ከፕሮፌሰር አለማየሁገ ብረማርያም

ትርጉምበነጻነት ለሀገሬ

ማዳም ክላሬ አሸንፈዋል! እንኳን ደስ ያለዎት፣ ማዳም ክላሬ!

ባለፈው ሳምንት የ አምራች ኢንዱስትሪዎች የግልጽነት ተነሳሽነት/Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) ሊቀ መንበር የሆኑት ማዳም ክላሬ ሾርት ስልጣናቸውን ከህግ አግባብ ውጭ በመጠቀም እና በማስፈራራት በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የሙስና ማጋበሻ ቡድናቸው አባል እንዲሆን ለማስቻል የEITI የቦርድ አባላት ድምጻቸውን እንዲሰጡ በማድረጉ ጥረት ሲያካሂዱት የቆዩት ዥዋዥዌ ጨዋታ ተሳክቶላቸዋል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …


click here for pdf

በተፈጥሮ ካልተገኙና ሰው ልጅ ከፈጠራቸው ከማይንቀሳቀሱ የሥልጣኔ ውጤቶች አንዱ ከተማ ነው፡፡ ከተማ የአንድ ሕዝብ ሥልጣኔ የሚታይበትና የሚቀላጠፍበት ማዕከል ነው፡፡ በዚህም የተነሣ የሰው ልጅን ታሪካዊ ሂደት በመመዝገብና የደረሰበትንም ሥልጣኔ በማሳየት ረገድ የከተማን ያህል የተሻለ ቦታ የለም፡፡ የጥንታዊ ሰዎችን ሥልጣኔና ታሪክ የሚያጠኑ ባለሞያዎች የጉዞውን ሂደት የሚገልጡ መረጃዎችን የሚያገኙት በቁፋሮ ከሚገኙ ጥንታውያን ከተሞች ነው፡፡ በእነዚህ ጥንታውያን ከተሞች የሰው አነዋወር፣ ታሪክ፣ የመንግሥት አሠራር፣ የንግድና የኢኮኖሚ ሁኔታ፣ ወግና ሥርዓት፣ እምነትና ባሕል በተሰናሰለና ሥርዓት በጠበቀ መንገድ ይገኝባቸዋል፡፡
በአብዛኛው የገጠሩ ማኅበረሰብ ባልተሰባሰበ፣ አንድ ወገን በሆነ፣ ግልጽ የአኗኗር መርሕ፣ አስተዳደራዊ መዋቅር እምብዛም ባልተዘረጋበት መንገድ የሚኖር ነው፡፡ የከተማ ማኅበረሰብ ግን በተወሰነ ቦታ፣ ከተለያየ ማኅበረሰብ ተውጣጥቶ፣ በአንድ ውሱን ሕግ እየተዳደረ፣ ለክዋኔዎች ቦታ ወስኖ(ለንግድ፣ ለአምልኮ፣ ለመንግሥት አስተዳደር፣ ለመኖሪያ፣ ወዘተ) የሚኖር በመሆኑ የሥልጣኔ መገለጫዎች በከተሞች የሚገኙትን ያህል በገጠር አናገኛቸውም፡፡ ሐውልቶች፣ አደባባዮች፣ አብያተ መንግሥት፣ ሳንቲሞች፣ የኪነ ጥበብ ሕንጻዎች፣ የተደራጁ ገበያዎች፣ የውኃ መሥመሮች፣ የከተማ መከለያ ግንቦች፣ የእምነት ማዕከሎች በከፍተኛ የሥልጣኔ ደረጃ ተሠርተው የምናገኛቸው በከተሞች አካባቢ ነው፡፡

በሀገራችንም የታሪክና ቅርስ ማዕከል የሆኑትን አኩስምን፣ ሮሐን፣ ሐረርን፣ ጎንደርን፣ አንኮበርን፣ አዲስ አበባን፣ ሌሎችንም ብንመለከተ የመንግሥት፣ የኢኮኖሚና፣ የእምነት መናኸሪያ ከተሞች የነበሩና የሆኑ ናቸው፡፡ በእነዚህ ቦታዎች የምናገኛቸውን እርስ በርስ የተግባቡ፣ የተሠናሠሉና የተመጋገቡ የሥልጣኔ መገለጫዎችን ያህል በሌሎች ቦታዎች አናገኝም፡፡ በሌሎች ቦታዎች የምናገኛቸው በተናጠል የተቀመጡ የሥልጣኔ መገለጫዎችን ነው፡፡
የሰው ልጅ በተፈጥሮው ምክንያት ትናንትን ይጠይቃል፡፡ እንዲሁ ዛሬን ብቻ ዝም ብሎ አይቀበልም፡፡ እንደ ሥነ ፍጥረት ሊቃውንት ይህንን የሚጠይቁት መላእክትና ሰዎች ብቻ ናቸው፡፡ መላእክት በተፈጠሩ ጊዜ ‹‹ከየት ተገኘን? እንዴትስ ልንገኝ ቻልን?›› ብለው የጠየቁት ግእዛን ያላቸው (ማሰብና መመርመር የሚችሉና የሚያስፈልጋቸው) ፍጡራን በመሆናቸው ነው፡፡ የሰው ልጅም በምድር ላይ መኖር ከጀመረበት ዘመን ጀምሮ በእምነትና በፍልስፍና መስኮች ሲጠይቃቸው ከኖራቸው ጥያቄዎች አንዱ ‹‹ዓለም ከየት መጣች?›› የሚለውን ነው፡፡
ሰው ትናንትን የማወቅ፣ ከትናንቱም የመማር፣ ከትናንት ተምሮም ወደፊት የመንደርደር ዕምቅ ፍላጎትና ችሎታ ስላለው መሬት እየጎረጎረ፣ ዋሻ እየበረበረ፣ ዐለት እየፈለጠ፣ ተራራ እየገለበጠ የጥንት ሰዎችን አድራሻ፣ ማንነትና ሥራ ሲመረምር ይኖራል፡፡
ሰው እንደ እንስሳ የዛሬን ብቻ ኑር ሊባል አይችልም፡፡ እንስሳ ትናንትም ነገም የለውም፡፡ ሰው ግን የሦስት ነገሮች ውጤት ነው፡፤ የትናንት አሻራ፣ የዛሬ ሥራ፣ የነገ ራእይ፡፡ ሰው ነገን ያለ ትናንት ማሰብ አይችልም፡፡ ተፈጥሮ አንድን ነገር ለብቻው በንጣሌ እንድንረዳው አልተወችንምና፡፡ ተፈጥሮ ራሷ የትይይዝ ውጤት ናት፡፡ ሊቃውንት ይህንን ለማስረዳት እንደ ቀላል ማሳያ የሚሰጡን ቀለማትን ነው፡፡ አንዱ ቀለም ከሌላ የሚግባባው ቀለም ጋር ስምምነት ፈጥሮ(harmony) ነው የሚኖረው፡፡ ይህንን የቀለማት ተግባቦት የሰዎች አለባበስ፣ የቤት አሠራር፣ የፀጉርና የሰውነት ቀለም፣ የሚተከሉ ዛፎችና እንዲፈጥሩት ይደረጋል፡፡ ምንም እንኳን እነዚህን ቀለማት አስበን ባንመርጣቸውም ተፈጥሮ ተግባቦትንና ስምምነትን ስለምትፈልግ ደመ ነፍሳዊ በሆነ መንገድ እናከናውነዋለን፡፡ 
በአንዲት ከተማ ሕይወት ውስጥም እንደ ቀለማቱ ተግባቦት ሁሉ ትናንት፣ ዛሬና ነገ ተግባብተው መገኘት አለባቸው፡፡ እንኳን እንደ አዲስ አበባ ያሉ ከመቶ ዓመታት የዘለለ ታሪክ ያላቸው ከተሞች ቀርተው የቅርብ ዘመን የምሥረታ ታሪክ ያላቸው እነ ዱባይ እንኳን አንዳች ከጥንታዊነት ጋር የሚያያዝ ታሪክ ፍለጋ ሲኳትኑ፣ ያንንም ለማሳየትና የከተማቸው የሕይወት አካል ለማድረግ ሲጥሩ እናያቸዋለን፡፡
በአንድ ከተማ ሕይወት ውስጥ በሳል ነቢብ(ቲወሪ)፣ አመራርና አሠራር ከሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች አንዱ ትናንትን፣ ዛሬንና ነገን ከከተማዋ ዕድገት፣ ሥልጣኔና የአነዋወር ዘይቤ ጋር አጣጥሞ የመሄድ ብልሃት ነው፡፡ የከተማዋ ጥንታዊነት የዛሬ ዕድገቷንና የነገ ተስፋዋን እንዳይገታው፤ የከተማዋ የዛሬ መስፋፋት፣ ዕድገትና ሥልጣኔ የትናንት አሻራዋን እንዳያጠፋው፤ የከተማዋ የትናንት ታሪክና የዛሬ ዘይቤም የነገውን ትውልድ ድርሻና ዕጣ ፋንታ እንዳያቀጭጨው – በሳል የሆነ ነቢብ፣ አመራርና አሠራር ይጠይቃል፡፡
የአንዲት ከተማ መልክዐ ጠባይ፣ ሕይወትና እሴት የሚገነባው ከዚህ መሰሉ ነቢብ፣ አመራርና አሠራር ነው፡፡ የከተማዋ ሕንጻዎች፣ መኖሪያዎች፣ መንገዶች፣ የሕዝብ ቦታዎች፣ ገበያዎች፣ የእምነት ቦታዎች፣ ማኅበራዊ ተቋማት፣ የአካባቢ ጥበቃ፣ ጽዳትና ውበት፣ ከዚህ ነቢብ፣ አመራርና አሠራር ይወለዳሉ፡፡ የሚፈቀዱና የሚከለከሉ ነገሮች ከዚህ ይመነጫሉ፤ የሚጠበቁና ለሕዝብ ክፍት የሚሆኑ ነገሮች ከዚህ ይመሠረታሉ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ቁልፍ ችግሯ ትናንት፣ ዛሬና ነገን የምታግባባበት የራስዋ የሆነ፣ በዘመናት የዳበረ፣ የተፈተነና ውጤታማነቱ የተመሰከረለት ‹ነቢብ፣ አመራርና አሠራር› ማጣት ይመስለኛል፡፡ በአንድ የውይይት መድረክ አንድ የከተማ ዐቅድ ባለሞያ እንደገለጡት ‹‹አዲስ አበባ እያንዳንዱ መንግሥት የየራሱን ርዕዮተ ዓለም ያነባበረባት ከተማ ናት – The layer of different Ideologies ፡፡ ያ ነው ከተማዋን ሲምታታባት እንዲኖር ያደረገው››
አዲስ አበባ አሁን ዐሥረኛውን የከተማ መሪ ዕቅድ እያዘጋጀች ነው፡፡ እነዚህ መሪ ዕቅዶች ምንም እንኳን ሳይንሳዊ አሠራርን የተከተሉ ሞያዊ ሥራዎች ቢሆኑም የሚዘወሩት ግን በየዘመናቱ ሀገሪቱ በምትመራባቸው ርእዮተ ዓለሞች ነው፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ አዲስ አበባ ‹ወጥ፣ ለዘመናት የዳበረ፣ የተፈተነና የተመሰከረለት የከተማ ዘይቤ› እንዳይኖራት አድርጓታል፡፡
ባለፈው መንግሥት ጊዜ የቁጠባ ቤቶች የአዲስ አበባ የቤቶች መልክዕ ሆኖ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ኮንዶሚኒየምና ሪል እስቴት የአዲስ አበባ የቤት መልክዕ ሆነዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከንቲባነት ለረዥም ዓመታት በማገልገል የሚታወቁት ከንቲባ ዘውዴ እንደሚሉት በአዲስ አበባ ቀበሌ ሲቋቋም ከ2500 – 4000 የሚደርስ ሕዝብ የሚይዝ አንዳች የጉርብትና ማዕከል ለመፍጠር ነበር፡፡ ጉርብትናን ዘመናዊ ለማድረግ፡፡ ‹ከተማ ማለት የጉርብትና ሥርዓት ነውና›፡፡ ርእዮተ ዓለሙ ሲቀየር ግን ቀበሌዎች የጉርብትና ማዕከላት መሆናቸው ቀርቶ የቀይ ሽብርና የነጭ ሽብር ማዕከላት ሆኑ፡፡ ቀበሌ ማለትም የአብዮት ማራመጃ ማዕከል ሆነ፡፡ በሀገራችን መንግሥታት የሚቀያየሩት በመፍረስ በመሆኑ በመንግሥታት መካከል ርክክብ አልተደረገም፡፡
ይህንን መሰሉ በየጊዜው የሚለዋወጡ ነቢቦች፣ አመራሮችና አሠራሮች አንዳቸው ከሌላቸው ጋር ተግባብተው የሚመሠረቱ ባለመሆናቸው አዲስ አበባ ስትፈርስ ስትሠራ የምትኖር መሞከሪያ ከተማ እንድትሆን አድርጓታል፡፡ እንኳንስ በተለያዩ መንግሥታት ርእዮተ ዓለሞች መካከል ቀርቶ በአንድ መንግሥት ዘመናት እንኳን ሲያፈርሱ ሲሠሩ መኖር እየተለመደ መጥቷል፡፡ ከሸራተን አካባቢ የተነሡ ነዋሪዎች ለድጋሚ ተነሺነት የተጋለጡት በዚህ ያልተግባባ አሠራር ጭምር ነው፡፡ አዳዲስ ቤቶች እንደገና ለመንገድና ለሌሎች ግንባታዎች ተብለው የተሠሩበት ሲሚንቶ ሳይደርቅ እንዲፈርሱ የሚደረጉት በዚህ ወጥነት በሌለው የከተማዋ ነቢብ፣ አመራርና አሠራር የተነሣ ነው፡፡ በተሠሩ በጥቂት ዓመታት ለባቡር ተብለው የፈረሱትንና 900 ሚሊዮን ብር የፈጁትን የአዲስ አበባ መንገዶችን በዚህ በበሰለ ነቢብ፣ አመራርና አሠራር ብቻ ነበር ማትረፍ ይቻል የነበረው፡፡ አንድም ቀድሞ በማሰብ፣ አለያም አጣጥሞ በመሥራት፡፡ 
አዲስ አበባ ዕድገቷንና ታሪኳን የማጣጣም ፈተና ገጥሟታል፡፡ ለመሆኑ ያለፉ ነገሮቿን ሁሉ እንዳሉ ይዛ መቀጠል አለባት? ያለፉ ነገሮቿንስ ሙሉ በሙሉ አፈራርሳስ መቀጠል አለባት? ለመሆኑ ታሪክና ዕድገት፣ ቅርስና ሥልጣኔ እንዴት ነው የሚጣጣሙት? ከተማዋ እነዚህን በትክክል ካልመለሰች ከተማ ሳይሆን ዘመናዊ የሰው ልጅ ማጎሪያ ትሆናለች፡፡ ዛሬ የሚሠሩት ታላላቅ ግንባታዎቻችንስ የነገውን ትውልድ ሥልጣኔ፣ አነዋወርና ፍልስፍና ከግምት ውስጥ እያስገቡ ናቸው? የዛሬ አምስት ዓመት የገነባናቸውንና ስናስመርቃቸው ጉሮ ወሸባ ያረገድንባቸውን እንዲህ በፍጥነት የምናፈርስ ከሆነ ሌሎቹን እንድንጠራጠር ያደርገናል፡፡
አሁን አሁን አዲስ አበባ ትናንትን ከዛሬ፣ ዛሬንም ከነገ የሚያጣጥም ነቢብ፣ አመራርና አሠራር በማጠቷ ምክንያት የአዲስ አበባ ከተማን ጥንታዊነት የሚያሳዩ ቅርሶች እንደ ነፍጠኛና ፊውዳል መገለጫዎች እየተቆጠሩ፣ ቀጥታና ቀጥታ ያልሆነ ሞት እየተፈረደባቸው ነው፡፡ ቀጥተኛ የሆነ ሞት የሚባለው ለዕድገት ፀር፣ለግንባታ ዕንቅፋት፣ ለመስፋፋት እንከን አድርጎ በማየት የማፍረስ ርምጃ መውሰድ ነው፡፡ በዚህ ፍርድ ምክንያት ጥንታውያን መንደሮች፣ ቤቶች፣ ድልድዮች፣ ሐውልቶች፣ አደባባዮች፣ የንግድ ማዕከላት፣ እንዲፈርሱ ተደርገዋል፡፡
ሁለተኛውና ቀጥታ ያልሆነ ሞት የምንለው ደግሞ እነዚህን ጥንታውያን ሀብቶች የመከባከብ ኃላፊነት ያለበት አካል ክብካቤ በመንፈግና ቀስ በቀስ እንዲፈርሱ ሆን ብሎ በመተው የሚደረግ ግድያ ነው፡፡ ይህ ፍርድ የተፈረደባቸው ቅርሶች በአካባቢያቸው ለእነርሱ ሕልውና አሥጊ የሆነ ሥራ ሲከናወን የሚያስጥላቸው የለም፤ የቆሻሻ መጣያ ሲሆኑ በዝምታ ይታለፋሉ፤ ሲፈርሱና ሲበላሹ በዝምታ ይታያሉ፤ ሲዘረፉና ሲወሰዱ የሚያስጥል አያገኙም፤ ጥበቃ አይደረግላቸውም፤ ሞያ በሌላቸው አካላት እንዲጠገኑ ይደረጋል፤ ታጥረውና ተከልለው እንዲቀመጡ ይደረጋል፤ በውስጡ ነዋሪዎች ሲቀመጡባቸውና ግንባታ ሲያከናውኑባቸው ተከታታይ አይኖርም፤ በጢስና እሳት እንዲበላሹ ይተዋሉ፡፡
በአንድ በኩል ያለፈው ነገር ሁሉ መነካት የለበትም የሚሉ የታሪክና ቅርስ ወግ አጥባቂዎች (ወግ አጥባቂነት አዎንታዊ ነው) አሉ፡፡ እንደ እነርሱ ከሆነ የአዲስ አበባ ነባር ነገሮች ሁሉ ተጠብቀውና ተከብረው መኖር አለባቸው፡፡ እነርሱ የከተማዋን፣ ብሎም የሀገሪቱን ጥንት የሚመሰክሩ ናቸውና፡፡ ሌሎቹ ደግሞ በቦታው ላይ የሚሠራ ሌላ ነገር እስካለ ድረስ የጥንቱ መፍረስ አለበት፡፡ የጥንቱ ጥንት አገልግሏል፡፡ አሁን ዘመኑ የዛሬ ነው፡፡ ጥንቱ ለዛሬ ዕንቅፋት ከሆነ ያለው ዕድል መፍረስ ብቻ ነው ይላሉ፡፡
እነዚህ ሁለቱም ለእኔ ጽንፎች ናቸው፡፡ ሁሉም የጥንት ነገር እንዳለ ሊቀመጥ አይችልም፡፡ በሦስት ምክንያት፡፡ አንድ ሁሉም የጥንት ነገሮች እኩል የሆነ ታሪካዊ፣ ቅርሳዊና ባሕላዊ ዋጋ የላቸውም፤ ሁለተኛ ደግሞ ሁሉም የጥንት ነገሮች ይቀመጡ ካልን ለአዳዲስ ነገሮች ቦታ ላይገኝ ይችላል፤ በመጨረሻም ሁሉንም የጥንት ነገሮች ለማቆየት፣ ለመጠበቅና ለመከባከብ ዐቅም ያስፈልጋል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ለአዳዲስና ለዘመናዊ ነገሮችና ሐሳቦች ሲባል ሁሉንም የጥንት ነገሮችን በግዴለሽነት ማፈራረስ ሦስት ጉዳቶች ያስከትላል፡፡ የሰው ልጅን የጥበብ፣ የባሕል፣ የሥልጣኔና የክሂሎት አሻራ ያጠፋል፤ አንድን ነገር ምንጊዜም እንደገና እንድንጀምረው በማድረግ ተያያዥና ተደጋጋፊ ነገርን ያሳጣል፤ በመጨረሻም የከተማዋን የቱሪዝም ገቢ ያመክናል፡፡ 
እነዚህን ሁለት ጽንፎች ለማስታረቅ የሁለቱንም አዎንታዊነት የያዘ አንድ ሌላ መንገድ ያስፈልጋል፡፡ እርሱም አዳዲስ ነገሮችን ከጥንታውያን፣ ዘመናዊነትን ከነባርነት፣ ታሪክን ከዕድገት፣ ቅርስን ከሥልጣኔ ጋር አስማምቶ፣ አደጋግፎና አመጋግቦ መምራት ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ወጥነት ያለው፣ በየዘመናቱ የሚዳብር በሳል ሀገራዊ ፍልስፍና ያስፈልጋል፡፡
ይህንን መንገድ ተግባራዊ ለማድረግ የሚከተሉት አካሄዶች ያስፈልጋሉ
  1. የከተማዋን ታሪካዊና ባሕላዊ ቅርሶች የመለያ መመዘኛ ማስቀመጥ
  2. በመመዘኛው መሠረት የከተማዋን ታሪካዊና ባሕላዊ ቅርሶች በዝርዝር መለየት
  3. እነዚህ የከተማዋ ቅርሶች በልዩ ልዩ መንገድ ለትውልድ የሚተላለፉበትን መሥፈርት ማውጣት
  • እንዳሉ ባሉበት ሁኔታ ለሌላ አገልግሎት ሳይውሉ ለትውልድ መተላለፍ ያለባቸው
  • መጠናቸው ተቀንሶ ናሙናቸው መተላለፍ ያለባቸው( ለምሳሌ አንድን መንደር ሙሉውን ቅርስ አድርጎ ማቆየት ከባድ ቢሆን እንኳን ያ መንደር ምን ይመስል እንደነበር የሚያሳይ አንድ ናሙና ቦታ ለይቶ ማቆየት ይቻላል)
  • በልዩ ልዩ የመቀረሻ መሣሪያዎች(ፎቶ፣ ሥዕል፣ ቪዲዮ፣ ወዘተ) ተመዝግበው መተላለፍ ያለባቸው(አንዳንድ ሠፈሮች የቀድሞ መልካቸውና አሠራራቸው በልዩ ልዩ መቀረሻ መንገዶች ቀርጸ ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባል)
  • ወደ ሙዝየም ገብተው መተላለፍ ያለባቸው
  • ቅርስነታቸውንና ይዞታቸውን በማይጎዳ መንገድ ለሌላ የማይጣረስ አገልግሎት ተላልፈው ግን ተጠብቀው መተላለፍ ያለባቸው(ጣይቱ ሆቴል እንደተደረገው)
  • ቦታቸውን ቀይረው በቅርስነት መጠበቅ ያለባቸው
  • ማናቸውም ከተማዊ እንቅስቃሴዎች ከእነዚህ የተመዘገቡ ቅርሶች ጋር ያላቸውን ተግባቦት በቅርብ መከታተል፣ ለክትትሉም እንዲያመች የሚመለከተው አካል ከማናቸውም ግንባታ በፊት አካባቢው ከቅርስ ነጻ መሆኑን ምስክርነት እንዲሰጥ ማድረግ
  • የከተማዋ መሪ ዕቅድ ሲዘጋጅም እነዚህን ታሪካዊ ቦታዎችና ቅርሶችን በሚገባ የለየና የእነርሱን የሕልውና መብት የጠበቀ መሆኑን ማረጋገጥ
  • በታሪካዊና ባሕላዊ ቅርሶች አካባቢ ይፋዊ መለያ መለጠፍ፤ ይህ ምልክት የተለየ ቀለም ወይም ዐርማ እንዲኖረው በማድረግ ማንኛውም ሰው እንዲለየው ማስቻል
  • የፌዴራል ቅርስ አዋጅ ቁጥር 209/92 ለክልሎችና ለከተማ አስተዳደሮች ምንም ዓይነት ሥልጣን ስለማይሰጥ ይህንን ማስተካከል
  • የታሪካዊና ባሕላዊ ቅርሶች አካባቢዎች የተዛማጅ ልማቶች ማዕከል (የሆቴል፣ የጥበበ ዕድ መሸጫ፣  የዐውደ ርእይ ማሳያ፣ የባሕላዊ ገበያዎች) መጠቀም
  • በተማሪዎች፣ በአካባቢው ነዋሪዎችና በቱሪስቶች እንዲጎበኙ መርሐ ግብሮችን ማመቻቸት

