አርኣያ ጌታቸው Araya Getachewአርኣያ ጌታቸው

የዘንደሮ ክረምት ከቀደምቶቹ በጥቂቱ ጠንከር ያለና ብዙዎችን በተለይም አዲስ አበቤዎችን እያማረረ ነው። ሌላው “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” የሚያስብለው ደግሞ የከተማዋ መንገዶች በአብዛኛው ጥገና ላይ መሆናቸውና በዚህም ሳቢያ የበርካቶች መኖርያና የንግድ ሱቆቻቸው መፍረሳቸው ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዩሱፍ ያሲን

የአሜሪካ ድምፅና የዶቼቬሌ አማርኛ ራዲዮ ፕሮግራሞች ላይ የቁጫ ሕዝብ የራሱን ማንነት የመወሰን ጉዳይ አስመልክቶ ለመንግሥት ጥያቄ ያቀረቡ ሰዎች መታሰራቸው ዜና በቅርቡ ተዘግቦ ሰምተናል። 40 የሚሆኑ የአካባቢ ሽማግሌዎች እነዚህ የተሳሩ ሰዎችን ለማስፈታት አዲስ አባባ ድረስ መምጣታቸውንም ተዘግቦዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

እ ጎ አ በ 2030 ምናልባትም ከዚያ ቀደም ብለው ሰዎች ወደ ማርስ ይጓዙ ይሆናል። ለጤና የሚስማማ አየር በሌለባት ፣ ሣር ቅጠል በማይታይባት፣ ቀይ አቧራ በሸፈናት ማርስ ፤ እንዴት ኅልውናቸውን ጠብቀው ይቆያሉ? በጤናስ መመለስ ይቻላል ወይ? ወደ ማርስ

በግብፅ መዲና በካይሮ፤ ከሥልጣን የተወገዱት የሙሐመድ ሙርሲ ደጋፊዎች በተቃውሞ ከመሸጉባቸው አደባባዮች እንዲነሱ ለማድረግ ፖሊስ በወሰደው የኃይል እርምጃ፣ ቢያንስ 124 ሰዎች መገደላቸውን AFP አስታወቀ። በሌላ ዜና የሞቱት 95 ፤ የቆሰሉት ደግሞ

አንድነት ፓርቲ የጀመረውን ህዝባዊ ንቅናቄ ለማስተጓጎል ከፍተኛ አበል በመክፈል ለአባላቱ ስልጠና ማዘጋጀቱን ለኢህአዴግ ቅርበት ያላቸው የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ጠቆሙ፡፡ አንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት በሚል መሪ ቃል የጀመረው ህዝባዊ ንቅናቄ ህዝባዊ ተቀባይነት ማግኘቱንና በስኬት መቀጠሉን ተከትሎ ኢህአዴግ “አንድነት ፓርቲንና ንቅናቄውን እንዴት ማስቆም ይቻላል” በሚል በከፍተኛ አመራሮቹ ውይይት ካደረገ በኋላ በመላ ሀገሪቱ ፀረ አንድነት ፓርቲ ስልጠና […]

አፍሪቃ ያለፈውን አሠርተ-ዓመት ባልተቋረጠ የኤኮኖሚ ዕድገት በማሳለፍ ለውጭው ዓለም የመዋዕለ-ነዋይ ባለቤቶች ከመቼውም ይልቅ ማራኪ እየሆነች መምጣቷ በየጊዜው የሚጠቀስ ጉዳይ ነው።

የፕሬዝዳት ማሕሙድ አባስ ፅሕፈት ቤት «ለድርድሩ ትልቅ እንቅፋት» ባለዉ የሠፈራ መንደር ግንባታ ላይ ሁለቱን ወገኖች የምታደራድረዉ ዩናይትድ ስቴትስ ግልፅ እንድታሳዉቅ ጠይቋል። የዩናይትድ ስቴትስ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትር ጆን ኬሪ የመንግሥታቸዉን ግልፅ አቋም ግልፅ ማድረጋቸዉ አልቀረም።

ባለፈዉ ሳምንት ከሊቢያ ባህር ዳርቻ በአንድ ትልቅ አሮጌ ጀልባ ተሳፍረዉ ወደሞልታ ደሴት ሲቃረቡ ጀልባዉ ተበላሽቶ ከመቶ በላይ ስደተኞች ነፍሳቸዉን የሚታደግ እስኪያገኙ ባህር ላይ ለቀናት ሲጨነቁ ቆይተዋል።

ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብለዉ የተጠበቁት ቢላል የተሰኘዉ የኢንተርኔት ራዲዮ ሁለት ጋዜጠኞች እስከ ቀኑ አስር ሰዓት ድረስ ወደፍርድ ቤቱ ብቅ እንዳላሉ ተገለጸ።

የሞስኮዉ ሉዙኒኪ ኦሎምፒክ ስታዲዮም ከ33ዓመታት የሻምበል ምሩጽ ይፍጠር ድርብ ድልና ከሻምበል እሸቱ ቱራ አስደናቂ ዉጤት በኋላ ትናንት ማምሻዉን በመካከለኛ ርቀት ሩጫ ታሪክ ተሠራበት ትላለች ሞስኮ የምትገኘዉ ዘጋቢያችን ሃይማኖት ጥሩነህ።

