ኢንጂነሩ ካቤኔ ውስጥ መቀጠላቸው ትርጉመ ቢስ መሆኑን መረዳታቸውን በመግለጽ ለግዛቸው ደብዳቤ ያስገቡት የአንድነት አመራሮች ተክሌ በቀለ –ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት በላይ ፈቃዱ —ምክትል ፕሬዘዳንት ሰለሞን ስዮም —የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ ዳንኤል ተፈራ — የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ዳዊት አስራደ —የኢኮኖሚ ጉዳዮች ሀላፊ ኢንጂነር ግዛቸው በአንድነት እና በመኢአድ መካከል የሚደረገውን ውህደት በማኮላሸት ስራ ላይ ከመሰማራታቸውም ሌላ ሰርጎገቦችን እየሰበሰቡ ፓርቲው […]

አብዛኞቻችን የአንድነት እና መኢአድ ዉህደት ተጠናቆ፣ በአዲስ መንፈስ የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄን እንቀጥላለን የሚል ተስፋና ጉጉት ነበረን። የኢትዮጵያዉያንን መተባበር የማይፈልገው ሕወሃት/ኢሕአዴግ፣ በሚቆጣጠረው ምርጫ ቦርድ አማካኝነት፣ ዉህደቱን ለማጉዋተት እንደተለመደው መስራት ጀመረ። «መኢአድ ያላሙዋላቸው ወረቀቶች አሉ» በማለት ዉህድቱን ማድረግ እንደማይችል አሳወቀ። (የተለመደው የማሰናከል እጁት ተግባር) መኢአድ ሕዝብ ያውቀው ዘንድ፣ ያለውን ሁኔታ ለማሳወቅ መግለጫ አወጣ። በጉዳዩ ላይም ከምርጫ ቦርድ […]

ነሃሴ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተለያዩ ፓርቲዎች ስብስብ የሆነው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ባወጣው መግለጫ በቡርጅ ብሄረሰብና በቦረና ህዝብ መካከል ለዘመናት ሰፍኖ የኖረው መልካም ግንኙነት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጸረ-ሰላም ሃይሎች እየደፈረሰ እንደሚገኝ ገልጿል። ከ2 ሺ በላይ የሆኑ የቡርጅ ብሄረሰብ አባላት ከታህሳስ ወር 2006 ኣም ጀምሮ  ከአካባቢው ተፈናቅለው ወደ ደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ …

ነሃሴ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በእረፍት ላይ የሚገኙ ነባር የዩኒቨርስቲ  ተማሪዎችን፣ የኮሌጅና የቴክኒክ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎችን እንዲሁም የዘንድሮውን የሁለተኛ ደረጃ ፈተና አልፈው ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ተማሪዎችን ስለመጪው ምርጫ እና ስለአገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ለማወያየት በየክልሎች ስብሰባ መጠራቱ ታውቋል። ከነሃሴ 10 እስከ ነሃሴ 25 በሚቆየው ሰሚናር ላይ ተማሪዎች ምርጫውን ተከትሎ ስለሚፈጠሩ  ረብሻዎች፣ ስለአገሪቱ ወቅታዊ የፖለቲካ ትኩሳትና …

ነሃሴ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአንባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ተቀባይነት የነበረው ሳምንታዊ መጽሔት ባለቤት  እና የመጽሔቱ ሶስት አዘጋጆች ሀገር ለቀው ተሰደዋል። የመጽሔቱ ባለቤት አቶ እንዳልካቸው ተስፋዬ ለኢሳት እንደገለጸው፤ እርሱና ጋዜጠኞቹ  በስርአቱ ሲደርስባቸው የነበረውን ወከባና አፈና ተቋቁመው የአዲስ ጉዳይ መጽሔትን  ህልውና ለማስቀጠል ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት ፤ መጽሔቱዋ  በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍ ያለ ተቀባይነት ከማግኘቷም ባሻገር በገንዘብ አቅምም …

ነሃሴ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ነዋሪዎች እንደሚገልጹት ካለፈው አንድ ወር ጀምሮ ከፍተኛ የሆነ የስኳር፣ የቡናና ዱቄት እጥረት ተፈጥሯል። በዱቄት እጥረት የተነሳ በተለይ በአማራ ክልል ሰዎች ዳቦ ለማግኘት ራጃጅም ሰልፎችን ተሰልፈው ወረፋ ለመተበቅ ተገደዋል። ቡና የመጨረሻ ደረጃ የሚባለው በኪሎ እስከ 100 ብር በመሸጥ ላይ ሲሆን፣ ሁለተኛና አንደኛ ደረጃ የሚባሉትን የቡና አይነቶች ፈልጎ …

ነሃሴ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሪፖርተር የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ፈቃዱ ሃይሌን ጠቅሶ እንደዘገበው ከባቡር ፕሮጀክቱ ጋር የተያያዙትን መንገዶች ከመምራት ጋር የተያያዘ ችግር አለ። ዋና ስራ አስኪያጁ ያለምንም ዝግጅትና እውቀት የአስፋልት መንገድ ይቆራጣሉ፣ በቅንጅትም ለመስራት ፈቃደኞች አልሆኑም በማለት ተናግረው፣ “የባቡር ኮርፖሬሽን ቦርድ አባል ሆኜ እንዲህ የተቸገርኩኝ እዚያ ውስጥ ያልገባ ሰው …

ነሃሴ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በግብጽ ከስልጣን በተወገዱት ሙሀመድ ሙርሲ ዳጋፊዎች ላይ የጸጥታ ሃይሎች  የወሰዱትን እርምጃ የሚዘረዝረውንሪፖርት ይፋ ለማድረግ ካይሮ የተገኙት የሂውማር ራይትስ ወች ዋና ስራ አስኪያጅ ኬኒስ ሮዝና ሌላዋ ከፍተኛ ባለስልጣን ሳራ ሊህ ወደ መጡበት አገር እንዲመለሱ ተደርጓል። ከ1500 በላይ የተገደሉበትን በአንዳንዶች ዘንድ እንደመፈንቅለ መንግስት የሚታየውን ድርጊት ሂውማን ራይትስ ወች በተደጋጋሚ ሲያወግዝ መቆየቱ …

– ኢንጂነግር ግዛቸው በሕዝብ ዘንድ በጉጉት የሚጠበቀዉን፣ ለአገዛዙ ራስ ምታት የሆነው፣ የመኢአድ እና አንድነት ዉህደት አመቻች ኮሚቴን አፈረሱ። በአባላትና ደጋፊዎች ዘንድም ትልቅ ድንጋጤ ተፈጥሩዋል። በአገዛዙም ዘንድ ደስታው ጨምሩዋል። – በዉጭ አገር ያሉ የአንድነት ደጋፊዎች በኢንጂነር ገዛቸው ላይ ከፍተኛ ተቃዉሞ እያሰሙ ናቸው። የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ፣ አቶ ተስፋሁን አለምነህ፣ ለሕብር ራዲዮ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ጸሓፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ

——–

የሀገራችን ቋንቋዎች ከውጪ ቋንቋዎች በርካታ ቃላትን ወርሰዋል፡፡ ይህም ከብሉይ ዘመን ጀምሮ ይታይ የነበረ ክስተት ነው፡፡ የመወራረሱ አድማስ ስፋቱን የጨመረው ግን በአስራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ ነው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በቀጣዮቹ አንድ መቶ ሀያ ዓመታት ውስጥ የታዩት ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ክስተቶች የሀገራችን ቋንቋዎችን ለውጪ ቋንቋዎች ተጽእኖ የበለጠ ክፍት እንዲሆኑ አድርገዋቸዋል፡፡  

  ታዲያ ከሶስት ሺህ ከሚልቁት የውጪ ቋንቋዎች መካከል ለሀገራችን ቋንቋዎች ብዙ ቃላትን ለማውረስ የበቁት አራቱ ብቻ ናቸው፡፡ እነርሱም ዐረብኛ፣ ፈረንሳይኛ፣ ጣሊያንኛና እንግሊዝኛ ናቸው፡፡ የቱርክ እና የጀርመን ቋንቋዎችም ጥቂት ቃላትን ለሀገራችን ቋንቋዎች አበርክተዋል፡፡

*****

   ዐረብኛ በሀገራችን ቋንቋዎች ላይ ተጽእኖ ለመፍጠር የቻለው በዋናነት የእስልምና ሀይማኖት የአምልኮና የትምህርት ቋንቋ ስለሆነ ነው፡፡ በመሆኑም ከእስልምና እምነት ጋር በተያያዘ ለአምልኮና ለትምህርት አገልግሎት ላይ የሚውሉ ቃላት በአብዛኛው ከዐረብኛ የተገኙ ናቸው፡፡ ለምሳሌ መስጊድ/መስጂድ፣ ኢማም፣ ቃዲ፣ አዛን፣ መጅሊስ፣ መድረሳ ወዘተ… የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ በሂደት ደግሞ የዐረብኛ ቃላት በአምልኮ ውስጥ ካላቸው አስፈላጊነት አልፈው በተራው ሰው ንግግር ውስጥም ገብተዋል፡፡ ይህ ክስተት በስፋት የሚስተዋለው ግን አብላጫው ነዋሪ ህዝብ ሙስሊም በሆነባቸው እንደ ወሎ፣ ሀረርጌ፣ ባሌ፣ ጅማ፣ ሶማሊ (ኦጋዴን)፣ ቤኒሻንጉልና አፋር አካባቢዎች ነው፡፡ በነዚህ አካባቢዎች ከሚነገሩት ቋንቋዎች “መርሐባ”፣ “አሕለን”፣ “ፉጡር”፣ “ሀድራ”፣ “ሙሐባ”፣ “መናም”፣ “ጂስም”፣ “አዛ”፣ “ኩርሲ”፣ “ማዕና”፣ “ዒልም”፣ “አስል” እና ሌሎች በርከት ያሉ የዐረብኛ ቃላትን በቀላሉ ለይቶ ማውጣት ይቻላል፡፡

