ኢትዮጵያ ዉስጥ በHIV ቫይረስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየቀነሰ መሄዱ እየተነገረ ነዉ። በአንጻሩ የጸረ ኤድስ መድሃኒት የሚወስዱ HIV በደማቸዉ የሚገኝ ወገኖች ቁጥር መቀነሱ ተገልጿል። መድሃኒቱ ከተጀመረ መቋረጥ እንደማይኖርበት ነዉ ባለሙያዎች የሚያሳስቡት።

ጀርመን ከሌሎች የአውሮፓ ሃገራት በግንባር ቀደምትነት በዚህ ዓመት 5 ሺህ የሶሪያ ስደተኞችን ለመውሰድ ቃል ገብታለች ። በጀርመን ፌደራል መንግሥት የሃገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴታ ኦለ ሽሮደር እንደተናገሩት ጀርመን ከለላ የምትሰጠው ሰብዓዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሶሪያውያን ብቻ ነው ።

የቁጫ ሕዝብ ጥያቄ ሕጋዊ ምላሽ እንዲያገኝ ጥሪ እናቀርባለን!!! ከአንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ (አንድት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ፓርቲያችን አንድነት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆኑ ከሚታገልላቸውና ገዥው ፓርቲ ከወረቀት በዘለለ ያልተገበራቸው ሀገራዊ ቁምነገሮች ውስጥ ዜጎች ሳይሸማቀቁ በነፃነት ሃሳባቸውን የመግለፅ፣ በነጻነት የመደራጀት፣ በገዛ ሀገራቸው በነጻነት የመንቀሳቀስ፣ በፈለጉበት አከባቢ የመኖር፣ ሀሳባቸውንና አመለካከታቸውን በነጻነት የመግለጽ፣ የመደገፍ፣ የመቃወም፣ ስለመብታቸው ሳይሸማቀቁ የመጠየቅ […]

ግርማ ሠይፉ ማሩ

“የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ ለምን ያስፈራል?” በሚል ርዕስ ሪፖርተር ጋዜጣ በእሑድ ነሓሴ 5 ህትሙ ረጅም ፅሁፍ አሰነበቦናል። ፀሐፊው በቦነያ ሰ. በሚል አቶ/ወሪት/ወሮ ይሁን በማይታወቅ ስም ነው ያወጡት። ይዘቱን ሳነበው የምናውቃቸው የኢህአዴግ ሹሞች በብዕር ስም ልከውት ያው የኢህአዴግ አቋም ነው ብዬ ለመውሰድ ዝግጁ ሆኜ ንባቤን ሳጠናቅቅ፤ ፀሐፉው የሕግ ባለሞያ እንዲሁም በተለያየ የመንግሥትና መንግታስዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ በሙያቸው ሰርተዋል የሚለው የአዘጋጁ ማስታወሻ መልስ እንድሰጥ ጋበዘኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

ተመስገን ደሳለኝ

ኢህአዴግ ባለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት በስራ ላይ ካዋላቸው አዋጆች መካከል የ‹‹ፀረ-ሽብር ህጉ››ን ያህል ያጨቃጨቀ የለም ቢባል ከእውነቱ ብዙም አልራቀም፡፡ በርግጥ ከተቃውሞ አቅራቢው አብዛኛው በደፈናው ‹‹ህጉ አያስፈልግም›› የሚል አልነበረም፡፡ ህጉ ‹‹ሽብርተኝነት››ን የገለፀበት መንገድና አንዳንድ አንቀፆቹ ለትርጉም አሻሚ በመሆናቸው ከስርዓቱ ባህሪ አኳያ ለፖለቲካ ጥቅም የሚውሉበት ዕድል መኖሩ አይቀሬ ነው የሚል ስጋት ነበር፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  የቀድሞ ጠ/ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ሙት ዓመት በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ጉለሌ ዕጽዋት ማዕከል በልዩ ልዩ ፕሮግራም ታስቦ እንደሚውል ለማወቅ የታቸለ ሲሆን፣ በዛሬው እለት ደግሞ  የተለያዩ የመንግስት ሰራተኞች ምሽትና ነገ  ሻማ በማብራት እንዲዘክሩት ታዘዋል። አንዳንድ የመንግስት ሰራተኞች  ኢቲቪ አቶ መለስ ዜናዊ ከተናገራቸው ንግግሮች መካከል እያለ ሲያቀርብ መሰንበቱ …

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  በወረዳው የተነሳውን ከማንነት ጋር የተያያዘ ጥያቄ ለማፈን መንግስት የጀመረውን ዘመቻ በማጧጧፍ ለውጭ አገር ሚዲያ መረጃ ይሰጣሉ የተባሉትን የቁጫን ህዝብ በመወከል ሲከራከሩ የነበሩት መቶ አለቃ ማሴቢ ማዳልቾ፣ ባለፈው ቀድሜ ተይዘው ዛሬ ወደ አርባምንጭ ተልከዋል። በአጠቃላይ እየታደኑ ካሉት መካከል 12 አንጋፋና ታዋቂ ሰዎች ሲታሰሩ፣ 9ኙ የገቡበት  አልታወቀም። በወረዳው የተነሳውን …

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  ስምምነቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሞባይል ስርጭት ተጠቃሚ ወደ 50 ሚሊዮን ለማሳደግ የተደረገ ነው ተብሎአል። መንግስት ለዘርፉ ከመደበው 1 ቢሊዮን 600 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ ከፊሉን ለሌላው የቻይና ኩባንያ ሀዋይ መስጠቱ ታውቋል። ሁለቱም የቻይና ኩባንያዎች የመንግስትን የስልክና የሌሎች የመገናኛ መንገዶች ጠለፋ አቅም እንደሚያዳብሩለት ኢሳት ምንጮችን በመግለጽ መዘገቡ ይታወሳል። የኢህአዴግ …

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  “በሳምንት አንድ ቀን ውሃ ማግኘት ብርቅ የሆነባቸው ሰፈሮች፣ በውሃ እጦት አካባቢያቸውን በመጥፎ ጠረን የሚበክሉ የኮንዶሚኒየም መኖሪያዎች፣ ለተደጋጋሚ አቤቱታ ምላሽ ሳያገኙ በርካታ ወራት እየተቆጠሩ የሚማረሩ ነዋሪዎች የአዲስ አበባ የዘመኑ ገጽታ ሆነዋል” ሲል አዲስ አድማስ ዘገበ የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ” በቂ ውሃ ስለሌለ በራሽን ለማከፋፈል እየሞከረ” መሆኑን ገልጿል። ባለስልጣኑ …

ነሃሴ ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-  ታዋቂው ድምጻዊ እዮብ መኮንን በብስክሌት ላይ ሆኖ ሲጓዝ በመውደቁ ሆስፒታል ከገባ በሁዋላ በህክምና ሲረዳ ቆይቷል። አርቲስት እዮብ በባልደረቦቹ እርዳታ  ወደ ኬንያ በመሄድ ለአጭር ቀናት በህክምና ሲረዳ ቆይቷል። ኢሳት በአርቲስት እዮብ ሞት የተሰማውን ሀዘን ለመግለጽ ይወዳል።

 ሉሉ ከበደ (ደራሲና ጋዜጠኛ)

ሙስሊም ወንድሞቻችን ሁለት አመት ለሚጠጋ ጊዜ እየተገደሉ ነው።  በጽናት፤ በጀግንነትና በብልሀት እናም በመስዋእትነት የመብት ትግላቸውን ቀጥለዋል። በለተ – አውዳመት ኢድ አልፈጥርም የመስዋእትነት ደማቸውን፤ …ኢትዮያን የተቆጣጠራት የትግራይ ዱር አራዊት መንጋ አፍሷል። የሞቱትን ሁሉ አላህ በጀነት ነፍሳቸውን ያኑር ከማለት በቀር ምን ይባላል ?  ለሁሉም ወገኖቻችን ለቤተሰቦቻቸው፤ ለዘመዶቻቸው አላህ ጥናቱን ይስጥ እላለሁ። በከንቱ ለፈሰሰ ደማቸውም እሱ በማያልቅበት ስልጣኑ ፍርዱን ይስጥ። ሳይውል ሳያድር።…አላህ ሁ አክባር!!!