  • እነዚህንና የመሰሉትን ተግባራት በጊዜ ማከናወን ካልቻልን አዲስ አበባ ‹ትናንት የሌላት ከተማ› ትሆናለች፡፡ ያውም በታሪክ አጋጣሚ ሳይሆን ሳያስቡ የሚሠሩ አመራሮችና ነዋሪዎች ስላሏት ብቻ፡፡ ከተማ እንደ ፈጣን ምግብ(fast food) ለዕለት ሆድ መሙያ የምትሠራ አይደለችም፡፡ እንደ ገጠር ጠላ ለነገም ጭምር የምትጠነሰስ ናት፡፡ ከተማዋን ለሰዎች መኖሪያነት ምቹና ተመራጭ ለማድረግ መንገድ፣ ሆቴል፣ ሰማይ ጠቀስ ሕንጻ፣ ባቡር፣ ሱፐር ማርኬት፣ የገበያ ማዕከል፣ የግል ኮሌጅ፣ ዓለም ዐቀፍ ተቋማትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ብቻቸውን በቂ አይደሉም፡፡ ጥንታዊ፣ ታሪካዊ፣ ባሕላዊ፣ መንፈሳዊና ሞራላዊ እሴቶች፣ ቅርሶችና ቦታዎችም ያስፈልጓታል፡፡ እነዚህ ራሳቸው ነገ ታሪክና ቅርስ ስለሚሆኑ፡፡ ከተማ እንደ ላም ዱካ የሚተው እንጂ እንደ አዞ በጅራታቸው ዱካ የሚያጠፉ አመራሮች አያስፈልጓትም፡፡

     © ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው

    abuna tomas 2(MKWebsite):- የምእራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ቶማስ ዐረፉ:: የቀድሞ ስማቸው አባ መዘምር ተገኝ የአሁኑ ብፁዕ አቡነ ቶማስ ጥር 14 ቀን 1932 ዓ.ም ጎጃም ደጋ ዳሞት ዝቋላ አርባዕቱ እንስሳ ተወለዱ፡፡ መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርትን በሚገባ ከተማሩ በኋላ ጸዋትወ ዜማን ከመሪጌታ አንዱዓለምና መሪጌታ ካሣ ይልማ ፣ ቅኔ ከመሪጌታ ፈንቴ /ዋሸራ/፣ መጻሕፍተ ሐዲሳትን ከመሪጌታ ብርሃኑ ወልደ ሥላሴ ፣ መጻሕፍተ ሊቃውንትን ከመሪጌታ ቢረሳ ደስታ ተምረዋል፡፡ በዘመናዊ ትምህርትም እስከ 6ኛ ክፍል ፣ የእንግሊዝኛን ቋንቋ በግላቸው የተማሩና የመኪና ጽሕፈት /type writing/ የሚያውቁ ነበሩ፡፡ ብፁዕ አቡነ ቶማስ ዲቁና ከአቡነ ማርቆስ፣ ቅስና ከአቡነ ባልዮስ፣ ቁምስና ከብፁዕ አቡነ ተክለሃይማኖት ተቀብለዋል፡፡

    በደብረ ሊባኖስ ገዳም መጻሕፍተ ሊቃውንትን ረዘም ላለ ጊዜ አስተምረዋል፡፡ በገዳሙ የሠራተኞች ቅርንጫፍ ማኅበር ሲቋቋምም የመጀመሪያው ሊቀ መንበር በመሆን አገልግለዋል፡፡ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ ተዛውረው በጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል በአስተዳዳሪነትና መጻሕፍተ ሓዲሳትንና ሊቃውንትን በማስተማር የሚጠበቅባቸውን ተልእኮ ተወጥተዋል፡፡ ጥር 14 ቀን 1972 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ አንብሮተ ዕድ ተሹመው ሰፊ አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ በመመለስ የታእካ ነገሥት በዓታ ለማርያምና መንበረ መንግሥት ግቢ ገብርኤል ገዳም የበላይ ጠባቂ ሆነው አገልግለዋል፡፡
    ብፁዕነታቸው ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ የምእራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተው፤ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው መጋቢት 16 ቀን 2006 ዓ.ም መንበረ ጵጵስናቸው በሚገኝበት በፍኖተ ሠላም ከተማ ዐርፈዋል፡፡ ሥርዓተ ቀብራቸውም በዚያው በፍኖተ ሰላም እንደሚፈጸም ይጠበቃል፡፡
    Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

    ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

    Image

    በኢትዮጵያ የውጭ እርዳታ ይጎርፋል፤ በግርድፉ ከ40-50 ቢሊዮን ዶላር ባለፉት 22 አመታት ተለግሷል። ወደ 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብም ተበድረናል፡፡ የውጭ ኢንቨስትመንትም ይፈሳል፤ ግንባታዎችም ይካሄዳሉ። በእነዚህ ፈንድሻ ዜናዎች መሃከል ግን ብዙ ችግሮችም አሉ። ውሃ ፣ መብራት፣ ስኳር እና ዘይት በፈረቃ ይከፋፈላሉ፤ ትራንስፖርት ችግር ነው፤ በቀን ሶስት ጊዜ ለመብላት ጭንቅ ነው፤ ነጻነት፣ ፍትህ፣ ሰብዓዊ መብት የሚባሉት ነገሮች ከመንግስት መዝገበ-ቃላት ተሰርዘዋል።

    የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አንድ ልዩ ባህሪ አለው። እንደሚታወቀው ልማትና ድህነት ተጻራሪ ሃይሎች ናቸው። ሁለቱ ሃይሎች በአንድ አቅጣጫ መጓዝ አይችሉም። ልማት ወደ ግራ ከሄደ ድህነት የግድ ወደ ቀኝ መጓዝ አለበት። በሃይማኖታዊ ቋንቋ ሰይጣንና መላዕክ ማለት ናቸው። አንዱ ባለበት ቦታ ሌላው ድርሽ አይልም። ይሄ ህግ ተዛብቶ “ልማትና ድህነት በአንድ ላይ ተቃቅፈው ታንጎ የሚጨፍሩበት አገር የት ነው? ” ከተባለ ያች አገር ኢትዮጵያ ናት። ልማቱ አደገ ሲባል፣ ድህነቱም በዚያው ልክ ያድጋል።

    አገሪቱ ለ10 ዓመታት በ11 በመቶ እንዳደገች ከተነገረ በሁዋላ እንኳ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ( ምግብ፣ መጠለያና ልብስ) ማሟላት ጭንቅ ሆኗል። የልማቱን ኬክ ጥቂቶች ይበሉታል፣ ብዙዎች ፍርፋሪውን እንኳ አጥተው በረሃብ ያሸልባሉ። ቀኑ ይርዘም እንጅ የባስቲሌ አመጽ በአራት ኪሎ መደገሙ አይቀሬ ነው፤ ድህነትና ልማት ተጣምረው ታንጎ በሚደንሱባቸው አገሮች ማህበራዊ ምስቅልቅል የመጨረሻው ምርት ይሆናል።

    የገዚው ፓርቲ ካድሬ ኢኮኖሚስቶች “ልማቱ ጤነኛ አይደለም” ተብሎ ሲነገራቸው አይቀበሉም፤ ክርክር ሲነሳም ብዙውን ጊዜ የሚሰጡት መልስ ” የሚቀጥለው ትውልድ ያልፍለት ዘንድ ይህኛው ትውልድ መስዋትነት መክፈል አለበት” የሚል ሆኖ ይገኛል። በካድሬው አስተሳሰብ ይሄ ትውልድ ጨለማ ውስጥ ቢኖር፣ የሚቀጥለው ትውልድ መብራት እንደልቡ ያገኛል፣ ይሄ ትውልድ ውሃ ቢጠማው ፣ መጪው ትውልድ በጁስ ይራጫል፣ ይሄ ትውልድ ትራንስፖርት ቢቸግረው፣ መጪው ትውልድ በቤት መኪና ይንበሻበሻል ።

    የካድሬ ኢኮኖሚስቶች ዋና አላማ ይሄ ትውልድ የመብትና የማህበራዊ ግልጋሎት ጥያቄዎችን እንዳያነሳ የተስፋ ዳቦ እየመገቡ ማዘናጋት ነው፤ አንዳንዴ የሚገነቡ መንገዶችን እያሳዩ ” የወደፊቱ ልጅህ መኪናውን የሚያሽከረክርበት ነው፣ ዘመናዊ ህንጻዎችን እያሳዩ ” የወደፊቱ ልጅህ የሚኖርበት ቤት ነው” እያሉ ያማልሉታል። ይሄ ትውልድ የውሃና የመብራት ጥያቄ ይሟላልኝ ብሎ እስካልተነሳ ድረስ የዛሬው ካድሬ ጭንቀት የለበትም፤ ለመጪው ጊዜማ የመጪው ትውልድ ካድሬ ይጨነቅበታል። “ለመሆኑ መጪው ትውልድ የሚባለው ስንተኛው ትውልድ ነው? የሚቀጥለው ትውልድ እንደሚያልፍለትስ ማረጋገጫው ምንድነው?” እንዲህ አይነት ጥያቄዎች ለካድሬ ኢኮኖሚስቶች መጠየቅ የሌለባቸው” ነውር ” ናቸው።

