ነሃሴ ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢትዮጽያ ሃይማኖቶች ተቋማት ጉባዔ ዛሬ ከቀትር በሁዋላ በአ/አ አምባሳደር ቲያትር አካባቢ በሚገኘው ጽ/ቤቱ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አክራሪነትን ለመቃወም የፊታችን እሁድ ነሃሴ 26 ቀን በመስቀል አደባባይ ሰልፍ መጥራቱን አስታወቀ፡፡ በዕለቱ ሰማያዊ ፓርቲ ሁለተኛ ሰልፉን በመስቀል አደባባይ ለማድረግ በይፋ ለአስተዳደሩ አሳውቆ ምላሽ እየተጠባበቀ የሚገኝ ሲሆን ምናልባት የሃይማኖት ተቋማቱ ሰልፍ ለማካሄድ …

ነሃሴ ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ለኦሮሞ ህዝብ መብት በመታገል ላይ የነበረው የ37 ዓመቱ ወጣት ኢ/ር ተስፋሁን ጨመዳ ቃሊቲ እስር ቤት ውስጥ እንዳለ መሞቱ ታውቋል። ኢ/ሩ በምን ምክንያት እንደሞተ ግን አልታወቀም።  ከጓደኞቹ ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው ኢ/ር ተስፋሁን የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ከነበረበት ጌዜ ጀምሮ ገዢውን ፓርቲ ይቃወም ነበር። ኢ/ር ተስፋሁን ኬንያ በነበረበት ወቅት ምንም …

ነሃሴ ፳(ሃያ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከአባይ በፊት ዘረኝነት የወገድ በማለት መቃወማቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። የመንግስት ወኪሎች ተቃውሞውን በመፍራት ሊሰበሰቡበት ተከራይተውት የነበረውን አዳራሽ በመተው በሰዎች ቤት ስብሰባውን በግለሰቦች ቤት ለማድረግ ተገደዋል። በስፍራው ለተገኙት አንዳንድ አረጋውያን ለአባይ ቦንድ የሚገዙ ከሆነ የቤት መስሪያ ቦታ እንደሚሰጠቻው በስበሰባው መሪዎች ተነግሮአቸዋል። መንግስት በውጭ አገራት የሚያደርገው …

የርምጃውን ጅምር የወሰደው የአ/አ መካነ ሰማዕት ቅ/ቂርቆስ ደብር ሰበካ ጉባኤ ነው፡፡ የደብሩ የስብከተ ወንጌል ክፍል ጥብቅ ክትትል እንዲያደርግ ማሳሰቢያ ተሰጥቶታል፡፡ ለሰ/ጉባኤው የእግድ ውሳኔ ዝርዝር መረጃ የሰጠው የደብሩ ሰንበት ት/ቤት ነው፡፡ ሰንበት ት/ቤቱ ከአምስት ዓመት በፊት ከመናፍቃን ኅትመቶች ገልብጦ ባዘጋጀው በራሪ ወረቀት ምክንያት ከማንኛውም አገልግሎት አግዶ ክትትልና ማጣራት ሲያደርግበት ቆይቷል፡፡ ዲ/ን ኀይሉ በነገሌ ቦረና የሀ/ስብከቱ ስብከተ …

ኢንጂነር ተስፋሁን ጨመዳ ወኅኒ ውስጥ አረፉ
የሽብር ክሥ ተመሥርቶባቸው የዕድሜ ልክ እሥራት የተፈረደባቸው ኢንጂነር ተስፋሁን ጨመዳ ለሰባት ዓመታት እሥር ላይ ከቆዩ በኋላ እዚያው ወኅኒ ውስጥ ማረፋቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቪኦኤ ገለፀዋል፡፡

ፖሊስ የሰጠውን ማስረጃ አይተናል ያሉት እስከፍርዱ ድረስ ከይግባኝ በፊት ቆመውላቸው የነበሩት ጠበቃ አቶ ጥላሁን ታደሰ ኢንጂነር ተስፋሁን ያረፉት ባለፈው ዓርብ ሌሊት መሆኑን አመልክተው የፖሊሱ መረጀ እራሣቸውን ማጥፋታቸውን እንደሚጠቁም ጠቁመዋል፡፡

ኢንጂነር ተስፋሁን እራሣቸውን አጥፍተዋል የሚለውን መግለጫ ለማመን እንደሚቸገሩ የሚናገሩት አቶ ጥላሁን ታደሰ ሕክምና እንዲደረግላቸው በተደጋጋሚ ሲጠይቁ እንደነበረና የጠየቁትን አለማግኘታቸውን እንደሚያውቁ፤ ከእህታቸው ጋርም በማግስቱ ለመገናኘት ቀጠሮ ይዘው እንደነበረ ቤተሰብ እንደነገራቸው …

