አገርን የሚመሩና የሚያስተዳድሩ ሰዎች የሚወስኗቸው ዉሳኔዎች፣ አገርን በማልማትም ሆነ በማጥፋት ረገድ ትልቅ አስተዋጾ አላቸው። ብዙዎች በአፋቸው «ፖለቲካን አንፈልግም። ፖለቲካ ውስጥ የለንበትም» ቢሉም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ግን፣ የፖለቲካዉ አካል ናቸው። ፖለቲካዉ የማይነካዉ ማንም ዜጋ የለም። የፖለቲካ ስልጣን የያዙ በሙስና ከተጨማለቁ፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንደ ዜጋ ሊያገኝ የሚገባዉን አገልግሎት በሚገባ አያገኝም። ፖለቲካዉ ዜጎችን በዘር ከፋፍሎ ፣ «የዚህ […]

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሥነ-ህዝብ ጠበብት ጥናታዊ ትንበያ እንደሚጠቁመው ከሆነ ፣ ምድራችን፣ እ ጎ አ እስከ 2100 ዓ መተ ምኅረት፤ 11 ቢሊዮን ያህል ዜጎችን ማስተናገድ ግድ ሳይሆንባት አይቀርም። አሁን የዓለም ህዝብ ቁጥር 7 ቢሊዮን ነው።

ትምህርት ቤቶች ለረዥም ጊዜ የሚዘጉበት የሰሜኑ ንፍቀ ክበብ የበጋ ወራት በርካታ የጀርመንና የእስራኤል ወጣቶች የልምድ ልውውጥ መርኀ ግብር የሚያካሂዱበት ወቅት ነው ። ካለፉት 50 ዓመታት ወዲህ ጀርመናውያን ወጣት በጎ ፈቃደኞች በእስራኤል ማህበራዊ አግልግሎቶችን በመስጠት ላይ ናቸው

አሁን ሶስተኛው ትውልድ ላይ መድረሱ እየተነገረ ነው፤ አልቃይዳ። የመጀመሪያው ትውልድ በጎርጎሮሳዊው አቆጣጠር ከመስከረሙ የ2001 ዓም ጥቃት በፊት የነበረውን እንቅስቃሴ ይጠቀልላል። ሁለተኛው ትውልድ ደግሞ የአልቃይዳው ዋና ሰው ቢን ላደን እስከተገደለበት ጊዜ ድረስ የነበሩትን ሁነቶች ያካትታልል። ሶስተኛው ትውልድ የቢን ላደን መገደልና የአረብ

አገርን የሚመሩና የሚያስተዳድሩ ሰዎች የሚወስኗቸው ዉሳኔዎች፣ አገርን በማልማትም ሆነ በማጥፋት ረገድ ትልቅ አስተዋጾ አላቸው። ብዙዎች በአፋቸው «ፖለቲካን አንፈልግም። ፖለቲካ ውስጥ የለንበትም» ቢሉም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ግን፣ የፖለቲካዉ አካል ናቸው። ፖለቲካዉ የማይነካዉ ማንም ዜጋ የለም። የፖለቲካ ስልጣን የያዙ በሙስና ከተጨማለቁ፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንደ ዜጋ ሊያገኝ የሚገባዉን አገልግሎት በሚገባ አያገኝም። ፖለቲካዉ ዜጎችን በዘር ከፋፍሎ ፣ «የዚህ […]

ዩኤስ አሜሪካ እና አፍሪቃ፣ «አፍሪካን ግሮውትስ ኤንድ ኦፖርቹኒቲ አክት» በምሕፃሩ «አ ጎ አ» በሚል ውል ባነቃቁት የንግድና የኤኮኖሚ ትብብር ዛሬ በአዲስ አበባ ምክክር ማካሄድ ጀመሩ።

አንባገነኖች ስልጣን ላይ የሚቆዩበት ጊዜ እየረዘመ በሄደ ቁጥር አሰራራቸውን እየገመገሙና ራሳቸውን እያረሙ፤ ስልጣን ላይ ለመዝለቅ ያበቋቸውን ስልቶች የበለጠ ማጠናክራቸው እንዳለ ሆኖ፤ ቆይታቸው አዳዲስ ስልቶችን ለመፍጠርና ለመሞከርም እድል ይሰጣቸዋል ። ለምሳሌ መለስ ዜናዊ አባይን እንገነባለን ብሎ ድንገት እየተጯጯኽ ህዝብን ማሯሯጥ እንደጀመረው አይነት። ይህ አባይን የመሰለ ብሄራዊ ጉዳይ ባልታሰብ ሁኔታና ጊዜ ድንገት ያነሳው ቡድን፤ ኢትዮጵያን እንደሀገር ሊያቆዩአት […]

