የለውጥ አመራር ሂደቱን የሚያስቀጥል ዋና ሥራ አስኪያጅ ይፈለጋል የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን የዋና ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት በጊዜያዊነት የሚመሩ ሓላፊ ተመደቡ፡፡ ሓላፊነታቸውን በድንገት ለቀው ወደ አሜሪካ ባቀኑት መጋቤ ሐዲስ ይልማ ቸርነት ምትክ የተመደቡት ጊዜያዊ ሓላፊ የክህነትና መንፈሳዊ ፍትሕ ዋና ክፍል ሓላፊ ንቡረ እድ አባ ዮሐንስ ገብረ ሕይወት ናቸው፡፡ የንቡረ እድ አባ ዮሐንስ ገብረ ሕይወት ጊዜያዊ ሓላፊነት እስከ …

በቅርቡ ከሰማናቸው ዜናዎች ውስጥ አንዱ‹‹በጋምቤላ በሕንዳዊው ኩባንያ ቨርዳንታ ሐርቨስት የተያዘው እርሻ በአካባቢው ሰዎች እሳት ተለቀቀበት›› የሚል ይገኝበታል፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች እርሻውን ማቃጠላቸው ስህተት እንደሆነ አምናለሁ፤ ነገር ግን በዚህ ጽሑፍ በነርሱ ቦታ ሳልሆን ልፈርድባቸው አልደፍርም፡፡ ይልቁንም በዚህ መረጃ ላይ ተመስርቼ ‹‹ለምን›› የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ እሞክራለሁ፡፡
ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም የዛሬ ሁለት ዓመት (ኦክቶበር 16፣ 2011) ‹‹ቀጣዩ እሳት በምን ይመጣ ይሆን?›› በሚል ስጋታቸውን የጻፉት በዚያው ክልል ትልቅ የእርሻ ቦታ የገዛውን የካሩቱሪስታን ኩባንያ የመጀመሪያ ምርቱን የሰደድ እሳት ከበላበት በኋላ ነበር፡፡ ይህ በሆነ ልክ በሁለት ዓመቱ ነው ዘንድሮ ሌላኛው የሕንድ ኩባንያ እርሻ ላይ ነዋሪዎቹ እሳት የለቀቁበት፡፡
ብዙ የሚታወቀውና 300ሺሕ ሔክታር የእርሻ መሬት በየዓመቱ ተከፋፍሎ የሚከፈል 50 ሚሊዮን ብር ሊዝ የተከራየው ካሩቱሪስታን (ካራቱሪ) ነው፡፡ የግብርና ድርጅቶቹ የሥራ ማስኬጂያ ገንዘባቸውን የሚያገኙት ከዚሁ አገር በመሆኑ ኢንቨስትመንቱ በዚህ ረገድ የሚያስገኘው ጥቅም የለም፤ እንዲያውም ‹ካራቱሪ 62 ሚሊዮንብር የባንክ ዕዳውን መክፈል አልቻለም፡፡ ይባስ ብሎ የሠራተኞች ጡረታ ተቆራጭ እና የገቢ ግብር ለመንግሥት አላስገባም› ብሎ ሰንደቅ ጋዜጣ የዘገበው በቅርቡ ነበር፡፡ ከመሬት ሊዙ ይገኛል የሚባለው ጥቅም ‹‹የቴክኖሎጂ ሽግግር›› ነው፡፡ ነገር ግን የአካባቢዎቹን ነዋሪዎች እያበሳጨና በሌላም፣ በሌላም ከወዲሁ በተለይ ለነዋሪዎቹ አለመመቸቱን ምልክቶች ያሳያሉ፡፡
ይህን የእርሻ መቃጠል ስናነሳ በታሪክ ወደኋላ ተጉዘን ዘመነ መሳፍንት ላይ እንደርሳለን፡፡ በዘመኑ አቅም ያለው ሁሉ ባላባት የነበረበት እና ምስኪኑን ገበሬ በተደጋጋሚ እያስገበረ ያስመርር ነበርና የወቅቱ ገበሬ ገና ወታደሮች መምጣታቸውን ሲሰማ የገዛ መኸሩ ላይ እሳት ይለቅ ነበር ይሉናል የታሪክ ባለሙያዎች፡፡
ታሪክ ራሱን ደገመ!
ሰሞኑን አንድ ወዳጄ ያዋሰኝ በ2011 በFSS የታተመ የደሳለኝ ራሕመቶ ጥናት (LAND TO INVESTORS: Large-Scale Land Transfers in Ethiopia) መንግሥት የመሬት ልማት የሚለውን መቀራመት ችግሮች በአምስት አንኳር ነጥቦች ያስቀምጧቸዋል፡፡ እኔ በራሴ አገላለጽ እንደሚከተለው እዘረዝራቸዋለሁ፡-

