ነሃሴ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-”ሕገመንግሥቱንናሕገመንግሥታዊሥርዓቱንበኃይልለመናድናሕዝቡበመንግሥትላይ አመኔታእንዲያጣአድርገዋል በሚልመከሰሳቸውንበመንግሥትመገናኛብዙሃንባለፈውማክሰኞእለትየሰሙትአምስትመጽሔቶችእናአንድጋዜጣ ከእንግዲህሊታተሙእንደማይችሉከወዲሁምልክቶችበመታየትላይናቸው። በተለይአዲስጉዳይ፣ፋክትእናሎሚመጽሄቶችአሳታሚዎችእስካሁንበመንግሥትመገናኛብዙሃንከሰሙትዜናውጪ በይፋየደረሳቸውክስየሌለሲሆን ነገርግንመንግሥትባሰራጨውፕሮፖጋንዳምክንያትበተለይየህትመትድርጅቶች ፕሬሶቹንላለማተምእያንገራገሩመሆኑታውቋል፡፡በዚህምክንያት የፊታችንቅዳሜዕለትመውጣትየነበረበት አዲስጉዳይመጽሔትበዕለቱየማይወጣመሆኑከወዲሁየተረጋገጠሲሆንየፋክትእናየሎሚመጽሔቶችምየመውጣት፣ ያለመውጣታቸውነገርባይለይለትም ያለመውጣታቸውጉዳይግንያመዘነመሆኑታውቋል፡፡ የብሮድካስትባለስልጣንበሰኔወር 2006 ባወጣውመረጃመሰረትፋክትበወርበአማካይ 17 ሺ 993፣አዲስጉዳይ በወር 11 ሺ 750፣ሎሚበወር 11 ሺ 250 የኮፒብዛትወይንም  ከፍተኛስርጭትያላቸውመጽሔቶችመሆናቸውን አስታውቆአል፡፡

ነሃሴ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አማጽያኑ በአዲስ አበባው ጉባኤ ላይ ለመገኘት ለምን እንዳልፈቀዱ ግልጽ አይደለም። ይህ አቋማቸው ያአበሳጫቸው የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ የአማጽያኑ መሪ ሪክ ማቻርን ተጠያቂ አድርገዋል። አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ደግሞ ሁለቱም ሃይሎች ወደ ሰላም ስምምነቱ የማይመጡ ከሆነ የምስራቅ አፍሪካ አገሮች እርምጃ ይወስዳሉ ብለዋል። በደቡብ ሱዳን አሁንም ከፍተኛ የሆነ ሰብአዊ እልቂት …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የኢትዮጵያ ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ቅርሶች በተየያዩ አጋጣሚዎች ከሀገሪቱ ሲወጡ ኖረዋል። በተለይ በዉጭ ወረሪዎች አስገዳጅነትም ይሁን፤ ቅርሶቹን ጠብቆ ለማቆየት በሚል በታሪክ አጋጣሚ ቅርሶች ከኢትዮጵያ የወጡባቸዉ ዘመናት በመረጃም ጭምር ተመዝግበዉ የሚገኙበት ሁኔታ አለ።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ዋሽንግተን ዲሲ ዩናይትድ ስቴትስ ለሦስት ቀናት በተካሄደው በዚሁ ጉባኤ ፍፃሜ ላይ ባሰሙት ንግግር ጉባኤው በንግድ በመልካም አስተዳደርና በደህንነት ጉዳዮች ላይ ተጨባጭ እርምጃዎችን ለመውሰድ የጋራ ስምምነት ላይ መደረሱን ተናግረዋል ።

በንክኪና ከሰውነት በሚወጣ ፈሳሽ በሚተላለፈው በገዳዩ ኤቦላ ምክንያት ተውሃሲው በተሰራጨባቸው ሃገራት የንግድ ልውውጥ ቀንሷል ።የአገልግሎት ሰጭ የንግድ ተቋማት ገበያም ቀዝቅዟል ።

መኢአድ ባለፈው ዓመት ሐምሌ 2005 ዓም ከ600 ጠቅላላ አባላቱ 390ው በተገኙበት ስስበባ ቢያካሂድም ምርጫ ቦርድ ግን ምልዐተ ጉባኤው አልተሟላም ሲል መዋሃድ እንደማይችሉ ማሳወቁን የአመራር አባላቱተናግረዋል ።የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ጉባኤ ሲያካሂድ የተገኙት 285 አባላት በመሆናቸው ይህ ሕጋዊ እንዳልሆነ በፅሁፍ ማሳወቁን ገልጿል ።

በአራዳ መጀመሪያ ፍ/ቤት ችሎት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ይቀርባል ቢባልም ዘግይቶ 10 ሰዓት ከ25 ላይ ቀርቧል፡፡ ፖሊስ ሀምሌ 3 ቀን ፍ/ቤት ቀርቦ ከግንቦት 7 ጋር በተያያዘ በሽፋን ትሰራለህ በሚል በቁጥጥር ስር አድርጎ ለምርመራ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆበት የነበረ ሲሆን በ28 ቀን ውስጥም ምንም ማስረጃ ለችሎቱ አላቀረበም፡፡ በችሎቱ ላይ የአረና አመራር አቶ ካህሳይ፣የአብርሃ እህት በችሎቱ እንዲታደሙ […]

መኢአድና አንድነት ወደ ሰላማዊ የትግል ፍልሚያ ውስጥ መግባታቸውን ለሕዝባቸው ማሳወቅ ይወዳሉ!! መኢአድና አንድነት በዛሬው ዕለት ውህደቱን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ በህወሓት/ኢህአዴግ አባላት የሚመራው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በበሰላማዊ ትግሉ ላይ መሰናክሎችን በመፍጠር ካሁን ቀደም የተደረጉ ምርጫዎች እንዲዘረፉና ኮሮጆ እየተገለበጠ ለገዢው ፓርቲ እንዲሰጥ ከፍተኛ ሚና ሲጫወት መቆየቱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ እንደሆነ ገልጸው በየክልሉ፣ በየዞኑና ወረዳዎች የተሰማሩ የምርጫ ቦርድ […]

ንሥር ሳይፈትን አያምንም፤ አይተማመንምም፡፡ ሴቷ ንሥር ባል ማግባት ስትፈልግ አንድ እንጨት ታነሣና ወንዱ እየተከተላት ወደ ላይ ትመጥቃለች፡፡ እስከ ሰማይ ጥግ ከደረሰች በኋላም ያንን እንጨት ትለቀዋለች፡፡ ያን ጊዜ ወንዱ እንጨቱ መሬት ከመድረሱ በፊት በፍጥነት በመወርወር መያዝና ለሴቷ መልሶ ማምጣት ይጠበቅበታል፡፡ ሴቷም እንጨቱን ተቀብላ እንደገና ወደ ቀጣዩ ከፍታ ትመጥቅና እንጨቱን መልሳ ትጥለዋለች፡፡ አሁንም ወንዱ ንሥር ከእንጨቱ የውድቀት ፍጥነት ቀድሞ ያንን እንጨት በመያዝ ለሴቷ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡ እንዲህ ያለው ፈተና ወንዱን ለሰዓታት ያህል ይጠብቃዋል፡፡ ከፍታው እየጨመረ፣ እንጨቱም ይበልጥ እየተወረወረ ይሄዳል፡፡ ሴቷ ንሥር ወንዱ ንሥር ፈጣንና የተወረወረለትን ለመያዝ ያለውን ቆራጥነት እስክታረጋግጥ ድረስ ፈተናው ይቀጥላል፡፡ በመጨረሻም ቆራጥና ፈጣን፣ ማንኛውም ችግር የማይበግረው መሆኑን ስታረጋግጥ ባልነቱን ትፈቅድለታለች፡፡

