የሙዚቃ ቃና ቅንብር – ማርች 13, 2014
ዘወትር ቅዳሜ ማታ ከደሳለኝ መኮንን ጋር፣ምርጥና አዳዲስ የካንትሪ ማለትም የአሜሪካ አገር ሰብእ፣ የሮክ፣ተሶል፣የፖፕ፣የአር-ኤን-ቢ፣ብሉዝ፣የሬጌና የሂፕ-ሃፕ ዜማዎችን እንዲያደምጡ ተጋብዘዋል።
ዘወትር ቅዳሜ ማታ ከደሳለኝ መኮንን ጋር፣ምርጥና አዳዲስ የካንትሪ ማለትም የአሜሪካ አገር ሰብእ፣ የሮክ፣ተሶል፣የፖፕ፣የአር-ኤን-ቢ፣ብሉዝ፣የሬጌና የሂፕ-ሃፕ ዜማዎችን እንዲያደምጡ ተጋብዘዋል።
ከሰባት መቶ የንግድ መደብሮች በላይ ባወደመዉ እሳት በብዙ መቶ ሚሊዮን ብር የሚገመት ኪሳራ ደርሷል
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ የትምህርት ክፍል በተማሪዎች ብዙም የማይመረጥበት ሁኔታ የትምህርት ዘርፉን ሕልዉና ሳይፈታተን እንደሚይቀር እየተገነገረ ነዉ።
ባለፈው ዓመት ፣ የዩናይትድ ስቴትስና የብሪታንያ የስለላ ድርጅቶች ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ፣ የድርጅቶችን ፣ የግለሰቦችን የታወቁ የሀገር መሪዎችን የግል ተንቀሳቃሽ ስልኮች የድምጽ፤ የጽሑፍና ስዕል አገልግሎት ጭምር ይጠልፉ ነበር ተብሎ፣ ዜናው በዓለም
ፕሬዝዳንት ኪር ባለፈዉ ታሕሳስ በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሐላፊዎችን ከመንግሥት እኩል ሐገር ለመምራት ይሞክራሉ በማለት ወንጅለዋቸዉ ነበር።በቀደም ጁባ ዉስጥ ለተሰለፉት ወጣቶች ንግግር ያደረጉት ምክትል ፕሬዝዳንት ጄምስ ዋኒ ኢጋ የአለቃቸዉን አባባል ደገሙት
የአፍጋኒስታን ምርጫ ከመካሄዱ አንድ ወር በፊት ታዛቢዎች በዚህ አጋጣሚ ለፉክክር የሚቀርቡ 11 እጩዎች ሶስቱ የሕዝቡን ቀልብ እንደያዙ ያመለክታሉ። የፕሬዝደንት ሃሚድ ኻርዛይ ወንድም ቃዩም ኻርዛይ ከፉክክሩ ራሳቸዉን አግልለዉ የቀድሞ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩትን ዛልማይ ራሶልን እንደሚደግፉ ገልጸዋል።
በማዕከላይ አፍሪቃ ሬፓብሊክ በቀድሞ የሴሌካ ሙሥሊም ዓማፅያን አንፃር የሚንቀሳቀሱት ራሱን ፀረ ባላካ ብሎ የሚጠራ የወጣት ክርስትያን ሚሊሺያ ቡድን አባላት ሽብራቸውን አስፋፉ። ሚሊሺያዎቹ ሙሥሊሞቹን ዜጎች መግደል ብቻ ሳይሆን
በጀርመናዊቷ የሀኖፈር ከተማ ባለፈው እሁድ የተከፈተው እና አምስት ቀናት የሚቆየው ትልቁ የኮምፒውተር ትርዒት የመረጃ ቴክኖሎጂን አጠባበቅ እንዴት አስተማማኝ ማድረግ ይቻላል ለሚለው ጉዳይ ትኩረት ሰጥቶዋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ የትምህርት ክፍል በተማሪዎች ብዙም የማይመረጥበት ሁኔታ የትምህርት ዘርፉን ሕልዉና ሳይፈታተን እንደሚይቀር እየተገነገረ ነዉ።
የዕለቱ ዜና
ለማንበብ እዚህ ይጫኑ !

ለኢትዮጵያ የዛሬ አርባ አመት ነው አዲስ ህይወትና ምዕራፍ የተከሰተው፡፡ ሆኖም 1966 ዓ.ም የነገሮች ሁሉ መነሻ አልነበረም፡፡ በዛች ወቅትና አመት በተከሰተው ሁኔታ ብቻ አይደለም ወጣቱ ህይወቱን ለመስጠት የተሰናዳው፡፡ ነገር ግን የአብዮት መፈንዳት የእያንዳንዳችን የውስጥ ስሜት ስለነካ ይመስለኛል፡፡ ለዚህም ምሳሌ የማደርገው ራሴን ነው፡፡ ማህበረሰብ እንዲለወጥ የአንድ ጊዜ የጋራ እርምጃ ሳይሆን የተጠራቀመ ነገር ያስፈልገዋል፡፡ በወቅቱ ወደ 11ኛ ክፍል አልፌ ነበር፡፡ እኔ እኖር የነበረው ከአዲስ አበባ ውጭ ፍቼ ከተማ ነው፡፡ ይህም ለገጠሩ ህዝብ ቅርብ እንድሆን አድርጎኛል፡፡ ቤተሰቦቼ የሀይማኖት ሰዎች ናቸው፡፡ አባቴ ቄስ ነው፡፡ የአባቴ ወንድሞች፣ የአባቴ አባት፣ የእናቴ ወንድሞች፣ የእናቴ አባት…ብዙዎቹ ቄስና የሀይማኖት ሰዎችና ቤተሰብ ነበሩ፡፡ እንደሚታወቀው በነበረው ስርዓት የቤተ ክርስትያን ሰዎችና የመንግስት አስተዳደር ቅርብ ነበር፡፡ በመሆኑም እኔም ለሀይማኖት ቅርበት ነበረኝ፡፡ ቅረበቴ ግን ለእኔ የሰጠኝ ከስርዓቱ ጋር መሳሳብና መዋደድ አልነበረም፡፡ እኔ የቄስ ልጅ እንደመሆኔ የሀብታም ልጅ አልነበርኩም፡፡ (መቼም ዛሬ ካልሆነ ቄስ ሀብታም ሆኖ አያውቅም፡፡)
ለቤተ-ክርስቲያን ቅርብ ስትሆኑ ለጪሰኛውና ለመሬት ቅርብ ትሆናላችሁ፡፡ ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን ‹‹እኩል ከእርስት›› የሚባል ነገር ስለነበራት ነው፡፡ እኔ ቤት ባይሆንም የአባቴ ቤተሰቦች ቤት ይህን ስርዓት በግልጽ ማየት ችያለሁ፡፡ ገና 6ኛ እና 7ኛ ክፍል ሆኜ ጭሰኞች ከገጠር እህል ሲያመጡ፣ ግብር ሲበላ፣ ድግስ ሲደገስ፣ ሲስተናገድ (እንዴት ህዝብ በየ ደረጃው ይስተናገድ እንደነበር) በቅርብ ማየት ችያለሁ፡፡ በነገራችን ላይ ገና 6 እና 7ኛ ክፍል ሆኜ ይመስለኛል ፍቅር እስከ መቃብር የታተመው፡፡ ፍቅር እስከ መቃብርን አነበብኩ፡፡ ፍቅር እስከ መቃብር ላይ የፊውዳልና የጭሰኛውን ግንኙነት ሳነብም በስርዓቱ የተማረርኩት እኔ ብቻ አለመሆኔን አመንኩ፡፡ ፍቅር እስከ መቃብር ለልቤ ጥያቄ መልስ ሰጠኝ፡፡ ከእኔው ውጭ ሌሎች ሰዎች እንደሚከፋቸው ማየት ችያለሁ፡፡ ከዛ በፊት ግን የጭሰኞችን ግንኙነት አይቻለሁ፡፡ አንድ ሰው ሁለት አጥር ይኖረዋል፡፡ ጭሰኞች የውስጠኛውን አጥር ከመግባታቸው በፊት ማደግደግና፣ አጋሰሶቻቸውን ማራገፍ አለባቸው፣ እህሉን ተሸክመው ለመግባት፡፡
6ኛ ክፍል ሆኜ ትምህርት ቤት ስሄድ ትንሽ ልጅ የሚመራቸው አንድ መንገድ ዳር ላይ የሚለምኑ ሽማግሌ ነበሩ፡፡ እናም በዛች ትንሽ ጭንቅላቴ ብዙ አስብ ነበር፡፡ ጭሰኞቹ ሲያረጁ እንደዚህ ሰውዬ እንደሚሆኑ አስብ ነበር፡፡ ምክንያቱም ያፈሩትን እየሰጡ ነው፤ ሲያረጁ ደግሞ ከመሬታቸው ይነሳሉ፡፡ እናም ግን ለምን? ግን ለምን? ግን ለምን? የሚል ጥያቄ በብዛት በአዕምሮዬ ይመላለስ ነበር፡፡ ፍቅር እስከ መቃብርን እንዳገኝና እንዳነብ ያደረገኝ ወንድሜ ስለ ችግሮቹ እንድጽፍ ያደርገኝ ነበር፡፡ የተሰማኝን መጻፍ ጀመርኩ፡፡
እስከ 9ኛ ክፍል እስክደርስ ድረስ ሶስትና አራት ባለ 50 ገጽ ደብተር ጻፍኩ፡፡ በ1966 የጻፍኳቸውን ደብተሮች ብቻ ይዤ አዲስ አበባ በመምጣት ንግድ ስራ ትምህርት ቤት ገባሁ፡፡ በ1967 ዘመቻ መሄድ ነበረብኝ፡፡ ዘመቻ እንደሄድኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ያነበብኩት የማኦን ስለ ጭሰኞች የሚያወራ ‹‹The peasant uprising›› የሚለውን መጽሃፍ ነበር፡፡ ውስጤ ያለውን የሚነካ ነገር ተፈጠረ፡፡ ይህ ነገር (አብዮት) ያስፈልገናል ብዬ አመንኩ፡፡ የቄስ ልጅ፣ አክራሪ ኦርቶዶክስ ነበርኩ፡፡ ሆኖም በዘመቻው ወቅት በመጾምና ባለመጾም ተፈትኛለሁ፡፡ ወጣት ስትሆኑ ደግሞ አዲስ ነገር መቀበልና መሆን አለባችሁ፡፡ በሶሻሊዝም መጾም የለም፣ እንዲያውም በሶሻሊዝም ስም ማረድ (መባረክ) አለብን ሁሉ ይባል ነበር፡፡ በዚህ ጉዳይ ለ6 ወር ያህል ተፈትኛለሁ፡፡ በኋላ ተሸነፍኩና ተቀላቀልኩ፡፡ ስለ ኮምኒዝም የሰማሁት 7ኛ ክፍል ሆኜ ነው፡፡ ስለቻይና ሶቬት አብዮት ነው፡፡ ኮሚኒስት ከሆንን መኪና የለም፣ ቤት የለም፣ ሱፐር ማርኬት ሄዶ መግዛት የለም፣ በካርድ ብቻ መግዛት ነው የሚል ነው፡፡ ይህ ለእኔ በውስጤ የነበር ነው፡፡ የማኦ መጽኃፍና ሌሎች መጽሃፎች ሲጨመሩ ሶሻሊዝም ለኢትዮጵያ እንደሚያስፈልጋት አመንኩ፡፡ ይህ መነሻ ሆኖ ዘመቻ ጣቢያ እያለሁ ዴሞክራሲያን ሳነባት ደግሞ ይበልጡን አመንኩበት፡፡ እንዲያውም ዴሞክራሲያን የሚጽፉት ሰዎች መላዕክት ይመስሉኝ ነበር፡፡ እስከዚያ ድረስ የሚመስጥ ጽሁፍ ነበር፡፡ ያ መመሰጥ ውስጤ ከነበረው መመሳሰል ጋር በመመሳሰሉ ነው ኢህአፓ ውስጥ ያስገባኝ፡፡ ማንም ቀስቅሶኝ አይደለም፡፡ እኩል ተቀስቅሰን እኩል መሄድ አልቻልንም፡፡ እኩል እንደ እኔ ቢቀሰቀሱም ከዘመቻ ተመልሰው ትምህርታቸውን የቀጠሉና ሌላ አቅጣጫን የመረጡ ነበሩ፡፡ ስለዚህ ውስጤ ያለውን ነገር ስለነካ ነው ገብቼ የቀረሁት፡፡ ባላምንበት ኖሮ ከተቀሰቀስኩ በኋላ ቤት ስመለስ በተውኩት ነበር፡፡