መጠለያ ​​
ኢትዮጵያ በምሥራቅ ተከሰተ የተባለውን ፖሊዮ እያጠናች ነው
ኢትዮጵያ እአአ ከ 2008 አም አንስቶ ማለት በአምስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በፖልዮ ማለትም በልጅነት ልምሻ የተያዘ ሰው እንደተገኘ ማስታወቋን የአሜሪካ ድምጽ ሬደዮ ዘጋቢ ሜሪ አሊስ ሳሊናስ ያነጋገረቻቸው የሮተሪ-ኢንተርናሽናል ፖሊዮን የማጥፋት ዓለምአቀፍ ዘመቻ አባል ካሮል ፓንዳክ መግለፃቸውን ዘግበናል፡፡

የታመችው ያልተከተበች የአንድ ዓመት ተኩል ሕፃን መሆኗን ያስታወቁት ፓንዳክ ሶማልያ ውስጥ አንድ መቶ የሚሆኑ፣ በሰሜን ኬንያ ደግሞ ከአሥር በላይ የሚሆኑ የፖልዮ ህሙማን እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡
ኢትዮጵያ በምሥራቅ ተከሰተ የተባለውን ፖሊዮ እያጠናች ነው ​​
“አካባቢው ለሶማሊያ ቅርበት ያለው በመሆኑ የቫይረሱ ወደዚያ መዛመት የሚደንቅ አይደለም፡፡ ይህ በኢትዮጵያ፣ ኬንያና ሶማሊያ ውስጥ …

መሠረት ደፋር በስቶክሆልም ዳያመንድ ሊግ በ 3 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር የዓመቱን የዓለም ፈጣን ጊዜ በማስመዝገብ አሸንፋለች። በሉዥኒኪ ሞስኩ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ 5 ሺህ የወርቅ ሜዳልያ ከወሰደች ከሁለት ሳምንት ባነሰ ጊዜ መሆኑ ነው መሠረት ይህን ድል የተቀዳጀችው።

በሐሙሱ የዳያመንድ ሊግ 3 ሺህ ሜትር አዲሱ የመሠረት ደፋር የዓመቱ ፈጣን ጊዜ 8 ደቂቃ ከ 30 ነጥብ 29 ሴኮንድ ነው።

ሌላዋ የኢትዮጵያ አትሌት ሲፋን ሐሰን የግሏን ፈጣን ጊዜ አስመዝግባ በሦስተኝነት ጨርሳለች።

መርሲ ቼሮኖ ከኬንያ የብሩን ሜዳልያ አጥልቃለች።

  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

ሄሊኮፕተሮቹ አገልግሎት እንዲሰጡ ለታሰበው ተግባር አመቺ እንዳልሆኑና የጥራት ደረጃቸውም ከጊዜው ጋር አብሮ የሚሄድ እንዳይደለ ዛሬ ታትሞ የወጣው ፍራንክፉርተር አልገማይነ የተባለው የጀርመን ጋዜጣ ዘግቧል ።

ሠፊዉ ዓለም የግብፅን እልቂት ፍጅት፤ የሌላዉን ዓለም አፀፋ በቅጡ ለማስተንተን እንደገና ጊዜ አልነበረዉም።ወይም የሰዉ ደም ጠጥቶ ደም የሚጠማዉ ምድር ለሌላ ጥማቱ እርካታ ሶሪያን በመርዝ ጋዝ ሲያጥናት ትልቁም፥ ትንሹም፥ ምሥራቁም ምዕራቡም ቱጃሩም፥ ሐያሉም በሶሪያ የእልቂት ዜማ ያንጎራጉር ሌላዉ ይፎክር-ይዝት ገባ።

የድርጅቱ አመራር አባላት አዲስ አበባ ውስጥ በሰጡት መግለጫ የኤርትራ መንግሥት በተለያዩ ጊዜያት በሚወስዳቸው እርምጃዎች የቀይ ባህር አፋሮችን እንደሚገድል እንደሚያስርና ከቀያቸው እንዲሰደዱ እንደሚያደርግ ተናግረዋል ።