ንሥርም እንዲህ ትልሃለች፡- በግላዊ ሕይወትህ፣ በንግድህም ሆነ በሌላው ኑሮህ ከሰዎች ጋር መወዳጀት፣ አብሮ መሥራትና መንገድ መጀመር ያለብህ ለዓላማቸው ምን ያህል ጽኑና ቆራጥ፣ ትጉና አይበገሬ መሆናቸውን አረጋግጠህ መሆን አለበት፡፡ ሳታረጋግጥ መግባት ትርፉ ፀፀት ነው፡፡ እንኳን ሌሎችን ራስህንም ለአዲስ ተልዕኮ ከማሠማራትህ በፊት ፈትነው፡፡

ንሥር በሕይወቱ የሚመጡ ለውጦችን እንደመጡ በአጋጣሚ አይቀበላቸውም፡፡ ተዘጋጅቶና ዐቅዶ እንጂ፡፡ ሴቷ ዕንቁላል የመጣያ ጊዜዋ ሲደርስ ባልና ሚስቱ ዕንቁላል ለመጣያ ምቹና ተስማሚ የሆነውን ቦታ ያፈላልጋሉ፡፡ ያ ቦታ ማንኛውም ዓይነት ጠላት የማይደርስበት፣ ከከፍታዎች ሁሉ በላይ የሆነና ከማንኛውም ዓይነት አደጋ  ራስንና ልጆችን ለመከላከል የሚመች መሆን አለበት፡፡ ቦታው በባልና ሚስቱ ከተመረጠ በኋላ ወንዱ ወደ መሬት ወርዶ እሾህ ለቅሞ ወደ ተራራው ንቃቃት ያመራል፡፡ በዚያም ይደለድለዋል፡፡ ከዚያም ለሁለተኛ ጊዜ ወርዶ አስፈላጊ የሆኑትን እንጨቶች ሰብስቦ ወደ ንቃቃቱ ይመጣና በእሾሁ ላይ ይረመርመዋል፡፡ እንደገና ለሦስተኛ ጊዜ ወደ ምድር ይመለስና እሾህ ሰብስቦ ወደ ጎጆው ያመራል፤ በእንጨቱም ላይ ይረበርበዋል፡፡ ለአራተኛ ጊዜ ወደ መሬት ተመልሶም ለስላሳ ሣር ያመጣና በእሾሁ ላይ ያነጥፋል፡፡ በአምስተኛ ጉዞውም እሾህ አምጥቶ በሣሩ ላይ ያደርጋል፡፡ በስድስተኛ ጉዞውም በእሾሁም ላይ ሣር ይነሰንሳል፡፡ በመጨረሻውና በሰባተኛ ሥራው ላባዎቹን በመካከል ላይ ያደላድላቸዋል፡፡ በጎጆው ዙሪያ የተደረገው እሾህም ዙሪያውን ከጠላት ያጥርለታል፡፡
እነሆ ንሥር እንዲህ ይልሃል፡- ምንጊዜም ለለውጥ ራስህን አዘጋጅ፡፡ ነገሮች ድንገት እንዲደርሱብህ ዕድል አትስጣቸው፡፡ አስበህ፣ ተዘጋጅተህ፣ ወስነህ፣ ሂሳብ ሠርተህ እንጂ፡፡ ኑሮህ በድንገቴና በአጋጣሚ የተሞላ አይሁን፡፡ የቻልከውን መጠን ያህል ተዘጋጅ እንጂ፡፡ መጽሐፉስ ‹ተዘጋጅታችሁ ተቀመጡ› አይደል የሚለው፡፡ ለማደግ ተዘጋጅ፣ ለመማር ተዘጋጅ፣ ለጓደኝነት ተዘጋጅ፣ ለማግባት ተዘጋጅ፣ ለመውለድ ተዘጋጅ፣ አዲስ ሥራ ለመሥራት ተዘጋጅ፣ ቤት ለመሥራት ተዘጋጅ፣ መኪና ለመግዛት ተዘጋጅ፣ ለምትለውጣቸው ነገሮች ሁሉ ቅድመ ዝግጅት ይኑርህ፡፡
ንሥር ትዳሩን በእኩልነት ነው የሚመራው፡፡ ወንዱ ንሥር ጎጆውን ሠርቶ ሲጨርስ ሴቷ ወደ ጎጆው ትገባና ዕንቁላል መጣል ትጀምራለች፡፡ ትዳርን በእኩልነት ነው የሚመሩት፡፡ እርሷ ዕንቁላል ስትጥል እርሱ ደግሞ አካባቢውን ከጠላት ይጠብቃል፡፡ ወደ መሬት እየተመላለሰም ምግብ ይሰበስባል፡፡ ልጆችን መመገብ፣ ማሳደግ፣ በረራ ማለማመድ፣ ከጎጇቸው ርቀው እንዲያድኑ ማሠልጠን የሁለቱም የጋራ ኃላፊነት ነው፡፡ ድርሻ ይካፈላሉ እንጂ አንዱ የበላይ አንዱ የበታች አይሆኑም፡፡
ስለዚህም ንሥር እንዲህ ይልሃል፡- ትዳር የእኩልነት ጉዞ ነው፡፡ የሥራ ድርሻ ክፍፍል እንጂ የበታችና የበላይ ክፍፍል አይኖረውም፡፡ ሁሉም የችሎታውንና የተፈጥሮውን የሚያደርግበት፣ የጋራ ኃላፊነት የሚወሰድበት ቤት ነው ትዳር፡፡
ንሥር ልጆቹን ደስታንም መከራንም ያስተምራቸዋል፡፡ የንሥር ጫጩቶች አምሮና ደኅንነቱ ተጠብቆ በተሠራው ጎጆ ይፈለፈሉና ወላጆቻቸው እየመገቧቸው እዚያ ጥቂት ያድጋሉ፡፡ ለዐቅመ ንሥር ሲደርሱ የምቾቱ ድልቅቂያ ያበቃና ሴቷ ንሥር ጫጩቶቹን ከጎጆዋ እያወጣች ዐለቱ ላይ ትጥላቸዋለች፡፡ ጫጩቶቹ በፍርሃት ይዋጡና ተመልሰው ወደ ጎጆው እየዘለሉ ይገባሉ፡፡ ይህ እንግዲህ ማደፋፈሪያ ነው፡፡ የማያድሩበት ቤት አያመሻሹበትም ይባል የለ፡፡‹ሰው እናትና አባቱን ይተዋል› የሚለው በእነርሱም መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ሊኖር ይችላል ማን ያውቃል፡፡ ለጥቂት ጊዜያት እንዲህ ታለማምዳቸውና በቀጣዩ ጊዜ ከጎጆው አውጥታ ወደ ዐለቱ በመጣል የጎጆውን ለስላሳውን ክፍል ታነሣባቸዋለች፡፡ እነርሱም እንደለመዱት ወደ ጎጆው ሮጠው ዘለው ሲገቡ እሾሁ ይቀበላቸዋል፤ ያቆስላቸዋል፣ ያደማቸዋልም፡፡ እነርሱም እንዲያ የሚወዷቸው እናትና አባታቸው ለምን እንደሚያሰቃዩዋቸው ግራ እየገባቸው ወደ ዐለቱ ተመልሰው ይወጣሉ፡፡