1. የገጠር ኢኮኖሚ መዛባት
ለውጭ ባለሀብቶች የሚያደላው ይህ ስርዓት ግዙፍ የግብርና ፕሮጀክቶቹ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ተጠቃሚዎች ከመሆናቸውም ባሻገር የትናንሽ ገበሬዎቹን ኢኮኖሚ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በማቃወስ የሀብት ልዩነቱን ይበልጥ ያሰፋዋል፡፡ ፉክክሩም ‹‹ባላቸውና በሌላቸው›› መካከል ይሆናል፡፡ በረዥም ጊዜ ሀብታሞቹ በኬሚካሎች ይዘቱን አራቁተው ሲሄዱ ድሀዎቹ ደረቅ መሬታቸውን ታቅፈው ይቀራሉ፡፡

2. የተጠቂነት ስሜት
የመሬት ነጠቃው /ኢንቨስትመንት የሚሰጥበት መንገድ/ ግልጽነት የጎደለው እና ያለነዋሪዎቹ ሙሉ ፈቃደኝነት የሚከናወን በመሆኑ፣ ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሱ በተጨማሪ ሰሚ እና ዋስትና የማጣት ስሜት /voiceless-ness and insecurity/ በነባሮቹ ማኅበረሰቦች ላይ ይፈጥራል፤ ስለሆነም ነዋሪዎቹ ‹‹ኢንቨስትመንቱን›› በቀና አይቀበሉትም ወይም ሊቀበሉት የሚያስችል ምክንያት የላቸውም፡፡
3. ‹‹የማያልፍለት ድኻ ሀብታም የመጋበዙ›› ጉዳይ
የውጭ ባለሀብቶች ምርታቸውን ስለሚያቀርቡለት አካል መደበኛም ሆነ ኢ-መደበኛ ስምምነት የለም፡፡ እንደምሳሌ የሕንድ ኩባንያዎች እዚህ ያመረቱትን ከፊሉ የአገራቸውን ‹‹የምግብ ክፍተት›› ለመሙላት፣ ከፊሉን ደግሞ ለሌሎች አገራት በጥሩ ትርፍ ለመሸጥ ነው መሬት ከኢትዮጵያ የገዙት፡፡ ኢትዮጵያ ግን በየዓመቱ የምግብ እጥረት የሚያጋጥማት እና ከውጭ እጆቿን ዘርግታ የምትለምን አገር ናት፤ (እጅ መዘርጋት መፍትሔ ይመስል!)
4. የቴክኖሎጂ ሽግግር ብሎ ነገር አለመኖር
የግዙፍ ግብርና ፕሮጀክቶች በባሕሪያቸው ትላልቅ ማሽነሪዎችን የሚጠቀሙ በመሆናቸው እና በበሬና ገበሬ ትከሻ አራሽ የገበሬ ቤተሰቦች ቴክኖሎጂ ሽግግር ያድርጉ ቢባል እንኳን ከነዚህ ግዙፍ ማሽነሪዎች ምንም ማግኘት አይችሉም፡፡ ስለዚህ አንዱ የመንግሥት መሬት በርካሽ የመቸብቸብ ግብ መቼም የተባለለትን አያመጣም፡፡
5. ሌሎች አማራጮች አልተቀመጡም
መንግሥት መሬት ለግዙፍ የግብርና ፕሮጀክቶች ማከራይትን እንደብቸኛ አማራጭ በመያዙ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች እንደተሞከረው መሬቱን፣ የደን እና የእንስሳት ይዘቱን እንደጠበቀ የገቢ ምንጭ ማግኛ አማራጭ መፈለግ ይቻል ነበር፡፡ በተለይም የጋምቤላ ደን እና የእንስሳት ይዘት /ecosystem/ በግዙፍ ግብርና ስም አደጋ ላይ ወድቋል፡፡ በረዥም የጊዜ ሒደት ወደማይመለስበት የደን ሀብት መራቆት ደረጃ ይደርሳል፡፡
እንግዲህ ገበሬዎቹን የሕንዶቹን እርሻ ለማቃጠል ያበቃቸው ከነዚህ ችግሮች አንድ ሁለቱ ብቻ ይሆናሉ፡፡ ነገር ግን ችግሮቹ ከዚያም የባሱ ናቸው፡፡