ታዲያ የዐረብኛ ቃላትን የመውረሱ ተግባር በኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ብቻ የተገደበ አይደለም፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በእኩል ደረጃ የሚጠቀምባቸው በርከት ያሉ የዐረብኛ ቃላትንም ወርሰናል፡፡ ይህም ክስተት የተፈጠረው ከንግድ መስፋፋት ጋር ነው፡፡ በተለይ እስከ አስራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ድረስ የሀገራችንን ንግድ በበላይነት ተቆጣጥረው የነበሩት ሲራራ ነጋዴዎች ዐረብኛን በንግድ ቋንቋነት በስፋት ይጠቀሙበት የነበረ ከመሆኑ የተነሳ በሀገራችን ቋንቋዎች ውስጥ መሰረት ያልነበራቸው በርካታ ቃላት እንዲወረሱ ምክንያት ሆነዋል፡፡ ለምሳሌ ዛሬ የአማርኛ ቃላት አድርገን የምንጠቀምባቸው እንደ  ሀዋላ፣ ጉምሩክ፣ ሰንዱቅ፣ ሱቅ፣ መጋዘን፣ ሽርክና፣ ወኪል፣ ሰነድ፣ ደላላ፣ መሃለቅ ወዘተ የመሳሰሉት የአማርኛ ቃላት ምንጫቸው ዐረብኛ ነው፡፡ እንደ ሐዲድ፣ ባቡር እና መኪና የመሳሰሉ ቃላትም ከዐረብኛ ነው የተወረሱት፡፡ ይሁንና ዐረብኛና አማርኛ ሴማዊ ቋንቋዎች በመሆናቸው የሚጋሯቸውን ቃላት እንደ ውርስ ቃላት ማየት ስህተት ነው፡፡ ለምሳሌ ሰላም፣ ደም፣ ቤት፣ ፎቅ፣ ክፍል፣ ዐይን፣ ፈረስ፣ ዘመን፣ ሐሩር፣ ሚዛን የመሳሰሉ ቃላት በሁለቱም ቋንቋዎች ውስጥ አሉ፡፡ ሁለቱም ቋንቋዎች ሴማዊ በመሆናቸው ነው እነዚህን ቃላት የተጋሩት፡፡ የነዚህ ቃላት መነሻ የሁሉም ሴማዊ ቋንቋዎች አባት እንደሆነ የሚታመንበት ግንደ-ሴማዊ ቋንቋ (Proto-Semetic Language) ነው፡፡

*****

     አዲስ አበባን ከጅቡቲ ጋር የሚያገናኘው የኢትዮ-ጅቡቲ የምድር ባቡር መስመር ሲሰራ ደግሞ ፈረንሳይኛ ወደ ሀገራችን ቋንቋዎች እየሰረገ መግባት ጀምሮ ነበር፡፡ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤትም በ1910ዎቹ ውስጥ ሲከፈት የፈረንሳይኛ ተጽእኖ በጣም ተጠናክሯል፡፡ የዘመኑ የትምህርት ካሪኩለምም ከፈረንሳይ የተቀዳ በመሆኑ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎችና ምሩቃኑ ፈረንሳይኛን ይናገሩ ነበር፡፡ በነዚያ ምሩቃን በተሞላው ሲቪል ሰርቪስም ሆነ በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ውስጥ ፈረንሳይኛ እንደ ሁለተኛ ቋንቋ ሆኖ አገልግሏል፡፡ ለመንግሥታዊ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ሰነዶችና የስራ መመሪያዎችም ከፈረንሳይኛ ሲተረጎሙ ነው የኖሩት (የመጀመሪያው ህገ-መንግሥትም ከፈረንሳይ የተቀዳ ነው)፡፡  በዚህም ሂደት በርካታ የፈረንሳይኛ ቃላት በአማርኛ ተወርሰዋል፡፡ ከፈረንሳይኛ ከወረስናቸው ቃላት መካከል “ኦፊሴል”፣ “ሞኖፖል”፣ “ሌጋሲዮን”፣ “ኮሚስዮን”፣ “ፔኒስዮን”፣ “ዲክላራሲዮን”፣ “ኦፕራሲዮን”፣ “ካሚዮን”፣ “ፍሪሲዮን”፣ “ሬኮማንዴ”፣ “ለገሀር (ላጋር)፣ “ቡፌ”፣ “ሌሲ ፓሴ”፣ “ዴኤታ”፣ “ ካፌ”፣ “ራንዴቩ”፣ የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ፡፡

   የኢጣሊያ ወረራ ከተወልን ማስታወሻዎች መካከል ትልቁ በሀገራችን ቋንቋዎች ውስጥ የሚታየው የጣሊያንኛ ተጽእኖ ነው፡፡ በአማርኛ፣ ኦሮምኛና ትግርኛ ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ የጣሊያንኛ ቃላትን መቁጠር ይቻላል፡፡ በተለይም በቀድሞ ዘመናት ከተሽከርካሪ እና ትራንስፖርት እንቅስቃሴ፣ እንዲሁም ከኢንዱስትሪ ጋር በተያያዘ ከሚሰራባቸው ቃላት መካከል ብዙዎቹ የጣሊያንኛ መሰረት ያላቸው ናቸው፡፡ ዛሬም ድረስ የነዚያ ቃላት ቅሪቶች በሀገርኛ ቋንቋዎች ውስጥ ይስተዋላሉ፡፡ ከጣሊያንኛ ከወረስናቸው ቃላት መካከል “ፓስታ”፣ “ማካሮኒ”፣ “ላዛኛ”፣ “ስፓጌቲ”፣ “ስልስ” (ሳልሳ)፣ “አሮስቶ”፣ “ፋብሪካ”፣ “ጋዜጣ”፣ “ሊቼንሳ”፣ “ፉርኖ”፣ “ቪያጆ” (በመኪና የሚደረግ ጉዞ)፣ “ላቫጆ”፣ “ካሮሴሪያ”፣ “ካምቢዮ”፣ “ሞቶሪኖ”፣ “ፍሬን”፣ “ፊልትሮ”፣ “ሳልቫታዮ”፣ “ፖርቶ መጋላ”፣ “ፒንሳ”፣ “ቺንጊያ” ፣ “ፈረፋንጎ”፣ “ኩሽኔታ” “ኪያቤ”፣ “ካቻቢቴ” “ባሌስትራ”፣ “ቸርኬ” “ፒስታ” “ኮማርዳሬ” “ጎሚኒ” “ሮንዴላ” “ዲፍረንሻሌ” “ስፒናታ” “ሳልዳሬ” “ቡኮ”፣ “ፖምፓ” (ቧንቧ)፣ “አውታንቲ”፣ “ማኖ”፣ “ኢሊ ጎሬ”፣ “ቴስታ”፣ “ፑንቶ”፣ “ቦጦሎኒ”፣ “ካምቦ” ወዘተ…. የመሳሰሉት ተጠቃሽ ናቸው፡፡

*****

ጣሊያኖች ከተባረሩ በኋላ እንግሊዝኛ በሀገርኛ ቋንቋዎች ውስጥ ሰርጾ መግባት ጀመረ፡፡ በተለይ እንግሊዞች በኢትዮጵያ ውስጥ በነበሩባቸው አስር ዓመታት የእንግሊዝኛ ቃላት በሀገራችን ቋንቋዎች በብዛት ተወረሱ፡፡ በዚያን ጊዜ ከተወረሱት ቃላት ውስጥ እስከ አሁን ድረስ በአገልግሎት ላይ ያሉትን እንደ “ፖሊስ”፣ “ባንክ”፣ “ሚኒስቴር”፣ “ካፒታል”፣ “ኤሌክትሪክ”፣ “ኮሌጅ”፣ “አካዴሚ”፣ “ኤክስፐርት”፣ “ዲሬክተር” የመሳሰሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ እንዲሁም እንደ ፕሮፌሰር፣ ዶክተር፣ ኢንጂነር፣ ጄኔራል፣ አድሚራል፣ ኮሞዶር፣ ኮሎኔል እና ካፒቴን የመሳሰሉ የማዕረግ ስሞችም የተወረሱት ከእንግሊዝኛ ነው፡፡

    በእንግሊዝኛ ወደ ኢትዮጵያ መምጣት የተነሳ ፈረንሳይኛና ጣሊያንኛ በሀገራችን ቋንቋዎች ላይ የነበራቸው ተጽእኖ በፊት ከነበረበት ደረጃ ሊያድግ አልቻለም፡፡ ነገር ግን በሀገራችን ቋንቋዎች የተወረሱት የጣሊያንኛና የፈረንሳይኛ ቃላት በዘመኑ አገልግሎት መስጠታቸውን አላቆሙም፡፡ ለምሳሌ በቀዳማዊ ኃይለሥላሤ ዘመን “ኮሚሲዮን” እንጂ “ኮሚሽን” የሚባል የአማርኛ ቃል አይታወቅም፡፡ ከፈረንሳይኛና ከጣሊያንኛ የተወረሰ የሀገርና የከተማ አጠራርም ቢሆን በአማርኛ ቋንቋ አንዳች ለውጥ ሳይደረግበት ያገለግል ነበር፡፡ እንደ ምሳሌም “ቤልጅግ”፣ “ስዊስ”፣ “ሎንዶን”፣ “መስኮብ”፣ “ብሩክሴል” የመሳሰሉትን የሀገርና የከተማ ስሞች መጥቀስ ይቻላል፡፡

    ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ መንግሥት ውድቀት በኋላ ግን ከፈረንሳይኛና ከጣሊያንኛ የተገኙ የሀገርና የከተማ ስያሜዎች ከእንግሊዞች በተወረሱ ስሞች ተተክተዋል፡፡ በዚህም መሰረት “ቤልጅግ” ወደ “ቤልጅየም”፤ “ስዊስ” ወደ “ስዊትዘርላንድ.፣ “ብሩክሴል” ወደ “ብራሰልስ”፣ “መስኮብ”ም ወደ “ሞስኮ” ተለውጠዋል፡፡ በመሆኑም ከልዩ ልዩ  ቋንቋዎች በተገኙ የቦታ ስያሜዎችና ቃላት ተውቦ ይታይ የነበረው አማርኛ የመኮማተር ባህሪን ለማዳበር ተገዷል፡፡

   ይህ ቀደምት ውርስ ስሞችን በእንግሊዝኛ አጠራሮች የመተካቱ ሂደት ሳያቋርጥ በመቀጠሉ ከሁለቱ ቋንቋዎች (ከፈረንሳይኛና ጣሊያንኛ) የተወረሱ የሀገር ስሞችን ከማራገፍ አልፎ በጥንታዊው አማርኛ ውስጥ መሰረት የነበራቸውን የሀገር ስሞችንም በእንግሊዝኛ ስያሜዎች መለወጥ ተጀምሯል፡፡ ለምሳሌ የዓለም ትልቋ ሀገር ከጥንት ጀምሮ በአማርኛ ስትጠራ “ሩሲያ” ነው የምትባለው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን “ራሽያ” የሚለው አጠራር እያየለ መጥቷል፡፡ “ስጳኝ” የሚለው ትክክለኛ የአማርኛ አጠራር “ስፔን” በሚለው የእንግሊዝኛ ቅጂ ተቀይሯል፡፡ “አርመን” የሚለው አጠራርም በ“አርሜኒያ” ተተክቷል፡፡ “ቤልጅግም” ወደ “ቤልጅየም” ተቀይሯል፡፡ “ቆጵሮስ” የሚለውን ጥንታዊ የአማርኛና የግዕዝ አጠራር “ሳይፕረስ” በሚለው አዲስ ደራሽ የቅጂ ስም የሚለውጡ ሰዎችም እየበረከቱ ነው፡፡ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን በኦፊሴል ያገለግሉ የነበሩት እንደ “ነምሳ” (አውስትሪያ) እና “ናርበጅ” (ኖርዌይ) የመሳሰሉ የሀገራት መጠሪያዎች በዚህ ዘመን በአማርኛ ቋንቋ አገልግሎት መስጠታቸውን አቁመዋል፡፡