    “ይሄ ትውልድ ለመጪው ትውልድ ሲል መስዋትነት መክፈል አለበት” የሚለውን የካድሬ ቅስቀሳ አምነው የተቀበሉ ሰዎች አጋጥመውኛል። እነዚህም ሰዎች በፊናቸው”ልማትና ዲሞክራሲ በአንድ ጀምበር አይመጣምና ታገሱ ” ሲሉ ከካድሬው የሰሙትን ስብከት መልሰው ለሌሎች ሰዎች ለማስረዳት ሲሞክሩ አይቻለሁ። እንዲህ አይነቱ ስብከት ዜጎች ለመብታቸው እንዳይነሱ በማድረግ በኩል የራሱ አስተዋጽዎ አለው። መሰረታዊ ለውጥ በአገራችን እንዲመጣ የሚፈልጉ ሃይሎች እንዲህ አይነቱን የማዘናጊያ ቅስቀሳ ፣ በእውቀት ላይ በተመሰረተ ክርክር ሊመክቱት ይገባል። በኢትዮጵያ ስላለው ልማትና ድህነት የጠራ ግንዛቤ መያዝ ለዲሞክራሲያዊ ለውጥ የሚደረገውን ትግል ያግዛልና ሁሉም አስተያየቱን ሊሰጥበት ግድ ይላል።

    በቀድሞው የሲንጋፖር ጠቅላይ ሚኒስትር ፣ ሊ ኩዋን ስም የተሰየመ “የሊ ንድፈ ሃሳብ” የሚባል በፖለቲካ ኢኮኖሚ ትምህርት ውስጥ የሚገኝ አስተሳሰብ አለ። ይህ አስተሳሰብ ዜጎችን ከብዙ ጊዜያዊ መብቶቻቸው በመገደብ ልማትን ለማምጣት የሚያልም ሲሆን፣ ዳቦን ከመብት እንዲሁም አምባገነንነትን ከዲሞክራሲ ያስቀድማል ። በዚህ አስተሳሰብ መነሻነት ኢኮኖሚያቸውን የመሩ የእስያ ነብሮች የሚባሉ አገሮች ድህነትን “ቻው” ለማለት እንደቻሉ ይነገራል ። ኢህዴግም የዚህ አስተሳሰብ ተከታይና አራማጅ ነው። አስተሳሰቡ ለብዙ አምባገነን መንግስታት የሚጥም፣ ያለ ገደብ በስልጣን ላይ ለመቆየትም እንደምክንያት ሆኖ የሚያገለግል ” ተወዳጅ” አስተሳሰብ ሆኖ ተገኝቷል- በአንባገነኖች ዘንድ። አቶ መለስም ይህን ሃሳብ መነሻ አድርገው ” ዲሞክራሲና ልማት ግንኙነት የላቸውም” የሚል የመመረቂያ ጽሁፍ መጻፋቸውን ሰምቻለሁ፣ ባላነበውም። የኖቤል ተሸላሚው አማርትያ ሴን የነጻነትና የልማት ግንኙነቶችን የሚያሳይ ውብ መጽሃፍ ባይጽፉ ኖሮ ፣ “ልማት ያለነጻነት ዋጋ የለውም” እያልን የምንጮኸውን ጩኸት ትንሽም ቢሆን የሚሰማን አናገኝም ነበር። እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በዘር ተደራጅተው አገር ከሚመሩት መንግስታት በስተቀር ዛሬ አብዛኛው አለም፣ ነጻነት ለልማት አስፈላጊ መሆኑን ይቀበላል። የእስያ ነብሮች ያደጉት ከነጻነት በፊት ልማትን ስላስቀደሙ ነው የሚለው መከራከሪያም ብዙ አሳማኝ ሆኖ አልተገኘም፤ የእስያ ነብሮች እድገት የራሱ የሆኑ ብዙ ፖለቲካዊና ስትራቴጂካዊ ምክንያቶች አሉት። በተለይ ስለ ቀጣይ እደገት (sustainable development) ስናስብ፣ ነጻነት እጅግ አስፈላጊ ነገር መሆኑን ከአረብ አገራት አብዮትና ውድመት ተምረናል። ነጻነት ከሌለ ዘላቂና ለትውልድ የሚተላለፍ ልማት አይኖርም፤ ዛሬ የተጀመረው ልማት ነገ ለነጻነት በሚደረግ ትግል የሚወድምበት አጋጣሚ ከፍተኛ ነው። ለዚህ ደግሞ ሊቢያ፣ ሶሪያና ግብጽ ምስክሮች ናቸው። ቻይናም ቢሆን ፖለቲካዊ ለውጥ ካላደረገች እጣፋንታዋ መስቅልቅ ነው።

    “ከነጻነት በፊት ልማትን እናስቀድም” የሚሉ አምባገነን መንግስታት፣ ልማት በእነሱ ብቻ እንደሚመጣና እነሱ ከሌሉ ልማቱ እንደሚደናቀፍ በማስወራት እድሜ ልክ በዙፋኑ ላይ ለመቀመጥ ያልማሉ። ይህን ህልማቸውን እውን ለማድረግም ” አሳማኝ የሚመስሉ” የኢኮኖሚ ትንተናዎችንም ያቀርባሉ። ከእነዚህ ትንተናዎች አንዱ ይህን ይመስላል ፦ “የካፒታሊዝም ስርአት ለሰዎች ኑሮ መሻሻል አስፈላጊ ነው። ስርአቱ እውን ይሆን ዘንድ ደግሞ ካፒታሊስቶችን በብዛት ማፍራት አስፈላጊ ነው። ካፒታሊስቶች ሀብት እንዲያጠራቅሙ ደግሞ ሰራተኛው የደሞዝና ሌሎች ጥቅማጥቅሞችን መጠየቅ የለበትም። ባለሀብቱ ሃብት ማጠራቀም ከቻለ፣ አዳዲስ ግንባታዎች ይካሄዳሉ፣ ብዙ ሰራተኞችም ይቀጠራሉ። እድገትም ይኖራል፣ ሁሉም ተያይዞ ያልፍለታል። መንግስትም ቢሆን የህዝቡን ፍላጎት አሟላለሁ ብሎ ባለሃብቶች ብዙ ቀረጥ እንዲከፍሉ ማስገደድ የለበትም። የህዝቡን ጥያቄ ለመመለስ ሲል ባለሀብቱን ብዙ ግብር ማስገበሩ አይቀርምና የህዝቡን ጥያቄ ለጊዜው ገሸሽ ያድርግ።” አስተሳሰቡ በአጭሩ “ታገሱ፣ ይህኛው ትውልድ ባያልፍለት የሚቀጥለው ትውልድ ያልፍለታል።” የሚል ነው።

    በዚህ ንድፈ-ሀሳብ መሰረት የመብትና የኢኮኖሚ ጥያቄዎችን “ያለጊዜው” መጠየቅ ጎጂ ነው፤ ህዝቡ በችግር ብዛት ቢያልቅም የሚጠበቅ ነው። መንግስት የስራ ማቆም አድማዎችንና ሌሎች የመብት ጥያቄዎችን በሃይል ለመጨፍለቅ ጦሩን ቢሰብቅና ዜጎች ቢሞቱ ለካፒታሊዝም ግንባታ እስከሆነ ድረስ የተቀደሰ እርምጃ ነው። አስተሳሰቡ ኢኮኖሚውን ነጻ ፖለቲካውን እዝ የሚያደርግ፣ “ፖለቲካው ኮሚኒዝም- ኢኮኖሚው ካፒታሊዝም” ነው።

    ይህን አስተሳሰብ ወደ አገራችን ነባራዊ ሁኔታ እናምጣ እንየው። “ባለሀብቱ ሀብት ያጠራቅም ዘንድ መታገስ አስፈላጊ ነው” የሚለው ምክር አሳማኝ ነው እንበል። ይሄ ትውልድ ተበድሎ የሚቀጥለው ትውልድ ይለፍለት የሚለውም አርበኝነት ነው እንበልና እንቀበለው። ነገር ግን ይህን አስተሳሰብ በአገራችን ተግባራዊ ብናደርገው የሚፈለገውን ውጤት እናመጣለን ወይ? ብለን ስንጠይቅ ፣ የምናገኘው መልስ አሉታዊ ይሆናል። እነሆ ምክንያቶቹ-

    በቅድሚያ በእኛ አገር ሃብት እንዲያጠራቅሙ ስርአቱ የሚንከባከባቸው አዲስ-ሰዎች በአብዛኛው ከአንድ አካባቢ የመጡ ወይም የአንድ ብሄር አባላት ናቸው። እነሱ ሃብት እስኪያጠራቅሙ ሌላው ህዝብ እንዲሞት መፍረድ ከሞራል አኳያ ተቀባይነት አይኖረውም። እነሱ ብቻ ካፒታሊስቶች እንዲሆኑና ኢኮኖሚውን እንዲቆጣጠሩት ከፈቀድን ሌላው ህዝብ በባርነት ስር እንዲኖር እየፈረድንበት ነው። ኢኮኖሚውን እነሱ ብቻ ከተቆጣጠሩት ፖለቲካውንም መቆጣጠር አይሳናቸውም። ደቡብ አፍሪካ በኢትዮጵያችን ትመሰረታለች፤ ልዩነት ቢኖር የካፒታሊስቶቹ ቀለም ብቻ ነው።

    “ግደየለም እነሱም የእኛው ሰዎች ናቸው” ብለን ብንተዋቸው እንኳ ፣ የአገር ፍቅር ስሜት አልባነታቸው ፈቅደን እንዳንገዛላቸው ያደርገናል። እነዚህ አዳዲስ ካፒታሊስቶች ገንዘባቸውን በአገር ውስጥ ባንክ አያስቀምጡም፣ ፋብሪካ ከሚገነቡ ህንጻ ቢቀጣጥሉ ይመርጣሉ፤ ህንጻ ሲሰራ እንጅ ከተጠናቀቀ በሁዋላ ብዙ ሰው አይቀጥርም። ግሎባል ፋይናንሻል ኢንቴግሪቲ 11 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የአገሪቱ ገንዘብ በውጭ ባንኮች መቀመጡን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። ይህ ሃብት የማን ነው? ተከድኖ ይብሰል። ነገር ግን እነዚህ ባለሃብቶች የአገር ፍቅር ስሜት እንደሌላቸው በደንብ ያሳያል።

    የእኛ አዲሶቹ ባለሃብቶች ጉራና ልታይ ልታይ ማለትን ይወዳሉ። ደሃው እየደማ በሚያገኙት ገንዘብ አንድ ጠርሙስ ውስኪ እስከ 30 ሺ ብር እየገዙ ይራጬቡታል፤ ፈረንጆች እንኳ ለመያዝ የማይደፍሩትን ዘመናዊ መኪኖችን እያሽከረከሩ በሚሞትላቸው ህዝብ ላይ ይንደላቀቁበታል። ለጎራ ካልሆነ ሃመር መኪና በእግሩ በሚሄድ ህዝብ መሃል ምን ይሰራል? የሆላንድ ባለሀብት እኩል እንደ ነዋሪው ቅናሽ ሱቅ ውስጥ ገብቶ እቃ ይገዛል፣ ሚሊኒየሩን ከሌላው ህዝብ መለየት አይቻልም። የእኛን አዳዲስ ባለሀብቶች ለመለየት በጣም ቀላል ነው። እነዚህ ባለሀብቶች ናቸው የነገውን ትውልድ ያሳልፉለታል ተብሎ የሚጠበቀው።
    ከሁሉም በላይ እነዚህ አዳዲስ ባለሀብቶች ገንዘብ የሚያጠራቅሙት የመንግስትን ስልጣን ይዘው እንጅ ሰርተው፣ ለፍተው፣ በእኩልና በፍትሃዊ መንገድ ተወዳድረው አይደለም። የሃብት ምንጭ የሆነውን መሬት እንደልብ እያገኙ፣ ከታክስ ነጻ እቃዎችን እያስገቡ፣ ተቀናቃኞቻቸውን በተንኮል ከገበያ እያስወጡ ነው የከበሩት።

    ከእነዚህ ባለሀብቶች ውጭ ያለው ዋና ካፒታሊስት ( ባለሀብት) ደግሞ መንግስት ነው። በኢትዮጵያ እንዲያውም ዋናው ኢንቨስተር መንግስት ነው። መንግስት መሬትና ፋብሪካዎችን እየጨሸ የሚሰበስበውን ገንዘብ ከላይ ያሉት ቁንጮዎች ይመዘብሩታል። ከዝርፍያ የተረፈው ገንዘብ ለድሃው የኑሮ መደጎሚያ ይዋል ሲባልም ጦርነት ይሰበቃል። መንግስት ሃብት እስኪያጠራቅም ጥያቄዎችን ከመጠየቅ ታገሱ የሚባል ነገር ተቀባይነት የለውም ። መንግስት ሲደኸይና ዜጎች ሲበለጽጉ እንጅ ተቀራኒው ከተፈጠረ አደጋ ይኖራል።

    አሁን ያሉት አዲሶቹ ባለሀብቶችም ሆኑ አሁን ያለው መንግስት የሚቀጥለውን ትውልድ ህይወት መለወጥ የሚችሉ አይደሉም። ባለሀብቶች ሃብት ሲያጠራቅሙ ለድሃው ተንጠባጥቦ ይደርሰዋል የሚለው የ trickle-down የኢኮኖሚ አስተሳሰብ ለአሁኑዋ አገራችን አይሰራም፤ ምክንያቱም ያሉን ባለሀብቶችና መንግስት በድሃው ላይ የሚዘምቱ እንጅ ለድሃው የሚቆሙ አይደሉም። ጤነኛ ካፒታሊዝም በጤነኛ ከፒታሊስቶች ይገነባል፣ ጤነኛ ካፒታሊስት ባይኖርም፣ አገር ወዳድ ካፒታሊስት ግን አለ። የእኛዎቹ፣ ከመንግስት ጀምሮ ጤነኞችም አገር ወዳዶችም አይደሉም።
    ደሃው ኢትዮጵያዊ ዛሬ ለመብቱእና ለማህበራዊ አግልግሎት መሻሻል ካልተነሳ፣ ነገ በህይወትም ላይኖር ይችላል።

    ስደመድመው – “የዛሬው ትውልድ ተበድሎ የነገው ትውልድ ይለፍለት” የሚለው አስተሳሰብ አሁን ባለው የአገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ፈጽሞ የማይሰራ ፣ ሰዎች ለነጻነታቸውና ለመብታቸው እንዳይነሱ የሚያዘናጋ እንዲሁም የአንድን በዘር ላይ የተመሰረተ ስርዓት ቀጣይ ህልውና ለማረጋገጥ ተብሎ የሚነዛ አደገኛ አስተሳሰብ በመሆኑ፣ ዜጎች በዚህ አስተሳሰብ ሳይዘናጉ ዛሬውኑ ለመብታቸው መከበር መነሳት አለባቸው- ነገን ስንጠብቅ ዛሬ እንዳንሞት እንጠንቀቅ።

    በአትላንታ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን በአዋሳ፣ በደንቬር የሚኖሩ ደግሞ በደሴ ለሚደረጉት የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነትና ለፍትህ እንቅስቃሴዎች የሚያስፈልግትን ወጭዎች ሙሉ ለሙሉ እንደሚሸፍኑ ማረጋገጣቸውን ፣ የሰሜን አሜሪካ የአንድነት ድጋፍ ማህበራት፣ ሸንጎን እና የሽግግር ምክር ቤቱን ያሳተፈው የሚሊዮኖች ድምጽ የዳያስፖራ ግብረ ኃይል ገለጸ። የመጀመሪያዉን የአዲስ አበባ እንቅስቃሴን ላስ ቬጋሶች፣ በድረደዋ ከተማ የሚደረገዉን የደብተራዉ ፓልቶክ ክፍል ፣ የቁጫ ከተማ ደግሞ […]

    ለለውጡ ዝግጅት ያስፈልጋል! እንዲህም ተብሏል ለውጥን ማዘግየት ይቻል እንደሆን እንጂ ገድቦ ማስቀረት እንደማይቻል ከትርክት አልፎ በተግባር የታየ ሀቅ ነው፡፡ በተለይ ህዝባዊ የለውጥ እንቅስቃሴን አፍኖ መዝለቅ የማያዛልቅ ሙከራ እንደሆነ በተለያየ ጊዜ በተለያዩ ሀገራት ታይቷል፡፡ በዓለም ላይ የማይለወጥ ነገር አለ ከተባለ ራሱ ለውጥ ነው የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የነበሩት ጆን ኦፍ ኬኔዲ ‹‹እነዚያ ሰላማዊ ለውጥን የማይቻል […]

    የሀገራችን የተቃውሞ ፖለቲካ ወደ አንድ ጠንካራ የለውጥ አማራጭነት እንዲሰባሰብ እና ገዥውን ፓርቲ የሚገዳደር ወሳኝ ኃይል ሆኖ እንዲወጣ ማስቻል የብዙ ቀናት አሳቢ ኢትዮጵያውያን ፍላጎት እንደሆነ ይሰማኛል። እኔም ራሴን ይህ ዓላማ ከፍፃሜ እንዲደርስ ከሚፈልጉ ወገኖች ውስጥ እንደ አንዱ በማድረግ እቆጥረዋለሁ። ውህደት እንዲኖር መፈለግ አንድ ነገር ሆኖ፤ ማን ከማን ጋር ነው የሚወሃደው? የውህደት መስፈርቱን ምን መሆን ይኖርበታል? የሚለውንም […]