ሙሉውን አስነብበኝ …

በዓሉን የአካባቢው ተጨማሪ የቱሪስት መስሕብ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው መንፈሳዊ ይዘቱ እንዲጠፋ የሚሹ ግለሰቦች በበዓል ኮሚቴ መካተታቸው ቅር አሰኝቷል በበዓሉ አጋጣሚ ለቅ/ላሊበላ ደብር አስተዳደራዊ ችግር ትኩረት እንዲሰጥ ተጠይቋል የጾመ ፍልሰታ ለማርያምን ፍጻሜ ተከትሎ የሚከበረው የአሸንድዬ በዓል ከነገ ጀምሮ የዓለም አቀፍ ብርቅዬ ቅርስ ማእከልና የውብ ባህል መድረክ በኾነው ላሊበላ ከተማ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡ የቅዱስ ላሊበላ …

ግብፅ ጥይት፥ አረር፥ እየዘራች፥ አስከሬን-አጭዳ በእሳት ታጋያለች።ያቺ አስከሬን ለዝንታ-ዓለም የሚቀመጥባት ሐገር ዛሬ የሰዉ አካል ይተለተልባታል።ያቺ የጥንታዊ ሥልጣኔ ጎተራ፥ ያቺ የታሪካዊ የቅርስ ቋት፥ ያቺ ሥልታዊት ሐገር ታወረች? ወይስ አበደች? እዉሩ ወይም እብዱስ ማነዉ?

ኢቲዮ ቴሌኮም ፣ ከፊል የቴሌኮሙዩኒኬሽን ማስፋፊያ ዕቅድ ማስፈጸሚያ የሚሆን 800 ሚሊዮን ዶላር የሚያስወጣ ውል፣ ZTE በሚል ምህጻር ከታወቀው የቻይና ኩባንያ ጋር ተፈራረመ። ቀደም ሲል፣ ከሌላው «ሁዋዌ» በሚል መጠሪያ ከታወቀው


በፍቃዱ ኃይሉ
‹ከናንተ መካከል የሕዝብ ንቀት የሌለበት ማነው?›
ከትንሹ እስከ ትልቁ፣ ከመንግሥት እስከ ልሒቁ፣ ከሊቁ እስከ ደቂቁ – ሁሉም መጠኑ ይለያይ እንጂ የሕዝብ ንቀት አለበት፡፡ ‹‹ይሄ ሕዝብ…›› ብሎ የበቀለበትን ሕዝብ የማይተች ግለሰብ ማግኘት ከባድ ነው፡፡ እኔ ራሴ ከዚህ በፊት ሕዝብን በአደባባይ ከተቸሁባቸው ጽሑፎች ውስጥ ‹‹ሁሉም ሕዝብ ገዢው መንግሥት ይመጥነዋል››፣ ‹‹ሕዝቦች ግለሰብን ይጨቁናሉ›› እና ‹‹ሕዝብ ምንድን ነው?›› የሚሉ ርዕሶች የሰጠኋቸው አይዘነጉኝም፤ የተሳሳተ መልዕክት ይዘዋል ማለቴ ግን አይደለም፡፡ ለዚህም ነው ሕዝብን እንደተራ መንጋ ብቻ መቁጠር በጣም ስህተት መሆኑን እና የእያንዳንዱ ዜጋ ድምር ውጤት መሆኑን እና ማኅበረሰቡን ወካይ መሆኑንም ለመጥቀስ ይህንን መጻፍ ያስፈለገኝ፡፡
ንቀት በያይነቱ
በአንድ መጽሔት ውስጥ ለተወሰኑ እትሞች በኤዲተርነት ተቀጥሬ በመሥራት ውስጣዊ አሠራራቸው ምን እንደሚመስል ለመገምገም እና ከተለያዩ በአገራችን በሚዲያ ሥራ ላይ ለረዥም ጊዜ ከተሰማሩ ሰዎች ጋር ለማውራት ሞክሬ ነበር፡፡ የተረዳሁት ነገር ቢኖር በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የተፈጠሩ የሕዝብ ንቀቶችን ነው፡፡
ቢያንስ ብዙዎቹ የሚዲያ ሰዎች ‹‹ሕዝቡ የሚወደው እንዲህ ዓይነቱን ነገር ነው…›› የሚሉት ነገር አላቸው፡፡ በደንብ እንድንግባባ ‹‹ሎሚ›› መጽሔት በአሁኑ ሰዓት ከፍተኛ ገቢና ስርጭት ያለው ነገር ግን ከፌስቡክ እና ከተለያዩ ብሎጎች ላይ የተቃረሙ፣ ቢያንስ አንድ ሳምንት ያለፋቸው ታሪኮች ጥርቅም ነው፡፡ ይህ ተሞክሮ ሌሎቹን ሚዲያዎች ሎሚ ሞዴላቸው እንዲሆን እና ሕዝቡ ‹በቅጡ ያልታሰበበት እና ያለፈበት ጽሑፍ በተቀጠሩ ሠራተኞች በጥንቃቄ ከተዘጋጀ እና ከትኩስ መጣጥፎች የበለጠ ይመርጣል› የሚል ድምዳሜ ላይ እንዲደርሱ አድርጓቸዋል፡፡ በሁለት እና በሦስት ሠራተኛ ብቻ ከኢቪዲዮ ላይ በወረዱ ሥራዎች አንዱ ሲከብር ሌላው ሌላው ግን በርከት ያሉ ሠራተኞችን ቀጥሮ፣ ከየትም ቀራርሞ የሚያመጣው መረጃ ገዢ አያገኝም፡፡ ለዚህ ደግሞ ‹‹ተጠያቂው የሕዝቡ ቅሽምና ነው›› ይሏችኋል፡፡ እውነታው ግን ይሄ አይደለም፤ እውነታውን እንመለስበታለን… ከዚያ በፊት ግን ይህ ዓይነቱ ችግር ሚዲያው ላይ ብቻ ሳይሆን በየዘርፉ ያለ ችግር መሆኑን ተጨማሪ ምሳሌዎች መዘርዘር አለብን፡፡

የአገራችንን ፊልሞች ከተከታተልን ‹‹በጣም ብዙዎቹ የአገራችን ፊልሞችን ከድርሰት ጀምሮ እስከ ዝግጅት፣ ከቀረጻ ጀምሮ እስከ ‹ኤዲቲንግ›፣ ከትወና ጀምሮ እስከ ዘውግ ድረስ የሚዘልቁ ችግሮች አሉባቸው፤ የፊልም ባለሙያዎች ራሳቸውን በማሻሻል ሥራቸውን ማሻሻል አለባቸው›› የሚል አስተያየት ሲሰነዘር (በተለይ ከባለሙያዎቹ) የሚቀርበው መልስ አስገራሚ ነው፡፡ የፊልም ሠሪዎቹ የፊልሞቹን ችግሮች ይቀበሉና፤ ነገር ግን ‹‹ሕዝቡ የሚፈልገው እንዲህ ዓይነት ፊልም ነው፤ እኛ ምን እናድርግ? ብዙ ወጪ አውጥተን ጥሩ ፊልም ብንሠራ ማን ያይልናል? ብንከስርስ?›› ይሏችኋል፡፡
በተመሳሳይ መንገድ የአገራችንን የሬዲዮ ፕሮግራሞች ተመልከቱ ‹‹ሆይ፣ ሆይታ›› ያበዛሉ… ሌሎችም፣ ሌሎችም፡፡ እንግዲህ ሚዲያውና የፊልም ‹‹ኢንደስትሪው›› (የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ናቸው ብያለሁ) ሕዝቡን በዚህ መንገድ መመልከታቸው ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳለው አትጠራጠሩ፡፡ ችግሩ ግን በነርሱም አይወሰንም፡፡
ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ሂዱና ‹ለምንድን ነው ሕዝቡ ሰብኣዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቱ ሲጣስ ዝም የምትሉት?›› ሲባሉ ሕዝቡ እንደማይተባበር ይናገራሉ፡፡ በነርሱ አተያይ ሕዝቡ በደሉን ውጦ ዝም የሚል እንጂ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ እነዚህን ለማስቆም የሚያስችል (ልብ በሉ ለማስቆም የሚያስችል ነው ያልኩት) ዕቅድ ይዘው ቢመጡ የማይተባበራቸውና ዕቅዳቸው በወረቀት ላይ የሚባክን ነው የሚመስላቸው፡፡
ገዢው ፓርቲም የተለየ ሐሳብ የለውም፡፡ ሕዝቡ በራሱ ማገናዘብ የማይችል ይመስል፣ ሕዝቡ ምን ማሰብ እንዳለበት፣ እንዴት ማሰብ እንዳለበት መናገር ይቀናዋል፤ በመሠረቱ አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚያምነው ይህንኑ ነው – ‹ሕዝብ በነጻነት ከተለቀቀ መረን ይወጣል› ብሎ ያስባል፡፡ ለምሳሌ ለሕዝቡ የሚበጀውን የማውቅለት እኔ ነኝ ስለዚህ ‹አዋጅ አጽድቄ ስለጠቀሜታው አስረዳዋለሁ እንጂ በቅድሚያ አላማክረውም› የማለት ዝንባሌ አለው፡፡
ለመሆኑ ሕዝባችንን እናውቀዋለን?
ስለሕዝብ ማንነት እና ምንነት ስናወራ ባብዛኛው እኛ ስለምናውቀው እና ስለበቀልንበት ሕዝብ ማውራታችን አይቀርም፡፡ ይህ ደግሞ በመጠኑም ቢሆን እኔና እኔን መሰሎቼ በአንድ ላይ ስንሆን ስለምንሰጠው ትርጉም እያወራን ነው ማለት ነው፡፡ ሕዝብ ማለት በግርድፉ ግለሰቦች በአንድነት ማለት ነው፡፡ ሕዝብ ለመሆን እያንዳንዱ ግለሰብ ከሌላውጋ ሊያመሳስለው የሚያስችለውን የነጠላ ማንነት በከፊል መሸራረፍ የግድ ይጠይቀዋል፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን ሕዝባችንን እናውቀዋለን የሚለውን ጥያቄ መጠየቅ ያስፈልገናል፡፡
በኔ እምነት ሕዝባችንን አናውቀውም፡፡