   ለሌሎች አገልግሎቶች የሚውሉ የፈረንሳይኛና የጣሊያንኛ ውርስ ቃላትም ቢሆኑ የመጥፋት እጣ ደርሶአቸዋል፡፡ ለምሳሌ በዛሬው ዘመን ከፈረንሳይኛ በተወረሰው “ኮሚሲዮን” የሚገለገል ሰው የለም፡፡ በአማርኛና በኦሮምኛ ቋንቋዎች በስፋት ሲያገለግል የነበረው “ኦፕራሲዮን”ም በዚህ ዘመን “ቀዶ ጥገና” እና “ኦፕሬሽን” በሚሉት ስሞች ተተክቷል፡፡ “ፔኒሲዮን” የሚለው ቃልም ሙሉ በሙሉ አገልግሎቱን አቁሟል፡፡

*****

 “እነዚህ ቃላት ድሮውንም የውጪ ቃላት በመሆናቸው ከአማርኛ መጥፋታቸው የሚያስነሳው አቧራ የለም” ይባል ይሆናል፡፡ ነገሩን በታሪክና በአንትሮፖሎጂ መነጽር ካየነው ግን ትልቅ ጉዳት አለው፡፡ ምክንያቱም የነዚህ ቃላት በቋንቋዎቻችን ውስጥ መኖር የ20ኛው ክፍለ ዘመን ታሪካችን የተጓዘበትን መንገድና የእኛነታችንን ህብርነት የሚያሳይ በመሆኑ ነው፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው የፈረንሳይኛ ቃላት በአማርኛ ውስጥ በመኖራቸው ተገርሞ “ይህ እንዴት ተከሰተ?…” የሚል ጥያቄ ቢያቀርብ የጅቡቲው ምድር ባቡርና የተፈሪ መኮንን ትምህርት ታሪክ ይተረክለታል፡፡ በጣሊያንኛ ቃላት ላይ ጥያቄ ለሚያቀርብ ሰውም የአምስቱ ዓመቱ የኢጣሊያ ወረራና የአርበኞቻችን የተጋድሎ ታሪክ ይነገረዋል፡፡

በሌላ በኩል በአንድ ቋንቋ ውስጥ ያሉ ውርስ ቃላትና ሀረጋት የታሪካዊ ምርምር መሰረቶች የሚሆኑበት አጋጣሚም ሞልቷል፤ ቃላቱና ሐረጋቱ እንደ ታሪክ ማስረጃ የሚያገለግሉበት ሁኔታም አለ፡፡ ብዙ የታሪክ እንቆቅልሾች በቃላትና በሀረጋት መነሻነት ሊፈቱ ችለዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ዛሬ በግዴለሽነት ከኦሮምኛና ከአማርኛ ቋንቋ ውስጥ እየተወገዱ ያሉት የፈረንሳይኛና የጣሊያንኛ ውርስ ቃላቶቻችን ጠሊቅ የሆኑ ኪነታዊ ስራዎች የሚወጠኑበት መሰረቶች ሆነው ሲያገለግሉ ታይተዋል፡፡ እንደምሳሌም የቴዲ አፍሮን “ሼ-መንደፈር” እና “ላምባ ዲና”ን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ቴዲ እየረሳናቸው ያሉትን አንድ የፈረንሳይኛና አንድ የጣሊያንኛ ቃላትን ወስዶ የሁለት ውብ ዜማዎች መሰረት አድርጎአቸዋል፡፡ በመሆኑም ውርስ ቃላቱን በነበሩበት ሁኔታ ማስቀጠሉ ተገቢ ነው፡፡  

   በዚህ ረገድ የሀገራችን ሚዲያዎችና ፕሬሶች ሃላፊነት በጎደለው ሁኔታ እያካሄዱት ያለውን አጥፊ ሚና መግታት አለባቸው፡፡ ፈረንሳይም ሆነ እንግሊዝ፣ ጣሊያንም ሆነ ጀርመን ሁሉም ባዕድ ነው፡፡ ፊት የመጣውንና በህዝቡ ውስጥ የቆየውን ቃል አስወግዶ በሌላ የባዕድ ቃል መተካት በምንም መልኩ የስኬት መለኪያ አይሆንም፡፡ በተለይ ግን በረጅም ዘመናት የታሪክ ጉዞአችን ያዳበርናቸውንና እኛ ብቻ የምንጠቀምባቸውን ጥንታዊ የሀገርና የከተማ አጠራሮች (ሩሲያ፣ ቆጵሮስ፣ አርመን፣ ደማስቆ፣ ስዊስ፣ ኡክራኒያ፣ ቱርክ፣ ኢጣሊያ፣ ሮማ፣ አቴና፣ ሶሪያ፣ ፍልስጥኤም፣ ሊባኖስ፣ ግብጽ ወዘተ.. የመሳሰሉትን) ከእንግሊዝኛ በተኮረጁ ስሞች (ራሽያ፣ ሳይፕረስ፣ ደማስከስ፣ ፓለስታይን፣ ኢጂፕት ወዘተ..) መተካት ይቅርታ የማይሰጠው ጥፋት ነው፡፡ ቴክኖሎጂንና የተቀላጠፈ አሰራርን መኮረጅ እንጂ ነባር ቃላትን ማጥፋት የእድገት መሰረት ሊሆን አይችልም፡፡ ዐረቦችም ሆኑ ፈረንጆች፣ ቱርኮችም ሆኑ ህንዶች እንዲህ ዓይነት ጥፋት ሲያጠፉ አይታዩም፡፡ እኛም ይህንኑ ፈለግ መከተል አለብን፡፡ ስለዚህ የሚመለከተው ሁሉ ለጉዳዩ አጽንኦት ሊሰጠው ይገባል፡፡

——–

አፈንዲ ሙተቂ

ግንቦት 13/2006

ሸገር-አዲስ አበባ

ጸሓፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ

———

በዲሞትፈር፣ አርገው ገፍተር

በወጨፎ፣ አርገው ቀፎ

በሰናድር፣ አርገው ክንችር

በምንሽር፣ ያዘው አብሽር

ባጭር አልቤን፣ ደረት ልቤን፡፡

(ወዳጄ ካሳሁን አለማየሁ ከጻፈው ሀገርኛ ግጥም የተወሰደ)

*****

ጠመንዣ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ሀገራችን የገባው በ16ኛው ክፍለ ዘመን መግቢያ ላይ ነበር፡፡ በዚያ ዘመን ከሰለሞናዊ አጼ ንጉሠ ነገሥቶች ጋር ሲፋለሙ የነበሩት የአዳል ሱልጣኔት ገዥዎች ናቸው ጠመንዣን ወደ ሀገራችን ያስገቡት፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ የሰለሞናዊ ነገሥታት ወታደሮችም ጠመንዣን ለመታጠቅ ችለዋል፡፡ ወታደሮች ሙሉ በሙሉ በጠመንዣ መዋጋት የጀመሩት ግን በአድዋው ጦርነት ማግስት ነው፡፡ እስከ አድዋው ጦርነት ድረስ ጦርና ጎራዴን ከጠመንጃ ጋር በማፈራረቅ ይጠቀሙ ነበር፡፡

    እንደዚህም ሆኖ ግን የያንዳንዱ ዘመን የቴክኖሎጂ ውጤት የሆነ ጠመንዣ ወደ ኢትዮጵያ ይገባ እንደነበረ ይታመናል፡፡ የውጪ መንግሥታት ለኢትዮጵያ ነገሥታት ከሚያቀርቧቸው ገጸ-በረከቶች መካከል አንዱ ጠመንዣ ስለመሆኑም በስፋት ተጽፏል፡፡ ከነዚያ የጠመንዣ ዓይነቶች መካከል አንዳንዶቹ እስከዚህ ዘመን ድረስ ይደነቃሉ፡፡ ለምሳሌ በጅማ ከተማ በሚገኘው የአባጅፋር ሙዚየም ውስጥ አነስተኛ ከዘራ የሚመስል አንድ ጠመንዣ አለ፡፡ ያ መሳሪያ ጠመንዣ መሆኑን የምትረዱት አስጎብኚው አተኳኮሱን ሲያሳችሁ ብቻ ነው፡፡ በሌላ ቦታ ብታዩት ትንሽዬ ከዘራ ነው ብላችሁ የምታልፉት ይመስለኛል (ኮ/ል መንግሥቱ ኃይለማሪያም እንደዚያ ዓይነት የከዘራ ጠመንዣ እንደነበራቸው አንድ የቀድሞ ጦር አባል ጥቅምት 1985 በታተመው በእፎይታ መጽሔት ላይ አስነብበውን ነበረ)፡፡

   ጠመንዣ በኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት የተሰራጨው በሀያኛው ክፍለ ዘመን ነው፡፡ ከነዚያ ጠመንዣዎች ውስጥ አንዳንዶቹ ዛሬም ድረስ ያገለግላሉ፡፡ አንዳንዶቹ ግን የአገልግሎት ዘመናቸው አብቅቶ ስሞቻቸው ብቻ ቀርተውናል፡፡ በዚህ ጽሑፍ ውስጥ በጥቅሉ “አንድ በላተኛ” የሚባሉትን ጠመንጃዎች በጥቂቱ እንቃኛለን፡፡

*****

“አንድ በላተኛ” ኦቶማቲክ ያልሆኑ ጠመንዣዎች በወል የሚጠሩበት የአማርኛ ስም ነው፡፡ እነዚህ ጠመንዣዎች በኦሮምኛ “ተከ ኛቴ” (takka nyaattee) ይባላሉ፡፡ ጠመንዣዎቹ እንዲህ እየተባሉ የሚጠሩት አንድ ጥይት ብቻ ስለሚጎርሱ ሳይሆን የጎረሱትን ጥይት አንድ በአንድ የሚተኩሱ በመሆናቸው ነው፡፡ ይህም ማለት ጠመንዣው ተቀባብሎ አንዴ ከተተኮሰበት በኋላ እንደገና ማቀባበልን ይጠይቃል፡፡ በመሆኑም “አንድ በላተኛ” ከተሰኘው ስያሜ በተጨማሪ “ቆመህ ጠብቀኝ” የሚል የፉገራና የስላቅ ስያሜም ወጥቶላቸዋል፡፡

    “አንድ በላተኛ” የሆኑ ጠመንዣዎች በአብዣኛው አምስት ያህል ጥይቶችን ነው የሚጎርሱት፡፡ እነዚህም ጥይቶች ትልልቆች ናቸው፡፡ ጥይቱ ከተተኮሰ በኋላ በርቀት ላይ የሚገኝን ነገር መትቶ የመጣል ሀይሉም ከፍተኛ ነው ይባላል፡፡ በመሆኑም “አንድ በላተኛ” ጠመንዣዎች በተለይ ለአደን ስራ በጣም ተመራጭ ናቸው፡፡

  በድሮው ዘመን ለውጊያ ይፈለጉ የነበሩት እነዚህ “አንድ በላተኛ”ዎች በሰለጠነው ዓለም እምብዛም አያገለግሉም፡፡ በኛ ሀገር ግን አስከ አሁን ድረስ በጥበቃ ስራ ላይ የተሰማሩ ዘበኞችና የአካባቢ ሚሊሻዎች በብዛት የሚያነግቱት “አንድ በላተኛ” ጠመንጃዎችን ነው፡፡  

   በሀገራችን ውስጥ የብዙ ሀገራት ስሪት የሆኑ “አንድ በላተኛ” ጠመንዣዎች አሉ፡፡ እነዚህን ጠመንዣዎች የምንጠራባቸው የተለምዶ ስያሜዎች በፋብሪካ የተሰጧቸው የሞዴል ስሞች ናቸው ብሎ ለመናገር ይከብዳል፡፡ የሆነው ሆኖ በኛ ሀገር ሲያገለግሉ ከነበሩት የጠመንዣ ዓይነቶች መካከል ጥቂቶቹን እንተዋወቃቸው፡፡  

1.      ምንሽር፡

“ምንሽር” ጣሊያን ሰራሽ ጠመንዣ ነው፡፡ በሀገራችን ውስጥ በስፋት ያገለግል ነበር፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ አርበኞች የጣሊያን ወራሪዎችን የተፋለሙበት ዓይነተኛው የጠመንዣ ዓይነት ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ጠረፎችና በትግራይ ገጠሮች በአገልግሎት ላይ ያለ መሆኑ ይነገራል፡፡ በሌሎች ክልሎች ግን እምብዛም አይታይም፡፡  

2.     አልቤን:

የአልባኒያ ስሪት የሆነ የጠመንጃ ዐይነት ነው፡፡ በዚህ ዘመን ብዙም የማይታየው ይህ ጠመንጃ በኢጣሊያ ወረራ ዘመን ከፍተኛ አገልግሎት ሰጥቷል፡፡

3.     ውጅግራ፡

ይህኛው ጠመንዣ ድምጹ ብራቅ ነው ይባልለታል፡፡ እንደ ከርከሮ እና ጅግራ ያሉት እንስሳት ወደ ሰብል ማሳ እንዳይጠጉ ለመከላከል ከተፈለገ አንድ የውጅግራ ጥይት ይበቃቸዋል፡፡

4.     ረሽ፡

ብዙ ጊዜ ለአደን ስራ የሚያገለግል ነው፡፡ ለዚህም ያግዝ ዘንድ በጠመንዣው ላይ የማነጣጠሪያ “ቴሌስኮፕ ተገጥሞለታል፡፡ ብዙ ሰዎች “መተሬ” (sniper) እያሉ የሚጠሩት ጠመንዣ እርሱ ሳይሆን ይመስለኛል፡፡

 ይህ ጠመንዣ ጥይት በሚጎርስበት ጊዜ ከሰደፉ በኩል ሰበር ብሎ ይቆለመማል፡፡ በተጨማሪም ሁለት አፈሙዝ ነው ያለው፡፡ ጥይቱ ከተተኮሰ በኋላ በአየር ላይ ስለሚበተን እንደ ጅግራ፣ ቆቅና ዳክዬ መሳሰሉ አዕዋፋት በመንጋ በሚበሩበት ወቅት ለማደን ተመራጭ ነው፡፡ ረሽ በሰሜን ኢትዮጵያ ገጠሮች “ግንጥል” የሚል ስያሜ እንዳለው “እንዳላማው አበራ” የሚባል የፌስቡክ ጓደኛዬ አጫውቶኛል፡፡

5.     ዲሞትፈር

በኢትዮጵያ ውስጥ በብዛት የተሰራጨ የጠመንጃ ዓይነቶች አንዱ ነው፡፡ የዘንጉ ርዝማኔ ይለያያል፡፡ ከዚህ ጠመንዣ ጋር በተያያዘ በሀገራችን ውስጥ ታሪካዊ እና አወዛጋቢ የሆነ አንድ አባባል ተፈጥሯል፤ “ዲሞን በዲሞትፈር” የሚል፡፡ አባባሉ የተፈጠረው በዘመነ ቀይ ሽብር ነው፡፡ “ዲሞ” እየተባሉ የተጠሩት የኢህአፓ አባላትና ደጋፊዎች ናቸው፡፡ (“ዲሞ” የኢህአፓ ልሳን ከነበረችው “ዲሞክራሲያ” ጋዜጣ ስያሜ ላይ የተቀነጨበ ነው)፡፡

   ይህ አባባል ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰማው ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም ጥር 26 ቀን 1969 በተቀናቃኝ የደርግ አባላት ላይ  የወሰዱትን እርምጃ ለመደገፍ በሚል በቀጣዩ ቀን በተዘጋጀው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ነው፡፡ ብዙ ጸሐፍት እንደሚሉት “ዲሞን በዲሞትፈር” የሚለውን አባባል ፈጥረው ወደ አደባባይ ያወጡት የመኢሶን አመራሮች ናቸው፡፡ መኢሶን ግን ነገሩን ያስተባብላል፡፡ ያም ሆነ ይህ አባባሉ “ዲሞትፈር” ጠመንዣ በቀይ ሽብር አፈጻጸም ውስጥ የነበረውን ሚና የሚያስረዳ ይመስለኛል፡፡

ዲሞትፈር በሀገራችን ውስጥ አሁንም በስፋት ያገለግላል፡፡ ይሁንና በጎንደርና ጎጃም ክፍለ ሀገራት ይበልጥ የሚታወቀው “ጓንዴ” በሚለው ስም ነው፡፡

  

6.     ቺኮዝ

በደርግ ዘመን የመጨረሻ ዓመታት በቀበሌ ደረጃ የተደራጁ የአብዮት ጥበቃ ጓዶች ሲታጠቁ የነበሩት ጠመንዣ ነው፡፡ ከስያሜው ለመረዳት እንደሚቻለው ጠመንጃው የተሰራው በቼኮዝሎቫኪያ ነው፡፡ ቼኮዝ ግራጫ ቀለም ያለው ጠመንዣ ነው፡፡

ቺኮዝ በጣም አደገኛ መሳሪያ ነው፡፡ ጥይቱ ወደ ሰውነት ሲገባ ቀዳዳው ትንሽ ነው፡፡ ሲወጣ ግን አካልን በሰፊው ቦድሶ ነው የሚወጣው፡፡ አንድ ሰው በቺኮዝ መመታቱን ለማወቅ ጥይቱ የገባበትንና የወጣበትን ቦታ ብቻ መመልከት ይበቃል፡፡

7.     ቤንቶቭ

“አንድ በላተኛ” ጠመንዣዎች ሁሉ ለመሸከም የማይከብደው ይህኛው ነው፡፡ የጠመንዣው እንጨትም ጥቁር ቡናማ መልክ አለው፡፡ በደርግ ዘመን የቀበሌ ጥበቃ ጓዶች ከቺኮዝ ቀጥሎ በብዛት ይታጠቁ የነበሩት ቤንቶቭን ነው፡፡

*****

እላይ ከዘረዘርናቸው መሳሪያዎች ሌላ ወጨፎ፣ ቤልጅግ፣ መውዜር፣ ሰናድር፣ ናስማሰር፣ ጉንጮ፣ ስኩዌር ወዘተ… የሚባሉ “አንድ በላተኛ” ጠመንዣዎች በሀገራችን ውስጥ በስፋት ያገለግሉ እንደነበረ መዛግብትና የቃል ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ ከላይ እንደገለጽኩት በውጪው ዓለም በከፍተኛ ፍጥነት እየተለወጠ በመሄድ ላይ የሚገኘው የመሳሪያና የወታደራዊ ምህንድስና ቴክኖሎጂ እነዚህን አንድ በላተኛ ጠመንጃዎች ከአገልግሎት ውጪ አድርጎአቸዋል፡፡ በሀገራችንም ውስጥ ብዙዎቹ ለጥበቃ ስራ ቢያገለግሉም በቅርብ ዓመታት አገልግሎታቸውን ማቋረጣቸው እንደማይቀር ይታመናል፡፡ ቢሆንም አባቶቻችን ታሪክ ሲሰሩ የነበሩት በነርሱ ነውና የያንዳንዱን መሳሪያ ስርጭትና የአገልግሎት አድማስ መዝግቦ ለመጪው ትውልድ ማቆየት ይገባል፡፡ ሰላም!!

እ ጎ አ፣ ከ 2003 ዓ ም አንስቶ ፣ ላለፉት 11 ዓመታት ገደማ ፣ ቱርክን በ ጠ/ሚንስትርነት ሲያስተዳድሩ የቆዩት ሪቸፕ ጣይብ ኤርዶጋን፣ በዚያች ሀገር ለመጀመሪያ ጊዜ ፕሬዚዳንት በህዝብ እንዲመረጥ በተደረገበት ደንብ፤

የጀርመን ብሄራዊ የእግር ኳስ ቡድንና የባየር ሙኒክ ግብ ጠባቂ ማኑዌል ኖየር የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ተባለ። ኖየርን የመረጠዉ ታዋቂዉ የጀርመን የስፖርት መጽሔት ኪከር የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ዮአኺም ለቭንም የዓመቱ ምርጭ አሰልጣኝ በማለት መርጧል።

ባለፈው ሳምንት 24 ኢትዮጵያውያን ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ 16 ሰዎችን በምትጭን አንዲት ታክሲ ውስጥ ተሳፍረው ሲጓዙ የትራፊክ ፖሊስ እንዳስቆማቸው እና በብሪክስተን የፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተሰምቷል።

በሃይማኖት ተጨቁነው እና በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ወደሚገኝ ተራራ ተሰደው የሚገኙ 20 000 የሚደርሱ የያዚዲ እምነት ተከታዮች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ እንደሆነ ነው የሚሰማው። ይህም አንዳንድ ጠበብት እንደሚሉት አሜሪካ ጣልቃ ከገባች በኋላ የተገኘ ለውጥ ነው።

Befekadu Hailu Zone 9 Blogger በፍቃዱ ኃይሉ (የዞን 9 ብሎገር ከቂሊንጦ እስር ቤት)በፍቃዱ ኃይሉ (የዞን 9 ብሎገር ከቂሊንጦ እስር ቤት)

”ታዲያ ጥፋቴ ምንድን ነው ትላለህ?!”፣ ብሎኛል አንዱ መርማሪዬ ስለዞን ዘጠኝ እና እኔም እራሴ እንደጦማሪም እንደአራማጅ ተራማጅም ሠራሁ የምላቸውን ነገሮች ዝርዝር ነግሬው ሳበቃ። በኋላ ላይ በእስር ቤት ቋንቋ ከ”አባሪዎቼ” ጋር መገናኘት ከተፈቀደልን በኋላ ስንጠያየቅ  ለካስ ሁላችንም ይቺኑ ጥያቄ ተጠይቀናል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Befekadu Hailu Zone 9 Blogger በፍቃዱ ኃይሉ (የዞን 9 ብሎገር ከቂሊንጦ እስር ቤት)በፍቃዱ ኃይሉ (የዞን 9 ብሎገር ከቂሊንጦ እስር ቤት)

”ታዲያ ጥፋቴ ምንድን ነው ትላለህ?!”፣ ብሎኛል አንዱ መርማሪዬ ስለዞን ዘጠኝ እና እኔም እራሴ እንደጦማሪም እንደአራማጅ ተራማጅም ሠራሁ የምላቸውን ነገሮች ዝርዝር ነግሬው ሳበቃ። በኋላ ላይ በእስር ቤት ቋንቋ ከ”አባሪዎቼ” ጋር መገናኘት ከተፈቀደልን በኋላ ስንጠያየቅ  ለካስ ሁላችንም ይቺኑ ጥያቄ ተጠይቀናል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