ትብብራችን የሙስሊሙ ማኅበረሰብ በህገ መንግሥቱ የተረጋገጠውን የእምነት ነጻነት መብቱን ተከትሎ ጣልቃ አትግብቡኝ ሲል ያቀረባቸውን ሦስት ጥያቄዎች በሚመለከት መንግሥት ከሰለጠነ የመፍትሄ ውይይት ፋንታ ከሚወስዳቸው ህገወጥ እርምጃዎችና ፍረጃ እንዲቆጠብ፣ በፈጠራ የሽብር ወንጀል ያሰራቸውን የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት እንዲፈታና ለጥያቄዎቹም ፍትሀዊ ምላሽ እንዲሰጥ የካቲት 05/2005 ባወጣነውና ሌሎች መግለጫዎች በተደጋጋሚ መጠየቁ ይታወሳል፡፡ ገዢው ፓርቲና መንግሥት ግን በሙስሊሙ ማኅበረሰብ፣ በሙስሊሙ […]

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢድ አልፈጥርን በዓል ለማክበር ባለፈው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ከተጓዙ በርካታ የእስልምና እምነት ተከታዮች መካከል አስራ ሁለት የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው እንደሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ለኢሳት አስታወቁ፡፡ አራት የአሜሪካ፣ ሁለት የሲዊዲን፣ አንድ የአውስትራሊያና አምስት የተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ኢትዮጵያውያኑ ከትላንትናው እለት ጀምሮ በማዕከላዊ ማረሚያ ቤት …

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአሜሪካ ፖሊሶች ከኢትዮጵያ ለምስክርነት መጥቶ የጠፋን ኢትዮጵያዊ ዱካ ለማግኘት ፍለጋ ላይ መሆናቸውን ሲአትል ኒውስ ዛሬ ዘገበ፡፡ ካሳይ ወልደ ፃድቅ የተባለው ኢትዮጵያዊ አሜሪካዊያኖቹ ጥንዶች ከኢትዮጵያ በማደጎ ያመጧትን ልጅ ገድላችኋል ተብለው ለተከሰሱበት ወንጀል አቃቢ ህግ ለምስክርነት ማስረጃ ይሆን ዘንድ ብለው ነበር ከኢትዮጵያ ያመጡት፡፡ ካሳይ በፍርድ ሂደት ላይ ላለው ጉዳይ ባለፈው አርብ …

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተባበሩት አለም አቀፍ የምግብ ድርጅት በኦሮሚያና አማራ ክልሎች በተለያዩ ግጭቶችና አደጋዎች ጉዳት ለደረሰባቸው 250 ሺህ ዜጎች አስቸኳይ እርዳታ መስጠት መጀመሩን ለኢሳት በላከው መግለጫ አስታወቀ፡፡ ድርጅቱ በኦሮሚያና አማራ ደርሶ ስለነበረው ግጭት ዝርዝር መረጃን ከመስጠት ቢቆጠብም 250ሺህ ለሆኑት ዜጎች ግን ጊዜያዊ የሆነ የምግብና የገንዘብ እርዳታ መስጠት ላይ እንደሆነ ገልጿል፡፡       …

  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

አጎአ – አዲስ አበባ – 2013 ​​
አጎአ – ከንግድ አስከ አቅም ግንባታ
ዩናይትድ ስቴትስ ለአፍሪካ ሀገሮች ያወጣችው ከቀረጥና ታሪፍ ነፃ የንግድ ተጠቃሚነት ዕድል ሕግ አጎአ ከንግድ በተጨማሪ የቴክኒክና የአቅም ግንባታ ድጋፍ ማድረግ እንዳለበት በአዲስ አበባ ጉባዔ ላይ የተሣተፉ ኢትዮጵያዊያን የንግድ ማኅበረስብ አባላት አስታወቁ።

ኢትዮጵያ የአጎአ የንግድ ዕድልን ተጠቅማ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ የምትልከው የምርት መጠን ቢጨምርም ከዚህም በላይ የማደግ አቅም እንዳለው የኢትዮጵያ መንግሥት ይገልፃል።

ለተጨማሪ ዝርዝር የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

የቢላል ራዲዮ ጋዜጠኞች መታሠር ያሣዘነው መሆኑን ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች ደኅንነትና የፕሬስ ነፃነት ተሟጋች ድርጅት ሲፒጄ አስታውቋል፡፡

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንዲት አራስን ጨምሮ ከ19 ያላነሱ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ለአንድ ወር ያክል በእስር ካሳለፉ በሁዋላ ዛሬ ፍርድ ቤት ቢቀርቡም ምንም መፍትሄ ሳይሰጥ ወደ እስር ቤት እንደሚለሱ ተደርጓል። የአካባቢው ሰዎች ፍትህ ለማግኘት በፍርድ ቤቱ አካባቢ ቢሰባሰቡም በፖሊስ ሀይል እንዲበተኑ ተድርጓል። አንዳንድ የከተማዋ ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጹት ፍርድ ቤቱ በተከሳሾች ላይ በቂ ማስረጃ ያልቀረበለት …

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ መለስ ዜናዊን አንደኛ የሙት አመት መታሰቢያ በማድረግ በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች የዝክረ መለስ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ነው። በአዲስ አበባ 100 ሄክታር መሬት ስፋት ያለው ቦታ ከሀያት ሆስፒታል ፊት ለፊት ለመለስ ማእከል ግንባታ ተከልሏል። መስተዳድሩ ማእከሉን እንደሚያሰራ የአዲስ አበባ መስተዳድር አዲሱ ከንቲባ ድሪባ ኩማ የመሰረት ድንጋይ ባስቀመጡበት ወቅት ገልጸዋል። ግንባታው …

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የኦሮሚኛ ፕሮግራም ባልደረባ የነበረው ባለቤቷ ጋዜጠኛ ዳበሳ ዋቅጅራ ከሦስት ዓመት እስር በሁዋላ ከአገር መውጣቱን ተከትሎ   በኦነግ አባልነት ክስ ተመስርቶባት  ታስራ የቆየችው  ጋዜጠኛ ሌሊሴ ወዳጆ ከ እስር ተፈታች። በ 1995 ዓመተ ምህረት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እየሠራ ሳለ  ድንገት ለእስር የተዳረገው ጋዜጠኛ ዻበሳ ዋቅጅራ አንዳችም ክስ ሳይመሰረትበት ለሦስት ዓመታት በእስር …

