የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ወደ አውስትራልያ ያመራሉ የሀ/ስብከቱ ሰንበት ት/ቤቶች ማ/ክፍል ሓላፊ የታገደውን አመራር ለሁከት እየገፋፋ ነው በአመራሩ የቃለ ዐዋዲ ጥሰትና ሃይማኖታዊ ሕጸጽ ምክንያት የታሸገው የድሬዳዋ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ሰንበት ት/ቤት ተከፍቶ አገልግሎቱን በጊዜያዊ ሥራ አመራር ቀጠለ፡፡ ሰንበት ት/ቤቱ እንዲከፈት የተወሰነው የካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ ከነሐሴ ፳፯ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ ሲኾን ይህም …

ኤርትራ ውስጥ የፖለቲካ ተሳትፎንና የአመራር ብቃትን ለማጠናከር ሲባል መንግስታዊ መስርያ ቤቶች በአዲስ መልክ እየተዋቀሩ እንድሆነ የሀገሪቱ ፕረዚዳንት አስታውቀዋል።

መስከረም ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ አየር ሃይል በመተው ሰሞኑን ግንቦት 7ትን  ከተቀላቀሉት አብራሪዎች እና የበረራ አስተማሪዎች መካከል የተዋጊ ሄሊኮፕተር ተዋጊና አዛዥ የሆኑት ካፒቴን አክሊሉ መዘነ ዛሬ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ በአንድ ወቅት በገናናነቱ የሚታወቀው የኢትዮጵያ አየር ሐይል አሁን ያለበት ደረጃ የሚያሳፍር መሆኑን ተናግረዋል። በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ ሰፍኖ አየር ሀይሉ ተመልሶ የሚገነባበት ጊዜ እንደሚመጣ …

መስከረም ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መስከረም 12 እና መስከረም 19 ሰማያዊ እና አንድነት ፓርቲዎች በተከታታይ የጠሩዋቸው ሰልፎች በመስቀል አደባባይ እንደማይካሄዱ የአዲስ አበባ መስተዳድር ህዝባዊ ስብሰባ ማስታወቂያ ክፍል አስታውቋል። ጽህፈት ቤቱ ይህን ያስታወቀው ከሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ጋር ውይይት ካደረገ በሁዋላ ነው። ይህንን ውሳኔ ተከትሎ ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ” ህዝባዊ አገልግሎት የሚሰጥ ቦታ ለዜጎች ሁሉ …

መስከረም ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በቆላማና ከፊል  ቆላማ በሆኑ አካባቢዎች የሚኖሩ  አርብቶአደሮች ባለፉት 20 ዓመታት በአካባቢው በተደጋጋሚ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ለከፍተኛ ጉስቁልና መዳረጋቸው ታውቋል። በቦረና ዞን ብቻ በ2005 ዓ.ም 30 ሺህ 216  እንስሳት  በድርቅ  ሲያልቁ፣  በ2004 ዓ.ም ደግሞ 10 ሺህ 609 እንስሳት አልቀዋል፡፡ በማኅበራዊ ጥናት መድረክ የአካባቢ ጉዳዮች ተመራማሪ የሆኑት አቶ  አለባቸው …

መስከረም ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፕሬዚዳንት ሙርሲ ስልጣናቸውን በሀይል ከተነጠቁበት ጊዜ ጀምሮ ግብጽ ሰላም ማግኘት አልቻለችም። የአገሪቱ  መንግስት የፕሬዚዳንት ሙርሲን ደጋፊዎች ለማደን በሚያደርጉት ጥረት አንድ የፖሊስ ጀኔራል ተገድለዋል። መንግስት በርካታ የፕሬዚዳንቱን ደጋፊዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን ሲያስታውቅ፣ ደጋፊዎቹ ግን ራሳቸውን መሰራያ በማስታጠቅ መንግስት ለመፋለም ቆርጠው መነሳታቸው ይነገርላቸዋል። መንግስት በያዘው አቋሙ ከገፋበት ግብጽ ዳግም ሶሪያ ልትሆን …

ዛሬ እንግዳችን ጋሽ አበራ ሞላ በሚል ቅፅል ሥም ፤ የሚታወቀዉ አርቲስት ስለሺ ደምሴ ነዉ። አርቲስት ስለሺ ደምሴ፤ በባህላዊዉ የሙዚቃ መሣሪያ፣ ክራር ፤ ለየት ባለ ግርፉ ይታወቃል።