#Ethiopia #FreeZone9Bloggers #FreeEdom #FreeTesfalem #FreeAsmamaw #FreeAllPoliticalPrisoners

“Dear Hyena no need for excuses, just eat me” – Ethiopian Proverb 
By BefeQadu Hailu

“So what do you think is your crime?” I was asked by one of my interrogators while I was telling him about what I did as a blogger, an advocate and an activist. Later on, after I was allowed to meet with my “collaborators” according to my prisoners and asked each other, we found out we were all asked this same question “what do you think is your crime”? This describes the overall outcome of our interrogation. Since they couldn’t figure out what our supposed crime was or what law we were suspected of violating, we were asked “So what do you think is your crime?”. The interrogation was not to ultimately find out whether we are innocent or not but to find anything that could be a crime. Some have asked why the Government has tolerated Zone 9 for 2 years, because tolerance isn’t in its nature. Ethiopia’s Freedom of expression, as I have imagined, has easily gotten us arrested, interrogated, alleged with being a member of Ginbot 7 (OLF as well) and is prosecuting us. The rest will be left for the court to deal with in time.
Many people who have known Zone 9 in the past could be confused and would demand an explanation to figure out why we’re being prosecuted. This is what has forced me to respond in this short piece. How did we get here? What is our imprisonment like? How was the interrogation? Are we really members of Ginbot 7? If not then why were we arrested? Will we be released soon?
Whether a scholar or a layman, anyone who writes about Ethiopian politics will always have a fear of being imprisoned. That is why, I think, Professor Mesfin wrote on one of his books that the people of Ethiopia are of three categories, the imprisoned, the imprisoned and released, and the one that is waiting to be imprisoned. In fact everyone that has refrained from expressing ones views in fear of persecution is technically imprisoned and can easily put all the categories into one, the imprisoned. Two weeks after we officially started blogging as Zone9ers, we had to set up a second blog after our first one was blocked in Ethiopia. We knew one day that it will be us who will be locked up behind bars. We were under surveillance, have been receiving threats and signals that indirectly revealed what is to come. Though our arrest caught us by surprise, it was not unexpected.   
Following the surveillance, the arrest targeted six members of Zone9 and three journalist who are our close friends. The arrest of the three journalists has been a complete surprise at least to us. Later we were able to understand their arrest in relation to their friendship and closeness to us was well orchestrated as a sweep up operation. All of us except Asmamaw were arrested on Friday April 25th at 5:00pm from different locations at the same time. Asmamaw was arrested the next day on Saturday. They were also conducting the search warrant in our houses after it expired at 6:00pm.The brutal and unjust treatment started immediately after our arrest.

The picture shows the six bloggers and three journalists

For anyone who knows about the notorious Maekelawi, finding oneself in its compound sends shocks to the heart. In the contrary I was a bit optimistic and knew my friends have felt the same the minute they stepped in because one we are bloggers not soldiers or spies and two I had a foolish impression that there is better human treatment than the bygone era of the past.  On the first day an inmate conveyed to me that I am in the worst part of Maeklawi called Siberia. Later it took me less than a week to admit what was written in the report “They want a Confession”  by HRW was all true.
Interrogation Maekelawi Style
Interrogation in Maekelawi is more brutal than technical. The interrogators spend more time trying to show their skill than actually interrogating and attempting to find out more. If that doesn’t work they will slap, kick and make the prisoner perform tough physical exercise. These are among the few things that I went through in the hands of the five interrogators and also what I heard from other inmates. Some are made to stand naked and do sit ups. Other inmates told me that they have gone through even more brutal punishments like hanging upside down and removing nails but that was before they were moved to Maekelawi. Among them were students from Haromaya University  Intriguingly the confession the prisoners give after such punishment was brought to Maekelawi as an evidence to their alleged crime. Similarly these prisoners had their eyes covered so that they would not know where they were. This reminds me of DERGs Bermuda – another notorious place of interrogation. 
Hence we gave our confession after being humiliated, insulted and brutally treated under the roof of the horrific Maekelawi. Our confession was 100% untrue. When the brutal force used against us became unbearable we admitted to crimes of “Conspiring to instigate violence”. While taking notes they were making sure every word we spitted out was twisted as “self-incriminating” to help with our prosecution. We argued to the best of our physical and mental abilities and when it became impossible we signed the documents, they beat us to sign these documents. The only person who managed to withstand the beating was Abel, who refused to sign by saying “I will not sign anything other than my own confession”.
The important thing that we understood was that Maekelawi’s interrogators are experienced in brutality than fundamental intelligence. I always had an impression that the police will acquire all the relevant evidence and then interrogate the prisoner how and why they carried out the crime. Thanks to Maekelawi now I understand that interrogation starts with “What is the crime you committed? Tell us!” Maekelawi style. “I am innocent” will always fall on deaf ears. Once you are arrested, you must admit to a crime or else they will bake one for you.
When I think about it now, Maekelawi investigation center needs a fundamental restructuring due to two important reasons.
1.     The interrogation technique (as I have understood from our case) is more about carrying out an order, meaning it is not strategized or determined on case by case basis.  
2.     The interrogation is not knowledge or intelligence based. And this will endanger the security of the country as such approach will certainly fail to gather, capture or control real threat. This problem occurs because police investigators are recruited more based on loyalty and a willingness to take orders than carrying out skillful investigation.  
The Goat is here but the herder rod is there, afar
In the interrogation process what we were forced to sign was an admittance to inciting violence through the articles we have written, the campaigns we conducts, the trainings we took or the trainings some of us gave hence our expectation was to be charged with crime under the criminal code 238 and 257.  Unfortunately we were charged with Terrorism, a crime that could get us 15 year to life sentence. This actually made me laugh. 
The evidence that were brought against us were the articles we wrote, the campaigns we conducted, the press releases and training manuals. In addition to these were documents of Ginbot 7 and OLF which they claimed they found under our possession. First evidence was Ginbot 7’s newsletter that was sent to Natnail Feleke in September 2009 that is way before the Anti-Terrorism Proclamation was set in motion and way before Ginbot 7 was convicted as a Terrorist organization. The second was a Ginbot 7 recruitment document claimed to be found in Soliyana’s home in which her mother refused to sign accepting the document was found in the house. What I remember, before my arrest was Soliyana’s twitter bio read “No for war”. The third evidence was OLF’s program that was found on Mahlet’s computer. Apparently there were other Oromo Party programs found as well but were not presented as evidence. Neither was she asked why OLF’s or other Oromo party programs were found in her computer while she’s being prosecuted for possessing only one? Needless to say, having these documents does not and does not mean working with them or agreeing with what they do. This wasn’t clear to our interrogators but I am sure our compatriots and friends will definitely understand.
The other laughable charge was that states “they have accepted and distributed among themselves 48 thousand Birr(Eth) that was sent through Natnail Feleke”. Though the charge is written so as to create an impression that the money was sent from the so called “Terrorist Organizations, the bank receipt shows that the money was sent from Article 19. We explained to the interrogators that the money was sent to an imprisoned journalist and her family. They still made it part of the charge not because they believed we are criminals but rather due to their evil intention of getting us punished or use it to buy time during the series of court appearances.
Stop looking for excuses!
A donkey and a hyena were drinking at the river. The donkey was drinking downstream and the hyena was drinking upstream. The hyena looked at the donkey and said, “You dirty fellow, you’re dirtying the water.”
The donkey said, “That’s impossible. I’m drinking from downstream.” The hyena said, “But you are.”
The donkey said, “Look, if you want to attack me, stop looking for excuses.” Such is our story!
The police arrested us with no evidence. They did not even know more than our names. By the time they arrested us, they had not even read a collection of our writings that we sent them through one of their security agents. And I believe that ninety percent of the “document” evidence the police presented against us now are our own writings which we gave them in good faith. In our interrogator’s statements, we have seen their desperate interest to make us criminals. As we guessed it, maybe they do not want our presence on social media, at least until the upcoming 2015 election. May be they have not found other options. 
So far, we have witnessed how the investigators are biased towards the ruling party. What follows is for us to publicly test the justice system. For now, however, could we be free soon? I will say we’ve theoretical, not legal options. 
When EPRDF (or the police that EPRDF orders) arrested us, they did not have a “beyond reasonable doubt” evidence, as the lawyers would say. They only hoped to find a mistake, any mistake. However, they have found nothing that could stick and make us criminals within the anti-terrorism law which is already criticized for being  a potent tool for suppressing political opposition and independent criticism of government policy to mean stretched to its limit.
However, the fact that they were not able to find evidence did not prevent them from their objective of charging us. The fact that they did not even write a coherent statement by the time they appeared in court to charge us is an evidence that they do not have a valid suspicion or evidence. Yet, I do not believe that they will release us soon. Why?
1st Unless it is in a humiliating way, one of the things EPRDF does not do is release individuals it detains, especially those who have many supporters. By this I mean EPRDF is as stubborn as a child. (I am not saying I do not like the cries against our unjust detention. Our spirit would not have healed without such a support. We will, one day, publicly say thank you)
 2nd. Their initial paranoia and the paranoia that they found was wrong: meaning, even if they know that we have no plan (following the election) to instigate violence, may be they do not want to miscalculate and take a risk. (one recalls the intentions of the documentary “Colour revolution” to begin with)
3rd. Even though they believe that we have no intention or the capacity to instigate violence, they know that we are strong critics of the ruling party and they do not like it. For this reason, they want us to suffer the bitter reality of detention. At least serving time and following our case in court. It’s as if being released after finishing our sentence.
4th EPRDF is not afraid of judging


Translated by Mahilet Solomon

”ለሰብአዊ መብትና ለዴሞክራሲ ጥብቅና መቆም ሽብርተኝነት ነው”፡- የጸረ ሽብርተኝነት አዋጅ

የሂዩማን ራይትስ ዎች የዓለም አቀፍ ዘገባ ስለ ኢትዮጵያ፤ በኢትዮጵያ የፖሊስ ሃይል፤ በጦር አባላትና በሌሎችም ተመሳሳይ አባላት፤ በደህንነት አባላት በቅጣት መልክ በተቃዋሚ ደጋፊዎችና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ላይ የሚፈጸመው ስቃይና የእስረኞች የአያያዝ ሁኔታ አሳሳቢነትና መከራ የከፋ ከመሆኑም ባሻገር በሚስጣራዊ ማጎሪያዎች፤ በወታደራዊ ካምፖች ውስጥ በእስር የሚገኙት ንጹሃን ዜጎች ሁኔታ አሳሳቢነቱ በየጊዜው እየከፋ የሚሄድ መሆኑን በተደጋጋሚ በግልጽ አስቀምጧል፡፡በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች መለቀቅ አለባቸው፡፡ ሁኔታቸው በአ……..

