሩበትን ትክክለኛ ቀን እስካሁን በይፋ አላሳወቁም ።

የጎርጎሪዮሳዊውን የቀን ቀመር ለሚያሰሉ አዲስ ዓመት ማለትም 2014 ከጠባ ዛሬ ማግስቱ ነው። የአዲስ ዓመት በዓል ዋዜማ አቀባበልን በአውሮጳ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን እንዴት ይመለከቱታል? ከዝግጅቱ የምናገኘው ይሆናል።

ባለፈው ኅዳር 14 እና 15 ,2006 በለንደን ብሪታንያ፤ ኢትዮጵያውያን ምሁራን ባዘጋጁት ዓለም አቀፍ የዕውቀት ልውውጥ ነክ ጉባዔ ተሳትፈው ከተመለሱት አንዱ ናቸው። በጎንደር ዩንቨርስቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ፣ «ባዮ -ሜዲካል እና ላበራተሪ ት/

ማቸር ለመደራደር ፍቃደኛ ከመሆናቸዉ ጋር ተኩስ እንደማያቆሙ እንዳስታወቁ ሁሉ ፕሬዝዳት ሳልቫ ኪርም ዉጪ ጉዳይ ሚንስትራቸዉን ለድርድር ወደ አዲስ አበባ ከመላካቸዉ እኩል ሥልጣን እንዲለቁ ወይም አዲስ ምርጫ እንዲደረግ ተቃዋሚዎች ያቀረቡትን ሐሳብ ዉድቅ አድርገዉታል

ዛሬ እኩለ ለሊት የምንሸኘው የጎርጎሮሳውያኑ 2013 በአውሮፓ የሥራ አጡ ቁጥር ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ያሻቀበበት ፣ የወጣት ሥራ አጦችን ቁጥር ለመቀነስ የክፍለ ዓለሙ መሪዎች መፍትሄ ይሆናል ያሉትን ያቀዱበት ፣

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትኅ ፓርቲ አዲስ አበባ ውስጥ እሁድ ታኅሣሥ 20 ቀን፥ 2006 ዓም ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ኢንጅነር ግዛቸው ሽፈራውን በከፍተኛ ድምፅ የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጎ መርጧቸዋል።

ነገ አምና ለመባል የሰዓታት እድሜ የቀረዉ የጎርጎሪዮሳዊዉ የዘመን ቀመር 2013 የተለያዩ የተፈጥሮ ቁጣና አደጋዎችን አስተናግዷል። የመሬት መንቀጥቀጥ፤ ኃያል ማዕበልና ሞገዶች፤ ጎርፍና ድርቅ።

ዋሽግተን-ብራስልሶች በጋራ ሶሪያ ላይ የመዘዙትን ሰይፍ ካፎቱ የዶሉበት፣ የግብፅ የዴሞክራሲ ጭላንጭል፣ በመፈንቅለ መንግሥት፣ በዜጎቿ ደም አጥንት የተመረገበት። ባሜሪካኖች የተሾሙት፣ አሜሪካኖችን ለዓመታት በታማኝነት ያገለገሉት ሐሚድ ካርዛይ የዋሽግተኖችን ትዕዛዝ እንቢኝ ያሉበት ዓመትም ነዉ

በአሁኑ መንግሥት ሳንሱር ሲነሳ የግል ጋዜጦች ቁጥር ከፍ ቢልም በሂደት ግን ቁጥራቸው አሽቆልቁሎ አሁን በጣት የሚቆጠሩ ብቻ ቀርተዋል ፤ ከ1997 ምርጫ ወዲህ የጋዜጠኞች መከሰስ መታሰርና ከሀገር መሰደድ ተባብሷል ። ለዚህም በምክንያትነት የሚነሱት የሃገሪቱ የፕሬስና የፀረ ሽብር ሕግ ናቸው ።

በስዑዲ ዐረቢያ መዲና በሪያድ፤ በተለይም ማንፉህ በተባለው ቀበሌ ከሁለት ወር በፊት እንደሆነው ሁሉ፤ አሠሳ ፤ ከትናንት በስቲያ በጦር ሠራዊቱ ልዩ ኃይል የተጀመረ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ኤምባሲና ቆንስላ ጽ/ቤት ሕጋዊ የመኖሪያና የሥራ ፈቃድ የሌላቸው