ዓረና ትግራይ ፓርቲ ፣በቅርቡ 3ኛ ዐቢይ ጉባዔውን ሲያካሂድ ፤ የቀድሞው የትግራይ ክፍለ ሀገር ርአሰ-መስተዳድርና የተጠቀሰው ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ገብሩ አሥራት ሥልጣናቸውን ማስረከባቸው ተነግሯል። አቶ ገብሩ፤ ይህን ያደረጉት፤ ድርጅቱ፤ በቅርቡ

በሶማልያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች በበላይ አለቆቻችን እየተበደልን ነው አሉ። አንዳንድ የሠራዊቱ አባላት፤ በ SMS መልእክት አማካኝነት ለ DW እንደገለጹት ከሆነ የውስጥ ነጻነታቸውን እየተነፈጉ ነው። የህክምና ፈቀድ በተለይ እንደነርሱ አገላለጽ

ቀነኒሳን አንበሳ አሉት፡፡ ኃይሌንም አንበሳ አሉት፡፡ እንደምን ነው ቢሉ፡፡ አንድም አንበሳ ሲተኛ የሞተ፤ የደከመ፣ የታመመ ይመስላል፡፡ እንስሳት እየመጡ ይጎበኙታል፡፡ ያዩታል፤ አንዳንዶቹም ይራመዱታል፡፡ ሌሎቹም አንበሳው ደክሟል ብለው የአራዊት ንጉሥ እኛ ነን ይላሉ፡፡ እንደ ዝንብ ያሉትም ይወርሩታል ‹‹አንበሳ ሲያረጅ የዝንብ መጨዋቻ ይሆናል›› እንዲሉ፡፡ እርሱ ግን የሚያደርገውን ያውቃልና ዝም ይላቸዋል፡፡

ታሪክ እንደ አንድ አንበሳና አይጥ፡፡ ታሪኩስ እንደምን ነው ቢሉ እንዲህ ነው፡፡ በአንድ ጫካ የሚኖር አንበሳ ደከመውና አፉን ከፍቶ ተኛ፡፡ እንደተኛም አንዲት አይጥ መጣች፤ መጥታም አልቀረች ትዞረው ጀመር፡፡ ወደ ወገኖቿም ሄዳ አንበሳ ደክሞ ተኝቷል ብላ በሰፊው አወራች፡፡ ተመልሳም መጣችና ተጠጋችው፡፡ እርሱም ዝም አላት፡፡ እርሷም ጠጋ ብላ ጅራቷን በአፍንጫው ከተተችበት፡፡ እንዳያነጥስ ችሎ ዝም አላት፡፡ አይጧም ጠጋ ብላ አፉን ተመለከተችው፡፡ ምቹ ዋሻ መስሎም ታያት፡፡ አሁንም ተጠጋች፡፡ በመጨረሻም ያንን የተከፈተ ዋሻ ልትጎበኝ ወደ አፉ ውስጥ ዘው አለች፡፡ ያን ጊዜም አንበሳ አፉን ግጥም አደረገው፡፡ ሲጥ ብትል ሚጥ መውጫ አልተገኘም፡፡

ቀነኒሳም እንዲሁ ነው፡፡ እርሱ ከውድድር ሲርቅ ደከመ፣ ሰለቸ፣ መከነ፣ ተወ፤ ተብሎ ነበር፡፡ ሌሎችም እኛ የትራክ ላይ ንጉሦች ነን፡፡ የጎዳና ላይ ነገሥታት ነን ብለውም ነበር፡፡ እንደ አይጧም ብዙ ወሬ አውርተው ነበር፡፡ አፈፍ ብሎ ሲነሣ ግን እነዚያን ሁሉ ድል ያደርጋቸዋልና ቀነኒሳን አንበሳ ብለውታል፡፡