በተመስገን ደሳለኝ
‹‹በድብልቅልቁ አምላክ››

መግቢያ
ዛሬ በስሱ ላነሳው ያሰብኩትን አ ንዳ አለቃ አፅሜ በምኒልክ ዘመን ካሳተሙት አንድያ መጽሐፋቸው ላይ ባገኘሁት ታሪክ ል ምር፤ እንዲህም ይነበባል፡- ‹‹በሸዋ መርድ አዝማች ኃይሌ፣ በሣህለ ሥላሴ አልጋ ከተቀመጡ በኋላ ከአቶ ሰይፉ ጋር ቂሙ የማይበርድ የቅድስት ኃይማኖት ጦርነት ተ መረ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከማልታና ከግሪክ ቀጥሎ በርካታ አፍሪቃውያን ስደተኞች የሚጎርፉባት አውሮፓዊት ሃገር ኢጣልያ ናት።በአንዳንድ የኢጣልያ ግዛቶች መንግሥት ህገ ወጥ የሚላቸው አፍሪቃውያን ስደተኞች ደግሞ በኢጣልያ ጎስቋላ ህይወት ነው የሚገፉት።

የሴት ልጅ ግርዛት በተለያዩ 28 ሃገራት ተግባራዊ እንደሚሆን ሲነገር የቆየ ጉዳይ ነዉ። አሁን አሁን ግን በሰዎች ከሀገር ወደሀገር መዟዟር ምክንያት ቀድሞ በማይታወቅበት አካባቢ ሁሉ እየተዳረሰ መሆኑ እየተነገረ ነዉ።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፊደሪሽን የልዑካን ቡድን ትናንት ባካሄደዉ አስቸኳይ ስብሰባ ሞስኮ በመካሄድ ላይ ባለው 14ኛዉ የዓለም አትሌቲክስ ሻንፒዮና ባለፈዉ ቅዳሜ በተካሄደዉ የሴቶች ማራቶን ዉድድር ላይ ኢትዮጵያን ወክለዉ፤

የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ኢብራሂም ቡባከር ኬይታ የማሊ 2ኛ ዙር ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አሸናፊ ሆኑ። ምንም እንኳን የምርጫው ውጤት በይፋ ባይወጣም በኬይታ አንፃር ለከፍተኛው የሀገሪቱ ሥልጣን የተወዳደሩት የቀድሞው የገንዘብ ሚንስትር ሱማይላ ሲሴ ትናንት ባልተለመደ ሁኔታ ሽንፈታቸውን በመቀበል

በሚኪያስ በቀለ    
እንደ መነሻ፤ የግብጽ አብዮቶች
ግብጽን ለሠላሳ ዓመታት ያስተዳደራት የሁስኒ ሙባረክ መንግሥት ወዳጆቹን በሙስና አበለፀገ፣   የኑሮ ውድነትን ከማየት በቀር መፍትሔ ማምጣት አቃተው፡፡ በቱንዚያ የሕዝቡን ሥልጣን ያዩት የግብጽ ሕዝቦች በቃን እንዲሉ ምክንያት ሆናቸው፡፡ ሠላሳ ዓመታት ተንደላቀው ሀገሪቷን ያስተዳደሯት፤ ሙባረክን ጨምሮ የተለያዩ ኃላፊዎች ዕጣ ፈንታቸው በሰልፉ ላይ የተሳተፉ ግለሰቦችን በማስገደል እና በፈፀሙት ሰፊ የሙስና ተግባር ችሎት መቆም ሆነ፡፡ በመቀጠል የወታደራዊ መንግሥት ግብጽን ያስተዳድር ጀመር፡፡ አሰተዳደሩን በሲቪል ለመቀየር ሀገራዊ ምርጫ ተሰናዳ፡፡
በሙርሲ የሚመራውና በሙስሊም ወንድማማቾች የተመሠረተው የነጻነት እና ፍትሕ ፓርቲ (Freedom and Justice Party) አባላት 47.1 በመቶ በሆነ ጠባብ አብላጫ ድምጽ ግብጽን ለማስተዳደር ምክር ቤቱን ተቀላቀሉ፡፡ ሙሐመድ ሙርሲም 51.7 በመቶ ድምጽ አግኝተው የሃገሪቷ ጠቅላይ ገዥ ሆኑ፡፡ ነገር ግን ፕሬዘዳንት ሙርሲ የሥልጣን መንበራቸውን ከያዙ በኋላ ውሳኔያቸው በፍርድ ቤት ሳይቀር አይተችም የሚል መመሪያ አወጡ፡፡ የሀገሪቷን ኢኮኖሚ ቁልቁል ለቀቁት፡፡ ሕዝቡ የሙባረክ አስተዳደር በምን ጣዕሙ ይል ጀመር፡፡ የታህሪር አደባባይ በአዲሱ ፕሬዘዳንት ላይ ተቃውሞ በሚያቀርቡ ግብጻዊያን በድጋሚ ተሞላች፡፡ እራሳቸው የሾሙዋቸው የወታደሪያዊ ኃላፊዎች ሙርሲ ለሃገሪቷ መፍትሄ ማምጣት አይችሉም አሉ፡፡ አደባባይ የወጡትን ሰዎች ፍላጎት እንዲያሟሉ እና ውጥረቱን እንዲያረግቡ የ48 ሰዓት ገደብ አውጡላቸው፡፡ ሙርሲ አሻፈረኝ አሉ፡፡ በጭብጨባ በተሾሙ በዓመታቸው በወታደሩ ጉልበት እና በሕዝቡ ጩኸት ከመንበራቸው ተነሱ፡፡ የሙርሲ ደጋፊዎችም ዲሞክራሲ ለእስላም አይሠራምን? ብለው ጠየቁ፡፡ የመረጥናቸው ፕሬዘዳንት በመፈንቅለ መንግሥት ነው የተነሱትና ወደ ሥልጣናቸው ይመለሱ በሚል አመጻቸውን አቀጣጠሉ፡፡ ፖሊስ እና ወታደሩ በከፈቱት ተኩስ 54 የሙርሲ ደጋፊዎች ሐምሌ 2 ቀን ተገደሉ፡፡ አንዳንዶች በመሣሪያም ሳይቀር እንዋጋለን ብለው ሲያስተጋቡ ተደመጡ፡፡