ሎሚ መጽሔት በሳምንት 20 ሺሕ ሸማች አለው፡፡ ከዚህ ተሞክሮ በመነሳት ‹‹የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚወደው እንዲህ ዓይነት መጽሔት ነው…›› የሚል መደምደሚያ ላይ መድረስ አይቻልም፡፡ አንደኛ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ በ20 ሺሕ አይወከልም፡፡ ሁለተኛ፤ ያ 20 ሺሕ ሸማች የሚወክለውን ‹‹ሎሚ›› መጽሔትን አግኝቶ ከሆነ ያንን ዓይነት ሳይሆን የተሻለ ይዘት እና ደረጃ ያለው ጽሑፍ ያለው መጽሔት የሚፈልጉ ሚሊዮኖች አሉ፡፡ ነገርግን በዘርፉ የተሰማሩት በአሁኑ ገበያ ሚዛን ብዙ የሚሸጠው ‹ሎሚ› ስለሆነ የሎሚን ደምበኞች ለመሳብ ነው፡፡ ስለዚህ በተለየ አቀራረብ የሎሚ ደምበኞችን ለመሳብ ሲሞክሩ ባክነው ይቀራሉ፡፡ ነገር ግን የራሳቸው የደረጃ ጣሪያ እና የጥራት እሴት ይዘው ቢመጡ በሎሚ ዓይነቶቹ መጽሔቶች ተሰላችቶ የተገፋው አንባቢን ልብ እና ቀልብ ማግኘት ይችላሉ፤ ነገር ግን አልሞከሩትም፡፡
የአገርኛ ፊልም ተመልካቾች በጣም ጥቂት ናቸው፡፡ ብዙኃኑ የሚያስበው በገንዘብ እና በጊዜ መቀለድ እንደሆነ ነው፡፡ ነገርግን የፊልም ሠሪዎቹ አሁንም የሚደክሙት በተዘረጋው የፊልም ባሕል ውስጥ ያሉትን ጥቂት የፊልም ተመልካቾች ከበፊት ፊልሞች ገበያ አንፃር ‹‹ይወዷቸዋል…›› ብለው የሚገምቷቸውን ታሪኮች እና እንቶ ፈንቶዎች ይዞ መፍጨርጨር ነው እንጂ፣ አዲስ እና የተሻለ ነገር ይዘው ሲመጡ አይታዩም፡፡ ሌላው ቀርቶ ሴባስቶፖል ሲኒማ የሚያመርታቸው ፊልሞች በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እየወጣባቸው፣ በሚሊዮኖች ሲያተርፉ በመመልከት ፈንታ… ‹ሕዝባችን ሮማንቲክ ኮሜዲ ካልሆነ በቀር አይወድም› በሚለው አባባላቸው መቁረባቸውን ቀጥለዋል፡፡
የተቃዋሚ ፓርቲዎች… በአብዛኛው የብሶተኞች እና የሥልጣን ጥመኞች ቤቶች ናቸው፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በሕጋዊ መንገድ መወዳደር ከጀመሩባቸው ጊዜያት ጀምሮ የተፈጠሩት ችግሮች፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጠራ ፖሊሲ አለመኖር፣ እርስ በእርስ መጋጨት፣ እና ሌሎችም ችግሮች ተደማምረው ሕዝቡ በፖለቲካ ፓርቲዎች ተስፋ እንዲቆርጥ አድርጎታል፡፡ ብዙኃኑ ልሒቅ ተቃዋሚዎቹን ጥሎ ሲሸሽ፣ ጥቂት ሕዝባዊ ልዩነቶችን እና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ራሱ በቅጡ የማይረዱ ግለሰቦች ፓርቲዎቹን ተቆጣጥረዋቸዋል፡፡ እያንዳንዱን ዝርዝር የማያውቀው ሕዝብ፣ ድምሩን ግን መረዳት ይችላልና በተቃዋሚዎች እምነት ቢያጣ ‹‹ሕዝቡ ጭቆና ተስማምቶት እንደተኛ…›› ሊታሰብ አይገባም፡፡

ከዚህ በፊት አንድ ወዳጄ ከጠቀሳት በኋላ ደጋግሜ እንደተጠቀምኩበት ‹‹አህያ ማር አይጥማትም ሲባል ማን ሰጥቶ ሞከረኝና›› እንዳለችው ሕዝባችንን ማር ሳናቀርብለት ያቀረብኩለትን ሬት ካልተጋተ ብለን ልንንቀው አይገባም፡፡

ኢትዮ-ምኅዳር ማክሰኞ ነሐሴ 8/2005 ዓ.ም

  • በእነ ኤልያስ ክፍሌ መዝገብ በሽብርተኝነት ክስ ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት ከሚገኙት አራቱ ኢትዮጵያውያን መካከል ይቅርታ ጠይቀው የነበሩት ሶስቱ፤ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ እና አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር፤ ጥያቄያቸው ከቀረበ ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ ሐምሌ 25/2005ዓ.ም የይቅርታ ቦርድ ጽ/ቤት ማህተም አርፎበት ለወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ በተላከ ደብዳቤ የይቅርታ ጥያቄቸው ለፕሬዝዳንቱ ቀርቦ ውድቅ መደረጉን እንደተገለፃለቸው ነገር ግን የጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ እና የአቶ ዘሪሁም ገ/እግዚአብሔር ግን ምላሽ እንዳልደረሳቸው
  • የአምስት ፓርቲዎች ጥምረት የሆነው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት መድረክ ቅዳሜ ነሐሴ 1 ቀን 2004ዓ.ም ባካሄደው ጉባዔ ዶ/ር መራራ ጉዲናን ሊቀመንበር አድርጎ መምረጡን እና ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት መድረክን እንደሚመሩ
  • አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የፀረ ሽብር ህጉን እንዲሰረዝ የሚያካሂደውን የ3ወር የሚሊዮኖች የነፃነት ድምፅ ንቅናቄ የመጀመሪያው ምዕራፍ ማጠናቀቂያ አስመልክቶ መስከረም 5 ቀን 2006ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያደርግ እንዳቀደ
  • ሁለት የሬድዮ ቢላል ጋዜጠኞች ክስ ሳይመሰረትባቸው ከሣምንት በላይ ታስረው መቆየታቸው እንዳሳሰበው የጋዜጠኞች ተንከባካቢ ቡድን (CPJ) ባለፈው ሳምንት ባወጣው መግለጫ ማሳወቁን

