ሦስት አሣታሚ ድርጅቶችንና ሥራ አስኪያጆቻቸውን ሕዝብን ለአመፅ በማነሣሣትና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስ በሚደረጉ ወንጀሎች ፌደራል አቃቤ ህግ ከሰሳቸው።

የ“ፋክት” መፅሄት አሣታሚ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ በፖሊስ ተይዘው እንዲቀርቡ ታዝዟል።

ለዝርዝሩ የፍርድ ቤቱን ውሎ የተከታተለውን የመለስካቸው አምሃን ዘገባ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በተለያዩ የሊቢያ ከተሞች የሚካሄደው ውጊያ በቀጠለበት በአሁኑ ጊዜ በሃገሪቱ የሚገኙ ስደተኞችና የውጭ ዜጎች የሰቀቀን ህይወት በመግፋት ላይ ይገኛሉ ። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ከሚገኙት መካከል ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ይገኙበታል ።

በኢትዮጵያ ረጅም እድሜ ያስቆጠረው የቴአትር ጥበብ ዛሬም በአዲስ አበባ መድረኮች የተወሰነ ነው። ሙያውን የሚያስተምሩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መበራከት ቢታይም ወጣት ተመራቂዎች ግን በሥራ ለመሠማራት እድሉን ማግኘት ከባድ ነው ሲሉ ይደመጣሉ።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ፋክልቲ 38 የጽዳት ሠራተኞችን አሰናበተ። ካላንዳች ማስጠንቀቂያ እና ምክንያት ከሥራ መባረራቸውን ለዶይቸ ቬለ ያስታወቁት ሴቶች በዚህ ምክንያት ትልቅ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ገልጸዋል።

በተለያዩ ሀገራት የሚካሄዱ ውዝግቦችን እየተከታተለ የመፍትሔ ሀሳብ የሚጠቁመው «ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ» ሰሞኑን ስለኤርትራ አንድ ዘገባ አውጥቷል። የ«ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ» ዘገባ በተለይ ትኩረቱን

ፀሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ

——–

ኢራቅ በሳዳም ሁሴን አገዛዝ ስር በነበረችበት ዘመን ከሞላ ጎደል ሰላምና መረጋጋት ነበራት፡፡ ሀገራዊ አንድነቷም የተጠበቀ ነው፡፡ አሜሪካ አንድም ማስረጃ ባልነበረው ወሬ ተነሳስታ በ2003 (እ.ኤ.አ) ሀገሪቷን ከወረረቻት በኋላ ግን አንድነቷም ሆነ ሰላሟ ተናግቷል፡፡ በኤፍራጥስና ጤግሮስ ወንዞች ላይ የከተመችው ውቢቷ ባግዳድም በየዕለቱ የቦንብና የፈንጂ ፍንዳታ ማስተናገድ ምሷ ሆኗል፡፡ 

    ከዚህ ባሻገር ሀገሪቷ ክቡር የሆነውን የእስልምና አስተምህሮ እንዳሻቸው እየተረጎሙ ስውር አጀንዳዎቻቸውን ለማስፈጸም የሚተጉ ጽንፈኛ ግለሰቦችና ቡድኖች መፈልፈያ ሆናለች፡፡ አቡ ሙስዓብ አል-ዘርቃዊን የመሳሰሉ ጽንፈኞች ኢራቅን የእቶን እሳት መቀጣጠያ ሲያደርጓት እንደከረሙ ተመልክተናል፡፡ በዘንድሮው ዓመት ደግሞ ድሮ ከምንሰማቸው እጅግ የከፋ ጽንፈኛ ቡድን በዚያው ምድር ላይ እጆቹን ሲዘረጋ ለመታዘብ በቅተናል፡፡

  ራሱን “የኢራቅና የሻም ኢስላማዊ መንግሥት” እያለ የሚጠራው (ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “ኢስላማዊ መንግሥት” በሚለው አጭር ስያሜ ብቻ የሚጠራው) ቡድን ከየት ተገኘ?.. እንዴት ተመሰረተ?… መስራቾቹስ እነማን ናቸው?… ከጀርባ የሚገፉትስ እነ ማን ናቸው?…. የመጨረሻ ዓላማው ምንድነው?…. እነዚህን ጥያቄዎች ለመመለስ የነጠረ መረጃ ሊኖረን ይገባል፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ግን ብዙዎቹን ጥያቄዎች ለመመለስ አይቻልም፡፡ ስለዚህ ጥያቄዎቹን ጊዜ ይመልሳቸው ማለቱ ይሻላል፡፡ ቡድኑ ለሚተግብራቸው የጽንፈኝነት አድራጎት እስልምናን እንደ ማስረጃ እየጠቀሰ ማነብነቡ ግን በጣም ያሳምመናል፡፡

   በዘመናችን የሚታዩትና በእስልምና ስም የሚነግዱ ጽንፈኞች በሙሉ “ጂሃድ እያደረግን ነው” እያሉ ነው የሚፎክሩት፡፡ ለብዙ ክፍለ ዘመናት በሙስሊሞች መሀል በሰላም ሲኖሩ የነበሩ ማህበረሰቦች ሀይማኖታቸውን እንዲቀይሩ ማስገደድም ጀምረዋል፡፡ “ጂሃዳቸው” ግብ መትቶ ሀገር ከተቆጣጠሩ በኋላ የሚመሰርቱት “ኋላቀር” መንግሥት ምን ዓይነት እንደሆነም ምልክቱን እያየን ነው፡፡ በርግጥ በእስልምና እይታ እንዲህ ዐይነቱ ጽንፈኝነት “ጂሃድ” ማድረግ ነው ተብሎ ሊጠራ ይችላልን?… እስልምናስ “ኋላቀርነትን” የሚናፍቅ እምነት ነውን?… በነዚህ ነጥቦች ዙሪያ አንዳንድ ነገሮችን ለመናገር አስቤ ነው ይህንን መጣጥፍ የጻፍኩት፡፡