በናይል ጉዳይ ተጠመዶ የከረመው የግብጽ መገናኛ ብዙሃን ለአዲሱ አብዮት ቦታውን ለቀቀ፡፡ የወታደራዊው ተቋም በድጋሚ አዲስ የሽግግር መንግስት አቋቋመ፡፡ የሽግግር መንግሥቱ ጊዜያዊ ፕሬዘዳንት ከፀደቀ 7 ወር ያስቆጠረውን ሕገ መንግሥት እንዲያሻሽሉ 10 የሕግ ባለሙያዎችን ያካተተ ኮሚቴ እንዲዋቀር መመሪያ አወጡ፡፡ ግብጽም እንዲሁ በሁለት ዓመት ሁለት አብዮቶችን አስተናገደች፡፡
የናይል ፖለቲካ፤ የሙርሲ አካሄድ
መሐመድ ሙርሲ ጊዜ መለወጡን ግምት ውስጥ ሳይከቱ፣ ኢትዮጵያ ‘ግድብ በራሴ ወጪ አሠራለሁ’ ማለቷን ሳያጤኑ፣ በፊት ከነበሩት የግብጽ አስተዳደሮች ባልተለየ የራስጌ ተፋሰስ ሀገሮች በናይል ላይ ምንም ፕሮጀክት መሥራት አይችሉም፣ ናይል የግብጽ ብቻ ነው የሚል አመለካከት ሲያራምዱ ተስተውለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት የሕዳሴውን ግድብ ለመገንባት ውኃውን 500 ሜትር ማስቀየሱን ካሳወቀበት ጊዜ ተከትሎ በፕሬዘዳንታዊ ቤተመንግሥታቸው የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮችን ሰብስበው ኦነግ እና ኦጋዴንን ከመርዳት፣ ግብጽ መሳሪያ እየገዛች ነው የሚል የውሸት መረጃ እስከመልቀቅ እና ሁሉም አማራጭ ክፍት ነው እስከሚል አሳፋሪ ውይይት በቀጥታ የቴሊቪዥን ስርጭት አሳዩ፡፡ ‘የናይልን አንድ ጠብታ ውኃ ሳይቀር እንጠብቃለን’ ብለው ስብሰባውን ሲዘጉ ተስተዋሉ፡፡ ‘ናይል ከቀነሰ አማራጫችን ደማችን ነው’ ብለው ከበፊት ፕሬዘዳንቶች ባልተለየ የጦርነት ታንቡር አስጋቡ፡፡ የግብጽ አርበኝነታቸውን ለማሳየት ‘የግብጽ ሕዝብ አንድ መሆን አለበት’ በማለት የውስጥ ተቃውሟቸውን ለማብረድ ሞክሩ፡፡ ብዙም ባያዛልቃቸውም፡፡
ሙርሲ የተሳሳቱት ኢትዮጵያ ከበፊቱ በተሻለ መረጋጋቷ እና ለግንባታው ከሀገር ውስጥ ወጪዎች መጠቀሟ ግብጽ ግንባታውን ለማስቆም የሚያስችላትን አጋጣሚ ማጥበቡን ነው፡፡ የኢሕአዴግን መንግሥት ለማናጋትም ሆነ የግድቡን ወጪ ማስከልከል እንደ በፊቱ ቀላል እንዳልሆነ ዘነጉት፡፡ የተፋሰስ ሀገራቱ የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያበረታታ የሕግ ማዕቀፍ በመፈረም መተባበራቸውን ከወረቀት የዘለለ ትርጉም አይኖረውም የሚል አቋም አራመዱ፡፡ የውኃ ጦርነት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያስተች እና የማያዋጣ ተግባር መሆኑን ከግምት ሳይከቱ ማስፈራራት ተያያዙ፡፡ በተቃራኒው የኢትዮጵያ መንግሥት ይህን አስመልክቶ የወሰደው እርምጃ የተረጋጋና የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያበረታታ ሆኖ መቀጠሉ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነትን እንድታገኝ እና በትክክለኛው አቅጣጫ እንደተራመደች አስመሰከረ፡፡
በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ የሕዳሴውን ግድብ እንዳታስፈጽም ከግብጽ ሊደርስባት የሚችለው ብቸኛ ጥቃት ለውስጥ ተቃዋሚዎች እና ለሽምቅ ተዋጊዎች መርዳት ይመስለኛል፡፡ የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው የተለመደ የውጊያ ስልት ነው፡፡ ሕውኀት ከግብጽ ባገኘው እርዳታ ደርግ በአባይ ላይ ያስጀመረውን ግድብ መምታቱ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ መንግሥት በውስጥ ያሉትን እንደ ኦጋዴን እና ግንቦት 7 ያሉ ታጣቂዎችን አሸባሪ ከማለት ከልማት ተጠቃሚ በማድረግ ለጥያቂያቸው ምላሽ መስጠት ይኖርበታል፡፡ የሙስሊሙን ማኅበረሰብ እና የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ጥያቄ በአግባቡ በመመልስ አንድ ኢትዮጵያን መመሥረት ከግብጽ ጥቃት ለመዳን ያለው ብቸኛ አማራጭ ነው፡፡ አባይን ስንገድብ የዜጎችን ሰብኣዊ መብት ጥሰት አብሮ መገደብ ያስፈልጋል፡፡ ለግድቡ የሚሰበሰቡትን ገንዘቦች በግልጽነት የተለያዩ የኅብረተሰቡን ክፍሎች ባሳተፈ መልኩ ኦዲት መደረግ እና ግድቡ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የጋራ ፕሮጀክትነቱ መረጋገጥ አለበት፡፡
የሕዳሴው ግድብ በዋነኛነት ለኃይል ማመንጫ ጥቅም ታስቦ የተረቀቀ ነው፡፡ ከሦስቱ (ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን) ተፋሰስ ሃገሮች ሁለት፣ ሁለት እና አራት ገለልተኛ ባለሙያዎችን ያሳተፈው ኮሚቴም ያቀረበው ሪፖርት ከሞላ ጎደል ግድቡ በግብጽ እና ሱዳን ላይ ወሳኝ ጉዳት እንደማያደርስ ነው፡፡ ተጨማሪ ጥናት እንደሚያስፈልግ በመግለጽ፡፡ ስለዚህ የግብጽ አስተዳደር እንደ ሱዳን ከግድቡ ያለውን ተጠቃሚነት (ከጎርፍ አደጋዎች፣ ከደለል፣ እና ከርካሽ የኃይል አቅርቦት) ለማስጠበቅ ፖሊሲውን ቀስ በቀስ በማስተካከል የግድቡን ግንባታ መቀበል ብቻ ሳይሆን በባለሙያዊ እርዳታም መተባበር ይገባዋል፡፡
የምዕራብያውያን ወደ ግብጽ መመለስ
ገማል አብዱልናስርን ተከትለው የፕሬዝዳንትነቱን ቦታ የተቀናጁት አንዋር ሳዳት ግብጽ ከእስራኤል ጋር ያላትን ግጭት በካምፕ ዴቪድ ስምምነት ቋጩት፡፡ ወራሻቸው ሁስኒ ሙባረክም ከአውራሻቸው በተሻለ ከእስራኤል ጋር ፍቅራቸውን ጨመሩ፡፡ የእስራኤል ቀኝ እጅ አሜሪካም ከግብጽ ጋር ያላትን ወዳጅነት ጨመረች፡፡ መሣሪያ እስከ አፍንጫዋ አስታጠቀቻት፡፡ ቢሊዮን ዶላሮችን በሰበብ አስባቡ ታቀብላት ጀመር፡፡ ነገር ግን እስራኤልና ግብጽ ታሪካዊ ጠላት ናቸውና ፍቅራቸው ከመንግሥታት አልፎ ሕዝቡ ውስጥ መስረጽ አቃተው፡፡ በተቃራኒው የኢትዮ-ኤርትራ ጠብ በመንግሥታቱ መሃል ብቻ እንደሆነው፡፡ እንግዲህ ይህ ቀዝቃዛ ፍቅር ባለበት የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ  ወደ ሥልጣን መጣ፡፡ የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ ከእስራኤል ጋር የነበረውን የካምፕዴቪድ ስምምነት ካለው ነባራዊ ፖለቲካ አንጻር ቢቀበለውም፤ የእስላማዊ አስተዳደርን የሚደግፍ ሕገ መንግሥት ለመመሥረት ያለውን ፍላጎት ግልጽ አደረገ፡፡ ይህም ለአሜሪካ በተለይም ለእስራኤል ስጋት የሚያሳድር ኩነት ሆነ፡፡ አሜሪካ ከሙስሊም ወንድማማቾች ይልቅ የዘመናት ወዳጇ የሆነውን የግብጽ ጦር መርጣለች፡፡ የሙርሲን ውድቀት መፈንቅለ መንግሥት ለማለት ድምጽ አንሷታል፡፡ ምክንያቱም አባባሉ በዓመት ለግብጽ የምትሰጠውን የ1.5 ቢሊዮን ዶላር እርዳት እንድታቆም ሕጓ ያስገድዳታል፡፡ ፖለቲከኞቿ እንደ በፊቱ አቋማቸውን ማስቀመጥ ከብዷቸዋል፡፡ ዝምታቸው በሙርሲ ውድቀት እጃቸው አለበት ከሚል እስከ እስላማዊ ዲሞክራሲ በምዕራብያውያን ዘንድ አይፈቀድም ወደ ሚል ድማዳሜ እወሰደ ነው፡፡
በግብጽ ውስጥ ከእስራኤል እና/ወይም ከምዕራብያውያን ጋር ተቃርኖ ያለው አስተዳደር መመሥረቱ ኢትዮጵያ በናይል ላይ ለሚሠሩ ፕሮጀክቶች በዓለም ባንክ እና በመሳሰሉት ተመካኝቶ ገንዘብ እንድታገኝ መንገድ ይከፍታል፡፡ ግብጽን ለመቅጣት የናይል ወንዝ ፍሰትን ከመቀነስ ሌላ ወሳኝ አማራጭ የለም፡፡ የበፊት ተሞክሮዎች ይህንን ይመሰክራሉ፡፡ ሦስት ቀደምት ተሞክሮችን እንመልከት፡፡ ግብጽ በእንግሊዝ ቀኝ ግዢ ስር በነበረችበት እ.ኢ.አ. በ1924 ዓ.ም ላይ የግብጽ ወታደር ጠቅላይ ገዢ እና የሱዳን አስተዳዳሪ የነበሩት ሰሊስ ስታክ በካይሮ አደባባይ መገደላቸውን ተከትሎ የእንግሊዝ መንግሥት እንደ ቅጣት በሱዳን የጎዚራ እስኪም ለተሰኘውን ትልቅ የጥጥ እርሻ የሚረዳ እ.ኢ.አ. በ1925 ዓ.ም የተጠናቀቀ የሲና ግድብ ለማሠራት ምክንያት ሁኗቸዋል፡፡
የግብጹ ገማል አብዱልናስር ለአስዋን ግድብ ማስገንቢያ እ.ኢ.አ በ1953 ዓ.ም ከአሜሪካ የተገባላቸው ቃል በሦስት ዓመቱ በመሰረዙ ከሩስያ ለመበደር በወሰኑት መሠረት እ.ኢ.አ በ1964 ዓ.ም አሜሪካ ለቀዝቃዛው ጦርነት ምላሽ በኢትዮጵያ ውስጥ በናይል ላይ ሊሠሩ የሚችሉ የኃይል ማመንጫ እና የመስኖ ፕሮጀክቶችን እንዲጠኑ አድርጋለች፡፡ የሕዳሴው ግድብም የዚህ ጥናት አንዱ ውጤት ነው፡፡ ጉልበት ከመጠቀሟ በፊት እንግሊዝ የስዊዝ ቦይን የግብጽ ንብረት ለማድረግ የተነሱትን ገማል አቡዱልናስር ሐሳብ ለማስለወጥ በኡጋንዳ የኦይን ፎል ግድብ ለመሥራት ዋነኛ ምክንያቷ እንደነበር ይገለጻል፡፡
እስራኤል እና አሜሪካ በተለየ እንዲሁም ምዕራብያውያን ባጠቃላይ የሕዳሴውን ግድብ እና ሌላ የአባይ ፕሮጀክቶችን ከግብጽ ጋር እንደ መደራደሪያነት ሊጠቀሙበት ይችላሉ፡፡
የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ በዚህ ጊዜ ከሥልጣን መባረር ብቻ አይደለም፣ ሙርሲ በቁም እስር ላይ ሲሆኑ ለሌሎች አመራሮቹ የእስር ፍቃድ አቃቢ ሕግ ከፍ/ቤት እንዳወጣ ሰምተናል፡፡ በሽግግር መንግሥቱ ውስጥ አንድም የወንድማማቾች ፓርቲ አባል አልተሳተፈም፡፡ የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ ከግብጽ ፖለቲካ በድጋሚ እየራቁ ይመስላል፡፡ በሚቀጥለው ምርጫም እስላማዊ ፓርቲ ካልተሳተፈ፤ የምዕራብያውያን ድጋፍ ያለው አስተዳደር እንደሚመጣ አመላካች ነው፡፡ የግብጽ ወታደራዊ ተቋም ከአሜሪካ ጋር ካለው የከረመ ወዳጅነት እና የሽግግር መንግሥቱ ባለሙያዎችና ሊበራሎችን ማካተቱ ለዚህ ትንበያ እንደ ምክንያት ተጠቃሽ ነው፡፡ በአንዋር ሳዳት እና በሁስኒ ሙባረክ አስተዳደር ጊዜ እንደነበረው ግብጽ በሰሜን ምስራቅ አፍሪካ የአሜሪካ ዋነኛ ወዳጅ መሆኗ ከቀጠለ ኢትዮጵያ የናይል ፕሮጀክቶቹን በራሷ ወጪ ማሠራቷን ትቀጥላለች፡፡ በተቃራኒው በግብጽ የእስራኤልን ጠብ አጫሪ ድርጊት በመቃወም አሻፈረኝ የሚል አስተዳደር ከመጣ ቦንድ ከመግዛት የሚያስጥለን አጋጣሚ ሊመጣ ይችላል፡፡ እስራኤልም ከግብጽ ጋር ያላትን ቀዝቃዝ ሠላም አመካኝታ በዓለም ላይ የታወቀችበትን በአግባቡ መስኖ የመጠቀም ልምድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለራስጌ ሀገራት ማስተማሩዋን ትቀጥላለች፡፡
የግብጽ አለመረጋጋት በናይል ፖለቲካ ላይ የሚኖረው እንድምታ
ግብጽ የናይልን ውኃ ለዘመናት እንግሊዝ በሰጠቻት የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ በመመራት በበላይነት ስትጠቀም እና ስታስተዳድር ቆይታለች፡፡ የብቻ የመጠቀም መብቷን እ.ኢ.አ በ1959 ዓ.ም ሙሉ የናይል ፍሰትን ለሁለት የተከፋፈሉበትን ስምምነት በመጥቀስ ስታሰፍፅም ቆየች፡፡ የራስጌ ሀገራት ውኃውን እንዳይጠቀሙ ለፕሮጀክቶች የሚሰጡ እርዳታዎችን በማስከልከል፣ እርስ በርስ ጦርነቶችን በመደገፍ እና የጦርነት ዛቻዎችን በመለፈፍ የናይልን ሙሉ ተፋሰስ ሳይነካ ከታች ሆና ስትቀበል ኖረች፡፡ አሁን ጊዜው ተለወጠ፤ የተፋሰስ ሀገሮቹ የተረጋጋ መንግሥት ኖራቸው፣ ኢትዮጵያ በራሴ ወጪ ትልቅ የኃይል ማመንጫ እገነባለሁ አለች፣ ሁሉን ያሳተፈ የተፋሰስ ውኃ የሕግ ማዕቀፍ ኢትዮጵያን ጨምሮ በስድስት የተፋሰስ ሀገሮች ተፈረመ፡፡
የግብጽ አለመረጋጋት ምን ያህል ዘላቂ ነው? ክብደቱስ ምን ያክል ነው? የሚለው ጥያቄ የዓለም አቀፍ ተንታኞችን የሚያነጋግር ጉዳይ ሆኗል፡፡ በሕዝቡ ድምፅ ሥልጣን ላይ የወጡት መሐመድ ሙርሲ በመፈንቅለ መንግሥት ነው የተነሱት በሚል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው ወደ መንበራቸው እንዲመለሱ ተቃውሟቸውን ቀጥለዋል፡፡ የሙስሊም ወንድማማቾች ደጋፊዎች ‘ዲሞክራሲያችንን ሊቀለብስ የሚሞክረውን በመሳሪያ ሳይቀር እንዋጋለን’ ሲሉ እየተደመጡ ነው፡፡ ሁለተኛው ትልቅ እስላማዊ ፓርቲ-ኑር ፓርቲ- የወታደራዊ አማራጮች ሊኖሩ እንደሚችሉ ገልል፡፡ የሙርሲ የደኅንነት አማካሪ የነበሩት ኢሳም ኤል ሀዳድ ‘መፈንቅለ መንግሥቱ ለዓለም ግልጽ የሆነ መልዕክት ነው፤ ዲሞክራሲ ለእስላም አይሆንም’ የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ ከሞላ ጎደል የግብጽ አለመረጋጋት በቀላሉ መፍትሄ አይገኝለትም የሚሉ የፖለቲካ ተንታኞች ትንሽ አይደሉም፡፡ አዲሱ የሽግግር መንግሥት ከሁለቱ ትልልቅ እስላማዊ ፓርቲዎች – ከሙስሊም ወንድማማቾችም እና ከኑር ፓርቲ – አንድ አባል ሳያሳትፍ 34 አባላትን ይዞ ተዋቅሯል፡፡ የግብጽ ዕጣ ፈንታ እርስ በእርስ ጦርነት ነው የሚሉ ትንበያዎችም ከየአቅጣጫው እየተሰሙ ነው፡፡
የግብጽ አለመረጋጋት በናይል ፖለቲካ ላይ የሚኖረውን እንድምታ ከሁለት አቅጣጫ ማየት ይቻላል፡፡ በናይል ላይ የሚደራደረው የሽግግር መንግሥት ከሚኖረው አቋም እና ግብጽ ለዘመናት ስታስኬደው የነበረውን ለብቻ የመጠቀም እና የማስተዳደር አካሄድ ከማስፈጸም አኳያ፡፡
የሕዳሴውን ግድብ በተመለከተ በኢትዮጵያና በግብጽ ተደጋጋሚ ድርድሮች ያስፈልጋሉ፡፡ በናይል ተፋሰስ ጊዜያዊ ድርጅት የውኃ ሚኒስቴሮች ስብሰባ በዓመት አንዴ ተፋሰሱ ለጋራ ተጠቃሚነትን ወደ ፊት የሚራመዱበትን አጋጣሚ ለማጎልበት ምክክር ያደርጋሉ፡፡ በእነዚህ ድርድሮች የሽግግር መንግስቱ በውስጥ ፖለቲካ ከመጠመዱ እና በሕዝቡ የተወከለ ባለመሆኑ የግብጽን አቋም በግልጽ ማስቀመጥ ያዳግተዋል፡፡ የውኃ ጦርነት ከቃላት ባያልፍም ግብጽ በወታደራዊ አስተሳሰብ እንደመተዳደሩዋ የውስጡን ተቃውሞ ለማርገብ ጦርነት ወደ አማራጭ የሚመጣበት አጋጣሚም ጠባብ ቢሆንም የለም ለማለት አይቻልም፡፡
ግብጽ እኔ ብቻ የሚለውን የውኃ መጠቀም አካሄድ የምታስፈፅመው በዋናነት ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ ፖለቲካዋ እንዳትረጋጋ ተቃዋሚዎችን በመርዳት፣ ለፕሮጀክት የሚሰጡ ገንዘቦችን በማስከልከል እና እ.ኢ.አ በግንቦት 2011 ዓ.ም ለፊርማ ክፍት የሆነውን፤ በ6 ተፋሰሶች ተፈርሞ በኢትዮጵያ በቅርቡ የፀደቀውን የሕግ ማዕቀፍ እንዳይፀድቅ ተፋሰሱን በመደለል ነበር፡፡ ነገር ግን በዚህ ሰዓት እራሷ ሳትረጋጋ የኢትዮጵያን አስተዳደር ማተራመስ አስቸጋሪ ነው፡፡ ሁሉን አቀፍ የውኃ ስምምነቱ የተፋሰስ ሀገራቱ እንዳያፀድቁ መደለልም የተረጋጋ አስተዳደር ይፈልጋል፡፡
የፊተኞች ወደ ኋላ እንዲሉ ግብጽ በራስጌ ሀገራት እርስ በርስ ጦርነት እና መተራመስ ስትጠቀም እንደነበረው የራስጌ ሀገራት በግብጽ ትርምስ የሚጠቀሙበት ጊዜ የደረሰ ይመስላል፡፡
—–

ጸሐፊውን ለማግኘት በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ይጻፉላቸው፡፡

የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ኢብራሂም ቡባከር ኬይታ የማሊ ፪ኛ ዙር ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አሸናፊ ሆኑ። ምንም እንኳን የምርጫው ውጤት በይፋ ባይወጣም በኬይታ አንፃር የተወዳደሩት የቀድሞው የገንዘብ ሚንስትር ሱማይላ ሲሴ ሽንፈታቸውን በመቀበል ትናንት ከተፊካካሪያቸው ኬይታ ጋ በመገናኘት የእንኳን ደስ ያልዎት ምኞታቸውን መግለጻቸውን አስታውቀዋል።

  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሣለኝ – /ፎቶ – ፋይል/ ​​
አጎአ እንዲሰፋ ኃይለማርያም ደሣለኝ ጠየቁ
ዩናይትድ ስቴትስ ከሠሃራ በስተደቡብ ላሉ የአፍሪካ ሃገሮች ያወጣችው በምኅፃር አጎአ የሚባለው ከቀረጥ ታሪፍ ነፃ የመናገድ፤ የአፍሪካ የዕድገትና የንግድ ዕድሎች ተጠቃሚነት ሕግ ረዘም ላሉ ዓመታት መቀጠል እንዳለበት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ጠይቀዋል፡፡
አጎአ – አዲስ አበባ – 2013 ​​
አዲስ አበባ ላይ በተከፈተው የአጎአ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ባደረጉት ንግግር ጠቀሜታው ሊሰፋ፤ ከገበያ ዕድልም ሊያልፍ ይገባዋል ብለዋል፡፡

የአሜሪካው የንግድ ከፍተኛ ባለሥልጣን ማይክል ፍሮማን በበኩላቸው አጎአ አሜሪካና አፍሪካን በንግድና በምጣኔ ኃብት የሚገኛኙበትን ሁኔታ በእውነት የቀየረ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
አጎአ – አዲስ አበባ – 2013 ​​
ዝርዝሩን …

ሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ ላይ እየተካሄደ ባለው 14ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የኢትዮጵያ አትሌቶች ያገኙት ድል በዓለሙ ሠንጠረዥ ሁለተኛ ቦታ ላይ አስቀምጧቸዋል፡፡

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ መራሹ መንግስት የሕዝበ ሙስሊሙን ከ18 ወራት በላይ የዘለቀ እንቅስቃሴ በኃይል ለማፈን ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ እየወሰደ ያለው እርምጃ በሙስሊም አባላቱ ዘንድ ቅሬታ ማሳደሩ የግንባሩን ከፍተኛ አመራር ስጋት ውስጥ እንደጣለ የውስጥ ምንጮች ጠቆሙ፡፡ አብዛኛዎቹ የግንባሩ ሙስሊም ከፍተኛ የአመራር አባላትን ጨምሮ በየደረጃው ያሉ መካከለኛ፣ ዝቅተኛ አመራር አባላት መንግስት በሙስሊሙ ጥያቄ አፈታት …

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቁጫ ወረዳ ከማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በአካባቢው የተሰማራው የፌደራል ፖሊስ ከ50 በላይ ሰዎችን ማሰሩን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። ከታሰሩት መካከል 6ቱ ሴቶች ናቸው። ባለፈው ሐሙስ የኢህአዴግ ካድሬዎችና ፖሊሶች መደብደባቸውን የሚያመለክት ሪፖርት መቅረቡን ተከትሎ የፌደራል ፖሊስ አባላት ወደ አካባቢው በብዛት በማቅናት ሰዎችን በማሰር ላይ የሚገኙ ሲሆን፣ መረጃዎችን በማቀባባል የአካባቢውን ህዝብ ለአመጽ …

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመልካም አስተዳደር ኮማንድ ፖስት እየተባለ የሚጠራው መስሪያ ቤት በክልሉ ባሉ የአስተዳደር ቢሮዎች ባካሄደው ቅኝት የመልካም  አስተደዳር ችግር በክልሉ ተባብሶ መቀጠሉን ገልጿል፡፡ በተለይም በፍትህ ፤ በፖሊስ ፤ በማረሚያ ቤቶች ፤ በመሬት ፤ኢንቨስትመንት፤ መብራት እና ውሃ ደግሞ የችግሩ መለያ ቦታዎች መሆናቸውን ለክልሉ ካቢኔ የቀረበው ሪፖርት የቅሬታ ምንጭ መሆናቸውን ያወሳል፡፡ በክልሉም ከጊዜ …

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች በነቀምት ባደረጉት ስብሰባ ህዝቡ ኢሳትን እንዳይመለከት ካድሬዎች ከፍተኛ ስራ መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል። አመራሮቹ ኢሳት የአሸባሪ ድርጅቶች ንብረት በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ኢሳትን መመልከቱን እንዲያቆም ባለስልጣኖቹ ወትውተዋል። በስብሰባው ወቅት ለካድሬዎች ከተነገራቸው ነገር መካከል አንዱ ኢሳትን በሚመለከት ህግ ሊወጣ ነው መባሉ ነው። ምን አይነት ህግ እንደሚወጣ ግን ባለስልጣኖቹ ከማብራራት …

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሱዳን አብየ ግዛት የሚገኘው የጥምር ኮሚቴ ስብሳቢዎች አንዱ የሆኑት አልከሄር አል ፋቲም አማጺ የሆነውን የሱዳን አብዮታዊ ግንባር በአካባቢው መኖሩ እያወቀ በስፍራው የሚገኘው የኢትዮጵያ ጦር በዝምታ በማለፉ ክፉኛ ወቅስዋል:: አልከሄር አል ፋቲም ሰሜን ሱዳንን ወክለው የሚገኙ ሲሆን እንደሳቸው ገለጻ አማጺው ሃይል በምስራቅ አብየ ሰፍሮ እንደሚገኝ ገልጸዉ የኢትዮጵያን ጦር ዝምታ ግን …