    ለፍጥረተ ዓለም(ዩኒቨርስ)መከሠት ፤ መገኘት ፤ መዘርጋት– መንስዔ ነው ተብሎ የሚጠቀሰው «ታላቁ ፍንዳታ» (BIG BANG) ከ 14 ቢሊዮን ዓመት ገደማ በፊት ማጋጠሙን የሚጠቁም መረጃ በምርምር አግኝተናል ሲል አንድ የጠፈር ሳይንቲስቶች በድን ከወዲያኛው ሳምንት መግለጹ የሚታወስ ነው።

    በዓለም ላይ ቁጥራቸው ከአንድ ቢሊዮን የሚበልጥ አካል ጉዳተኞች አሉ ። አብዛኛዎቹም በማደግ ላይ ባሉ ሃገራት ውስጥ ነው የሚኖሩት ። በተለይ በአፍሪቃ አካል ጉዳተኞች ብዙውን ጊዜ አድልዎና መገለል የሚደርስባቸው ሲሆን ብዙዎቹም ስር በሰደደ ድህነት ውስጥ ነው ያሉት ።

    የአሸባሪዎች ጥቃት፣ የሐይማኖት ግጭት እና ሙስና ባልተለያት ናይጄሪያ በኢኮኖሚ ከፍተኛ እድገት በማስመዝገብ ላይ እንደሆነች ነው የሚነገረው። ይህ እዕን ከሆነ ደግሞ በነዳጅ ዘይት ሀብታም የሆነችው ናይጄሪያ በቅርቡ በኢኮኖሚ እድገቷ ከአፍሪቃ አንደኛ ከሆነችው ደቡብ አፍሪቃ መቅደሟ አይቀሬ ነው።

    የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ በአዉሮጳ የሚያደርጉትን ጉብኝት ቀጥሎ ዛሬ ብራስል ቤልጅግ ይገኛሉ። በብራስልስ ከአዉሮጳ ኅብረት መሪዎች ጋ ካደረጉት ዉይይት በኋላም ከሰዓት በኋላ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

    ነገረ ኢትዮጵያ ቁጥር – 5 ቁልፍ አገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮችን ይዛ እነሆ በ PDF ያንብቧት

    – መዝሙረ ኢህአዴግ!
    (በላይ ማናዬ)

    – የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ከአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት በተደረገላቸው ግብዣ ወደ አሜሪካ ያመራሉ፡፡ በጉዞው ዓላማና በተለያዩ የአገራችን ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡

    – ኢትዮጵያና የዩክሬኑ ግጥምጥሞሽ
    ባለ ቀለሙን አብዮት ማን ይመራዋል?
    (በጌታቸው ሺፈራው)

    – አዲስ ጠብመንጃ በምንሽር፤
    አገዳደሉ ሆድ የሚያሽር፡፡
    (በዝክረ ታሪክ አምድ፡- አቶ ታዲዎስ ታንቱ)

    – “የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት ዘመቻ”
    (ግርማ ሞገስ)

    – ኑሮ ሆነብን እሮሮ
    (ጋሻው መርሻ)

    – የኢትዮጵያ ፖለቲካና የሴቶች ተሳትፎ
    (ኤልሳቤት ወሰኔ)

    – ሰላማዊ ትግሉ መሪዎቹን ይሻል
    (ታምራት ታረቀኝ)

    – ኢትዮጵያዊነት ለእኔ!
    (አፈወርቅ በደዊ)

    – እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ ፕሮግራሞች የሚተዋወቁበት ገጽ አለልዎት

    መልካም ንባብ !

    Image

    ታላቁን ገመና የደበቀው የ“የንጉሡ ገመና”
    የመጽሐፉ ርዕስ – የንጉሡ ገመና
    የገጽ ብዛት – የ172
    የታተመበት ዘመን – 2006 ዓ.ም
    የሽፋን ዋጋ – ብር 49.75
    አሳታሚ – ግርማ ለማ
    የመጽሐፉ ይዘት ከታሪክ ዘውግ የሚመደብ ሆኖ አሳታሚው ሁለት ምንጮችን ተጠቅመው ነው ያሳተሙት፤ እነሱም ለ14 ዓመታት በንጉሥ አሽከርነት ያገለገሉት የአቶ ሥዩም ጣሰው መንዜው የግል ማስታወሻና የልዩ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ጽ/ቤት ቀይ ሽብርን አስመልክቶ ያሳተመው “ደም ያዘለ ዶሴ” የተሰኙ መፃሕፍት ናቸው፡፡
    በተለይ አቶ ሥዩም ከልጅነታቸው ጀምረው በቤተመንግሥት ያደጉና ለድፍን 14 ዓመታት በንጉሡ አሽከርነትና አልባሽነት ያገለገሉ በመሆናቸው የንጉሠ ነገሥቱን ጓዳ ጐድጓዳ፤ የአሽከሮችን፣ የደንገጡሮችንና የወቅቱን ባለሥልጣናት ጠቅላላ ሁኔታ የማየት ብቻ ሳይሆን የማወቅ ዕድሉ ስለነበራቸው ማስታወሻቸው ተአማኒነት ይኖረዋል። አቶ ሥዩም ንጉሠ ነገሥቱ ሥልጣናቸውን ተቀምተው መጀመሪያ በቤተመንግሥታቸው ቀጥሎም በ4ኛ ክፍለ ጦር እስረኛ እስከሆኑበት ድረስ ንጉሡን በታማኝነት አገልግለዋል፤ በደርግ ዘመን እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ኖረው ኢህአዴግ ሲገባ በቁጥጥር ስር መዋላቸውና ከጠባቂዎች አምልጠው ራሳቸውን ማጥፋታቸው ይነገራል፡፡ ወደ መጽሐፉ እንመለስ፡፡
    አሳታሚው ግርማ ለማ፤ በምስጋና ገጹ ላይ የጽሑፉን ዋና ቅጅ (ኦሪጅናል) የሰጠው “በያን ናስር” የተባለ ሰው መሆኑን ጠቅሷል፤ ግን በያን የሥዩምን ጽሑፍ እንዴት እንዳገኘው ወይም የሥዩም ወኪል ይሁን፤ የገለጠልን ነገር የለም፤ የተገኘበት መንገድ ቢጠቀስ በጣም ጥሩ ነበር፡፡ ምክንያቱም ሥዩም የሞተው በድንገት ነው፤ የተያዘውም ሳያስበው ቤቱ በታጣቂዎች ተከቦ ነው፡፡ ስለዚህ ሃሳባችንን ወደአልተፈለገ ጥርጣሬ እንዳያመራን ግርማ ረቂቁን እንዴት እንዳገኘው ቢገልጥልን መልካም ነበር፡፡ የተጻፈልን ታሪክ ነዋ! ታሪክ ያለአስተማማኝ ማስረጃ ሊታሰብም ሊጻፍም እጅግ ይከብዳል፡፡
    መጽሐፉ የምስጋናና የመግቢያ ገጾችን ሳይጨምር፣ በዘጠኝ ምዕራፎች የተዋቀረ ነው፡፡ ስምንቱ ከስዩም ጣሰው ማስታወሻ የተወሰዱ ሲሆን ዘጠነኛው ምዕራፍ “ደም ያዘለ ዶሴ” ከተባለው መጽሐፍ የተገለበጠ ነው፡፡
    የመጽሐፉ ጠንካራ ጐኖች
    መጽሐፉ በንጉሡ ጓዳና ቢሮ ውስጥ ስለነበረው እውነት የገለጠልን በመሆኑ፣ የንጉሠ ነገሥቱን አጠቃላይ ሰብዕና ለሚያጠና ሰው ትልቅ የታሪክ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ ንጉሡ በካህናትና ባለሥልጣናት ዘንድ ተፈርተው ይከበሩ ስለነበር፣ ድምሩ ህዝብም አባቱን እየተወ “ኃይለሥላሴ ይሙት” በማለት በስማቸው ይምልና ይገዘት ነበር፡፡ ግን እንደ ሥዩም ጣሰው ጓዳቸውን ገብቶ የማየት ዕድል ቢገጥመው ኖሮ ምን ያህል ሲታለል እንደኖረ ይገባውና ከልቡ ይቆጭ ነበር ያሰኛል፡፡ ለማንኛውም የመጽሐፉን ጠንካራ ጐኖች በአምስት ከፍያቸዋለሁ፡፡
    ገመና አንድ
    ንጉሡ ተደባዳቢ ነበሩ
    ንጉሡ አሽከሮቻቸውን ይደበድቡ ነበር፤ “…የፀጉር ቅባት ፓንተን ሳቀርብላቸው ቀና አሉ፤ አዩኝ፡፡ አሰቡ አሰቡና ‘ማታ ማነው ፍራፍሬውን የደገሰው’ ብለው ጠየቁኝ፡፡ እኔም ራሴ መሆኔን ነገርኋቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ብድግ አሉና ተያያዙኝ፡፡ እስከሚደክማቸው ድረስ ደበደቡኝና ቁጭ ብለው ፀጉራቸውን አበጠሩ፡፡ ክራባታቸውን አሰሩና ተነሱ። ልብሳቸውን ለብሰው ሲጨርሱ ጠሩኝ፡፡ እኔም አቀርቅሬ ተጠጋሁ፡፡ አስጐነበሱና እስከሚበቃቸው ወገሩኝና እየተሳደቡ ወደ ቁርሳቸው ሄዱ” (ገፅ 11-12)
    ይህን አይነት እርግጫና ጥፊ ለሥዩም አዲስ አልነበረም፤ በየጊዜው ይገረፋል፤ የስድብ ውርጅብኝ ይዘንብበታል፡፡ ሁለት ቀን ብቻ ከተገረፈ በኋላ ብር እንዲሰጠው አድርገዋል፤ ይህ አንድም ምሥጢራቸው እንዳይወጣ ማባባያ ነው፡፡ አለዚያም ካሣ ነው ማለት ይቻላል፡፡
    ሆኖም የሥዩም (አሽከርና የታሪኩ ፀሐፊ መሆኑን አንዘንጋ) ትልቁ ፈተና ከንጉሡ ዱላ ይልቅ የሴት አሽከሮች በእሱ ላይ ማደምና ከባለሥልጣናት ጥርስ ውስጥ ማስገባት ነበር ትልቁ ፈተና የሆነው። ለዚያ ሁሉ እርግጫ፣ ጥፊና ዱላ ሰበቡ ንጉሡ የገረዶችንና የአሽከሮችን ወሬ ስለሚሰሙ ነው፡፡ (ገፅ 14)
    ንጉሡ ወሬ ይወዳሉ፤ የሆነ ያልሆነን ሁሉ የሚቀላምድላቸውን ሰው ያስጠሩትና ምንም ሳያጣሩ የተወራበትን ሰው ራሳቸው ይገርፋሉ፤ ካስፈለገም ግዞት ይልካሉ፡፡ (ገፅ 21 እና 24)
    ገመና ሁለት
    ንጉሡ ሴሰኛ ነበሩ
    ንጉሡ ሴት በጣም አብዝተው ይወዱ ነበር፤ በዚህ የተነሳ ከጽዳት ሠራተኞች፤ ከአበሻ ወጥ ቤቶች፣ ከእንጀራ ጋጋሪዎች፣ ከቅንጬ ቤቶች፣ ከሴተኛ አዳሪዎች፣ ከሆስተስና ከባለ ትዳር ሴቶች ጋር ይቀብጡ ነበር፡፡ “ሴቶቹ አብዛኛውን ጊዜ የሚገቡት ቀን ከምሳ መልስ እረፍት በሚያደርጉበት ጊዜ ከ8-10፡30 ባለው ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ ጃንሆይ ገብተው ከተኙ በኋላ ትንሽ ቆይተው ደወል ይደውላሉ፡፡ በዚያ ጊዜ በዚህ ነገር የተለየ ባለሟል የሆኑ አሽከሮች በተራቸው ይገቡና “ዕገሊትን ጥራ” ሲባል ይጠራል፡፡ ምን አልባት እርሱ ከተጠራችው ሴት ጋር ሽርክና ከሌለው ወይም ከምትወስደው ገንዘብ በብዛት ካላካፈለችው “እርሷ አሁን የለችም” በማለት የርሱ ሽርክ በየጊዜው ብዙ ገንዘብ የምትሰጠውን ሴት “ዕገሊት አለች፤ እርሷ ከሥራዋ ላይ አትጠፋም” በማለት ይቀላምድና ይጠራል፡፡ ሲገቡና ሲወጡ የተለየ ጥንቃቄ ይደረጋል፡፡ ነገር ግን ሴቶቹ በሚያሳዩት መለዋወጥ የተቀረው ሰው እዚያ ቦታ እንደደረሰች ይገባዋል” (ገፅ 51)
    “ቢሮ የሚደረገው ደሞ ሌላ ነው፤ ቢሮ በሚሠሩበት ጊዜ ረፈድ ሲልና አንዳንድ ባለሥልጣኖችን ካነጋገሩ በኋላ ገለል ብለው ቢሮ አጠገብ ካለው መኝታ ቤት ጐራ ይላሉ፡፡ ከዚያም በዚያ አካባቢ ከሚሠሩት ሴቶች ውስጥ የፈለጓትን አስጠርተው ትንሽ ከተጨዋወቱ በኋላ ወደ ቢሮአቸው ይገባሉ፡፡ …ሆስቴሶችንና ሌሎችን ደግሞ እምድር ቤት ካለው ቢሮ ነው የሚያገኙአቸው” (ገፅ 51)
    ይህ ሁሉ ሲሆን እንደየሴቶቹ የንቃት መጠን ዛቅ ያለ ገንዘብ ይከፈላቸዋል፤ ከሥራ ቤት፣ እንጀራ ቤትና ወጥ ቤት ለሚመጡት ሴቶች የሚከፈላቸው አነስተኛ ገንዘብ ሲሆን ለጽዳት ሠራተኞችና ለሌሎች ሴቶች ግን ከ70-80 ሺህ ብር ይከፍሉ ነበር፡፡ ሴቶቹ ደግሞ ወደ ንጉሡ ላቀረባቸው ሰው (ደላላው) ከ5-10 ሺህ ብር ቀረጥ የመክፈል ግዴታ ነበረባቸው። በዚህ የተነሳ ከንጉሡ ጋር የተገናኙ ሴቶች ሁሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ቆንጆ ቪላና ዘመናዊ መኪና ይገዙ ነበር፡፡ ቀስ በቀስ እንዲያውም ፖለቲካዊ ሥልጣኑን ተቆጣጥረው የፈለጉትን ያስሾሙ ያስሸልሙ፤ የጠሉትን ደግሞ ያሰቃዩት ነበር (ገፅ 51)
    አንዳንድ የንጉሡ ውሽሞች በጣም ቀበጦች ስለነበሩ በመንግሥት ወጭ፣ አስተርጓሚ ጭምር ተመድቦላቸው ለሽርሽር ፈረንጅ አገር ይሄዱ ነበር። በጣም የሚያሳዝነው ግን ንጉሡ የባለቤታቸውን የዕቴጌ መነን አስፋውን ጌጣጌጥ ሳይቀር ለውሽሞቻቸው መስጠታቸው ነው፡፡ ለአንዳንድ ውሽሞቻቸውም ቋሚ ደሞዝ ተቆርጦላቸው የቤተ መንግሥት አሽከሮች በየወሩ እቤታቸው ድረስ እየሄዱ ይከፍሉ ነበር፡፡ (ገፅ 56)
    ይህ ድርጊት ያንገበገበው ሥዩም “ኢትዮጵያ በተለይ ከ1960 ዓ.ም ጀምሮ ስትገዛ የኖረችው በንጉሠ ነገሥቱ ሳይሆን በእልፍኝ አስከልካዮች፣ በጥቂት የእልፍኝ አሽከሮችና በገረዶች ነበር፡፡ …ቤተመንግሥቱ ቤተመንግሥት መሆኑ ቀርቶ ፍጹም የሰይጣን ቤት ሆኖ ነበረ” ሲል ትዝብቱን አስፍሯል። (ገፅ 20)
    ገመና ሶስት
    ንጉሡ አይጾሙም ነበር
    ንጉሡ አክሱም ጽዮንንና ሌሎች አብያተ ክርስቲያናትን ስለአሠሩ ካህናት ያወድሷቸዋል፤ ይሰግዱላቸዋል፡፡ “አቤቱ ፍርድን ለንጉሣችን ስጠው” እያሉም ዘወትር ይፀልያሉ፤ እንደ ጻድቃንና ሰማዕታት በመቁጠርም መልክአ ኃይለሥላሴ ደርሰውላቸው ነበር፡፡ ሆኖም ንጉሡ የክርስቲያንን ህግና ሥርዓት በመጣስ፣ አርብና ረቡዕን እንዲሁም ሌሎች አጽዋማትን አይጾሙም ነበር፡፡ (ገጽ 25 እና 34)
    ገመና አራት
    ንጉሡ ጠንካራ ሰራተኞችንና ታማኞችን አይወዱም ነበር
    “ግርማዊነታቸው የሚወዱት ሰው ፈጣን፣ አጭበርባሪ፣ አሳባቂ፣ በዕውቀት ያልበሰለ፣ እርሳቸውን አምታቶ የሚያታልላቸውን ሰው በጣም ይወዱታል፡፡ የጥቅም ተካፋዮቻቸው በሙሉ በዕውቀት ያልበሰሉ፣ የሰውን መብት በፍጹም ያልተረዱ፣ ሰውን ሸጠው ለመክበር ብቻ ጽኑዕ ዓላማ ያላቸው፣ ለኔ እንጂ ለኛ የሚል መንፈስ ፈጽሞ የሌላቸው ጨካኞች፣ ሰው በችግር ሲሰቃይ ሲያዩ ከማዘን ይልቅ መደሰትን የሚመርጡ ከንቱዎች ናቸው፡፡
    “ግርማዊነታቸው አጥብቀው የሚጠሉት ሰው እውነትን በጣም አድርጐ የሚወድ፣ ዘወትር የሚከራከራቸው፣ በእውነት ፍጹም በሆነ መንገድ የሚወዳቸው፣ ሲዋሹ የሚያስተባብላቸው፣ የሚታሙበትን ነገር እንዲተው የሚነግራቸው፣ የማይንቀዠቀዥ፣ አዋቂ ሰው በፍጹም አይወዱም” (ገፅ 31) ይለናል፤ ሥዩም በ14 ዓመት የአሽከርነት ዘመኑ የታዘበውን ሲያካፍለን፡፡
    ገመና አምስት
    ንጉሡ ስስታም ነበሩ
    ንጉሠ ነገሥቱ ኢትዮጵያን የምታክል ታላቅ አገርና እጅግ ብዙ ህዝብ የመግዛታቸውን ያህል ስስታቸውም ያን ያህል አሳፋሪ እንደነበር በመጽሐፉ ላይ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል፡፡ በልጅነት ዘመናችን የምናውቃቸው ንጉሥ፤ በየቦታው ሲዘዋወሩ ብር እንደጥሬ እየበተኑ የሚሄዱ መሆናቸውን ነበር፡፡
    ሥዩም የሚያውቀውን እውነት ሲነግረን ግን ስስታቸው በጣም የወረደና ለማመን የሚያስቸግር ሆኖ እናገኘዋለን “…በተለይ ከኬኩ ትንሽ በቄንጠኛ አኳኋን ቆርሰው ከበሉ በኋላ በምልክት አድርገው በጥንቃቄ እንዲቀመጥ ይናገራሉ፡፡ በማግስቱ ሲመጣ ትንሽ ለውጥ ከታየበት “ማነው የተጫወተበት” በማለት ማሰቃየት ነው፡፡ አንድ ኬክ ከሶስት እስከ አምስት ቀን ድረስ እየተመላለሰ ይቀርባል፡፡ ለምሳሌ ሐሙስ ቀን ተጀምሮ እንደሆነና ቅዳሜ ደብረዘይት ቢሄዱ አብሮ ይሄዳል፤ ማሩንም በጣም አድርገው ይቆጣጠራሉ፡፡ ከማስቀመጫው ብልቃጥ ውስጥ ትንሽ ጐድሎ ያገኙት እንደሆነ “እንደፈለጋችሁ ትጫወቱበታላችሁ” ብለው መለብለብ ነው” (ገፅ 33) ሲል ያየውን ትዝብት ያካፍለናል፡፡
    ከዚህ ሌላ መኝታ ቤታቸው በስጦታ ዕቃዎች፣ በቸኮላት፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ስለሚሞላ ዕቃ ቤት ይመስል ነበር፤ እንዲያውም አትክልትና ፍራፍሬው፤ እንዲሁም ቸኮላትና ኬኩ እየተበላሸ የመኝታ ቤታቸውን ሽታ ያበላሸው ነበር፡፡ (47፣ 116፣ 117)
    ከመጽሐፉ ውስጥ በጣም የገረመኝ ቢኖር (ገፅ 149) ቀኛዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ ከ1963 ዓ.ም ጀምሮ ለንጉሡ ልክ “ልዩ ካቢኔ” ይባል እንደነበረው የስለላ ተቋም፣ በየቀኑ ለንጉሡ ደብዳቤ ይልኩ የነበሩ መሆናቸው ነው፤ ለመሆኑ ቀኛዝማች ተሥፋን ከንጉሡ ጋር ያውም በየቀኑ የሚያገናኛቸው ምን ብርቱ ምሥጢር ነበር ይሆን እንድል አድርጐኛል፡፡
    የመጽሐፉ ድክመት
    መጽሐፉ ከላይ በመጠኑም ቢሆን የነካካኋቸውን ጉዳዮች የዓይን ዕማኙን ሥዩም ጣሰውን ዋቢ አድርጐ የመቅረቡን ያህል ሌላ ድክመት እንዳለበትም መዘንጋት አያሻም፡፡
    አሳታሚው በመግቢያው ላይ “አሽከር ሥዩም (አፈሩን ገለባ ያድርግለትና) በሰነዱ ውስጥ ጽሑፉን ለንባብ ሳያበቃው እንዳይሞት አምላኩን የተማጸነበት ፀሎት አለ” ብሎናል፡፡ ግን ይህንን ከሰነዱ ውስጥ አናገኘውም፡፡ ይህ የሚያሳየን የሥዩም ሰነድ የተነካካ ወይም የተቆራረጠ ፍሬ ነገር አለው ማለት ነው፤ ይህ ከሆነ ደግሞ ፍጹም ስህተት ነው፡፡ አንድ አካል ሲቆረጥ ሌላውን ምሉዕ እንደማያደርገው ሁሉ የሥዩም ጽሑፍም የቋንቋ አርትኦት ብቻ ተደርጐለት መታተም ነበረበት፡፡
    ሌላው ከወሲብ፣ ከንዋይና ከሃይማኖታዊ ገመናቸው ይልቅ የንጉሱ ፖለቲካዊ ገመና ቢታከል ኖሮ ጽሑፉን ተወዳጅ ያደርገው ነበር፤ ሰዎችን በምሥጢር መግደልና ማስገደል፣ በፍርድ አካባቢ የነበረው ሸር ሁሉ ሊገለጽ በተገባ ነበር፡፡ ይህን አይነቱን ታላቅ ገመና ሥዩም ሳይነካካው አልቀረም፤ ግን በመጽሐፉ ላይ አናገኘውም፡፡ ይህ ደግሞ ታላቁንና ለ44 ዓመታት የኖሩበትን ገመና ምስጢር አድርጐብናል፡፡ ከገጽ 141 ጀምሮ እስከ ገጽ 172 ያለውና “ደም ያዘለ ዶሴ” ከሚለው መጽሐፍ እንዳለ ተገልብጦ የቀረበልንም የመጽሐፉ ትልቅ ድክመት ነው፡፡ እንደ ትርፍ አንጀት የተለጠፈውን 32 ገጽ ከዋናው መጽሐፍ “ደም ያዘለ ዶሴ” ላይ አንብበነዋል፤ እዚህ ላይ መደረቱ ለምን አስፈለገ?
    addis admass newspaper