==“ጂሃድ” እና ጽንፈኞች=


  ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በህይወት ዘመናቸው ከብዙ ባላንጣዎቻቸው ጋር ተጋድለዋል፤ ተዋግተዋል፡፡ ይሁንና እሳቸውም ሆኑ ተከታዮቻቸው ከባላንጣዎቻቸው ጋር የተጋደሉት ሰዎች እስልምናን በጉልበት እንዲቀበሉ ለመጫን በሚል አይደለም፤ እነዚያ ባላንጣዎቻቸው ሊያጠፏቸው ስለተነሱባቸው ነው ራሳቸውን ለመከላከል የተዋጉት፡፡ ጠላቶቻቸው ከመካ ከተማ ጀምሮ ሊያጠፏቸው ሲዶልቱ፣ ሴራ ሲሸርቡና ቅጥረኞችን ሲልኩባቸው ነበር፡፡ ይባስ ብሎም “ሀይማኖታችንን አርክሶ አዲስ እምነት የጀመረው ሙሐመድ ተላልፎ ካልተሰጠን በስተቀር ከማንም ጋር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙት እንዲያደርግ አይፈቀድለትም” ተብሎ ለሁለት ዓመታት ያህል ነብዩ በተገኙበት የበኒ ሐሺም ቤተሰብ ላይ ማዕቀብ ተጥሏል፡፡ የነቢዩ ቤተሰብም “ሙሐመድን አሳልፈን አንሰጥም” በማለት እቀባው እስኪነሳለት ድረስ ከመካ ከተማ ተሰዶ ለመኖር ተገዷል፡፡ በርሳቸው ተከታዮች ላይ የደረሰው ሰቆቃና ችግር ደግሞ በቀላሉ አይነገርም፡፡ በተለይ ደካሞችና ተከላካይ ያልነበራቸው እንደ አማር ቢን ያሲር እና ወላጆቹ፣ ኢትዮጵያዊው “ቢላል”፣ ወዘተ… የመሳሰሉት የሰቆቃና የስቃይ መሞከሪያ ሆነው ነበር ለማለት ይቻላል፡፡ ይህ ስቃይ ሲባባስ ነው ነብዩ ግማሾቹን ተከታዮቻቸውን በስውር ወደ ኢትዮጵያ የሰደዱት፡፡ በመጨረሻም ነቢዩና ተከታዮቻቸው በሙሉ ከመካ ወደ መዲና ለመሰደድ የበቁት ከቁሬይሽ መኳንንቶች ከሚመጣባቸው ጥቃትና በደል ለመሸሽ ሲሉ ነው፡፡

  የነቢዩ ጠላቶች ግን እዚያም አላረፉላቸውም፡፡ “ሙሐመድ ሀይል ገንብቶ እኛን ከማጥፋቱ በፊት እዚያ ሄደን ልናጥፋው ይገባናል” በማለት የክተት አዋጅ አውጀው እስከ መዲና ድረስ ሄዱላቸው፡፡ በዚህን ጊዜ ነው አላህ በቅዱስ ቁርኣን “ለነዚያ በእምነታቸው ምክንያት አላግባብ ለተፈተኑት ሙስሊሞች መዋጋት ተፈቀደላቸው” በማለት ጠላቶቻቸውን በጦርነት እንዲዋጉዋቸው መንገዱን ያሳያቸው፡፡ “ጂሃድ” (ተጋድሎ) የተሰኘው ጽንሰ-ሐሳብም ያኔ ነው የተፈጠረው፡፡

  “ጂሃድ” ቃሉ ራሱ እንደሚያመለክተው “ትግል” ወይንም “ተጋድሎ” ማለት ነው፡፡ ሐቀኛ ሰው ሐቁን ላለማስደፈር የሚያደርገው ትግል ነው በዚህ ስም የሚጠራው፡፡ አንድን ውጥን ከግብ ለማድረስ የሚደረግ ርብርብም “ጂሃድ” ሊባል ይችላል፡፡ ሀጢአተኛ ሰው ነፍሱን ከሐጢአት ለማጽዳት የሚያደርገው ትግልም ጂሀድ ነው፡፡ ነገር ግን አንዳንዶች አላግባብ “ቅዱስ ጦርነት” እያሉ ይፈቱታል፡፡ ፍቺውን ሲያሰፉትም “እስልምናን ለማስፋፋትና በሸሪዓ የሚተዳደር መንግሥት ለመመስረት የሚደረግ ጦርነት ነው” ይላሉ፡፡ ስህተት ነው፡፡ በጣም ስህተት! ጦርነት በባህሪው አውዳሚ ነው፡፡ የትኛውም ጦርነት “ቅዱስ” ሊባል አይችልም፡፡ የትኛውም ሀይማኖት ጦርነትን “ቅዱስ ነው” ብሎ አይባርክም፡፡ ነቢዩ ሙሐመድም ጦርነትን፣ ሁከትና ብጥብጥን አውግዘዋቸዋል፡፡

  ይሁንና አንተ የማታውቀው ጠላትህ አንተን አጥፍቶ ሀገርህን ሊወርስብህ ሲመጣብ ቆመህ አትጠብቀውም፤ የራስህን ሀይማኖት ትተህ የርሱን እምነት እንድትከተል ሲወጋህም በዝምታ አትመለከተውም፡፡ ያኔ በምትችለው መንገድ ሁሉ ትዋጋዋለህ፤ ቢቻል በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲመለስ ታደርገዋለህ፤ እምቢዮው ካለ ግን በሚገባው የጦርነት ቋንቋ ታናግረዋለህ፡፡ “ጂሃድ” የሚባለውም እንዲህ ዐይነቱ ፍትሐዊ ትግል ነው፡፡

    ለሀገርህ፣ ለህዝብህና ለሀይማኖትህ የምታደርገው ተጋድሎ በሰላማዊ መንገድ ካልተቋጨ ብቻ ነው የጦርነትን አማራጭ የምትከተለው፡፡ ታዲያ ጦርነቱን የምታከናውነው እንዲሁ በዘፈቀደ አይደለም፡፡ ለ“ጂሃድ” ስትሰለፍ በማንኛውም መልኩ ገደቡን አታልፍም፤ አንተን በቀጥታ ከሚወጉት ውጪ ሌሎችን አታጠቃም፤ በጦርነቱ ውስጥ የሌለውን ሰላማዊ ህዝብ አትነካም፡፡ በተለይም በጦርነት እሳት ቀዳሚ ተጠቂ በሆኑት ህጻናት፤ ሴቶችና አረጋዊያን ላይ በጭራሽ እጅህን አታነሳም፤ በማሳ ላይ ያለ አዝመራ፣ በበረት ውስጥ ያሉ ከብቶች፣ ህዝብ የሚጠቀምበት የጉድጓድ ውሃ፣ መስጊድ፣ ቤተክርስቲያን፣ ምኩራብ (የአይሁድ ቤተ-ጸሎት) ወዘተ… አታጠቃም፡፡ እነዚህን እያጠፋህ “ጂሃድ እያካሄድኩ ነው” ብትል በእስልምና ሚዛን አንድም ተቀባይነት አታገኝም፡፡

