የጋምቤላዉ ተፈናቃይ ክስ

ከሳሽ እንደሚሉት የኢትዮጵያ መንግሥት በሠፈራ መርሐ-ግብሩ በብዙ መቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎችን ማፈናቀል፥ ማሰደዱን የብሪታንያ መንግሥት እያወቀ ለኢትዮጵያ መንግሥት በተለይም ለፀጥታ አስከባሪዎች ማሰልጠኛ ርዳታ መስጠቱ ለተፈፀመዉ በደል አባሪ ተባባሪ መሆኑን አመልካች ነዉ።