የደቡብ ሱዳን ግጭት ዛሬም አልሰከነም። የቀድሞዉ ምክትል ፕሬዝደንት ሬክ ማቻር ታማኞች ማላካል የተባለችዉ የነዳጅ ዘይት ያለባት ግዛት ቁልፍ ከተማ ይዘናል ሲሉ ዛሬ ገልጸዋል። በተቃራኒዉ የመንግስት ኃይሎች የላይኛዌዉ ናይል ግዛት የሆነችዉ ከተማ ማላካል ከቁጥጥራችን አልወጣችም እያሉ ነዉ።

የግብፅ የሽግግር መንግስት የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበርን በአሸባሪነት ከፈረጀ በኋላ ዛሬ ለተቃዉሞ የወጡ ደጋፊዎቹ ከፖሊስ ጋ ተጋጭተዋል። ድንጋይ ይወረዉሩ እንደነበር የተገለጸዉን የቡድኑን ደጋፊዎች ለመበተንም ፖሊስ የሚያስለቅስ ጭስ ተጠቅሟል።

በምድራችን የሚኖረው ህዝብ ብዛት ከ 7 ቢሊዮን ቢበልጥ እንጂ እንደማያንስ የታወቀ ሆኖ ሳለ ፣ ላሁኑና ለመጪውም ዘመን ፤ በዝች ምድር የሰዎችን ህልውና እንዴት አስተማማኝ ማድረግ ይቻላል ? ለሚለው ጥያቄ መልሱ የሚያከራክርም የሚያነታርክም ሊሆን ይችላል?

የለጋዋን ሀገር ደቡብ ሱዳንን ወቅታዊ የግጭት ጦርነት ሁኔታ ለማርገብና ተፋላሚዎቹ የቀድሞዉ የደቡብ ሱዳን ነፃ አዉጭ ቡድን አመራሪዎች ለማስማማት ጥረቱ ቀጥሏል። እዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ለስጋትና ዘረፋ ተጋልጠዋል።

በደቡብ ክልል የቁጫ ብሄረሰብን በሚመለከት ተደጋጋሚ ችግር እንግልቶችና የሰዉ ህይወትም የጠፋበት በመሆኑ አሳሳቢ ደረጃ ደርሷል ሲል አንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ አስታወቀ። የፓርቲዉ አመራር አባላት አካባቢዉን ሄደዉ በመጎብኘትም ዘገባ አቅርበዋል።

ዓለም ሲያሳስብ፥ ሲያጠነቅቅ፥ ለዲፕሎማሲ ሲጠራራ፥ አፍሪቃ ጁባ ሲመላለስ፥ጁባ አስከሬኖቻን ቆጥራ፥ቀብራ ደሟን አድርቃ ሳታበቃ ቦር ተደገማለች። ድፍን የዩኒቲ ግዛት ቀጠለች። ጃግሌዬም አሰልሳለች።

በረዶዉ ቢጥል ኖሮ የበዓሉ አክባሪዎች «ነጩ ገና ይሉት ነበር።በቅፅሉ።ዘንድሮ ብዙ ቦታ ይሕ አልሆነም።የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ ዓየር ነፋስ፥ ዝናብ፥ አንዳዴም ወጀቦ ነዉ ያጠላበት።ድፍርስ ዓየር፥ ጭፍግግ ድባብ።ብሪታንያ ደግሞ ብሶባታል።እንግሊዝ ግን የበዓሉ ወግ አንድም አልቀረበትም።አበሻስ?«ሮም ስትሆን እንደ ሮሞች ሁን» ብሏል ነዉ-ያሉት አዋቂዉ።

በአዲስ አበባ በቦሌ ክፍለ ከተማ በመድሐኔዓለም ቤተክርስትያን ጀርባ ቤቶችና የመንገድ ሱቆች እየፈረሱ በመሆኑ ጉዳት የደረሰባቸው ነዋሪዎች በቂ ጊዜ ሳይሰጠን ተፈናቀልን ሲሉ ያማርራሉ።