አንድም አንዱ አንበሳ ሲያድን ሌላው አንበሳ በሦስት ነገር ይረዳዋል፡፡ አንድም አካባቢውን በመጠበቅ፣ አንድም ታዳኙን በማድከም፣ አንድም አዳኙን በማጀብ፡፡ ኃይሌም እንዲሁ ነው፡፡ ቀነኒሳን በለንደኑ ሩጫ በሦስት ነገር ረድቶታል፡፡ አንድም የሩጫውን ሂደትና ድል በመጠበቅ፣ አንድም ሞ ፋራህን በማድከም፣ አንድም ቀነኒሳን በማጀብ፡፡ አንበሳ ሲያጠቃ በቡድን ነው፡፡ ኃይሌና ቀነኒሳም በቡድን አጥቅተዋልና አንበሶች ተብለዋል፡፡ ኃይሌ ከቀናት በፊት ስለ ሞ ፋራህ የሰጠው አስተያየትና ለቀነኒሳ የሰጠው ምክር ለለንደኑ የቀነኒሳ ድል ረድቶታልና ኃይሌን አንበሳ ብለውታል፡፡

አንድም ኃይሌን በስፖርተኛ የዕርግን ዘመኑ ባስመዘገበው ውጤት አንበሳ ብለውታል፡፡ እንደምን ነው ቢሉ፡፡ አንበሳ ቢያረጅም እንኳን ፈጽሞ ካልወደቀ በቀር እንስሳት አይተው ይፈሩታል፡፡ እርሱም ተንቀሳቅሶ በዐቅሙ ያድናቸዋል፡፡ ኃይሌም ምንም በዕድሜ ቢገፋ ሯጮች አይተው ይፈሩታል፡፡ ሮጦም ድልን በዐቅሙ ያድናልና አንበሳ ብለውታል፡፡

ነገር እንደ ተረትና ምሳሌ

አንበሳ ተኝቶ ፍየል ዘለለችው

ንቆ ቢያሳልፋት ሞኝ አደረገችው

አንድም አንበሳ በሦስት ነገር ተፈርቶ ይኖራል፡፡ አንድ በድምጹ፣ ሁለት በግርማ ሞገሱ፣ ሦስት በክርኑ፡፡ በድምጹ እንደምን ነው ቢሉ አንበሳ ገና ከሩቁ ሆኖ ሲጮኽ ሲሰሙት እንስሳቱ ሁሉ ይርዳሉ፣ ይንቀጠቀጣሉ፡፡ በግርማ ሞገሱስ እንዴት ነው ብለው ቢጠይቁ አንበሳ ባይጮኽም ባይባላም በጫካው ውስጥ ጎምለል ጎምለል ሲል እንስሳቱ ፈርተው ይሸበራሉ፡፡ በክርኑስ እንደምን ነው ያሉ እንደሆን በእግሩ ርግጥ አድርጎ በክርኑ አድቅቆ ይመገባልና ነው፡፡ ቀነኒሳም አንበሳ ነው ሲሉ ምንም ባያሸንፍ እንኳን እዚህ ውድድር ላይ ሊወዳደር ነው፣ ሊሮጥ ነው ሲባል አብረውት የሚሮጡ ሁሉ ይፈራሉ ይርዳሉ፡፡ አንድም ምንም ባያሸንፍ እንኳን እርሱ በውድድሩ ውስጥ ገብቶ ሲሮጥ ሲያዩት ድል ይነሣን ይሆናል ብለው ብዙዎቹ ሯጮች ይሸበራሉ፡፡ አንድም አምርሮ የሮጠ እንደሆነ ደግሞ ኃያላኑን ከኋላው አስከትሎ ድል በኃያል ክንዱ ድል ያደርጋቸዋልና ነው፡፡

አንድም አንበሳ ከአፍሪካ ሄዶ በእንስሳት ማቆያ ውስጥ ካልሆነ በቀር በፈረንጅ አገር አይገኝም፡፡ እንደ ቀነኒሳ ያለ ሯጭም ከአፍሪካ ሄዶ ለሰው ሀገር ይሮጥ ይሆናል እንጂ በፈረንጅ አገር አይገኝምና ቀነኒሳን አንበሳ ብለውታል፡፡ አንድም አንበሳ የሀገራችን የጀግንነት፣ የአልበገር ባይነትና የድል አድራጊነት ምልክቷ ነው፡፡ ኃይሌና ቀነኒሳም በረሃብ፣ በችግርና በጦርነት ስሟ በክፉ የሚነሣውን ሀገራችንን በጀግንነት፣ በድል አድራጊነትና በአልበገር ባይነት እንድትታወቅ አድርገዋታልና አንበሳ ተብለዋል፡፡

ያሉንን አናብስት እያወደስን ሌሎች አናብስትን እናፈራለን፡፡ 

የአካዳሚክ እና አስተዳደር ዲኖችን መድበዋል ቋሚ ሲኖዶሱን ያጠያየቀው ምደባ አጽድቆቱን ይጠብቃል ዘላለም ረድኤት ባቀረበው የመልቀቂያ ደብዳቤ ይሰናበታል መምህራኑ ደመወዛቸው ታግዶ ያለውኃና መብራት ሁለት ሳምንት አስቆጥረው ነበር ቋሚ ቅ/ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ሳምንታዊ መደበኛ ስብሰባው÷ ከሥልጣናቸው ተገልለው እንዲቆዩ የተወሰነባቸው ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ፣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህራንና ሠራተኞችን ከኮሌጁ መኖርያ ቤቶች የማስለቀቅ፣ ደመወዝ የማገድ፣ አዲስ ቅጥር …

አስተዳደሩና ማኅበረሰቡ የመረጣቸው አስተዳዳሪ ምደባ እንዲወሰንለት ጠይቋል ሊቀ ጳጳሱ ለምደባ ያቀረቧቸው ስድስት ሠራተኞች ማንነት እያጠያየቀ ነው ቋሚ ሲኖዶስ በአህጉረ ስብከቱ አስተዳደር ላይ የቀረቡ አቤቱታዎችን እየመረመረ ነው ለደቡብ አፍሪካ የቅዱስ ያሬድ ገዳም ከአ/አ አድባራት የተሰበሰበውና በሊቀ ጳጳሱ የግል አካውንት ተልኮ የነበረው አራት ሚልዮን ብር ጉዳይ ልዩ ትኩረት እንደሚሻ ተጠቁሟል ላለፉት ሦስት ወራት ያለአስተዳዳሪ የቆየው በምድረ ሱዳን …

ለያዝነው የአውሮፓ 2013 ዓ.ም የአውሮፓ ፓርላማ የሳኻሮቭ ሽልማት ሁለት ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ሰባት ዕጩዎች ቀርበዋል፡፡

መስከረም ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ አየር ሀይል ውስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙ አራት አብራሪዎች ፣ የበረራ አስተማሪዎች ስርአቱን ከድተው ግንቦት7ትን መቀላቀላቸው ታውቋል። ከኢትዮጵያ አየር ሀይል በመለየት ግንቦት 7ትን መቀላቀላቸውን ለኢሳት ያረጋገጡት የበረራ ባለሙያዎች በአየር ሀይል ውስጥ የተንሰራፋውን ዘረኝነትና አድሮ ለርምጃው እንደገፋፋቸው አመልክተዋል። በኢትዮጵያ አየር ሀይል ውስጥ ከዘረኝነትና አድሎው ባሻገር በሰራዊቱ ውስጥ የተስፋፋው ሙስና ተቋሙን …

መስከረም ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦህአዴድ፣ ብአዴን፣ ኢህዴንና ህወሀት ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ካለፈው እሁድ ጀምሮ በየክልሎቻቸው ተሰባስበው ግምገማ እያደረጉና ስልጠናም እየወሰዱ መሆኑን ከድርጅቱ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። ለ10 ቀናት በሚቆየው ስልጠና አመራሮቹ እርስ በርስ ከመገማገም ባለፈ ስለ ልማት ሰራዊት አደረጃጀት፣ ስለ አንድ ለአምስት  አተገባበር ፣ አክራሪነትና ኪራይ ሰብሳቢነት እንዲሁም በመጪው አመት ስለሚካሄደው አገራቀፍ ምርጫ ስልጠናዎች …

መስከረም ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ ሁለቱ ፓርቲዎች የጠሩዋቸውን ሰልፎች ተከትሎ በከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የሚገኘው መንግስት በዛሬው እለት በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች የሚገኙ ሊስትሮዎችን፣ በጎዳናዎች ላይ እቃዎችን የሚሸጡትን በጸጥታ ሀይሎቹ አማካኝነት  እንዲሰበሰቡና ወደ አልታወቀ ስፍራ እየወሰዱዋቸው ነው። የሚታፈሱት ሰዎች ወዴት እንደሚወስዱ ባይታወቅም ከአንዳንድ ሰዎች  ባገኘነው መረጃ ሰዎቹ ፓርቲዎቹ ያዘጋጁት ሰልፍ እሲከጠናቀቅ ታግተው ይቆያሉ። …

