ሲአይኤን ያጋለጠው ሠነድ

የአሜሪካው የስለላ ተቋም «CIA» በሽብርተኝነት ተጠርጣሪ እስረኞችን በምርመራ ወቅት በከፍተኛ ሁናቴ ማሰቃየቱን የሚያጋልጠው ሠነድ በስተመጨረሻ ይፋ ሆኗል። የሰብአዊ መብት ተሟጋቿ ሎውራ ፒተር ሠነዱን፦ «ለበርካታ አሜሪካውያን እጅግ አስደንጋጭ ነው» በማለት ገልፀዋል።