ከጎጆው ውጭ በአድናቆት መቆማቸውን የምታየው ኣናታቸው ከዐለቱ ገፋ ታደርጋቸውና አየር ላይ እንዲንሳፈፉ ትለቃቸዋለች፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ አየሩን የቀዘፉት ጫጩት ንሥሮች በፍርሃትና በድንጋጤ ተውጠው ወደ ታች ሲወረወሩ አባታቸው ይመጣና ከመውደቃቸው በፊት ቀልቦ በትከሻው ተሸክሞ ወደ ዐለቱ ያወጣቸዋል፡፡ እነርሱም በደስታ ይዋኛሉ፡፡ እናት ስትወረውር፣ አባት በአየር ላይ ሲቀልብ፣ ልጆችም ሲወረወሩና ሲጨነቁ፣ አባታቸው ሲቀልባቸው ሲደሰቱ ጥቂት ጊዜያት ያልፋሉ፡፡ በአካል እየጠነከሩ፣ ከመከራውም ከደስታውም እየተማሩ፣ አካባቢውንም እየለመዱት ይሄዳሉ፡፡ በመጨረሻም ራሳቸውን ችለው ይበራሉ፡፡ ከወላጆቹ ጋር ኖሮ የሚያረጀውን ቢያዩ ኖሮ ንሥሮች ምን ይሉ ይሆን?
ለዚህ ነው ንሥር እንዲህ የሚለው፡- ለልጆቻችን ከልክ ያለፈ ክብካቤ መስጠት የትም አያደርሳቸውም፡፡ መከራውንም፣ ችግሩንም፣ ፈተናውንም፣ ትግሉንም፣ ተግዳሮቱንም እንዲለምዱት ማድረግ አለብን፡፡ አፈር አይንካህ፣ የፈሰሰ ውኃ አታቅና፣ ማንም በክፉ አይይህ፣ እንደ ዕንቁላል ትሰበራለህ፣ እንደ መስተዋት ትሰነጠቃለህ እያሉ ነገ በእውኑ ዓለም የማያገኙትን ቅንጦትና ምቾት ብቻ ማሳየቱ የትም አያድርሳቸውም፡፡ እሾሁንም፣ ዐለቱንም፣ መወርወሩንም፣ መውደቁንም፣ መታገሉንም፣ ማሸነፉንም ይልመዱት፡፡ ነገን በጥቂቱ ዛሬ እናሳያቸው፡፡ የሚወዱን ሰዎች ማለት የሌለ ገነት ፈጥረው የሚከባከቡን ማለት ብቻ አይደሉም፡፡ ሰው መሆን ለሚያጋጥመው ተግዳሮት ሁሉ ዝግጁ እንድንሆን የሚያደርጉን እንጂ፡፡ ቤት ሣርና ላባ ብቻ ሳይሆን እሾህም ሊኖረው ይገባል፡፡
ንሥር ሲዳከም የት መሄድ እንዳለበት ያውቃል፡፡ ንሥር ሲዳከም ላባዎቹ ደካሞች ይሆናሉ፡፡ እንደቀድሞው በፍጥነት እንዲበር፣ ወደ ላይም እንዲመጥቅ አያስችሉትም፡፡ እንደ በረቱ መዝለቅ የለ፡፡ ጉልበቱ ሲደክም፣ ላባው ሲነጫጭና የሞት ሽታ ሲሸተው፣ ጉልበቱ ሳይከዳው በፊት ወደ አንድ ማንም ወደማይደርስበት የተራራ ጫፍ ያመራና በንቃቃቶቹ መካከል ጎጆ ሠርቶ ይቀመጣል፡፡ እዚያ ምግቡን አከማችቶ ያርፋል፡፡ የጽሞና ጊዜም ይወስዳል፡፡ የተረፉትን ላባዎቹን እየነጨ መለመላውን ይቀራል፡፡ ቀስ በቀስም አዲስ ላባ ያበቅላል፡፡ ኃይሉም እንደ ጥንቱ ይታደሳል፡፡ ያን ጊዜ ወደ ቀድሞ ኑሮው በአዲስ ጉልበትና በአዲስ መንፈስ ይመለሳል፡፡
እናም ንሥር እንዲህ ይልሃል፡- ጉልበትህና መንፈስህ፣ ሐሳብህና የማመንጨት ዐቅምህ ሲዳከም ዝም ብለህ አትናውዝ፤ እስክትደከርትም አትሟዘዝ፡፡ ነገሮች እንጨት እንጨት ሲሉህ፣ የማስቲካው ቃና ሲያልቅ፣ የሸንኮራው ጣዕም ሲሟጠጥ ‹ደኅና ነኝ› እያልክ ራስህን አትሸንግል፡፡ ይልቅ የት መሄድ እንዳለብህ አስብ፡፡ የጽሞና ጊዜ ውሰድ፤ ለአእምሮህ ምግብ የሚሆኑህን ሰብስብና መንን፡፡ የማሰቢያ፣ የማሰላሰያም ጊዜ ውሰድ፡፡ የድሮ ሐሳቦችህን እንደ ላባዎቹ ነቃቅል፡፡ በቃኝ በል፡፡ ጊዜ ወስደህ ካሰብክ፣ ካነበብክ፣ ከመረመርክ፣ ካሰላሰልክ፣ ካወጣህና ካወረድክ አዳዲስ መንገዶች፣ አዳዲስ ሐሳቦች፣ አዳዲስ ነገሮች፣ አዳዲስ አመለካከቶችን ማብቀል ትችላለህ፡፡ ያን ጊዜ በአዲስ ጉልበት እንደገና ለመመለስ ትበቃለህ፡፡
እንደ ሰው ብትፈጠርም እንደ ንሥር ኑር፡፡
(መረጃ የሰጠኝን የሲያትሉን ኃይለ ኢየሱስ አመሰግነዋለሁ)
© ሁለቱም ክፍሎች በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ ወጥተዋል

ዛሬ ከቀኑ 8፡00 በአራዳ ምድብ ችሎት ሐብታሙ አያሌው ዳንኤል ሺበሺና የሺዋስ አሰፋ እንደሚቀርቡ በመነገሩ ብዛት ያላቸው ሰዎች ቀደም ብለው በፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ተገኝተው ነበር፡፡ፖሊስ በፍርድ ቤቱ የተሰጠውን የቀጠሮ ሰዓት አክብሮ እስረኞቹን ማቅረብ በመቻሉ ላይ ብዙዎች ስጋት የነበራቸው ቢሆንም አልተሳሳቱም፡፡ መደበኛው የስራ ሰዓት ከተጠናቀቀ በኋላ ከፍተኛ ታጣቂ ሃይል የፍርድ ቤቱን ቅጥረ ግቢ ተቆጣጠረው ከደቂቃዎች በኋላም […]

ጆን ኬሪ ትላንት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝንና የኢጋድ ማለት የምስራቅ አፍሪቃ የልማት ትብብር በይነ-መንግስታት መሪዎችን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ መስርያ ቤታቸው ተቀብለው ሲያነጋግሩ ኢትዮጵያን በክልሉ መሪነት ሚናዋ አሞግሰዋል።

ሐምሌ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዞኑ ፖሊሶች ትናንት ከሌሊቱ 10 ሰአት ላይ ወደ ሰማያዊ ፓርቲ የአርባ ምንጭ አመራሮች መኖሪያ ቤት በመሄድ ፍተሻ ካደረጉ በሁዋላ ፣ አመራሮችን ወስደው አስረዋቸዋል። የፍርድ ቤት ማዘዣ ይዘናል በማለት ፍተሻ ያካሄዱት ፖሊሶች በአንደኛው ቤት ውስጥ ሁለት ፍሬ ጥይቶችን ማግኘታቸውን ሲያስታወቁ፣ በሌሎች መኖሪያ ቤቶች ደግሞ ቪዲዮ ካሜራዎችን፣ ፊልሞችንና የተለያዩ ወረቀቶችን ሰብስበው …

ሐምሌ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው ሃምሌ ወር ጀምሮ በከተማው የታየው ከፍተኛ የውሃ እጥረት በአሁኑ ጊዜ አሳሳቢ ደርጃ ላይ መድረሱን ነዋሪዎች ገልጸዋል። አንድ የከተማው ነዋሪ ውሃ በቦቴ ጭነው አንድ ጀሪካን ውሃ በ10 ብር እየሸጡ ሲሆን፣ አብዛኛው ነዋሪ ደግሞ ወንዝ ውሃ በመጠቀም ችግሩን ለማለፍ እየሞከረ ነው። ” ከፍተኛ ችግር ውስጥ ነው ያለነው፣ ስለ ንጹህ ውሃ …

ሐምሌ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከ40 በላይ አፍሪካ መሪዎችን በአንድ ጊዜ ጋብዘው በማነጋገር ላይ ያሉት የአሜሪካው መሪ ፕ/ት ባራክ ኦባማ አፍሪካ እያደገችና ጠንካራ አህጉር እየሆነች መሆኑን ተናግረዋል። ከዚህ ቀደም እንደነበረው ሳይሆን አፍሪካ በአለም ላይ ተጽእኖ ፈጣሪ መሆን መጀመሩዋን ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል። የአፍሪካ ስኬት ከወጣት ህዝቦቿ ጋር የተያያዘ መሆኑንም ፕሬዚዳንቱ አክለዋል። አሜሪካ በአፍሪካ የጸጥታ ስራ ለመስራትና …

 

 

 

እኛ ከአፍሪካ የተፈጥሮና የከርሰ-ምድር ሃብቷን ብቻ ፈልገን ሳይሆን በቅድሚያ የምናየውና የምንተማመንበትም የሰው ሃብቷ ነው ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ በአፍሪካ ላይ ያላቸውን የወደፊት ተስፋና እምቅ አቅም አድንቀው ተናግረዋል፡፡

 

የእርሣቸው መንግሥት ፍላጎት በአፍሪካና በአሜሪካ መካከል ያለው2ን ሥራና መተጋገዝ አሁን ባለው ሁኔታ እንዲቀጥል ማድረግ ሳይሆን ከፍ ወዳለ ደረጃ እንዲሸጋገር መሥራት ነው ብለዋል፡፡

በመላ አፍሪካ ለሚንቀሣቀሱ የግልና የመንግሥት አጋርነት ሥራዎችን ለማገዝ የተገኘው ገንዘብ ዋሺንግተን ዲሲ ላይ እየተካሄደ ላለው የአሜሪካ-አፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ ትናንት እርሣቸው ንግግር ያደርጉ እስከነበረበት ጊዜ 33 ቢሊየን ዶላር መድረሱን አስታውቀዋል፡፡

ለዝርዝሩ…

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

አዲስ አበባ የሚገኘው የብሪታንያ ኤምባሲ ሰራተኞች የመን ካለፉት ስድስት ሳምንታት በፊት ለኢትዮጵያ መንግሥት አሳልፋ የሰጠቻቸው እና በእስር የሚገኙትን የግንቦት ሰባት የፍትህ የነፃነትና የዴሞክራሲ ፓርቲ ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለመጎብኘት ያደረጉት ሙከራ ሳይሳካ መቅረቱ ተገለጸ።

ኢትዮጵያ ከአበባ፣ አታክልትና ፍራፍሬ የውጭ ገበያ በዚህ ዓመት ብቻ ከ245 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንዳገኘች የኢትዮጵያ ዘርፉ ልማት ተቋም ዋና ዳሬክተር አቶ ዓለም ወልደገሪማ ለዶይቸ ቬለ ዛሬ ገለጹ።

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት -አምነስቲ ኢንተርናሽናል የናይጀሪያ ጦር የሰብዓዊ መብት ረገጣ ፈፅሞዋል ሲል ወቀሳ ሰንዝሯል። ይህንን ወቀሳ የናይጄሪያ የመከላከያ ሚኒስቴር ዝም ብሎ አላለፈውም።

በሜክሲኮ አደባባይ የሚገኘው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ባለፈው የረመዳን ጾም ወቅት በአንዋር መስጊድ በተካሄደው ረብሻ ላይ ተሳትፋችኋል በሚል የተጠረጠሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባል ወይንሸት ሞላን እና የአዲስ ጉዳይ የፎቶ ጋዜጠኛ አዚዛ ን ጉዳይ

አርባ ምንጭ ከተማ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ የዞኑ አስተባባሪዎች በፖሊስ ተይዘው መታሰራቸው ታወቀ፡፡ ትናንት ሐምሌ 29 ሌሊት የዞኑ ሊቀመንበር አቶ ሉሉ፣ አቶ ፈቃዱ አበበና አቶ ጌታሁን በየነ ከየ ቤታቸው በፖሊስ ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ የተወሰዱ ሲሆን አሁን ያሉበት ቦታ እንደማይታወቅ ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡
አመራሮቹ በፖሊስ በተያዙበት ወቅት ቤታቸው እንደተበረበረና የፓርቲው አባላት አርባ ምንጭ በሚገኘው የፓርቲው ቢሮ እንዳይገቡ ቢሮውን ከበው የሚገኙ ፖሊሶች እየከለከሉ መሆኑም ለማወቅ ተችሏል፡፡
በሌላ በኩል በዞኑ በየ ወረዳው የሚገኙትን የፓርቲው አባላት ከሰማያዊ ፓርቲ እንዲወጡ ጫና እየጠደረገባቸው እንደሚገኝ የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ ገልጸዋል፡፡

ንሥር እጅግ ግዙፍ ከሆኑ የአዕዋፍ ዝርያዎች አንዱ ነው፡፡ ክብደቱ እስከ 6.7 ኪሎ ሲደርስ ቁመቱ ደግሞ ከአንዱ ክንፉ ጫፍ እስከ ሌላው ጫፍ ድረስ 2 ሜትር ተኩል ይደርሳል፡፡ በዓለም ላይ እስከ ስድሳ የሚደርሱ የንሥር ዝርያዎች ይገኛሉ፡፡
በኢትዮጵያ ጥንታዊ ሥነ ጽሑፍ ውስጥ ንሥር የትንሣኤ ሙታን፣ አርቆ የማሰብ፣ ወደ ላይ የመምጠቅና የመነጠቅ፣ የጥበቃና የምናኔ ተምሳሌት ሆኖ ተገልጧል፡፡ ግብጻውያን ደግሞ የተቀበሩ ሰዎችን አጋንንት እንዳይደርሱባቸው በመቃብራቸው በር በድንጋይ ላይ የንሥርን ምስል ያስቀርጹ ነበር፡፡ ይጠብቃቸዋል ብለው፡፡ በግሪክ አፈ ታሪክ የአማልክት ንጉሥ የሚባለው ዜውስ በንሥር የሚመሰል ነበር፡፡ ጥንታውያን የአሜሪካ ሕዝቦች እጅግ ለሚያከብሩት የሌላ ወገን ሰው የንሥርን ላባ በመስጠት ክብራቸውንና ፍቅራቸውን ይገልጡ ነበር፡፡ ሞቼ የተባሉት የፔሩ ሕዝቦችም ንሥርን ያመልኩት ነበር ይባላል፡፡
ንሥር ይህንን ያህል ቦታ በሕዝቦች ባሕል ውስጥ ሊይዝ የቻለው በተፈጥሮው በታደላቸው የተለያዩ ጸጋዎች የተነሣ ነው፡፡ 