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ//

http://wp.me/p3p0Hd-CG

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በሃገሪቱ ያለውን ሁኔታ በትክክለኛው መንገድ የማያስቀምጡ የወያኔ ፕሮፓጋንዲስቶች እርስ በእርሳቸው የሚጋጩ ዘገባዎችን በመስራት እና እውነትን ለመሸፋፈን በመትጋት የሕዝቦችን የማወቅ መብት ያለርሕራሄ እየተጋፉ ይገኛል። ይህ በወያኔ የፕሮፓጋንዳ አካላት የሚፈጸም ማጭበርበር እና ማደናገር የገዢውን ፓርቲ ውስጣዊ ዝርክርክነት በይፋ ያሳብቃል።ያለለውን እንዳለ ድሮ ተግንብቶ የታደሰውን እንደ አዲስ እንደተገነባ ፤ ያልተሰራውን እንደተሰራ ሕዝቡ የማያገኘውን አገልግሎት እንደሚያገኝ ወዘተ በማድረግ በሁለት እና […]

በደቡብ ሱዳን የሚካሄደው የርስ በርስ ጦርነት የሚያበቃበትን መንገድ የሚያፈላልገው ተቋርጦ የነበረው የሰላም ድርድር ባለፈው ሰኞ አዲስ አበባ ውስጥ ቢጀምርም፣ በደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር አንፃር የሚፋለሙት

የአንድ ሀገር መገበያያ ገንዘብ በተለያዩ ምክንያቶች ዋጋዉ ወይም የመግዛት አቅሙ የሚቀንስበት አጋጣሚ በርካታ ነዉ። በተለይ ደግሞ ጠንካራ ከሚባሉት ዓለም አቀፍ መገበያያ ገንዘቦች ጋ ሲወዳደር እያደር አቅሙ ዝቅ የሚልበት አጋጣሚ ነው ያለው ።