መንግሥት አያውቅም እንዳይባል ብዙ ምሁራን ብለውት፣ ብለውት ደክሟቸው ነው የተዉት፡፡ ስለዚህ አጥኚው (ደሳለኝ ራሕመቶ) እንደሚሉት ‹‹ill-conceived›› (በክፋት የተፀነሰ) ሐሳብ ስለሆነ፣ በእኔ እምነት መፍትሔው የስርዓቱን ክፋት በሠላማዊ ሁኔታ እስከገጥግ መታገል ነው፡፡

ብዙዎቻችሁ ከኢትዮጵያ ውጭ ምትኖሩ አንባብያን አዲሱን መጽሐፍ ባላችሁበት ለማግኘት ጠይቃችኋል፡፡ ያለው አማራጭ በ [email protected] ኢሜይል ላኩልን፡፡ በኢሜይላችሁ ያላችሁበትን አድራሻ አብራችሁ ላኩልን፡፡ የመላኪያውን ዋጋ ጠይቀን እንነግራችኋን፡፡ ከዚያም የመጽሐፉንና የመላኪያውን ዋጋ በባንክ በኩል ከላካችሁ መጽሐፉን በነጠላም ሆነ በብዛት እንልክላችኋለን፡፡ አስቀድመን በመላክም ከሀገር ቤቱ አንባቢ እኩል እንድታነቡ እናደርጋለን፡፡
መልካም ንባብ፡፡ 

ግምገማውን ተከትሎ የዋና ሥራ አስኪያጅ ሹመትና መዋቅራዊ ለውጡን ለማደናቀፍ በተለያዩ የመቀስቀሻ አጀንዳዎች አሉባልታ ሲነዙ፣ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያንን ለአድማ ሲቀስቀሱ በቆዩ ሓላፊዎች ላይ የሚወሰዱ ርምጃዎች ይጠበቃሉ፡፡ ለዋ/ሥ/አስኪያጅ ሹመት÷ በጎጠኝነትና በጥቅመኝነት የማግባባት እንቅስቃሴ እየተካሄደ ነው፤ ወደ ረዳት ሊቀ ጳጳሱ እና ወደ ፓትርያርኩ የጳጳስና የባለሥልጣን አማላጅ የላኩ፣ የድጋፍ ፊርማ በማሰባሰብ የተጠመዱም አሉ፤ ከብር 6.7 ሚልዮን በላይ በኾነ የገቢ …

የጋራ ማሕበር ለመመስረት የተስማማሙት ፖለከኞች እንደሚሉት የመጨረሻ አላማቸዉ ቢቻል ሁሉንም በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ ተቃዋሚዎችን ይሕ ቢቀር ሰላሳ ሰወስት ፓርቲዎችን አስተባብሮ አንድ ጠንካራ ተቃዋሚ ጎራ ለመፍጠር ነዉ።ይሕ ምናልባት ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት በተቃዋሚዉ ጎራ የሚታየዉን መከፋፋል፥ መሰነጣጠቅና መጠላለፍ ለማስቀረት ይረዳ ይሆን?

ፕሬዚደንታዊ ምርጫ በደሴቲቱ ማዳጋስካር ከዘጠኝ ቀናት በፊት የተካሄደው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ የመጀመሪያ ውጤቶች እንዳሳዩት፣ በተወዳዳሪነት ከቀረቡት 33 ዕጩዎች መካከል አንዱም ለድል የሚያበቃውን ድምፅ ባለማግኘቱ በሀገሪቱ እአአ የፊታቸን ታህሳስ ፣ 2013 ዓም ሁለተኛው ዙር ምርጫ ይደረጋል።

click here for pdf
በቅዱሳት መጻሕፍት ዕውቀትና በቤተ ክርስቲያን ትምህርት የበሰሉ፣
ዘረኝነትንና ጠባብነትን እስከ መጨረሻው የተዋጉ፣
የፍቅር መሥፈርታቸው ሰው መሆን ብቻ የሆነ፣
ቤተ ክርስቲያን የቤተ መንግሥቱ ጥገኛና ተቀጽላ እንዳትሆን በብርቱ የተጋደሉ፣
ለእምነታቸውና ለአቋማቸው ሲሉ ከነገሥታቱ ጋር ፊት ለፊት የተገዳደሩ፣
ከእሳት፣ ከግርፋት፣ ከአራዊት፣ ከዘንዶ፣ ከግዞት፣ ከስደት ጋር ተጋፍጠው እምነታቸውን ያስከበሩ፣
ነገሥታቱ በተሳሳተ መንገድ ሲሄዱ እንደ ዮሐንስ መጥምቅ ያለ ፍርሃት የገሰጹ፣
በመላዋ ኢትዮጵያ ለስብከተ ወንጌል የተሠማሩ፣
ቤተ መንግሥትን ለሥልጣንና ለጥቅም ሲሉ ከተጠጉ ሥጋውያን ካህናት ጋር በእምነትና በጽናት ያደረጉት ትግል፤
ምንኩስና መንኖ ጥሪት(ሀብት ንብረትን መተው) ነው ብለው የተሰጣቸውን የማባበያ ገንዘብ፣ ወርቅና ርስት ላለመቀበልና       ሃይማኖታዊ ነጻነታቸውን ለመጠበቅ ያደረጉት ተጋድሎ፣

የአራት የእምነት ኃያላን አበው

                             (አቡነ በጸሎተ ሚካኤል፣ አቡነ ፊልጶስ፣ አቡነ አሮን፣ አቡነ አኖሬዎስ) ታሪክ
ከበቂ ታሪካዊ ማብራሪያ፣ የፎቶ ግራፍና የሥዕል ማስረጃዎች፣ የቦታና የሰዎች ስሞች መዘርዝሮች ጋር፣

የመካከለኛው ዘመን ኢትዮጵያ ሃይማኖታዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊና ባሕላዊ ታሪክ በሰፊው የተዳሰሰበት፣
        ጠፍተው የነበሩ ቦታዎችን በአሠሣ በመፈለግ፣ የጠፉ መረጃዎችን ከየገዳማቱና አድባራቱ በማፈላለግ፣ በቀደምት ሊቃውንት            የተጻፉትን በማጣቀስ፣ የተዘጋጀ የጥናት መጽሐፍ፣

በመጽሐፉ ውስጥ

• የአቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ የአቡነ ኤዎስጣቴዎስ፣ የአቡነ ዜና ማርቆስ፣ የአቡነ ኢየሱስ ሞአ፣ የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ፣
• በአሥራ ሁለት አህጉረ ስብከት ለስብከተ ወንጌል የተሠማሩት የአሥራ ሁለቱ ንቡራነ ዕድ ታሪክና የሥምሪት ሀገረ ስብከት            በስፋት ቀርቧል፤
• በመካከለኛው ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ የኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሰፊ ቦታ ያላቸው ግብጻውያን ጳጳሳት – የአቡነ ዮሐንስ፣           የአቡነ ያዕቆብ፣ የአቡነ ሰላማ መተርጉምና የአቡነ በርተሎሜዎስ ታሪክ ቀርቧል፤
• በደቡብ ኢትዮጵያና በኦሮሚያ ጥንት የነበሩትን የስብከተ ወንጌል እንቅስቃሴዎች ያሳያል፤
• አቡነ ፊልጶስ ዛሬ ስላለችው ቤተ ክርስቲያን ከ600 ዓመታት በፊት የተነበየውን ትንቢት ያዩበታል

ነገሥታቱና መኳንንቱ ሲያሳድዷቸውና መከራ ሲያበዙባቸው፤ ከነገሥታቱ ጋር የተጠጉ የቤተ መንግሥት ካህናትና መነኮሳት ሲያሳብቁባቸውና ተንኮል ሲሠሩባቸው፤ እግዚአብሔር ደግሞ ቅድስናቸውንና እምነታቸውን በተአምራት ሲገልጥላቸው ያያሉ፡፡

                            አራቱ ኃያላን – ከአሥራ አምስት ቀን በኋላ በገበያ ላይ ይውላል

Ethiopia Zare (አርብ ጥቅምት 23 ቀን 2006 ዓ.ም November 1, 2013):- ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል በእስር ላይ የሚገኘውን የብእር ሰው፣ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ ባለቤቷን እስክንድር ነጋን ተለይታ ከምትኖርበት ዋሽንግተን ዲሲ የሀገሯን የመጨረሻ ስንብት በሚመለከት ለህሊና እስረኞች ለሆኑት ታሳሪዎች ያስተላለፈችው መልእክት ይፋ ተደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Ethiopia Zare (አርብ ጥቅምት 23 ቀን 2006 ዓ.ም November 1, 2013):- ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል በእስር ላይ የሚገኘውን የብእር ሰው፣ ጋዜጠኛና የፖለቲካ ተንታኝ ባለቤቷን እስክንድር ነጋን ተለይታ ከምትኖርበት ዋሽንግተን ዲሲ የሀገሯን የመጨረሻ ስንብት በሚመለከት ለህሊና እስረኞች ለሆኑት ታሳሪዎች ያስተላለፈችው መልእክት ይፋ ተደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ኦህዴድ ከወረዳ ጀምሮ ያሉ አባላቱን እየገመገ ሲሆን፣ ግምገማው በእርስ በርስ ሽኩቻና መጠላላፍ እየተካሄደ ነው። ከድርጅቱ አመራሮች መካከል አንዱ ለኢሳት እንደገለጹት ድርጅቱ ህልውና አደጋ ውስጥ ወድቋል።የዝምድና አሰራር እንዲሁም በቡድን ተደራጅቶ አንዱ ሌላውን የሚያጠቃበት ሁኔታ በሰሞኑ ግምገማ በስፋት የታየ ሲሆን፣ አብዛኛው ከታች እስከ ላይ ያለው …

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አለማቀፉ የገንዘብ ተቋም ባወጣው የ2004-2005 ግምገማ ኢትዮጵያ ድህነትን ለመቅረፍ የምታደርገውን ጥረት አድንቋል። በኢኮኖሚው ረገድ ስኬት እየታየ መሆኑን፣ አገሪቱም የ7 በመቶ እድገት ማስመዝገቡዋን የገለጸው አይ ኤም ኤፍ፣ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር መንግስት የወሰደውን እርምጃንም አድንቋል። የአቶ መለስ ሞት በፈጠረው መደናገጥ ሁሉም የውጭ ምንዛሬ ለመግዛት መገደዱን በዚህም ሳቢያ የተፈጠረው የምንዛሬ …

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በክልሉ ለረጅም አመታት ኖረው በተለያዩ ምክንያቶች ከአካባቢው እንዲለቁ የተደረጉ አንዳንድ ሰዎች ለኢሳት እንደገለጹት ፣ መስተዳድሩ እንኳንስ የሌሎችን አካባቢዎች ህዝብ መብት ለማክበር ቀርቶ የክልሉን ነዋሪዎች መብት ማክበር አልቻለም ብለዋል። ከሌላ ክአካባቢዎች የመጡ በተለይም የአማራ ተወላጆች ሶማሊያ መናገር አትችሉም እየተባሉ ከስራ መባረራቸውን የገለጹት እኝህ ነዋሪዎች፣ በንግድ ስራ የሚተዳደሩና በጅጅጋ …

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ ሌተናንት ጄኔራል ሆነው የተሾሙት በሱዳን የሚገኘውን እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስር በመሆን  በጸጥታ መስከበር ስራ ላይ የተሰማራውን የኢትዮጵያ ጦር የሚመሩት ምናልባትም ጀኔራል ሳሞራ የነሱን ሊተኩ ይችላሉ የሚባሉት ሌተናንት ጀኔራል ዮሀንስ ገብረመስቀል ተስፋማርያም በአዲስ አበባ የገነቡዋቸው የንግድ ህንጻዎች በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዋጋ እንደሚያወጡ ለእርሳቸው ቅርብ የሆኑ ሰዎች …

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሀኪሙላ መሱድ የሚባለው የፓኪስታን ታሊባን መሪ የተገደለው በአሜሪካ ሰው አልባ የጦር ጅቶች መሆኑን አለማቀፍ ሚዲያዎች ቢዘግቡም እስካሁን ከአሜሪካ መንግስት በኩል የተሰጠ ማረጋገጫ የለም። ግለሰቡ በአሜሪካ ከሚፈለጉ አሸባሪዎች ማካከል አንዱ ነው። አሜሪካ ግለሰቡ ያለበትን ለጠቆመ 5 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት ቃል ገብታ ነበር። የመሱድ ምክትል ባለፈው ግንቦት ወር በተመሳሳይ …

ትላንት ዘሄግ ኔዘርላንድ ውስጥ ያስቻለው ዓ/ዓቀፉ የወንጀል ፍ/ቤት በኬኒያው ፕ/ት ኡሁሩ ኬኒያታ ላይ የተያዘውን የክስ ሂደት እስከሚቀጥለው የካቲት ወር ድረስ ለሶስት ወር ማራዘሙን ኣስታወቀ። የኣፍሪካ ህብረት ግን በቂ ኣይደለም እያለ ነው።

እንግዳችን የኤሌክትሪላል ኢንጂነሪንግ ምሩቅ ነው። በተማረበት ሙያ ሥራ አግኝቶ ነበር ይሁንና በፍላጎት ወደ ንግድ ሥራ ነው የገባው። ለምን? ስለዚህ ወጣት ማንነት እና ከሌሎች አራት ባልደረቦቹ ጋ ተደራጅቶ ስለሚሠራው ያስረዳናል።

በአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት የተዘጋጀው የ5 ሳምንት ስልጠና የመጀመሪያው ክፍል (1) እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ ረጅም የነፃነት ዘመን ሲኖራት በስልጣኔ ግን ብዙም እንዳልገፋችም። ስለዚህ ስልጠና ክፍል አንድ “ኢትዮጵያ ምን ስትሰራ ነበር?” የሚል ጥያቄ አንስቶ ሁለት አብይ ክሎች ያሉት ሰፊ ታሪካዊ መልሶች ሰጥቷል። በመቀጠል ክፍል አንድ (2) የሰላማዊ ትግልን እድገት አስመልክቶ ከክርስቶስ ልደት በፊት አንስቶ ዛሬ እስካለንበት ዘመን […]

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምክንያቱ በውል ባይታወቅም ካለፉት 4 ቀናት ጀምሮ በከተማዋ ከፍተኛ ፍተሻ እየተካሄደ እንደሆነ የዘጋብያችን መረጃ ያመለክታል። በተለይ ዛሬ በከተማዋ መውጫና መግቢያ በሮች ላይ ሰዎች ከመኪናዎች እና ባጃጆች ላይ እንዲወርዱ እየተደረገ በጥብቅ ተፈትሸዋል። አንዳንድ ወገኖች  መንግስት ጸረ ሰላም እና አሸባሪዎች በከተማዋ ገብተዋል የሚል ወሬ እንደሚያስወራ ሲገልጹ፣ ሌሎች ነዋሪዎች ደግሞ …

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዓመት 50ሺ የኮንዶምኒየም ቤቶችን ለመገንባት የያዘው ዕቅድ ከባድ ትችትን ያስከተለበት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዓመት ከ 100ሺ በላይ የቤቶች ግንባታ ለማከናወን ፊቱን ወደቻይና ኩባንያዎች ማዞሩ ተሰማ፡፡ አስተዳደሩ ከ800ሺ በላይ የኮንዶምኒየም ፣ ከ 136 ሺ በላይ የ40 በ60 ቤት ፈላጊ ነዋሪዎችን የመዘገበ ሲሆን ከዚህ ፍላጎት ጋር በማይጣጣም መልኩ …

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ በከፍተኘው ፍርድ ቤት ባለው የአስተዳደር ቊንጮ ማለትም በዋናው ፕሬዚዳንት በዳኛ ውብሸት ሽፈራውና በምክትሉ ማሃል ያለው አለመስማማት እየጨመረ በመሄዱ የፍርድ አሰጣጥ ሂደቱን እያበላሸው መሆኑን ውስጥ አዋቂዎች ገለጹ ። አሁን ባለው አሰራር ተሰሚነት ያለው የኢሃዴግ አባል የሆነው ምክትሉ ሲሆን ፣  ፕሬዘዳንቱ የኢሃዴግ አባል ባለመሆኑ ተሰሚነት አጥቷል ይላሉ …

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቅዱስ ሲኖዶሱ ሰሞኑን ሲያደርግ የነበረውን ምልዓተ ጉበኤ ሲያጠናቅቅ ባወጣው የአቋም መግለጫ ፣ በውጭ አገር ከሚገኙ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ጋር ተጀምሮ የነበረው እርቀ ሰላም ወደ ፊት እንዲቀጥል እና ቤተክርስቲያን አንድነት እንዲጠናከር ወስኗል። የኦሮቶዶክስ ሀይማኖት ተከታዮች ቆጠራ እንዲካሄድና  የቤተክርስቲያኒቷ ታሪክ በደንብ ተጠንቶ እንዲቀርብም ወስኗል። ከፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ተወክለው የመጡ …

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ እና በአማራ ክልሎች ያሉ አርሶ አደሮቹ ለኢሳት እንደተናገሩት ውጤታማ ባልሆኑበትና በግዴታ እንዲገዙ በተጠየቁት የምርጥ ዘርና የማዳበሪያ እዳ እየተዋከቡ ነው። እዳችንን መክፈል አልቻንም የሚሉት አርሶ አደሮች መንግስት መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጠይቀዋል። ግብርና ሚኒስቴር ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያ ጥቅም ላይ የዋለውን ዳፕ የተባለውን ማዳበሪያ ውጤታማ አልሆነም በሚል እንደሚቀይር ማስታወቁ ይታወቃል። …

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቁም ነገር አዘል በሆኑ ቀልዶቹ የሚታወቀው ኮሜዲያን አብረሀም ከጀርባ ህመም ጋር በተያያዘ ሲሰቃይ ቆይቷል። ከጥቂት ወራት በፊት ወደ አውሮፓ በመምጣት በጀርመን አገር ህክምናውን ተከታትሎአል። አብርሀም በማእደ ኢሳት ዝግጅት ላይ ቀርቦ ለኢትዮጵያ ህዝብና የህክምና እርዳታ እንዲያገኝ የረዱትን ወገኖች ማመስገኑና ጤናውም መሻሻልእያሳየ እንደሆነ መግለጹ ይታወሳል ፡፡ ከዲስከ መንሸራተት ጋር  …

ባሰላው ባሰላው እንቢ አለኝ እንዝርቱ፣ ከታችም አይደለ ከላይ ነው ጥመቱ። የጎንደር ሕዝብ እንጉርጉሮ ኦክቶበር 28 እንደ ሃገሩ አቆጣጠር ጠዋት ጉልበተኛ ነፋስ ከባሕር ተነስቶ በደቡብ እንግሊዝ በኩል አድርጎ እያቆራረጠ ወደ ሰሜን ተፈተለከ። የባሕሩ ሰይጣን የላከውን ጉልበተኛውን ነፋስ የፈራው አዳሜ ፈረንጅ ሁሉ ተርበትብቶ እኛንም በሬዲዮንና በቴሌቪዚዮን ሲያርበተብተን ሰነበተ። “ይህንን ቀን ከቆመ የተቀመጠ፣ ከተቀመጠም የተደበቀ ነው የሚያልፈው። ደፍሮ […]

በአዲስ ግንኙነት ዓለምን መቀየር በሚል መሪ ሃሳብ በታላቋ ብሪታንያ ዋና ከተማ ሎንዶን ለሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየዉ የዘጠነኛዉ የዓለም ዕስልምና ምጣኔ ሃብት መድረክ ዛሬ ተጠናቋል።

« በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያዊ ሕጻናት ስሞችን ስንመለከት በአብዛኛዉ ኢትዮጵያዊ ይዘት እንደሌላቸዉ እንረዳለን፤ አብዛኞች ስሞች ቅላጼያቸዉ ለጆሮ እንዲጥሙ እንጂ ፤ ታሪኩ ምን ማለት ነዉ ብለን ጠይቀን ለልጆቻችን ስም ስንሰጥ አንታይም። ይህ ደግሞ የባህል ወረራ እንዳያመጣብን እሰጋለሁ» ያሉን