    Image

    በአሜሪካ፣ በፈረንሳይና ቤልጂየም ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ነበራቸው
    የ25 ሚሊዮን ዶላር ባለፀጋ ነበሩ – ወደ ቢሊዬነርነት ተጠግተዋል
    ቤተ-መፅሃፋቸው ራሳቸው ባሰባሰቡት 10ሺ መፃህፍት የተሞላ ነበር

    በሳምንቱ ማጠናቀቂያ ግድም “ጮማ” የሆነ መረጃ እጄ ገባ፡፡ አንድ ወዳጅ ነው መረጃውን ከባህር ማዶ በኢሜይል ያሻገረልን፡፡ The New York Times የዛሬ 105 ዓመት፣ አፄ ምኒልክ ሲሞቱ ነው ዘገባውን ያወጣው – ኖቨምበር 7 ቀን 1909 ዓ.ም፡፡ “ንጉስ ምኒልክ እዚህ ኢንቨስትመንት አላቸው” በሚል ርዕስ የቀረበው ፅሁፍ፤ከአቢሲኒያ የተመለሰውን የቤልጂየም አሳሽ ባሮን ዲ ጃርልስበርግ ቃለመጠይቅ በማድረግ የተጠናቀረ እንደሆነ ኒውዮርክ ታይምስ ይገልፃል፡፡ የሚታወቁትን ታሪኮች እየዘለልኩ “ጮማ ጮማ” የሆኑትን መረጃዎች ነው የማቀብላችሁ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል ከመዘጋቱ በፊት በዚህ በአዲሱ የአፄ ምኒልክ ታሪክ ላይ ትንሽ ጥናትና ምርምር ቢያካሂድ ትክክለኛው ታሪክ (ያልተጭበረበረው ማለቴ ነው!) ለትውልድ ይሸጋገራል የሚል እምነት አለኝ፡፡ “የለም! የአፄ ምኒልክን ጉዳይ አጥንቼ ፋይሉን ዘግቻለሁ” የሚል ከሆነም እንዳሻው፡፡ የኒውዮርክ ታይምስ መረጃ ግን የሚያወላዳ ዓይነት አደለም፡፡ ለመሆኑ እኚህ የጥቁር ህዝብ ኩራት፣የአድዋ ጀግና—–አዳዲስ ገድሎች ምን ይሆኑ? (የተጭበረበርነው ታሪክ ማለት ነው!)
    ባሮን ዲ ጃርልስበርግ ለጋዜጣው እንደተናገረው፤ ምኒልክ ከሌሎች የአህጉሪቱ ነገስታት ጨርሶ የተለዩ መሪ ነበሩ፡፡ በዲፕሎማትነት፣ በኢንቨስተርነት (ፋይናንሰር)፣ በተዋጊነት የሚስተካከላቸው አልነበረም፡፡ በተዋጊነትና በዲፕሎማትነት ያላቸውን ብቃትና ዋጋ ያስመሰከሩት ጣልያን በአቢሲኒያዎች ድል በተነሳች ወቅት ነበር ይላል – ጃርልስበርግ። በመጨረሻዎቹ የንግስና ዘመናቸው ግን ምኒልክ ይበልጥ በኢንቨስትመንት እንቅስቃሴያቸው እንደታወቁ ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል፡፡
    የንግስና ዘውድ ከመድፋታቸው ቀደም ብሎ በወጣትነት ዘመናቸው የኢንቨስትመንት ዝንባሌ እንደነበራቸው የሚያስታውሰው ዘገባው፤በዚያ እድሜያቸው በፈረንሳይና ቤልጂየም የማዕድን ማምረቻዎች ውስጥ ቀላል የማይባል መዋዕለ ንዋይ አፍስሰው ነበር ይለናል፡፡ ከንግስናቸው በኋላ ግን አገር በማስተዳደር ሥራ በመወጠራቸው ከኢንቨስትመንቱ ተስተጓጉለው እንደነበር የኒውዮርክ ታይምስ ዘገባ ያመለክታል፡፡
    “ዛሬ የአቢሲኒያው ገዢ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴያቸውን ወደ ዩናይትድ ስቴትስ በማስፋፋት በአሜሪካ የባቡር ሃዲድ ሥራ ላይ ከፍተኛ የአክስዮን ድርሻ አላቸው” ሲል አሳሹ የንጉሱን ወቅታዊ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ገልጿል፡፡
    አፄ ምኒልክ በአሜሪካ እንዲሁም በፈረንሳይና ቤልጂየም ያላቸው አክስዮንና ኢንቨስትመንት ሲደማመር ከ25 ሚሊዮን ዶላር የማያንስ የግል ሃብት እንደነበራቸው ይገመታል ብሏል- አሳሹን ጠቅሶ የዘገበው ጋዜጣው፡፡
    “እኚህን ጥቁር የአቢሲኒያ ገዢ በተመለከተ በእጅጉ የሚያስደንቀው ጉዳይ ሁለ-ገብነታቸው ነው” ሲል የሚያደንቀው የቤልጂየሙ አሳሽ፤ንጉሱ የተዋጣላቸው ቋንቋ አዋቂ ነበሩ ይላል – ፈረንሳይኛ፣ እንግሊዝኛና ጣልያንኛ አቀላጥፈው ይናገሩ እንደነበር በመጥቀስ፡፡ ሁለመናቸውን ለአገራዊ ጉዳዮች ለመስጠት ቢገደዱም አዲስ የወጡ የአውሮፓ የስነጽሑፍ ስራዎችን ለመቃኘት ግን ጊዜ አያጡም የሚለው ጃርልስበርግ፤ ብዙ ጊዜ አዲስ የአውሮፓ ደራሲ ስም ሲጠቀስ እምብዛም አይደናገራቸውም ነበር ብሏል፡፡
    እሳቸውን ከሁሉም በላይ የሚያኮራቸው ራሳቸው ባሰባሰቧቸው 10ሺ መፃሕፍት የተደራጀው ቤተመፅሃፋቸው ሲሆን መፃህፍትን በተመለከተ ዋነኛ ትኩረታቸው በአፍሪካና በእስያ ጥንታዊ ስልጣኔዎች ላይ የሚያጠነጥኑ ሥራዎች ነበሩ ይላል – ለኒውዮርክ ታይምስ ምስክርነቱን የሰጠው ባሮን ዲ ጃርልስበርግ፡፡ ለካስ ምኒልክ ወደው አይደለም– ትምህርት፣ ቴክኖሎጂ፣ ሥልጣኔ፣ ዘመናዊ አስተዳደር ወዘተ—-ሲሉ የኖሩት፡፡ (የንጉሱን ታሪክ ተጭበርብረናል!?)

    addis admass amharic newspaper

    ምንሊክ ሳልሳዊ:- ሃገራችን ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢና አስጊ ስለሆነ ሕወሓት መራሹ ገዥው ፓርቲና አማካሪዎቹ ባለስልጣኖቹ ችግሩን ዓይተው መፍትሔ ካላስቀመጡ፣ አገርንና ሕዝብን በማስቀደምና በማሳተፍ ካልተንቀሳቀሱ አደጋ አለ፡፡ ያልታሰበና ያልተጠበቀ ግጭትና ችግር በአገራችን ውስጥ ብቅ ጥልቅ እያለ ነው::ኢትዮጵያ ደሃ አገር ናት ተብላ ትጠቀሳለች እንጂ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮች ተከፋፈሉ ተጣሉ፣ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ተከፋፈሉ ተጋጩ፣ የእስልምናና የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ተባሉ፣ ወዘተ የሚል አንሰማም ነበር፡፡

    አሁን በዘመን ወያኔ በመስጊድም በቤተክርስቲያንም አካባቢ ይህን እየሰማን ነው፡፡ የህዝብን አንድነት ለመናድ የሚፈልገው ገዢው ኢህኣዴግ በሃይማኖቶች መካከል ግጭት እና መተራመስን ለመፍጠር ፕሮፓጋንዳውን በስፋት እየነዛ ይገኛል::በምእራብ ኢትዮጵያ ያልተሳካውን በምስራቅ ኢትዮጵያ ለመድገም አዲስ ዘመቻ ተጀምሯል::ይህ መንግስታዊ ሽብር አደጋ አለው::ድሮ እንዲህ ዓይነት ችግር ሲፈጠር ለማስታረቅ ሩጫ ነበር፡፡ አሁን ለማባባስ የሚሯሯጥ ወያኔያዊ ኃይል እንዳለም በግልጽ እየታየ ነው፡፡ መፍትሔ ከማስገኘት ይልቅ የበለጠ ብጥብጥ እንዲከሰት የመንግስታዊ አካላት ስውር እጆች ግፊት እየበዛ ነው፡፡

    የኑሮ ውድነት በህዝቡ ላይ ተደራርቦ ከጭነት ልክ በላይ እየሆነ ነው፡፡ ብር እየመነመነችና እየከሳች በመሞት በየቀኑ የቀብሯ ጥሩንባ እንደተነፋ ነው፡፡ የሃገራሽን ገንዝብ ብር በራሷ ግሽበቱ ተሽኖባት አትክልትና ፍራፍሬን ፣ ስንዴና ጤፍን፣ ትራንስፖርትና ልብስን፣ የላስኪት ቤትን እና የቤት ኪራይን፣ የተማሪውን ደብተርና ስክሪፕቶን መጋፈጥ ተስኗታል፡፡ የኑሮ ውድነት የሚያስከትለው የወንጀል ድርጊት አለ፡፡ ኑሮ ውድነቱ ወንጀልን ወልዷል::ሴቶች እህቶቻችን እድሜ እና የስራ ሁኔታ ሳይለይ ስጋቸው በመሸጥ ስራ ላይ ሲሰማሪ ከተማሪ እስከ ባለትዳር ከሕጻናት እስከ አዛውንት የሚያቀርቡ የወሲብ ደላሎች በሃገሪቱ ከትመዋል::ይህም ዋነኛ አደጋ ነው::