ለስድስት አመት ኤፈርትን ሲመሩ የቆዩት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከሃላፊነት መነሳት ተከትሎ በሕወሐት ውስጥ ውጥረት መንገሱን ምንጮች አመለከቱ። የኤፈርት ቦርድ ሰብሳቢ በነበሩት ባለቤታቸው አቶ መለስ አማካይነት ዳይሬክተር ተደርገው አዜብ መሾማቸውን ያስታወሱት ምንጮች፣ ከመለስ ሕልፈት በኋላ ቦታውን የተረከቡት ኤርትራዊው ቴዎድሮስ ሃጎስ መሆናቸውን፣ እንዲሁም ዳይሬክተር የመሾምና የመሻር ስልጣኑ የቦርዱ መሆኑን ያስረዳሉ። አዜብ ከኤፈርት እንዲወገዱ የተደረገው ግን በነቴዎድሮስ ሃጎስ […]

በጥቅመኝነት ላይ የተመሠረተ የአገልጋዮች ምደባና ስምሪት፣ ለምእመናን ወቅታዊ ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ አለመስጠት፣ በዕቅበተ እምነት ሊቀ ጳጳሱ ይታይባቸዋል የሚባለው ቸልተኝነት እና የጎጠኝነት ዝንባሌ በዋናነት ተጠቅሰዋል፡፡ *       *      * ሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በቅርቡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሥራች አባል ለኾነችበት ለመላው አፍሪቃ አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ በምክትል ፕሬዝዳንትነት መመረጣቸው ለውጭ ግንኙነታችን መልካም ዜና ነው፡፡ ከጉባኤው …

የቀድሞው ጠ/ሚንስትር መለስ ዜናዊ፣ አምና ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ ወዲህ የአገሪቱ ፖለቲካዊ ፣ ኤኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ገጽ ምን ይመስላል?

አባይ የህዝብ እንጂ የፖለቲካ መጠቀሚያ አይሆንም!

Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 19  ቀን 2004 ዓ.ም. August 25, 2013)የአባይ ግድብ ሂደት ግልጻማነት የጎደለውና ኢትዮጵያዊያን ያልመከሩበት አገዛዙ የፈጠረው የፖለቲካ መጠቀሚያ ነው የሚሉ ኢትዮጵያዊያን በቫንኩቨር ካናዳ የተጠራውን የግድብ ገንዘብ ማሰባሰቢያ ምሽት በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸው ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አንድነት ታርቲ ዛሬ በባሌ ሮቤ የሚያደርገውን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በኦህዴድ ባለስልጣናትና በደህንነት ሀይሎች አፈና ተፈፀመበት፡፡ ሰልፉን ለማደናቀፍ የአካባቢው ባለስልጣናት ትላንት ምሽት የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት ካረፉበት ታይታኒክ ሆቴል ንብረታቸውን ሳይዙ በግዳጅ እንዲወጡ ከመደረጉም በላይ አብዛኞቹ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና የቅስቀሳ ቡድን አባላት ታግተዋል፡፡ በስፍራው የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና የቅስቀሳ ቡድን አባላት ደህንነት አደጋ ላይ እንደሆነም ከስፍራው […]

አንድነት ሰላማዊ እንቅስቃሴ እያደረገ ነዉ። አገዛዙ ግን ሕገ መንግስቱን በመርገጥ የሰለጠነን ሳይሆን፣ የዛቻን ፖለቲካ እያራገበ ነዉ። «በሮቢ ደም ሊፈስ ይችላል» በማለት ማስፈራሪያዊች እየቀረቡ ሲሆን፣ ፖሊሲስ ሰልፍን የምታደርጉ ከሆነ እርምጃ እንደሚወስድ አሳዉቀዋል። የሮቢ የአገዛዙ አስተዳዳሪዎች፣ 20 ሰዎች የሚገኙበት የ«ሽማግሌዎች» ቡድን አቋቁመዋል። ይሀ ቡድን ከጥቂት ሰዓት በኋላ ከሚሊየነም ድምጽ ለነጻነት ግብረ ኃይል ጋር ዉይይት ያደርጋል። ኮምቴዉ፣ ስብሰባው […]

ግብፅ (ምስር) እንደሃገር ከምትታውቅበት ማለትም ከፈሮኦኖች ዘመን ጀምሮ ፤ የታሪኳም ሆነ የህልውናዋ መሰረት አባይ ነው። አባይ ባይኖር የግብፅ የቆየና ጥንታዊ ታሪኳ የለም ፤ የፈርኦኖች ታሪክ የለም፤ አባይ ባይኖር የክሊዮፓትራ ታሪክ የለም ። ባጠቃላይ አባይ ባይኖር ግብፅም ታሪኳም፤ ጥንታዊ ስልጣኔዋም፤ የአለማችንን …