1966 አብዮት በእኔ ምሳሉ ሳየው ድንገተኛ አልነበረም፡፡ የካቲት ወር በአንድ ሰልፍ ዩኒፎርም ለብሰን መንገድ ላይ ስንወጣ ‹‹እንኳን ደስ አላችሁ!››፣ ‹‹እንኳን ጀግና ሆናችሁ!›› እንባል ነበር፡፡ ነባራዊ ሁኔታው፣ የኑሮ ውድነት (ከዛሬው ጋር የሚወዳደር አልነበረም) አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ አባቴ በርካታ ቤተሰብን በ80 ብር ማስተዳደር ይችል ነበር፡፡ የዛን ጊዜና የአሁኑን ማመሳሰል አይቻልም፡፡ የተወደደው ቅቤ ሳንቲም ጨምሮ 3 ብር፣ ዘይት ሁለት ብር፣ ጤፍ 50 ብር ይሸጥ ነበር፡፡ የ1966ቱ የኑሮ ውድነት ከዛ በፊት ከነበረው ርካሽ ኑሮ ጋር የሚነጻጸር ነው፡፡ ከድሮው ጋር ሲነጻጸር የኑሮ ውድነቱ እሳት እንደነደደ ይቆጠራል፡፡ ያ የምርት ግንኙነት፣ ማህበራዊና ስነ ልቦናዊ ችግር ጋር ሲደማመር እንጅ ወታደሩና ተማሪው ስለተሰለፈ ብቻ የመጣ አይደለም፡፡ ያን ሁኔታ ወደ አንድ ሁኔታ (አብዮት) ለመቀየር፣ የታክሲ ሾፌሮች፣ የወታደሩ የደሞዝ ጭማሬ፣ የሴክተር ሪቪው ተጨምሮበት 1966ን የኢትዮጵያ አንድ ምዕራፍ አደረገው፡፡ ስርዓቱ ጠንቃቃ ባለመሆኑና ብዙ ስላልተሰራ ነው አብዮቱ የፈነዳው፡፡ አሁን እኮ እየተመለስን ያለነው ወደ ካፒታሊዝም ነው፡፡ ስርዓቱ ጠንቃቃ ቢሆን ያለምንም ውጣ ውረድ የተሳካ ስርዓት በገነባን ነበር፡፡ የከፈልነው መስዕዋትነት የማይገባ ነበር፡፡
በዘመቻው ወቅት ከአዲስ አበባ ወጥተን ገጠር በመግባታችን ለማንበብም ሆነ ለህዝብ ቅርብ መሆን ችለናል፡፡ ውስጣችን የነበረውን እምነት የቀየረው ይህ ነው፡፡ ወጣቱም አንዴ ከተነሳ መመለስ ያቃተው ለዚህ ነው፡፡ ኢህአፓ ውስጥ ስገባ ያጋጠመኝ ነገር ደግሞ በፊት ከማስበው የተለየና እምነቴን ያሳደገልኝ ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች እንደ ሰው አይደሉም የሚለውን እምነቴን አጠናክሮልኛል፡፡ በወጣት ማህበራት እንገናኝ ነበር፡፡ የፓርቲው ሳይሆን ኢህአወሊ (የወጣት ማህበሩ) አባል ነበር፡፡ ኢህአወሊ ራሱን የቻለ ፓርቲ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ከወጣት ሊጉ ከገባሁ በኋላ ሀይለኛ ስብዕና አግኝቻሁ፡፡ ከዛ በፊት የነበረኝ አላማ ዩኒቨርሲቲ መግባት የዩኒቨርሲቲ መምህር፣ ፕሮፌሰር ሆኜ የምሁር ህይወት መኖር ነበር፡፡ ያ ሁሉ ህልሜ ቀርቶ ከዘመቻ ስንመለስ ‹‹ከትግል በኋላ ትምህርት›› የሚለው የወጣት ሊጉን መፈክር ይዘን ትግል ገባን፡፡ ትግሉ እየከረረ መጣ፡፡ ደም በደም ሆነ፡፡ የመጀመሪያው ደም በሚኒስትሮቹ ጀመረ፡፡ በእነሱ የተጀመረው ግድያ ወደ ሌላ ግድያ ተቀየረ፡፡
ኢህአፓ ውስጥ ከገባን በኋላ የሰዎቹ መልካምነት፣ እድገት በህብረት ሄጄ የዩኒቨርሲቲ ካየሁ በኋላ ባገኘኋቸው ተማሪዎች ስብዕና በማየቴ ከውስጤ ነው ያመንኩት፡፡ ምክንያቱም ኢህአፓ የውስጣችን ስሜት ነው የነካው፡፡ ፓርቲ ውስጥ ያየሁት ደግሞ ይበልጡን ልቤን የሚሞላ ነበር፡፡፡ ለራሳችን መኖርና ስብዕናችንን መጠበቅ እንዳለብን፣ ነገር ግን ቅድሚያ ለህዝብ እድንኖር በተግባር አስተምረውናል፡፡ ኢህአወሊ እያለሁ አንድ ሰልፍ ነበር፡፡ ለማምለጥ ስንሮጥ አንድ ሰፈር ውስጥ የተደረመሰ ሽንት ቤትና ውጭ ደግሞ የሚመጥ የቆመ መኪና ላይ ደረስን፡፡ በዚህም ምክንያት አስም ተቀሰቀሰብኝ፡፡ ትንሽ እንደሄድን መራመድ አቃተኝና ተቀመጥኩ፡፡ ሌላው እየሮጠ አንድ በእድሜ የሚበልጠኝ ሰው ቆሞ ይጠብቀኛል፡፡ ‹‹ለምንድን ነው የቆምከው? አምልጥ!›› ስለው ‹‹ለምን ጥየሽ እሮጣለሁ? ይልቁን ጥቂት እርጅኝና ጥግ አስይዤሽ እሄዳለሁ›› አለኝ፡፡ ጥይት እየተተኮሰ እኔን ይጠብቃል፡፡ ይህ ድርጅቱ ለእኔ እንደሚቆም ማወቅ ስላስቻለኝ ብርታት ሰጥቶኛል፡፡ አስሙ እየባሰብኝ ሲሄድ ባልጠበኩት ሁኔታ የአስም መድሃኒት ተላከልኝ፡፡ ይህኛውም ሌላ ጉልበት ነበር፡፡
ሌላ ጊዜ ደግሞ አዲስ አበባ ላይ መኖር ከባድ ሆነ፡፡ ወደ አሲምባ ለመሄድም አይቻልም ነበር፡፡ ናዝሬት ላይ አንድ ቤዝ ሊቋቋም ነበር፡፡ ያኔ ከእኛ ሰፈር ሶስት ወጣቶች ወደ ቤዙ ሊሄዱ ነበር፡፡ ግን መድረስ ባለመቻላቸው ተመልሰው መጡ፡፡ ከተመለሱ በኋላ ታሰሩ፡፡ ልጆቹ በመታሰራቸው ለእኔ ሂስ መጣልኝ፡፡ ቁጭ ብየ አነበብኩት፡፡ ሂሱም ልጆቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት በሚተዋወቁት ሰዎች መካከል ሊሆን እንደሚችልና፤ መረጃ ከእኔ በኩል አፈትልኮ እንደሆነ የሚያሳይ ጠንከር ያለ ሂስ ነው፡፡ እኔ የት እንደሄዱ ስላላወቅሁ በጣም አዘንኩ፡፡ መልስ መጻፍ እንዳለብኝ አሰብኩ፡፡ እኔም ለእንዲህ አይነት ድርጅት ከሆነ አባል የሆንኩት መሳሳቴንና ከድርጅቱ እንደምወጣ ጻፍኩ፡፡ በሳምንቱ ግን የሚገርም መልስ ጻፉልኝ፡፡ መልሱ ለእኔ ለትንሹዋ ልጅ የሚሰጥ አልነበረም፡፡ ‹‹ተንበርክከን ይቅርታ እንጠይቃለን›› የሚል ከጸኃፊው ማብራሪያ ጋር ተዳምሮ ይቅርታ ተጻፈልኝ፡፡ ‹‹እንደ አንቺ ያለ ጠንካራ አባል ስላለን እንኮራለን›› አሉኝ፡፡ ይህም ሌላ ጉልበት ነበር፡፡ ይህን የጻፉልኝ ለአባላት ትልቅ ክብር እንዳላቸው መሆኑን አምኛለሁ፡፡ ሂስና ግለሂስን የተማርኩት ያኔ ነው፡፡
ብዙዎቹ ጓደኞቻችን ሞቱ፣ የተረፍነው ዳንን፣ ከእስር ተፈታን፣ መኖር የግድ ነውና መኖር ጀመርን፡፡ ያ ውስጤ የነበረን አላማ የነካውን ኢህአፓና ኢህአወሊ ውለታ ተሸክሜ መኖር አቃተኝ፡፡ በእርግጥ 20ና 30 አመት አልፎታል፡፡ ያ ትውልድ የሞተው፣ እኔ ያን ሁሉ የሆንኩት ኢትዮጵያን ለማጥፋት ባይሆንም በርካቶች ግን መኖር እንዳንወድ አድርገው ይወቅሱናል፡፡ በእርግጥ ስለማያውቁን ነው የሚል ጥያቄ ይመላለስብኝ ነበር፡፡ አንድ ወቅት ይህን መልስ እንዳገኝ አደረገኝ፡፡ አንድ ዓለም አቀፍ ድርጅት በምሰራበት ወቅት አንድ ቡድን ይዤ ለልምድ ልውውጥ ወደ ኬንያ ሄድኩ፡፡ በእረፍት ሰዓት ሰብሰብ ብለን ስናወራ ስለ ‹‹ያ ትውልድ›› መወራት ጀመረ፡፡ አጥፍተውት አለፉ እያሉ ይወቅሱታል፡፡ የአንድን ነገር ውጤቱን ብቻ አይቶ መገምገምና መውቀስ ተገቢ አይደለም፡፡ ‹‹ለምን እንዲህ ትወቅሷቸዋላችሁ?›› ስለቻው፤ ‹‹አታውቂያቸውም!›› አሉኝ፡፡ ‹‹እኔን አታውቁኝም? እንዴት ነው እኔ የማላውቃቸው? ያ ትውልድ ማለት እኔ ነኝ!›› አልኳቸው፡፡ ‹‹አንቺ ምንድን ነሽ?›› አሉኝ፡፡ ‹‹ኢህአፓ ነበርኩ!››፡፡ አላመኑም፡፡ ‹‹እኔ አላማ የለኝም? ጭራቅ ነኝ? እኔ ክፉ ነኝ? እኔ ኢትዮጵያን አልወድም?›› የሚል ጥያቄ አነሳሁላቸው፡፡ ‹‹አትቀልጅ! ያ ትውልድማ እንዲህ ሊሆን አይችልም›› አሉኝ፡፡ በእርግጥ በደርግ ጊዜ ሲማሩ ኢህአፓን እንደ ጭራቅ አድርገው ይስሉላቸው ስለነበር ነው፡፡ ‹‹እንግዲያውስ የጠፋው ጠፍቷል ነገር ግን አውቀን አላጠፋነውም አልኳቸው፡፡›› አንድ ነገር መለካት ያለበት በውጤቱ ብቻ አይደለም፡፡ የእኛ አጀንዳ ኢትዮጵያን ማጥፋት አልነበረም፡፡
ልጆቹን ‹‹ስለዛ ትውልድ፣ ስለ ኢህአፓ ማወቅ ትፈልጋላችሁ ልጻፍ?›› አልኳቸው፡፡
‹‹አዎ ጻፊ!››
‹‹ምን አይነት ልጻፍ?››
‹‹ትንሽ እንጨት እንጨት እንዳይል እንጅ ጻፊ!››
‹‹ምንድን ነው እንጨት እንጨት እንዳይል ማለት?
‹‹ትንሽ ፍቅር ቢጤ ጣል አድርጊበት?