    ለፖለቲካው እና ለስልጣኑ አትኩሮት የሚሰጠው ኢህኣዴግ ተቋማትን በሚገባ አለመገንባቱና ሥርዓቱን በሁሉም ዘርፍና መስክ አለመሞከሩን ብዙ ቀዳዳዎችን እንዲፈጠሩ ከማድረጉም በላይ፣ ለችግርና ለአደጋ የሚዳርግ ሁኔታ መኖሩ በገሃድ እየተስተዋለ ነው፡፡ የሃገሪቱ የተፈጥሮ ሃብት በስራ ላይ ሊውል ነው ከሚለው ዘገባ ጀምሮ እስከ ማዕድን በመገኘቱ ሀብት ተፈጠረ ብለን በሰማን ማግስት ፖታሽና ወርቅ ፍለጋው ዩራኒየም ፍተሻው ተቋረጠ:ነዳጅ የሚፈልግ ኩባንያ ሥራ እንዲያቆም ተደረገ መባሉን ስንሰማ ያሳስበናል፡፡ ሃገሪቱ ወደ አደጋ ውስጥ ሰተት ብላ መግባቷን እና እንደማትወጣውም ይጠቁመናል::

    ወያኔ በፖለቲካ ታማኝነት ያደራጃቸው እውቀት እና ልምድ የሌላቸው በሙስና እና በዝምድና የተሳሰሩ አትኮሮታቸው በሰው አገር ንብረት እና ገንዘብ ማከማቸት በሆኑ ባለስልታናት የተዋቀሩ መሥርያ ቤቶች ሲልፈሰፍሱና ውሳኔ መስጠት ሲያቅታቸው ማየቱም ወዴት እየሄድን ነው የሚያሰኝ ሆኗል፡፡ ይህም ከባድ እና እስካሁን ሊፈታ ያልቻለ አደጋ ነው::

    በዳያስፖራው ያለው ዘረኝነት፣ ጐሰኝነት፣ መከፋፈል፣ መራራቅ፣ ሃይማኖትን መጠቀሚያ ማድረግ፣ ከጠላት ጋር ወግኖ መሟገት፣ አገርንና የአገርን ክብር አሳልፎ መስጠትና ፖለቲካን ቢዝነስ በማድረግ ለአትራፊነት መወራጨት፣ አስፈሪ የሆነ አቋምና እንቅስቃሴ ማድረግ አሳሳቢ ነው፡፡ይህም እንዲፈጠር ከባድ ሚና የሚጫወተው ከሃገር ቤት የሚራመደው አሳዛኝ የፖለቲካ ፖሊሲ ሲሆን እንዲሁም ወያኔ እያሰለጠነ የሚያሰማራቸው የበግ ለምድ የለበሱ ቀበሮዎች የሚረጩት መርዝ ነው ይህም ሌላኛው በሃገር ላይ የተደቀና አደጋ ነው::

    አንድነታችንን የሚፈታተኑ የጠባብ ጐሰኝነትና አካባቢያዊ ስሜት የተላበሱ አስተሳሰቦች እዚህም እዚያም ሲሰሙና በቦታው መሟሟቂያ ሲሆኑ ማስተዋልም የተለመደ ሆኗል፡፡ የረዥም ዘመናት አንድነት ያለውን በፍር የተሞላውን በማህበርዊ እሴቱ እና ጉዞው አለም ያደነቀውን ኢትዮጵያዊነት የሚሸረሽሩ መንግስታዊ የማፊያ እጆች ሕዝብን በማፈናቀል እና ጎሰኝነትን እና ስልጣንን የማስረዘሚያ ስልት በማድረግ ከህዝብ አናት ላይ የሚሸኑ ትናንሽ የመንደር መንግስታት እንዲፈጠሩ በማድረግ የአብሮነት ፍቅርን እና አንድነትን በማደፍረስ በስፋት እየሰሩ ነው::ይህ ደግሞ እያየነው ያለነውን ከባድ አደጋ በሃገሪቱ ላይ እንዲሰራፋ አድርጓል::

    እደግመዋለሁ::ሃገራችን ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢና አስጊ ስለሆነ ሕወሓት መራሹ ገዥው ፓርቲና አማካሪዎቹ እና ባለስልታኖቹ ችግሩን ዓይተው መፍትሔ ካላስቀመጡ፣ አገርንና ሕዝብን በማስቀደምና በማሳተፍ ካልተንቀሳቀሱ አደጋ አለ፡፡ ሃገራችን እና ህዝቧ ሊወጡበት የማይችሉት ከባድ አደጋ ከፊታችን መደቀኑን ልብ ብለን በአንድነት እና በጋራ ከላይ የተቀመጡትን አደገኛ ሽብሮች የፈጠረውን በስልታን ላይ ያለውን መንግስት በአንድነት በመታገል ወደ ከርሰ መቃብሩ ከተን ዳግም እንዳያንሰራራ ማድረግ የኢያንዳንዳችን የዜግነት ግዴታ ነው::

    ከጸጋዬ ገ.መድኅን አርአያ
    በአጤ ኀይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት (በ1960 አካባቢ) ኤድመንድ መሪ የተባለ አሜሪካዊ የዕለታዊው ኢትዮጵያ ሔራልድ ጋዜጣ አማካሪ ሆኖ ይሰራ ነበር። እኛም እንጠረጥረው እንደነበረ ሁሉ የአሜሪካ ስለላ ድርጅት ሠራተኛ (ኮንታክት ማን) ነው። (እግዜሩ ይይላቸውና ለካ በእኛም መሐል ሰዋቸውን ይተክሉ ነበር) ኤድ መሪ የሥነ ጽሑፍ ሰው ስለሆነ በማስታወቂያ ሚኒስቴር “ተረፈ ዜና” የምንለውን – የማይታተመውንና የማይታወጀውን (በራዲዮና በቴሌቪዥን) በንጥረ ነገሩ መውሰጃ ሥፍራ የተነፈስነውን ሁሉ ሰብስቦ ካገጣጠመው በኋላ ወደ አሜሪካ ሲመለስ Kulubi የሚል መጽሐፍ አወጣ። እንግዲህ ተረፈ ዜና የገባችሁ ይመስልኛል።

    ሙሉውን አስነብበኝ …

    ኢሕአዴግ አዲስ አበባ ሲገባ፣ በጎሳ የተደራጁ ድርጅቶችን በማሰባሰብ ፣ በ1991 በተደረገው የአዲስ አበባ ኮንፈራንስ ፣ የሽግግር መንግስት ቻርተር ተብሎ የሚታወቀዉን ሰነድ እንዲጸድቅ ማስደረጉ ይታወቃል። ቻርተሩ አሁን ያለውን በጎሳ ላይ የተመሰረተ ዘረኛ ፌዴራል አወቃቀር ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲገበር ያደረገ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ በየትኛው አገር የሌለ፣ ጸረ-ኢትዮጵያዊ የብሄረሰቦች የመገንጠልን መብትን በሕግ ለመጀመሪያ ጊዜ የደነገገም እንደሆነ ይታወቃል። ዶር ነጋሶ ጊዳዳ […]

    Human Rights Watch የተባለው የሰብአዊ መብት ተሟጋች ቡድን ያወጣው አዲስ ዘገባ ኢትዮጵያ በአገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ከሚኖሩት ኢተዮጵያውያን ጋር የሚደረገውን ግንኙነት ለመከታተል ሲል በጣም የተራቀቀውን የሰለላ ሶፍት ዌር ይጠቀማል ይላል።

    የአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቅ ክፍል የፓርቲውን ደብዳቤ ተቀብሏል የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የከተማይቱ መሰረታዊ ችግሮች እየተባባሱ ከመምጣት ውጪ ለውጥ ማሳየት ባለመቻላቸው ለዚህ ተጠያቂ መሆን ያለበትን የከተማይቱን አስተዳደርና ገዢውን ፓርቲ የሚቃወም ‹‹የእሪታ ቀን››በሚል መሪ ቃል መጋቢት 28/2006 ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚደርግ አስታውቋል፡፡ በዛሬው እለት የፓርቲው ተወካዩች ለአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቅ ክፍል […]

    በሃይማኖት መሪዎችና አገልጋዮች ዙሪያ ሰሞኑን አንዲት መጣጥፍ ጽፌ ለድረ ገፆች ልኬ ነበር፡፡ ለኅሊናቸው ተገዢ የሆኑ አወጡት – አስነበቡን፤ እግዚአብሔር ይስጣቸው፡፡ ለባህልና ለይሉኝታ ያደሩት እንዲሁም እነሱ በሚፈልጉት ሙዚቃ ብቻ ታንጎና ማሪንጌ መደነስ የሚፈልጉት ወደቅርጫታቸው ከተቱት – ይክተቱት፡፡ ሁሉም የመሰለውን የማድረግ መብት አለውና ያነበበም ያስነበበም፣ ያፈነም ያሳፈነም የኅሊናው ዳኝነት ይፍረደው ከማለት ውጪ በዚህ በውዥንብር ዘመን መወቃቀሱም ሆነ […]

    በአገራችን ኢትዮጵያ ሁሉም መብቶች ያለምንም ገደብ የሚከበሩበትን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ላለፉት ዓመታት በርካታ መስዋዕትነቶች ተከፍለዋል፡፡ ዜጎች የመደራጀትና ሀሳባቸውን የመግለጽ ህገ-መንግሥታዊ መብት እንዳላቸው ጧት ማታ በመንግሥት ብዙሀን መገናኛዎች ቢለፈፍም፤ ሁሉም ነገር የይምሰልና የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ስልት እንደሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልፅ ነው፡፡ ከሕግ በላይ የሆነ አገዛዝ ባለበት አገር በየስፍራውና በየክልሉ የሚገኙ ካድሬዎችና የስርዓቱ ባለሟሎች እራሳቸውን ከህግ በላይ […]

    ተፈናቃዩቹ ከጎንደር አካባቢ ተነስተው ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ወደ ምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ በመውረድ በእርሻ ስራ የተሰማሩ ገበሬዎች ናቸው፡፡ከ1996ዓ.ም ጀምሮ በተለያየ ደረጃ ‹‹ክልላችንን ለቅቃችሁ ውጡ››ሲባሉ ቆይተዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማስፈራሪያው ወደ ግድያ፣ድብደባና ወከባ በማደጉ ለአቤቱታ አካባቢያቸውን ጥለው አዲስ አበባ ለመግባት ተገደዋል፡፡ ከተፈናቃዩቹ መካከል የተወሰኑት ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ካሳ ተ/ብርሃን […]

    በሕወሓት/ኢሕአደግም ይሁን በተቃዋሚዎች በረት እና ማደሪያ …….
    እየከፋ ያለን ጉዳይ እየተሻሻለ ነው ማለት = እያወቁ ማለቅ ……. ‪

    = ሥልጣንህን አድን = ኢሕአደጋዊ አጀንዳ ወደ = አገርህን አድን = ሕዝባዊ አጀንዳ ይቀልበስ።
    እየተሻለኝ ነው እያለ ከሚሞት፣ በጣም ጥሩ ምልክት ነው እያለ ከሚገድል ያድነን ፡፡ ደግ ደጉን ማውራት የተሻለ ዓለም ለማየት ይጠቅማል የሚለው ብሂል እንደተጠበቀ ሆኖ፤ እየከፋ ያለን ጉዳይ እየተሻሻለ ነው ማለት ግን እያወቁ ማለቅ ዓይነት ነው፡፡

    ምንሊክ ሳልሳዊ ዕውነቱን ተናግሮ የመሸበት ማደር ለአገርና ህዝብ ይበጃል እንጂ ጐጂ አይደም፡፡ የማይሰጋ ተስፋ የሌለው ሰው ነው ፡፡ አይመጣምን ትተሽ ይመጣልን ጨምሪበት” የሚሉት ዓይነት::
    በየኑሮ መስኩ ያለውን ህመም፣ በየሙያ መስኩ ያለውን ተወሳክ፣ በየፖለቲካ መስኩ ያለውን ወረርሽኝ በጊዜ መመርመር ዋና ነገር ነው፡፡ እኛ የወደድነውን እያጐላን በየሚዲያው ብንለፍፍ ለሀገርና ለህዝብ ፋይዳ አይኖርም።

    ለምርጫ እወዳደራለሁ የሚል ፓርቲም ይሁን ፕሮፓጋንዳ የሚረጭ ሚዲያ ፍትሐዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ ሰላማዊና ሕዝባዊ ሥርዓት ለመገንባትና በዚህ መንገድ ለመምራት ከፈለገ፣ ሕዝብን ማክበርና ማዳመጥ ጥበብ መሆኑን፣ አማራጭና ተለዋጭ የሌለው መርህ መሆኑን ለመግለጽና አፅንኦት ለመስጠት ነው፡፡
    የሕዝብን ብሶት ማዳመጥና ለሕዝብ ከበሬታ የመስጠት ጉዳይ ጥበብ መሆን ብቻ ሳይሆን፣ ጊዜ የማይሰጥና በእጅጉ አንገብጋቢ ሕዝብ አድን እና አገር አድን አጀንዳ እየሆነ ነው፡፡ሥልጣንህን አድን ከሚለው ኢሕአደጋዊ አጀንዳ በላይ፡፡

    በኢትዮጵያችንም እንደዚሁ ሕዝብን የማክበርና የማዳመጥ ጉዳይ ተገቢና አስፈላጊ ተብሎ ብቻ የሚታለፍ ሳይሆን፣ አንገብጋቢ ሆኖ የተግባር ያለህ እያለ በመጮህ ላይ ያለ አጀንዳ ነው፡፡ ላለው ችግር ብቸኛው ፍቱን መድኃኒትና ጥበብ ሕዝቡን ማክበርና ማዳመጥ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ እየጠየቀ ነው፡፡ አቤት እያለ ነው፡፡ እየጮኸ ነው፡፡ ጥያቄው ማነው ሕዝቡን እያከበረና እያዳመጠ ያለው ? የሚል ነው፡፡ ምንሊክ ሳልሳዊ

    አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
    UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)

    በአገራችን ኢትዮጵያ ሁሉም መብቶች ያለምንም ገደብ የሚከበሩበትን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ላለፉት ዓመታት በርካታ መስዋዕትነቶች ተከፍለዋል፡፡ ዜጎች የመደራጀትና ሀሳባቸውን የመግለጽ ህገ-መንግሥታዊ መብት እንዳላቸው ጧት ማታ በመንግሥት ብዙሀን መገናኛዎች ቢለፈፍም፤ ሁሉም ነገር የይምሰልና የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ስልት እንደሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልፅ ነው፡፡

    ከሕግ በላይ የሆነ አገዛዝ ባለበት አገር በየስፍራውና በየክልሉ የሚገኙ ካድሬዎችና የስርዓቱ ባለሟሎች እራሳቸውን ከህግ በላይ አድርገው ቢቆጥሩ የሚገርም አይደለም፡፡ በዚሁም ምክንያት በገዢው ፓርቲ ተቋማት፣ ኃላፊዎችና ባለስልጣናት የሚፈፀመው ኢ-ሰብአዊና ኢ-ዴሞክራሲያዊ ድርጊቶች እጅግ እየከፋ መጥቷል፡፡

    ባሳለፍነው ሳምንት በፓርቲያችን በአንድነት የተሰጣቸውን የተለያዩ ተልዕኮዎችን ለለማስፈፀም ወደ ደቡብ ክልል በተንቀሳቀሱት የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራና ም/ኃላፊው አቶ ዳንኤል ሽበሺ ላይ እና ከ32 በሚበልጡ የወላይታ ዞን አመራሮች ላይ መጋቢት 13 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም መንግስታዊ ውንብድና ተፈፅሞባቸዋል፡፡ በወላይታ ዞን ፖሊስ አዛዥ ሻለቃ ላሊሼ ኦሌ የሚመሩና የደህንነት ሰዎችን ጨምሮ ከ8-1ዐ የሚሆኑ መንግስታዊ ወሮበሎች የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን ምክር ቤት አባላት የተሰበሰቡበትን ግቢ በሀይል ሰብረው በመግባት የፓርቲ ሰነዶችን፣ ሁለት ሳምሰንግ ጋላክሲ ስልኮችን ጨምር በድምሩ ከ2ዐ የሚበልጡ የሞባይል ስልኮችን ዘርፈው ሄደዋል፡፡