ንሥር ከእንስሳት ሁሉ ወደ ሰማይ በመነጠቅ የሚተካከለው የለም፡፡ እርሱ የሚደርስበትን የሕዋ ከፍታ የትኛውም ዓይነት ወፍ አይደርስበትም፡፡ አንዳንድ አዕዋፍ እስከ ተወሰነ ድረስ ቢከተሉትም እንኳ እርሱ ግን ጥሏቸው ማንም በማይደርስበት የሰማይ ጥግ ብቻውን ይንሸራሸራል፡፡ ለዚህም ነው ጥንታውያን ሰዎች በሐሳብ የመምጠቅ፣ ማንም ከማይደርስበት የጸጥታ ሕዋ ላይ አእምሮን የማሳረግ፣ ተራ ነገር ማሰብና ተራ ነገር መሥራት ከሚችሉ ደካማ ልቦች ርቆ በሉዓላዊ ሐሳብ ላይ የመምጠቅ ምሳሌ ያደረጉት፡፡
ታድያ ይኼ ንሥር እንዲህ ይልሃል፡- ከቁራዎችና፣ ከሌሊት ወፎች፣ ከጥንብ አናሣዎችና ከድንቢጦች፣ ከተባዮችና ከነፍሳት ጋር እዚህ ምን ታደርጋለህ? በወረደ ሐሳብ ለምን ትመስላቸዋለህ? ውጣ ወደላይ፤ ሂድ ዐርግ፣ ምጠቅ ተመሰጥ፣ እስከ ተወሰነ ቦታ ድረስ ዝንብና ትንኝ፣ እስከ ተወሰነ ቦታ ድረስም ነፍሳት፣ እስከ ተወሰነም ቦታ ድንቢጦችና የሌሊት ወፎች፣ እስከ ተወሰነውም ቁራዎችና ጥንብ አንሣዎች ይከተሉህ ይሆናል፡፡ ሐሳብህን ከፍ፣ አእምሮህንም ሉዓላዊ፣ ልቡናህንም ምጡቅ፣ አመለካከትህንም ከፍ ያለ ባደረግከው ቁጥር ግን ደካቹ ከሥር እየቀሩ ከሚመስሉህ ከንሥሮች ጋር ብቻ በጸጥታው ሕዋ ላይ ትንሳፈፋለህ፡፤ ሂድ ዐርግ፡፡
ንሥር እጅግ አስደናቂ የሆነ የማየት ችሎታ የተሰጠው ፍጡር ነው፡፡ እስከ አምስት ኪሎ ሜትር በሚደርስ ርቀት ውስጥ አንዲትን ትንሽ ጥንቸልን አንጥሮ ማየት ይችላል፡፡ የንሥር ዓይን ከጭንቅላቱ በተነጻጻሪ ሲታይ እጅግ ታላቅ ነው፡፡በንሥር ዓይን ውስጥ በአንድ ሚሊ ሜትር ስኩዌር ረቲና አንድ ሚሊዮን ለብርሃን ስሱ የሆኑ ሴሎች አሉት፡፡ ሰዎች ስንት ያለን ይመስላችኋል? ሁለት መቶ ሺ ብቻ፡፡ የንሥር አንድ አምስተኛ ማለት ነው፡፡ ሰው ሦስቱን መሠረታዊ ቀለሞች ብቻ ማየት ሲችል ንሥር ግን አምስቱን ማየት ይቻለዋል፡፡ እንዲያውም ከሩቁ አንጥሮ በማየት ንሥርን የሚተካከለው እንስሳ የለም የሚሉ ጥናቶችም አሉ፡፡
ንሥር የሚፈልገውን ለማሰስ እስከ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ዙሪያ ይዞራል፡፡ ሲያገኝ ግን ሌላውን ነገር ሁሉ ትቶ በሚያድነው ነገር ላይ ብቻ ያተኩራል፡፡ ‹ሁሉ አማረሽን ገበያ አታውጧት› የሚለውን የአማርኛ ብሂልና ‹jack of every thing master of non› የሚለውን የእንግሊዝኛ አባባል በደመ ነፍስ ዐውቆታል፡፡ ከትኩረቱ ፈጽሞ ንቅንቅ የለም፡፡ ምንም ዓይነት ግርዶሽ፣ ምንም ዓይነት መሰናክል፣ ምን ዓይነት መደለያ አያዘናጋውም፣ ተስፋም አያስቆርጠውም፡፡ የዚያን የአደኑን ነገር በንቃትና በትጋት እስከ መጨረሻ ይከታተለዋል፡፡ እንዲሁ አይወረወርም፤ ጊዜና ሁኔታ ይመርጣል፡፡ ጊዜና ሁኔታ ሲገጥሙለት ትኩረቱን ሰብስቦ በመወርወር ታዳኙን ይሞጨልፈዋል፡፡
ንሥር እንዲህ ይልሃል፡- ደጋግመህ አስብ፤ ለመወሰን ጊዜ ውሰድ፤ ዙር ተዟዟር፡፡ ልፋ ድከም፤ አንድ ጊዜ ለመቁረጥ ሺ ጊዜ ለካ፡፡ በመጨረሻም ዒላማህን ለይ፡፡ አስተካክል፡፡ ትኩረትህንም በዒላማህ ላይ ብቻ አድርግ፤ ምንም ዓይነት ማታለያ፣ ምንም ዓይነት መደለያ፣ ምንም ዓይነት ማሰናከያ፣ ምንም ዓይነት ፈተና፣ ምንም ዓይነት ተስፋ መቁረጥ ከዓላማህ ሊያግድህ አይገባም፡፡ ማየትና ማሰብ ያለብህ ሁሉም ሊያየውና ሊያስበው የሚችለውን ተራ ነገር አይደለም፡፡ ሊታይ የማይችለውን ለማየት፣ ሊለይ የማይችለውን ለመለየት፣ ሊተኮርበት ያልቻለውን ለማተኮር ጣር፡፡ ዒላማህን ካገኘህ አትልቀቅ፤ ጊዜና ሁኔታ አመቻችና ዒላማህ ላይ ተወርወር፡፡ ያንተ ከመሆን ማንም አያግደውም፡፡
ንሥር በምንም ዓይነት የሞቱ እንስሳትን አይበላም፡፡ እርሱ እቴ፡፡ በሕይወት ያለውን እንስሳ የገባበት አሳድዶ፣ ከተደበቀበት ጠብቆ አድኖ ይበላዋል እንጂ እርሱ እንደ ቁራና ጥንብ አንሣ የሞተ ላይ አያንዣብብም፡፡ እንደ አራዳ ልጆች ከተበላ ዕቁብ ጋር አይጨቃጨቅም፡፡ ቀላል ነገር ቢያጣ በግና ፍየልም ቢሆን ተወርውሮ አድኖ፣ ከዐለት ላይ ፈጥፍጦ እንደ አጥንት ወዳጅ አበሻ ቅልጥም ሰብሮ ይበላል እንጂ የሞተ ጥንብ ሲያልፍም አይነካው፡፡ ያቺን ከባዷንና በድንጋይ የተሸፈነችውን ዔሊ እንኳን ከዐለት ስባሪ ላይ ከስክሶ ድንጋይዋን አራግፎ ይበላታል እንጂ  እንደ አበሻ ማን እንዳረደው ያላወቀውን ነገር አይበላም፡፡
ንሥር እንዲህ ይልሃል፡- ልቡናህንና ኅሊናህን፣ አእምሮህንና መንፈስህን ምን እንደምትመግባቸው አስብ፡፡ የሞተ፣ የማይሠራ፣ የተበላሸ፣ ጊዜው ያለፈበት፣ ቁራና ጥንብ አንሣ የሚጫወቱበትን አትመግበው፡፡ ፊልምና ፕሮፓጋንዳ፣ ዋዛና ፈዛዛ፣ የወረዱና የበከቱ አስተሳሰቦችን አትመግበው፡፡ ከተፋና ለብለብ ሐሳቦችን አትጋተው፡፡ ይልቅ አድን፣ ድከም፣ ልፋ፣ ተሟገት፣ ተመራመር፣ እንደ ዔሊ ድንጋይ የከበደውን አስተሳሰብ ገልብጠህ፣ ፈንክተህ ተመገብ፤ ድካምና፣ ጽሞና፤ ማሰብና መመርመር የሚሻውን ንባብ ውደድ፤ ሳይለፉና ሳይደክሙ እንደ ሞተ እንስሳ ሥጋ የትም የሚገኘውን ነገር ሳይሆን ጥረትና ግረት የሚሻውን፤ ላብ ጠብ የሚያደርገውን ሞያና እንጀራ ፈልግ፡፡
ንሥር ዐውሎ ይወዳል፡፡ ሰማዩ ሲጠቁርና ደመናው ሲሰበሰብ ወጀቡም ሲያይል ሌሎች አዕዋፍ በዐለት ንቃቃትና በጫካው ችፍርግ ውስጥ ይደበቃሉ፤ በቤት ታዛ ሥርም ይሠወራሉ፡፡ ንሥር ግን ደስ ይለዋል፡፡ ወጀቡና ዐውሎው ሲጀምር ንሥር የንፋሱን ኃይል በመሞገት የራሱን ጥንካሬ ይለካበታል፡፡ የነፋሱን አቅጣጫ በመከተልም ይበራል፡፡ ራሱን ወደ ላይ ለማምጠቅና የከፍታውን ጫፍ ለመጨበጥ ይጠቀምበታል፡፡ በዚያ ጠንካራ ነፋስ ትከሻ ላይ ሲጫን ነው ንሥር ዕረፍት የሚወስደው፡፡ ክንፉን ብቻ ዘርግቶ በዕረፍት ስሜት ከደመና በላይ የኃያሉን ዐውሎ ዐቅም ተጠቅሞ ይንሸራሸራል፡፡
አንተንም ንሥር እንዲህ ይልሃል፡- መከራንና ፈተናን አትፍራ፤ በወጀብና በዐውሎ ነፋስ ውስጥም ቢሆን መንገድ አለና፡፡ መከራውንና ችግሩን፤ ፈተናውንና ግብግቡን የአዳዲስ ሐሳቦች መነሻ፤ የጥንካሬህ መለኪያ፤ ዐቅምህን የምትሰበስብበት አጋጣሚ፣ ወደላይ የምትመጥቅበትና ከችግር ደመናዎች በላይ የምትንሳፈፍበት ዕድል አድርገው፡፡ እንደ ሌሎች ወፎች ከመከራው አትሽሽ፤ ከችግሩም አትደበቅ፤ መከራን ለበረከት ተጠቀምበት፡፡