ቅ/ሲኖዶስ ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪካዊነትና ቀዳሚነት እውነታውንና ትክክለኛውን የሚገልጽ ጽሑፍ እንዲዘጋጅ መመሪያ ሰጠ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት ለምልአተ ጉባኤው ስብሰባ የሰጠው ሽፋን ‹‹የጉርሻ ያህል ነው›› በሚል ተነቀፈ ‹‹ጉባኤው አገር አቀፍ ብቻ ሳይኾን ዓለም አቀፍም ነው፤ የምንሰጠው ትምህርት ነው፤ የምንወድቀው የምንነሣው ስለ ሀገር ጉዳይ ነው፤ ቤተ ክርስቲያን በዐይን የሚታይ በእጅ የሚጨበጥ ታሪክ ነው …

በአገልግሎት ጥራት /በሰው ተኮር ነፍስ የማዳን አገልግሎት/ ምእመናንን ማብዛትና ማጽናት፣ ቤተ ክርስቲያንን ከባይተዋርነትና ጠባቂነት ወደነበራት ሚና መመለስ፣ አስተምህሮዋን ከማይቃረኑ ጋራ ዓለም አቀፍ አጋርነትን በማጠናከር የሰላምና አንድነት ተምሳሌት ማድረግ፣ ለሙስና ችግሮች በንስሐ መንገድ መፍትሔ ማበጀት የቤተ ክርስቲያናችን ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማሕቀፍና ቊልፍ ጉዳዮች ኾነዋል፡፡ በቡድን እየተደራጁ የመንግሥትን ወቅታዊ አጀንዳዎች በአሉታዊ መንገድ የሚጠቀሙ አሉባልተኞችና ሙሰኞች እንዲሁም በቤተ ክህነቱ …

Prof. Al Mariam ፕ/ር ዓለማየሁ ገብረማርያም ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም፦ ነጻነት ለሀገሬ)
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ሕገመንግሥት በሕግ ከለላ ጥላ በቁጥጥር ስር የሚውሉ ዜጎችን አስመልክቶ የሚከተሉትን መብቶች ያጎናጽፋል። “በሕግ ከለላ ጥላ በቁጥጥር ስር የዋለ ማንኛውም ሰው በሕግ አግባብ መብቱ ተጠብቆ ይያዛል። ማንኛውም ሰው በሀሰት ለመረጃ ጠቀሜታ ተብሎ በማስገደድ እንዲያምን ወይም የተባለውን እንዲቀበል አይገደድም። ማንኛውም በማስገደድ የተገኘ መረጃ ተቀባይነት አይኖረውም።” ይላል አንቀጽ 19(2)(5)። እውነታው ሲታይ ግን ይህ የይስሙላ ሙበት የተጻፈበትን ወረቀት ዋጋ ያህል የለውም።

ሙሉውን አስነብበኝ …

 

ኢትዮጵያዊያን በፍርዱ ረክተዋልወ/ሮ ሙሉመቤት ረታ (በሲያትል ኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር)

በእኔ አስተያየት ፍትህ ተበይኗል፤ ዳኛዋም ሆኑ ፍርድ ሰጭዎቹ (ጁሪዎቹ) በትክክል ጉዳዩን አይተው ወስነዋል ብየ አምናለሁዶ/ር ሸክስፒር ፈይሳ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ጥቅምት 20  ቀን 2006 ዓ.ም. October 30, 2013)፦ ከሁለት ዓመት በፊት ሃና ዊሊያምስ የተባለችውን ታዳጊ በቅዝቃዜ ደጅ ላይ በማዋልና በማሳደር አሰቃይተው ገድለዋል የተባሉት አሳዳጊዎቿ ኬሪ ዊሊያምስና ባለቤቷ ላሪ ዊሊያምስ የ37 ዓመትና የ29 አመት ጽኑ እስራት የተወሰነባቸው ሲሆን በሲያትል አካባቢ የሚኖሩ ትዮጵያዊያን በፍርዱ መደሰታቸውን በተለይ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ …