ጀርመንና የሶሪያ ስደተኞች

ጀርመን ከሌሎች የአውሮፓ ሃገራት በግንባር ቀደምትነት በዚህ ዓመት 5 ሺህ የሶሪያ ስደተኞችን ለመውሰድ ቃል ገብታለች ። በጀርመን ፌደራል መንግሥት የሃገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴታ ኦለ ሽሮደር እንደተናገሩት ጀርመን ከለላ የምትሰጠው ሰብዓዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሶሪያውያን ብቻ ነው ።