(ይቀጥላል)

 

 

 

አፍሪካ ተለዋዋጭ በሆነው የአየር ንብረት ሁኔታ ውስጥ ቻይ ሆና እንድትዘልቅና በምግብ እራሷን እንድትችል አንድም ሌሎች በአፍሪካ ሊያምኑ እንደሚገባ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የአህጉሪቱን ቁርጠኝነት ወደተግባር ለመለወጥ የአሜሪካ ድጋፍ እንዲሰፋ ተጠይቋል፡፡

እነዚህ ሃሣቦች በተነሱበት በፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ጋባዥነትና አስተናጋጅነት በተካሄደው የአፍሪካ – ዩናይትድ ስቴትስ የመሪዎች ስብሰባ ላይ በተሰናዳው የአፍሪካ ተለማጭነት ወይም የተፈጥሮ አካባቢና የአየር ንብረት መለዋወጥ ቻይነትና የምግብ ዋስትና መድረክ ላይ መክሯል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ አፍሪካና ዩናይትድ ስቴትስ ተባብረው በመሥራታቸው በያዝነው የአውሮፓ ዓመት የውጭ መዋዕለ ነዋይ ፍሰቱ ሰማንያ ቢልዮን ዶላር መድረሱ ተገልጿል፡፡

በፍጥነት በማደግ ላይ የሚገኘውን…

ሐምሌ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግንቦት7 ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የጸጥታ ሃይሎች ከተያዙ በሁዋላ ሰቆቃ እየተፈጸመባቸው ያለፉት 44 ቀናትን በደብረዘይት አየር ሃይል እስር ቤት ውስጥ ካሳለፉ በሁዋላ የብሪታንያ መንግስት  የኢትዮጵያን ጉዳይ አስፈጻሚ አስጠርቶ በጽህፈት ቤቱ አነጋግሯል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርክ ሲሞንድስ አቶ አንዳርጋቸው የኮንሱላር አገልግሎት በአፋጣኝ እንዳያገኙ መደረጉ እንዳሳሰባቸው ለኢትዮጵያው ዲፕሎማት …

ሐምሌ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመለስ ዜናዊን ፋውንዴሽን እንሰራለን በሚል ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችና አርሶአደሮች በነፍስ ወከፍ ከ50 ጀምሮ እንዲያዋጡ መገደዳቸው በቅርቡ ከተደረገው የደሞዝ ጭማሪ ጋር ተያይዞ የህዝቡን ቁጣ ሊያባብሰው ይችላል ተብሎ በመሰጋቱ ፣ የገንዘብ መሰብሰቡ ሂደት ለጊዜው እንዲቋረጥ መደረጉን የኢህአዴግ ምንጮች ገልጸዋል። ፋውንዴሽኑን ለማሰራት ከሚፈለገው ገንዘብ 10 እጥፍ እንደተሰበሰበ የሚነገርለት ፋውንዴሽን በወ/ሮ አዜብ መስፍን …

ሐምሌ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዲስ አበባ ፖሊስኮሚሽንባለፉትወራትለተካታታይ 3 ወራትያክልለሁሉምመካከለኛናከፍተኛፖሊስመኮንኖች ለደህንነትስራእገዛበሚልስልጠናከሰጠ በሁዋላ፣  ከሃምሌ 26 ቀን 2006 ዓ.ምጀምሮደግሞበአዲስአበባምኒልክትምህርትቤትግቢአዳራሽውስጥበስሩለሚገኙትሁሉም የፖሊስአባሎችስልጠናእየሰጠእንደሚገኝ ታውቋል። ስልጠናውለሁሉምፖሊሶች በተለያየዙርእንደሚሰጥይጠበቃል፡፡የስልጠናው ዋና አላማ መጪውን ምርጫ ተከትሎ የፖሊሱን ሚና ማሳወቅ፣ የፖሊሶችን የፖለቲካ አቋም መገምገምና የደህንነት አጠባበቅ ስልጠና መስጠት ነው ። በስልጠናው ላይ አንዳንድ ፖሊሶች የሙስሊም ኢትዮጵያውያንን ተቃውሞ እንዲሁም የመልካም አስተዳደር፣ የኢኮኖሚና የመብት ጥሰቶችን እያነሱ …