*****

ለ“ጂሀድ” የወጣ ጦር ከውጊያ ሜዳው ከደረሰ በኋላ እንኳ ውዝግቡ በሰላም እንዲያልቅ የሚቻለውን ጥረት ያደርጋል፡፡ የሰላሙ ጥረት መፍትሔ ካላገኘ ብቻ ነው ወደ ውጊያ የሚገባው፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በህይወት ዘመናቸው 27 ዘመቻዎችን አድርገዋል፡፡ ከነዚህ ዘመቻዎች መካከል ውጊያ የተደረገው በስምንቱ ብቻ ነው፡፡ አስራ ዘጠኙ ዘመቻዎች ያለ አንዳች ጦርነት ነው የተጠናቀቁት፡፡

  ከዚህ ሌላም ሁኔታዎች አስገደድውት በጦርነት ውስጥ የገባ “ሙጃሂድ” (ታጋይ) ጦርነቱ እንዳይራዘም እና አውዳሚ ባልሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ ዘዴዎችን መጠቀም ይኖርበታል፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) በመዲና ዙሪያ ምሽግ በመቆፈር በአምስት እጥፍ የሚበልጣቸው የአህዛብ ሰራዊት በፍርሐት ተርበድብዶ እንዲመለስ አድርገውታል፡፡ እንዲሁም ደግሞ በስምንተኛው ዓመተ-ሂጅራ የመካ ከተማን በአነስተኛ ውጊያ (13 ሰው ብቻ የሞተበት) ለመቆጣጠር የቻሉት ሰራዊታቸውን በአራት አቅጣጫዎች በማሰማራት ከተማዋን ለመክበብ በመቻላቸው ነው፡፡ በዚህም በመካ ከተማ ላይ አንድም ውድመት እንዳይሰከት ለማድረግ ችለዋል፡፡

     በጂሃድ ውስጥ ሌላው ውግዝ ተግባር ደግሞ ጦርነትን በጠቅላላ ድምሰሳ (total destrcuction) ስልት ለማሸነፍ መሞከር ነው፡፡ የጠላትን ሀይል በሚቻለው ዘዴ ሁሉ ለማንበርከክ እስከ መጨረሻው ድረስ መታገል ይቻላል፡፡ ይህ ዘዴ ግን ከተዋጊው ውጪ በጦርነቱ ውስጥ ባልተሳተፈው ሲቪል ህዝብ ላይ አደጋ የሚያደርስ መሆን የለበትም፡፡ አንድን ከተማ መቆጣጠር ሲያቅትህ በጅምላ ጥቃት ከተማዋን ማውደም በጭራሽ ከ“ጂሃድ” አይቆጠርም፡፡

  ለምሳሌ ነቢዩ ሙሐመድና ተከታዮቻቸው “ሐዋዚን” ከሚባለው የዐረብ ጎሳ ተዋጊዎች ጋር ውጊያ ገጥመው አሸንፈውታል፡፡ በጦርነቱ የተሸነፉት የሀዋዚን ተዋጊዎች “ጧኢፍ” በምትባለው ከተማ መሸጉ፡፡ ነቢዩ ጣኢፍን ለበርካታ ቀናት ከበቡ፤ የሀዋዚን ተዋጊዎችም እጃቸውን እንዲሰጡ ጠየቁ፡፡ ባላንጣዎቻቸው ግን አምቢኝ አሉ (ጣኢፍ በዘመኑ ሉአላዊነት ያላት የከተማ መንግሥት ነበረች)፡፡ ይባስ ብሎም በከተማዋ ግንቦች ጫፍ ላይ ሆነው በነቢዩና በተከታዮቻቸው ላይ ልዩ ልዩ የባለጌ ስድቦችን ያወርዱ ጀመር፡፡ ይሁንና ነቢዩ በምላሹ ተናድደው የጧኢፍ ከተማዋን አላወደሟትም፡፡ የሀዋዚን ተዋጊዎችን እንቅስቃሴ በዐይነ ቁራኛ የሚጠብቅ ጦር በከተማ አቅራቢያ መድበው ለራሳቸው በክብር ወደ መዲና ተመለሱ፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ እዚያ የመደቡትን ጦር አስነሱ፡፡ ከዓመት በኋላ በጦርነት ያልተቻሉት የሀዋዚን ተዋጊዎች በራሳቸው ፈቃድ እጅ ሰጡ፡፡ ሁሉም በፍላጎታቸው እስልምናን ተቀበሉ፡፡

   ይህ የነቢዩ አድራጎት ያስገርማል፡፡ “ጧኢፍ” ነቢዩ በመልዕክተኛነት ከተላኩ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ስደትን የሞከሩባት ከተማ ናት፡፡ ነቢዩና ጥቂት ተከታዮቻቸው ወደ ከተማዋ ደርሰው ነዋሪቿ እስልምናን እንዲቀበሉ ጠየቋቸው፤ በከተማዋ ለመኖር እንዲፈቀድላቸውም ለመኑ፡፡ የጧኢፍ ነዋሪዎች ግን ነቢዩን የድንጋይ ውርጅብኝ አከናነቧቸው፤ ጧኢፍ ውስጥ የነበሩ ህጻናትና ታዳጊዎች ተሰባስበው ያንን አሰቃቂ ትርኢት በጩኸትና በዘፈን አዳመቁት፡፡ የትኛውም ከተማ ነቢዩን በእንደዚያ ዓይነቱ ወራዳ ምግባር አላስተናገደም (በመካ ከተማ ካዩት ስቃይና ሰቆቃ በስተቀር)፡፡ ከአስር ዓመታት በኋላ ያቺ ከተማ በነቢዩና በተከታዮቻቸው ተከበበች፡፡ በከተማዋ የመሸጉት የሀዋዚን ተዋጊዎች አስነዋሪ ስድቦችን እየተሳደቡ ተፈታተኗቸው፡፡ ይሁንና ነቢዩ የጥንቱን የድንጋይ ወገራ ትዝታቸውን ከሀዋዚን ጦረኞች ስድብ ጋር በመደመር ከተማዋን አላጠፏትም፡፡ በራሷ ጊዜ ከእጃቸው እንደምትገባ በመተማመን ወደ መናገሻ ከተማቸው ተመለሱ፡፡ በዚያ ዘመን የነበረ ሌላ መሪ እንዲህ ሲያደርግ አልታየም፡፡ አንድ ከተማ እጅ አልሰጥም ካለች ከተማዋን ማውደም ነው እንጂ ጦሩን ይዞ ወደ ኋላ መመለስ በዚያ ዘመን አይታወቅም፡፡ ሰውዬው ግን ነቢይ ነውና  ለ“ጠቅላላ ድምሰሳ” (total destrcuction) አልቸኮለም፡፡  የኢራቅ ጽንፈኛ ሚሊሻስ?…. አሜሪካስ?…. እስራኤልስ?.. አል-ሸባብስ?… ሂትለርስ?… ሁሉም በጠቅላላ ድምሰሳ (total destrcuction) ስልት ያምናሉ፡፡