በአዲስ አበባ በቦሌ ክፍለ ከተማ በመድሐኔዓለም ቤተክርስትያን ጀርባ ቤቶችና የመንገድ ሱቆች እየፈረሱ በመሆኑ ጉዳት የደረሰባቸው ነዋሪዎች በቂ ጊዜ ሳይሰጠን ተፈናቀልን ሲሉ ያማርራሉ።

የተቀሰቀሰው ግጭት በአስቸኳይ እንዲቆም ካልተደረገ ሀገሪቱ ወደ አስከፊ የእርስ በእርስ ጦርነት ልታመራ የምትችል መሆኑን በርካታ የዓለም ዓቀፍ የሠብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶችና የመንግሥታቱ ድርጅት ጽ/ቤት በማስጠንቀቅ ላይ ናቸው።

ከ 4 ዓመት ገደማ በፊት፤ ወደ ኢትዮጵያ የተጓዙ አንድ የኔልሰን ማንዴላ ድርጅት ዋና ተመራማሪ፤ ማንዴላን በማሠልጠን ያገዙ በሕይወት የሚገኙ ሰዎችን ሁሉ ጠይቀው ያሰባሰቡት መረጃ ፣ ማንዴላ ከእሥራኤላውያን ጋር ግንኑነት እንደነበራቸው የሚያረጋግጥ አንዳችም እውነታ አልተገኘበትም።

የሜዴትራንያንን ባህር አቋርጠው ወደ ኢጣልያ የሚገቡ ስደተኞች በተለይ በላምፔዱዛ ደሴት የሚፈፀምባቸው ሰብዓዊነት የጎደለው አያያዝ እዚህ አውሮፓ እያነጋገረ ነው ። በኢጣልያ የስደተኞችን መብት የሚጋፉ አያያዝ የመኖሩን ያህል በአንፃሩ ተፈላጊ የሆኑባቸው አካባቢዎችም አሉ ። የዛሬው አውሮፓና ጀርመን ዝግጅታችን ያስቃኘናል ።

የአየር ብክለት በአዉሮጳ ለበርካቶች ሕይወት መቀጠፍ ምክንያት መሆኑ እየተነገረ ነዉ። ዲ ቬልት የተሰኘዉ የጀርመኑ ታዋቂ ጋዜጣ በጎርጎሪዮሳዊዉ 2010 ዓ,ም በአዉሮጳ ሃገራት ጎዳናዎች ላይ በተለያዩ አደጋዎች የ35 ሺ ሰዎች ህይወት መጥፋቱን ሲያመለክት፤

በስዑድ አረቢያ ወደ80 ሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዉያን እጃቸዉን በሰላም እየሰጡ ወደሀገራቸዉ እንዲመለሱ መጠየቁ እየተነገረ ነዉ። ከጄዳ ቆንስላ እንደተነገረ የተጠቀሰዉን ማሳሰቢያ አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጡን ወደቆንስላዉ ባለስልጣናት ያደረግነዉ ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ምላሽ አላገኘም።

ከፖለቲካ ዲፕሎማሲዉ ይልቅ፥ ጠመንጃ ጦርነትን ያደጉ የኖሩበት ሳልቫ ኪር የዲንካን፥ እንደ ፖለቲከኛ-ሻጥርን፥ እንደ ዲፕሎማት ግድምድሞሽ ዘይቤን፥ እንደ ታጋይ የጫካ ዉጊያ አጣምረዉ የያዙት ዶክተር ሪክ ማቼር የኑዌር ጎሳን፥ ከየጎናቸዉ አሰልፈዉ ተፋጠዋል።

ኢትዮጵያዉያን እስራኤላዉያን ለዘመናት ወደናፈቋት እስራኤል በብዛት መሄድ ከጀመሩ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ሆኗል። እስከዛሬም ወደመቶ ሰላሳ ሺህ የሚበልጡ እስራኤል እንደገቡ ይታመናል።