‹‹እንዴ! እኛም እኮ ፍቅር እናውቅ ነበር ከየት አምጥቼ ነው ጣል የማደርገው?››
ከዛም ‹‹ምርኮኛ››ን መጻፍ ጀመርኩ፡፡ ከ30 አመት በኋላ ይህን መጽኃፍ የጻፍኩት የዛ ዘመን ፖለቲካ ስላሳመነኝ ነው፡፡ ከአንድ ነገር ጋር ለመዝለቅ ውስጣችን መነካት አለበት፡፡ ሌላ አጀንዳ ካለን፣ ሌላ የምናስበው ነገር ካለን፣ ያንን አጀንዳ ብለን የምንገባ ከሆነ በጊዜ መውጣት ነው የሚያዋጣው፡፡ እኔ የምችለውን ያህል ሄጃለሁ ብዬ አስባለሁ፡፡ ተሂዶ ተሂዶ መዝለል የማይቻል ጎርጅ ላይ ሲደረስ የግዱን ይቆማል፡፡ ከዛ በኋላ ያ ትውልድ ለምንድን ነው ያልቀጠለው የሚለው ሌላ ጉዳይ ነው፡፡ በደርግ ዘመን የደረሰውን ስነ ልቦናዊ ችግር ሲታሰብ ከባድ ቢሆንም ከዛም በኋላ ግላዊ ህይወት ባሻገር ለአገር መስራት አይቻልም ነበር ወይ? የሚለው የእኔም ጥያቄ ነው፡፡ የትውልዱ አለመቀጠል ግን በርካታ ምክንያቶች ይኖሩታል፡፡
የ1966 አብዮት ሲፈነዳ ከላይ የጠቀስኳቸው እርሾዎች ሆነው አብላልተውታል፡፡ ተማሪውም ጥያቄ የጀመረው ቀደም ብሎ ስለነበረ ነው፡፡ የዓለም የፖለቲካ ሁኔታም ስላገዘው ነው፡፡ ይህ ጉዳይ የ1966ን አብዮት አዲስ ምዕራፍ ቢያስከፍተውም ያ ምዕራፍ ግን መዝለቅ አልቻለም፡፡ ምክንያቱም አንዳንዴ ያልታሰበ ውጤትና ስኬት ሰውን ወደ ሰማይ እንዲመጥቅ ያደርጋል፡፡ በዚህም ምክንያት መነሻን አለማሰብ ነገር ተከስቷል፡፡ ብዙ ፖለቲካ ብስለት ሳይኖር ብዙ ነገሮች ተከሰቱ፡፡ ስለዚህ የ1966 አብዮት ለውጥ አምጥቶ ነበር፡፡ ሆኖም የመከነ ለውጥ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ በሌላ በኩል ለብዙዎቻችን ዛሬ ድረስ የተሻገረ የአገር ፍቅር ሰጥቶን አልፏል፡፡ ስብዕናችንን እንድንሞርድና እንድንሻሻል አድርጎናል፡፡ እኔ ስለ እራሴ ብቻ ነው መናገር የምፈልገው፡፡ ቢያንስ እኔ አጭበርብሬ አላውቅም፡፡ እንዳላጭበረብር ያደረገኝ ግን እኔ ልዩ ሰው ሆኜ ሳይሆን ያኔ የተፈተሸው ማንነቴ ይመስለኛል፡፡ እኔ ለራሴ ጥቅም ብዬ በማንም ላይ ተራምጄ አላውቅም፡፡ ዛሬ 55 አመት ያለፈኝ ትልቅ ሰው ነኝ፡፡ ግን አጭበርብሬ አላውቅም፡፡ ይህን ያላደረኩት ግን የሚፈትነኝ ነገር ጠፍቶ አይደለም፡፡ ህይወትን ለማሸነፍ ይህኛውን መንገድን (ማጭበርበሩን) ብመርጥ እንደሚያዋጣኝ አጥቸው አይደለም፡፡ ግን በዛን ወቅት የተሞረደው ስብዕናዬ ዛሬም ድረስ አብሮኝ ስላለ ነው፡፡ ብዙዎቹ ይህ ስብዕና አላቸው፡፡ እናም 1966 ብዙ ሰው ፈጥሯል፣ ብዙ ሰው ገድሏል፡፡ የገደለው ግን ያመዝናል፡፡ ለዚህም ይመስለኛል ኢትዮጵያ አሁን ለምትገኝበት ሁኔታ የደረሰችው፡፡ የትም አልደረስንም፤ መዋሻሸት አያስፈልግም፡፡ ዛሬም የትም አይደለንም፡፡ የኢትዮጵያን ህዝብ ወደ ውስጥ ገብተን ካየነው ዛሬም የምንበላው የለንም፣ ዛሬም ድሃ ነን፣ እኔ በዙሪያዬ ብዙ በልተው የማያድሩ ሰዎች አሉኝ፡፡ በዙሪያየ የሚኖረው ህብረተሰብ በታክሲ መሄድ የማይችልና ድሃ ነው፡፡ ጤፍ መግዛት የማይችል ማህበረሰብ ነው፡፡ እነዚህ ሁሉ ምክንያት ከ1966 በኋላ በተከሰተው ችግር ነው፡፡ እሴቶቻችንን አጥተናል፡፡ እምነታችንን አጥተናል፡፡ ድሮኮ የእኛ ቤተሰቦች የሆነ ቦታ መሄድ ፈልገው የተሸከሙትን ነገር ቁጥቋጦ ውስጥ ደብቀው ተመልሰው ያገኙት ነበር፡፡ ይህን መጣል ነበረብን? በምን ተክተነው? መጣል አልነበረብንም፡፡ ነገር ግን እምነትን ጣልን፣ መታመንን ጣልን፡፡ አገር ባላደገበት ግን ለራሳችን ለማደግ ብንፍጨረጨርም ከመውደቅ አንድንም፡፡ አንድን ነገር ይዞ ለመዝለቅና ለመነሳሳት ከውስጥ እርሾ ታስፈልጋለች፡፡ 1966ንም የወለደው ያ እርሾ ነበር፡፡ ነገር ግን መነሻው ጥሩ አልነበረምና የተጋገረው ዳቦ ሊጥ ሆነብን፡፡ እናም እዚህ ደረስን፡፡
(ከአዘጋጁ:- ይህን ጽሑፍ ያሰናዳነው ቆንጅት ብርሃኑ ባለፈው ቅዳሜ በሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ተገኝተው ለወጣት የፓርቲው አባላት የትግል ልምዳቸውን ባካፈሉበት ወቅት ከተናገሩት ውስጥ ነው፡፡)
ክንፉ አሰፋ ብርሃኑ ዳምጤ እንደገና ሲገለበጥ የአስር አመት ልጅ ሳለሁ ያጋጠመኝን አንድ ክስተት አስታወሰኝ። በሰፈራችን ውስጥ ልጆችን ሁሉ የሚጠሉ አንድ ሰውየ ነበሩ። አንድ ቀን በድንገት ተነሱና የሰፈሩን ሰው ሁሉ መሰናበት ጀመሩ። በእጃቸው 3 ሜትር የሚያህል ርዝመት ያለው ገመድ ይዘዋል። “የሰፈሩ ልጆች ስላስቸገሩኝ ራሴን ልስቅል ነው። ደህና ሁኑ…” እያሉ ሁሉንም ተሰናብተው ሲያበቁ ለመሰቀል መንገዳቸውን ጀመሩ። የእኝህ […]
ማጋቢት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ለሦስት ወራት በሚካሄደው ክፍል ሁለት “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ሪፎርም” በሚለው ዘመቻ፣ በዋነኛነት በተመረጡ 14 ከተሞች እና በሦስት ተጓዳኝ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍና ህዝባዊ ስብሰባ ይካሄዳል። የመሬትን አጀንዳ የሁለተኛው ዙር የመታገያ አጀንዳ ለምን እንዳደረገ ፓርቲው ሲያብራራ፣ “በባለሃብት ስም ገበሬው ከይዞታው መፈናቀሉ፤ በከተሞች በልማት ስም ዜጎች እየተፈናቀሉ […]
በአሸናፊ ንጋቱ ጽሁፉን ለማንብ እዚህ ላይ ይጫኑ። ህዝብን በመጨቆን ሀገርን መምራት አ ይቻልም የፖለቲካ ስርአትና የአንድ ሀገር እድገት ቀጥተኛ የሆነ ግንኙነት አላቸዉ። አንድ አገር ትክክለኛ ባልሆነ የፖለቲካ አገዛዝ ይበለፅጋል ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ሃገራችን ኢትዮጵያም የወያኔ መንግስት ባነገሰው የተዛባ አገዛዝ …
ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። ወያኔ በሁሉአቀፍ ትግል ከሥልጣን ይውረድ አሁን እንደሚታየዉ በሁሉም አቅጣጫ በኢትዮጵያ ዉስጥ አዲስ የፖለቲካ ለዉጥ እንድሚያስፈልግ እና ከፍተኛ የሆነ መነቃቃት በወጣቱ ሀይል ላይ እየታየ ነዉ፡፡ ይህ የለዉጥ ፍላጎት እና መነቃቃት ወደኋላ እንዳይመለስ ትግሉ የበለጠ ተጠናክሮ …
ሙሉውን ጽሁፍ በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። በቅማንት ብሔረሰብ ላይ እየደረሰ ያለዉ እስራት አፈና የቅማንት ህዝብ በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞን በስምንት ወረዳዎች በኩታ ገጠምና በተያያዘ …
ዘወትር ቅዳሜ ማታ ከደሳለኝ መኮንን ጋር፣ምርጥና አዳዲስ የካንትሪ ማለትም የአሜሪካ አገር ሰብእ፣ የሮክ፣ተሶል፣የፖፕ፣የአር-ኤን-ቢ፣ብሉዝ፣የሬጌና የሂፕ-ሃፕ ዜማዎችን እንዲያደምጡ ተጋብዘዋል።
ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በቨርጅንያ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የነበሩት ቄስ ታደሰ ሲሳይ በተደጋጋሚ የፈጸሙትን ስህተት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ወንድምህ ቢበድልህ አንተና እሱ ሆናችሁ ውቀሰው ። ቢሰማህ ወንድምህን ጠቀምከው …
“ቀሲሲ” ታደሰ ሲሳይ ስልጣነ ክህነታቸውን ተገፈፉ ጽሁፉን በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። አቶ ታደሰ ሲሳይ በአሌክሳንደሪያ፣ ቨርጂኒያ ሐመረኖህ ኪዳነ ምሕረት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተዳዳሪ የነበሩት “ቀሲስ” ታደሰ ሲሳይ በመባል ይታወቁ የነበሩት ግለሰብ ከዛሬ የካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. (ማርች 9, 2014) አንስቶ …
ምንሊክ ሳልሳዊ ፦ህዝብ በኢኮኖሚ ሲጐሳቆል፣ በፖለቲካ በደል ሲሰማውና በማህበራዊ ህይወቱ ያልተረጋጋ ከሆነ ደግ አደለም፡፡ በጥንቱ ማርክሳዊ አካሄድ ፖለቲካ ማለት የተጠራቀመው የኢኮኖሚ ይዘት ነፀብራቅ/መገለጫ እንደማለት ነው፡፡ በግድ አራምደዋለሁ ካሉ አንገት መቀጨት፣ መሰበር፣ መውደቅ፣ አልጋ ላይ መቅረት ይከተላል ማለት ነው፡፡ ለማደግ አቅጣጫ ያስፈልጋል፡፡ ከመዓቱ ለማምለጥ መፍጠንም ያስፈልጋል፡፡ አቅጣጫ ማወቅ ብቻ ሳይሆን መሮጥና መፍጠን ያስፈልጋል ስንል ግን፣ ከምን አቅም? በምን ነፃነት? በምን ፍትሐዊ እርምጃ? በምን ዓይነት ቢሮክራሲያዊ ተቋም? በምን ዓይነት እርስበርስ መተማመን? በምን ዓይነት የገዢ ተገዢ ግንኙነት? ብሎ መጠየቅ ያባት ነው፡፡
የአስተዳደር ነገር መቼም ዋና ጉዳይ ነው፡፡ ኢኮኖሚያችን በኑሮ ውድነቱ መነጽር ሲታይ ዛሬ አሳሳቢ ነው፡፡ የሁሉም ነገር ዘዴው ተገኝቷል እንዴት እንደምንኖር መላው ከመጥፋቱ በስተቀር ፡፡ለፍቶ ለፍቶ፣ ዳክሮ ዳክሮ ኑሮ ጠብ አልል ያለው ሰው ከምሬት ሊወጣ አይችልም፡፡“እምዬ ኢትዮጵያ ሥራሽ ብዙ ፍራንክሽ ትንሽ” አለ አሉ አንድ ሠራተኛ! በእርግጥ በሊቀ – ሊቃውንት አስተሳሰብና ስሌት “ከአምስት አመት በኋላ ሠንጠረዡ ከፍ ይላል”፤ “በ2017 ዓ.ም አያሌ ፕሮጄክቶች ስለሚጠናቀቁ የተለየ ዓለም ይታያል” ወዘተ ይባላል፡፡ ምንሊክ ሳልሳዊ ችግሩ ህዝባችን “ሰብል በጥር ይታፈሳል” ቢሉት “ሆዴን እስከዚያ ለማን ላበድረው” አለ፤ የሚባለው ዓይነት ችግር ውስጥ ይገባል፡፡ አጣብቂኙ ከባድ ነው፡፡ ያለፈው ዘመን መሪ “የወረቀቱ ገብቶኛል፡፡ የገበያውን፣ የመሬት ያለውን ጉዳይ አስረዱኝ” አሉ አሉ፡፡ በግራፍ (ሠንጠረዡ ላይ) ሰብሉ ሰማይ ነክቶ፣ ከገበያው ግን ጠፍቶ ሲያዩት ቢጨንቃቸው ነው፡፡
የአመራራችንን ጉዳይ ችላ ብለን፣ የቢሮክራሲውን አካሄድ ወደጐን ትተን፣ ወደየትም የተሻለ ህይወት መዝለቅ አንችልም፡፡ በአካላችን እያወደስን በሆዳችን እየሰደብን የቱንም ወንዝ አንሻገርም፡፡ የምርጫችንን የዲሞክራሲያችንን ነገርም አደራ መባባል ያለብን ጊዜ ነው፡፡ መጽሐፍ ከመፃፍ፣ አዋጅ ከማወጅ፣ መመሪያ ከማውጣትና ጋዜጣዊ ጉባዔ ከማካሄድ አልፈን በቀናነት ለህዝባችን የሚበጀው ማንኛው መንገድ ነው? ማለት በጐ ነገር ነው፡፡
በኢኮኖሚያዊ ገቢያችን፣ በፖለቲካዊ መልካም አስተዳደራችን፣ በማህበራዊና ባህላዊ ማንነታችን የሚደርስብንን ጉስቁልና አሸንፈንና ድህነታችንን ታግለን በሁሉም አቅጣጫ ለውጥ እናመጣ ዘንድ፤ የህዝብ መነሳሳትን የሚያህል ካፒታል የለም፤ መነሳሳት ተገቢ ነው! አለበለዚያ ትላንት የነበርንበት ቦታ እንደተመቸን ቆጥረን መቀበል “ያደሩበት ጭቃ ከጭድ ይሞቃል” የሚለውን ተረት ከማረጋገጥ በቀር ፋይዳው በድን ነው፡፡
በትዕዛዝ እንግዳ ከመቀበል ይሰውረን፡፡ ባህላዊ እንግዳ – ተቀባይነታችንን ይባርክልን፡፡ ከጐረቤት ጋር ከመጣላት ይሰውረን፡፡ ተጣልተን ከታረቅንም ዕውነቱን የሚነግረን አያሳጣን፡፡ ስንጣላ መፈክር ከማስነገርና ከመራገም፤ ስንታረቅ ከማጨብጨብ ይሰውረን፡፡ የመንግስታችንን ልብና ልቦና እናውቅ ዘንድ የመረጃ ደሀ አያድርገን! የምንሰማውን በሌላ እንዳንተረጉም ንቃተ – ህሊናውን ያድለን ዘንድ፤ የሰላምና የማስተዋል ያድርግልን፡፡ ብሶት ሁሉ የፈጠራ፣ ጩኸት ሁሉ የሁከት፣ ሥጋት ሁሉ የትርምስ፤ እንዳያስመስልብን አስተዋይ ተመልካች ይሰጠን፡፡ ማየት – የተሳነው ተመሪ እንዳይሸበር ነገሩን ግልጥልጥ የሚያደርግ መሪ ይባርክልን፡፡ምንሊክ ሳልሳዊ
በጅጅጋ 300 እስረኞች መንገድ ላይ ተጣሉ
በጅጅጋ እስር ቤት ውስጥ ታስረው ከነበሩ ቁጥራቸው በውል ከማይታወቅ እስረኞች መካከል 300 ያክሉ ከአራት ቀናት በፊት በጅጅጋ መንገድ ላይ መጣላቸው ታውቀ።
የኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት ያላከውን መረጃ በመንተራስ ኢሳት ባደረገው ማጣራት፣ ባለፈው ሃሙስ ለአርብ አጥቢያ አካላቸው በምግብ እጦት የከሳ፣ አይናቸው የታወረ፣ እግሮቻቸው ሽባ የሆኑ፣ የአእምሮ መታወክ የደረሰባቸውና አሰቃቂ የእስር ቤት ህይወት እንዳሳለፉ የሚናገሩ እስረኞች በጅጅጋ ጎዳናዎች ላይ ተጥለዋል።
ከተጣሉት መካከል ወላጅ አልባ የሆኑ ምናልባትም በእስር ቤት ውስጥ የተወለዱ ህጻናት፣ ወጣቶችና አዋቂዎች ይገኙበታል።
አብዛኞቹ እስረኞች ከሰውነት ተራ የወጡና በበሽታ የተጠቁ እንዲሁም ለረጅም ጊዜ በእስር ቤት ውስጥ የቆዩ ናቸው። ኢሳት ለማረጋገጥ ባይችልም፣ የኦብነግ መረጃ እንደሚያሳየው ከተፈቱት እስረኞች መካከል 20ዎቹ በሶስት ቀናት ውስጥ በበሽታ ሞተዋል።
ከአንድ ወር በፊት ኢሳት ከጅጅጋ ከተማ 25 ኪሜትር ርቆ በሚገኝ እስር ቤት ውስጥ በኮሌራ በሽታ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተው በእስር ቤቱ አካባቢ አግባብ ባልሆነ መንገድ በመቀበራቸው አስከሬናቸውን ጅቦች እያወጡ በመብላታቸውና እና አካባቢው በበሽታ በመበከሉ በድጋሜ እንዲቀበሩ መደረጉን ዘግቧል።
የክልሉ መንግስት አሁን የወሰደው እርምጃ በእስር ቤቶች ውስጥ የተነሳውን የኮሌራ በሽታ ለመከላከል እንደሆነ እየተነገረ ነው።
በሶማሊ ክልል የተካሄደውን የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን አስመልክቶ የክልሉን ገጽታ ያበላሻሉ የተባሉ ከ700 በላይ የጎዳና ላይ ተዳዳሪዎችና መታወቂያ የሌላቸው ሰዎች እንዲታሰሩ መደረጉ ይታወቃል።በጉዳዩ ዙሪያ የክልሉን የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። ማጋቢት ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና

እንደልቡ/ዳግም (ከቫንኮቨር፣ ካናዳ)
አባ መላ ማን ነው?
በቅጽል ስሙ “አባ መላ” በእውነተኛ ስሙ ደግሞ ብርሃኑ ዳምጤ ተብሎ ይጠራል፣ በ60ዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ አዛውንት ነው (ምንም እንኳ ስራው እንደ እድሜው ባይሆንም)። ፓልቶክ የሚባለውን የማህበራዊ መገናኛ መድረክ በመጠቀም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዲስኩር በማሰማት ይታወቃል። በወጣትነቱ ኢህአፓ ውስጥ ነበር የሚባለው ብርሃኑ ዳምጤ ወዲያውም የኢህአፓን መዳከም አይቶ ወደ ደርግ ቡድን መቀላቀሉን የሚያውቁት ይናገራሉ። በወቅቱ አብረውት በኢህአፓ ውስጥ ይሳተፉ የነበሩ ወጣቶችን ለደርግ በእጅ መንሻ መልክ አሳልፎ ሳይሰጥ እንዳልቀረ በደርግ ካድሬነት ቆይታው የሚያውቁት ይጠረጥራሉ አንዳንዶች ደግሞ አፋቸውን ሞልተው ይናገሩታል።
ብርሃኑ ዳምጤ ከደርግ መውደቅ በኋላ በስደቱ ዓለም (ዳያስፖራ) ፖለቲካ መድረክ ብቅ ያለው በምርጫ 97 ወቅት የዝነኛውን ቅንጅት ማልያ ለብሶ ነበር። ይሁንና በስልጣን ላይ ያለው የህወሃት/ወያኔ መንግስት ምርጫውን አጭበርብሮ፣ የምርጫውን መጭበርበር የተቃወሙትን በገፍ በአደባባይ በጥይት ደብድቦ፣ ህዝቡ የመረጣቸውን የቅንጅት አመራሮች፣ ጋዜጠኞችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን ጨመሮ ከ50 ሺህ በላይ ባብዛኛው ወጣቶችን አስሮና በየጦር ካምፖቹ አጉሮ በአምባገነንነቱ ለመቀጠል ሲወስን ብርሃኑ ዳምጤም ባፋጣኝ የቅንጅትን ማልያ አውልቆ የህወሃት/ኢህአዴግን ማልያ ለብሶ ቁጭ አለ።
ሰሞኑን ደግሞ ብርሃኑ ዳምጤ አስደናቂ መገለባበጥን ፈጽሞ የህዝብን አይን አስበልጥጧል። እነዚህ ብርሃኑ ዳምጤ (አባ መላ) ሰሞኑን የሚፈጽማቸው መገለባበጦች በ1960ዎቹ እና 70ዎቹ ከነበሩት የመገለባበጥ ትሪኢቶቹ ለየት የሚያደርጋቸው ነገር ቢኖር አሁን መገለባበጡን የሚፈጽመው በቀጥታ ስርጭት ወቅት (በፓልቶክ) መሆኑና ጉዳዮን በመሪ ዜና መልክ የሚዘግብለት የቴሌቪዥን ጣብያ “ኢሳትን” ማግኘቱ ነው።
ብርሃኑ ዳምጤ ከጥቂት ወራቶች በፊት ነበር የተሰለፈበት የህወሃት/ኢህአዴግ ጎራ በተለይም ከወያኔው ቁንጮ መለስ ዜናዊ ሞት በኋላ እየተዳከመ መምጣትን አይቶና ገምቶ ወያኔዎችን “አፍንጫችሁን ላሱ፣ እኔ ከአሁን ብኋላ የድሮው አባ መላ አይደለሁም፣ እንዲያውም ጉዳችሁን አዝረጠርጣለሁ…” በማለት ፉከራ ቢጤ አሰምቶ የዲሞክራሲና የነጻነት ታጋዮችን ጎራ መቀላቀሉን ያበሰረው።
መንፈቅ እንኳ ሳይሞላ አባ መላ በመጣበት አይነት መንገድ ተመልሶ ህወሃት/ኢህአዴግን ለማገልገል መወሰኑን ይፋ አደርጓል። ለሱ እምብዛም አዲስ ያልሆነውን የክህደት ቁልቁለትም ዳግም ተያይዞታል።
አባ መላ፣ ኢሳትና ዳያስፖራው
የኢሳት ጋዜጠኞች፣ አንዳንድ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና የተቃዋሚ ፖለቲከኞችም ጭምር ይህ አባ መላ የሚባለውን ቦታ እየቀያየረ ይሚጫወት ዝቅተኛ ካድሬ ከሚገባው በላይ ቦታ ሰጥተውት እንደነበር እገምታለሁ፣ በውጤቱም ተከታዮቻቸውን ያሳሳቱና ያዘናጉ ይመስለኛል። ይህንን ጉዳይ ማንሳቴ “ብዬ ነበር” ለማለት ሳይሆን ይልቁኑም ይህ ክስተት እንደ መማሪያ ሆኖ እንዲያልፍ በመፈልጌ መሆኑን አባብያን እንዲረዱልኝ እፈልጋለሁ።
እንደ አባ መላ አይነቱ ቀደም ሲል በተደጋጋሚ የመገለባበጥ ብቃቱን ያሳየ ወለፈንዴ ተቃዋሚ ጎራ ገብቻለሁ ሲል አያያዛችን ጥንቃቄ የተሞላበት፣ ሊሆን ይገባል። በቅርቡ ተገልብጦ ሊያሳፍረን ይችላል ብሎ መስጋት፣ ለጉዳዩ መጠነኛ የአየር ሰዓት መስጠትና ውሎ አድሮ ደግሞ መርጋቱን እያዩ ወደሌላው መተላለፍ ተገቢ ነው። እንደው በአንድ ጊዜ ይህን ከምላስ በስተቀር ቁም ነገር የሌለው ተራ ካድሬ ወደላይ ቆልሎ አንድ ጊዜ “አክቲቪስት” ሌላ ጊዜ ደግሞ “የፖለቲካ ተንታኝ” እያሉ በኢትዮጵያውያን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ የተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅትን እንዲመራ ማጨት ድረስ መጓዙና አሉ ከሚባሉ ፖለቲከኞች ጋር መድረክ እንዲጋራ ሁኔታዎችን ማመቻቸቱ አገባብ አልነበረም።
የኢሳት ባልደረባ ደረጀ ሃብተወልድ የአባ መላን መገልበጥ አስመልክቶ በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዳሰፈረው ከሆነ ግን ኢሳቶች ከስህተቶቻቸው ሊማሩ የተሰናዱ አይመስልም ይልቁኑም አባ መላን አስመልክቶ ሊቀርቡ የሚችሉ ትችቶችን ቀድሞ ለመከላከል ነው ሙከራ የሚያደርጉ ያሉት። ደረጀ ሃብተወልድ እንዲህ ነበር ያለው፣
“ነገሩ ወዲህ ነው። አባ መላ ኢህአዴጎችን እየሰደበ ወደ ተቃዋሚው ጎራ ሲቀላቀል “አገኛለሁ” ብሎ ያሰላው ጥቅም ነበር። ሆኖም ሀሳብን በነፃነት ለመግለጽ ከሚያስችል ነፃ መድረክ ውጪ ሌላ ነገር ሊያገኝ አልቻለም። ባገኘው ነፃ መድረክም ማንም ሳይቆነጥጠው ከትንሽ እስከ ትልቅ የቀድሞ አለቆቹን እስከ ዶቃ ማሰሪያቸው ነግሯቸዋል። እኛንም አስቆናል። ስንስቅለት ጨምሮ ጨማምሮ አቅምሷቸዋል። እኛም፦“የአገሩን ሰርዶ ባገሩ በሬ” እያልን ተዝናንተናል። ከዚያ ባለፈ ግን ለቁም ነገር ያሰበው ሰው ስለመኖሩ እጠራጠራለሁ።”
የደረጀን አባባል ሁሉም ሰው የተቀበለው አይመስልም ይህን ለማሳየት ከተቃውሞ ሃሳቦች መካከል አንዱን ከዚያው ከደረጀ ሃብተወልድ የፌስቡክ ገጽ ልበደር፣
“የአባ መላን መገልበጥ ተከትሎ ኢሳቶች ከተወቃሽነት ለመዳን የዘየዳችሁት ይሄው ነው? ደረጀ “አባ መላን ለቁም ነገር ያሰበው ያለ አይመስለኝም” ያልከው ፈጽሞ ከእውነት የራቀ ነው፣ በሳውዲ ወገኖቻችንን ለመታደግ በተቋቋመው አለም አቀፍ ድርጅት ውስጥ ከታማኝ እና አበበ ገላው ቀጥሎ ሶስተኛ ሰው ተደርጎ አልነበረም? በጣም ብዙ ማለት ይቻላል… “እጄን በጄ” ሆኖብን እንጂ። ለማንኛውም ከስህተቶቻችሁ ተማሩ፣ በጣምም አንፍጠጥ ያስተዛዝባል።” ethiopian unity
ለማጠቃለል ያህል የሚሰራ ጋዜጠኛ፣ ለውጥ ለማምጣት የሚተጋ ፖለቲከኛና የዲሞክራሲ ታጋይ በሂደት ውስጥ ስህተት ሊሰራ ይችላል፣ ከስህተቶች ትምህርት ወስዶ ለሁለተኛ ጊዜ ተመሳሳይ ስህተትን ላለመድገም ጥረት ማድረግ ግን ሊለመድ ይገባል። ነገሮቻችን ሁሉ “ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ” እንዳይሆኑ ሃላፊነት ወስደን ከስህተቶቻችን ለመማር ዝግጁ እንሁን።

(ሁኔ አቢሲኒያዊ ከፒተርቦሮው ዩ.ኬ) :-አቶ ስብሃትን ጠጋ ብለው የሚያውቁት ሰዎች “አቦይ ብላችሁ አትጥሩት። አባታዊ አንደበትና ምግባር የለውም እርሱን አቦይ ማለት ትግራይ የሽማግሌ መሀን እንደሆነች መቁጠር ነው” ይሉታል፡፡
ሰውዬው ስብሐት ነጋ የህወሓትን አመሰራረት ቅድመ ታሪክ ለሚያውቅ ሰው ምን ያህል ተንኮለኛ እና በዘር ልክፍት የተለከፈ እንደሆነ ግልጽ ይሆንለታል፡፡ በ1963 ዓ.ም እንደተመሰረተ የሚነገርለት ማገብት (ማህበር ገስገስቲ ብሔረ ትግራይ) የተመሰረተው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የትግራይ ተወላጅ ተማሪዎች ነበር፡፡ የማህበሩ ተልእኮም የተለያዩ የበጐ አድራጐት ስራዎችን በክረምት ወደ ትግራይ በመሄድ ማከናወን የሚል ነበር፡፡ በሂደት ሙሉ በሙሉ ወደ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ በመቀየር ለተሐህት/ህወሓት መመስረት መሰረት ሆነ ለዚህ ዓላማ የማስቀየር ስራ ትልቁን አስተዋፅኦ ካደረጉት መካከል ደግሞ ዛሬ ታሞ የሚማቅቀው ስብሐት ነጋ አንዱ ነው፡፡
ስብሐት ነጋ የህወሀትን መስመር እና ዓላማ መሀንዲስ ከመሆንም አልፎ እስከዛሬ ለብዙ ሰዎች ምስጢር በሆነ መልኩ መለስ ዜናዊንም ወደ ህወሀት ሊቀመንበርነት ብሎም የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስተር ያደረገ እና በህወሀት ክፍፍል ወቅትም ትልቅ ሚና ከነበራቸው ቀደምት የህወሀት ታጋዮች አንዱ ነው፡፡
ለባለፉት 23 ዓመታት የኢትዮጵያን ህዝብ ከጀርባ ሆነው ሲያንቀጠቅጥ የነበረው አይተ ስብሐት ነጋ እርሱም ተራው ደርሶ ቤልጅየም ብራሰልስ በሚገኘው ሴንት ሚካኤል ሆስፒታል Hôpital Saint Michel – (Brussels) መመላስ ከጀመረ 11 ዓመታት እንደሞላው የውስጥ አዋቂዎች ቢገልፁም የበሽታው አይነትና የሰውዬው የጤንነት ሁኔታ እስካሁን ድረስ ከቅርብ ሰዎች ውጪ ሳይወጣ ቀርቷል ሆኖም የህወሀት የውስጥ ሹኩቻን ተከትሎ ሚስጥሮ እያፈተለኩ መውጣታቸውን ቀጥለው ዛሬ ስለ ስብሀት ነጋ ጤንነት በተመለከተ ለዚህ ጽሁፍ ፀሀፊ አፈትላኪ መልዕክት ደርሷል፡፡
ከታማኝ ምንጮች የተገኙት መረጃዎች እንደሚያሳዩት ሰውዬው ማለትም ስብሐት ነጋ brainstem glioma በተባለ የካንሰር አይነት መጠቃቱን ገልፀዋል፡፡ ይህ የካንሰር አይነት በብዛት በህፃናት ላይ የሚታይ ሲሆን በአዋቂዎች ዘንድ ግን በዚህ የካንሰር ዓይነት የሚያዙ ሰዎች ቁጥር ከ100,000 አንድ እንደሆነ የሳይንስ ማስረጃዎች ያሳያሉ፡፡
Brainstem glioma ስለተባለው የካንሰር አይነት መንስዔ እስካሁን የህክምና ባለሙያዎች ምንም ያሉት ነገር ባይኖርም በካንሰሩ የተጠቃ ሰው ግን ከፍተኛ የሆነ የራስ ህመም፣ ራስን የመቆጣጠር እና የማስመለስ ችግር እንደሚያጋጥመው ያስረዳሉ፡፡
በዚህ ካንሰር ተጠቅተው ወደ ህክምና ከሄዱ ሰዎች መካከል 37% የመኖሪያ እድሜያቸው ቢበዛ ዓንድ ዓመት 20% ያህሉ ሁለት ዓመት 13% ቢበዛ ቢበዛ ከሶስት አመት በላይ በህይወት የመኖር እድላቸው አነስተኛ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ከህወሀት አፈትልኮ የወጣው መረጃ እንደሚያሳየው ስብሐት ነጋ ባለፉት 11 ዓመታት ቤልጂየም ሲመላለስ የነበረው በዚሁ የካንሰር ምክንያት እንዳልነበረ እና የዚህ አይነት የካንሰር ተጠቂ እንደሆነ የተነገረው ፌብራዋሪ 9 እለተ እሁድ ቀን እንደነበር ጨምረው ገልፀዋል፡፡
የአቶ ስብሐት ነጋን መታመም ተከትሎ በሰውዬው ላይ በየዕለቱ የተለያየ ባህሪ እንደሚመለከቱ ገልፀው በተደጋጋሚ ከተለያዩ ስብሰባዎች ላይ አቋርጠው እየሄዱ እንደሚገኙ አክለው ገልፀዋል፡፡
በጦርነቱ ዘመን የትግራይ ህዝብ እጅግ የከፋ ድርቅና ረሀብ ሲፈራረቅበት፤ ከመሀል አገር የእርዳታ እህል እንዳይደርሰው መንገድ በመዝጋት፤ እነሱ በተቆጣጠሩት አካባቢና ባልተቆጣጠሩትም አካባቢ “እኛ ነን ለህዝባችን ረድኤት ድርጅቶች የሚያቀርቡትን እርዳታ ማደል ያለብን” ብለው የተባበሩት መንግስታትን ግራ አጋብተው ለረሀብተኛው እንዲያከፋፍሉ መድሀኒትና ምግብ ይሰጣቸው የነበሩ ሲሆን ያንን በብዙ ሚሊዮን የሚገመት የእርዳታ እህልና ቁሳቁስ ከአረብ ነጋዴዎች ጋር በመመሳጠር በቀጥታ ባህር እያሻገሩ በመሸጥ፤ በኩንታሎች አሸዋ እየሞሉ ለጋሾችን በማታለል እንዲገዙአቸው በማድረግ፤ በሚሊዮን ዶላር ሲንበሸበሹ፤ የጦር መሳሪያ ሲሸምቱ፤ የትግራይ ህዝብ እንደቅጠል ይረግፍ ነበር። እነሱ በየጫካው ከሰራዊቱ እየተሸሸጉ አረቄ ጠግበው ከውሽሞቻቸው ጋር ከበሮ እየደለቁ እየጨፈሩ ይዳሩ እንደነበር ህወሀትን ጥለው የኮበለሉ የቀድሞ አባላቶች የሚገልፁ ሲሆን ለእነዚህ ሁሉ ግፍ እና በደል መፈፀም ከፍተኛ ሚና የነበራቸው እኚሁ የካንሰር ተጠቂ ነበሩ፡፡
ሞት ፍትሃዊ ነው በቅርቡ እንኳን አፈ ቀላጤ መለስ ዜናዊን ከህወሀት አለማየው አቶምሳን ከኦህዴድ ( ኦህዴድ ብዬ ስጠራው የዋሸው ይመስለኛል) የወሰደ ሲሆን አሁን አፉን ከፍቶ ከስብሐት ነጋ ደጃፍ ደርሷል ስብሀት ነጋም ሞትን ወደ ቤቱ ላለማስገባት ከአዲስ አበባ ወደ ብራሰልስ በየዕለቱ እየተመላለሰ ይገኛል ግና ሞትን ሸሽቶ እስከመቼ ሊደበቅ እስከ አንድ ወር ወይስ?
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
ጀርመን ውስጥ በሚገኙ የስደተኞች መጠለያዎች ላይ በቀኝ አክራሪዎች የሚደርሱ ጥቃቶች መባባሳቸውን የጀርመን መንግሥት አስታውቋል ። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችም የችግሩን አሳሳቢነት አጉልተው በማሳየት ላይ ናቸው ።
ጥናቶች እንደሚያመለክቱት ላለፉት ሁለት አሥርት ዓመታት ዓለም ዓቀፉ ሕብረተሰብ በተለይ ከሰሃራ በስተደቡብ ከሚገኙ ሃገራት የወባ ስርጭትን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ገንዘብ መድቧል። በዚህ አማካኝነት የተከናወኑ የተቀናጁ ጥረቶችም ለዉጥ ማሳየታቸዉ እየተነገረ ነዉ።
ባለፈው ሳምንት የተከፈተዉ በርሊን ላይ የተካሄደዉ ትልቁ የዓለም ዓቀፍ የቱሪዝም ድርጅቶች ትርኢት ለተሳታፊዎቹ ጥሩ ዉጤት አስገኝቶ መጠናቀቁን የበርሊኑ ወኪላችን በላከዉ ዘገባ ጠቅሷል።
የሶማልያ መንግሥት ጦር እና የአፍሪቃ ህብረት ሰላም አስከባሪ ወታደሮች፣ አሚሶም በደቡባዊ እና ደቡብ ማዕከላይ የሀገሪቱ ከፊል በሚገኙት የአሸባብ ተዋጊዎች አንፃር ካለፉት ሰባት ቀናት ወዲህ ሰፊ የጥቃት ዘመቻ በማካሄድ ላይ ይገኛሉ።
በአፋር ክልል የሚገኙ ጨዉ አምራቾች መንግስት የሚያስፈልገንን አዮዲን በወቅቱ ስለማያቀርብልን ምርቶቻችን በዝናብና አቧራ እየባከ ለኪሳራ እየተዳረግን ነዉ አሉ።
መላዋ ኢትዮጵያ እንደ አንድ የኮፕት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሀገረ ስብከት ትቆጠር የነበረችበት የ1600 ዓመታት የሞግዚትነት ታሪክ ከብዙ ተጋድሎና እልክ አስጨራሽ ጥረት በኋላ አክትሞ የመንበረ ፕትርክናውን ነጻነት መቀዳጀቷ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን የተበሠረበት ዘመን ነው – በዓለ ሢመተ ፓትርያርክ፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በመንበረ ተክለ ሃይማኖት የመጨረሻውን የክህነት ማዕርግ መብቷን (የኤጲስ ቆጶስነት፣ የሊቀ ኤጲስ ቆጶስነትና የፓትርያርክነት ጸጋን) ለማረጋገጥ …![]()
አፈንዲ ሙተቂ
———-
ኤርትራ ዛሬ ራሷን የቻለች ሀገር ናት፡፡ ትናንት ግን የኛው አካል ነበረች፡፡ አጼ ኃይለ ሥላሤ ብልጥ የሆኑ መስሎአቸው ለሁላችንም አስፈላጊ የነበረውን የፌዴሬሽን ፎርሙላ ሰረዙትና ህዝቡን አስቀየሙት፡፡ ደርግ ደግሞ የራሳችንን ህዝብ እንደ ባዕድ እየቆጠረ በመትረየስ አጨደው፡፡ በታንክ ደመሰሰው፡፡ በዚህም የተነሳ ወጣቱ “አደይ ኤሪቲሪያ”ን እየዘመረ ወደ ባርካና ሳህል ነጎደ፡፡ ራሱን አደራጅቶ ጀብሃና ሻዕቢያ ሆኖ መጣ፡፡ ውጤቱም 1983 ላይ ታየ፡፡
የደርግና የኃይለ ሥላሤ መንግስታት ያደረጓቸው ነገሮች ሲገርሙን በጣም ግራ የሚያጋባው ሶስተኛው መንግሥታችን መጣ፡፡ ይህ የኛ መንግሥት “የተበላሸውን ሁሉ አስተካክለን አብረን መኖር እንችላለን” ብሎ መከራከር ሲገባው ጭራሹኑ “ኤርትራ ካልተገነጠለች ኢትዮጵያ ሰላም አታገኝም” ባይ ሆኖ ተገኘ፡፡ ክፍለ ሀገሩ ወደዚያ ከሄደ በኋላም መንግሥቱ ከሚከተለው ግልጽነት የጎደለው አሰራር የተነሳ በ1990 ዓ.ል. ሺዎችን ያረገፈ ግዙፍ ጦርነት ተቀሰቀሰ፡፡ ከአንድ ምንጭ የተቀዱ ህዝቦች ተጋደሉ፡፡ እነሆ ዛሬም ድረስ ነገሩ ሳይለይለት በጨለማ ውስጥ ነው ያለነው፡፡
እኛ ግን ተስፋ አንቆርጥም! በአያያዝ ጉድለት የተለየንን ወገናችንን መመለስ እንፈልጋለን፡፡ ህዝቡ ለጊዜው ሪፈረንደም አድርጎ ነጻነቱን ማወጁን ብንደግፍለትም አንድ ቀን ተቀራርበን በጋራ ስለመስራት እንወያይ ይሆናል ብለን እናልማለን፡፡ የኛ ልጆች ደግሞ በኮንፌዴሬሽን ስለመስራት ያስቡ ይሆናል፡፡ የልጅ ልጆቻችን በፈቃደኝነት ስለመዋሃድ ያስቡ ይሆናል፡፡ በዚያን ጊዜም አሁን የምንመኘው በአንድነት ውብ የመሆን ሚስጢራችን ይመለስልናል ብለን እናልማለን፡፡ ምን ይታወቃል?
ወገኖቼ ደጉን ነው የተመኘሁት፡፡ በቅን ልቦና በርትተን ከጸለይንና ከኛ የሚጠበቀውን ካደረግን ሁሉንም የሚችለው ፈጣሪ ህልማችንን እውነት ያደርግልናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን፡፡
——-
ምን እንደጣለብኝ እንጃ! ያንን ምድር እጅግ ሲበዛ እወደዋለሁ፡፡ እኔ ለተወለድኩበትና አብዛኛውን ዘመኔን ለጨረስኩበት የምስራቅ ኢትዮጵያ ክልል ጎረቤት ከሆነችው ሶማሊያ ይልቅ በ1600 ኪ.ሜ. የምትርቀው አስመራ ናት የምትናፍቀኝ፡፡ ስለሶማሊያ የተጻፈ መጽሐፍ ማንበብ ብዙም አይማርከኝም፡፡ ስለ ኤርትራ የተጻፈ መጽሐፍ ካጋጠመኝ ግን ሳላየው አላልፍም (ይህ ግን ሶማሊያን ከመጥላት እንደማይቆጠርብኝ ተስፋ አደርጋለሁ)፡፡
ታዲያ በርካቶቻችሁም እንደኔው ትመስሉኛላችሁ፡፡ ለምሳሌ ከ1970ዎቹ ጀምሮ ሲታተም የቆየው የቤኒ አምሩን ወጣት የሚያሳየው ፖስተር ዛሬም ድረስ ከኛ ጋር ተሳስሮ ነው ያለው፡፡ አሁንም ድረስ በበርካታ ስፍራዎች ተለጥፎ አይቼዋለሁ፡፡ በፌስቡክም እርሱን እንደ ፕሮፋይል ፒክቸር የሚጠቀም ኢትዮጵያዊ ሞልቷል፡፡ በሌላ በኩል የኤርትራን ሙዚቃ የሚያዳምጡ ሰዎች በሽ ናቸው፡፡ ደራሲ መሐመድ ሳልማን መቐለ ሄዶ ያየው ነገር ቢያስገርመው “በኤርትራ ሙዚቃ የምትጨፍር ከተማ” የሚል አስደናቂ ወግ ጽፎ እውነቱን አስረድቶናል፡፡ መንግሥታት ቢጣሉ እንኳ ህዝቦች ምንጊዜም እንደሚነፋፈቁ ከዚህ በላይ የሚያስረዳ ዋቢ ያለ አይመስለኝም፡፡
——–
ማርታ ሀይሉን አስታወሳችኋት? አዎን! ማርታን “ብራ… ነው… ብራ ነው”፤ “አዘዞ”፤ “ሎጋ ..ና እናውጋ” በተሰኙት ዘፈኖቿ እናውቃታለን፡፡ ከማርታ ዘፈኖች ዘወትር ቀልቤን ይገዛ የነበረው ግን የትግርኛ ዜማዋ ነው፡፡ አዝማቹ እንዲህ ይመስለኛል፡፡
ካብ አስመራ ድንገት ርእዮ
ምጽዋ ገባሁ ልበይ ሕብዮ
እንተርጉመው እንዴ?… ግድ የለም ማርታ ራሷ እንዲህ እያለች በአማርኛ ተርጉማዋለች፡፡
“ከአስመራ ድንገት አይቼው
ምጽዋ ገባሁ ልቤን ሰጥቼው”፡፡
አዎን! ትናንት የኛ ናት ስንላት ለነበረችው ኤርትራ ነው እንዲህ የዘመርንላት፡፡ ዛሬም ብንዘምርላት እንከበራለን እንጂ አንወቀስም፡፡ ምክንያቱም በመንግሥት ደረጃ ነው የተለያየነው፡፡ ሁለት ፓስፖርት እንዲኖረን ነው የተደረግነው፡፡ ሁለታችንም ግን አንድ ህዝቦች ነን፡፡ በደምም ሆነ በባህል በጣም የተዋሃድን የአንድ መሬት ብቃዮች ነን፡፡ ሁለታችንም የተዋብን የሴምና የኩሽ ህዝቦች ውቅር ነን፡፡ እንደኛ የሚያምር ህዝብ በትኛውም ዓለም የለም፡፡ የጀበና ቡና፣ ዶሮ ወጥ፣ ድፎ ዳቦ፣ የስጋ ፍትፍት፣ አምባሻ፣ ወዘተ…. ሁለታችን ዘንድ ብቻ ነው ያለው፡፡
—–
በርግጥ እላችኋለሁ፡፡ በምንባብና በወሬ እንጂ በአካል የማላውቃት ኤርትራ ትናፍቀኛለች! ያ በታሪክ ምዕራፎች “ምድሪ ባህረ ነጋሽ” እየተባለ ሲጠራ የኖረው ጀግና መሬትና ህዝብ ይናፍቀኛል፡፡ ያ የሰሜኑ በረኛ እያልን እንመካበት የነበረው ህዝባችን ይናፍቃል፡፡
እውነትም ኤርትራ ! የዳማት ታሪክ ውቅር! የመጠራ አብያተ መንግሥታት ከርስ! የሀውልቲ ፍርስራሾች ቀብር! የአዱሊስና የዙላ ወደቦች መዘክር! የሱዋኪምና የዳህላክ ሱልጣኖች ደብር!
ኤርትራ የአብረሃ ደቦጭ ሀገር! የሞገሥ አስገዶም ሀገር! የዘርዓይ ደረስ ሀገር! የሎሬንዞ ታዕዛዝ ሀገር! የደጃች ሀረጎት ሀገር! በአይበገሬ ጀግንነታቸው ድፍን አፍሪቃን ያኮሩ አርበኞች የበቀሉበት ምድር!
ኤርትራ የበረከት መንግሥተ አብ ሀገር! የአብረሃም አፈወርቂ ሀገር! የአሕመድ ሼኽ ሀገር! የሄለን መለስ ሀገር! የየማነ ባሪያው ሀገር! የሄለን ጳውሎስ ሀገር! በስርቅርቅ ድምጻቸው የሰውን ልብ እየሰረሰሩ የመግባት ሀይል ያላቸው የጥበብ ከዋክብት የወጡበት መንደር!
ኤርትራ የፊያሜታ ጊላይ ሀገር! የስዕላይ በራኺ ሀገር! የኦቦይ ተኽሌ ሀገር! የተክላይ ዘድንግል ሀገር! የሆቴል ፓራዲዞ ሀገር! የዕቁባይ ሲላ ሀገር! የምንወደው ደራሲያችን በዓሉ ግርማ በ“ኦሮማይ” መጽሐፉ እንደ ፊልም ግልጥልጥ አድርጎ እየተረከልን ዝንተ-ዓለም እንድንወዳት ያደረገን የቀይ ኮከብ ትዝታ ወመዘክር!
ኤርትራ የፊዮሪ ሀገር! የሳባ ሀገር! የማርቲና ሀገር! የብርኽቲ ሀገር! ፊያሜታ ጊላይን የመሳሰሉ “ሽኮሪናዎች”ን ያበቀለች ውብ የውቦች እመቤት!
—–
ኤርትራን ስንጠራ በቅድሚያ ወደ አዕምሮአችን የምትመጣው አስመራ ናት፡፡ የአስመራ ናፍቆት ይገድላል፡፡ አስመሪና፣ አስመሪቲ፣ አቲ ጽብቕቲ!…
ውይ ስታምር! “ቀሽቲ” እኮ ናት፡፡ ያኔ በልጅ አዕምሮአችን በዘምባባ ጥላዋ ተሸክፋ በፖስትካርድ ስትቀርብልን “የኛ ውቢት” እያልን እንመጻደቅባት ነበር፡፡ እንቆቅልሽ ስንጫወትና መልሱ ጠፍቶን “ሀገር ስጠኝ” ስንባል እርሷን ለመስጠት እንሰስት ነበር፡፡ ጠያቂውም የዋዘ ስላልሆነ “አስመራ” ካላልነው ለጠየቀን ጥያቄ ትክክለኛውን መልስ አይነግረንም ነበር፡፡ ከማናውቃቸው “ዋሽንግተንና” ሮማ አስመራ ነበር የምትበልጥብን፡፡ በትምህርት ቤት መዝሙራችንም እንዲህ እንል ነበር፡፡
ኦኬ ኦኬ ኦኬ ስራ
ሰላም ሰላም ወደ አስመራ
አዲስ አስተማሪ ከጃፓን የመጣ
ማስተማሩን ትቶ በቦክስ የሚማታ
አናግረኝና አናግርሃለሁ
በአሜሪካ ሽጉጥ አዳፍንሃለሁ፡፡
ግጥሙ “አንታራም” የሚሉት የህጻናት ጨዋታ ዓይነት ነው፡፡ ነገር ግን አስመራ ከልባችን እንዳትጠፋ አድርጓል፡፡ ዛሬም በልባችን ነግሳለች አስመሪና!
—-
አስመሪና! እንተይ ሽኮሪና! ሰሜናይት ጽብቕቲ! በዓሉ ግርማ ላንቺ ክብር የጻፈው ትዝ ይልሻል? እስቲ እናስታውሰው!
አስመሪና አስመራዬ
ካብ ሐንቲ ንግሥቲ ይበልፅ መልክእኪ
አማአድዬ ክርእየኪ ከሎኹ ኽአ
አብ ኢደይ ዘሎ ነገር ይወድቕ፡፡
——
ጸጸራት፤ ፎርቶ፣ ሐዝሐዝ፣ አርበእተ አስመራ፣ እምባጋሊያኖ፣ ኮምቢሽታቶ፣ አዲጓእዳድ፣ ቃኘው፣ ማይተመናይ፣ ሰምበላይ፣ ጎዳይፍ፣ ገጀረት፣ ወዘተ…በጽሑፍ የማውቃቸው የአስመራ ሰፈሮች ናቸው፡፡ አንድ ቀን በሆነልኝና ባየኋቸው እያልኩ አልማሁ፡፡ እነዚህ አስገራሚ የአስመሪና ሰፈሮች ብዙ ባለታሪኮችን አብቅለዋል፡፡ ብዙዎች ገድላቸው እየተደጋገመ ሲነገርላቸው እሰማለሁ፤ አነባለሁ፡፡ ለኛ ቅርብ የነበረ አንድ ውድ ልጅ እየተረሳ በመሆኑ ግን አዝኛለሁ፡፡
አማኑኤል እያሱ ይባላል! አስታወሳችሁት አይደል? አዎን! አማኑኤል በኛ ዕድሜ ዘመን ኢትዮጵያ ዋንጫ መብላት እንደምትችል ያስመሰከረው የታላቁ የ1980 የእግር ኳስ ቡድናችን ቋሚ ተሰላፊ ነበረ፡፡ የማሊያ ቁጥሩ 2 ይመስለኛል፡፡ አማኑኤል የያኔው ቡድናችን ባደረጋቸው ሁሉም ጨዋታዎች ተሰልፏል፡፡ ቡድኑ ዋንጫውን ሲበላም ከጓደኞቹ ጋር ቤተመንግሥት ድረስ ተጋብዞ ተሸልሟል፡፡ አማኑኤልን ያስገኘው ከዚያ ዘመን ዝነኛ ቡድኖቻችን መካከል አንዱ የነበረው የኤርትራ ጫማ ቡድን ነው፡፡ ይህ ቡድን የኤርትራ አንደኛ ዲቪዚዮን ዋንጫን በተደጋጋሚ ያሸነፈ ነው፡፡
አማኑኤል እያሱ በኢትዮጵያ ትቅደም አንደኛ ደረጃ ዋንጫም ለኤርትራ ክፍለ ሀገር ምርጥ ቡድንም ተሰልፎ ተጫውቷል፡፡ ባልሳሳት የ1981 የኢትዮጵያ ዋንጫን ያሸነፈው እነ አማኑኤል የነበሩበት የኤርትራ ክፍለ ሀገር ቡድን ነው፡፡ የአማኑኤል እያሱን ወሬ ለመጨረሻ ጊዜ ያነበብኩት በ1988 ለወዳጅነት ጨዋታ አዲስ አበባ መምጣቱን በማስመልከት በርካታ የግል ጋዜጦች ቃለ-መጠይቅ ባደረጉለት ጊዜ ነው፡፡ ከዚያ ወዲህ በምን ሁኔታ ላይ እንዳለ መረጃው የለኝም፡፡ እስቲ የአስመራ ልጆች ወሬው ካላችሁ ስለአማኑኤል እያሱ አንድ ነገር በሉን፡፡
—–
ወደ ምዕራብ ኤርትራ ተሻግረናል! ባርካና ጋሽ የሚባሉት የኤርትራ ቆላዎች እዚህ ነው ያሉት፡፡ አቆርዳት፣ ተሰነይ፣ አሊጊደር፣ ባሬንቱ የተሰኙት ከተሞችም በቆላው ውስጥ ተዘርግተዋል፡፡ ኩናማ፣ ናራ እና ቤጃ የተሰኙት ብሄረሰቦች እዚህ ነው የሚኖሩት፡፡ የአካባቢው ዋነኛው ህዝብ ግን ለኛ በጣም ቅርብ ሆኖ ዓመታትን ያስቆጠረውን ሳቂታውን የቤኒ አምር ወጣት ያስገኘው የትግረ ህዝብ ነው፡፡
የትግረ ህዝብ በውስጡ በርካታ ጎሳዎች አሉት፡፡ ከሁሉም የሚበረክተው ግን የቤኒአምር ጎሳ ነው፡፡ ህዝቡ የሚነጋገርበት የትግረ ቋንቋ ከሴማዊ ቤተሰብ ነው የሚመደበው፡፡ ለዚህ ቋንቋ በጣም የሚቀርበው በደጋው ኤርትራና በኛዋ የትግራይ ክልል የሚነገረው ትግርኛ ነው፡፡ እነዚህ ሁለት ቋንቋዎች ከጥንታዊው የግዕዝ ቋንቋ ነው የተወለዱት፡፡ የትግረ ቋንቋ ከኤርትራ ሌላ በሱዳንም (ከሰላ አካባቢ) በስፋት ይነገራል፡፡
ትግረና ትግርኛ በጣም ከመመሳሰላቸው የተነሳ እንግዳ ለሆነ ሰው አንድ ዓይነት ቋንቋዎች ሊመስሉት ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም ለትግርኛ ተናጋሪዎች የትግረ ቋንቋን መልመድ በጣም ቀላል ነው ይባላል፡፡ የትግረ ተናጋሪም ትግርኛን በቶሎ መልመድ ይቀለዋል፡፡ በመሆኑም በዛሬዋ ኤርትራ ከግማሽ በላይ የሚሆነው ህዝብ ሁለቱንም ቋንቋዎች መናገር ይችላል፡፡
ምዕራባዊው ቆላ ኤርትራዊያን በጣም የሚያደንቋቸውን እንደ ሃሚድ ኢድሪስ አዋቴ፣ ሙሐመድ ኢድሪስ እና ኢድሪስ ገላውዴዎስን ያፈራ መሬት ነው፡፡ በዚህ ሰሞኑን ልቤን ያሸፈተው የትግረ ልጅ ግን “አሕመድ ሼክ” ነው፡፡ አሕመድ ሼክን አወቃችሁት አይደል? አዎን! “ባቡሬይ”፣ “ኢላ ሰርጎ” ወዘተ.. እያለ በማይጠገበው የትግረ ምት የሚያዜመው ተወዳጅ ድምጻዊ ነው፡፡ አንድ ኤርትራዊ ወዳጃችን “ኤላ ሰርጎ”ን ሲፈታልን `ከጀርባው ፌሎሶፊ አለው” ነው ያለኝ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡፡
የትግረ ሴት ለምትወደው አንድ ሰው (ለባሏ) እንጂ ለማንም ጸጉሯን አትገልጠውም፡፡ ስለዚህ ጉብሊቷን ልጅ የወደደው አሕመድ ሼክ በተዋቡ ግጥሞች እያወደሳት ዘፈነላትና ፍቅሩ ልቧ ውስጥ ዘልቆ መግባቱን ለማረጋገጥ ጸጉሯን ማየት ጀመረ፡፡ እርሷም ግጥሞቹን ከሰማችለት በኋላ ጸጉሯን ገልጣ አሳየችው፡፡ ድል አድራጊው ወዲ ሼክም ይዟት በረረ፡፡ ኤላ ሰርጎ! ኤላ ሰርጎ” እያለ ነጎደ!
——
ሰሜን ኤርትራ!
ተወዳጇ የከረን ከተማ እዚህ ነው ያለችው! የሀረርጌዋ የድሬ ዳዋ ከተማ መንትያ እህት የምትመስለው ውቢቷ የሰሜን ፈርጥ! በቪዲዮ አይቻት ውበቷን አደነቅኩላት! አበቦቹ! ቤቶቹ! መንገዶቹ ሁሉም ውብ ናቸው፡፡ ከትግራይ የተገኘው ዝነኛው ብርሃነ ሃይለ አንድ ላይ በነበርነት ዘመን ለከረኗ ጉብል እንዲህ ብሎላታል፡፡
ሸው በሊ ብለነይ ብለነይ
ዝለሊ ብለነይ ብለነይ
አሊሊ ብለነይ ብለነይ
አቲ ጓል ከረነይ ብለነይ
አዎን! ቢለን ከከረን ከተማ ጋር ስሙ የሚጠቀስ ብሄረሰብ ነው፡፡ ቋንቋው ከኛው የአገው ቋንቋ ጋር አንድ ዐይነት ነው፡፡ እንግዲህ እዚህ ላይ ነው አንባቢ ሊመራመር የሚገባው፡፡ በወሎና በጎጃም የሚኖረው አገው ምን ሊያደርግ እዚያ ሄደ?… መቼ ነው እዚያ የሄደው?… መላምት ከመዘብዘብ በስተቀር ማንም ሰው ይህንን እንቆቅልሽ በሚያመረቃ ሁኔታ ሊፈታው አልቻለም፡፡ ኤርትራና እኛ አንድ ነን የሚያሰኘኝ እንዲህ ዓይነት ተጨባጭ ማስረጃ ስላለን ነው፡፡
ቢለን ውብ ባህል ያለው ህዝብ ነው፡፡ በዚህ ህዝብ ባህል መሰረት ሴቶቹ ካገቡ በኋላ ጸጉራቸውን መሰተር ግድ ነው፡፡ ህዝቡ የቢለን ቋንቋ ተናጋሪ ቢሆንም የትግረ ቋንቋንም ይጠቀማል፡፡ ትግርኛም በስፋት ይነገራል፡፡ እጅግ ታዋቂ የሆነው የቢለን ተወላጅ “ዑመር እዛዝ” ነው፡፡ የጀብሃ ጦር ከመፍረክረኩ በፊት የሁለተኛው ዞን አዛዥ እንደነበረ ከዚህ በፊት ጽፌ ነበር፡፡
ከከረን ሽቅብ ወደ ሰሜን ስናመራ ታሪካዊቷ አፋቤት አለች፡፡ ጄኔራል ታሪኩ አይኔ የሚመራው ናደው እዝ እዚህ ነበር የሰፈረው፡፡ የቀይ ኮከብ ዘመቻ ዋና አምባም ይህ ነበር፡፡ ከአፋቤት ወደ ሰሜን ስንበር ንዳዳማውና አስቸጋሪው የሳህል መሬት አለ፡፡ በዓሉ ግርማ እንደተረከልን ከሆነ ሳህል ማለት እሳት ነው፡፡ ነገር ግን ሰዎች ይኖሩበታል፡፡ ከብቶች ይሰማሩበታል፡፡ ተክልም ይበቅልበታል፡፡ እዚህ አካባቢ በብዛት የሚኖረው ህዝብ “ረሺዳ” ይባላል (አንዳንዶች “ራሻይዳ” ይሉታል፤ ስህተት ነው፤ ትክክለኛው አጠራር “ረሺዳ” ነው)፡፡
የ“ረሺዳ” ህዝብ ከሌላው የኤርትራ ህዝብ የሚለይበት በርካታ ነገሮች አሉት፡፡ ለምሳሌ ይህ ህዝብ ከሳዑዲ ዐረቢያ ተነስቶ ወደ ኤርትራ የገባው በቅርብ ዘመን (በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ) ነው፡፡ በዚያ ወቅት የአሁኗ ሳዑዲ ዐረቢያ አልነበረችም፡፡ ሀገሩ ሁሉ በጎሳዎች የተከፋፈለ በረሃማ ምድር ነበር፡፡ ከነዚህ ጎሳዎች አንዱ አል-ረሺድ ይባላል፡፡ ይህ የአል-ረሺድ ህዝብ የአካባቢው የበላይ እንዲሆን በኦቶማን ቱርክ ተወሰነ፡፡ አብዛኛው ህዝብም ለነርሱ አደረ፡፡ “አል-ሱዑድ” የሚባለው ቤተሰብ ግን “አሻፈረኝ” አለ፡፡ “ራሴ በረሃውን ጠቅልዬ መግዛት ስችል ለምን በአል-ረሺድ ጎሳ የበላይነት አድራለሁ” በማለት አንገራገረ፡፡ በሁለቱ መካከል ጠብ ተነሳ፡፡ በመጀመሪያው ላይ የአል-ረሺድ ጎሳ አሸነፈ፡፡ አል-ሱዑዲዎች ወደ ኢራቅ ሸሹ፡፡
ከጥቂት ዓመታት በኋላ ግን የአል-ሱዑድ ቤተሰብ በእንግሊዞች ደጋፊነት ራሱን አጠናክሮ መጣ፡፡ በአል-ረሺድ ጎሳ ላይም ድልን ተቀዳጀ፡፡ በዚህም የተነሳ የዐረቢያ በረሃ ለአል-ረሺድ ጎሳ አባላት ሲኦል ሆነ፡፡ ረሺዳዎች እየተያዙ በጅምላ ታረዱ፡፡ ንብረታቸው ተዘረፈ፡፡ በፊት ይረዳቸው የነበረው የቱርኮች መንግሥት በራሱ ችግር በመወጠሩ ምንም ሊያደርግላቸው አልቻለም፡፡ በመሆኑም ከእልቂቱ ለመዳን ሲሉ ባህር እያቋረጡ ወደ አፍሪቃ ምድር ተሰደዱ፡፡ በሱዳንና በኤርትራ መኖሪያቸውን ቀለሱ፡፡
እንግዲህ ረሺዳዎች ከዘር ማጥፋት ወንጀል ለመሸሽ ወደ ኤርትራ የመጡ ተፈናቃዮች ናቸው ማለት ነው፡፡ በኤርትራ ውስጥ ንጹህ የዐረብ ዝሪያ የሚባሉት እነርሱ ናቸው፡፡ የአፍ መፍቻ ቋንቋቸውም ዐረብኛ ነው፡፡ በረሺዳ ባህል መሰረት ለአካለ መጠን የደረሰች ማንኛዋም ሴት ፊቷንም ሆነ ጸጉሯን መሸፈን ግዴታዋ ነው፡፡ በዓሉ ግርማ በኦሮማይ ውስጥ ሲተርክልን “ማንኛውም የረሺዳ ባል የሚስቱን ፊት ገልጦ የሚያይበትን ሰው አይፈልግም” በማለት የተናገረውም የባህላቸው አንድ አካል ነው፡፡