 
የኛ ፕሬስ ማክሰኞ ነሐሴ 8/2005 ዓ.ም

  • ነሐሴ 14/2004ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት የተነጠሉት የጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በሥላሴ ካቴድል ቅጥር ግቢ ውድ በሆነ የእምነበረድ አይነት የታነፀው የተቀማጠለ መካነ መቃብር ተጠናቆ በመጪው ሳምንቶች ይመረቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ
  • የወሲብ ድረገፆችን በማሰስ ኢትዮጵያ፤ ስሪላንካን ተከትላ ሁለተኛ መውጣቷን ጎግል የተሰኘው እውቅ ዓለም አቀፍ ተቋም ይፋ ማድረጉን እና ኢትዮጵያ ከቀዳሚዎቹ ተርታ እንድትቀመጥ በዘንድሮ ኣመት በደቡብ አፍሪካ እየተካሄደ ባለው የቢግ ብራዘር አፍካ ውድድር ተሳፊ የነበረችው ቤቲ አበራ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳበረከተች
  • ከስምንት ወር በፊት ለተለያዩ ስልጠናዎች ወደ ደቡብ ኮሪያ ካመሩ 59 ኢትዮጵውያን መካከል 38 ኢትዮጵያውያን የኮርያን መንግስት ጥገኝነት መጠየቃቸውን


ሪፖርተር ነሐሴ 8/2005 ዓ.ም

  • ነሐሴ 2 ቀን 2005 ዓ.ም. 1434ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በእስልምና እምነት ተከታዮች በተለይ በአዲስ አበባ ብሔራዊ ስታዲየም ሲከበር፣ ከፖሊሶች ጋር በተፈጠረ ግጭት በቁጥጥር ሥር ውለው ከነበሩ በርካታ ሰዎች መካከል፣ አብዛኛዎቹ በምክርና በከባድ ማስጠንቀቂያ መለቀቃቸውን ፖሊስ ማታወቁን እና ፍርድ ቤት የቀረቡት የምርመራ ጊዜ እንደተጠየቀባቸው
  • እስከ ነሐሴ 17 ድረስ የሚቆየው የ40/60 ቤቶች ምዝገባ ባለፈው ሰኞ ነሐሴ 6 ቀን 2005 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ 116 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎችና መገናኛ አካባቢ ከአምቼ ፊት ለፊት በሚገኘው የአዲስ አበባ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት መጀመሩን

ሠንደቅ ነሐሴ 8/2005 ዓ.ም

  • የመብት ጥያቄ ያነሱ የሙስሊሙ ማኀበረሰብ አካላት ላይ መንግሥት እየወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ አጥብቀው እንደሚቃወሙት ሶስት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ማለትም የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ)፣ የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ እና የመላ ኦሮሞ ሕዝብ ድርጅት ነሐሴ 5 እና 6 ቀን 2005 ዓ.ም በተናጠል መግለጫ መስጠታቸውን (እና የመግለጫቸውን ሙሉ ቃልም ተካቷል )
  • በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር የሆኑት፤ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ፓርቲ (ኦፌኮ)ሊቀመንበር እና በቅርቡ መድረክ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ የመድረክ ሊቀመንበር ሆነው የተመረጡት ዶ/ር መረራ ጉዲና “የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምስቅልቅል ጉዞና የህይወቴ ትዝታዎች” በሚል ርዕስ አዲስ መፅሐፍ ማሳተማቸውን እና ገበያ ላይ መዋሉን 

አድማስ ነሐሴ 11/2005 ዓ.ም

  • ድምፃዊ ኢዮብ መኮንን፣ “ስትሮክ” ተብሎ በሚታወቀው ህመም ቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል ስለመግባቱ እና ለተጨማሪ ህክምና ወደ ኬንያ ስለሚኖረው ጉዞ (ይህ ዜና በአድማስ ጋዜጣ ከወጣ በኋላ ትላንት ማታ ላይ ድምፃዊ እዮብ ኬንያ ሄዶ ህክምናውን እየተከታተለ እያለ ከዚህ ዓለም በሞት  መለየቱ ተሰምቷል፡፡ ነፍስ ይማር!)
  • የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህራን በተማሪዎችና በአስተዳደር መካከል የነበረው ውጥረት እንዲረግብ ጥረት በማድረጋችን በኮሌጁ ቅጽር ግቢ ከሚገኙ መኖርያዎቻችን አለአገባብ ልቀቁ ስለመባላቸው
  • በሳምንት አንድ ቀን ውሃ ማግኘት ብርቅ የሆነባቸው ሰፈሮች፣ በውሃ እጦት አካባቢያቸውን በመጥፎ ጠረን የሚበክሉ የኮንዶሚኒየም መኖሪያዎች፣ ለተደጋጋሚ አቤቱታ ምላሽ ሳያገኙ በርካታ ወራት እየተቆጠሩ  ስለ ሚማረሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች
  • አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ፣ በመቀሌና በወላይታ ሶዶ ከተሞች ሠላማዊ ሠልፍና ህዝባዊ ስብሠባ ለማካሄድ የነበረው እቅድ በተለያዩ ጫናዎች መጨናገፉን የፓርቲው ሊቀ መንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ መግለፃቸውን

የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል ከአድማስ ጋዜጠኛ ጋር ያደረጉት ቃለመጠይቅ ተካቷል፡፡
ለአቶ ሽመልስ ከማ የቀረቡት ጥያቄዎች እና ከምላሹ ውስጥ የተወሰዱ በጥቂቱ፡-

በተቃዋሚ ፓርቲዎች እየተካሄዱ ስላሉ ሰላማዊ ሰልፎች የመንግስት አቋም ምንድነው?

“ተቃዋሚዎች ባይቃወሙና ባይሰባሰቡ ነው እንጂ የሚደንቀው ይህን ማድረጋቸው ብዙም የሚያስደንቅ አይደለም፡፡ ነገር ግን ከሚያነሷቸው ጉዳዮች ውስጥ የበርካታ ዜጐች ስጋት የሆኑ ጉዳዮችም አሉ፡፡ በተለይ ከአክራሪ ጽንፈኛ ሙስሊም ቡድኖች ጋር አንዳንድ ፓርቲዎች የፈፀሙት ያልተቀደሰ ጋብቻ አሳሳቢ ነው፡፡ በሀገራችን ህገመንግስትም ፖለቲካ እና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው፡፡ የፖለቲካ ስብሰባዎች፣ የፖለቲካ ሰልፎች እንኳን ሃይማኖተኞችን ሊቀላቅሉ፣ የሃይማኖት ተግባራት ከሚፈፀምባቸው ቦታዎች በተወሰነ ርቀት መሆን አለባቸው፡፡ አሁን ግን ሁለቱ መቀያየጥ የሌለባቸውን ነገሮች ሲያካሂዱ እያየናቸው ነው፡፡”

“በየአደባባዩ የጠሩትና ሚሊዮኖችን እናስከትላለን ብለው የለፈፉለት ሰላማዊ ሰልፍ፣ በመቶዎችና በአርባዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ይዞላቸው ሲመጣ ያዩ ተቃዋሚዎች፣ ሌላ ሃይል እናገኝበታለን ብለው የገቡበት ስሌት አደገኛ ስሌት ነው፡፡ ከሽብርተኝነት ጋር የተፈጠረ ድሪያ ነው የሚሆነው፡፡ እንዲህ አይነቱን ነገር ሊጠነቀቁ ይገባቸዋል፡፡ መጥፎ አካሄድ ነው፡፡ ካለፈው ስህተታቸው ትምህርት መውሰድ አለባቸው፡፡ ህገመንግስቱ ሲጣስ ዳር ቆሞ የሚመለከት መንግስት አይደለም ያለው፡፡”

በሠልፎቹ ከሚጠየቁት ጉዳዮች መካከል መንግስት ምላሽ ያሻቸዋል ብሎ የተቀበላቸው የሉም? በተለይ ከሰብአዊ መብት አያያዝ ጋር    የሚነሱ ጥያቄዎች ላይ?