የግብፅና ኢትዮጵያ መጪው ዘመን ምን ሊመስል ይችል ይሆን? Read more »

በማዳጋስካር ከአራት ዓመት ተኩል በፊት መፈንቅለ መንግሥት ከተካሄደ ወዲህ ደሴቲቱ እከፋ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ትገኛለች። በሀገሪቱ ይካሄዳል የተባለው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በተደጋጋሚ መተላለፉ የሚታወስ ነው።

የዛሬው የሙዚቃ ቃና ፕሮግራም ስለ Martin Luther King, I have a dream ንግግር 50ኛ አመት በአል የሚዘክሩ ዜማዎችን እና ሙዚቃ ነክ ዜናዎችን ያስተናግዳል፡፡

የአንድነት ፓርቲ የቅስቀሳ ቡድን አባላት የሚደርስባቸውን ጫና ተቋቁመው በባሌ ሮቤ የተሳካ ቅስቀሳ በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ የቅስቀሳ ቡድኑ አባላት “የህዝቡ አቀባበል መንግስት የሚያደርስብንን ጫና ተቋቁመን ስራችንን እንድናከናውን ረድቶናል” ብለዋል፡፡ በባሌ ሮቤ ከንቲባ ጽ/ቤት አራት የአንድነት ፓርቲ ተወካዮች ለውይይት ተጠርተው ታግተው የነበሩ ሲሆን እነዚሁ የአንድነት ፓርቲ ተወካዮችና የቅስቀሳ ብድን አባላት አሁን የተለቀቁ ቢሆንም በሁለት መኪኖች የተጀመረውን ቅስቀሳ […]

የአንድነት ፓርቲ የቅስቀሳ ቡድን መኪናና በባጃጆችን በመጠቀም የተቀናጀ ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የፍቼ ከተማ የኢህአዴግ ካድሬዎችና የመንግስት ሹመኞች ህዝቡ ለነገው ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይወጣ ቤት ለቤት በመሄድ በማስፈራራት ላይ ቢገኙም ህዝቡ በነገው የተቃውሞ ሰልፍ ብሶቱን ለመግለፅ ተዘጋጅቷል፡፡ ዘግይቶ በደረሰን ዜና በፍቼ ከተማ የሚገኘውን የአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት የመንግስት የደህንነት ሀይሎች ሰብረው በመግባት በቢሮው ውስት ያሉትን አባላት ቢያባርሩም […]

  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

ነሃሴ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከአዲስ አበባ ወደ ወልድያ ሲጓዝ የነበረ ሚኒባስ አውቶቡስ ደሴ አካባቢ ሲደርስ በመገልበጡ የ21 ሰዎች ህይወት ጠፋ፣ የዛሬውን ጨምሮ በአንድ ሳምንት ውስጥ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 66 ደርሶአል። የአደጋው  መንስኤ ጥራት የሌለው የአስፓልት መንገድ በጎርፍ በመቆረጡ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። የወልድያ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ለኢሳት እንደገለጸው ደግሞ የአደጋውን መንስኤ …

ነሃሴ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዛሬ በአንዋር መስጂድ የጁምአ ሰላታቸውን በመስገድ ላይ የነበሩ ሙስሊም ሴቶች በፖሊስ መደብደባቸውን የ ኢሳት ወኪል ከስፍራው ዘግቧል። በጁምአ ሰላት ላይ የነበሩት ሙስሊም ሴቶች የተደበደቡት፤ “ሶላት መስገድ የምትችሉት በግቢ ውስጥ እንጂ ከግቢ ውጪ አንጥፋችሁ አትሰግዱም” ተብለው በውጪ እንዳይሰግዱ በፖሊሶች መከልከላቸውን ተከትሎ በተፈጠረ አለመግባባት ነው። ሙስሊም ሴቶቹ ሁልጊዜ እንደሚያደርጉት …

በመጪው እሁድ ነሃሴ 19 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚገኘው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት/መ.ኢ.አ.ድ/ ዋና ጽ/ቤት 33ቱ ፓርቲዎች ለጠሩት ህዝባዊ ውይይት የመኪና ላይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ የፓርቲዎቹ አባላት በህገወጥ መንገድ ታስረዋል፡፡ አቶ ደመላሽ፣ አቶ አብርሃም ፣ አቶ አታላይ በለው፣ አቶ እዮብዘርና አቶ መላኩ መሰለ የተባሉት አባላት የቅስቀሳ መከናውን ከያዘው ሹፌርና ረዳት ጋር ታስረዋል፡፡ የፓርቲዎቹ አመራሮች […]