    ወሮበሎቹ ታርጋ የሌላቸው ሞተር ሳይክሎችን በመጠቀም አመራሮቻችንን ወደ ፖሊስ ጣቢያ አስገድደው ወስደዋል፡፡ ከፓርቲያችን አመራሮቻችን የተነጠቁ ስልኮች በዞኑ ፖሊስ አዛዥ ቢሮ ውስጥ ፈሳሽ ውስጥ በመጨመር ከጥቅም ውጭ በማድረግ ሁለቱ ከፍተኛ አመራሮችና የዞኑን ም/ቤት አመራሮች ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳይኖራቸው አድርገዋል፡፡ አመራሮቹን አፀያፊ በሆነ ማጎሪያ ውስጥ ከቀኑ 5፡00 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 6፡30 አስረው ማደሪያ ሊያገኙ በማይችሉበት ሰዓት ለቀዋዋቸዋል፡፡ ይህ አይነቱ ከመንግስታዊ አካል የማይጠበቅ ውንብድና በሚሊዮኖች ድምጽ የመጀመሪያው እንቅስቃሴ ወቅት ሐምሌ 5 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም በዚሁ ዞን ተፈፅሞ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ በወቅቱ የጠራነውን ሕዝባዊ ስብሰባ ለማደናቀፍ ታርጋ የሌላቸውን ሞተር ሳይክሎች በመጠቀም በቅስቀሳ ላይ የነበሩ አባላትን በመደብደብና በመዝረፍ እንዲሁም የተከራየነውን አዳራሽ ጥበቃዎች ዘግተው እንዲሄዱ ከመደረጉም ባሻገር ከግለሰብ የተከራየነውን ሞንታርቮ ዘርፈው እስከ ዛሬም አልመለሱም፡፡

    ምንም እንኳ የአንድነት ከፍተኛ አመራርና አባላት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መስፈን በሚካሄደው ትግል ውስጥ መንገላታት፣ መደብደብ፣ መታሰርና ሞትም ካለ አይናቸውን ሳይጨፍኑ አፍጠው ለመቀበል ዝግጁ ቢሆኑም ይህን አሳፋሪ ድርጊት በቸልታ የማንመለከተውና አስፈላጊውን ነገሮች አጣርተን ተገቢውን ፖለቲካዊና ሕጋዊ እርምጃ የምንወስድበት ጉዳይ መሆኑን መግለጽ እንወዳለን፡፡

    ሕገ መንግሥቱ ላይ የሠፈረውን የመደራጀት መብትና እና በተሻሻለው በፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 573/2ዐዐዐ አንቀጽ 46 ንዑስ አንቀጽ‹2› የፖለቲካ ፓርቲዎች የዕለት ከዕለት ተግባሮችን ስር ፤ የሕዝቡን ፖለቲካዊ ግንዛቤ ማዳበር፣ የፓርቲውን ዓላማ ለሕዝቡ ማስረጽ፤ ዜጎች በአገሪቱ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው መቀስቀስ፣ በሕዝቡና በመንግሥት ተቋማት መካከል ግንኙነት እንዲጠናከር ማድረግ የሚሉ ግልጽ ድንጋጌዎች ሰፍረዋል፡፡ በአንፃሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከገዛ አባሎቻቸው ጋር በማንኛውም ጊዜ መሰብሰብ እንደሚችሉ እየታወቀ በመንግስትና በገዢው ፓርቲ የሚፈፀሙ ሕገ ወጥ ተግባሮች በየእለቱ ተጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ ሕግ ማክበርም ማስከበርም ያልቻለው ኢህአዴግ ሠላማዊ ትግሉን የሚደፈጥጡ ድርጊቶች ፈፃሚና አስፈፃሚ ካድሬዎች እና ሕገ አስከባሪ የተባለው የወላይታ ዞን ፖሊስ አዛዥ አይነት ግለሰቦችን በማበረታታት ሕጋዊና ሠላማዊ ትግሉን ወደ ጠርዝ እየገፋ ይገኛል፡፡

    በዚህ አጋጣሚ ለፓርቲያችን ከፍተኛ አመራሮችና ለወላይታ ዞን የወረዳ አመራሮችና አባላት ያለንን ክብር እየገለፅን፣ በወላይታ ሶዶ በአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና የፓርቲያችን የዞኑ ምክር ቤት አባላት ላይ የተፈፀመው መንግስታዊ ውንብድና ስርአቱ የወረደበትን የዝቅጠት ደረጃ አመላካች እንደሆነ ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

    ድል የሕዝብ ነው!
    መጋቢት 16 ቀን 2ዐዐ6 ዓም
    አዲስ አበባ

    ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

    የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ምድብ ችሎት በዛሬው ውሎው የሙሥሊም መሪዎችን የክስ ሂደት ተመለከተ። ችሎቱ በነአቶ አቡበከር አህመድ መዝገብ ዓቃቤ ሕግ በአሸባሪነት ክስ የመሠረተባቸውን ተከሳሾች ጉዳይ ከተመለከተ በኋላ

    የታዋቂው የጀርመን የእግርኳስ ክለብ ባየር ሚውኒክ ፕሬዝዳንት ኡሊኽነስ የገቢ ግብር በማጭበርበር ወንጀልከ 12ቀናት በፊት 3 ዓመት ተኩል የእስር ቅጣት ተበይኖባቸዋል ። ባለፀጋ ኽነስ ብይኑን ይግባኝ ሳይሉ ወህኒ እንደሚወርዱ አስታውቀዋል። የዛሬው አውሮፓና ጀርመን ዝግጅታችን በኽነስ ላይ የተላለፈው ብይንና አስተምህሮቱ ላይ ያተኩራል ።

    የቡድን ሰባት ሀገራት መሪዎች ትናንት በዘ ሄግ፣ ኔዘርላንድ ስለዩክሬይን ውዝግብ ለመምከር በጠሩት ልዩ ስብሰባ ላይ፣ ሩስያ የዩክሬይን ግዛት የነበረችውን ክሪሚያን የግዛቷ አካል አድርጋ በመቀበሏ ፣ ሞስኮ

    የዓይን ማዝ በሽታን በቀላሉ መከላከል ሲቻል ዛሬም ለብዙዎ የዐይን ብርሃን ማጣት ምክንያት እየሆነ ነዉ። የድህነት በሽታ በመባል የሚገለፀዉ ይህ የዐይን ህመም በዓለም 21 ሚሊዮን ሰዎችን እንደጎዳ የዓለም የጤና ድርጅት መረጃዎች ያመለክታሉ። ኢትዮጵያ ዉስጥም ይህ የዓይን ሕመም በተለያዩ ክልሎች ተንሰራፍቶ እንደሚገኝ እየተገለጸ ነዉ።

    በትናንትናዉ ዕለት የግብፅ ፍርድ ቤት በ529 የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር አባላት ላይ የሞት ቅጣት በይኗል። ዉሳኔዉ በተሰጠበት በዚሁ ችሎት 147ቱ ብቻ ናቸዉ በስፍራዉ ተገኝተዉ ፍርዱን ያደመጡ ሲሆን ቀሪዎቹ ከሚጠብቃቸዉ ፍርድ ለማምለጥ በሽሽት ላይ መሆናቸዉ ተገልጿል።

    ደቡብ ሱዳን ከግብፅ ጋ የሁለትዮሽ ወታደራዊ ትብብር ስምምነት መፈራረሟን ዘገባዎች ያመለክታሉ። ጁባ ተመሳሳይ መግባባት ላይ ከሁለት ዓመታት በፊት ከተነጠለቻት ሰሜን ሱዳን ጋም መድረሷ ተገልጿል።


    (ደጀ ሰላም፣ መጋቢት 14/2006 ዓ.ም፤ ማርች 24/2014/ PDF በፍቅር ለይኩን):- ባለፈው ሳምንት ‹‹የፓትርያርኩ የለውጥ ተስፋዎች ወዴት ገቡ?›› በሚል አቶ መብራቱ መርሳ የተባሉ ግለሰብ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ን ፓትርያርክ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ በቤተ ክህነቱ ተቋም የተንሰራፋውን ሙሰኝነትንና ጎጠኝነትን በተመለከተ የተማፅኖ ጦማራቸውን በሪፖርተር ጋዜጣ በኩል ለቅዱስ ፓትርያርኩ ይደርስ ዘንድ አቅርበው ነበር፡፡ እኚህ ግለሰብም ባቀረቡት የተማፅኖ ደብዳቤያቸው ዋና አሳብም፣ ቅዱስ ፓትርያርኩ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደር ውስጥ የነገሠውን አድር ባይነት፣ ዘረኝነት/ጎጠኝነትና ሙስና ለማጥፋት በአደባባይ ቃል የገቡበትን ዘመቻቸውን አጠንክረው እንዲቀጥሉበትና ፍሬውን በተግባር እንዲያሳዩ የሚጠይቅ ነው፡፡