*****

“ጀሃድ” በትንኮሳ የሚፈጸምም አይደለም፡፡ ሌሎች ሳይደርሱብህ የሰው ሀገርና ድንበር ወርረህ “ለእስልምና ነው የምዋጋው” ማለት የለም፡፡ በቅዱስ ቁርኣን በተጻፈውም ሆነ ነቢዩ በአንደበታቸው ባስተማሩት መልዕክት ውስጥ “እንዲሁ ከመሬት ተነስህ ሌሎችን ተዋጋ” የሚል ነገር አናነብም፡፡ እያንዳንዱ እርምጃህ የመነሻ ምክንያት ሊኖረው ግድ ይላል፡፡ ነቢዩ ያካሄዷቸው ዘመቻዎች በሙሉ በቂ ምክንያቶች ነበሯቸው፡፡ ጠላቶቻቸው ከተነኮሷቸው በኋላ ነው ነቢዩ ለጂሃድ የወጡት (ሰ.ዐ.ወ)፡፡ በኋለኞቹ ሁለት ዓመታት ውስጥ የተደረጉት ዘመቻዎች ደግሞ ነቢዩ ዐረቢያ ማዕከላዊ መንግሥት መሪነታቸው የሀገሩን ጸጥታና ዳር ድንበር ለማስከበር ያካሄዷቸው ናቸው እንጂ ውጊያ በመሻት የተደረጉ አልነበሩም፡፡

      ከነቢዩ ህልፈት በኋላ የነቢዩ ተከታዮች ከፋርስና ከሮማዊያን ጋር ያኳሄዷቸው ጦርነቶች ብዙ መነሻዎች ነበሯቸው፡፡ ከጀርባቸው የነበረው ዋነኛ ምክንያት ግን አንድና አንድ ብቻ ነው፡፡ ይህም ሮማዊያንና ፋርሶች ከዐረቢያ የተነሳውን አዲስ ሀይል በቅኝ ግዛቶቻቸው ላይ የተጋረጠ አደጋ አድርገው መውሰዳቸው ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ሁለቱም ሀይሎች የነቢዩን መንግሥት በስውርና በግልጽ ውጊያ ሊያጠፉት ሞክረዋል፡፡ ይሁንና አዲሱ ሀይል የሚበገርላቸው አልሆነም፡፡ ሮማዊያንንና ፋርሶችን በከፍተኛ ወኔ እየተዋጋቸው ከያዟቸው የእስያ፣ የመካከለኛው ምስራቅና የሰሜን አፍሪቃ (ስፔንን ጨምሮ) ቅኝ ግዛቶች በሙሉ አባሮአቸል፡፡ ከነዚህ ቄሳራዊ ቅኝ ገዥዎች የነጠቃቸውን ግዛቶች በአዲስ የኸሊፋ መንግሥት ስር አጠቃሎአቸዋል፡፡ የሮም መንግሥት በደንበኛው መሬቱ (hinterland) ላይ ከተገደበ በኋላ ከሙስሊሞች ጋር በጉርብትና የመኖር ፖለሲን ስለተከተለ ከርሱ ጋር የሚደረገው ጦርነት ቆሟል፡፡ የፋርሶች መንግሥት ግን በጄ አላለም፡፡ በሙስሊሞች ላይ ትንኮሳ መፈጸሙንና ከተሞችን ማውደሙን ስለቀጠለ ውድቀቱን በራሱ እጅ አፋጥኗል፡፡

*****

የጅሃድ እስላማዊ ግንዛቤ ይህ ነው፡፡ በትክክል ጂሃድ ማድረግ ማለት እንዲህ ነው፡፡ አላህ ታጋዮችን ሊረዳቸው ቃል የገባው ይህንን መርህ ተከትለው የታገሉ እንደሆነ ነው፡፡ ነቢዩንና ተከታዮቻቸውን “አንድ ከልቡ የሚታገል ሙጃሂድ ለአስር ጠላቱ ይበቃል” በማለት ያወደሳቸው በዚህ መመሪያ መሰረት ይታገሉ ስለነበር ነው፡፡ ጥቂቶች ሆነው በብዙ እጥፍ የሚበልጧቸውን የሮምና የፋርስ የጦር ሀይሎችን ለማሸነፍ የበቁት ሐቁን ይዘው በወኔና በቆራጥነት ስለተዋጓቸው ነው፡፡

  የዘመናችን ጽንፈኛ ሀይላት ከዚህ መርህ ጋር በጭራሽ የሚተዋወቁ አይደሉም፡፡ ለጂሃድ የጨፈገገ ትርጓሜ እየሰጡት በአሉታዊ መልኩ እንዲታይ አድርገውታል፡፡ ቅዱስ ቁርአንንና የነቢዩን ሐዲሶች እንዳሻቸው እየተረጎሙ የድብቅ ፍላጎታቸው ማስፈጸሚያ ያደርጉአቸዋል፡፡ በሴፕቴምበር 11/2001 እንደታየው አውሮፕላኖችን እየጠለፉ በሺህ የሚቆጠሩ ንጹሐንን ይፈጃሉ፡፡ በህዝብ ማጓጓዣ ባቡሮችና አውቶቡሶች ላይ ቦንብ ያጠምዳሉ፡፡ የመኖሪያ ህንጻዎችን በፈንጂ ያጋያሉ፡፡ እንደ ሶማሊያው አል-ሸባብ የአንድ አባት ልጆችን ያጋድላሉ፡፡ እንደ ቦኮ-ሀራም በምንም ውስጥ የሌሉ ሴቶችን እየጠለፉ መደራደሪያ ያደርጉአቸዋል፡፡ አልፎ ተርፎም የነርሱን ድርጊት የማይደግፈውን “ሙስሊም አይደለህም” እያሉ ይረሽኑታል፡፡ ይህ ነው እንግዲህ ጽንፈኝነት ማለት!

  ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ዓይነት ጽንፈኛ ቡድኖች ወደፊት እንደሚነሱ ተንብየዋል፡፡ የጽንፈኝነቱ የመጀመሪያው ምልክትም በኸሊፋ ዑመር (ረ.ዐ) ዘመን ታይቷል፡፡ ከዚያም የዑስማን መንግሥት በነዚህ ጽንፈኞች ታውኳል፤ ኸሊፋ ዑስማንም በነርሱ እጅ ተገድለዋል፡፡ በኸሊፋ ዓሊ ዘመን ደግሞ ጽንፈኞቹ ለይቶላቸው ከኸሊፋቸው ጋር በግልጽ ተዋግተዋል፤ ከኸሊፋው ጋር የቆሙትንም “ከእስልምና የወጡ ካፊሮች” በማለት ፈርጀዋቸዋል፡፡ በመጨረሻም የዓሊ ህይወት በነርሱ እጅ ጠፍቷል፡፡

   በዚህ ዘመን የተነሱት ጽንፈኞችም የነዚያዎቹ ተከታዮች ናቸው፡፡ ነገር ግን ክርር ያለው አካሄዳቸው ለየትኛውም ሰው ስለማይመች ተቀባይነት አያገኙም፡፡ በተጨማሪም ከክር የቀጠነው ጽንፈኝነታቸው አንድነታቸውን ጠብቀው እንዲሄዱ አያስችላቸውም፡፡ በታሪክ እንደታየው እንዲህ ዓይነት ቡድኖች በጥቂት ዓመታት ውስጥ በብዙ ቡድኖች ተፈረካክሰው እርስ በረስ መባላት ይጀምራሉ፡፡ በዓሊ ዘመን የተነሱት የ“ኸዋሪጃ” ጽንፈኞች ተፈረካክሰው እንደጠፉት ሁሉ በሌሎች ዘመናት የተነሱ ጽንፈኞችም ራሳቸውን በራሳቸው ያጠፋሉ፡፡ የአሁኖቹም መንገዳቸው ይኸው ነው፡፡


===ጽንፈኞችና ሽብር===


ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ለጂሃድ የወጣ ሰው የሚዋጋው መሳሪያ ታጥቆ ለውጊያ ከተሰለፈ ሀይል ጋር ነው፡፡ በውጊያው ውስጥ ባልተሰለፉ ሲቪል ዜጎች ላይ ጥቃት ማድረስ በፍጹም አይፈቀድለትም፡፡ የዘመናችን ጽንፈኞች ግን ከዚህ መርህ ጋር የሚተዋወቁ አልሆኑም፡፡ ዓላማቸውን ለማሳካት የሚጠቀሙበት ዋነኛ ዘዴ ሽብር ፈጠራ ነው፡፡ ጽንፈኞቹ በሚያደርሱት ጥቃት የሚሸበሩትም ሆኑ የሚሞቱት በአብዛኛው ሲቪሎች ናቸው፡፡ ንጹሐንን እየቀጠፉ ነው “ለእስልምና ነው የምንታገለው” የሚሉት፡፡

እስልምና ግን እንዲህ የዘቀጠ ርዕዮት አይደለም፡፡ ኢስላም የሰው ልጅ ከየትኛውም ፍጥረት በላይ የተከበረ መሆኑን ነው የሚያስተምረው፡፡ ቅዱስ ቁርኣን “አንዲት ነፍስን ያለ ሐቅ ያጠፋ ሰው በምድር ላይ የሚኖሩ ሰዎችን በሙሉ እንደገደለ ይቆጠራል” ይላል፡፡ ጽንፈኞች በምን ማስረጃ ነው ይህንን ቁርኣናዊ ህግ የሚሞግቱት?… “ለአሜሪካ መንግሥት ታክስ የሚከፍል ሁሉ የእስልምና ጠላት ነው” የሚል ሎጂክ በጭራሽ ኢስላማዊ መሰረት የለውም፡፡ ኢስላም በግልጽ በተደነገገ ህግ ነው የሚተገበረው፡፡ እንደ ኒኮሎ ማኪያቬሊ “ወደ እውነት ለመድረስ በብዙ ውሸቶች ውስጥ መዘፈቅ” ወይንም “ዜጎችን እየጨረሱ ወደ ውጤት መድረስ” የሚል መመሪያ በእስልምና ውስጥ የለም፡፡ ሽብር ምን ጊዜም ቢሆን ሽብር ነው፡፡


==ጽንፈኞችና ብዝሐነት==


የጽንፈኛውን የኢራቅ ሚሊሻ መነሳትን ተከትሎ የዓለም ሚዲያዎችን የተቆጣጠረው ሌላኛው ርዕስ “ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች በግዴታ እስልምናን እንዲቀበሉ ተደርገዋል” የሚል ነው፡፡ ጽንፈኞች ለዚህኛው አድራጎታቸውም “እስልምና እንደዚያ እንድናደርግ አዟል” ይሉናል፡፡ ለመሆኑ ቅዱስ ቁርኣን “ሌሎችን በግዴታ እንዲሰልሙ አድርጉ” ይላል? በፍጹም! ቅዱስ ቁርኣን እንዲህ ነው የሚለው፡፡


لَاۤ اِکۡرَاہَ فِی الدِّیۡنِ ۟ۙ قَدۡ تَّبَیَّنَ الرُّشۡدُ مِنَ الۡغَیِّ


“በሀይማኖት ማስገደድ የለም፤ ቀጥተኛው ጎዳና ቀጥተኛ ካልሆነው በርግጥ ተብራርቷል”

(አል-በቀራህ-266)