የሀገርን ክብር ከፍ የሚያደርጉ፣ ጽናትንና ብርታትን የሚሰብኩ፣ አልበገር ባይነትንና ተጋድሎን የሚያውጁ፣ ለዓላማ ቁርጠኝነትንና ትጋትን የሚናኙ የተባረኩ እግሮች፡፡ ምን ነበር ይሆን የምታስቢው እንዲያ ተከበሽ ስትሮጭ፣ ምን ነበር ይሆን የምታልሚው እንዲያ ሀገርሽ አንድ ወርቅ እንኳን አጥታ ስሟ ከሠንጠረዡ ሲጠፋ፤ ምን ነበር ይሆን የምታስቢው የእነ አበበና የነ ማሞ፣ የነ ምሩጽና የነኃሌሌ፣ የነ ቀነኒሳና የነ ገዛኸኝ ታሪክ ወደ ተረትነት ሲለወጥ፤ ተንታኙ ሁሉ እንዲህ ነበሩኮ የሚለንን ስትሰሚ ምን ነበር ይሆን የምታስቢው፡፡

የሮጥሽውን እንጂ ያሰብሽውን አላየነውም፡፡ ያደረግሽውን እንጂ የወሰንሽውን አልተመለከትነውም፡፡ ወደየት ነበር የሮጥሽው? ምን ነበር ከፊት የሚታይሽ? አበበ ነው ወይስ ኃይሌ? ባንዲራሽ ነው ወይስ ሕዝብሽ? መቼም ምንመ ሳታይ እንዲያ አልተፈተለክሽም፡፡ ምንስ ነበር የምትሰሚው? መቼም የሞስኮን ሕዝብ ጩኸት አይደለም፡፡ በማያውቁት ቋንቋ የሚነገር ጩኸት ምች እንዲያ ያስሮጣልና፡፡ ሂጂ፣ ሂጂ፣ ሂጂ ጥሩነሽ ሩጭ፤ ታሪክ ተረት ሆኖ እንዳይቀር ለሀገርሽ ወርቁን አምጭ› ‹ሂጅ አብረንኅ እየሮጥን ነው፣ ብቻሽን ከቶ አይደለሽም፤ ምሩጽ ቀድሞ ሰባብሮታል፣ ይህ አየር ለኛ አዲስ አይደለም› የሚለው የሕዝብሽ ድምጽ ነበር በሹክሹክታ የተማሽው? አርምሞኮ ቋንቋ ነው በውስጥ ከነፍስ ጋር የሚያወሩት፡፡

እነዚያ እግሮችሽ እንደ ሲላ ሲወረወሩ፣ እንደ ንሥር ሲበርሩ፣ እንደ አቦ ሸማኔ ሲፈተለኩ፣ እንደ ሚግ ሲምዘገዘጉ፣ እጆችሽ እንደ መልአክ ክንፍ አየሩን ሲሰነጥቁ፣ ደረትሽ እንደ ሚሳይል እየከፈለው ሲተኮስ፤ እንደታቀፈች ሰጎን ዓይኖችሽ ምድር ምድር ሲያዩ፣ ከአየር ጋር ስትሟገች፣ ከድል ጋር ስትጠራሪ፣ ከእልክ ጋር ተወራርደሽ፣ ከእምቢ ጋር አብረሽ ስትሮጭ፤ ልብና እግሮችሽ ተስማምተው እየተማከሩ ሲነጉዱ፤ ዓይንና እጆችሽ ተፋቅረው የርቀት መጠን ሲለኩ፤ እንደ ንብ አውራ ታጅበሽ፣ እንደ ንብ ንግሥት ስትከንፊ፤ ምነ ነበር ያኔ የምታስቢው?