    በእርግጥ ይህ የአንድ ግለሰብ ብቻ ሳይሆን የበርካታዎች የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ መሪዎች፣ አባቶች፣ አገልጋዮችና ምእመናን የቀን ተሌት ብርቱ ምኞትና ተማፅኖ ነው፡፡ እኚህ ሰው ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ወደ ፕትርክና መንበር በመጡ ማግሥት የቤተ ክህነቱን ተቋም ከጎጠኞችና ከሙሰኞች ለማጥራት የገቡት ቃል ተግባራዊ ኾኖ ለማየት የነበራቸው ምኞት ከዓመት በኋላ የተጠበቀውን ያህል ዘመቻው ስኬት ባለማሳየቱና የለውጡም ሂደት በመንቀራፈፉ ሥጋት ቢጤ ገብቷቸው ይመስላል ይህን የተማፅኖ ደብዳቤ ለፓትርያርኩና ለሚመሩት የቤተ ክህነት ተቋም ለማድረስ የወደዱት፣ የተገደዱት፡፡
    የእኚህ ግለሰብ ‹‹የለውጥ ያለኽ›› ተማፅኖ ጦማር በርካታዎችን የቤተ ክርስቲያኒቱን አባቶችን፣ አገልጋዮችንና ምእመናን የሚወክል እንደሆነ ነው በግሌ የማምነው፣ የምቀበለውም፡፡ የብዙዎች የአባት ያለኽ፣ የመሪ ያለኽ፣ የፍቅር ያለኽ፣ የእውነት ያለኽ፣ የፍትሕ ያለኽ፣ የበጎነት ያለኽ፣ የቅንነት ያለኽ፣ የመንፈሳዊነት ያለኽ፣ የለውጥ ንፋስ ያለኽ ጩኸትና አቤቱታ የቤተ ክህነቱን ተቋምና የአገሪቱን ሰማይ ክፉኛ ካደፈረሰው ሰንብቷል፣ ከራርሟልም፡፡
    እውነተኛ የኾኑ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች፣ መንፈሳዊ መሪዎች፣ አገልጋዮችና ምእመናንም፣ አምላክ ሆይ ዝምታህ እስከ መቼ ነው?!፣ በቅዱስ መቅደስህ አደባባይ በትእቢትና በድፍረት እየተንጎማለሉ መሠውያህን በድሆች ዕንባና ደም የሞሉ ክፉዎችን የምትታገሳቸው እስከ መቼ ነው?!፣ በአፍቅሮተ ንዋይ አቅላቸውን የሳቱ፣ በክቡር ደምህ በዋጃኻቸው በጎችህ/በመንጋዎችህ ላይ በዋጋ የሚደራደሩ ይሁዳዎች- ምንደኞችና ነጋዴዎች ላይ የተግሣጽህ፣ የቁጣህ ጅራፍህ መቼ ነው የሚነሳው?!፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በዘርና በጎሳ የሚለያዩና የሚከፋፍሉ ዘረኞችና ጎጠኞችስ መቼ ነው ክፉ ዘራቸው የሚመክነው?!
    የወንጌልን እውነት ቃል የሚሸቃቅጡ፣ መንፈሳዊ ሕይወትንና ስኬትን በግፍ በተከማቸ የዓመፃ ገንዘብና በዓለማዊ ሀብት የሚለኩ፣ የእግዚአብሔርን ስጦታ እንደ ስምኦን መሰሪ በገንዘብ ገዝተው በመቸርቸር ሀብትና ዝናቸውን ሰማይ ለማድረስ ዓውደ ምሕረቱን ያረከሱ አስመሳይ ነጋዴዎችና ምንደኞችስ ስለምን ቤትህን አጣበቡት?!፣ በቅድስናህ መቅደስ ላይ የሚዘባበቱ ፌዘኞችስ እስከ መቼ ሕዝብህን በሽንገላ ቃል ያባብሉታል፣ በክፉ ሥራቸውስ ያሰጨንቁታል፣ ያሰቃዩታል፣ ያስለቅሱታል?!
    ስለ ሕዝብ መከራና ሰቆቃ፣ በየቀኑ እየፈራረሱ ስላሉ በክቡር ደምህ ስለዋጃኻቸው መቅደሶችህ/ሕዝበ ክርስቲያን ግድ የሚለውና በፈረሰው ቅጥር በኩል የሚቆም ነቢይ ኢሳይያስ ወዴት ይገኝ ይሆን?!፣ በመቅደስህ አጥር ስር ስለወደቁ የምድሪቱ ጎስቋሎችና መፃጉዎች፣ በረሃብ አለንጋ እየተገረፉ በቤተ መቅደስ ደጃፍ ስለሚያነቡ የዋኃን ሕፃናትና እናቶቻቸውስ ማን ነው ግድ የሚለው?!፣ ሕዝብህ በየቀኑ እየፈረሰ፣ እየተናደ ባለበት፣ የአንተን ቤት በዕብነ በረድና በከበሩ ድንጋዮች አንሠራለን፣ እነገነባለን የሚሉ ግብዞችንና ሙሰኞችንስ የሚገሥጻቸው ማን ይሆን?!
    ነገሥታትንና መሪዎችን በአደባባይ የሚገጥሙ፣ ስለ ክፋታቸው፣ ኃጢአታቸውና በደላቸው ፊት ለፊት የሚገሥጹ፣ ስለ እውነትና ፍትሕ የሚቆሙ መንፈሳዊ ዐርበኛ የኾኑ ባህታውያን ዮሐንሶች ወዴት አሉ?!፣ ሕዝብን ከአስጨናቂው የፈረዖን አገዛዝ ነፃ የሚያወጡ፣ በሕዝባቸውና በወገናቸው ፍቅር የነደዱ የዘመናችን ሙሴዎችስ አድራሻቸው ወዴየት ነው?!፣ እንደ ነቢዩ ኤርምያስ ዕንባቸውን እያፈሰሱ ‹‹አቤቱ የኾነብንን አስብ፣ ስለ ቅዱስ ስምህ ስትልም ዘመናችን አድስ!›› የሚሉ ኤርምያሶችን ከወዴት እናገኝ ይሆን በማለት ብዙዎች በተማፅኖ ዕንባቸውን እንደ ራሄል ወደ ጸባዖት፣ ወደ አርያም እየረጩት ነው፡፡
    ምድሪቱን በከደነው በዚህ ሁሉ ዋይታ፣ ጩኸትና ሰቆቃ መካከል እጅግ ወደ ተከበረው መንፈሳዊ መንበር፣ ሥልጣንና ኃላፊነት የመጡት ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ በሹመታቸው ማግሥት ሙሰኝነትንና ጎሰኝነትን አልታገሥም፡፡ ይህ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ የልጆቻችን ብርቱ ጩኸትና ዋይታ ወደ ጆሮዬ ደርሷል እናም ጊዜው የለውጥ ነው፡፡ ከቅዱስ ሲኖዶስ፣ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች፣ መንፈሳዊ አገልጋዮችና ልጆቻችን ጋር በመሆን ለለውጥ እንሠራለን፣ እንደክማለን በማለት የብዙዎችን ልብና ስሜት ከፍ አደርገውት ነበር፡፡ በዚሁ መንፈሳዊ ቆራጥነትና ትጋትም የተወሰዱ የብዙዎችን ልብ በተስፋና በሐሤት የሞሉ አንዳንድ የለውጥ ዕርምጃዎችም ነበሩ ማለት ይቻል ይመስለኛል፡፡
    በመጀመሪያ ደረጃ ቅዱስ ፓትርያርኩ በቤተ ክርስቲያኒቱ የተንሰራፋውን የጎጠኝነትና የሙሰኝነት ችግሮች መኖራቸውን አምነው መቀበላቸው አንድ የለውጥ ዕርምጃ ነው ማለት የሚቻል ይመስለኛል፡፡ ‹‹በቅጡ ተለይቶ የታወቀ ችግር በከፊል እንደተፈታ ይቆጠራል፡፡›› እንዲሉ፡፡ ሲቀጥልም ፓትርያርኩ እነዚህ ለበርካታ ዓመታት ሲንከባለሉ የቆዩ ችግሮችን በትክክል ለይቶ ከማስቀመጥና ባለፈም ተግባራዊ ዕርምጃዎችን በመውሰድ የለውጥ ዕርምጃው በአምላካችን ረዳትነት ፍሬ እንዲያፈራ እናደርጋለን በማለት እንቅስቃሴ መጀመራቸው ለብዙዎች ብሩሕ የለውጥ ተስፋን የፈነጠቀ ነበር ማለት ይቻላል፡፡
    ለአብነትም ያህል ፓትርያርኩና ቅዱስ ሲኖዶሱ በበዓለ ሲመትና በሌሎች ክብረ በዓላት ሰበብ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪና የተንዛዛ ድግስና ውዳሴዎች እንዲቀሩ ማድረጋቸው፣ በድግስ ሰበብና በበዓላት ሽርጉድ ኪሳቸውን የሚያደልቡ ሙሰኞችን በሩ እንዲዘጋባቸው አድርጓል፡፡ በዚህም በውድ ስጦታዎችና ገጸ በረከቶች ሰበብ፣ እጅ የመጠመዘዝ ያህል ድብቅ አጀንዳቸውንና ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም የሚተጉና የሚሯሯጡ አስመሳዮችና ሙሰኞችም ቀኑ እንዲጨልምባቸው ኾኗል፡፡
    ሌላውና በተለይም በግንባር ቀደምትነት ሊጠቀስ የሚገባው የለውጥ እንቅስቃሴ ደግሞ በቤተ ክህነቱ አስተዳደር ሥራ ውስጥ ግልፅነትና ተጠያቂነት ያለበት፣ መንፈሳዊ ትጋት፣ በጎነትና ቅንነት የሚንጸባረቅበት ሙያዊ/ፕሮፌሽናል አሠራር እንዲኖርና ለማድረግ ከመነጋገር አንስቶ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ ልጆችና ምሁራን የተሳተፉበት ‹‹የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መዋቅር አደረጃጀትና የአሠራር መመሪያ ጥናት›› ሰነድ ቀርቦ ሰፋ ያለ ተከታታይ ውይይቶች የተደረገበት የዛን ሰሞኑ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የቤተ ክህነቱ የአስተዳደር ሠራተኞችና መንፈሳዊ አባቶች የተሳተፉበት ጉባኤ በዋናነት የሚጠቀስ ነው፡፡
    ይህን የለውጥ ትግበራ ጥናት ሰነድን ያዘጋጀው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶችና ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ነው፡፡ ይህ ዳጎስ ያለ ጥናትም በቁጥር ጥቂት የማይባሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች የኾኑ ምሁራንና ባለሙያዎች የተሳተፉበትና በገንዘብ ሲሰላም ቤተ ክርስቲያኒቱን በመቶ ሺኅዎች የሚገመት ወጪን ከማውጣት የታደጋት በብዙ ድካምና በብርቱ ጥንቃቄ የተዘጋጀ የጥናት ሰነድ እንደሆነ ነው አብዝቶ የተነገረለት፡፡
    በዚህ የጥናት ሰነድ ላይም በየደረጃው ተከታታይ የኾኑና ውጤታማ ነበሩ ሊባሉ የሚችሉ ውይይቶች ተደርጎባቸዋል፡፡ ይሁን እንጂ በጉባኤው ላይ ይህን የመዋቅር አደረጃጀትና የአሠራር ጥናት ሰነድ በምን መልኩ ሥራ ላይ ልናውለው እንችላለን የሚለው ላይ በተነሡ አንዳንድ ልዩነቶችና አለመግባባቶች የተነሳ የተለያዩ ቡድኖች ጎራ ለይተው የቃላት ጦር ሲማዘዙ፣ ሲጠዛጠዙ ታዝበናል፡፡ አሁንም የቃላት ጦርነቱ፣ መወራረፉና መጎነታተሉ እንደቀጠለ ነው፡፡ በአንፃሩም ችግሩንና ቀውሱን ከቤተ ክህነቱ ክልል በማውጣት በስውርም ኾነ በግልጽ እየታየ ያለ ሌላ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መሠረት ያለው ጠንካራ ግፊት እንዳለ የሚከራከሩ ድምፆች ደግሞ እዚህም እዛም እየተሰሙ ናቸው፡፡
    ለቤተ ክርስቲያኒቱ የሚቆረቆሩ፣ በአገር ውስጥና በውጭ አገራት ባሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች የተማሩ ምሁራንን በሥሩ አሳባስቦ የያዘው ማህበረ ቅዱሳን ለዚህ የለውጥ ዕርምጃ የበኩሉን ዕገዛና ጥረት ለማድረግ ደፋ ቀና ቢልም፣ ማኅበሩ ያቀረበው የዳጎሰ የጥናት ሰነድ ሁሉንም የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችና አባቶች ባስማማ መልኩ ተቀባይነት አግኝቶ የለውጥ ትግበራውን ዕውን ለማድረግ ዕንቅፋት እንደገጠመው ግን በግልጽ እየተስተዋለ ነው፡፡
    ማኅበረ ቅዱሳን ይህ የጥናት ሰነዱ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ተዛማጅ የኾኑ እንቅስቃሴዎቹም ከሰሞኑን እክል እንደገጠማቸው ሰምተናል፣ ታዝበናልም፡፡ ለአብነትም የአብነት መምህራንን በተመለከተ የጠራው አገር አቀፍ ጉባኤ መታገዱ የሰሞኑን በርካታዎችን ያሳዘነ ዜና ሆነ ማለፉን ልብ ይሏል፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ቅዱስ ፓትርያርኩ ከሰሞኑን፣ ‹‹ቤተ ክርስቲያን በባይሎጂና በኬምስትሪ ምሩቃን አትመራም፡፡›› የሚለው መረርና ከረር ያለ ውስጠ ወይራ ንግግራቸው በማኅበሩ ማንነትና አቋም ላይ ያነጣጠረና ጥርጣሬያቸውንም ገሃድ ያወጣ ንግግር እንደሆነ ነው ብዙዎች ሲናገሩ የተደመጡት፡፡
    የኾኖ ኾኖ ፓትርያርኩ በአደባባይ ያወጁትንና ቃል የገቡለትን ቤተ ክህነቱን ተቋም ከሙሰኞችና ከጎጠኞች እናጻዳለን ዘመቻቸውም ኾነ ለዚሁ የለውጥ ዘመቻ ያግዛል በሚል በማኅበረ ቅዱሳን ያቀረበው የጥናት ሰነድ የመጨረሻው ዕጣ ፈንታ ምን ይኾናል የሚለውን በእርግጠኝነት ለመናገር ግን አሁንም በትዕግሥት መጠበቅ የሚያስፈልግ ነው የሚሉ በርካታ ታዛቢዎች አልጠፉም፡፡
    በሌላ በኩል ደግሞ የቤተ ክህነቱ ተቋም ትልቁና ዋንኛ ችግሩ የሚጀምረው ከላይ ከመንፈሳዊ መሪዎቹ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች አካባቢ መንፈሳዊ ሕይወትና መንፈሳዊ ቆራጥነት/ቅንዓት መጥፋቱ በቤተ ክህነቱ ተቋም ለተከሰተው የዚህ ሁሉ ምስቅልቅልና ቀውስ ዋንኛው ምክንያት እንደኾነ አድርገው ያቀርባሉ፡፡ በከፋ የሞራል ውድቀትና ዝቅጠት ውስጠ የተዘፈቁ፣ ምድራዊ ሀብትና ዝና የሚያንኾልላቸው፣ የለየላቸው ሙሰኞችና ጎሰኞች ከላይ እስከ ታች በተሰገሰጉበት የቤተ ክህነቱ ተቋም ውስጥ ለውጥን ለማምጣት መንገዱ አልጋ በአልጋ ይኾናል ተብሎ አይታሰብም፣ አይጠበቅምም፡፡
    ላለፉት በርካታ ዓመታት ሲንከባለል የቆየ ይህ የተወሳሰበው የቤተ ክህነቱ ተቋም ችግሮች በአንድ ጀምበር ይፈታሉ ብሎ ማሰብም የዋኽነት ነው፡፡ እናም ለውጡን ዕውን ለማድረግ ከሚያስፈልገው ትዕግሥትና ቁርጠኝነት ባሻገር የክርስትና ሃይማኖት ዓምድና መሠረት የኾኑት ፍቅር፣ በጎ ሕሊና፣ ቅንነትና ታማኝት እንዲኖሩ የግድ ይላል፡፡ መሰሪነት፣ አድር ባይነት፣ አጎብዳጅነትና ግብዝነት በነገሡበትና መንፈሳዊነት ፈፅሞ እየተሰደደበት ባለበት ተቋም ውስጥ ለቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ መሪዎችና አባቶች ፍቅርና ኅብረት፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ ህልውና፣ የመንፈስ አንድነትና ሰላም ቀዳሚና ዋና አጀንዳ ሊኾን በተገባው ነበር፡፡
    ከሁሉም በፊት ፍቅርንና መንፈሳዊ አንድነትን ለማምጣት ፈቃድም ኾነ አቅም ያነሰው የቤተ ክህነቱ ተቋም ጋሪውን ከፈረሱ በማስቀደም ጉልበቱንና አቅሙን በከንቱ እያባከነ ነው በማለት የሚተቹ ብዙዎች ናቸው፡፡ የቤተ ክህነቱ ተቋምም ኾነ መሪዎች በእውነትም ሊያሳስባቸውና ሊያስጨንቃቸው የሚገባው ቀዳሚው ጉዳይ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ አንድነትና ሰላም መሆን ነበረበት፡፡ ይህ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ መሪዎችና አባቶች ወይም የቤተ ክህነቱ ተቋም ወሳኝና ቀዳሚ አጀንዳ የአንድ ሰሞን ብቻ ወሬና ግርግር ኾኖ ማለፉና አሁን አሁን ደግሞ ከእነ መፈጠሩም የመረሳቱ ነገር ለመኾኑ መቅደም ያለበት የትኛው ነው ‹‹ሰላምና አንድነት ወይስ …›› የሚል ጥያቄን በተደጋጋሚ እያስነሳ ነው፡፡
    ይህ የቤተ ክርስቲያኒቱ የአንድነትና የሰላም ጉዳይ የሚያሳስባቸው በርካታዎችም የፓትርያርኩም ኾነ የቤተ ክህነቱ ተቋም የለውጥ እንቅስቃሴ የቤቱ መሠረት ተነቃንቆ እያለ ጣርያውና ግድግዳው እንዳይፈረስ ከሚታገል የዋኽ ሰው ጋር በማመሳሰል የሚያቀርቡ ታዛቢዎች አልጠፉም፡፡
    በቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ ኾኖ በማያውቅ ለሦስት ተከፍላ፣ የኢትዮጵያ ሲኖዶስ፣ ሕጋዊው ሲኖዶስ፣ ገለልተኛ በሚል የተለያዩ፣ የተከፋፈሉና ተገለባባጭና አድር ባይ የኾኑ ፖለቲከኞች እንደሻቸው የሚጠመዙዟቸው አባቶች ልዩነታቸውን በሰላም ፈተው ወደ አንድነት መምጣት እስካልፈቀዱ ድረስ፣ ለቤተ ክህነቱ የምንመኘው እውነተኛውና ተግባራዊው ለውጥ ህልም ነው ሲሉ አጥብቀው ይከራከራሉ፡፡ ዛሬ ከዳር እስከ ዳር መነጋገሪያ የኾነው ሙሰኝነትም ኾነ ጎጠኝነት የቤተ ክህነቱ ለገባበት ቀውስና የሞራል ውድቀት አንድ ወይም ጥቂቱ መገለጫ እንጂ የቤተ ክርስቲያኒቱ መሠረታዊ ችግር ጥልቅ፣ የተወሳሰበና ዕድሜ ጠገብ ነው፡፡ መፍትሔውም ፍቅር፣ አንድነትና ሰላም ግድ የሚላቸው፣ ለእግዚአብሔርና ለቤቱ መንፈሳዊ ቅንአት ያላቸው መንፈሳዊ መሪዎች እንዲኖሩና እንዲበዙ መጸለይና መሥራት ነው፡፡  
    የፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ ሙሰኞችንና ጎጠኞችን የማጥራት ዘመቻው ፍሬያማ እንዲኾንና ለዚሁ የለውጥ ዘመቻ ትግበራም ያግዛል ተብሎ በቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች/ምሁራን የቀረበው የጥናት ሰነድ ተግባራዊ ውጤት እንዲያመጣ ከተፈለገ መቅደም ያለበት አማራጭ ይህ ነው ሲሉም ይናገራሉ፡፡ ስለሆነም ይላሉ እነዚህ አስተያየት ሰጪዎች፣ የቤተ ክህነቱ ተቋም ማስቀደም ያለበት ዋነኛው ዕርምጃ መሆን ያለበት መንፈሳዊነትን ያስቀደሙ የእግዚአብሔርና የቤቱ ቅናት የሚያቃጥላቸው፣ መመሪያቸውና መለያቸው ፍቅር የኾነ፣ ሰላምንና ዕርቅን የሚሰብኩ፣ ለእውነትና ለፍትሕ የቆሙና የሚከራከሩ መሪዎችና አባቶች እንዲኖሩና እንዲበዙ መሥራትና መትጋት የግድ ይላል በማለት አስተያየታቸውን ይሰነዝራሉ፡፡
    እነዚህ ትችቶች፣ መከራከሪያዎችና አስተያየቶች እንዳሉ ኾነው ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የጀመሩት የቤተ ክህነቱን ተቋም ከሙሰኞችና ከጎጠኞች የማፅዳት ዘመቻቸውን አጥብቀው እንዲገፉበት የሚመኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባቶች፣ አገልጋዮችና ምእመናን ድምፅ አሁንም ጎልቶ እየተሰማ ነው፡፡ በመጨረሻ አንድ ነገር ለማለት እወዳለኹ፡፡ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በፕትርክና ዘመናቸው የተከፋፈለችውን ቤተ ክርስቲያን አንድነት በማስጠበቅ፣ የቤተ ክህነቱን ተቋም ከሙሰኞች፣ ከአስመሳዮችና ከጎጠኞች የፀዳች በማድረግ አዲስ ታሪክ ያስመዘግቡ ዘንድ ልባዊ ምኞቴ ነው፡፡
    Deje Selam is a venue of news, views and opinions about or related to the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. [email protected]

    ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
    (ይህ “ኑ! እንዋቀስ” የሚለው ስር ነቀል የለውጥ ጥሪ ቀጥታ የሚያነጣጥረው በኢህአዴግ አባላት ላይ ብቻ ነው፤ አመራሩን በፍፁም አይመለከትም) ኢህአዴግ ራሱ በይፋ ሲናገር እንደተደመጠው፣ በአሁኑ ጊዜ የአባላቱ ቁጥር ወደ ሰባት ሚሊዮን ገደማ ደርሷል። ይህም የአገሪቱ ቁጥር አንድ ግዙፍ የፖለቲካ ፓርቲ ያደርገዋል። በርግጥ ግዙፍ እንጂ ጠንካራ እንዳላልኩ ልብ ይሏል። ምክንያቱም ጥንካሬ የሚለካው በአባላት ቁጥር ሳይሆን በድርጅት ፍቅር፣ በዓላማ ፅናትና በሚሰጡት ልባዊ አበርክቶ ነው።

    ሙሉውን አስነብበኝ …

    በሕዝብ ብዛት ቁጥር ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሁለተኛ ከአለም ደግሞ አሥራ አምስተኛ ናት። ወደ ሰማኒያ ሚሊዮን ሕዝብ ሲኖራት፣ ያን ያህል ሕዝብ ኖሯት የባህር በር የሌላት ብቸኛ አገር ናት። ከኢትዮጵያ ቀጥሎ ብዙ ሕዝብ ኖርቷት የባህር በር የሌላት አገር፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ አንድ ሶስተኛ የሚሆን ሕዝብ ያላት ዩጋንዳ ናት። የቀድሞ ጥቅላ ሚኒስተር አቶ መለስ ዜናዊ፣ በባህር ወደብ ዙሪያ ሲጠየቁ «ለእድገት […]

    ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

    የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ዖባማ፤ ዛሬ ኔድርላንድ እንደገቡ በሰጡት መግለጫ ፣ አውሮፓውያንን ዩናይትድ ስቴትስ ሩሲያ በክሪሚያ በወሰደችው እርምጃ ሳቢያ ዋጋ የሚያስከፍላትን የማዕቀብ ርምጃ በመተባበር ወስደናል አሉ። ሰፊ የጦር ኃይል አንቀሳቅሶ

    በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ፣ ባለፈው ቅዳሜ ከቀትር በኋላ በደረሰው የአሳት ቃጠሎ፣ በዋናው ህንጻና ማሺኖች ላይ የደረሰ ጉዳት ባለመኖሩ፤ የማተሚያ ቤቱ መደበኛ ሥራ አለመተጓጎሉን ማተሚያ ድርጅቱ ገለጠ። በቃጠሎው የወደሙት በጓሮ በኩል የነበሩ ትርፈ