ነብዩ እና ተከታዮቻቸው በዘመናቸው የነበሩ የበርካታ እምነት ተከታዮች እምነታቸውን እንዲቀይሩ ያላስገደዱት በዚሁ ቁርአናዊ መመሪያ ስለሚመሩ ነው፡፡ ክርስቲያኖች፣ አይሁዶች፣ ዞራስትሪያኖች (መጁስ)፣ ሳቢኢን (የጥንታዊ የሜሶጶጣሚያ እምነት ተከታዮች)፣ ቂብጢዎች (የጥንታዊ የግብጽ እምነት ተከታዮች)፣ የዚዲዎችና ሌሎችም ከሙስሊሞች ጋር በሰላም ይኖሩ ነበር፡፡ አሁን እንደምንሰማው ቤተክርስቲያንና ምኵራብ ማፍረስም ሆነ ቄስና ካህን መግደል በዚያ ዘመን በጭራሽ አልነበረም፡፡ ጽንፈኞች የሚነዙት ወሬ ከየትኛውም እስላማዊ መመሪያ ጋር አይጣጣምም፡፡

   በዚያ ዘመን ነቢዩና ተከታዮቻቸው በግልጽ የተዋጉት ከአይሁዶች ጋር ነው፡፡ ይህም በሀይማኖታቸው ምክንያት አይደለም፡፡ አይሁዶቹ የመዲና ከተማን ደንብ አክብረው ለመኖር የገቡትን ቃል-ኪዳን አፍርሰው ከነቢዩ ጠላቶች ጋር በመወገን ስለተዋጓቸው ነው፡፡ በዚህም  የተነሳ አይሁዶቹ ለጥፋታቸው ተመጣጣኝ ቅጣት ከፍለው በከተማዋ እንዲኖሩ፤ አሊያም ከተማዋን ለቀው እንዲሄዱ ምርጫ ተሰጣቸው፡፡ ጥቂቶች ቅጣቱን ለመክፈል ተስማማሙ፡፡ አብዛኞቹ ግን ከተማዋን ለቀው ወደ ተቡክ (አሁን ሳዑዲና ዮርዳኖስ ድንበር) ተሰደዱ፡፡

  ነብዩ በሀይማኖት የተነሳ ከክርስቲያኖች ጋር የተጋጩበት የታሪክ አጋጣሚ የለም፡፡ በዑመር (ረ.ዐ) ዘመን ደግሞ አስገራሚ ድርጊት ተፈጽሟል፡፡ በወቅቱ ሙስሊሞቹ ከሮማዊያን ጋር በፍልስጥኤም ምድር እየተዋጉ ነበር፡፡ ሙስሊሞቹ አሸንፈው ከተማዋን በያዙበት ቀን ዑመር ሳይጠበቁ ወደ ከተማዋ መጡ፡፡ እኚህ መሪ የትልቅ ግዛት ገዥ ሆነው በመናኛ አለባበስ፣ ያለ አንዳች አጃቢ ወደ ከተማዋ በመግባታቸው ብዙዎች ተደነቁ፡፡ ከሁሉም በላይ በድርጊቱ የተደነቁት ግን የእየሩሳሌም ፓትሪያርክ ነበሩ፡፡ ፓትሪያርኩ “ የሙስሊሞቹ መሪ ይህ መናኛ ልብስ የለበሰ እና አጃቢ የሌለው ሰውዬ ከሆነ በርግጥም ይህ ሰው ቅዱስ ነው” በማለት ደመደሙ፡፡ በመሆኑም ዑመር ከቤተ ክርስቲያናቸው ገብተው በሙስሊሞቹ ስርዓት “ሰላት” እንዲሰግዱ ጋበዟቸው፡፡ ዑመርም ግብዣውን ተቀበሉ፡፡ ነገር ግን ከቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ሳይገቡ በቅጥረ-ግቢው ውስጥ “ሁለት ረከዓ” ሰላት ሰገዱ፡፡ (ዑመር ይህንን ያደረጉት ሙስሊሞች ወደፊት “ዑመር የሰገደበት ቤተክርስቲያን ለኛ የተገባ ነው” የሚል ውዝግብ ሊፈጥሩ ይችላሉ በሚል ምክንያት ነው እንጂ ወደ ውስጥ መግባቱን ጠልተውት አይደለም” )፡፡

*****

ሙስሊሞች፣ ክርስቲያኖች፣ አይሁዶችና ሌሎችም የሃይማኖት ቡድኖች ከዚያ ዘመን ጀምሮ ለብዙ ዘመናት በጉርብትና አብረው ኖረዋል፡፡ የኦቶማን ቱርኮች ኢምፓየር እስከፈረሰበት ድረስ በሙስሊሞች የበላይነት በተመራው ኢስላማዊ ኸሊፌት ውስጥ ክርስቲያኖችም ሆኑ አይሁዶች ሀይማኖታቸውን በግዳጅ እንዲቀይሩ የተደረገበት ዘመን የለም፡፡

  አዳዲሶቹ ጽንፈኞች ግን ከነብዩ

ይህን የአንዱአለም አራጌን በራሱ አገላለጽ ከጠባቧ የቃሊቲ እስር ቤት የተጻፈ ግሩም መጽሐፍ ሳነብ የተሰማኝን ስሜት ባጭሩ ለመግለጽ እንጂ ሥነ ጽሑፋዊ ደንብ የተከተለ ሂስ ወይም የመጽሐፍ ግምገማ ለመስጠት አለመነሳቴን መግለጽ እፈልጋለሁ – መሆኑን እንዴት ከረማችሁ? ከሁሉ በፊት ግን ከሰሞነኛ ጉዳዮች መካከል ቂላቂሉ ወያኔ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የሠራውን አስቂኝ ድራማ ስመለከት እያዘንኩ የታዘብኩትን በዓለም ወደር የማይገኝለት […]

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ40 በ60 በሚባለው የቤቶች መርሃግብር የታቀፉ የዲያስፖራ አባላት  ከቀጣዩዓመት ምርጫበፊት ቤት እንዲሰጣቸው የአዲስ አበባ መስተዳድር መመሪያመስጠቱ ታውቋል። ሆኖምየጠቅላላተመዝጋቢውንየቤትፍላጎትለመሸፈንበትንሹከ16 ዓመታትበላይጊዜን እንደሚወስድ የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ የአዲስ አበባቁጠባቤቶችኢንተርፕራይዝእስካሁን 13ሺህ 800 ቤቶችን  በሰንጋተራእና ቃሊቲ ክራውን ሆቴልበመሳሰሉአካባቢዎችላይእየገነባመሆኑየታወቀሲሆን ፣ እነዚህን ቤቶችእስከሚቀጥለውዓመትአጋማሽድረስለዕድለኞችለማስተላለፍታቅዷል። የአስተዳደሩምንጮችእንደገለጹትቤቶቹከቀጣይዓመትምርጫበፊትሙሉበሙሉ ተጠናቀውእንዲተላለፉከአስተዳደሩመመሪያተሰጥቷል። ሆኖም ለ40 በ60 የቤቶች ፕሮግራምየተመዘገበውጠቅላላሕዝብቁጥር 164 ሺህ 779 ያህልሲሆንአስተዳደሩግን  በዓመትከ10 ሺህቤቶችበላይቤቶችን የመገንባትአቅምባለመፍጠሩየተመዘገቡትንብቻ ለማዳረስከ16 ዓመታትበላይጊዜንእንደሚፈልግየአስተዳደሩምንጮችአስታውቀዋል፡፡ …