በመንግስት ተቋማት ውስጥ ተቀጥሮ መስራት በፈቃደኝነት ድህነትን ለመውረስ ዝግጁ መሆን ማለት ነው፡፡ የመንግስት ተቋማቶች ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ድርቅ ተመትተዋል፡፡ ተስፋ የቆረጡ፤በሙያቸው የማይተማመኑ ወይም ሙያ አልቦዎች፣ በሠራተኛው ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ ያልሆኑ የእውቀት የክህሎት፣ የዝግጅት እና የተነሳሽት ድኩማኖች መናኸሪያ እየሆኑ መጥተዋል፡፡ አማራጭ አጥቶ የመንግስትን ቤት ሙጥኝ ያለ ፈጻሚ እንኳንስ አገር ሊገነባና የአፍራሽነት ሚና ነው የሚጫወተው፡፡ መንግስት በክህሎት አልቦ እና በሙያ ለምኔ ፈጻሚዎች ተከብቦ እንዴትስ ህዝብን ማገልገል ይችላል? የግሉ ዘርፍ በሰው ኃይል አደረጃጀቱ በልጦት ከተገኘ መንግስት የግሉን ዘርፍ መምራት ቀርቆ መንግስት በግሉ ዘርፍ ይመራል፡፡

http://minilik-salsawi.blogspot.com/201 … ost_3.html

Image

ሐምሌ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዓቃቤሕግ  «ሕገመንግሥታዊሥርዓቱንበአመጽለመናድ…» በሚልክስመሰረትኩባቸውያላቸውአምስት መጽሔቶችእና አንድጋዜጣእስካሁንየክስቻርጅእንዳልደረሳቸውናጋዜጠኞቹ መከሰሳቸውንእንደማንኛውምሰውየሰሙት በቴሌቪዥንመሆኑንእየተናገሩነው፡፡ የኢሳት ዘጋቢ ከአዲስ አበባ የላከው ሪፖርት እንደሚያስረዳው ጋዜጠኞቹ እንደሚከሰሱ ያወቁት ከመገናኛ ብዙሃን መሆኑ አስገርሟቸዋል። የክስ ቻርጁን ለጋዜጠኞች ልኮ ከማሳወቅ ይልቅ ይህን አይነት አካሄድ ለመጠቀም ለምን እንደተመረጠ ግልጽ አልሆነም።

ሐምሌ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-50 የሚጠጉ የአፍሪካ መሪዎች በፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ግብዣ በዋይት ሃውስ እንዲሰበሰቡ ቢደረገም፣ አለማቀፍ እውቅና ያላቸው የመገናኛ ብዙሃን ብዙም  ለጉባኤም ትኩረት አለመስጠታቸውን የሚወጡ ዘገባዎች ያመለክታሉ። አንድ ከአፍሪካ ውጭ ያለ መሪ አሜሪካን ሲጎበኝ የሚሰጠውን የመገናኛ ብዙሃን ሽፋን ያክል 50 የአፍሪካ መሪዎች ተደምረው ሊያገኙ አልቻሉም። ቢቢሲ ከአንድ መለስተኛ ዘገባ በስተቀር ሌሎች …

በሐሰት መንግስታዊ ማጭበርበሮች ሳንታለል በጋራ በመታገል ቀጣይ ድሎችን እናረጋግጥ !!!
#Ethiopia #EPRDF #UDJ #Blueparty #Ginbot7 #Medrek #MinilikSalsawi

ህዝብ መንቃቱን መረዳት እስኪያቅተው ድረስ ወያኔ ማላዘኑን ተያይዞታል።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

በሃገሪቱ ያለውን ሁኔታ በትክክለኛው መንገድ የማያስቀምጡ የወያኔ ፕሮፓጋንዲስቶች እርስ በእርሳቸው የሚጋጩ ዘገባዎችን በመስራት እና እውነትን ለመሸፋፈን በመትጋት የሕዝቦችን የማወቅ መብት ያለርሕራሄ እየተጋፉ ይገኛል። ይህ በወያኔ የፕሮፓጋንዳ አካላት የሚፈጸም ማጭበርበር እና ማደናገር የገዢውን ፓርቲ ውስጣዊ ዝርክርክነት በይፋ ያሳብቃል።ያለለውን እንዳለ ድሮ ተግንብቶ የታደሰውን እንደ አዲስ እንደተገነባ ፤ ያልተሰራውን እንደተሰራ ሕዝቡ የማያገኘውን አገልግሎት እንደሚያገኝ ወዘተ በማድረግ በሁለት እና ሶስት እጥፍ በማባዛት በመቶኛ በማስላት በመደመር በማባዛት ያሌለውን ምስል በመፍጠር ሕዝቡን እያደናበሩ ይገኛሉ።

በአለም ላይ ካሉ መንግስታት በተለየ ሁኔታ ዜጎቹን እያጭበረበረ ወደ ድህነት አዘቅት እየከተተ ያለ መንግስታዊ አስተዳደር ነኝ የሚል ቢኖር ወያኔ እና ወያኔ ብቻ ነው። የወያኔ የማይሳኩ እና የሚያደሐዩ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ፖሊሲዎች መነሻቸው የተሳሳቱ ፕሮፓጋንዳዎች ናቸው። ማንኛውንም ፖሊሲ ይሁን አዋጅ መመሪያ ይሁን ደንብ ወያኔ ሲያወጣ በተቆጣጠራቸው ሚዲያዎቹ እያጋነነ የሕዝብን ልብ ለመስቀል በመሞከር እደርስበታለው ያለው ግብ ምንግዜም እየተኮላሸ ተጨባጩን ሁኔታ ባለማገናዘብ እየካደ ስለሚጓዝ የሃገር ኢኮኖሚ የጨው ክምር በመሆኑ እየተናደበት ይገኛል።

ሕዝቡ ትክክለኛ አስተዳዳሪ ባለማግኘቱ ምክንያት እየተንገላታ በየቦታው ምሬት በበዛበት በአሁኑ ሰአት ተገቢውን አገልግሎት እንዳገኘ በማድረግ የሃሰት ፕሮፓጋንዳ በመርጨት ለማሳሳት እየተሞከር ሲኦን በቀረቡ መዝገቦች ላይ ውሳኔ መስጠት አቅቶት ወይም በቸልተኝነት አልወስንም ብሎ የሚኮፈስ ቢሮክራሲ ዜጎችን ሲያስለቅስ በአደባባይ እየታየ መፍትሔ እየተገኘ ነው የሚል ማደናገሪያ ሲቀርብ ያሳዝናል፡፡ ያሳፍራል፡፡በፍትሕ ሥርዓቱ አካባቢም ሲታይ እየወጡ ያሉ መግለጫዎችና ሪፖርቶች የሚያስገርሙ ናቸው፡፡ ፍትሕ ዘገየብን፣ ፍትሕ ተነፈግን የሚሉ በርካታ ዜጎች ባሉበት አገር ውስጥ የፍትሕ ሥርዓቱ ተደራሽነት ወደር የለውም ዓይነት ሪፖርቶች ይቀርባሉ፡፡ ሕዝቡ በየፍርድ ቤቱ በተጓደለ ወይም በተነፈገ ፍትሕ ምክንያት ከላይ ታች ሲቅበዘበዝ እየታየ የማይመስል ነገር ይነገራል፡፡ በዚህ መስክ ያለው ማደናገር ራስ ያሳምማል፡፡

በኑሮ ውድነት በትራንስፖርት በውኃ በኤሌክትሪክና በስልክ አገልግሎቶች አለመሟላት እና መቆራረጥ ምክንያት ሥራውና ኑሮው አሳር እያየበት ያለው ሕዝብ የአገልግሎቱ ተደራሽነት በዚህን ያህል በመቶ አደገ ወይም ደረሰ ሲባል ቀልድ የተያዘ ይመስለዋል፡፡ ለሳምንታት ውኃ አጥቶ የሚንከራተት ሕዝብ የውኃ ተደራሽነት ከዘጠና በመቶ በላይ ሆኗል ተብሎ ሲለፈፍበት እንዴት ይቀበላል? በኤሌክትሪክ ኃይል እጦት ምክንያት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ማምረት እያቃተውና ሕዝቡ በጨለማ ሲሰቃይ ተደራሽነቱ ይህን ያህል ደርሷል ሲባል ማን ያምናል? በሌሎች ዘርፎችም ተመሳሳይ ማደናገሪያዎች ሞልተዋል፡፡ከመሃል አገር እና ከተለያዩ ክፍለሃገሮች ገበያዎች የተገኙ ተብለው የሚቀርቡ የእህል ዋጋዎች መጋጨት የሚያስገርሙ ናቸው፡፡ ጤፍ፣ በርበሬ፣ ጥራጥሬና የተለያዩ የግብርና ምርቶች ዋጋ በወያኔ መገናኛ ብዙኃኑ ሲተነተን፣ በፍፁም ገበያ ውስጥ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ አያሳይም፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ማደናገሪያ ማንን እንደሚጠቅም አይገባንም፡፡ ህዝብ መንቃቱን መረዳት እስኪያቅተው ድረስ ወያኔ ማላዘኑን ተያይዞታል።

ስለዚህ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ አንዱ ለሌላው መረጃዎችን በማስተላለፍ ወያኔ እና ሚዲያዎቹ የሚጠቀሙበትን የማደናበሪያ ስልት በማጋለጥ እና ሊደናበር የሚችለውን የዋሁን ኢትዮጵያዊ በማስረዳት የዜግነት ግዲታችንን እየተወጣን በጋራ በመታገል ይህንን ውሸታም እና አጭበርባሪ አደናባሪ ስርአት ልናስወግደው እና ለመጪው ትውልድ እውነትን የተሞላች አገር የማስረከብ ሃላፊነት እንዳለብን ለማሳሰብ እወዳለሁ። በጋራ በመታገል ቀጣይ ድሎቻችንን እናረጋግጣለን!!1 #ምንሊክሳልሳዊ

በጥርጣሬ/ግምት ካልሆነ በቀር አስራ አራቱ መኮንኖች የት እንደገቡ አይታወቅም።
ሁለት ከፍተና የጦር መሃንዲስች ዱካቸው ደብረዘይት ከሚገኘው እስር ቤት ተገኝቷል።
ወደ መቀሌ ከዲያስፖራው ጋር ለዘረፋ የንግድ ሽርክና ኢንቨስተሮች ለመመልመል ያመሩት ጄኔራሎች ሳይቀሩ በምን እንደመጡ በማይታወቅበት ሁኔታ አዲስ አበባ ደርሰው የመሃል አገር መኮንኖች መጥፋትን ተከትሎ ያመጣውን ውጥረት በስብሰባ ሲያሹት እና ከተለያዩ ወታደራዊ ደህንነቶች መረጃ ሲሰበስቡ እንደዋሉ ታውቋል።

በሰራዊቱ ውስጥ አለመተማመን የተፈጠረው ከምን የመነጨ ነው የሚል ጥናት በዚህ ሳምንት በተካሄደበት የመሃል አገር መከላከያ መምሪያዎች ውስጥ አጋጣሚ በተገኘ መረጃ 16 ከፍተኛ የጦር መኮንኖች የት እንደገቡ አይታወቅም ሲል ሪፖርት ያቀረበው የወታደራዊ ደህንነት ቡድን የቀረበለትን ጥቆማ ለበላይ አካላት ሪፖርት ሳያድርግ ፍተሻውን አጧጡፎት የነበረ ቢሆንም ምንም አይነት ፍንጭ ባለማግኘቱ ትላንትና የተነገረው የበላይ አካል በከፍተኛ ድንጋጤ ተውጦ የዋለ መሆኑን ለጦር ክፍሎቹ ቅርብ የሆኑ ምንጮቻችን ከመከላከያ ያደረሱን መረጃ ጠቁሟል።

ከመሃል አገር በተለያየ የጦር መምሪያ ውስጥ ተመድበው ይሰሩ የነበሩት እና የአንድ ኮርስ ምሩቅ ናቸው የተባሉት ወታደራዊ መኮንኖች ውስጥ የሕወሓት ጄኔራሎች ላይ ጥርሱን እንደነከሰ የሚነገርለት ኮሎኔል አለም የሚባለውን የተንቤን ተውላጅ ጨምሮ አስረ አንዱ ወደ ደቡብ ሱዳን ዘልቀው ገብተዋል የሚል መረጃዎች ቢኖሩም እስካሁን ማረጋገጥ እንዳልቻለ ለመከላከያ ደህንነት ቢሮ ምንጮቻችን የገለጹ ሲሆን የሶስቱ ዱካ አለመገኘቱን እና ሁለት ከፍተኛ የጦር መሃንዲሶች ከየት ታፍነው በማን ታፍነው እንደተወሰዱ ሳይታወቅ በደብረዘይት የምድር ውስጥ እስር ቤት እንደሚገኙ ተረጋግጧል።

የሕወሓት ጄኔራሎችን ያመሳቸው ጉዳይ የተንቤን ተወላጆች ሌሎች የደቡብ እና የአማራ ተወላጆች ተያይዞ መጥፋት ሲሆን እንዲሁም በጦር ሰራዊቱ ውስጥ እየላላ መጥቷል ሲሉ የደነፉበት የወታደራዊ ደህንነት ቁጥጥር መላላት ለነገው የስልጣን እድሜያቸው ከፍተኛ ስጋት እንዳጠላበታ ያሳያል ሲሉ መረጃውን የላኩልን የመከላከያ ምንጮቻችን ተናግረዋል። በሙሉ የሃገሪት እዞች ከፍተኛ ቁጥጥር እና ፍተሻ እንዲካሄድ በዛሬው ስብሰባ ጥብቅ ትእዛዝ ያስተላለፉት የሕወሓት ጄኔራሎች በደቡብ እና በምእራብ ድንበሮች አከባቢ ያሉ እንቅስቃሴዎች እንዲፈተሹ በወጪ ገቢው ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር እንዲደረግ እና የየቀኑ ሪፖርት እንዲላክ እንዲሁም በመሃል አገር ያሉ የቶር መኮንኖች በየቀኑ ለቅርብ አለቃቸው ዝርዝር የአባላት እንቅስቃሴ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ጥብቅ ትእዛዝ አውርደዋል።እንዲሁም ተጨማሪ ወታደራዊ ደህንነቶች በየእዙ እንዲመደቡ አዘዋል።

በዚህ ዙሪያ ያለውን ጉዳይ በተመለከተ የወታደራዊ ደህንነት ሪፖርቶቹን እየተከታተልን የምናቀርብ መሆኑን ቃል እንገባለን።
#ምንሊክሳልሳዊ

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች