አንዱአለም አራጌ (የአንድነት ምክትል ሊቀመንበር) በኢሳት ሬዲዮና ቲቪ የ2006 የዓመቱ ምርጥ ኢትዮጵያዊ እና ዘሐበሻ ድህረ ገጽ የ2006 የዓመቱ ምርጥ ሰው ተብሎ ተሰየመ!!! ይገባዋል!! አንዱአለም እንኳን ደስ አለህ!! ለቤተስቦቹ እንኳን ደስ አላችሁ!! መጪው አዲስ ዓመት የሰላም የደስታ እና የንጻነት ዓመት እንዲሆንላችሁ የአቡጊዳ ድህረ ገጽ መልካም መኞቱን ይገልጻል!!

ውድ ኢትዮጵያን ወገኖቼ እንኳን ለአዲሱ አመት አደረሳችሁ። እዲሱ አመት ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ታላቅ ብስራት ይዞ የሚመጣ ይሁን። ያለምንም ደም መፋሰስ ይህ ዘረኛ የወያኔ ገዢ ቡድን መቃብር ገብቶ፤ ዘረኝነት፤ ጎጠኝነትና በታኝነት ከምድራችን ጠፍቶ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ተፋቅሮ ተከባብሮ፤ ሲያጠፉ የሚቀጣቸውን የሚሽራቸውን፤ ሲያለሙ የሚሾማችውን የሚሸልማቸውን መሪዎች በድምጹ መርጦ፤ የሚኖርበት፤ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከዘር ማንነቱ በፊት በኢትዮጵያ ሲምል ሲገዘት የምናይበት፤ […]

ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

በብሄራዊ በዓላት ቀን በአብዛኛው ከወደ እስር ቤት የሚሰማው ዜና አስደሳች ነበር፡፡ይህንን አጼዎቹ ፣ሰው በላው የደርግ ስርዓትና ብሶት ወለደኝ ያለን ኢህአዴግ ሲያደርጉት ቆይተዋል፡፡ በዘንድሮው አዲስ አመትም የመንግስትን ይቅርታ በማግኘት ከወዳጅ ዘመዶቻቸው የተቀላቀሉ ስለመኖራቸው ተሰምቷል፡፡በአዲሱ ዓመት ይቅርታ ከተቸራቸው እስረኞች መካከል ታዋቂ ፖለቲከኞች፣አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች አለመኖራቸው ተፈቺዎቹ በደረቅ ወንጀል ታስረው የነበሩ መሆናቸውን ለመናገር ብዙ መድከም አይጠይቅም፡፡ መንገስት ጋዜጠኛ ውብሸት […]

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አመራሮች እድሜ ልክ ተፈርዶበት በቅጣት ቤት የሚገኘውን ሰላማዊ ታጋይ አንዷለም አራጌን ‹‹እንኳን አደረሰህ አዲሱ ዓመት ፍጹም ነጻነትህን የምትቀዳጅበት እንዲሆን እንመኛለን እንታገላለንም›› በሚል ስሜት ተነሳስተው ኬክ በማስጋገር ‹‹ከአንድነት›› የሚል ጽሁፍ አጽፈውበታል፡፡ የአንዷለም ጠያቄዎች በሩን አልፈው የያዙትን ኬክ ለማስፈተሸ አስቀማሽ ጋር እንደደረሱ አስቀማሹ ኬኩንና የተጻፈበትን እየተመለከተ አንዴ ቆዮኝ ብሎ ጥሏቸው ሄደ፡፡ አስቀማሹ ሃፊዎቹን […]

መቸም የዘመን ዑደት ማለት አሮጌው አልፎ አዲሱ የሚተካበት፣ ዘር አፈር ቅሞ ወሀ ጠጥቶ በቅሎና አብቦ የሚያሸትበት መስከረም ማለትም አይደል? አዎ አዲስ ዘመናችን ምድሪቱ ጭጋግን ለብሳ፣ አራዊቱ ያጠራቀሙትን ስብ እያቀለጡ የሚኖሩበት፣ አእዋፍ ስደት የሚጀምሩበትና የሰው ልጅ አንደ በቆሎ በልብስ የሚጠቀለልበት የበረዶ ወቅት ባለመሆኑ እርግጥም አዲስ አመት ነው። በምንም መስፈርት በማንም መለኪያ ዘመን አቆጣጠራችን ለኛ ተገቢም ትክክልም […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ላለፉት ሦስት ወራት ‹‹የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት›› በሚል መሪ ቃል በመላ ኢትዮጵያ ህዝባዊ ንቅናቄ ሲያደርግ መቆየቱ የሚታወቅ ነው፡፡ በዚህም መሰረት በጎንደር፣ በደሴ፣ በባህርዳር፣ በአርባ ምንጭ፣ በጅንካ፣ በፍቼና አዳማ ከተሞች ሕዝቡን ያሳተፉ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፎች ያጋጠሙ የገዥው ፓርቲ እንቅፋቶችን እየተራመደ በተሳካ ሁኔታ ያደረገ ሲሆን በተለያዩ ከተሞች ሕዝባዊ ስብሰባዎችንም አከናውኗል፡፡ ፓርቲያችን የመጀመሪያውን ሕዝባዊ […]

አዲሱ ዓመት ለዘመናት በህዝባችን ጫንቃ ላይ የተጫነው አምባገነነዊ መንግስት በሰላማዊ ትግላችን ተሸንፎ ነፃነት እና እኩልነት የሚሰፍንበት ፤ የእምነት ተቋማት የሀይማኖት ስርአታቸውን ያለማንም ጣልቃ ገብነት የሚያከናውኑበት፤ የሰላም ፤የፍቅር እና የጤና እንዲሆን ፤ እየተመኘን ይህ እንዲረጋገጥ ፓርቲያችን ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የጀመረውን ትግል አጠናክሮ እንደሚቀጥል እንገልፃለን ፡፡ ድል የህዝብ ነው !!!! ዘለዓለማዊ ክብር ለኢትዮጵያ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ […]

እውነት የማይመስሉ ግን እውነት የሆኑ የሙስና ታሪኮች – በኢትዮጵያ። አሁን በኢትዮጵያ አቆጣጠር ወደ 2006 ተሻግረናል። ከአመት ወደ አመት ስንሸጋገር ደግሞ ያለፈውን አመት የሙስና ነገር በገደምዳሜ ዳሰስ አድርገን ብናልፍ ክፋት የለውም። በመሆኑም የስራ ባልደረባዬ ክንፉ አሰፋ “ክፍል አንድ” ብሎ በጀመረው የሙስና ጉዳይ… “ክፍል ሁለት” ብዬ እኔ ቀጠልኩበት፤ አንብቡት። የጉምሩክ ከፍተኛ ሃላፊዎች ሲታሰሩ፤ በየፊናው የነበሩ ጉምቱ ባለስልጣናት […]

አንድየ ሆይ! ያላንተ እዚህ መድረስ አይታሰብምና ከሁሉ አስቀድሜ ለከበረው ስምህ ፣ ለማይደፈር ለማይገሰሰው ሰማያዊ ክብርህ ፣ ለቸርነት ፣ ምህረት ይቅርታህ ምስጋና ይድረሰው! አባታችን አዳም ትዕዛዝክህ ተላልፎ ታላቁን ስህተት ፈጸመ ፣ ከገነትም ተባረረ ! አባት ሆይ ! አዳም አጠፋ ብለህ አልተውከንም ! የምህረት አምላክ ነህና መንግስትህን እንወርስ ዘንድ በህግ ትዕዛዛትህ እንድንመራ አዘዝከን! ዳሩ ግን ትዕዛዛት ህግ […]

ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

ጳግሜ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ላሪ እና ካሪ ዊሊያምስ የተባሉ አሜሪካውያን ባልና ሚስቶች ሃና ዊሊያምስ የተባለቸውን የ13 አመት ታዳጊ ህጻን፣ ደብድበው፣ አስርበውና አሰቃይተው ገድለዋታል። ግለሰቦቹ በተመሳሳይ መንገድ አንድ ታዳጊ ወጣት በመግደላቸው በአንደኛ ደረጃ የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለዋል። ባልና ሚስቱ ለታዳጊዎቹ ሞት እርስበርሳቸው በፍርድ ቤት መወቃቀሳቸው ታውቋል። ሁለቱም ግለሰቦች በእድሜ ልክ እስራት ሊቀጡ ይችላሉ ሲል ቢቢሲ …

ጳግሜ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ኤጀንሲ በቴሌቪዥን ቻናል አንድ እና ሁለት የአየር ሰዓት ድልድል ወጥቶላቸው በቀን የአንድ ስዓት ስርጭት የክልሎችን ተደማጭነት እና የልማት ዘገባ ለህዝቡ ለማድረስ ፣ እያንዳንዱ ክልል ለኢቲቪ በአመት አምስት ሚሊየን ብር በነፍስ ወከፍ ይከፍላል፡፡  የኢትዩጵያ ሬዲዩና ቴሌቪዥን በእየአመቱ ከክልሎች ብቻ 55 ሚሊየን ብር ገቢ ያገኛል፡፡ ክልሎች በራሳቸው ሳተለይት …

ጳግሜ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ዌልፌር ሞኒተሪንግ ሰርቬይ ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ በኢትዮጵያ 66 በመቶ የሚሆኑ ቤቶች መፀዳጃ ቤት የላቸውም፡፡ መጸዳጃዎች ካሏቸው ውስጥ 2.2 በመቶ በውኃ የሚለቀቅ፣ 63.8 በመቶ ያህሉ በጉድጓድ የሚጠቀሙ ናቸው፡፡ በሜዳ ወይም በጫካ የሚጠቀሙት 33.7 በመቶ ያህሉን ይሸፍናሉ፡፡ በጫካ ወይም በሜዳ ከሚጠቀሙት 12.5 በመቶ ያህሉ በከተማ ሲሆን 39.5 በመቶው …

የኬንያው ፕሬዚዳንት ዑሑሩ ኬንያታ ምክትል ፣ ዊልያም ሩቶና አብሮአቸው የተከሰሰው ጋዜጠኛ ጆሽዋ ሳንግ፤ ፣ በዛሬው ዕለት ደን ኻኽ ውስጥ ከዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች መርማሪ ፍርድ ቤት ፊት ቀርበው በሰጡት ቃል፤ በሰብአዊነት ላይ የፈጸምነው ወንጀል

ኢትዮጵያዊት ጉዲፈቻ ልጃቸዉን አሰቃይተዉ ገድለዋል የሚል ክስ የተመሰረተባቸዉ አሜሪካዉያን ባልና ሚስቶች በተያዘባቸዉ ወንጀል ጭብጥ የጥፋተኝነት ብይን ተወሰነባቸዉ። ለማደጎ ከኢትዮጵያ ለወሰድዋት ህጻን ሐና ዊሊያምስ በ13 ዓመትዋ ህይወትዋ እንዲያልፍ በማድረግ ጥፋተኞች ናቸዉ ሲል የወሰነዉ አንድ የአሜሪካ ፍርድ ቤት ነዉ።

( የልጅነት ልምሻ) ፖልዮ ከምስራቅ አፍሪቃ አገሮች መጥፋቱ ሲነገር ቢቆይም ሰሞኑን የወጣው ዜና እንደሚያመላክተው ሶማሊያና ኬንያ ውስጥ መከሰቱ ተሰምቷል።

የኬንያ ምክትል ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ፣ በ 2000 ዓ ም፤ ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች መርማሪ ፍርድ ቤት በቆረጠው ቀጠሮ ዛሪ ደን ኻኽ ኔደርላንድ በሚገኝበት ፍርድ ቤት ቀረቡ። በኬንያ 2000 ዓ ም በነበረዉ ምርጫ ማግሥት ለሳምንታት በተካሄደው የጎሣዎች ግጭት

ዓመት በመጣ ቁጥር የግል ስኬቴን የምመዘግብበትና ዓመቱ ሲያልቅ የምለካበት አጭር ጽሑፍ አዘጋጃለሁ፡፡ ብዙ ጊዜ ከመቶ 40 እንኳን አይሳካልኝም፡፡ በሌላ ጽሑፍ በተረክኩት የመታሰር ገጠመኜ (…የቀይ ለባሾቹ ውሎና አዳር…) ፖሊሶች ወስደው ካስቀሩብኝ ብጭቅጫቂ ወረቀቶች መካከል የ2005 ዕቅዴ ይገኝበታል፡፡ በዚህ መሠረት ዓመቱ ቢደገም የማልጠላው አንድም የተሳካ ስለመሰለኝ፣ አሊያም አለመሳካቱን መለኪያ ስለሌለኝ ይሆናል ማለት ነው፡፡
2005 ብዙ የማኅበራዊ አውታር ወዳጆቼ እንደተስማሙበት አስተማሪ ነበር፡፡ እንዲያውም አንድ ወዳጄ እንዳለው ‹‹የዘንድሮው ማንነትህ፣ የአምናውን ቢያገኘው ተበሳጭቶበት በጥፊ ይመታዋል፡፡›› ማኅበራዊ አውታሮች (በተለይም ፌስቡክ) በኢትዮጵያ ወቅታዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ የሞቀ ሙግት በማስነሳት የአስተሳሰብ እና የውይይት ልምዳችንን ይሞግቱታል፡፡ ፌስቡክ ሰዎች በሙሉ ዕኩል ቢሆኑ ሊፈጠር የሚችለውን ነገር ማሳያ መሣሪያ እየሆነ ነው፡፡ ስንቶች በጥንቃቄና በስንት ልፋት የገነቡት በአንዲት ቃል የሚፈርስበት፣ ስንቶች ሊያፈርሱት የደከሙለት በሌላ አንድ ቃል የሚገነባበት መድረክ ነው፡፡ የሕዝባችን ጥንካሬም ድክመትም የሚስተዋልበት ገጽ ነው፡፡ ፌስቡክ ብስጭታችንን ማደቢያ (anger management) ትምህርት ቤት ነው፡፡ እውነቱም፣ ሐሰቱም ገዝፎ የሚታይበት ዓለም ነው፡፡ ፌስቡክ ከነድክመቱም ቢሆን መደበኛውን መገናኛ ብዙኃን (mainstream media) አጀንዳ እየሰጠ ይመግበው ጀምሯል፡፡


በኢትዮጵያ ፌስቡክ የኢንተርኔት ዕኩያ ቃል (synonym) ሆኗል ማለት ይችላል፡፡ ብዙ ጦማሪዎች ጦማራችን ሲታገድ ፌስቡክ ላይ የምንጽፈው ያንኑ በመተማመን ነው፡፡ እርግጥ ጦማር ላይ የሰፈረውም ጽሑፍ ማኅበራዊ አውታሮች ላይ ካልተጋራ አንባቢ አይጎበኘውም፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ረዣዥም ጽሑፎችን በጦማር ላይ ከማስፈር ይልቅ፣ አጫጭር የማኅበራዊ አውታር ጽሑፎች ተነባቢም፣ አሟጋችም ሆነው በማግኘት ከአጋማሽ ዓመቱ ወዲህ ትጋቴ ቀንሷል፡፡ ቢሆንም በዓመቱ ዞን ዘጠኝ እና የግሌም ጦማር ላይ ያሰፈርኳቸውን ጥቂት ጽሑፎች እዚህ ዘርዝሬላችኋለሁ፡፡ የአምናውን (2004 ሒሳብ ሲዘጋ) እና የካቻምናምናውን (ሁለት ሺህ ሦሰትን በአርባ ሁለት)ዝርዝሮቼን እዚሁ ማየት ይቻላል፡፡
የዘንድሮ ዓመት ስኬታማ ነው ያልኩባቸውን ጥቂት ነገሮች ሳልጠቅስ ማለፍ የለብኝም፤ ምክንያቱም ጽሑፉ ከርዕሱጋ ይጋጭብኛል፡፡ የመጀመሪያው ሊሆን የሚችለው፤ ምንም እንኳን ለታዳጊ ወጣቶች የተጻፈ ቢሆንም፣ ምንም እንኳን በአገርኛ ቋንቋ የተጻፈ ባይሆንም፣ ምንም እንኳን ልቦለድ ቢሆንም፣ ምንም እንኳን ብዙዎች ባያውቁትም የበኩር መጽሐፌ (‘Children of Their Parents’) የታተመለኝ በ2005 ነው፡፡ ‹ዞን ዘጠኝ› (ኢ-መደበኛ የጦማሪዎች እና አራማጆች ቡድንም) ከልቤ የማምንበትን ጉዳይ ጮክ ብዬ እንዳወራ፣ ባይበዛም ብዙዎችን የሚያነቃቃ ሥራ እንድሠራ ከዚያም በላይ ተጨማሪ የልብ ወዳጆችን እንዳገኝ የረዳኝ ከመቼውም በላይ በዘህ ዓመት ነው፤ በ2005 ‹ዞን ዘጠኝ› ተራ ቡድን ሳይሆን በብዙ ጎኑ ትምህርት ቤት ነበር፡፡ 2005 ቢደገም አልጠላም፡፡
በ2005 የጻፍኳቸው መጣጥፎች
10. ኢትዮጵያውያንፍቅር ያውቃሉ? (ከሶልያና ሽመልስ ጋር በጋራ)
12. መክሸፍእንደ ኢትዮጵያ ሚዲያመጽሔቶች(ከሶልያና ሽመልስ ጋር በጋራ)
26. ወጣትወንድ የመሆን ጣጣ (ከእንዳልካቸው ኃ/ሚካኤል ጋር በጋራ)
31. የኛኃይል (ከሶልያና ሽመልስ ጋር በጋራ)

በማሕሌት ፋንታሁን
ክቡራት የዞን 9 ነዋሪዎች ዓመቱ ከማለቁ በፊት እንዴት እንዳለፈ ለማስታወስ እንዲረዳን በማሰብ በ2005 የተከናወኑ አበይት ተግባራትን በዓመቱ የጊዜ መሥመር ላይ እንደሚከተለው ለማሳየት ሞክረናል፡፡ መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ፡፡

መስከረም
  • §  መስከረም 11/2005 የተከበሩ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ሆነው፣ የተከበሩ ደመቀ መኮንን ደግሞ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ቃለ መሐላ ፈፀሙ፣
  • §  መስከረም 17 ቀን 2005 ድምፃዊ ቴድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በሒልተን ሆቴል አንድ ሺሕ ያህል ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ጋብቻውን ፈፀመ፣
ጥቅምት
  • §  ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ አሜሪካን ሃገር ከሚገኘው የዓለም አቀፉ የሴቶች ሚዲያ ፋውንዴሽን የ2012 ‹ፅናት በጋዜጠኝነት ሥራ› የተሰኘ ሽልማት አገኘች፣
  • §  የ2005 የእስልምና ምክር ቤት /መጅሊስ/ ምርጫ በየቀበሌው ተካሄደ፣  

ሕዳር
  • §  የጋዜጠኝነት እና የኮሚውኒኬሽን ባለሙያ ዶ/ር መሠረት ቸኮል ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፣
  • §  ጠ/ሚኒስቴር ኃ/ማርያም ደሳለኝ አቶ ቴድሮስ አድሃኖምን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤አቶ ሙክታር ከድር እና ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በጠ/ሚኒስቴርነት ማዕረግ የሲቪል ሰርቪስ፣ የትራንስፖርት እና ቴክኖሎጂ ሚኒስተር፤ አቶ ከበደ ጫኔን የንግድ ሚኒስቴር እንዲሁም ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አድርገው ሾሙ፣
ታኅሳስ
  • §  በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ የወንጀል ችሎት በቀረበባት የሽብርተኝነት ወንጀል 14 ዓመታት እስርና 33 ሺሕ ብር ቅጣት የተጣለባት ጋዜጠኛና መምህርት ርዕዮተ ዓለሙ፣ በይግባኝ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የእስር ጊዜዋን ወደ አምስት ዓመታት በመቀነሱ ምክንያት ለሰበር ችሎት “በሥር ፍርድ ቤቶች ውሳኔ ላይ የሕግ ስህተት ተፈፅሟል” ስትል አቤቱታ አሰምታ፤ ሠበር ሰሚ ችሎቱ  በሰጠው የመጨረሻ የቅጣት ውሳኔ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትና ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያስተላለፉትን የቅጣት ውሳኔ አፀና፣
  • §  የአውሮፓ ፓርላማ አባላት ለጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በጻፉት ግልጽ ደብዳቤ፤ ከሽብርተኝነት እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ክስ ተመስርቶበት የ18 ዓመት እስር የተፈረደበት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በአፋጣኝ ከወህኒ ቤት እንዲለቀቅ ጥያቄ አቀረቡ፣
  • §  አራት በፍ/ቤት እስር የተፈረደባቸው የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች የ2012 የሄልማን/ሃሜት ሽልማት መሸለማቸውን፤ ተሸላሚዎቹ በእስር ላይ የሚገኙት እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ ውብሸት ታዬ እንዲሁም በሌለበት የተፈረደበት የቀድሞዋ የ“አዲስ ነገር” ጋዜጣ አዘጋጅ መስፍን ነጋሽ ሲሆኑ ጋዜጠኞቹ ሽልማቱን ያገኙት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን ለማስጠበቅ ላደረጉት ጥረት መሆኑም ተጠቅሷል፣
ጥር
  • §  የ33ቱ ፓርቲዎች ኅብረት በሚያዚያ ወር የተካሄደውን የአዲስ አበባ መስተዳደር እና በመላው ሃገሪቱ በሚካሄደው የወረዳና የክልል ምክርቤቶች ምርጫዎች ላይ ላለመሳተፍ ውሳኔ አሳለፉ፣
  • §  በአሠልጣኝ ሰውነት ቢሻው የሚመራው ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከ31 ዓመታት ቆይታ በኋላ በደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው 29ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ በቃ፤ በዚሁ የአፍሪካ ዋንጫ ላይ አዳነ ግርማ ከ37ዓመት በኋላ የመጀመሪያ የሆነችውን ብቸኛ ጎል ለኢትዮጵያ በአፍሪካ ዋንጫ አስቆጠረ፣
  • §  ኢትዮጵያየራሷን ሳተላይት ለማምጠቅናየሰው ኃይሏን ከቴክኖሎጂው ጋርለማስተዋወቅ የሚያስችል የሙከራሥራ መጀመሯን፣ በምክትል ጠቅላይሚኒስትር ማዕረግ የኢኮኖሚዘርፍ አስተባባሪና የመገናኛና ኢንፎርሜሽንቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ /ደብረ ፅዮን ገብረ ሚካኤል አስታወቁ፣
  • §  በ2004 ከሃያ ዓመት እስር በኋላ የተፈቱት ከፍተኛ የደርግ አመራር የነበሩት ኮሎኔል ደበላ ዴንሳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፣
የካቲት
  • §  ድምፃዊታምራት ሞላ ለረጅም ዓመታት ሕክምና ሲከታተል በነበረበት የደም ካንሰር ሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፣
  • §  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክርስቲያን 6ኛውን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስን አድርጋ መረጠች፣
  • §  የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ጽሑፍተባባሪ ፕሮፌሰር  የነበሩት ዶክተርዮናስ አድማሱ 69 ዓመታቸውከዚህ አለም በሞት ተለዩ፣
  • §  በአዲስአበባ በባሕል ሕክምና ታዋቂየነበሩት ሐኪም ማሞኃይሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፣
  • §  ከሁለትዓመት በፊት በአምባሳደርነትና በምክትል አምባሳደርነት ማዕረጐች ተሹመው በተለያዩ አገሮች ከተመደቡ የቀድሞ ከፍተኛ ባለሥልጣናት መካከልሥራ ስምንት የሚሆኑት ወደ አገር እንዲመለሱ ተደረገ፤ ሁለቱ በድጋሚ ሹመት ወደሌሎች አገሮች ሲመደቡ የተቀሩት ግን በአገር እንዲቀሩ ውሳኔ ተላለፈ፣
መጋቢት
  • §  በኢትዮጵያ ሕዝብ ክብር ተቆርቋሪ የግል ተነሳሽነት ኮሚቴ፣ በሰማያዊ ፓርቲ እና በባለራዕይ ወጣቶች ማኅበር አስተባባሪነት፤ በጣሊያን አፊሌ በተባለ ቦታ የተገነባውን የግራዚያኒ ኀውልት እና መታሰቢያ ቦታ በመቃወም፤ ከሰማእታት ኀውልት (6 ኪሎ) አንስቶ እስከ ጣሊያን ኤምባሲ የሚዘልቅ የእግር ጉዞ መጋቢት 8/2005 ጥሪ ተላለፈ፤ ሰልፉን ለማካሄድ የተገኙ አባላት እና የሰልፉ ዓላማ ደጋፊዎች ሰማእታት ኀውልት መሰባሰብ እንደ ጀመሩ  ፖሊስ ሰልፉን ሕጋዊ አይደለም ብሎ በኃይል በመበተን እና 40 የሚሆኑ በሰልፉ የተገኙ ሰዎች ለአንድ ቀን ታስረው ተፈቱ፣
  • §  የኢሕአዴግዘጠነኛ ጉባዔባሕርዳር ከተማ ለአራት ቀናት ተካሄደ፣
  • §  ‹ኢትዮትዩብ› በአሜሪካ አምስተኛ ዓመቱን አከበረ፣ በዕለቱም ‹ለፕሬስ ነፃነት የተጋ› በሚል ዓመታዊ  ሽልማት ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ተሸላሚ በወኪል ተበረከተለት፣
  • §  የቀድሞውየኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርመለስ ዜናዊ መታሰቢያመለስ ዜናዊፋውንዴሽንመሥራች ጉባኤበአፍሪካ ኅብረት የመሰብሰቢያአዳራሽ ተካሄደ፣
ሚያዚያ
  • §  ላለፉት አምስት ዓመታት በተደረገ ኮንትራት አማካኝነት በአሜሪካ ስትጎበኝ የነበረችው ሉሲ (ድንቅነሽ) ጉዞዋን ጨርሳ ወደ ሃገሯ ተመልሳ ለሕዝብ ዕይታ ክፍት ሆነች፣
  • §  ፒያሳ አራዳ ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን ጀርባ የሚገኘው የአቡነ ጴጥሮስ ኀውልት፤ በአዲስ አበባ በመሠራት ላይ በሚገኘው የቀላል ባቡር ግንባታ ምክንያት ከነበረበት ቦታ ተነስቶ ብሔራዊ ሙዚየም እንዲገባ ተደረገ፣
  • §  በጋምቤላ ክልል አኙዋክ ዞን አቦቦ ወረዳ ልዩ ቦታው ቁርጫ በሚባል አካባቢ 17 ተማሪዎችንና በኢንቨስትመንት ሥራ ላይ የተሠማራው ሳዑዲ ስታር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሠራተኞች የሆኑ ስድስት ሰዎችን፣ በድምሩ 23 ሰዎችን በጥይት ደብድበው በመግደልና በሽብር ወንጀል ተከሰው ከነበሩት 14 ግለሰቦች መካከል፣ ዘጠኙ በሞት እንዲቀጡ ተወሰነባቸው፣
  • §  ጋምቤላንለሰባት ዓመታት በፕሬዚዳንትነትየመሩት አቶ ኡሞድኡቦንግ የጋምቤላ ሕዝብዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢሕዴን) እና የክልሉ ምክር ቤትባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ከፓርቲውምክትል ሊቀመንበርነትና ከክልሉፕሬዚዳንትነት እንዲነሱ በመወሰኑ፣ምክትል ፕሬዚዳንቱ አቶጋትሉዋክ ቱት በምትካቸው የክልሉፕሬዚዳንትነት ሆነው ተሾሙ፣
  • §  የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰኔ 20 ቀን 2004 ዓ.ም. የሰጠውን የጥፋተኝነት ብይንና ብይኑን ተከትሎ የተጣለባቸውን የቅጣት ውሳኔ በመቃወም፣ ከነሐሴ ወር 2004 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የይግባኝ አቤቱታ አቅርበው በነበሩት፣ እነ እስክንድር ነጋ ላይ ሚያዝያ 24 ቀን 2005 ዓ.ም. የመጨረሻ ውሳኔ ተሰጥቶ ይግባኝ ካሉትፍርደኞች ውስጥ ከክንፈሚካኤልደበበ (አበበ ቀስቶ) በስተቀር የሁሉም የሥርፍርድ ቤት ቅጣት ውሳኔ እንዲፀና ተደረገ፤ በመሆኑም ክንፈሚካኤልበሥር ፍርድ ቤት ተጥሎበት የነበረው 25 ዓመት ፅኑ የእስራት ቅጣት ማቅለያውሲያዝለት ወደ 16 ዓመትፅኑ እስራት ተቀነሰ፣
  • §  የፌዴራሉ ዋና ኦዲተር በ124 የፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች የ2004 ዓ.ም. ሒሳብን ኦዲት በማድረግ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርብ፣ መንግሥት ሊያገኘው የሚገባ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ አለመታወቁንና በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ደግሞ መንግሥት ማጣቱን አሳወቀ፤ ከዚህ ውስጥ ትምህርት ሚኒስቴር 401.757 ሚሊዮን ብር የሚሆነውን ከፍተኛ ድርሻ የያዘ ሲሆን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 173.756 ሚሊዮን ብር፣ የግብርና ቴክኒክ ሙያና ትምህርት ሥልጠና ፕሮጀክት ማስተባበሪያ 155.597 ሚሊዮን ብር የታየባቸው መሥሪያ ቤቶች መሆናቸው ተገለፀ፣
ግንቦት
  • §  የፌደራል ፀረ ሙስና እና የሥነ ምግባር ኮሚሽን የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መላኩ ፋንታን ጨምሮ ሌሎች የባለሥልጣኑ ኃላፊዎችና ባለሀብቶች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር በመዋላቸው የክስ የፍርድ ሒደቱ ተጀመረ፣
  • §  በባሕርዳር ከተማ የፌደራል ፖሊስ አባል የሆነ ግለሰብ በከፈተው ተኩስ 10 የሚሆኑ ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ ወንጀለኛው ፖሊስም ራሱን አባይ ወንዝ ውስጥ ወርውሮ ሕይወቱን አጠፋ፣
  • §  በኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት አምባሳደር ዣቪየር ማርሻል በ61 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፣
  • §  በከፍተኛ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር በዋሉት በሚኒስትር ማዕረግ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ ምትክ፣ የአዳማ ከተማ ከንቲባ የነበሩት አቶ በከር ሻሌ ተሾሙ፣
  • §  በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ በመምህርነት፣ በተመራማሪነት እና በልዩ ልዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉት እና “ቤተ ክሕነትና መንግሥት በኢትዮጵያ ከ1262-1527” (Church and state in Ethiopia 1262-1527) በተሰኘው መጽሐፋቸው የሚታወቁት ፕሮፌሰር ታደሰ ታምራት ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፣
  • §  አዲስ አበባ የሚከበረውን የአፍሪካ ሕብረት 50ኛ ዓመት የወርቅ እዮቤልዩ በዓል ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ቢያደርግም የአ.አ መስተዳድር ሰልፉን ጥበያ የሚያደርግ የፖሊስ ኃይል እጥረት አለብን በማለት ለሌላ ጊዜ እንዲያዘዋውሩት ጠየቀ፣
  • §  የአፍሪካ አንድነት ድርጅት/የአፍሪካ ኅብረት የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት በተለያዩ ዝግጅቶች ዋናው ጽ/ቤት በሚገኝበት በኢትዮጵያ አከበረ፣
  • §  የሕዳሴው ግድብ ቀጣይ የግንባታ ምዕራፍ የሆነው ወንዙን አቅጣጫ የማስቀየስ ሽራ ተከናወነ፣ ይህን ተከትሎም ከሃገሪቷ ፖለቲከኞች ጋር በቀድሞው የግብፅ ፕሬዝዳንት ሙርሲ የተመራ ውይይት ሲካሄድ የግድቡ ሥራ እውን እንዳይሆን የሚያደርጉ ሐሳቦች መሰንዘራቸው፤ ይህ ውይይትም በስህተት በሃገሪቱ የብሔራዊ ቴሌቭዥን ጣቢያ በቀጥታ ተላለፈ፣   
  • §  ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ ከተማ መነሻውን የፓርቲው ፅ/ቤት፤ መድረሻ ቦታውን ኢትዮ-ኩባ አደባባይ ያደረገ፣ በርካቶችን ያሳተፈ እና ከ97 ምርጫ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደ  የተቃውሞ ሰልፍ አካሄደ፣
ሰኔ
  • §  አንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ‹‹ሚሊዮን ድምፆች ለነፃነት›› የተሰኘ፣ ለሦስት ወራት የሚቆይ ሕዝባዊ ንቅናቄ ጀመረ፤ በንቅናቄው ሕዝባዊ ስብሰባዎች፣ ሠላማዊ ሰልፎችና በፀረ-ሽብር ሕጉ ላይ የተቃውሞ ፊርማ እንደሚሰበሰብ ተነግሯል፣
  • §  ለቀደሙት 20 ወራት በሽብር ወንጀል ተፈርዶበት ቃሊቲ ማረሚያ ቤት የሚገኘው ጋዜጠኛ፣ ጦማሪ እና አራማጅ እስክንድር ነጋ፤ ከባለቤቱ እና ልጁ ውጪ በሆኑ ቤተሰቦቹ፣ ወዳጆቹ እና አድናቂዎቹ እንዲጎበኝ ሲፈቀድለት የሚጎበኝበት ሰዓትም እንደማንኛውም በማረሚያ ቤቱ የሚገኙ ታራሚዎች እንደሆን ተደረገ፣
  • §  በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የ2013ቱ የቢግ ብራዘር አፍሪካ ውድድር ከኢትዮጵያ የሄደችው ቤቲ የወሲብ ትእይንና አነጋጋሪ መሆን፣
  • §  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ሦስተኛውን ጨዋታ በሃገሩ አድርጎ ተጋጣሚውን ደ/አፍሪካን 2-1 በመርታት የቀሪውን ጨዋታ ነጥብ ሳያሳስበው ምድቡን በአንደኝነት መምራቱን ቢያረጋግጥም በማግስቱ በፌዴሬሽኑ ስህተት ብሔራዊ ቡድናችን ሦስት ነጥቦችንና ሦስት ጎሎች የሚያስቀጣውን ጥፋት ማጥፋቱን ተነገረ፣
  • §  ፓርላማው2005.የሥራ ዘመን ማጠናቀቂያ ላይ የሥልጣንሹም ሽር በማድረግ አስር አዳዲስ ሚኒስተሮችሾመ፣
  • §  የቅዱስጊዮርጊስ እግር ኳስክለብ በኢትዮጵያ እግር ኳስታሪክ ወደ ኮንፌደሬሽን ካፕ የምድብማጣሪያ ያለፈ የመጀመርያክለብ መሆኑ፣
ሐምሌ
  • §  ወጣት የፖለቲካ ተንታኙ ጃዋር መሐመድ አልጀዚራ የቴሌቪዥን ጣቢያ በሚያዘጋጀው   ‹ዘ ስትሪም› በተሰኘ ፕሮግራም ላይ ስለ ኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ እና ተያያዥ ጉዳዮች የብዙዎችን (በተለይም ማኅበራዊ አውታር ተጠቃሚዎችን) ትኩረት የሳበ እና ያነጋገረ ንግግር አደረገ፤
  • §  አንድነት ፓርቲ በጎንደርና ደሴ ከተሞች በተመሳሳይ ቀን (ሐምሌ 7/2005) ‹‹ሚሊዮን ድምፆች ለነፃነት›› በተሰኘው ሕዝባዊ ንቅናቄው ሠላማዊ ሰልፎችን አካሄደ፣
  • §  አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገ/ሥላሴ ከሁለት ዓመት በኋላ በሚካሄደው በ2007ቱ ጠቅላላ ምርጫ አዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ በመወዳደር ወደ ፓርላማ ለመግባት ማቀዱን በቃለ ምልልሶች አረጋገጠ፣
ነሐሴ
  • §  የአምስት ፓርቲዎች ጥምረት የሆነው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ አንድነት መድረክ ዶ/ር መረራ ጉዲናን ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ፣

  • §  1434ኛው የኢድአልፈጥር በዓል በእስልምናእምነት ተከታዮች በተለይበአዲስ አበባ ብሔራዊስታዲየም ሲከበር፣ ፌደራልፖሊስ በዓሉን ለማክበርየተገኙትን በርካታ ሰዎች ላይ እስር እና አካላዊ ጥቃት ፈፀመ፣

  • §  ሞስኮ በተዘጋጀው 14ኛው የዓለም አትሌትክስሻምፒዮና ኢትዮጵያ 3የወርቅ፣ 3 የብርእና 4 የነሃስሜዳሊያ በማግኘት ከዓለም6 ከአፍሪካ 2ሆና አጠናቀቀች፤ ወርቁንያስገኙት ዝነኞቹ የረጅምርቀት ተወዳዳሪዎች ጥሩነሽዲባባ እና መሰረትደፋር እንዲሁም በታሪካችንለመጀመሪያ ጊዜ የሆነውን800 ርቀትአሸናፊ መሐመድ አማንናቸው፣

  • §  የአቡነ ጳውሎስ እና  የቀድሞ ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ሙት ዓመት በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበሩ፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሙት ዓመት ለማክበር መንግሥት አረንጓዴ ዘመቻ አደረገ፣ በርካታ ፓርኮችንም በስማቸው ተሰየመላቸው፣
  • §  ወጣቱ ድምፃዊ ኢዮብ መኮንን ባደረበት ድንገተኛ ሕመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፣
  • §  የ33ቱ ፓርቲዎች ዐቢይ ኮሚቴ ባደረገው የጋራ ስብሰባ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት በየጋዜጣው ላይ የሚሰጡት መግለጫ የፓርቲው አቋም መሆኑ በመረጋገጡና በጋራ ለመሥራት ከተስማሙበት የጋራ ሰነድ ውጪ ሆነው መርሖችን በመጣላቸው ምክንያት ፓርቲው ከኅብረቱ መታገዱን አሳወቁ፣
  • §  ሰማያዊ ፓርቲ ነሐሴ 26/2005ዓ.ም በአዲስ አበባ  ሊያካሂድ ያቀደውን እና ከሦስት ወር በፊት ሲያስተዋቅ እንዲሁም ዝግጅት ሲያካሂድ የከረመበትን ሠላማዊ ሰልፍ፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰልፉ እንዳይካሄድ ከለከለ፣ 
  • §  በተለያዩ የእምነት ተቋማት ኅብረት ጠሪነት፤ በመንግሥት ወኪሎችና የኢሕአዴግ አባላት ቀስቃሽነት የሃይማኖት አክራሪነትና ፅንፈኝነትን ለመቃወም በሚል ነሐሴ 26/2005ዓ.ም በአዲስ አበባ  ሰላማዊ ሠልፍ  ተካሄደ፣
ጳጉሜ
  • የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ የምድብ ማጣርያ ከሴንትራል አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ኮንጎ ብራዛቪል ላይ ገጥሞ ተጋጣሚውን 2 ለ 1 በመርታት፤ ምድቡን በመሪነት በማጠናቀቅ አፍሪካን የሚወክሉ 5 ቡድኖች ተለይተው ለሚወጡበት 10 ብሔራዊ ቡድኖች ለሚያደርጉት የደርሶ መልስ ጥሎ ማለፍ ከገቡት ውስጥ መካተት ቻለ፡፡

ከጉልበተኞች ጠመንጃ የሚወጣ ጥይት ስጋን እንጂ እምነትን ሊገድል እንደማይችለው ሁሉ፣ ከቤተሰብና ወዳጅ ዘመድ ተነጥሎ ቅዝቃዜ በዋጠው ጠባብ ክፍል ውስጥ መታሰርም አካልን እንጂ ምናብን (ህልምን) ሊያስር የሚችልበት ጉልበት የለውም፡፡ ከቶስ እንደምናብ ሜዳውን፣ ተራራውን፣ ቁልቁለቱን፣ ዳገቱን፣ ሸለቆውን፣ ኮረብታውን በሰከንድ ክፍልፋዮች ከብርሃን ፈጥኖ በመምዘግዘግ ያለመዛነፍ ያሰበበት የሚደርስ ምን ኃይል አለ? ከጠባቧ ክፍል ውስጥ ‹‹ድርሻህ›› ተብላ በተሰጠችኝ 90 ሴንቲ […]

ጳግሜ ፬(አራት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች በተገኙበት ገዢው ፓርቲ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ከማውገዝ በተጨማሪ ህዝቡ ለእውነተኛ ለውጥ እንዲነሳ ጥሪ አድርጓል። ሰልፈኛው ሲያሰማቸው ከነበሩት መፈክሮች መካከል ጥያቄያችን ህገመንግስታዊ ነው፣ ውሸት ሰልችቶናል፣ ስራ መግኘት መብታችን ነው፣ ጸረ ሽብር ህጉ በራሱ አሸባሪ ነው፣ መንግስት፣ የኑሮ ድጎማ ያድርግልን፣  ድህነት በወሬ …

ጳግሜ ፬(አራት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትሩ ትላንትና እና ዛሬ ለሕትመት በበቃው ከመንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ላይ እንደተናገሩት “የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በርግጥም ለኢትዮጽያ ሕዝብ ዴሞክራሲ፣መልካም አስተዳደር ልማትና ሠላምን ለማምጣት አጀንዳ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ከሆነ አክራሪነትንና ሽብርተኝነትን ከመንግስት ጎን ተሰልፈው ሊያወግዙ ይገባል ብለዋል፡፡ ” በኢትዮጽያ አክራሪነትና ሽብርተኝነት የለም ብለው የሚያስቡ ከሆነ እነዚህ ሰዎች በኢትዮጵያ …

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችኹ፣ በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችኹ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ኾናችኁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤ የዘመናት ፈጣሪ እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከ፳፻፭ ዓ.ም ዘመነ ማቴዎስ ወደ ፳፻፮ ዓ.ም ዘመነ ማርቆስ በሰላም አደረሳችኹ!!! ‹‹ወሠርዐ ዕድሜኹ …

ጳግሜ ፬(አራት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቀዳማዊት እመቤት ሮማን ተስፋዬ የቤተመንግስት ኑሮ የሚመች አለመሆኑንና የቀድሞ ጠ/ሚኒስትርንም አኗኗር በማየት ያዝኑ እንደነበር ተናግረዋል። ቀዳማዊት እመቤቷ ትላንት ከወጣው መንግስታዊው ዘመን መጽሔት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ የቤተመንግስት ሕይወት አስደሳች አይደለም ብለዋል፡፡ “ የቤተመንግስትን ሕይወት ለማንም ተመኝቼው አላውቅም፡፡ የሴቶች ጉዳይን ስናቋቁም ስምንት ወር ተመላልሼበታለሁ፡፡ ዛሬ እናንተ ተፈትሻችሁ እንደገባችሁት እኛም ተፈትሸን ነበር …

ጳግሜ ፬(አራት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ታዋቂው አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው ቢሮክራሲ የኢንቨስትምንት ስራ  ለመስራት ዋነኛው እንቅፋት መሆኑን ከሪፖርተር ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ገልጿል። የመብራትና ውሀና መንገድ ችግሮችን በጋራ መቋቋም ይቻላል ያለው ሀይሌ ፣ ቢሮክራሲው ከፍተኛ ችግር መሆኑን ገለጿል። ሀይሌ እንደሚለው የቢሮክራሲው ዋና ምክንያት በራሳቸው የሚወስኑ ባለስልጣናት መጥፋታቸው ነው። በተለያዩ ሀላፊነት ላይ ያሉ …

ጳግሜ ፬(አራት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፕሬዚዳንቱ በህዝቤ ላይ የኬሚካል የጦር መሳሪያ የምጠቀምበት ምንም ምክንያት ለም በማለት ለአንድ የአሜሪካ የቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል። አሜሪካ ሶሪያን ብትደበድብ አንዳንድ ደጋፊ አገሮች አጸፋዊ መልስ ለመስጠት መዘጋጀታቸውንም አላሳድ አክለው ገልጸዋል። ይሁን እንጅ እነዚህን አገሮች  በስም ከመግለጽ ተቆጥበዋል። አለም በሶሪያ ላይ ስለሚወደው የሀይል እርምጃ ተከፋፍሎአል። ፕሬዚዳንት ኦባማ በሶሪያ ላይ እርምጃ ካልተወሰደ …

ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

የመለስ ዜናዊ አስተሳሰብና ምግባር ሕዝብን በተለይም ፖለቲከኞችን በተራራቀ ተቃራኒ ጫፍ እንዳቆሙ መሞታቸዉ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በበጎ ወይም በመጥፎ፥ ወይም በሁለቱም መሐል-ክፉኛ መንካቱ እንደማይቀር ያኔ ተብሎ ነበር።አሁንም አልቀረም።

ነሃሴ ወር አጋማሽ ሶርያ መንግስት በመርዘኛ ጋዝ ተጠቅሞአል ለተባለበት ወንጀል፤ ምዕራባዉያን አሳድ ላይ የአየር ጥቃት ለማካሄድ እቅዳቸዉ ላይ በሁለት ወገን የተከፈሉ ይመስላል። ሶርያ መንግስት በበኩሉ የኬሚካዊ መሳርያ ጥቃትን እንዳልፈጸመ እየገለፀ ነዉ።

ብራዚል ውስጥ ለሚካሄደው የዓለም የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር የአፍሪቃ እና የአውሮፓ አገሮች ማጣሪያ ውድድር፣ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ሲካሄዱ ቆይተዋል።

የዚህ ሳምንት የሙዚቃ ቃና ፐሮግራም የተለያዩ ምርጥ ምርጥ ዜማዎችን ያካተተ ሲሆን በ Billboard ሰንጠረዥ ላይ የበላይንቱን የያዙትን ዜማዎችን ጨምሮ ሙዚቃ ነክ ዜናዎችንም አካቷል፡፡

የተከበራችሁ የዲሲ እና አካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም የነፃነት ወዳጆች ዛሬ ለዚህ መድረክ የማስተላልፈውን መልዕክት ከምን እንደምጀምር ሳስብ “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መርዕ የተጀመረውን ህዝባዊ መነሳሳት መፍጠሪያ መድረክ እንደሚሆን ጥርጥር አልነበረኝም፤ ነገር ግን ሀገር ውስጥ በሚታተም አንድ መፅሄት ላይ ወጥቶ ለንባብ የበቃውን የአንዱዓለም አረጋጌን “የሐምሌ ጨረቃ” መጣጥፍ ሳነብና የእርሱን የሰለማዊነት መንፈስ ለገዥዎቻችን ግን የአሸባሪነት ድምፅ ትንሽ ማለት […]

ገዥዎቻችን መከፋፈል ስልጣንን ለሀያ ሁለት አመታት ያፀኑበት ዋና መሳርያቸው ነው። ሁሌም ለማራራቅ አጠንክረው ሲሰሩባቸው ከኖሩት ማህበረሰባዊ ልዩነቶች አንዱ በአገር ቤትና በውጪ አገራት የሚኖረው ኢትዮጵያዊ መሀከልም ነው። አሁን አሁን ይህ በተጠናከረና በረቀቀ መንገድ እየተሰራበት እንዳለ በግልፅ ይታያል። በወያኔዎች ዘንድ ትላልቆቹን መህበረሰባዊ ልዩነቶች አይደለም ከቅርበት አኳያ የተወሰኑ ዜጎች የሀመረኖ የቀሩት ደግሞ የጎርፍ አሶጋጅ እድርተኛ መሆናቸው እንደ አንድ […]

እዚያው ፉትስክሬይ ቁጭ ብለን ወግ በመሰለቅ ላይ ነን፡፡ ባለፈው ወዳጄ ስለ ‹‹ኢምፖርት›› አንሥቶ ነበር ያቆመው፡፡ እስኪ ይቀጥል፡፡
‹‹ምንድን ነው ኢምፖርት የሚያደርጉት ኢትዮጵያ ሄደው››

‹‹ሚስት ነዋ››

‹‹እንዴት ነው ደግሞ ሚስት ኢምፖርት ማድረግ ማለት››

‹‹እዚህ ሀገር ያለ ሐበሻ በሦስት መንገድ ነው ሚስት የሚያገኘው››

‹‹በምን በምን››

‹‹በኢምፖርት፣ በኤክስፖርትና በባላንስ››

‹‹ይሄ ትርጓሜ ያስፈልገዋል››

‹‹ኦኬ፤ ኢምፖርት የሚባለው ሀገር ቤት ትሄድና ሚስት ወይም ባል ይዘህ ስትመጣ ነው፡፡ ኤክስፖርት የሚባለው ደግሞ የውጭ ሀገር ሰው በተለይም የዚህን ሀገር ሰዎች ስታገባ ነው፡፤ ባላንስ ሠራህ የሚባለው ደግሞ ሁለት አበሾች እዚሁ ተገናኝተው ሲጋቡ ነው፡፡››

‹‹ታድያ የትኛው ነው የሚሻለው››

‹‹ሁሉም የራሱ ጣጣ አለው፡፡ ኢምፖርት ስታደርግ ከታደልክ ትዳር የጠማትን ወይም የጠማውን ታገኘዋለህ ወይም ታገኛታለህ፡፡ ካልታደልክ ደግሞ እዚህ ከመጣች በኋላ አቢዩዝ አደረገኝ ብላ ልትፈነግልህ ትችላለች፡፡ ወንዱም ትቷት ሊሄድ ይችላል፡፡ ወይም ይፋታሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ እዚህ ኢምፖርት ተደርገው ከመጡ በኋላ ስቃያቸውን ያዩም አሉ፡፡ ውጭ እንሄዳለን፣ ባል እናገኛለን፣ አለፈልን ብለው ሳያመዛዝኑ ውጭ ሀገር ስለተባለ ብቻ ይመጡና አበሳቸውን ያያሉ፡፡ በተለይ ስደት ላይ ብዙ ዘመን ኖረው፣ እድሜያቸውን ጨርሰው፣ ራሳቸውን መልጠው፣ ሁለት ጠጉር አውጥተው ከሀገር ቤት ዘልላ ያልጨረሰች ሚስት የሚያመጡ ፌንት ይገጫሉ፡፡››

እንዴት ነው የሚገጩት››

‹‹አየህ አንተ ሃያ ዓመቷን ሱዳንና ኬንያ ከጫርካት በኋላ አባባ የምትልህን ቆንጆ ልጅ ስታመጣ፤ እርሷ እያማረባት ሲሄድ አንተ ግን እድሜ ሲያናጭርብህ ቅናቱን አትችለውም፡፡ የነገር አባቷ እንጂ ባሏ ስለማትመስል ሥጋት እየገባህ ይሄዳል፡፡  ያም ያም አንተን ረስቶ የሚስትህን ቁንጅና ሲያወራ እርሷ ተጨዋች አንተ ተመልካች የሆንክ ይመስልሃል፡፡ ያን ጊዜ አበሻነትህ ይነሣብሃል፡፡ አውስትራልያ መሆንክን ትጠላውና መንዝና ሞላሌ፣ ወልቃይት ጠገዴ፣ ሽሬ እንዳ ሥላሴ መሆን ያምርሃል፡፡ መሳደብ፣ መጨቃጨቅ፣ ሲብስም መማታት፣ ሲያልፍም አካል መጉዳት፣ በመጨረሻም ሕይወት እስከ ማጥፋት ትሄዳለህ፡፡

እዚህ ሜልበርንኮ አንዱ እልኩና ቅናቱ አልወጣለት ሲል ከሕንድ ቤት ቀይ ቃርያ ገዝቶ ሚስቱን በበርበሬ አጥኗታል፡፡ ስንቱ ሚስቱን ገድሏል፤ ስንቶቹስ ተደብድበውና ተፈንክተው በሐኪም ጥረት ከሞት ተርፈዋል፡፡ ኢምፖርት ዕዳው ብዙ ነው፡፡

የዚህን ሀገር ሰዎች አግብተው የሚኖሩ ብዙ አበሾች አሉ፡፡ በተለይ ሴቶቹ በዚህ ጎበዞች ናቸው፡፡ እነርሱ ጋር እስካሁን የሰማሁት የከፋ ችግር የለም፡፡ ባይሆን ወንዶቹ ፈተና ይገጥማቸዋል፡፡ ፈረንጅ ወዳጄ ፍቅራዊ (ሮማንቲክ) ነገር ይወዳል፡፡ እኛ ደግሞ ሃኒ፣ ስዊት፣ ዳርሊንግ የሚል ነገር አልለመድነው፡፡ እኔ ሐኒ የማውቀው ከሦስተኛ ክፍል ጀምሮ ማር በእንግሊዝኛ ሐኒ መሆኑን ነው፡፡ ስዊት – ጣፋጭ ነው፤ በቃ፡፡ ዳርሊንግ እዚህ ነው የሰማሁት፡፡ እኛ ደግሞ ቆፍጠን ያልን ነን፡፡ ‹ሌቱን ለአራዊት ቀኑን ለሠራዊት› ነው ወዳጄ፡፡ የኛ አኗኗር ለእነርሱ መሥሪያ ቤት ይሆንባቸዋል፡፡ እንኳን እነርሱ እዚህ ሀገር ቆየት ያሉት ሴቶች እንኳን ‹‹የኛ ወንዶች አባወራነት እንጂ ፍቅረኛነት አይችሉም›› ይሉናል፡፡

ከቻልክ እዚህ ሀገር ባላንስ መሥራት ነው፡፡ ተዋውቀህ፣ ሀገሩንም ዐውቀህ መጋባት፡፡ ችግሩ እዚህ እንደ አሜሪካ ዲቪ የለ፣ እንደ አውሮፓ በመርከብ የሚገባ የለ፣ ከየት ታመጣለህ፡፡ ወይ እዚያው ስደት ላይ ተጋብተህ ካልመጣህ በቀር፡፡ ››

‹‹ይህን ችግርኮ ተባብራችሁ መፍታት ትችሉ ነበር››

‹‹አንዳንዱን አበሻ ተባበር ከምትለው ተሰባበር ብትለው ይሻለዋል፡፡ ሁሉም በየጎጡና በየሠፈሩ ነው፡፡ አብዛኞቹ ቤተ ክርስቲያኖች እንኳን ዘርን መሠረት ያደረጉ ናቸው፡፡ የአማራውን፣ የትግሬውን፣ የኦሮሞውን ቤተ ክርስቲያን ትለየዋለህ፡፡ ትግሬውም አንድ መሆን እያቃተው አድዋ፣ ሽሬ ሲል ታገኘዋለህ፡፡ አማራውም ወልቃይት፣ ጎንደር እየተባባለ ለብቻው ቸርች ይከፍትልሃል፡፡ ኮሙኒቲውም ለየብቻ ነው፡፡ እዚህ ሀገር የኦሮሞ፣ የሶማሌ፣ የሐረሪ፣ የትግራይ ኮሙኒቲዎች አሉ፡፡ አንደኛው ከአንደኛው ጋር የሚጠራጠሩ፣ የማይተባበሩ፡፡ ከትብብር ርቀው ንጽሕ ጠብቀው የሚኖሩ፡፡ በፍቅር የተጎዱ፣ ከኅብረት የጸዱ፡፡ አንዳንዶቹ ኢትዮጵያውያን ነን ይላሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ‹‹ምሥራቅ አፍሪካ›› የሚባል ሀገር ፈጥረውልሃል፡፡ …››

‹‹ኧረ እንዲያውም አዳሙ ተፈራ በጻፈው ‹‹ገመናችን በሰው ሀገር› የሚለው መጽሐፍ ላይ ሜልበርን የሚገኘው የኦሮሞ ኮሙኒቲ በ2010 እኤአ 25ኛ ዓመቱን ሲያከብር የጻፈውን አይቼ ገርሞኝ ነበር፡፡

‹‹The Oromo are indigenous African people from the north eastern of Africa.›› ይላል፡፤ ኢትዮጵያ ላለማለት አዲስ ሀገር ፈጥረዋል፡፡ ››

‹‹እይውልህ እንደዚያ ነው እንግዲህ፡፡ የሚገርምህኮ እዚህ ያለ ሰው መገንጠልን የሚጠላ ተገንጣይ መሆኑ ነው››

‹‹በዚህ ብቻ አይበቃም ትርጓሜ ያሻዋል – ብሏል ኪነ ጥበብ›› አልኩት፡፡

‹‹በውጭ ያለ ዳያስጶራ ስለ ኤርትራ መገንጠል ሁል ጊዜ እየተንገበገበ ያወራል፡፡ እርሱ ግን ራሱ በፈቃዱ ያለ ሪፈረንደም ተገነጣጥሏል፡፡ በምትቃወመው ነገር ውስጥ ራስህን እንደማግኘት ያለ አስነዋሪ አካሄድ የለም፡፡ በየስብሰባው ‹ዐንቀጽ 39› የምትባል ነገር ትነሣለች፡፡ ‹‹የብሔረሰቦች መብት እስከ መገንጠል›› የምትባለው፡፤ ይህች ዐንቀጽ እስካሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ አልተደረገችም፡፡ እዚህ ግን ተግባራዊ ተደርጋለች፡፡ የተገበሯት ደግሞ የሚቃወሟት ሰዎች ናቸው፡፡ ለዚህ ነው ‹‹መገንጠልን የማይደግፍ ተገንጣይ›› ያልኩህ፡፡ አሁን ዘመን መለወጫ እየመጣ አይደለ? ሦስት ቦታ ነው ፕሮግራም የተዘጋጀው፡፡ ከዚያ መርጠህ እንደየብሔረሰብህ መሄድ ነው፡፡ ወዳጄ እዚህ ሀገር ጩኒ ይምጣብኝ››

‹‹ማነው ጩኒ ደግሞ››

‹‹ጩኒ ሰው አይደለም፤ ሕዝብ ነው››

‹‹ጩኒ የሚባል ሕዝብ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ መስማቴ ነው፡፡››

‹‹ጩኒ ማለት ቻይና ነው፡፡ እዚህ ሀገር ጩኒ ነው የምንላቸው፡፡ ጩኒ እርስ በርስ በመደጋገፍ ማንም አይችላቸውም፡፡ ብድር ይሰጡሃል፤ መረጃ ይሰጡሃል፡፡ ያቋቁሙሃል፡፡ ከዚያ ምርጥ ኢንቨስተር ትሆናለህ፡፡ ያለበለዚያ ደግሞ ወጥሬ እሠራለሁ ካልክ በቀላሉ የምትከራየው ቤት ይሰጡሃል፡፡ እንዲት ክፍል ተከራይተህ ኑሮ ሳይከብድህ ወጥረህ ትሠራና በዓመትህ ቀና ትላለህ፡፡ ወዳጄ ጩኒ አንገቱን ደፍቶ እየሠራ ልጁን ምርጥ ትምህርት ቤት ነው የሚልከው፡፡ ኮሙኒቲያቸው ልጆቹን በሚገባ ነው የሚረዳቸው፡፡ ስለዚህ ልጆቹ ውጤታማ ናቸው፡፡ እኛጋኮ ወላጆችና ልጆች አልጣጣም ብለዋል፡፡ ልጆቹን የቤት ሥራ ማን ያሳያቸው፡፡ ማን በትምህርት ያግዛቸው፡፡

አገርሽ ምንኛ መንደርሽ ምንኛ

አላውቅበት አልኩኝ ያንችን አማርኛ

ሲባል አልሰማህም፡፡ በምን ቋንቋ በምን ዕውቀት ከልጆቻችን ጋር እንግባባ፡፡ ልጆቻችን አያውቁም ብለው ንቀውናል፡፡ በዚህ የተነሣ ከትምህርት የሚያቋርጡት ብዙ ናቸው፡፡››

‹‹ቆይ ግን እዚህ መጥተው የተሳካላቸው የሉም››

‹‹ለዓይነት ያህልማ አሉ፡፡ መቼም ለስማችን መጠሪያ ቁና ሰፍተናል፡፡ ለአካባቢ ምርጫ እስከመወዳደር የደረሱ አሉ፡፡ ያው ከሆቴልና እንጀራ ቤት ባናልፍም ቢዝነስ ያላቸውም አሉ፡፡ በተማሩት ሞያ የሚሠሩም በመጠኑ አሉ፡፡ እኔ የሚገርመኝ ግን በኢሕአፓ፣ በኢሕአዴግ፣ በግንቦት ሰባት፣ በኢዲዩ፣ በቅንጅት ውስጥ ለመግባት እንጂ በምንኖርበት ሀገር በሚገኙ ፓርቲዎች ውስጥ ገብቶ፣ አባል ሆኖ፣ ተወዳድሮ ፓርላማ ለመግባት፣ የአካባቢ ተመራጭ ለመሆን የሚተጋ አበሻ ብዙ አናይም፡፡ አሜሪካ እንኳን ሚሊዮን የሚሞላ ኢትዮጵያዊ ተከማችቶ እስካሁን አንድ የአካባቢ ተወካይ እንኳን አለማግኘታቸው ይገርመኛል፡፡ እኛ በሀገራችን አምባሻ ነው የምንራኮተው፡፡ ለምሳሌ እዚህ አውስትራልያዊ ዜግነት ካለህ መምረጥ ግዴታህ ነው፡፡ እንደ አሜሪካ አይደለም፡፡ የመምረጥ ግዴታ አለብህ፡፡ ያለበለዚያ ቅጣት አለው፡፡ የፓርቲዎቹ አባል ስትሆንና ሳትሆን ዕድልህ ይለያያል፡፡ if you are not a member, you are a number ይሉሃል፡፡ ችግሩ ግን እዚህ ሀገር ተመልካች እንጂ ተጨዋች የለም፡››

‹‹ማለት››

‹‹ኳሱ ጉዳያችን ነው፡፡ ሜዳው አውስትራልያ ይባላል፡፡ ሕጉ የሀገሪቱ ሕግ ነው፡፡ ዳኛው ሲስተሙ ነው፡፡ ዋንጫው ውጤትህ ነው፡፡ እዚህ በሚገባ ተጫውተህ የስኬትን ዋንጫ መሳም ትችላለህ፡፡ ምን ያደርጋል ታድያ፡፡ በዙሪያህ ቆሞ ለምን ይህ አይሆንም? ለምን ይሄ አይደረግም? እገሌ ለምን እንዲህ ያደርጋል? እንዲህ በመሆኑ አኩርፌ ቀርቻለሁ፣ የሚል የዳር ተመልካች እንጂ ሜዳው ውስጥ ገብቶ ለመጫወት የሚፈልግ የለም፡፡ እዚህ ያለውን ሰው ‹‹ሰይጣን›› ከምትለው ‹ኮሙኒቲ› ብትለው ደንግጦ ያማትብብሃል፡፡ ተበላ፣ ተጠጣ፣ ተጣሉ፣ ተከፋፈሉ ብቻ ነው የምትሰማው፡፡ አንድ ወዳጄ ምን ይላል መሰለህ

የትልቅ ሰው ልጅ ቀረ በከንቱ

ሀገር ሳይገዛ ሳይባል አንቱ – እንዲህ ነው እንግዲህ፡፡

ካሮላይን ስፕሪንግስ፣ አውስትራልያ

የአዳማ ሰልፍ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተጠናቅቋል!!! ኢቴቪ በአዳማ የሁከት ድራማ በመስራት ለመቅረጽ ያደረገችው ሙከራ ከሸፈ ብራቮ አዳማዊያን! ጉዞ ወደ አዲስ አበባ! በጎንደር፣ ደሴ ፣ባህር ዳር፣ጂንካ፣ ወላይታ፣ባሌ ሮቢ፣ ፍቼ፣ አርባ ምንጭ ዛሬ አዳማ ቆይታ በማድረግ የሚልዮኖችን ድምጽ ያሰማው የአንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ህዝባዊ ንቅናቄ ለመስከረም 5/2006 የመስቀል አደባባይ ሰለማዊ ሰልፍ ጓዙን ጠቅልሎ ሸገር ገብቷል፡፡ በዛሬው […]

ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

ተቃዋሚው ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ መድረኩን ተቆጣጠሮ ያዘ (ቪዲዮ አለው!)

በስዊድን ጉተንበርግ ከተማ ሊደረግ የታሰበው የዓባይ ግድብ የቦንድ ሽያጭ ከሸፈ

ከኢትዮጵያ ዛሬ ሪፖርተር

“ይገርማል!” ብሎ መጀመር ይቻላል። አዎን ይገርማል! ከስቶክሆልም የሄድነው ወደ አዳራሹ የገባነው ጥሪ ባደረጉበት 13፡00 ሰዓት ነበር። እ.ኤ.አ ኦገስት 31 ቀን 2013.። ህዝቡ እስኪሰባሰብ ጥቂት ከተጠበቀ በኋላ ስብሰባው በአንድ የኢህአዴግ/ወያኔ ካድሬ ተከፈተ። እንዲህም አለ፤ “እዚህ እኛን ለመቃወም የመጣችሁ እንዳላችሁ እናውቃለን። ሃሳባችሁን እንድትናገሩ አንከለክልም፤ ነገር ግን ጩኸት፣ አላስፈላጊ ረብሻና ግርግር የምትፈጥሩ ከሆነ ወዮላችሁ! አስቀድመን ባዘዝነው የፖሊስ ኃይል እየተለቀማችሁ ትወጣላችሁ። መውጣታችሁ ብቻ አይደለም፤ ታሪካችሁ ይጠፋል፣ ውርደት ይከተላችኋል። በመለያ ቁጥራችሁም ላይ የሚጻፈው ወንጀል ዕድሜ ልካችሁን ይከተላችኋል።”

ሙሉውን አስነብበኝ …