‹‹ታዲያ ጥፋቴ ምንድን ነው ትላለህ?!››፣ ብሎኛል አንዱ መርማሪዬ ስለዞን ዘጠኝ እና እኔም እራሴ እንደጦማሪም እንደአራማጅ ተራማጅም ሠራሁ የምላቸውን ነገሮች ዝርዝር ነግሬው ሳበቃ፡፡ በኋላ ላይ በእስር ቤት ቋንቋ ከ‹‹አባሪዎቼ›› ጋር መገናኘት ከተፈቀደልን በኋላ ስንጠያየቅ  ለካስ ሁላችንም ይቺኑ ጥያቄ ተጠይቀናል፡፡ ይኼ ነው እንግዲህ የምርመራችንን ሒደት የሚገልፀው ጥያቄ፡፡ ‹‹ተጠርጥረን›› የተያዝንበትን ጉዳይ የሚያረጋግጥ ሥራ ሠርተን ባለመገኘታችን (ወይም ‹‹ባለመናገራችን››) ታዲያ ጥፋትህ ምንድን ነው? ተባልን፡፡ ምርመራው የኛን ነፃ መሆን አለመሆን ለማጣራት ሳይሆን ጥፋት ለማግኘት ነበር፡፡ ብዙዎች ‹መንግሥት ዞን ዘጠኝን ለምን ሁለት ዓመት እንደታገሠው› ግራ በመጋባት ይጠይቃሉ፤ ባሕሪው አይደለምና፡፡ የኢትዮጵያ ሀሳብን የመግለጽ ነጻነት ምኅዳር በቀላሉ እንደገመቱት ተይዘን፣ ተመርምረንና ‹‹ተገኘባችሁ›› የተባልነው ‹‹ የግንቦት 7 [እና ኦነግም ጭምር] አባልነት [ብሎም ግብ አስፈጻሚነት] ›› በሽታ ለተከሳሽነት አብቅቶናል፡፡ ቀጣዩ የክርክር ሂደት ነው፡፡
ከዚያ በፊት ግን ዞን ዘጠኝን በሩቅም በቅርብም የሚያውቁ በግራ መጋባት መልስ እንደሚሹ በማሰብ ይቺን አጭር ማስታወሻ ለመጻፍ ተገድጃለሁ፡፡ የእስራችን ሂደት ምን ይመስላል? የምርመራችንስ? እውን የግንቦት ሰባት አባል ነን? [ታዲያ] ለምን ታሰርን? በቅርቡ እንፈታ ይሆን? 
ደቂቅም ይሁን ሊቅ ስለኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እውነታ የሚጽፍ ማንኛውም ሰው [ኢትዮጵያ ውስጥ ሳለ] አንድ ቀን እታሰር ይሆን እያለ መስጋቱ አይቀርም ፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም በአንድ መጽሐፋቸው ላይ ሰው ነገረኝ ብለው የኢትዮጵያ ሕዝብን በሦስት የመደቡት፡- የታሰረ፣ ታስሮ የተፈታ እና ወደፊት የሚታሰር በማለት፡፡ እርግጥ ዞን ዘጠኝ ‹‹ሐሳቡን መግለጽ ፈርቶ ዝም ያለ ሁሉ እስረኛ ነው›› ብሎ መደምደም ሦስቱም ምድብ አንደኛው ውስጥ ያጠቃልለዋል ‹‹የታሰረ›› በሚል፡፡ ዞን ዘጠኞች ጦማራችንን በከፈተን በሁለት ሳምንት ሲታገድብን እና ሌላ ስንከፍት ግና መጨረሻ ላይ ታጋቾቹ እኛ እንደምንሆን እናውቅ ነበር፡፡ ያንን የሚያረጋግጥ ተደጋጋሚ የደህንነቶች ክትትል እና ምልክቶች ስለደረሱን መታሰራችን ማስደንገጡ ባይቀርም ያልተጠበቀ ግን አልነበረም፡፡
እስሩ በክትትሉ የተገኘነውን ስድስት የዞን ዘጠኝ አባላት እና ሦስት ጋዜጠኛ ጓደኞቻችንን መሆኑን በተለይ የጋዜጠኞቹ [ቢያንስ ለእኛ] ያልተጠበቀ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ የኋላ ኋላ ስንመለከተው ግን በእኛ አስታኮ እነሱንም ማሰሩ የታሰበበት ዘመቻ እንደሆነ መገመት አይከብድም፡፡ እኛን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሒደትም ቢሆን በቅጡ የታሰበበት ነበር ሁላችንም (ከአስማማው በቀር) ከቀኑ በ11፡00 ገደማ በያለንበት ስንያዝ አስማማው በማግሥቱ ታስሯል፡፡  ሌሎቻችን ቤታችን በሚፈተሸበት ሰዓት ሕጉ የሚፈቅድበት ሰዓት(12፡00) አልፎ ነበር፡፡ በቁጥጥር ስር ካዋሉን በኋላ የሕገ-ወጥ አያያዝ ሰለባ የመሆናችን ሂደት የሚጀምረው ከዚህ ነው፡፡
ማዕከላዊን በክፉ ስሙ ቀድሞ ለሚያውቀው ሰው ግቢውን መርገጥ በራሱ ልብን ያርዳል፡፡ ሆኖም በልቤ /ጓደኞቼም እንደእኔ ሳይሰማቸው አይቀርም/ አንደኛ እኛ ጸሐፊ እንጂ ወታደር ወይም ሰላይ ባለመሆናች፣ ሁለተኛ መቼም ከበፊቱ የተሻለ ሰብዓዊ አያያዝ ሳይኖርም አይቀርም የሚል የዋህ ተስፋ በማሳደሬ ብዙም አልተሸበርኩም ነበር፡፡ የገባሁ እለት ከታሳሪዎች በተሰጠኝ ማብራሪያ ‹‹ሳይቤሪያ›› መግባቴን አወቅኩ፡፡ ከዚያ የ HRW-They want confession የተሰኘ ሪፖርት ላይ የተፃፉ ነገሮች ሁሉ ትክክል መሆናቸውን ለመረዳት የፈጀብኝ ከአንድ ሳምንት ያነሰ ጊዜ ነበር፡፡
ምርመራ ማዕከላዊ ስታይል
ምርመራ በማዕከላዊ ከብልጠት ይልቅ ጉልበት ይበዛበታል፡፡ መርማሪዎቹ የምርመራ ችሎታቸው ተጠርጣሪውን የተጠረጠረበትን ጉዳይ ከማውጣጣት ይልቅ የምርመራ ችሎታ እንዳላቸው ለማሳመን የሚጥሩበት ጊዜ ይበዛል፡፡ ይህም አልሰራ ሲል ጥፊ፣ ካልቾ፣ ከአቅም በላይ ስፖርት ማሰራት እና ግርፋት ድረስ ይዘልቃሉ፡፡ ይህ እንግዲህ እኔ ላይ ከተፈራረቁብኝ አምስት መርማሪዎች እና ሌሎችም አብሮ ታሳሪዎቼ ከነገሩኝ የተረዳሁት ነው፡፡ እርግጥ ሌሎች ‹‹እርቃንን ቁጭ ብድግ›› የሰሩ ተጠርጣሪዎችም ገጥመውኛል፡፡ ከባባድ ቅጣት (ወፌ ላላ ግርፋት፣ ጥፍር መንቀል) የደረሰባቸው ሌሎች ታሳሪዎች አብረውኝ የታሰሩ ቢሆንም ይህ የተፈፀመባቸው ግን ወደማዕከላዊ ከመምጣታቸው በፊት  ነው፡፡ ከነዚህ መካከል የሀሮማያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ይገኙበታል፡፡ የሚገርመው በዚህ ዓይነቱ ምርመራ የሰጡት ቃል ለማመሳከርያ ማዕከላዊ መምጣቱ ነው፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ወደማዕከላዊ ከመዛወራቸው በፊት ከባድ ቅጣት የተቀጡበትን ቦታ የት እንደሆነ እንዳያውቁ አይናቸው ተሸፍኖ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ እሥረኞችም መኖራቸው ነው – የደርግን ‹‹ቤርሙዳ›› ያስታውሳል!
እናም በሚያዋርድ እና ክብርን በሚነካ ስድብ በሚያስፈራ የቤቱ (የማዕከላዊ) ጥላ እና ኃይል በተቀላቀለበት የምርመራ ሂደት የተከሳሽ ቃላችንን ሰጠን፡፡ ቃላችን መቶ በመቶ እውነት አልነበረም፡፡ ጫናው በበረታ ቁጥር መስማት የሚፈልጉትን ‹‹ዓመፅ ለመቀስቀስ ፈልገን›› የመሳሰሉ በራስ ላይ ፈራጅ (Self-incriminating) ሐረጎችን እየተናገርን ነበር፡፡ ያም ግን ለመርማሪዎቻችን በቂ አልነበረም፡፡ ስለዚህ በሚጽፉበት ሰዓት እያንዳንዷን ‹‹ሠራን›› ያልነውን ሁሉ ሊያስከስሰን በሚችልበት ሁኔታ እየገለበጡ እና እየበጠበጡ ፃፉት፡፡ አንዳንዶቻችን እየተከራከርን ሲያቅተን ፍርድ ቤት ይፍታው ብለን ፈረምን፣ቀሪዎቻችን የቻልነውን ያህል ተደብድበንበት ፈረምን፡፡ ‹‹ከተናገርኩት ቃል ውጪ አንድም ቃል አልፈርምም›› በሚል እስከመጨረሻው ታግሎ የተሳካለት አቤል ብቻ ነበር፡፡
በምርመራው ሂደት የተረዳነው ነገር ቢኖር የማዕከላዊ መርማሪዎች ብቃት (Intelligence) አርጩሜ ብቻ መሆኑን ነው፡፡ እኔ ምርመራ ሲባል ይመስለኝ የነበረው ፖሊሶች ተጠርጣሪዎችን ፈፀሙ ስለሚባለው ነገር በቂ መረጃ ይዘው ግፋ ቢል ለምንና እንዴት እንደፈፀሙት ማውጣጣት ነበር፡፡ ‹‹ዕድሜ ለማዕከላዊ›› የተረዳሁት ነገር ቢኖር ምርመራ ማለት ለካስ ‹‹የሠራኸው ወንጀል ምንድን ነው?አውጣት!›› ማለት ኖሯል- ማዕከላዊ ስታይል፡፡ ‹‹ነጻ ነኝ›› ቢሉ ሰሚ የለም፡፡ አንዴ ታስረሃል ወንጀል ሊገኝብህ የግድ ነው፤ ካልሆነ ይጋገርብሃል፡፡
አሁን ሳስበው ማዕከላዊ ፈርሶ በሥር-ነቀል ለውጥ እንደገና መቋቋም ያለበት ተቋም ነው፤ ቢያንስ በሁለት ምክንያት፡፡ አንደኛ የምርመራው ሂደት (በራሳችን ጉዳይ እንደተረዳሁት) ትዕዛዝ አስፈፃሚነት ይስተዋልበታል፡፡ ማለትም በመርህ የሚመራ አይደለም፡፡ ሁለተኛ ምርመራው እውቀት መር አይደለም፡፡ ይህ ደግሞ የአገሪቱን ደህንት አደጋ ውስጥ የሚጥል ጉዳይ በምርመራው ድክመት ሳይታወቅ ሊታለፍ ይችላል፡፡ ይህ ችግር የተከሰተው ደግሞ መርማሪ ፖሊሶቹ ከብቃት ይልቅ ለታዛዥነት የተመቹ ታማኞች ሆነው በመመልመላቸው ነው፡፡
‹‹ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ››
በምርመራው ሂደት የተጨቀጨቅነውም ሆነ ተገድደን የፈረምነው ጽሑፎቻችንን የበይነ መረብ ዘመቻዎቻችንን፣ የወሰድናቸው ስልጠናዎችም ሆኑ አንዳንዶቻችን የሰጠናቸው ስልጠናዎች አመፅ ለማስነሳት መሆኑን ‹‹እመኑ›› በሚል ስለነበር የጠበቅነው ግፋ ቢል በወንጀለኛ መቅጫው አንቀጽ 238 ወይም 257 ሊከሱን አስበው ነው ብለን ነበር፡፡ ይሁን እንጂ የክስ መዝገቡ ሲመጣ ‹‹ሽብር›› ያውም ከአስራ አምሰት ዓመት እስከ እድሜ ልክ የሚያስቀጣ አንቀጽ 4 መሆኑን ሳውቅ በበኩሌ ሳቄ ነበር የመጣው፡፡
ማስረጃ ተብለው ከክስ መዝገቡ ጋር የተያያዙት በአብዛኛው ጽሑፎቻችን፣ የዘመቻዎቻችን፣ የጋዜጣ መግለጫዎች እና በተለያዩ ሥልጠናዎች ወቅት የተዘጋጁ የሥልጠና መመሪያዎች (Manuals) ናቸው፡፡ ከዚህ በተረፈ ከግንቦት 7 እና ከኦነግ ጋር ያገናኛችኋል የተባልነው በሦስት ‹‹ሰነዶች›› ነው፡፡ አንደኛው ናትናኤል ኢሜይል ውስጥ በጥቅምት 2001 ተልኮለት የተገኘ የግንቦት 7 የዜና መጽሔት ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ገና የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ አዋጁ ሳይወጣ፤ ግንቦት ሰባትም አሸባሪ ከመባሉ በፊት መሆኑ ነው፡፡ ሁለተኛ ሶልያና ቤት ተገኘ ተብሎ እናቷ ‹‹ቤቴ ውስጥ አልተገኘም፣አልፈርምበትም›› ያሉት እና ለግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል ሰራዊት ምልመላ መመዘኛ ሰነድ ነው፡፡ ይህ የሶሊ የዘለቀ አቋም ለሚያውቅ ሙግት አያስፈልገውም፡፡ እኔ እንደውም ትዝ ያለኝ ከመታሰሬ በፊት የትዊተር ፕሮፋይሏ ውስጥ የነበረው ‹‹no for war›› የሚል መፈክር ነው፡፡ ሦስትኛው ደግሞ ማሕሌት ኮምፒውተር ውስጥ የተገኘው የኦነግ ፕሮግራም ነው፡፡ በርግጥ አብረው የተገኙት የሌሎች የኦሮሞ ፓርቲዎች ፕሮግራሞች ማስረጃ ተብለው አለመቅረባቸው መረዳት ብቻ – እሷም ለምን ፕሮግራሙን እንደያዘችው፤ እነሱም ለምን የኦነግን እንደመረጡ ያጋልጣልና የእመኑኝ ሙግት አያስፈልገንም፡፡ በመሰረቱ ሦስቱንም ‹‹ሰነዶች›› መያዝ ከቡድኞቹ ጋር ግንኙነት መመሥረት የሚሰሩትንም መውደድ ማለት አየደለም፡፡ ይህም ለመሪዎቻችን ባይታያቸውም እንኳ ለወገኖቻችን የጠፋቸዋል ብዬ አላስብም፡፡
ሌላውና በአስቂኝለቱ ተወዳዳሪነት የሌለው ውንጀላ ‹‹48 ሺሕ ብር በናትናኤል በኩል ተቀብለው ተከፋፍለዋል›› የሚለው ነው፡፡ ይህ ብር ፤‹‹አሸባሪ›› ከተባሉት ቡድኖች የተወሰደ እንዲመስል በሚያደናግር አገላለጽ የተጻፈ ቢሆንም የክስ መዝገቡ ውስጥ የተያያዘውና ገንዘቡ የመጣበት ደረሰኝ እንደሚያረጋግጠው የተላከው ከARTICLE 19 ነው፡፡ ይህንን ጨምሮ በእስር ላይ ለምትገኝ ጋዜጠኛ ቤተሰቦች መደገፊያ /ለእስረኛይቱም ማበረታቻ/ የተላከ መሆኑን ለመርማሪዎቹ በዝርዝር አስረድተናቸዋል፡፡ ይህንን እያወቁ ውንጀላውን ማኖራቸው እውነትም እኒህ ሰዎች ወንጀለኞች ናቸው ብለው አምነው ሳይሆን ‹‹ከቻልን አደናግረን እናስቀጣቸዋለን (የማይችሉበት ሁኔታ አይታየኝም)፣ካልቻልን ደግሞ በቀጠሮ ጊዜ እንገዛበታለን፣ ነጻ እስኪወጡም ቢሆን በእስር እናቆያቸዋለን›› የሚል ክፉ ምኞት ነው፡፡
… ሳታመኻኝ ብላኝ!
አህዩት ከታች አያ ጅቦ ከላይ ሆነው ወራጅ ውሀ እየጠጡ ነበር አሉ፡፡ ነገር ያማረው አህዩትን ‹‹አታደፍርሽብኝ›› ሲላት ነገሩ የገባት አህይትም ‹‹ሳታመኸኝ ብላኝ›› አለችው ይባላል፡፡ የኛም ነገር እንደዚያው ነው፡፡
ፖሊስ ሲይዘን እኛ ላይ ይህ ነው የሚባል የመክሰሻ መረጃ አልነበረውም፤ እንዲያውም ከስማችን በቀር የሚያውቁት ነገር አልነበረም፡፡ ሌላው ቀርቶ ከደህንነቶታቸው በአንዱ ልከንላቸው የነበረውን የጽሑፋችንን ስብስብ እንኳን ሳያነቡት ነበር የያዙን፡፡
አሁንም ማስረጃ ብለው ከክስ መዝገባችን ጋር ያያያዙት ቢያንስ በእኔ ግምት ዘጠና በመቶ የሚሆነው ‹‹ሰነድ›› እኛው ነፃ ያወጣናል ብለን የሰጠናቸው ጽሑፎቻችን ናቸው፡፡ በመርማሪዎቻችን ንግግር ውስጥ እኛ ላይ ወንጀል የማግኘት Desperate ፍላጎት አይተናል፡፡ ምናልባትም እንደገመትነው ቢያንስ እስከ 2007ቱ ምርጫ ድረስ ከማኅበራዊ ሚዲያ ገለል እንድንልላቸው ፈልገዋል፡፡ ከዚህ የተሻለም አማራጭ አልታያቸውም ይሆናል፡፡
በእስካሁኑ ሂደት የማዕከላዊን ለገዢው ፓርቲ ወገንተኝነት በዓይናችን አይተን አረጋግጠናል፡፡ ቀጣዩ ደግሞ የፍትሕ ሥርዓቱን በአደባባይ መፈተሽ ይቀረናል፡፡ ለአሁኑ ግን በቅርቡ እንፈታ ይሆን… የሚል ጥያቄ ‹ሕጋዊ› ሳይሆን መላ ምታዊ አማራጮችን እገምታለሁ፡፡
ኢህአዴግ ወይም የኢህአዴግ መንግሥት የሚያዘው ፖሊስ እኛን በቁጥጥር ሥር ሲያውለን ስለወንጀላችን ማረጋገጫ (ጠበቆች Beyond reasonable doubt) እንደሚሉት ዓይነት ባይኖረውም መቼም የሆነች ስህተት ሳላገኝባቸው አልቀርም በሚል ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ወትሮም የተንቦረቀቀ የሚባለው የፀረ-ሸብርተኝነቱ አዋጅ ውስጥ የሚጥለን ነገር በቀላሉ ማግኘት አልቻሉም፡፡ አለመቻላቸው ግን የተነሱበትን እኛን የመክሰስ ዓላማ አላጠፋውም፡፡  የክስ መዝገቡን ሲያዘጋጁ አንድም የረባ ዐረፍተ ነገር ሳይጽፉ ይዘውን ፍርድ ቤት መቅረባቸው በራሱ አንድም የረባ ጥርጣሬና ማረጋገጫ እንደሌላቸው አመላካች ነው፡፡ ቢሆንም በቅርቡ ይለቁናል የሚል ግምት የለኝም፡፡ ለምን;
1ኛ. ኢህአዴግ በጣም የሚናደድባቸው እና ታሳሪውን በሚያዋርድ መልኩ ካልሆነ በቀር ከማያደርጋቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ- አንዴ ያሰረውን ተቺውን ፤ ያውም ብዙ ደጋፊ ያለውን መፍታት ነው፡፡ ኢህአዴግ እንደልጅ እልህ ይጋባል ማለቴ ነው፡፡ (ይህንን ስል የእስራችንን ኢፍትሀዊነት የተመለከቱትን ጩኸቶች መጥላቴ አይደለም፤ ያለ እነርሱ መንፈሳችን አይጠገንም ነበር፡በአደባባይ የምናመሰግንበት ቀን ይመጣል)
2ኛ. መጀመሪያ የተጠራጠሩበት እና ኋላ የዋጧት ጥርጣሬያቸው፤ ማለትም (ምርጫውን ተከትሎ) አመፅ ማስነሳት በሚሉት ጉዳይ ላይ እቅድ እንደሌለን ቢያምኑም እንኳን ምናልባት እምነታቸው ከተሳሳተ Risk መውሰድ አይፈልጉም፡፡ ( መጀመሪያም የቀለም አብዩት ዶክመንተሪ አዝማሚያ ያስታውሷል)
3ኛ. ምንም እንኳን ዓመፅም፤ሽብርም  የማስነሳት ፍላጎትም አቅምም፤  እንደሌለን ቢያምኑም የገዥው ፓርቲ ጠንካራ ተቺዎች መሆናችንን ስለሚያውቁ እና ስላልወደዱልን ፍርድ ቤት በምንመላለስበት ረዘም ያለ ጊዜ ባለው እስር ወቅት ቢያንስ የእስርን ምሬት እንድንቀምሳት ይፈልጋሉ፡፡ ቅጣትን ጨርሶ በነፃ መለቀቅ እንደማለት፡፡
4ኛ. ኢህአዴግ መፍረድ አይፈራም፡፡
Befekadu Hailu