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ በአንዋር መስጊድ የተፈጠረውን ተቃውሞ መርተዋል በሚል ከታሰሩት መካከል 6 ሙስሊም ኢትዮጵያውያን የዋስትና መብታቸውን ተነጥቀው ለሰኞ ችሎት እንዲቀርቡ ታዘዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባሏ ወ/ት ወይንሸት ሞላ ፣ የፎቶ ጋዜጠኛ አዚዛ ሙሃመድ እና ኢብራሂም አብዱልሰላም በ5 ሺ ብር  ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት በድጋሜ አዟል። …

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዳግማዊ ሚኒልክና በሌሎችም አካባቢዎች የሚሰለጥኑ ፖሊሶች በቀን የሚታሰብላቸው ገንዘብ በቂ ባለመሆኑ ጥያቄ አንስተዋል። ፖሊሶቹ ለቁርስና ምሳ እንዲሁም ለሻሂና ቡና 24 ብር በቀን የሚታሰብላቸው ቢሆንም፣ ገንዘቡ አይበቃንም በሚል ጥያቄ አንስተዋል። ፖሊሶቹ  ስልጣናውን ሳያቋርጡ ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ የኮሚሽኑ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ለማግባባት እየሞከሩ ነው። በዳግማዊ ሚኒሊክ ት/ቤት ውስጥ ካለፉት 2 ሳምንታት ጀምሮ ከ500 …

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሼክ ሙሃመድ አላሙዲን ንብረት የሆኑ በአዲስ አበባ ለአመታት ታጥረው የተቀመጡ የግንባታ ቦታዎች፣ የመስተዳድሩ ባለስልጣናት እንዲነጠቁ ውሳኔ አስተላልፈው ውሳኔውም ተግባራዊ ሆኖ ቆይቷል። ይሁን እንጅ ሪፖርተር እንደዘገበው ሼክ ሙሃመድ አላሙዲን ለጠ/ሚኒስትር ጽ/ቤ የግባኝ በማለታቸው የተወሰደባቸው ቦታ እንደሚለስላቸው መደረጉንና የመስተዳድሩ ውሳኔ መቀልበሱን ገልጿል። ተወስደው የነበሩት ቦታዎች ልደታ ክ/ከተማ ዋቢ ሸበሌ ጎንና በየካ …

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጊኒ ፣ ሴራሊዮንና ላይቤሪያ የታየው የኢቦላ ወረርሽኝ ወደ ሌሎች የአፍሪካ አገራት እንዳይዛመት ከፍተኛ ስጋት በደቀነበት በዚህ ወቅት፣ ከምስራቅ አፍሪካ ኬንያ በበሽታው ከሚጠቁ ቀዳሚ አገራት ተርታ ተሰልፋለች።ኬንያ የብዙ የምእራብ አፍሪካ አገራት የትራንስፖርት ማእከል በመሆኗ በበሽታው የመጠቃት እድላን ከፍ እንዳደረገው የተባበሩት መንግስታት የጤና ድርጅት አስታውቋል። ጀርመን ዜጓቿ ከላይበሪያ፣ ጊኒና ሴራሊዮን እንዲወጡ …

 

 

 

ኢትዮጵያና ሱዳን የጋራ የመከላከያ ኃይል ለመፍጠር ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የሁለቱም ሃገሮች የመከላከያ ሚኒስትሮች አስታውቀዋል፡፡

ኃይሉ ሥራ የሚጀምረው የፊታችን መስከረም ላይ እንደሚሆን የኢትዮጵያው የመከላከያ ሚኒስትር ሲራጅ ፈጌሣ ተናግረዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

 

 

 

በምሥራቅ ሐረርጌ በሚዻጋ ቶላ ወረዳ ቆንቆ ዲሞ በሚባል ሥፍራ በሶማሌ ክልልና በኦሮሚያ ክልል ታጣቂዎች መካከል ግጭት ተቀስቅሶ የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰማ።

የአከባቢውም ሆነ የክልሉ ባለሥልጣናት ስለግጭቱ ማብራሪያ አልሰጡም።

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ መረጃው እንደደረሰው ይናገራል።

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

 

 

 

ኢትዮጵያ ተወልዳ በሦስት ዓመት ዕድሜዋ ከቤተሰቧ ጋር ወደ አሜሪካ የተጓዘችው ሜሮን በጤናና በሕብረተሰብ ሣይንስ የመጀመሪያ ዲግሪዋን አግኝታለች፡፡

ሜሪላንድ ግዛት ሞንትጎመሪ አውራጃ ውስጥ በተካሄደው ሥነ-ሥርዓት ሜሮን የተቀዳጀችው ሁለት ሽልማት ነው፡፡ አንደኛው ሚስ አፍሪካ-ዩኤስኤ እና በሕዝብ ድምፅ ብልጫም አሸናፊነት ነው፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ከቅርብ አመታት ወዲህ በኢትዮጵያ በስፋት ከተዋወቁት የወሊድ መቆጣጠሪያ መንገዶች መካከል « ኤሜርጄንሲ ኮንትራሴፕቲቭ» ወይም ድንገተኛ የእርግዝና መከላከያ ዘዴ

ባለፈው ቅዳሜ በአንባብያን ይጠበቁ የነበሩ ሦስት መፅሄቶችና አንድ ጋዜጣ ሳይታተሙ ቀርተዋል ። ያልታተሙት መፅሄቶችና ጋዜጣ የኢትዮጵያ የፍትህ ሚኒስቴር ባለፈው ሳምንት ክስ እንደመሠረተባቸው ካስታወቀው አምሥት መፅሄቶችና ጋዜጣ መካከል ናቸው ።

የኢራቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ኑሪ አልማሊኪ የኢራን መንግሥት ድጋፍ እንዳላቸዉ ይነገራል። የቴህራን መንግሥት አል ማሊኪ ገና በጎርጎሪዮሳዊዉ 2006ዓ,ም ባግዳድ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትርነቱን መንበር ለመጀመሪያ ከያዙበት ጊዜ አንስቶ አዎንታዊ አመለካከቱን ሲቸራቸዉ ታይቷል።

በሃይማኖት ተጨቁነው እና በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ወደሚገኝ ተራራ ተሰደው የሚገኙ 20 000 የሚደርሱ የያዚዲ እምነት ተከታዮች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ እንደሆነ ነው የሚሰማው። ይህም አንዳንድ ጠበብት እንደሚሉት አሜሪካ ጣልቃ ከገባች በኋላ የተገኘ ለውጥ ነው።

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የክልሉን ከፍተኛ ባለስልጣናት በመያዝ ከአብድራፊ ከተማ ነዋሪዎች ተወካዮች ጋር የተነጋገሩ ሲሆን፣ ህዝቡ በአስተዳደር እና በጸጥታ ችግሮች ምክንያት መማረሩን ተወካዮቹ ተናግረዋል። አንድ የቀበሌ አስተዳዳሪ ህዝቡ በመብራት፣ ውሃ እና በመንገድ ችግር እየተቸገሩ መሆኑን ተናግረዋል። ሌላ ተናጋሪ ደግሞ ህዝቡ በድብቅ ጠመንጃ እየተዳደረ መሆኑንና  ወረዳው ህዝቡን ማስተዳዳር …

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢ/ር ይልቃል ከ20 የአውሮፓ ህብረት አገራት ልኡካን ጋር በህብረቱ ጽ/ቤት ተገኝተው በተወያዩበት ወቅት እንደገለጹት ፣ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት ችግር ወደ ባሰ ችግር ሳትገባ ህብረቱ አፋጣኝ እርምጃ ሊወስድ ይገባዋል። ኢ/ር ይልቃል ገዢው ፓርቲ ስለሚያደርገው አፈና፣ በሚዲያው ላይ ስለሚወሰደው እርምጃ፣ በእስር ላይ ስለሚገኙት ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞችና ጸሃፊዎች የተናገሩ ሲሆን፣ ኢህአዴግ በርእዮታለም መደናበርና በአመራር …

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራልአቃቢያነህጎችእናዳኞች፣የፈደራልማረሚያቤቶችባለስልጣናት፣የፌደራልናየአዲስአበባፖሊስ አመራሮችናየደህንነትሃላፊዎችበአቶአባዱላገመዳአሰልጣኝነት  የኢትዮጵያህዝቦችትግልናሃገራዊሕዳሴያችንበሚልርእስስልጠናጀምረዋል። ስልጠናው ምናልባትም በቅርቡበቀድሞውም/ል ጠ/ሚ  አዲሱለገሰ  በቀረበዉና የኢህአዴግን የአመራር ችግር በሚዘረዝረውን  ጥናት ላይ ለመወያየት ሳይሆን እንደማይቀር ምንጮች ጠቁመዋል። በዚህጥናትኢህኣዴግበከፍተኛየአመራርእጥረትእየተቸገረመሆኑን፣ኦሮሞየሆኑየኦህዴድኣባላትሙሉበሙሉወደኦነግእንዳደሉእንዲሁምደግሞ፣የአማራውክፍልየሆነውብሄረ አማራዲሞክራሲያዊንቅናቄ ከግንቦት7 ጋር ሽርክና መፍጠሩን መግለጻቸው ይታወሳል። አቶ አዲሱ የትራንስፎርሜሽኑ እቅድ ሊሳካ ያልቻለው በአመራር ችግር ምክንያት መሆኑንም ተናግረዋል። ስብሰባው ነሃሴ5የተጀመረሲሆንለ3 ሳምንት ያክል ይቆያል ተብሎ ይጠበቃል።

ኢቦላን ለመከላከል የሰለጠኑ ባለሙያዎች ከዛሬ ማክሰኞ፤ ነኀሴ 6/2006 ዓ.ም ጀምሮ ቦሌ ዓለምአቀፍ አይሮፕላን ጣቢያ ላይ ተመድበው ፍተሻ እያካሄዱ መሆኑ ተገለፀ፡፡

በአለባበስ እና በአመጋገብ በክርስቲያንና በሙስሊም ተማሪዎች መካከል አድልዎ ይፈጸማል በተማሪዎች ዲኑ ማንአለብኝነት ተማሪዎች የፍልሰታ ለማርያምን ጾም ለመጾም ተቸግረዋል የጅማ የማኅበረ ቅዱሳን ማዕከል ምእመኑን በማስተባበር ለተማሪዎቹ ድጋፍ እያደረገ ነው ቅ/ሲኖዶስ ሃይማኖታዊ መብታቸውን የሚያስከብር አቋም እንዲወስድ ተማሪዎቹ ጠይቀዋል ‹‹ኦርቶዶክሳዊ ሥርዐተ እምነትን በማንአለብኝነት ለይቶ የመጋፋት አካሔዱ፣ አኹን በደረሰበት ደረጃ አሳሳቢ የሃይማኖታዊል ነፃነት መረገጥ እንጂ የመብል ጉዳይና የአንድ ዩኒቨርስቲ …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በምሥራቃዊው ሱዳን ገዳርፍ አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን «በሰበብ-አስባቡ የአንዳንድ አክራሪ ቡድኖች የጥላቻ ሰለባዎች ሆንን» ሲሉ ብሶታቸውን ገለጡ። በ« ኤስ ኤም ኤስ » የሚደርሱን አጫጭር መልእክቶች እንደሚሉት ከሆነ ብዙዎች

በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ህዝብ ያለቀበት አንደኛው የዓለም ጦርነት የተጀመረበት መቶኛ ዓመት በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ታስቧል ።በቅርቡ የጦርነቱ መቶኛ ዓመት ከታሰበባቸው ሃገራት አንዷ የጦርነቱ የመጀመሪያዋ ሰለባ ቤልጂግ ናት ።

ዩክሬይን በሀገርዋ ምሥራቃዊ ከፊል በመንግሥቱ ጦር እና በዓማፅያን መካከል በቀጠለው ውጊያ ሰበብ የመሠረታዊ አቅርቦት ችግር ላጋጠመው ያካባቢው ነዋሪ ሩስያ በ280 የጭነት ተሽከርካሪዎች አጀብ ሰብዓዊ ርዳታ ልካለች፣