ነሃሴ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከባህርዳር የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው ኢህአዴግ ለከተማው ነዋሪዎች አዲስ የአባልነትና አንድ ለአምስት አባልነት መለያ ወረቀት ያዘጋጀ ሲሆን፣ ይህንን ወረቀት ያላሳየ ሰው በመንግስት የሚከፋፈለውን ስኳር አያገኝም። አንዳንድ ነዋሪዎች ችግራቸውን በኤፍ ኤም ራዲዮ ላይ ቢናገሩም ምንም መፍትሄ እንደሌለው እንዳወቁ ለኢሳት ተናግረዋል። በጉዳዩ ዙሪያ የክልሉን ህዝብ ግንኙነት ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። …

ነሃሴ ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አለም የጤና ድርጅት እንደገለጸው በያዝነው ወር በጣለው ዝናብ ከ50 በላይ ሰዎች ሞተው፣ ከ300 ሺ ያላነሱት ደግሞ ተፈናቅለዋል። በተለይ በዋና ከተማዋ ካርቱም ላለፉት 25 አመታት ያልታየ ጎርፍ መታየቱን ድርጅቱ አስታውቋል። በአገሪቱ ካሉ 18 ግዛቶች መካከል በ14 ላይ ከፍተኛ የንብረት መውደምም ተከስታል።

በመጪው እሁድ ነሃሴ 19 ቀን 2005 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ሊያደርግ የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ወደ ጷጉሜ 3 መዘዋወሩን የአንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ግብረ ኃይል ማምሻውን አስታወቀ፡፡ ግብረኃይሉ እንዳስታወቀው የአዳማ ከተማ አስተዳደር ለአንድነት ፓርቲ በፃፈው ደብዳቤ ነሃሴ 19 በከተማው ስብሰባ በመኖሩና የሀይል እጥረትም ስላለበት አንድነት ሰላማዊ ሰልፉን እንዲያስተላልፍ ጠይቋል፡፡ አንድነት ፓርቲም የቀረበለትን ጥያቄ ከግምት በማስገባት ሰልፉን […]

ሀሙስ ነሃሴ 16 ቀን 2005 ዓ.ም የአንድነት ፓርቲ ተወካዮች ከሮቤ ከተማ ከንቲባ፣ ምክትል ከንቲባ፣ የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊና ከከተማው ካቢኔዎች ጋር 3 ሰዓት የፈጀ ውይይት አድርገዋል፡፡ ባለስልጣናቱ “አንድነት ሰላማዊ ሰልፉን ማድረግ አይችልም፤ እኛ ከፍተኛ የሆነ የፀጥታ ስጋት አለብን፡፡ የቀድሞው ጠ/ሚር መለስ በፓርላማ እንደተናገሩት በአካባቢያችን የአልቃይዳ ክንፍ አለ” ብለዋል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ተወካዮች በበኩላቸው “በባሌ አካባቢ ያለውን የፀጥታ […]

ጠጋ ብለው ሳያውቁ፤ የቀኝ ጽንፈኛ አመለካከታቸውን ብቻ በማንጸባረቅ፤ የውጭ ተወላጆችን፣ በጭፍን የሚጠሉ ፣ የሚያጥላሉ አካራሪ ጀርመናውያን በየጊዜው ነው ተቃውሞአቸውን የሚያሰሙት።

በምርጫ ሥልጣን የያዙት መሀመድ ሙርሲ በጦር ኃይሉ ከሥልጣን ተነስተው በታሰሩ በ7 ሳምንታቸው ሙባረክ ከእስር ቤት መውጣታቸው በሙባረክ ተቃዋሚዎች ዘንድ የግብፅ ህዝባዊ ንቅናቄ የመቀልበሱ ምልክት ተደርጎ ተወስዷል ።

ያኒንግ እንደሚያምኑት የአሜሪካ ጦር ሶሪያ ከዘመተ የደማስቆ መንግሥትን የምትደግፈዉ ኢራን አሜሪካኖች ነገር እንደፈለጓት ነዉ የምትቆጥረዉ።የእስራኤል ደሕንነትም ላደጋ መጋለጡ አይቀርም።«ከዚሕም በተጨማሪ» ይላሉ ያኒንግ አሜሪካኖች «ጣልቃ መግባት» መጀመሪያዉ እንጂ ፍፃሜዉ እንደማይታወቅ ካለፈዉ አስር ዓመት ልምዳቸዉ በቅጡ መማር አለባቸዉ።