«የደወሉት ቁጥር ከአግልግሎት መስጪያ ክልል ዉጪ ነዉ።» ትላለኝ አንዷ፥ «የደወሉላቸዉን ደንበኛ አሁን ማግኘት አይችሉም-» ደንበኛዉ ከጎንዎ ተቀምጦ ሊሆንም ይችላል። ብቻ -The Net work is Busy Now—-እያለች ትቀጥላለች፥ ሌለኛዋ።ያንኑ ቁጥር ደግመዉ ይሞክሩ—-መጀመሪያ ከሰሙት የተለየ መልዕክት ይሰማሉ

በኢትዮጵያ ፣ መስከረም ወር ፣ክረምት አልፎ ከባድ ደመና የሚገፍበት ሰማዩ የሚጠራበት ፤ ምድሪቱ በለምለም ሳርና በተፈጥሮ አበባ አጊጣ የምትታይበት ወቅት፣ ጥቢ ሲሆን ፣ በአንዳንድ የዓለም ክፍሎች ደግሞ ብርቱ ዝናም የሚያጋጥምበት ፣ ማዕበልም

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር በጋራ በመሆን በመጪው መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ግማሽ ሚሊዮን ሕዝብ እንደሚወጣ አስታወቀ። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በበኩሉ ሰልፉ እንዲሳካ ከሰልፉ ዋና አስተባባሪ አንድነት ፓርቲ ባልተናነሰ ሁኔታ ንቁ ተሳታፊ እንደሚሆን ገልጿል። የአንድነት ፓርቲ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስራት ጣሴ እና የመላው […]

መስከረም ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-33ቱ ፔቲሽን ፈራሚ ፓርቲዎች ባወጡት መግለጫ ፣ በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሰላማዊ ትግላቸውን ለማስፋት በተጠናከረ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ቢሆንም፣ መንግስት የህግ ጥበቃ ሊያደርግ ባለመቻሉ ከፍ ያለ ጉዳት እየደረሰባቸው ነው ብለዋል። አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ በወላይታ፣ በአርባ ምንጭ፣ በፍቼና፣ በጎባ ከተሞች በተንቀሳቀሰባቸው ወቅቶች አባሎቻቸው መደብደባቸውን፣ መታሰራቸውን፣ የሥራ መሣሪያዎቻቸውን መነጠቃቸውን፣  ለመኝታ ገንዘብ የከፈሉበት …

መስከረም ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጋዜጠኛ ርዕዮት ዐለሙን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን  እና አሜሪካዊው  ኤድዋርድ  ስኖውደንን ጨምሮ  ሰባት  ሰዎች የአውሮፓ ህብረት ለነፃነት ታጋዮች በየአመቱ ለሚያዘጋጀው የ “ሻካሮቭ ሽልማት” የ2013  ዕጩ ሆነው ተመረጡ። የአውሮፓህብረት የሻካሮቭ ሽልማት ኮሜቴ-ከህብረቱ የውጪ ጉዳይና ልማት ኮሚቴ እና ከሰብዓዊ መብት ንዑስ ኮሚቴ ጋር በመሆን ትናንት ሰኞ ይፋ እንዳደረጉት  ማላላ ዩሳፍዛይ ከፓኪስታን፣ ኤድዋርድ ስኖውደን …

መስከረም ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከ8 ሺ 800 በላይ ሰዎች በመልሶ ማልማት የተነሳ እንደሚፈናቀሉ ከክልሉ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።  ተፈናቃዮች እንደሚሆኑ ያወቁ ነዋሪዎች በከፍተኛ የኑሮ ችግር ውስጥ ወድቀናል ሲሉ አማረዋል።በአማራ ክልል በሚገኙ በሶስቱ የክልሉ ሜትሮፖሊታን ከተሞች ማለትም በባህርዳር፣ደሴና ጎንደር በመልሶ ልማት የሚፈናቀሉ 5 ሳይቶች ተለይተው ተከልለዋል፡፡  በባህርዳር  በመጀመሪያው ዙር  431 የቀበሌ ቤት ተከራዮች ፣ 2 …

መስከረም ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከስድስት አመታት በፊት በኬንያ ከተደረገው ምርጫ ጋር በተያያዘ ለተገደሉት ሰዎች ተጠያቂ የተደረጉት የአገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ዘ ሄግ በሚገኘው አለማቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት በአካል ቀርበው የመጀመሪያዋን የጉዳቱ ሰለባን ቃል አዳምጠዋል። ማንነቷ በውል ያላታወቀችው መስካሪ በረብሻው ጊዜ የደረሰውን ግፍ በዝርዝር አስረድታለች፡፤ ም/ል ፕሬዚዳንቱ ክሱን ውድቅ ማድረጋቸው ታውቋል። ሌሎች 22 …

ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሠላማዊ ትግላቸውን አድማስ ለማስፋት ከወትሮው በተሻለ ሁኔታና መተጠናከረ መንገድ በመላ ኢትዮጵያ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ ይህ እንቅስቃሴያቸው ግን ከመንግሥት የሕግ ጥበቃ ከማጣቱ የተነሳ ፓርቲዎቹ ከፍ ያለ ጉዳት እየደረሰባቸው ነው፡፡ ይህንን ሕገ-ወጥነት ሕዝቡ እንዲያውቀውና እንዲታገለው ይህንን መግለጫ ማውጣት አለስፈላጊ ሆኗል፡፡ ፓርቲዎቹ የተንቀሳቀሱባቸው ተግባራት በሕግ የተፈቀደላቸው ናቸው፡፡ አባላትን፣ ደጋፊዎችንና ሌሎችንም ዜጎች በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና […]

በሶማሊያ የተወለዱት የሴቶች ተሟጋች እና ሞዴል ዋሪስ ዲሪ ባለፈው ረቡዕ የሴት ልጅ ግርዛት ሰለባ የሆኑ የሚረዱበት «ዴዘርት ፍላወር ሴንተር» የተባለ ማዕከል በርሊን ውስጥ መርቀው ከፍተዋል።

የተመድ ዋና ፀሃፊ ባን ጊሙን በሶርያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች በኬሚካላዊ መሳርያ ማለቃቸዉን በጥብቅ አወገዙ። ዋና ጸሃፊ ባን ይህን የገለጹት በሶርያዉ የእርስ በርዕርስ ጦርነት ጅምላ ጨራሽ መሳርያ ለጥቃት ጥቅም ላይ ዋለ ከተባለ በኋላ፤

የሶማሊያ መንግሥትን ለማጠናከር እና ሰላምን ለማረጋገጥ ፣ልማትን ለማስፋፋት በሚያስችል አዲስ ዕቅድ ላይ የተወያየ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ትናንት በብራስልስ ተካሂዷል።

የዛሬው የሙዚቃ ቃና ፐሮግራም የአድማጮችን የእንኳን ለአዲስ አመት አደረሳችሁ መልእክት እና የዜማ ምርጫ ያስተናግዳል፡፡

መነኰሳቱ ገዳሙን ለቀው እንዲወጡ ዛቻና ማስፈራሪያ እየተደረገባቸው ነው አስተዳደሩ ለመነኰሳቱ ተደጋጋሚ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት አልፈቀደም ‹‹ከዚህ ቦታ ባትመጡ ይሻል ነበር፤ ብትውሉ አታድሩም!›› /ጥቃት ፈጻሚዎቹ/ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀ/ስብከት ወንጪ ወረዳ ሐሮ ወንጪ ቀበሌ በሚገኘው የሐሮ ወንጪ መልአከ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል አንድነት ገዳም ላይ የቦምብ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ፡፡ ጥቃቱ የተፈጸመው ጳጉሜ ፬ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም ምሽት …

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ምንም እንኳ የአዲስ አበባ መስተዳደር ለሰልፉ  በ12 ሰአታት ውስጥ መልስ የመስጠት ሀላፊነት የነበረበት ቢሆንም ይህን አላዳረገም።  ፓርቲው የሚጠበቅበትን ሁሉ ለሚመለከተዉ አካል የማሳወቅ ግዴታ በአግባቡ ስለተወጣና ለሰልፉም የሚያስፈልጉ ስራዎች እየተከናወኑ በመሆኑ መስከረም 12 ቀን 2006 ዓ.ም በታቀደው መሰረት ሰልፉ ይካሄዳል ብሎአል፡፡ በዚህ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ የምናነሳቸው ጥያቄዎች …

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ ከስነ ምግባር እና ፀረ ሙስና ኮሚሺን የተገኝው መረጃ እንደሚያመለክተው ከተለያዩ የፌደራል መስሪያ ቤቶች 734 ሚሊዮን 6 መቶ ሺ ብር የመዘብሩ የስራ ሃፊዎች በተጣራ መረጃ ክስ ቢመሰረትባቸውም የውሳኔ ቅጣት እንዳልተላለፈባቸው ታውቋል። ለረጅም ጊዜ በተደረገ ምርመራ ተጣርቶና መስረጃ ተገኝቶባቸው ከ2004 ዓም ጀምሮ ክስ የተመሰረተባቸው የተለያዩ የሙስና ወንጀሎች የውሳኔ ሀሳብ እንዳልተላለፈባቸው ከመሰሪያ …

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ በኢንዱስትሪ ዘርፍ ባለፈው ዓመት የተመዘገበው የወጪ ንግድ (ኤክስፖርት) አፈጻጸም እጅግ አነስተኛ እንደነበር ከኢንዱስትሪ ሚ/ር የተገኘ መረጃ አመለከተ፡፡ በ2005 የኢትዮጵያዊያን በጀት ዓመት ከጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ ከቆዳና የቆዳ ውጤቶች፣ከአግሮ ፕሮሰሲንግ፣ ከፋርማሲዩቲካልስና ከኬሚካል የወጪ ንግድ 542 ሚሊዮን  4 መቶ ሺ ዶላር ለማግኘት ታቅዶ ማሳካት የተቻለው 281 ሚሊዮን  2 መቶ ሺ  ዶላር ወይንም 52 በመቶ …

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲስ ከዓመት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ለ14 ወራት በቃሊቲ እስርቤት ከታሰሩ በኋላ  ተፈተው የወጡት ስዊድናውያን ጋዜጠኞች  ማርቲን ሺቢ እና ዩዋን ፐርሹን እንዲሁም ዓለምዓቀፍ የሰብዓዊና የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅቶች ተወካዮች፡ ጋዜጠኞችና በስዊድን የሚኖሩ በመቶ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እና ስዊድናውያን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባዘጋጀው ደብዳቤ ላይ ፊርማቸውን በማኖር  ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ  የታሰሩ ጋዜጠኞችን እንዲፈቱ ጠይቀዋል። ስዊድናውያን ጋዜጠኞች ኢትዮጵያ ውስጥ …

መስከረም ፮(ስድት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አዲስ አበባ በተለምዶ አንበሳ ግቢ ተብሎ በሚጠራው የአንበሶች ማቆያ ማእከል ውስጥ ዛሬ ከጠዋቱ 1:30 ላይ  የአንበሶች መጋቢ የነበሩ ግለሰብ በ አንበሳ መበለታቸውን ራዲዮ ፋና ዘገበ። እንደራዲዮጣቢያውዘገባአደጋው የተከሰተው   በዛሬው እለት ተረኛ ተንከባካቢ የነበሩት እና አቶ  አበራ ሲሳይ የተባሉትየአንበሶቹ መጋቢ፥ የአንበሶቹን ማዳሪያ እያጸዱ ባሉበት ወቅት ነው። ከጥንቃቄ ጉድለት ባልተዘጋው በር የገባውና  መጋቢውን ለህልፈተ ህይወት የዳረጋቸው አንበሳ ስሙ-ቀነኒሳ እንደሆነም ራዲዮው ጨምሮ ዘግቧል። የግለሰቡን ህይወት ለማትረፍ በወቅቱ በስራ ላይ የነበሩ የግቢው ሰራተኞች ጥረት ቢያደርጉም-ሳይሳካ መቅረቱንም ለማወቅ ተችሏል። የሟች አስከሬን ከመንከባከቢያ ስፍራው ወጥቶ ወደ ምኒሊክ ሆስፒታል ተወስዷል። የዚህ አይነት አደጋ  በ19 89 ዓ.ም መከሰቱ የሚታወስ ነው።

ወጣት ሮቤል ፍሊፖስ በቦስተን ማራቶን ላይ በተፈጸመው የቦምብ ጥቃት የሚጠረጠረው ዦኻር ሳርናየቭ ጓደኞች ጋር ቤቱ ውስጥ የገባ ቢሆንም አልገባሁም ሲል ለመርማሪዎች ዋሽቷል ለሚለው ክስ ጥፋተኛ አይደለሁም ብሏም።

እንደገና የተደላደለ መንግሥት ማቋቋም ይቻላት ዘንድ 22 ዓመታት የተለያየ እርዳታ ሲደረግላት የቆየችው ሶማልያ አሁንም ከዓለም አቀፍ ለጋሽ ድርጅቶችና መንግሥታት ቻንቃ አልወረደችም።