ተከብሮ ያላስከበረ፣ ሰርቶ ያላሰራ ‘ሕገ-መንግስት’

ሕዝባዊ መንግስት ማለት ሕዝቡ በቀጥታ የራሱ የስልጣን ባለቤትነት የተረጋገጠበት ማለታችን ነው:: ህዝቡ መሪዎቹን በነጻ የመምረጥ እና የማዉረድ መብቱ የተረጋገጠበት ማለት ነው:: ሕዝባዊ መንግስት ስንል የመግስት ስልጣን መነሻ እና መድረሻው ህዝቡ ነው ማለታችን ነው::
ህገ መንግስት ደግሞ የህጎች ሁሉ የበላይ ህግ ነው፡፡ አሁን በስራ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ‘ህገ መንግስት’ እንደሚለው ከሆነ ‘ማንኛውም ህግ፣ ልማዳዊ አሰራር እንዲሁም የመንግስት ባለስልጣን አሰራር ከህገ መንግስቱ የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት አይኖረውም።’
ሙሉውን ለማንበብ ይህንን ሊንክ ይጫኑ http://t.co/tM139HuDYt

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በደቡብ ሱዳን የሚካሄደው የርስ በርስ ጦርነት የሚያበቃበትን መንገድ የሚያፈላልገው ተቋርጦ የነበረው የሰላም ድርድር ባለፈው ሰኞ አዲስ አበባ ውስጥ ቢጀምርም፣ በደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር አንፃር የሚፋለሙት

ደራሲ፣ ኤርምያስ ለገሰ ብዛት፣ 406 ገጾች አሳታሚ፣ ነጻነት አሳታሚ ድርጅት እንደ መንደርደርያ በስፋት ሲወራለት የነበረውን ይህን መጽሃፍ ሙኒክ-ጀርመን ላይ ገዝቼ ለማንበብ እያፈላለግኩ ሳለሁ፤ አንድ ወዳጄ ይዞት አየሁ። የደበዘዘ የመለስ ፎቶ ያለበትን ይህንን መጽሃፍ የኦስሎው አበበ እጅ ላይ ነበር። ገና ሰላምታ ሳንለዋወጥ ነበር መጽሃፉን ከእጁ ላይ የነጠቅኩት። ታማኝ በየነም እዚያው አብሮን ስለነበር አስተያየቱን ጣል አደረገ። “መነበብ […]

ወር በተጠጋው የእስራኤል ጋዛን የማጥቃት ዘመቻ በአሳር በመከራ የተደረሰው የ 72 ሰዓቱ የጦርነት ማቆም ሊያልቅ የቀሩት ጥቂት ሰአታት ብቻ ናቸው። በእስራኤል የአየር የየብስና የባህር ድብደባ ከ1800 በላይ አብዛኛው የጋዛ ንጹሃን ፍልስጥኤማውያንን ተገድለዋል። ከ 9000 የማያንሱትን ቆሰለዋል። በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ በሃገራቸው ተሰደው ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። ጋዛ እንዳልነበረች ሆናለች ይህ ሁሉ ሆኖ ጦርነቱ እንዲያቆም በተደረሰው የ 72 ሰአታቱ […]

ሐምሌ 29 ጠዋት ሜክሲኮ ልደታ ፍርድ ቤት ቀርበው በ5000 ብር ዋስ እንዲወጡ የታዘዘላቸው ወይንሸት፣ አዚዛ እና ኡስታዝ በድብቅ በተካሄደ ይግባኝ ዋሱ ተነስቶ የ7 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ለፖሊስ ተፈቅዶለታል፡፡ በእለቱም ከሰዓት በኋላ በድብቅ ፍርድ ቤት ተወስደው የዋስ መብታቸው በይግባኝ ተገፏል፡፡ አሁን በእስር ቤት ይገኛሉ፡፡
እንዲሁም በተያያዘ ዜና ሐምሌ 30 ቀን ኢብራሂም አብዱልሰላም 5000 ብር ደመወዝተኛ ዋስ እንዲለቀቅ ተወስኖ የነበረ ቢሆንም ከ3 ሰዓታት በኋላ ፖሊስ ለይግባኝ ሰሚ ችሎት እንዲቀርብ አድርጎ ዋስትናው እንዲታገድ በማድረግ በእስር ቤት እንዲቆይ ተደርጓል፡፡

ነሃሴ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የመከላከያ ምንጮች እንደገለጹት የሰራዊቱ አባላት ለመለስ ፋውንዴሽን ገንዘብ እንዲያዋጡ በተጠየቁበት ወቅት ተቃውሞ አሰምተዋል። በባድሜ አካባቢ የሰፈሩት የመከላከያ አባላት በደሞዝ ክፍያ ሳምንት መነሻው 200 ብር ሆኖ በየደረጃው ያሉ ወታደሮች እንደ ማእረጋቸውና ደሞዝ መጠናቸው እንዲከፍሉ ሲጠየቁ፣ የሰራዊቱ አባላት ደሞዛችን አይቆረጥም በማለት ተቃውሞ አሰምተዋል። ደሞዝ ከፋዮቹ ከላይ የመጣ መመሪያ ነው በሚል …

ነሃሴ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የብሪታንያ መንግስት የግንቦት7 ዋና ጸሃፊ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጉዳይ ትኩረት ሰጥታ እንደትከታተለው የሚያሳስቡ የተቃውሞ ሰልፎች ካለፈው ወር ጀምሮ በእየሳምንቱ በመካሄድ ላይ ሲሆን፣ ዛሬ አርብም ለአምስተኛ ጊዜ ተካሂዷል። ኢትዮጵያውያኑ ስሜታቸውን በከፍተኛ ቁጣ በመግለጽ ላይ መሆናቸውን ከስፍራው ያነጋገርነው ዘጋቢያችን ወንድማገኝ ጋሹ ገልጿል። በሌላ በኩል ደግሞ የአቶ አንዳርጋቸውን ጉዳይ የሚከታተለው ግብረሃይል በውጭ …

ነሃሴ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በባህርዳር ከተማ ተደርጎ በነበረው ስብሰባ ላይ  የምክር ቤት አባላት ፣” የህዝብ ወኪሎች ብንሆንም ስራ አስፈጻሚው አካል የምናቀርበውን ሪፖርት አይቀበልም” ብለዋል። አንድ ኢንቨስተር ከአንድ የህዝብ ተመራጭ የተሻለ ተሰሚነት አለው ያሉት ተማራጮች መፍትሄ ለማምጣት ካልቻልን የእኛ ተመራጭነት ምንድነው ሲሉ የምክር ቤት አባላት ጥያቄ አቅርበዋል የህዝብ ተወካዮቹ እንደገለጹት በአሁኑ ጊዜ በፍድር ቤቶች …

ነሃሴ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኒው ቪዥን እንደዘገበው አበበ መኮንንና አስፋው ወንዶሰን ከመኖሪያ ቤታቸው በፖሊሶች ተይዘው ተወስደዋል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹንለመያዝ ለሁለት ቀናት አሰሳ ሲያካሂድ እንደነበር ተዘግባል። ኢትዮጵያውያኑ ለኢህአዴግ የደህንነት ሃይሎች ተላልፈው ይሰጡ ወይም ጉዳያቸው በዩጋንዳ ፍርድ ቤት ይታይ በዘገባው አልተጠቀሰም። ፖሊስ እስረኞቹ የታሰሩበትን ቦታም ለመግለጽ ፈቃደኛ አልሆነም።

ነሃሴ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ላለፉት ሶስት ቀናት ጋብ ብሎ የነበረው የእስራኤልና የፍልስጤማውያን ግጭት እንደገና ማገርሸቱን እስራኤል አስታውቃለች። በግብጽ አደራዳሪነት ሲካሄድ የነበረው የሰላም ድርድር ሃማስ ሮኬቶችን ወደ እስራኤል ማስወንጨፉን ተከትሎ እስራኤል የአየር ድብደባ ጀምራለች። ሃማስ የሰላም ድርድሩ እስራኤል በጋዛ ላይ ያደረገቸውን ከበባ ማስቆም አለበት የሚል አቋም ይዟል፡፤ እስረኤል በግብጽ በመካሄድ ላይ ያለውን የሰላም ድርድር …

(አለቃ አያሌው ታምሩ) በኢትዮጵያ እመቤታችንን መውደድ በልማድ እንደ ተረት በማይታይ ዓይነት ኹኔታ ተስፋፍቶ የኖረ አይደለም፡፡ ወንድም ሴትም ቢኾኑ እንዳላቸው የእምነት መጠን በእመቤታችን ስም ጸሎት ጸልየው፣ ስእለት ተስለው፣ ምጽዋት አድርገው፣ ዝክርዋን ዘክረው፣ ስምዋን ጠርተው፣ በአማላጅነትዋ ተማፅነው ዐሳባቸው እየተፈጸመላቸው፣ የጎደለው እየሞላላቸው፣ የጠመመው እየተቃናላቸው፣ ድውያን ፈውስ በማግኘት፣ ሠራተኞች ለሥራቸው የተቃና መንገድ በማግኘት፣ መምህራን በሚያስተምሩበት፣ ቅዱሳን ገድላቸውን በሚፈጽሙበት ጊዜና …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ በዴሞክራሲ ግንባታ‘ በሚል ርዕስበተካሄደ ውይይት ላይ የተካፈሉ ተሳታፊዎች ሴቶች መብታቸውን ለማስከበርም ሆነ በአገራቸው ተጠቃሚ ለመሆን በየመስኩ ተሳትፎአቸውን ማጎልበት እንደሚገባቸው ተናግረዋል ።

በዚህ ሳምንት ሰኞ አዲስ አበባ ውስጥ የተጀመረው የሰላም ንግግር የተቋረጠው ተቃዋሚው SPLM A አንዳንድ ተወካዮች በንግግሩ ላይ መሳተፋቸውን በመቃወሙ መሆኑን የድርድሩ ተካፋይ የሆኑት የሴቶች ተወካይ ለዶቼቬለ ተናግረዋል ።