—————–
ታላላቅ ግድቦችን በመሥራት ላይ የሚገኙ ታዳጊ አገራት ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸው ተነገረ፡፡ በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረገው የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው ዘገባ መሠረት አገራቱ ለከፍተኛ ዕዳ እና ከዚያ ጋር ተዛማጅ ለሆኑ ችግሮች የሚጋለጡ መሆናቸውን ፋይናንሺያል ታይምስ ጥናቱን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ “ለሕዝባችሁ የምታስቡ ከሆነ ገንዘቡን ለሌላ ተግባር አውሉት” በማለት ምክርም ሰጥቶዋል፡፡
እኤአ ከ1934ዓም ጀምሮ በ65 አገራት የተገነቡ 245 ግድቦችን በማካተት የተደረገው በዓይነቱ ለየት ያለው አጠቃላይ ጥናት በቅርቡ እየተገነቡ ያሉትን ታላቅ ግድቦችንም ያካተተ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ካለው የግልገል ጊቤ ሦስት ግድብ ጀምሮ እስከ ብራዚሉ የአማዞን ቤሎ ሞንቴ የግድብ ፕሮጀክቶችን የሚገነቡት ታዳሽ ኃይልን አጠቃቀም ለማጎልበት እና የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ለመጨመር በሚል እንደሆነ የጠቀሰው ጥናታዊ ዘገባ ግንባታው በርካታዎችን ከመኖሪያቸው እንዲፈናቀሉ የሚያደርግና ለብዝሃ ህይወት አደጋ እንዲጋለጡ የሚያደርግ መሆኑን ጠቁሟል፡፡
እንደነዚህ ዓይነቱን የግድብ ሥራ የሚቃወሙ ቡድኖች እንደሚሉት የታላላቅ ግድቦች የኮንስትራክሽን ወጪ ሲጀመር ከታሰበው በጀት በአማካይ ከ90 በመቶ በላይ ተጨማሪ ወጪ የሚያስከትል እንዲሁም ከአስር ግድቦች ስምንቱ ከተወሰነላቸው የመጠናቀቂያ ጊዜ እንደሚያልፉ ይናገራሉ፡፡ በመሆኑን በኢትዮጵያና በብራዚል የሚገነቡት ግድቦች የፓኪስታንንና የምያንማርን (በርማ) ጨምሮ “ከፍተኛ ወጪ እንዲሁም ከመመጠናቀቂያ ጊዜያቸው በማለፍ የአገራቱን የኢኮኖሚ ገጽታ ችግር ውስጥ” እንደሚከቱ ዘገባው ያስረዳል፡፡
ጥናቱን ያቀረቡት ምሁራን እንደሚሉት ግድብ መሥራት አስፈላጊና እነርሱም በዚህ ጉዳይ ላይ ተቃዋሚ አለመሆናቸውን በአጽዕኖት ተናግረዋል፡፡ ችግሩ ያለው ታዳጊ አገራቱ ካላቸው የኢኮኖሚ ሁኔታ አኳያ በእንደዚህ ዓይነት የታላላቅ ግድብ ሥራ ላይ መጠመዳቸው ወደፊት ግድቦቹ በሥራ ላይ ሲውሉ ከሚጠይቁት ከፍተኛ ወጪና አገራቱ ግድቦቹን ለማንቀሳቀስ ከሚጠፈለግባቸው ከፍተኛ የፋይናንስ ጥያቄና ብቃት ማነስ አኳያ ሁኔታው እጅግ አሳሳቢ መሆኑን በመዘርዘር አስረድተዋል፡፡ “በመሆኑም” ይላሉ ከምሁራኖቹ አንዱ “በመሆኑም ይህንን ሁሉ ሁኔታ አንድ ላይ ስንወስደው ግድቦቹን መገንባት ስሜት የሚሰጥ አይደለም፡፡”
እንዲህ ያለው መረጃና ማስጠንቀቂያ ይፋ ቢሆንም የግድቦቹን መሠራት የሚደግፉ ወገኖች ቀድሞ የተሠሩ ስህተቶች እንዳይደገሙ አድርገን ነው የምንገነባው በማለት ለሚቀርበው ማስረጃ መከላከያ ይሰጣሉ፡፡ ሆኖም የኦክስፎር ዩኒቨርሲቲ ዘገባ የበርካታ ዓመታት መረጃ በመውሰድ ያወጣው ዘገባ ላይ እንዳመለከተው የግድቦቹን ሥራ ለማጠናቀቅ፣ ከተሰሩም በኋላ ለጥገናና ግድቦቹ በሥራ ላይ እንዲቆዩ ለማካሄድ የሚወጣው ወጪ ባለፉት በርካታ ዓመታት እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ እንዳልመጣ ያስረዳል፡፡ በጥናቱ ላይ የተሳተፉ ሌላው ምሁር ሲናገሩ “እነዚህ ኢኮኖሚያችን እያደገ ነው የሚሉ አገራት በእርግጥ ለዜጎቻቸው ዋስትና ግድ የሚላቸው ከሆነ ገንዘባቸውን ከታላላቅ ግድብ ሥራ ይልቅ በሌላ (ሰብዓዊ) ተግባር ላይ ቢያውሉት ይሻላል” ብለዋል፡፡
ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት የኦሞ ወንዝን ተከትሎ በሚገነባው ግድብ ላይ ስለተፈናቀሉት ዜጎች በቅርቡ ባወጣው በሳተላይት ፎቶ በተደገፈ ማስረጃ መሠረት በኢትዮጵያና በኬኒያ የኦሞን ወንዝ ተከትለው የሚኖሩ እስከ ግማሽ ሚሊዮን የሚደርሱ የአካባቢው ነዋሪዎች በግድቡ ሥራ ምክንያት የመኖር ኅልውናቸው ያከተመ መሆኑን ዘግቦ ነበር፡፡ ሰሞኑን የኢህአዴግ ባለሥልጣናት (ከግብርና ሚ/ር) በኢህአዴግ ፓርላማ ሲጠየቁ በሰጡት ቃል አንዳችም የተፈናቀለ ሰው የለም በማለት የመለሱ ሲሆን በተደጋጋሚ ማስረጃ ተደግፎ የሚወጣውን መረጃ አጣጥለውታል፡፡
(ፎቶ: AP)
goolgul
ዘወትር ቅዳሜ ማታ ከደሳለኝ መኮንን ጋር፣ምርጥና አዳዲስ የካንትሪ ማለትም የአሜሪካ አገር ሰብእ፣ የሮክ፣ተሶል፣የፖፕ፣የአር-ኤን-ቢ፣ብሉዝ፣የሬጌና የሂፕ-ሃፕ ዜማዎችን እንዲያደምጡ ተጋብዘዋል።
የትላንት በስቲያውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን መታሰቢያ ተንተርሶ በተሠናዳው ታላቁ ሩጫ “ሃሳባቸውን ለመግለጥ” የወጡ ያላቸው አባሎቹ ለእስር ተዳረጉ ሲል፤ ሰማያዊ ፓርቲ ወነጀለ።
ይበልጡን የፓርቲው አባልና የአመራር አባል የሆኑ ወጣት ሴቶች የሚገኙባቸው በርካቶች አሁንም በእስር ላይ እንደሚገኙ ነው፤ ሰማያዊ ፓርቲ ያስታወቀው።
በእንቅስቃሴው በመሳተፋቸው ብቻ የደምብ ልብስ በለበሱ ፖሊሶችና እንዲሁም የሲቪል ልብስ በለበሱ የደህንነት ሠራተኞች ለአጭር ጊዜ ተይዘው ከቆዩ በኋላ፥“ሁከትና ሽብር እያነሳሳችሁ፤” የሚል ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው መለቀቃቸውን የፓርቲው የሴቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ ወ/ሪት ኢየሩሳሌም ተሥፋው።
በኢትዮጵያ የአዉሮፓ ሕብረት ልኡካን ቡድን መሪ አምባሳደር ቻንታል ሔበሬሽ፣ በአዉሮፓ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ እና የሕንድ ዉቂያኖስ አካባቢ ዴስክ ኦፌሴር ቪክቶሪያ ጋርሲያ ጉሌን እንዲሁም ቶማስ ሁይገባርቴስ የተሰኙ ፣ የአዉሮፓ ሕብረት ሃላፊ ፣ በነርሱ አነሳሽነት፣ ከአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር ሰፊ ዉይይት አደረጉ። ከአንድ ሳምንት በፊት በኢትዮጵያ ስላለው የዲሞክራሲ ግንባታ ዙሪያ ከጠ/ሚኒስተር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር እንደተነጋገሩ […]
መግቢያ ይህ ጽሑፍ በኢትዮጵያ ላለፉት አስርት አመታት ጎሣና ኃይማኖትን መሰረት አድርገው በተደጋጋሚ ጊዜያት በተከሰቱት ግጭቶች ዙሪያ እና ግጭቶቹ ባስከተሉት ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት ላይ የሚያተኩር ነው። በተለይም ከ1983 ዓ.ም. ወዲህ ጎሣን መሰረት ያደረገውን የኢሕአዴግ ፌዴራላዊ የመንግስት አወቃቀር ተከትሎ በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ውስጥ የተከሰቱ ዋና ዋና ግጭቶችን ይዳስሣል። ለግጭቶቹ መንስዔ ተደርገው የሚጠቀሱትን ጉዳዮች፣ በግጭቶቹ ሳቢያ በሰው ሕይወትና […]
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
ያቺ ትንሽ ግን ሥልታዊ ምድር ሐያል ዓለም ለጦርነት እንዳሰለፈች ሁሉ-ሐያላንን ለሠላም ሰብስባም ነበር።የሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት አሸናፊዎች የሶቬት ሕብረቱ መሪ ጆሴፍ ስታሊን፥የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳት ፍራክሊን ሩዘቬልት እና የብሪታንያዉ ጠቅላይ ሚንስትር ዊንስተን ቸርችር ዓለም የሸነሸኑት-ክሬሚያ ላይ ነበር
ትናንት ምሽትም 45 አፍሪቃውያን ስደተኞች በየመን የባህር ዳርቻ መስጠማቸውን የሃገሪቱ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል ። የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ድረ ገፅ እንዳስነበበው በባህር ዳርቻዋ ከተማ በቢር አሊ ከተማ ከደረሰው ከዚሁ አደጋ 30 ሰዎችን በህይወት ማትረፍ ተችሏል ።
ከአደጋው በኋላ ህዝብና ፖሊስ መጋጨታቸውን በግርግሩም ሶስት ሰዎች በጥይት መቁሰላቸውን የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር ዘግቧል ።