ስልጣን ያካፈለው የቡርኪና ፋሶ ጦር

ሌተና ኮሎኔል ያኩባ ኢሳክ ዚዳ የወታደር የደንብ ልብሳቸውን አውልቀዋል። ትናንት በተካሄደው የቡርኪና ፋሶ የሽግግር መንግሥት የመጀመርያዉን የካቢኔ ስብሰባ በጠቅላይ ሚኒስትርነት መርተዋል። ስብሰባው ከተከፈተ ከአንድ ሰዓት በኋላም ዚዳ « በርካታ ለውጦችን» ለሀገራቸው አውጀዋል።