ሀገር ነበረች ከኋላሽ፣ ሀገር ነበረች ከፊትሽ፤ እንዳንች ማልያ አጥልቀን፣ እንዳንቺ ሞስኮ ባንጓዝ፤ እንዳንቺ ሀገር ወክለን እንዳንቺ በመም ላይ ባንከፍ፤ ልባችን ካንች ጋር ነበር፣ ሁሉንም ዙር አብሮ ዞሯል፤ ኅሊናችንም ካንቺ ጋር ለአምላክ ሥዕለቱን አቅርቧል፡፡ እንዴት ደስ ይላል መሰለሽ አገር አስከትሎ መሮጥ፤ እያባረርሽን አልነበረም፣ እየተከተልንሽ እንጂ፣ በእጅሽ መሣሪያ አልያዝሽም፤ ውርደትን ቀዘፍሽው እንጂ፡፡ ሀገርን ሊያኮራ የሚሮጥ፣ ድሮም ሕዝብ አብሮት ይሮጣል፣ እግሮቹ ብሩካን ናቸው ብሎ ከጥንቱ መርቆታል፡፡ በሞስኮ አፈር ላይ አይደለም በብሩካን እግሮችሽ የሮጥሽው፣ በሚወድሽና በሚሳሳልሽ ሕዝብ በልቡናቸው ውስጥ ነው፡፡


አብረንሽ ባንሮጥ ኑሮ ድል ስታደርጊ ለምን አብሮ ደስ አለን? ድል አደረግን ሲሉንኮ አብረናቸው ያልተደሰትን ብዙዎች አሉ፡፡ ድሉ የራሳቸው ብቻ የሆነ፤ ብቻቸውን ያሸነፉ፤ ድላቸውን ያልገዛንላቸው፡፡ አንዳንዶች ወርቅ ከሀገራቸው ሲያወጡ አንቺ ግን ወርቅ ወደ ሀገርሽ አመጣሽ፤ ስለዚህ አብረንሽ ሮጥን፡፡ አብረንሽም ስለሮጥን አብረንሽ ተደሰትን፡፡ ሞስኮ ላይ ያዩሽ ሁሉ፤ ምሩጽ አልሞተም አሉ፡፡ አረንጓዴው ጎርፍ ቢደርቅም አረንጓዴ ወርቅ አላቸው አሉ፡፡ ሁሉንም የሚግባባ ሃሳብና ፕሮግራም፣ አስተዳደርና አመራር፣ አካሄድና መዋቅር በጠፋበት ጊዜ ምሥራቅ ከምዕራብ ሰሜን ከደቡብ አስተባብረሻልና የመግባቢያ ሰነዳችን ሆነሻል፡፡ በየጎራው የቆሙትን፣ በየተቃራኒው የተሰለፉትን ሁሉንም ሞስኮ አምጥተሸ አንድ አድርገሻቸዋልና የአንድነት ዓርማ ሆነሻል፡፡ 

ማጭበርበር በሌለው ምርጫ ተመርጠሻል፤ የምረጡኝ ዘመቻ ሳያስፈልግሽ በተግባር ሕዝብ አሰልፈሻል፤ ዙፋን ሳያስፈልገሽ ነግሠሽ፣ ሉል ሳያስፈልግሽ ገዝተሻል፡፡ ስም ወደ ግብር ይመራልና ጥሩነሽ ጀግና ሆነሻል፡፡

እግሮችሽን አበርትቶ፣ ጣቶችሽን ያለምልማቸው፣ ኅሊናሽን አንቅቶ፣ ለዓይኖችሽ ብርሃን ይጨምርላቸው፤ የልብሽን ምት ጠብቆ እጆችሽን አክናፍ ያርጋቸው፤ ሳትደክሚ ምትክሽን፣ ሳታርፊ ደቀ መዝሙርሽን ያሳይሽ፡፡ ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡ 

የግጭት አፈታት ​​
የግጭት አፈታት
በአንድ ቡድን ወይም በግለሰቦች መካከል የሚፈጠር ግጭት ቋሚ መፍትሔ የሚያገኘው በድርድርና በውይይት አንዱ የሌላውን ጥያቄ ግንዛቤው ውስጥ ሲጨምር መሆኑን የግጭት አፈታት ስልት ምሁሩ አቶ ሰለሞን ጥላሁን ገልፀዋል። የግጭት አፈታት ​​​​ አቶ ሰለሞን ከትዝታ በላቸው ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ግጭት ተወልዶ እስከሚሞት እንዲባባስ ስለሚያደርጉትና ስለሚያረግቡት፣ እንዲሁም የማጥፊያው መንገዶች በሰፊው ተንትነዋል፡፡

ባለሙያው በማብራሪያቸው በአንድ ርዕሰ ጉዳይ ላይ የሚኖሩ ተመጣጣኝ ያልሆኑ ግቦች ወደ መግባባትና ወደ ግጭት ሊያደርሱ እንደሚችሉም አመልክተዋል፡፡
የግጭት አፈታት ​​
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

በማደግ ላይ የሚገኙ ሃገሮች ከተለያዩ መንግስታትና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት የልማት ርዳታ ያገኛሉ። ኢትዮጵያ አፍሪቃ ዉስጥ ከፍተኛ የልማት ርዳታ ከሚያገኙ ሃገር ግንባር ቀደሟ ናት

በምደባ ቅር የተሰኙ ሓላፊዎች በየሆቴሉና ሬስቶራንቱ የዐመፅ ምክክር ይዘዋል ‹‹የቋሚ ሲኖዶሱ ምደባ በአተገባበር በደላሎች ተጠልፏል›› የሚል ቅሬታ አላቸው የረዳት ሊቀ ጳጳሱና ጽ/ቤታቸው ድርሻ የቋሚ ሲኖዶሱን ምደባ ማስፈጸም ብቻ ነው በዘላቂው የሀ/ስብከቱ መዋቅር ስፍራ የሚኖራቸው በጊዜያዊ ምደባቸው ብቃት ያሳዩ ሓላፊዎችና ሠራተኞች መኾናቸው ተገልጧል የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ በሚያደርገው ቅድመ ዝግጅት ለዘረጋው የሽግግር ጊዜ መዋቅር …

አንድነት በመብራት ሃይል አዳራሽ በአጭር ጊዜ የጠራው ስብሰባ በድምቀት እና በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ ታውቋል፡፡ በመብራት ሐይል በተካሄደው በዚሁ ስብሰባ ላይ የፓርቲው አመራር አባሎች እና ከአንድ ሺህ አምስት መቶ በላይ የሚሆን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን፤ በተለይ ዛሬ ለስብሰባው ቅስቀሳ ሲያደርጉ በህገወጥ መንገድ የታሰሩት የአንድነት ፓርቲ አባላት ተለቀው ወደስብሰባ አዳራሹ በማመራት ስበሰባውን መሳተፍ ችለዋል፡፡ ከነሱ መሀል […]

በማሊ ዛሬ 11.08.2013 ፪ኛ ዙር ፕሬዚደንታዊ ምርጫ እየተካሄደ ይገኛል።
በምርጫው የሚወዳደሩት የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ኢብራሂም ቡባከር ኬይታ እና የቀድሞው የገንዘብ ሚንስትር ሱማይላ ሲሴ ናቸው።

በናይጀሪያ የምክር ቤት እንደራሴዎች ለአካለ መጠን ያለደረሱ ሕፃናት ሴቶች ሊዳሩ ይቸላሉ የሚለውን ሕግ ወደፊትም ሊሰራበት ይችላል ካሉ በኋላ በሀገሪቱ ሰፊ ክርክር ተነስቶዋል። ሰሞኑንም በኤኮኖሚ መናኸሪያ በሆነችው በሌጎስ ከተማ አደባባይ በመውጣት «ለአካለ መጠን ያልደረሱ ሕፃናት እንጂ ለሙሽራነት አልደረሱም » የሚል መፈክር አሰምተዋል።

አንድነት ፓርቲ ነገ ነሃሴ 5, 2005 ዓ.ም ሜክሲኮ በሚገኘው የመብራት ሃይል አዳራሽ ለሚያደርገው ህዝባዊ ስብሰባ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ 12 የፓርቲው አባላትና ሁለት መኪኖች መስቀል አደባባይና ሳሪስ አካባቢ ህገወጥ እስር ተፈፅሞባቸዋል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችም አባሎቹ ወደ ታሰሩባቸው ፖሊስ ጣቢያዎች አምርተዋል፡፡ ቀደም ሲል አዲሱ ገበያ አካባቢ 3 አባላት ተይዘው የነበረ ሲሆን እስከ አሁኗ ሰአት ድረስም 15 […]

አንድነት ፓርቲ ነገ በመብራት ሃይል ለሚያደርገው ህዝባዊ ስብሰባ ባልቀ ከመንግስት የአዳራሽ ፍቃድ ዛሬ ከቀኑ 6 ሰዓት ቢሰጥም ገና የመከና ላይ ቅስቀሳ በጀመሩ በፖሊሶች ክልከላ ማድረግ ጀምረዋል፡፡ በአዲሱ ገበያ አካባቢ ሲቀሰቅስ የነበረው መኪና ላይ የነበሩት ሶስት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አባላት ማዕከላዊ (3ኛ ፖሊስ ጣቢያ) ታስረዋል፡፡ የታሰሩት አባላት ሰፊው መኮንን፣ አቶ ኃይሉ ግዛው እና ወርቁ ፡፡ […]

  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

አረም ማለት ያልተዘራበት የሚበቅል ገበሬ የዘራውን ሰብል የሚሻማ፣ ውሀውን የሚጠጣበት፣ ለበሽታና ተባይ መጠለያ በመሆን ለሰብል ጉዳት ምክንያት የሚሆን እጽዋት ማለት ነው። አረም በስሮቹ አማካይነት የሰብሉን ስር አንቆ የሚገድል፣ አንዳንዱም እንደ ፓራሳይት ሰብል ላይ ተጣብቆ የሚበቅል እንደ አቀንጭራ ያለ ማለት ነው። አረሞች በፈጣን አስተዳደጋቸው ሳቢያ አልሚ ንጥረ ነገሮችን ከመሬት የፀሀይ ብርሃን ከሰማይ በመሻማት የሚያቀጭጩና የሚገድሉ ናቸው። […]

ነሃሴ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለኢሳት የሚደርሱ መረጃዎች እንዳመለከቱት በ ኢድ አል ፈጥር እለት የፌደራል ፖሊሶች በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ የወሰዱትን እርምጃ ተከትሎ ሌሊቱንና ዛሬም በርካታ ሙስሊሞች ከቤታቸው እየተወሰዱ ታስረዋል። በአሁኑ ጊዜ በትክክል የታሰረውን ህዝብ ቁጥር ለማወቅ ባይቻልም   በሺዎች እንደሚቆጠር ይገልጻሉ። በዛሬው እለትም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከእስር ተፈተዋል።  ድምጻችን ይሰማ …

ነሃሴ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የጦር አውሮፕላኑ የተከሰከሰው በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዲሾ አለማቀፍ አየር ማረፊያ ላይ ነው። ሶቭየት ሰራሹ አንቶኖቭ አውሮፕላን መሬት ላይ እንደወደቀ በእሳት ጋይቶ 4 ቱን አብራሪዎች ገድሎአዋቸል። አውሮፕላኑ በአየር ላይ እያለ ችግር አጋጥሞት እንደነበር ዘገባዎች ያመለክታሉ። ከሳምንት በፊት አንድ የመከላከያ ንብረት የሆነ ሄሊኮፕተር ወድቆ መከስከሱ ይታወቃል።

ነሃሴ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ በወረዳው የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ በትናንትናው እለት አልፋ እየተባለ ወደ ሚጠራው ቀበሌ ያመሩ የፖሊስ አባላትና ካድሬዎች ምሽቱን መደብደባቸውን የተመለከተ መረጃ የደረሰው ፌደራል ፖሊስ ዛሬ ከፍተኛ ቁጥር አላቸው የፌደራል ፖሊስ አባላትን ወደ አካባቢው ልኳል። በዛሬው እለት በዙሁ ቀበሌ ያለው ውጥረት የጨመረ ሲሆን፣ በካድሬዎቹ እና በፖሊሶች ላይ ጥቃት ፈጽመዋል የተባሉ ሰዎችም …

ነሃሴ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከኮሪያ ዘማች ቤተሰቦች ተውጣጥው ወደ ደቡብ ኮሪያ ለትምህርት ከተላኩት 59 ኢትዮጵያውያን መካከል 38ቱ ጥገኝነት ጠይቀዋል። ኢትዮጵያውያኑ ለ8 ወራት የተሰጣቸውን ስልጠና ሊያጠናቅቁ የቀናት እድሜ ሲቀራቸው ነው ጥገኝነቱን የጠየቁት። በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ መበላሸት፣ ወጣቱ በአገሩ የሚሰራበት ሁኔታ ሊመቻች ባለመቻሉ ጥገኝነት ለመጠየቅ እንደተገደዱ ወጣት ሲሳይ ወልደገብረኤል ለኢሳት ገልጿል።

የዩጋንዳ የተቃውሞው ወገን የአገሪቱ ፓርላማ ፤ የህዝብን የመሰብሰብ መብት የሚያርቅ አዲስ ህግ ፣ ከትናንት በስቲያ ማጽደቁን አስመልክቶ ፣ ዓለም አቀፉ ማሕበረ-ሰብ ጣልቃ ይገባ ዘንድ ተማጽኖ ለማቅረብ መዘጋጀቱ ተነገረ። በአዲሱ ህግ መሠረት፤ ማንኛውንም

ከአንድ አመት በፊት ነበር «ጋንግናም ስታይል» በገበያ ላይ የዋለው።ደቡብ ኮሪያዊው አቀንቃኝ ፕሳይ በዚህ አዝናኝ የዳንስ ቪዲዮ በአለም አቀፍ እውቅናን አገኘ። ቢንያም ዳና ደግሞ «የኛ እስታይል» ሲል ተጫውቶታል።

ሙስሊም ወገኖቻችንን መግደል፣ ማሰርና መደብደብ ሕገ-ወጥነት እንጅ መፍትሔ አይደለም!! ፓርቲያችን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ሁለት ዓመት ለመሙላት ጥቂት ወራት የቀረውን የሙስሊም ወገኖቻችንን ሠላማዊ የመብት ጥያቄ እንዲያከብር፣ መንግሥት በእምነት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን እንዲያቆምና ያነሷቸውን ጥያቄዎች በአስተውሎት በማየት እንዲሁም ወደ ውይይት በመምጣት ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መንገድ ምላሽ እንዲሰጥ ሲያሳስብ መቆየቱ የሚታወስ ነው፡፡ የመንግስት ሚዲያዎችና አንዳንድ የገዢው […]

 

ሉሉ ደበደ (ደራሲና ጋዜጠኛ)


አንባ ገነኖች ስልጣን ላይ የሚቆዩበት ጊዜ እየረዘመ በሄደ ቁጥር አሰራራቸውንእየገመገሙናራሳቸውንእያረሙ፤ስልጣን ላይ ለመዝለቅ ያበቋቸውን ስልቶች የበለጠ ማጠናክራቸው እንዳለ ሆኖ፤ ቆይታቸው አዳዲስ ስልቶችን ለመፍጠርና ለመሞከርእድል ይሰጣቸዋል ለምሳሌ መለስ ዜናዊ አባይን እንገነባለን  ብሎ ድንገት  እየተጯጯኽ  ህዝብን ማሯሯጥ እንደጀመረው አይነት።

ሙሉውን አስነብበኝ …

(ተመስገንደሳለኝ)

…‹‹የጣር ቀጠሮው ስንት ነው
ለሰው ልጅ ሰው ለምንለው
ላይችል ሰጥቶት ለሚያስችለው
ስንት ቀን ነው? ስንት ሌት ነው?…››
(ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን ‹‹እሳት ወይ አበባ›› የግጥም መድብል)
እነሆም ለቅስቀሳ ሳይሆን፣ አንተንም እራሴንም እወቅስ ዘንድ ብዕሬን እንዲህ አነሳሁ፡- ‹‹ ገሬ መከታዬ፣ መኩሪያዬ…›› ከምትላት እናት ኢትዮጵያ ምንድር ነው የምትፈልገው? …ዳቦ፣ ማህበራዊ ፍትህ፣ ፖለቲካዊ ነፃነት፣ ቤት መስራት፣ መማር-አለመማር፣ መደገፍ-መቃወም፣ መተኛት-መነሳት፣ ፈጣሪን ማምለክ-መካድ፣ መስራት-አለመስራት፣ መምረጥ-አለመምረጥ፣ አደባባይ መዋል፣ ሰፈር መዋል፣ መደራ ት-አለመደራ ት፣ ማልቀስ-መሳቅ፣ መፃፍ፣ መናገር፣ መጮኽ-መመሰጥ፣ የግል መብት፣ የቡድን መብት?
ይህ ይሆን ዘንድ ከወዴት ትሻለህ? …ከሙት መንፈስ፣ ከውርሱ ድንዛዜ፣ ከሰማይ፣ ከምድር፣ ከፀሐይ፣ ከጨረቃ፣ ከርዕዮተ-ዓለም ወይስ….?

ሙሉውን አስነብበኝ …

 በክንፉአሰፋ

 “የአሲምባ ፍቅር” – መጽሃፍ ቅኝት
በክንፉ አሰፋ
ደራሲ፣ ካሕሳይ አብርሃ ብስራት
ብዛት፣ 446 ገጾች
በተስፋዬ ወልደዮሃንስ አዲስ አበባ ታትሞ የተሰራጨ
* ከስር በስእሉ እንደሚታየው ኢሲምባ 3250 ሜትር ከፍታ ላይ በትግራይ ውስጥ ያለ ተራራ ነው። አሲምባ በዚህ ከፍታው ሳቢያ ሌሊት ላይ በጉም ይሸፈናል። አሲምባ “ቀይ አንባ” ማለት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

አውሮፕላኑ ወደ ምድር ዝቅ እያለ መሆኑን አስተናጋጇ በመናገር ላይ ናት፡፡ የምናርፈው ባንዳር ሰሪ ባጋዋን የሚባለው የብሩናይ ዓለም ዐቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ነው፡፡ ብሩናይ እስከ ዛሬ ስሟን እንኳን ሰምቻት የማላውቅ ትንሽ የደቡብ እስያ (ኦሺንያ) ሀገር ናት፡፡ ወደ እርሷ ለመድረስ ከዱባይ ተነሥተን የ8 …

ጉዞ ወደ ምድር ጥግ (ሦስተኛ ክፍል) Read more »

  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

ነሃሴ ፪(አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ዘጋቢ ከጥቁር አንበሳ እንደገለጸው በዛሬው ድብደባ ሁለት ሰዎች ሞተዋል፣ በሺዎች የሚቆጠሩት ተደብድበዋል፣  እየታፈሱም ወደ ተለያዩ እስር ቤቶች ተግዘዋል። ኢሳት በራሱ ዘጋቢዎች ባያረጋገጥም፣ ያነጋራቸው ሰዎች አንድ ነፍሰጡርና አንድ ታዳጊ ልጅ መሞታቸውን ጠቁመዋል።  

ነሃሴ ፪(አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አካባቢው በከፍተኛ አስለቃሽ ጭስ ታፍኖ አርፍዷዋል፡፡በርካታ ሰዎች ተደብድበዋል ሆስፒታሎች ተጨናንቀዋል።  የደሴ ህዝብ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል። እስካሁን የሞቱትን እና የቆሰሉትን ለማወቅ በፊድራል ፖሊስ ሐይሎች ሆስፒታሎች በመከበቡ ለማወቅ አልተቻለም። በደሴ የሚኖሩ ሙስሊሞች 2 ሰዎች መገደላቸውን ለኢሳት ተናግረዋል በአማራ ክልል በወረባቡ ከተማ ፤ እና መርሳ አካባቢ ክፍተኛ ተቃውሞ የተደረገ ሲሆን በሙስሊሙ እና …

በወላይታ የአንድነት ሰብሳቢ ታሰሩ በደቡብ ክልላዊ መስተዳደር ወላይታ ዞን የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሰብሳቢ ታሰሩ፡፡ ሰብሳቢው አቶ ወኖ መንዓሳ ትናንት ነሐሴ 1 ቀን 2005 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ የዞኑ የፓርቲው ከፍተኛ አመራር የሆኑትንና ባለፈው ሳምንት ሐምሌ27 የታሰሩትን ወ/ሮ ሀዲያ መሐመድን ለመጠየቅ ከሚኖሩበት በዴሳ ወረዳ ወላይታ ሶዶ ከተማ ደርሰው ሊመለሱ ሲሉ ከአውቶቡስ ተራ ተይዘው መታሰራቸውን የዞኑ […]

የኢትዮጵያ እድሜ ጠገብ ቅርሶች ላይ በተለያየ አቅጣጫ ጥፋት እየፈጸመ መሆኑን፤ በሕገ ወጥ ቅርስ አቀባዮች የሀገሪቱ የታሪክ ማህደር ወደ ዉጭ እየተጋዘ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተነገረ።

1434ኛው የእድ አል ፈጥር በዓለ ዛሬ በሙሥሊም ሀገራት ተከበረ። ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ የሙሥሊሙ ህብረተሰብ አባላት በአዲስ አበባ ስቴድየም የተካሄደውን የበዓሉን አከባበር ሥነ ሥርዓት ወደዚያ በመሄድ እና በዙርያው በመገኘት ተከታትለውታል።

በሳውዲ ዐረቢያ ፣ በየመን እና በዩኤስ አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሙሥሊሞች ዕለቱን እንዴት እንዳከበሩት ከጄዳ፣ ከሰንዓ እና ከዋሽንግተን ዲሲ ወኪሎቻችን ጋ አጠር ያለ ቃለ ምልልስ አድርገናል።