“ዝም ብሎ ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ የሚያነሷቸው ካልሆነ በቀር፣ በሰብአዊ መብት አያያዝ በኩል መንግስት የዜጐችን የሰብአዊ መብት አያያዝ አተገባበር በጣም በተጠናከረ መልኩ እያሻሻለና አድማሱን እያሰፋ በመሄድ፣በቅርቡ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት አያያዝ መተግበሪያ (አክሽን ፕላን) ያወጣ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚያ ላይ የእያንዳንዱን ዜጋ ዲሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብት ጥበቃ ለማስተግበር የሚያስችሉ ዝርዝር መርሃ ግብሮችን ነው ያወጣው፡፡”

በተለያዩ ከተሞች እየተካሄዱ ያሉት ሰላማዊ ሰልፎች እና ህዝባዊ ስብሰባዎች በመንግስት ላይ ጫና የመፍጠር አቅም የላቸውም?
“እንዴት ነው የሚፈጥሩት! ጐንደር በጠሩት ሰልፍ ላይ 200 የሚሆን ሰው ነው የተገኘው፡፡ በሌሎችም ቦታዎች ተመሳሳይ ነው፡፡ እነሱ “ለምንድነው ስብሰባችን ባዶ የሆነው?”፣ “አዳራሻችን ባዶ የሆነው?” ብለው መጠየቅ አለባቸው፡፡ ጣታቸውን ወደ ውጪ ከመደንቆር ይልቅ የህዝቡን ፍላጐት ማየትና ወደ ውስጣቸው መመልከት አለባቸው፡፡”

“ነገር ግን ይህን ለመሸፋፈን መንግስት ጫና በማድረጉ ሰው ሊወጣልን አልቻለም ሲሉ ነው የሚደመጡት፣ ይሄ መሠረት የሌለው ውንጀላ ነው።”

አንድነት ፓርቲ የፀረ ሽብር አዋጁን በማሰረዝ የሚሊዮኖችን ድምጽ እያሰባሰበ ነው፡፡ የሚሰባሰበው ድምጽ አዋጁን ሊያሰርዘው ይችላል?

“የፀረ ሽብር ህጋችን ከተለያዩ የአለም ሀገራት ተጠንቶ የተቀረፀ ነው፡፡ የዜጐቻችንን ደህንነት ከሽብር ጥቃት ለመከላከል የህግ ከለላ ያስፈልግ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ህጉ ተቀርጿል፡፡ በህጉም እስካሁን ሊከሰቱ ይችሉ የነበሩ አያሌ ሙከራዎችን ማክሸፍ ችለናል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ስጋት የሚገባቸው ወገኖች እነማን እንደሆኑ ጥርጥር የለውም፣ ዜጐች ግን ስጋት ላይ አይወድቁም፡፡ ህጋዊ ፓርቲዎችንም ስጋት ላይ አይጥልም፡፡ ተገቢ የሆነውንና ያልሆነውን አጣቅሶ ለመሄድ ያሰበ ካለ ግን ድንጋጌው ስጋት ላይ ሊጥለው ይችላል፡፡ ዜጐች ግን ሙሉ ድጋፍ የሰጡት ህግ ነው፡፡”

ህጉን ድምጽ በማሰባሰብ ማሰረዝ አይቻልም ማለት ነው?

“ህግ የሚወጣው በህግ አውጪ አካላት ነው። እነዚህ አካላት ከማውጣቱ ባሻገር ህጉን መሻርም ማሻሻልም ይችላሉ፡፡ እነዚህ ድርጅቶች የህግ የበላይነት ለማክበርና ለህገመንግስታዊ ስርአት እውቅና ለመስጠት የሚያንገሸግሻቸው ተቋማት እንደሆኑ እናውቃለን፡፡ ህገመንግስታዊ ተቋማትንና ህጋዊ አሠራሮችን ለመቀበል የማይፈልጉ ፓርቲዎች ናቸው ይህን የሚያደርጉት፡፡”

ሪፖርተር ነሐሴ 12/2005

  • የአክሰስ ሪል ስቴት የቦርድ ሊቀመንበርና ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ በዚህ ወር መጨረሻ ስለመምጠታቸው እና ለአክሰስ ሪል ስቴት 40 ከመቶ ድርሻውን የሰጠውና 60 በመቶ የሚሆነው ከፍተኛ ባለድርሻ የሆነው ፓስፊክ ሊንክ ኢትዮጵያ ሪል ስቴት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ‹‹ከአክሰስ ሪል ስቴት ጋር በመሆን ቪላና አፓርትመንት እገነባላችኋለሁ በማለት ውል ካስገባን በኋላ ውላችን ሳይፈጸምልን ገንዘባችንን ከወሰደ አንድ ዓመት ሞልቶታል፤›› በሚል፣ 137 ደንበኞች የ73,388,844 ብር ከ50 ሳንቲም ክስ መመስረት 
  • የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ በሕግ በተፈቀደለት የፋይናንስ ኪራይ (ፋይናንስ ሊዝ) አገልግሎት መሠረት፣ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ አገልግሎት ወይም ለምርትና ለአገልግሎት የሚውሉ ማሽኖችንና ተሽከርካሪዎችን ለማከራየት ለሚፈልጉ ኩባንያዎች ፈቃድ ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን
  • የህንዱ ኩባንያ ካራቱሪ አግሮ ፕሮዳክትስ፣ የሼክ መሐመድ አል አሙዲ ሳዑዲ ስታርን ጨምሮ ሰፋፊ የግብርና መሬት ወስደው ያላለሙ ኩባንያዎችን መሬት መንግሥት መንጠቅ ሊጀምር መሆኑን

ባለፈው ሳምንት በቡሩኖ ደሴት በምትገኘው ብሩናይ አውሮፕላን ማረፊያ ነበር የተለያየነው፡፡ አንዲት የሀገሬን ሰዎች የመሰለች ልጅ ወደ እኔ አቅጣጫ ስትመጣ አይቼ፡፡ ልጅቱ መጣች፡፡ እንደ ዓይኔ ምስክርነት ከሆነ የሀገሬ ልጅ ናት፡፡ በአንገቷ ላይ ጣል ያደረገችው ሻርፕ ነገርም ነጠላ ቢጤ ነው፡፡ እንዲያውም የሆነ ጥልፍ ነገር ይታየኛል፡፡ መጣችና ከእኔ በትይዩ ከሚገኘው የተደረደረ ወንበር መካከል ተቀመጠች፡፡ ይኼኔ ዓይኔን ተጠራጠርኩት፡፡ ኢትዮጵያዊት አይደለችም ማለት ነው? አልኩ በልቤ፡፡ መሆን አለመሆኗን ለማረጋገገጥ የሆነ ምልክት መፈለግ ጀመርኩ፡፡ ምንም ነገር ሳጣ ‹‹ለምን አልጠይቃትም›› አልኩና አመራሁ፡፡

ወደ ወንበሯ ስጠጋ ባደረገችው ሻርፕ ላይ ኦዳ (የኦሮሞ ባሕላዊ መለያ የሆነው ዋርካ) ተጠልፎ አየሁት፡፡ በዚህ ተጽናናሁና

‹‹ኢትዮጵያዊት ነሽ›› አልኳት በአማርኛ፡፡

‹‹ይቅርታ አይደለሁም›› አለችኝ በእንግሊዝኛ፡፡

‹‹ይህንን የልብሱን ጌጥ ግን ዐውቀዋለሁ›› አልኳት እኔም በእንግልጣር፡፡

ቀና ብላ በአግራሞት እያየችኝ ‹‹ልክ ነህ ኦዳ ነው›› አለችኝ፡፡

‹‹ታድያ ቢያንስ በትውልድ ኢትዮጵያዊ ነሻ›› አልኳት እንደ ቀልድ፡፡

‹‹አይደለሁም›› ብላኝ ኮስተር አለች፡፡

እንዲህ ዓይነት ነገር በአሜሪካ ሚነሶታ አጋጥሞኝ ስለሚያውቅ ተጠራጠርኩና በእንግሊዝኛ ‹‹ይቅርታና ታድያ የየት ሀገር ሰው ነሽ?›› አልኳት፡፡

አሁን ከእርሷ አለፍ ብየ ቁጭ ብያለሁ፡፡ ‹‹እኔ ከኦሮሚያ ነኝ›› አለችኝ፡፡ ስልኳን እየነካካች፡፡

‹‹እኔምኮ ከኦሮሚያ ነኝ፡፡ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ዋና ከተማ አይደለች እንዴ›› አልኩ ለቀልድ ያህል፡፡

‹‹አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ናት፤ የኦሮሚያ ዋና ከተማ ፊንፊኔ ናት፡፡ አሁን እኔና አንተ መነጋገሩ ምን ይፈይድልናል›› አለች ለመገላገል ብላ፡፡

‹‹እኔና አንቺ ካልተነጋገርንማ ማንና ማን ተነጋግሮ መፍትሔ ያመጣል ታድያ››

‹‹ምናልባት ላንግባባ ስለምንችል››

‹‹አለመግባባታችንን በምን ዐወቅሽው?››

ተመቻቸችና ‹‹ለምሳሌ እኔ ፊንፊኔ ስል አንተ አዲስ አበባ አልክ፣ ለእኔ ኦሮሚያ ቅኝ የሚገዛ ሀገር ነው፤ ላንተ ደግሞ ክልል ነው፤ ታድያ እንዴት እንግባባለን?››

‹‹ሰዎች ሊግባቡ የማይችሉትኮ የተለያዩ ሃሳቦችን ስለሚይዙ አይደለም፡፡ የተለያዩ ሃሳቦቻቸውን የማስማሚያ መንገድ ስለማይኖራቸው ነው፡፡ ደግሞም የግድኮ መግባባት አይጠበቅብንም፤ ቢያንስ እንገናዘባለን፡፡ አሁን አንቺ ፊንፊኔ አልሽ፣ እኔ አዲስ አበባ አልኩ፤ ምናልባትም ከአዲስ አበባና ከፊንፊኔ በፊትም ቦታው ሌላ ስም ሊኖረው ይችላል፡፡ አዲስ አበባ ከየቦታው በግድም በውድም የመጣን የሀገሬው ሰዎች ብቻ ሳንሆን ጣልያኖችም፣ ግሪኮችም፣ ዐረቦችም፣ አርመኖችም፣ እንግሊዞችም፣ ፈረንሳዮችም፣ ሌሎችም ባዋጣነው አስተዋጽዖ እዚህ ደርሳለች፡፡ እንዲያውም በሌላው ሀገር እንዲህ የብዙ ዓይነት ወገን አሻራ ያረፈባት ከተማ ስትገኝ እንደ ልዩ ነው የምትታየው፡፡ የሚፈለገውም የሁሉ እንድትሆንና ሁሉም አስተዋጽዖውን የእኔ ብሎ እንዲቀጥል ነው፡፡ ቻይና ታውን፣ ኢትዮጵያን ስትሪት፣ ኮርያ ሠፈር፣ ስፓኒሽ ጎዳና እያሉ ለአስተዋጽዖ አድራጊዎቹ ዕውቅና በመስጠት የሁሉ እንድትሆን ያደርጓታል፡፡ አዲስ አበባ ወይም ፊንፊኔም እንዲሁ ናት፡፡

‹‹በሕዝብ ፍልሰትና በጦርነት በኖረ ሀገር የስም ተፋልሶ ያለ ነገር ነው፡፡ ለምሳሌ በምዕራብ ሸዋ ‹ወረብ›ና ‹እንደገብጦን› የሚባሉ የጋፋቶች ግዛቶች ነበሩ፤ በኋላ ግን በኦሮምኛ ስሞች ተተክተዋል፡፡ በምሥራቅ ሸዋ እነ ፈጠጋር፣ እነ ወጅ፣ እነ መሐግል ስማቸውን አጥተው ቀርተዋል፡፡ ዛሬ የመተሐራ አካባ የሚባለው ጥንት መሐግል ነበረ፡፡ ጎጃም ብትሄጂ አቸፈር፣ ሜጫ፣ አዴት፣ ዴንሳ፣ ብቸና የኦሮሞኛና የኦሮሞኛ ነክ ስሞች ናቸው፡፡ በፊት ግን የአገውና የአማራ ስሞች ነበሩባቸው፡፡ ያ ማለት ግን ቅኝ ተገዝተዋል ማለት አይመስለኝም፡፡

‹‹በባሌ፣ በሐርና በሸዋ ብዙ የአርጎባ ስሞች ወደ ኦሮምኛ ተቀይረዋል፡፡ በወለጋና በደቡብ ሸዋ ሰባቱ የጋፋት ፌዴሬሽን አካላት ይገኙባቸው የነበሩ ቦታች ዛሬ ሰዎቹም ስማቸውም ጠፍቶ ቀርቷል፡፡ ስማቸው ብቻ አይደለም፡፡ በኢትዮጵያ የጥበበ ዕድ ኢንዱስትሪ ታላቅ ቦታ የነበራቸው፣ በሕክምናና አስተዳደር ችሎታቸው የተመሰከረላቸው ጋፋቶች በኦሮሞ ፍልሰት ጊዜ ከመካከልና ከደቡብ የሀገራችን ክፍሎች ወጥተው መጀመሪያ ወደ ጎጃም ተሻገሩ፤ ከዚያም ደግሞ ቀስ በቀስ እየተዋጡ ጠፉ፡፡ ዛሬ ቋንቋቸውም ሆነ ባህላቸው ከኦሮሞዎች፣ ከአማሮችና ከአገዎች ጋር ተዋሕዶ ሕልውናውን አጥቷል፡፡

‹‹በትግራይ፣ በወሎና በጎጃም የአገው ሕዝቦች ከጥንት ጀምሮ ተስፋፍተውባቸው የነበሩ ቦታዎች በአማራና በትግራይ ሕዝብ ተውጠው፣ ስማቸውንም ቀይረው ጠፍተዋል፡፡ በደቡብ ምዕራብ ትግራይ የነበሩት የዶባ ሕዝቦች በአፋርና በትግራይ ተውጠው የቦታዎቻቸው ስሞችም ተቀይረው፣ ከጥቂቶች በቀር ጠፍተዋል፡፡ የጥንቷ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ተብለው የተመዘገቡትኮ አሁን ስማቸውን እንኳን አንሰማውም፡፡ ምናልባት ከአገው ሕዝቦች በቀር፡፡ ክርስቲያን ቶፖግራፊ በተሰኘው የኮስሞስ መጽሐፍ ውስጥ በአዱሊስ ያገኘውን የካሌብ የድንጋይ ጽሑፍ አኑሮልናል፡፡ በዚያን ጊዜዋ ኢትዮጵያ የተገለጡት ሕዝቦች ጋዜ፣ አጋሜ፣ ሲጊን፣ አቫ፣ ዚጋሪን፣ አጋቬ፣ ቲያማ፣ አታጋውስ(አገዎች)፣ ካላ፣ ሰሜን፣ ላዚን፣ ዚአ፣ ጋቫላ፣ አታልሞ፣ ቤጃ፣ ›› የሚባሉ ሕዝቦች ናቸው፡፡ ብዙዎቻችን እዚህ ዝርዝር ውስጥ የለንም፡፡ እነዚህ ቦታዎች ግን ዛሬ ወይ የወንዝ፣ ወይ የጎጥ፣ ወይ የተራራ ስሞች ሆነው ቀርተዋል፤ ያለበለዚያም ተለውጠዋል፡፡ ወሎ ብትሄጂ የአማራው ዋና ቦታ የነበረው ወለቃ ዛሬ ስሙ ቦረና ተብሏል፡፡ ወለቃ የወንዙ ስም ሆኖ ቀርቷል፡፡›› ስልኳን እየነካካችም ቢሆን ስትሰማኝ ቆየችና

‹‹የኦሮሞ ሕዝብ ግን የተለየ ነው፤ የሀገሪቱን ሰፊ ክፍል ይዞ ከሀገሪቱ ተጠቃሚ ሳይሆን፤ መሬቱንና መብቱን ተቀምቶ በገዛ መሬቱ ለሌሎች ገባር ሆኖ፤ ቋንቋውና ባህሉ ተረግጦ፤ ሌሎች ሕዝቦች መጥተው አገሩን ወስደውበት የሚኖር ሕዝብ ነው፡፡ በግድኮ ነው ኢትዮጵያ የሆነው፤ ኢትዮጵያ የሰሜን ሕዘቦች እንጂ የደቡቦቹ መጠሪያ አይደለችም፡፡ ኢትዮጵያ ሌላውን ጠቅልላ ነው የያዘችው፡፡›› አለችኝ፡፡ መነጋገሩን ወዳዋለች ማለት ነው፡፡

‹‹እይውልሽ እኅቴ እኔኮ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ ምንም ነገር አልደረሰም፤ መብቱ አልተነካም፣ መከራ አልተቀበለም፤ አልተሰቃየም፤ መሬቱን አልተነጠቀም፤ ሌሎች መሬቱን አልወሰዱበትም አይደለም የምልሽ፤ ነገር ግን ይህ ነገር የብዛትና ማነስ ካልሆነ በቀር በሁሉም ላይ የመጣ ነው፡፡ በዚያች ሀገር ውስጥ ለሥልጣንና ለሀብት ብዙ ትግግሎች ተደርገዋል፡፡ ‹‹ወረራ››፣ ፍልሰት፣ ጦርነት፣ ንጥቂያ፣ ስደት ተከስቷል፡፡ ይህ ግን የአንድ ሕዝብ ብቻ ስቃይ መገለጫ አይደለም፡፡ የብዛትና ማነስ ካልሆነ የሁላችንም አያቶች ቀምሰውታል፡፡ ጎንደሬው ዐፄ ቴዎድሮስኮ ጎንደሬዎቹን እጃቸውን ቆርጠዋል፣ በአንድ ቤት ውስጥ አስገብተው አቃጥለዋቸዋል፡፡ እንዲያውም ኦሮሞውን ምንም አላደረጉትም፡፡ ያ ግን የሥልጣን ጥያቄ እንጂ በአንድ ዘር ላይ የተፈጸመ ወንጀል አይደለም፡፡ ሁላችንም የያዝነው የተፈጠርንበትን መሬት ብቻ አይደለምኮ፡፡ ኦሮሞውም ቢሆን ከአማራው፣ ከትግሬው፣ ከጋፋቱ፣ ከአርጎባው፣ ከጉራጌው፣ ከሲዳማው፣ ከሌሎች ከጠፉ ሕዝቦች መሬት ወስዷል፡፡ ሁላችንም እዚህ አይደለም የነበርነው፤ አስፍተን ይዘናል፤ ተገፍተን ለቅቀናል፤ ተውጠን ቀርተናል፤ ውጠን ተዋሕደናል፡፡ የነገሥታቱን ታሪክ ስናይኮ የኦሮሞውም ሕዝብ ወደ ሸዋ፣ ወደ ጎጃም፣ ወደ ጎንደርም እየዘለቀ ከብት ዘርፏል፤ ሰዎች ገድሏል፤ እህል አቃጥሏል፡፡ መሬት ወስዷል፡፡ በጎጃምና በወለጋ ኦሮሞዎች ዘንድ ዓባይን እያለፉ የመዘራረፍ፣ የመገዳደል፣ የመዋጋት፣ ከዚያም በላይ የመጋባት ታሪክ ነበርኮ፡፡ ይህኮ ለኢትዮጵያ አዲስ አይደለም፡፡ ሁላችን እንዲህ ሆነን ነው እየተፈጠርን የመጣነው፡፡ ደግሞም ‹የመርገምት በረከት› እንደሚባለው ይህ ነገር አዋሕዶ ፈጥሮናል፡፡

‹‹የነበረው ትግልኮ ሀብትና ሥልጣንን መሠረት ያደረገ እንደነበር የምታዪው አንድ ‹ዘር› የሚባሉትም እርስ በርሳቸው ሀብትንና ሥልጣንን ለመንጠቅ ሲሉ ሲዋጉ መኖራቸው ነው፡፡ ዐፄ ቴዎድሮስ ጎጃም ገብተው ብዙ ሕዝብ ጨርሰዋል፡፡ ሞጣ አካባቢ ብትሄጂ የሚዘገንን ታሪክ ይነግሩሻል፡፡ ሸዋ ወርደው ብዙ እጆች ቆርጠዋል፡፡

ዐፄ ቴዎድሮስ እጅግ ተዋረዱ

የሸዋን ሰው ሁሉ እጅ ነሥተው ሄዱ የተባለውን አልሰማሽ፡፡

ያንን ግን አማራውን ከመጨቆንና ከማጥፋት አንጻር ካየነው፣ ቅኝ ግዛት አድርገን ከተመለከትነው ስሕተት ይመስለኛል፡፡ ሰዎች ተጨቁነዋል፤ አዎ፡፡ በራስ ሚካኤል ጊዜ ወሎና ሸዋ ተዋግቷል፡፡ በምኒሊክና በተክለ ሃይማኖት ምክንያት እምባቦ ላይ ሸዋና ጎጃም ተጫርሷል፡፡ ዐፄ ሱስንዮስ ከሸዋ አስከትለዋቸው ለሄዱት የኦሮሞ ወታደሮች የጎንደርን መሬት ከየአድባራቱ እየቀሙ እንዳደሏቸው የማኅደረ ማርያም ታሪክ በዝርዝር ይነግረናል፡፡ አንዱ ከካህናቱ ጋር ያጣላቸውም ይኼው ነበር፡፡

ዐፄ ታዎፍሎስ (1701-11) በነገሡ በሦስተኛው ዓመት ኦሮሞዎች ወሎ አምሐራ ሳይንት ወደምትገኘው አትሮንሰ ማርያም ደብር ገብተው በሮቿን ሰበሩ፤ ካህናቱንም በሙሉ ገደሉ፡፡ ምእመናኑንም ሁሉ ማረኩ፤ ዐፄ በዕደ ማርያም በፈረንጅ እጅ ያሳለውን የእመቤታችንን ሥዕልና የዐፄ በዕደ ማርያምን ዐፅም ሁሉ ነሐሴ 9 ቀን አውጥተው መሬት ለይ ጣሉት›› ይላል ዜና መዋዕሉ፡፡ እንግዲህ ይህንን ስታዪ እዚህች ሀገር ሳያጠፋም ሳይጠፋም የኖረ ሕዝብ አለመኖሩን ነው የምታዪው፡፡ ይህ ግን ኦሮሞዎች የኦርቶዶክስን እምነት ለማጥፋት፣ ወይም አማሮችን ለማጥፋት ብለው ያደረጉት አይመስለኝም፡፡ የሀብትና የሥልጣን ትግል ነው፡፡

ደግሞም በአንድ አካባቢ በነበረ ስም ተጠቅልሎ መጠራት በኛ አልተጀመረምኮ፡፡ ሀገር ተቀናንሶ ያንሳል፤ ወይም እምብርቱን ይዞ እየሰፋ ይሄዳል፡፡ አፍሪካ የሚለው ስም ላቲኖች በዛሬዋ ቱኒዚያ ለነበሩት ካርታጎአውያን የሰጡት ስም ነበረ፡፡ በመጀመሪያ አካባቢ የሊቢያ ጎሳዎችን ለመጥራት ነበር የሚውለው፤ በበርበሮች ቋንቋ ‹ኢፍሪ; ማለት ‹ዋሻ› ማለት ሲሆን ‹‹በዋሻ የሚኖሩ›› ለማለት የተጠቀሙበት ነው፡፡ ላቲኖች ‹ኢፍሪ› በሚለው ላይ ‹ኢካ› የሚለውን ለቦታ የሚቀጠል ቅጥያ ቀጠሉበትና ‹አፍሪካ› ብለው ጠሩት፡፡ በኋላ ግን የሁላችንም መጠሪያ ሆነ፡፡ እስያ ጥንት ዛሬ ቱርክ የያዘችው ቦታ መጠርያ ነበር፡፡ ዛሬ ግን እንዲያውም የሚጠሩበት የሩቅ ምሥራቅ ሕዝቦች ናቸው፡፡

‹‹አየህ›› አለችኝ መነጽሯን አስተካክላ፡፡ ‹‹አየህ አንተ ጭቆናው አይሰማህም፤ ምክንያቱም ከተጨቆኑት ወገን አይደለህምና፡፡ የደረሰብህ ነገር የለም፤ የመከራውን ገፈት አልቀመስከውም፡፡ እንደኛ በገዛ ሀገርህና መሬትህ ግፍ ቢደርስብህ፣ እንደኛ ቅኝ ተገዝተህ የቅኝ ግዛትን መራራ ነገር ብትቀምሰው እንደዚህ አትልም ነበር፡፡ አንዱ ልዩነታችን ከዚህ የሚመጣ ነው፡፡ በተግባር በቀመሰውና በትምህርት በሚያውቀው መካከል የሚኖር ልዩነት››

‹‹አንቺምኮ ከሌሎች ሰማሽው፣ አነበብሽው ወይም ወረስሽው እንጂ አልደረሰብሽም፡፡ የደረሰና የሚደርስ ካለም በሁሉም ላይ ይደርስ ይሆናል እንጂ የተለየ ነገር አሁን አይደርስብሽም፡፡

‹‹ለምሳሌ በስድሳ ስድስት አብዮት ጊዜ በአብዛኛው በቀይ ሽብር ያለቁት ኦሮሞዎች ናቸው›› አለች ስልኩን ወንበሩ ላይ አስቀምጣ፡፡

‹‹በምን ታወቀ?››

‹‹መረጃዎች አሉ››

‹‹ማን ነው ያን ጊዜ ሬሳ እያገላበጠ ዘር እየቆጠረ መረጃ የሰበሰበው››

‹‹ቢያንስ አብዛኛው የሀገሪቱ ሕዝብ ኦሮሞ በመሆኑ በብዛት የሚሞተው እርሱ ነው››

‹‹እንዴ አንድ ሕዝብኮ በብዛት ይኖራል ማለት በብዛት ይሞታል ማለት አይደለም፡፡ በወቅቱ በነበረው ተሳትፎ ነው የሚወሰነው፡፡ ያኔኮ የመፈረጃው ሳጥን ፀረ አብዮት፣ ፀረ ሕዝብ፣ አድኃሪ፣ ቡርዡዋ፣ ኢሕአፓ፣ ምናምን የሚል ነው፡፡ የዘር ፍረጃ አልነበረውም፡፡ አንዳንዴ ችግሩ እኔ ብቻ ነኝ መከራ ያየሁትና እኔ ብቻ ነኝ መፍትሔ የሚያስፈልገኝ ከሚል የሚመጣም ይመስለኛል፡፡ ችግሮችን ለመፍታት መነሣት እንጂ የተወሰኑ አካላትን ከችግር ለማላቀቅ መነሣት ተመልሶ ባልተፈቱት ችግሮች ወጥመድ የሚጥል ነው፡፡››

‹‹ከሆነ አካባቢ ነገሥታቱ መነሣታቸው በዓለም ታሪክ የተለመደ ነው፡፡ እንደ ፓርላማ ሥርዓት ንጉሣዊ አስተዳደር ሁሉን ያማከለ ሊሆን አይችልም፡፡ ኖርዌይን ሲገዟት የኖሩት የዴንማርክ ንጉሣውያን ቤተሰቦች ናቸው፡፡ አሁንም በእንግሊዝ ንጉሣዊነት በዘር ግንድ የሚሄድ ነው፡፡ አሁንም በጃፓንና ስፔን እንዲሁ ነው፡፡ በእሥራኤልም ታሪክ ብናየው የይሁዳ ቤት ነው፡፡ ይኼኮ የሰው ልጅ በሆነ ዘመን የደረሰበት ደረጃ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከዚያ የተለየች አትሆንም፡፡

‹‹ነገሥታቱ ከአማራው ወገን ስለነበሩኮ በ66 አብዮት የአማራው ሕዝብ አጥር ሆኖ ከውድቀት አላዳናቸውም፡፡ ንጉሣዊው ሥርዓት ሲወድቅኮ በተማሪው ንቅናቄ፣ በወታደሩ፣ በፓርቲዎች፣ በሠራተኛ ማኅበሩ ውስጥ የተለያዩ ማኅበረሰቦች ናቸው የነበሩት፡፡ ጨቁነውናል ብለው ከተነሡት ሕዝቦች መካከልኮ አማሮችም፣ ትግሬዎችም፣ ኦሮሞዎችም፣ ሲዳማዎችም፣ ወላይታዎችም፣ ጉራጌዎችም፣ ሶማሌዎችም ነበሩበት፡፡ እንዲያ ባይሆን ኖሮማ ተጠቅመናል በሚሉት አማሮችና ተጨቁነናል በሚሉት ሌሎች መካከል የርስ በርስ ጦርነት ይነሣ ነበር፡፡ አሁንኮ ያለፈውን ታሪክ በግልጥ መነጋገር፣ ከዚያ ትምህርት መውሰድና እንዳይደገም ማድረግ ነው የሚሻለው፡፡ እኛ ስለ ትናንት ብቻ ስንከራከር፣ ስለ ነገም ሳንነጋገር ስንት መልካም አጋጣሚዎች በዚህች ሀገር አለፉ፡፡ ስለ ትናንት ታግለን አብዮት እናመጣለን፤ ለውጥ ሲመጣ ግን ለነገ ያዘጋጀነው የጋራ የመግባቢያ ሰነድ ስለሌለን እንደገና አዙሪት ውስጥ እንወድቃለን፡፡ ተባብረን መሸከም ያልቻልነውን ችግር ለየብቻ እንሸከመዋለን ብሎ መመኘት ቅዠት ነው የሚመስለኝ፡፡››

ደኅና ሞቅ ወዳለው ውይይት በመግባት ላይ ሳለን

‹‹ወደ ማኒላ የምትሄዱ መንገደኞች ወደ በሩ ግቡ›› የሚል ማስታወቂያ ተነገረ፡፡ ቦርሳዋን ሸክፋ ከመቀመጫዋ ተነሣች፡፡

‹‹ደስ የሚል ቆይታ ነበር፡፡ እኔ ወደ ፊሊፒን ነው የምሄደው፤ የምኖረውም እዚያ ነው፡፡ በፊት ደቡብ አፍሪካ ነበርኩ፡፡ አሁን ወደ ሰባት ዓመት ሆነኝ፡፡ እዚያ ከመጣህ እንገናኛለን›› አለችኝ፡፡ የኢሜይል አድራሻየን ሰጠኋት፡፡ ወደ በሩ ስትገባ ዘወር ብላ ሰላም አለችኝ፡፡ አንደበቷ እንጅ ነፍስያዋ የሀገሬ ልጅ መሆንዋን ይነግራታልኮ፡፡

እኔም ከጥቂት ደቂቃዎች ወደ አውሮፕላኔ ገባሁ፡፡ ወደ አውስትራልያ ለመድረስ የሰባት ሰዓት በረራ ይጠብቀኛል፡፡ በቸር ሜልበርን ላይ እንገናኝ፡፡

ከብሩናይ ወደ አውስትራልያ መንገድ

የአቶ አማረ አረጋዊ ጋዜጣ ብቻ እንዲዘግበው በተፈቀደው መሰረት በቀደም ሶማሊያ ላይ ተከስክሶ የሰዎች ሕይወት የጠፋበት አንቶኖቭ 12 የተባለው ሩሲያ ሰራሽ አውሮፕላን አደጋ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁለተኛው አደጋ መሆኑን እ.ኤ አ በኦገስት 11,2013 ባሰፈረው ዘገባው ይነግረናል።ሌሎች ይህን ቢዘግቡት ምስጢር በማባከን የ”ብሔራዊ ደህንነትን”ሆነ ብሎ አደጋ ላይ በመጣል ወይም በዚያ በፈረደበት የሽብርተኛ ፍርደ ገምድል ሕግ ዘብጢያ ይወርዱ ነበር።ያም […]

ሙስሊም ወንድሞቻችን ሁለት አመት ለሚጠጋ ጊዜ እየተገደሉ ነው። በጽናት፤ በጀግንነትና በብልሀት እናም በመስዋእትነት የመብት ትግላቸውን ቀጥለዋል። በለተ – አውዳመት ኢድ አልፈጥርም የመስዋእትነት ደማቸውን፤ …ኢትዮያን የተቆጣጠራት የትግራይ ዱር አራዊት መንጋ አፍሷል። የሞቱትን ሁሉ አላህ በጀነት ነፍሳቸውን ያኑር ከማለት በቀር ምን ይባላል ? ለሁሉም ወገኖቻችን ለቤተሰቦቻቸው፤ ለዘመዶቻቸው አላህ ጥናቱን ይስጥ እላለሁ። በከንቱ ለፈሰሰ ደማቸውም እሱ በማያልቅበት ስልጣኑ […]

ከሰሜን አሜሪካው የኢትዮጵያውያን የስፖርት ፌዴሬሽን – ESFNA፤ የመላው ኢትዮጵያውያን ስፖርት ማኅበር – AESAONE እና ከጃኖ የሙዚቃ አባላት ጋር።