ጽዮን ግርማ

ኢትዮጵያ በፓርቲ ላይ የተመሰረተ ፖለቲካ ባህል ውስጥ የገባችው የ1960ዎቹን ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ተከትሎ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የተለያዩ ርዮተ ዓለሞች ተፋጭተው ዴሞክራሲያዊ ሥርዐት ይመሰረትባታል በሚል ተስፋ ቢጣልም የድርጅቶቹ የኋላ ታሪክ እንደሚያስረዳው ለሀገርና ለሕዝብ የሚጠቅም ለውጥ ከማምጣት ይልቅ እርስ በእርስ የመጨራረስ ባህል እንደነበራቸው ነው፡፡ ከበርካታ ንፁሃን ዜጎች ደም መፍሰስና እልቂት በኋላ ህወሓት ኢሕአዴግን መሥርቶ ወደ ሥልጣን ሲመጣም ከሻዕቢያ በስተቀር ሌሎቹ ድርጅቶች እስከ አመራሮቻቸው ደብዛቸው ጠፍቶ ነበር።ኢህአዲግ የሥልጣን ወንበሩን ከጨበጠ በኋላ በሽግግር መንግሥት ምስረታ ፓርቲዎች እንዲሳተፉ ይፋዊ ጥሪ በማስተላለፍ በፓርላማ መቀመጫ እንዲያገኙ በማድረግ ዴሞክራሲያዊ ሥርዐት የተመሰረተ ለማስመሰል ጥረት ቢያደርግም በተለያየ ምክንያት አባሮ መልሶ ለመበታተን ጊዜ አልወሰደበትም ነበር ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

በአገር ዉስጥም ሆነ ከአገር ዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ጉጉትና ምኞት ፣ ልጆችዋ ከርሷ የሚሰደዱባት ሳይሆን የተሰደዱት ተመልሰው ለሌሎች መጠጊያ የምትሆን፣ የሕግ የበላይነት የሰፈነባት፣ የሰብአዊ መብቶች የሚከበሩባት፣ ዘር፣ ኃይማኖት፣ ጾታና መደብ ሳይባል ለሁሉም እኩል የሆነች፣ አንዲት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ማየት ነው። ነገር ግን፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ በአገዛዙ እያየን ያለነው፣ ልብን የሚያደማና የሚያቆስል ነው። በስድሳዎቹ ከነበረው የደርግ ስርዓት በባሰ፣ […]

ሐምሌ ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የየመን መንግስት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ህገወጥ በሆነ መልኩ አሳልፈው ከሰጡዋቸው በሁዋላ ኢትዮጵያውያን አሁንም ቁጣቸውን እየገለጹ ሲሆን፣ አንዳንድ ወገኖች ” የአቶ አንዳርጋቸው መታሰር ልብን የሚሰብር ቢሆንም፣ ወሳኙ ነገር ማዘን ሳይሆን ለለውጥ ቆርጦ በመነሳት መታገል ነው” ብለዋል። በሌላ በኩል ደግሞ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የየመን መንግስት የወሰደውን እርምጃ እንዲሁም …

ሐምሌ ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በረመዳን ጾም ተጠናክሮ የቀጠለው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ፣ ዛሬም በበኒ መስጂድ እጅግ ከፍተኛ ህዝብ በተገኘበት ተካሂዷል። ኢትዮጵያውያኑ ሙስሊሞች ” የእምነት ነጻነታችን ይከበር፣ ለከፈልነው መስዋትነት ተመጣጣኝ ውጤት እናመጣለን” የሚሉ መፈክሮችን ጽፈው አሳይተዋል። ከሁለት አመት በላይ የዘለቀው የሙስሊሙ ተቃውሞ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መሪዎቹ እየገለጹ ነው።

ሐምሌ ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ተጠናክሮ የቀጠለው እስር በአገሪቱ ውስጥ ምንም አይነት ተቃውሞ እንዳይኖር ያደረገ ነው ብሎአል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ያሉበት ሁኔታ አለመታወቁንና ለከፍተኛ ስቃይ ሊዳረጉ እንደሚችሉ መግለጹንና አለማቀፉ ማህበረሰብ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ማሳሰቡን ያስታወሰው አምነስቲ፣ ከዚሁ ጋር በተያያዘ አቶ ደንኤል ሽበሺ፣ አብርሃ ደስታ፣ የሽዋስ አሰፋና ሀብታሙ …

” ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ፈታተን መግጠም አለብን። ” የወያኔ ባለስልጣናት ” አላርፍ ካሉ ፍቃዳቸውን ሰበብ ፈጥረን እንነጥቃቸዋለን። ” የምርጫ ቦርድ ሃላፊ በኢሕአዴግ ባለስልጣናት እና በምርጫ ቦርድ መካከል መጭውን ምርጫ በተመለከተ ሰፋ ያለ ዝግ ስብስባ ተካሂዶ ነበር ሲል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት አከባቢ የተገኘ መረጃ ጠቁሟል። በአይቶ ጸጋዬ በርሄ የተንታለለ የመሃይማን ቢሮ ውስጥ የምርጫ ቦርድ ታዛዥ ሃላፊዎች እስከምሽት […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በዉጭ የሚኖሩ የአፋር ተወላጆች መገናኛ መረብ የተሰኘዉ ስብስብ በሶማሌ ተወላጆችና በአፋሮች መካከል በመሬት ይገባኛል ምክንያት የሚነሳዉን ግጭት የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ትኩረት አልሰጠዉም ሲል ወቀሰ።

ከ15 ቀናት በፊት በማላቦ ኢኳቶሪያል ጊኒ በተደረገዉ የአፍሪቃ መሪዎች ጉባኤ የሰብዓዊና የሕዝብ መብት ጉዳይ ላይ በተወያዩበት ርእስ ለማብራሪያ ያህል በአፍሪቃ ሕብረት የሕግ መምሪያ ኃላፊዉ ፕሮፌሰር ቪንሰንት ሜኺዮሌ መግለጫ ሰጥተዋል።

ለመሆኑ ወጣቱ ፆሙን እንዴት ይጾማል? ያፈጥራልስ? የረመዳን ጾም ከገባ ሁለት ሳምንት ሊሞላው ጥቂት ቀናት ነው የቀሩት። በዚህ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በፆም ፀሎት የሚታሰበው የቅዱስ ወር ለማን ም ሙስሊም ቢሆን ግዴታ ነው።

ኢህአዴግ በምርጫ ዋዜማ የጀመረው እስር በአምባገነንነት መስመሩ ለመቀጠል የቆረጠ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው!!! በፖለቲካ አመለካከታቸው እና እምነታቸው የታሰሩ ዜጎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ በድጋሚ እንጠይቃለን!! ሕወሓት/ኢህአዴግ ለአለፉት 23 ዓመታት ወደር የሌለው የዴሞክራሲያዊ መብት ገፈፋና የሰብአዊ መብት ረገጣ በዜጎች ላይ ሲፈጽም መቆየቱና አሁንም በዚያው የአፈናና እስር መንገድ መቀጠሉን ዓለም የሚያውቀው እውነታ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በተለይም በሚቀጥለው ዓመት […]

ወያኔ አቶ አንዳርጋቸውን እንዴት ማፈን ቻለ? ለዚህ ጥያቄ መልስ መስጠት ለግንቦት 7 ብቻ ሳይሆን ለሁላችንም የሞትና የሽረት ጥያቄ ነው:: በቂ ማስረጃ እስክሚሰበሰብ ድረስ አራት አቅጣቻዎችን መመርመር ያስፈልጋል:: 1) ለሻቢያ ሁሉ ነገር ከራስ በላይ ነፋስ ነው:: ራሱ ሻቢያ በተዘዋዋሪ ለወያኔ የአቶ አንዳርጋቸውን የበረራ ሰዓታቸውን አሳልፎ ሊሰጥ ይችላል::ይህ እንግዲህ በኤርትራ ውስጥ የሚገኙ የግንቦት 7 መሪዎች ሁኔታውን በደንብ […]

ካሳለፍነው ማክሰኞ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር ውለው በማዕከላዊ በእስር ላይ የሚገኙት ወጣቱ ፖለቲከኛ ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ፣ ወጣቱ ፖለቲከኛ ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት ፓርቲ ድርጅት ጉዳይ ም/ሀላፊ ወጣቱ መምህርና ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታ የአረና ፓርቲ አመራር በትላንትው ዕለት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም ከምሽቱ 12፡16 ላይ የአረና ፓርቲ […]

በዚህ ወር ብቻ እጅግ ከባድ የሆኑ ለጆሮ የሚቅፉ እና ለሰው ልጆች የሚያሰቅቁ የሰብአዊ መብት ገፈፋዎች እና የዜጎች ወደ እስር ቤት መወርወር የበለከተበት ከሃገር ቤትም አልፎ እስከ ጎረቤት አገር ድረስ ተዘልቆ በጉቦ የዜጎች የመዘዋወር መብት በስውር እጆች የተደፈሩበት እሱንም ተከትሎ የተቃዋሚ ድርጅቶች አመራሮች ከየመንገዱ እና ከቤታቸው እየተያዙ ወደ እስር የተወረወሩበት ሁኒታ እያየን እየሰማን ነው። የግንቦት ሰባት […]

በአሸባሪው መንግስታዊ ዘራፊ እና አፋኝ ቡድን የታፈነው አቶ አንዳርጋቸው ጸጌ ወያኔ ለመፍታትም ሆነ ለመግደል ዝግጁ አይደለም ። ግደሉት አሊያም ስቀሉት ቢባሉ እንኳን በፍጹም አያደርጉትም። ምእራባውያኑ ከአፍ ወሬ ውጪ ምንም የሚተገብሩት ነገር የለም ፡ እስክንድር ነጋ በቂ ምሳሌ ሊሆን ይችላል ከሰብአዊ መብት ድርጅቶች ጀምሮ እስከ አሜሪካው የውጪ ጉዳይ አናት ኬሪ ድረስ ድምጻቸውን ቢያሰሙም ለይስሙላ እና ለብሄራዊ […]

ኢትዮጵያ ሪቪው ምንጮቹን ጠቅሶ ፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የታፈኑት፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ የሆኑት አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሳያወቁት ፣ በአቶ ጌታቸው አሰፋ የሚመራው የሕወሃት ደህንነት ጽ/ቤት እና በአቶ ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል ዉሳኔ እንደሆነ ዘገበ። ሁለቱ የሕወሃት ባለስልጣናት፣ የሆነውን ነገር ለጠቅላይ ሚኒስተሩ ለመንገር እንኳን ደንታ እንደልነበራቸው ኢትዮጵያ ሪቪው፣ እነ አቶ ጌታቸው አሰፋ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም […]

ሰላማዊ ሰዎችን ማሰር ቀለቡ ያደረገው መንግስት፣ በትላንትናው እለት ከአንድነት ፓርቲ አቶ ሀብታሙ አያሌው እና አቶ ዳንኤል ሽበሺ፣ ከሰማያዊ ፓርቲ አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ ከአረና አቶ አብርሃ ደስታ እንዳሰራቸው ተነግሯል። ይህንን በመቃወም በፌስቡክ ኢትዮጵያዉያን ካሰፈሩት መካከል ጥቂቱን እንደሚከተለው ቀንጭበን አቅርበናል፡ ያሬድ አማረ፡ «ወደኋላ አንመለስምዘመን ተሻጋሪ ወጣቶች በቅለናልና በምንም መልኩ ለሚደረግ ማዋከብ፤እስራት እና ግድያ ከጀመርነው የሰላማዊ ትግል መስመር […]

የህወሓት/ኢህአዲግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ዜጎችን በማፈንና በማሰቃየት ብሎም በመግደል የአፈና አገዛዙን ለረጅም ጊዜ ሲያራምድ መቆየቱ ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ በተለይም ባለፉት 10 ዓመታት የህዝብን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማፈን እስራትና ግድያውን ህጋዊ ለማስመሰል የተለያዩ አፋኝ አዋጆችን አውጥቷል፡፡ እነዚህን አዋጆችንም ተገን አድርጎ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና አባለትን፣ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን፣ እንዲሁም የእምነት ተቋማት […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ሐምሌ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት ሰሞኑን ከአገር ቤት በሚደወሉ ስለኮች የተጨናነቀ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ደዋዮች የኢህአዴግን ስርአት በሃይል ለመፋለም መቁረጣቸውን የሚገልጹ ናቸው። እንደሰሞኑ ሁሉ ” መንገዱን አሳዩን እና አቶ አንዳርጋቸው ይዘውት የተነሱትን ራእይ እውን እናድርገው ” የሚሉ ወጣቶች እየተበራከቱ ሲሆን፣ አንዳንዶች ደግሞ ህዝቡ ራሱን እያደራጀ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባው እያሳሰቡ ነው። አንድ አስተያየት ሰጪ መንግስት …

ሐምሌ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በፌደራል ፖሊሶች እየተደበደበ ወደ አልታወቀ ስፍራ ተወስዶ የነበረው ታዋቂው ፖለቲከኛና ጸሃፊ አብርሃ ደስታ ማእከላዊ እስር ቤት መታሰሩ ታውቋል። የአብረሃ መኖረያ ቤት በፖሊሶች እንደተፈተሸም ለማወቅ ተችሎአል። የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ የፓርቲው ምክትል የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ዳንኤል ሽበሺ እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ የሽዋስ …

ሐምሌ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የህወሃት አባል የሆነውና በሶማሊ ክልል የደህንነት ሃለፊ በመሆን ሲሰራ የነበረው መቶ አለቃ አወጣሃኝ በክልሉ ፕሬዚዳንት ትእዛዝ እንዲታሰር ተደርጓል። ግለሰቡ በምን ምክንያት እንደታሰረ ለማወቅ ባይቻልም፣ በክልሉ ፕሬዚዳንት እና በህወሃት የጸጥታ ሰራተኞች መካከል እየተካረረ የመጣው አለመግባባት ማሳያ መሆኑን ከስፍራው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።

የሶማልያ ጠ/ሚንስትር አብዲዋሊ ሼክ አህመድ ሙሐመድ፣የብሔራዊ ደኅንነት ድርጅት ሹም የነበሩትን በሺር ጉቤንና የፖሊሱን ኃይል አዛዥ አብዲከሪም ዳሒርን በመሻር በምትካቸው፤ በብሪታንያ የሶማልያ አምባሰደር የነበሩት

በብራዚል በመካሄድ ላይ ባለውና ፣ የፊታችን እሁድ በሚያከትመው የዘንድሮው የዓለም የአግር ኳስ ዋንጫ ውድድር፣ ትናንት ማታ በተካሄደው ሁለተኛው የግማሽ ፍጻሜ ውድድር አርጀንቲናና ኔደርላንድ በ9o ው ደቂቃ ጨዋታና 30 ደቂቃም ተጨምሮ ባለመሸና

Press Release by Blue Party Ethiopia / Semayawi Party- Ethiopia/
It is a well known fact that TPLF/EPRDF has slaughtered and oppressed Ethiopian citizens since it came to power. In order to oppress the peaceful struggle, especially within the last 10 years, the regime acclaimed several repressive proclamations and laws to legalize its butchery and tyranny. Many politicians, journalists, bloggers, religious leaders and people who raised question against the regime are victims of these proclamations. Since these controversial laws have been applauded by TPLF/EPRDF, the security institutions that serve the regime have put a lot of politicians, journalists, activists and many who issue its power to jails. The regime also tries to label Medias such as ESAT as terrorists’ medium to threaten politicians in relation to terror act which is ridiculous. Blue likes to stress out that no one should not and cannot choose Medias for anyone in regards to freedom of speech and press.

Accordingly, TPLF/EPRDF’s obsession of power and its negligence to accountability is leading the country in a wrong and chaotic situation. Particularly the last four years have been difficult and the arrest of many peaceful citizens made the political atmosphere very constricted. Nevertheless, countless people are struggling peacefully within the rule of law; many flee abroad to over throw the dictatorial government with whatever way they thought is possible. Thus, Blue Party /Semayawi/ finds it very significant to take this firm position due to the above reasons and more that hasn’t been mentioned here:

1- On June 24 2014, the rebel group Ginbot 7’s General Secretary, Andargachew Tsege was detained by the Yemeni intelligence officers in collaboration with Ethiopian intelligence officers. The officials of both countries knowingly violated international conventions. It is not legal or convenient to intervene in eternal matters of a sovereign country whatsoever. Consequently, the act of Yemeni officials will sure distress the upcoming relationships of the countries. Nonetheless, as the regime didn’t let the public and his family know his whereabouts for 16 days, the matter has been viewed suspiciously in our party, in the public at large and in the international community. It is our concern that he could be ill treated and more. Therefore, Blue Party strongly demands that Andargachew Tsege must be treated moderately and that all his rights under custody are respected.

2- The regime also illegally arrested prominent figures of Ethiopian politicians on July 8. The detainees are members and leaders of parties who are engaged in peaceful struggle. In fact it is not surprising to hear such news; however, we have learned that the regime is anxious and is trying to connect the detainees with rebel forces so that it hopes it can crack down the peaceful struggle before the 2015 election for they could be a threat to its power. It is clear that the dictatorial rule wants to stay in power more through spreading fear among the society. Thus its desperation is leading its ego to arrest one of our members and three other party leaders. Blue Party’s National Council Vice Chairperson Mr. Yeshiwas Assefa, Mr Habtamu Ayalew(Head of Public Relations Affairs of UDJ), Mr. Daniel Shibeshi(Vice Chairman of Organizational Affairs of UDJ) and Arana Tigray’s executive committee member and activist Mr. Abraha Desta are detained for activism and peaceful struggle. All these figures have been engaged in promoting peaceful struggle within the rule of law. Their arrest boldly hints that the regime’s final days in power are counted and change is inevitable in the near future. Hence, Blue Party demands an immediate release of the detainees and as well advocate the regime to stop the state terror. We condemn that TPLF/EPRDF comes to its sense and do what’s right for themselves and the country before it’s too late.
Finally we make sure that the act of state terror by TPLF/EPRDF will not hinder us for an inch from the none-violent struggle we are committed to. We have come into the decision that the offensive and atrocious act of TPLF/EPRDF required us to bring the struggle to the next level. Hence, we call upon the Ethiopian people to be ready to a nationwide movement and make sure that Blue Party is fully committed to provide the leadership needed at its unsurpassed. The Party also calls the peaceful parties, international institutes, human right activists, civic societies for all Ethiopian born and Ethiopians to stand together.

Long live Ethiopia
Blue/Semayawi Party Ethiopia
July 10, 2014

ተማርን የሚሉ ሰዎች አማርኛን ቋንቋ ዉስጥ አንዳንድ የእንግሊዘኛ ቋንቋን እየሰነቀሩ ቋንቋዉ እንዲመነምን እየዳረጉ ናቸዉ ይላሉ ምሁራን። በሌላ በኩል ሃሳብን ለመግለፅ አማርኛ ቋንቋ አስቸጋሪ ነዉ የሚሉም አልጠፉም!የባዕድ ቃላትን የመዋስ ጉዳይ እንዳለ ሆኖ፤ እንግሊዘኛ ቃላትን ጣል እያደረጉ የመናገር አባዜ የተለመደ ይመስላል

የእስራኤል የጦር አዉሮፕላኖች በፍልስጤም ግዛት ጋዛ ላይ ዛሬ ደጋግመዉ ባደረሱት ድብደባ የተጎዱ ሲቪሎች ቁጥር መጨመሩን ዘገባዎች ያመለክታሉ። የተመድ የፀጥታዉ ምክር ቤት እስራኤል ከሃማስ ጋ የገጠመችዉን ፍጥጫ ለመመልከት አስቸኳይ ስብሰባ ያደርጋል።

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
ሀምሌ 3/2006ዓ/ም
የህወሓት/ኢህአዲግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ዜጎችን በማፈንና በማሰቃየት ብሎም በመግደል የአፈና አገዛዙን ለረጅም ጊዜ ሲያራምድ መቆየቱ ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ በተለይም ባለፉት 10 ዓመታት የህዝብን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማፈን እስራትና ግድያውን ህጋዊ ለማስመሰል የተለያዩ አፋኝ አዋጆችን አውጥቷል፡፡ እነዚህን አዋጆችንም ተገን አድርጎ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና አባለትን፣ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን፣ እንዲሁም የእምነት ተቋማት መሪዎችን እና በአገዛዙ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ማሰሩን፣ ማሰቃየቱንና ግድያውን ተያይዞታል፡፡ በህገ መንግስቱ የተካተቱ የሰብዓዊ መብቶችንና ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን በሙሉ የሚጥሰውና የአምባገነንነት ስልጣኑን ለማራዘም ሲል ያፀደቀው የፀረ-ሽብር አዋጅ ከፀደቀበት እለት አንስቶ ኢህአዴግ ለስልጣኔ ያሰጉኛል የሚላቸውን ፍፁም ሰላማዊ ታጋዮችንና ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው በድፍረት የፃፉ ጋዜጠኞችን ብሎም የእምነት ነፃነታችን ይከበር ብለው የጠየቁ የሀይማኖት መሪዎችን በጠራራ ፀሃይ ያለምንም ወንጀል በዚሁ ህገ ወጥ አዋጅ ‹‹የፀረ ሽብር ግብረ ሀይል›› በሚባል ማንነቱ በማይታወቅ የጨለማ ቡድን ወደ እስር ቤት እያጋዘ ይገኛል፡፡

ይህን የሚያጋልጡ ሚዲያዎችንም ለማፈን እስር ቤቶችን ጨምሮ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር እያፈሰሰ የአየር ሞገድ ያውካል፤ በዚህ ሳያበቃ በሀገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን የሚያሰሙ ፖለቲከኞችን ለማሸማቀቅ እንደ ኢሳት ያሉ ሚዲያዎችን የአሸባሪ ልሳን ብሎ በመፈረጅ ሚዲያውን የሚጠቀሙትን ደግሞ ከአሸባሪዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው አድርጎ መወንጀሉን ቀጥሎበታል፡፡ እንደሰማያዊ እምነት ማንም አካል መልእክት የሚያስተላለፍበትን የሚዲያ ተቋም ሊመርጥለት እንደማይችል መንግስት እንዲገነዘበው ከዚህ በፊት በግልፅ ያሳወቀ ሲሆን አሁንም ፓርቲው በዚሁ የፀና አቋሙ እንደሚቀጥል በድጋሚ ይገልፃል፡፡

ባጠቃለይ የዚህን ገዢ አካል የእውር ድንብር ሀገር የማስተዳደር ጉዞ ለመታገል በርካቶች በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ቢሆንም በህወሓት/ኢህአዲግ ግፍና መከራ ተገፍተው ስርዓቱን በሃይል እናስወግዳለን ብለው ሀገር ጥለው የተሰደዱ ዜጎችም እንዳሉ ይታወቃል፡፡ የህወሓት/ኢህአዲግ ማናለብኝነትና የስልጣን ጥመኝነትም በግለሰቦች ላይ ከሚያስከትለው ማህበራዊ ቀውስ በላይ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ አለመረጋጋትን አስከትሏል፡፡ በአሁኑ ሰዓትም ይህ ገዢ ፓርቲ የፈጠረው ስርዓት የሀገሪቷን ሰላማዊ የፖለቲካ ምህዳር በማጥበብ ሀገራችንን ወደ አልተፈለገ አለመረጋጋትና ቀውስ እየመራት ይገኛል፡፡ፓርቲያችንም እነዚህን ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎችም በቅርቡ እየተፈፀሙ የሚገኙ ህገ ወጥ ድርጊቶች ስላሳሰበው ይህን መግለጫ ለማውጣት ተገዷል:-

1. ሰኔ 16 2006 ዓ.ም የየመን መንግስት የዓለም አቀፍ ስምምነቶችንና ድንጋጌዎችን በመጣስና በሰው ሀገር የውስጥ ጉዳይ በመግባት የአማፂ ቡድን ግንቦት ሰባት ዋና ፀሃፊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን መያዟ ይታወሳል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ለህወሓት/ ኢህአዴግ ተላልፈው መሰጠታቸውን ከ16 ቀናት በኋላ መታወቁና ይህንንም ሁለቱ ሀይሎች ማመናቸው ተሰምቷል፡፡ ነፃነት በሌለበት ሀገር ዜጎች ሰብዓዊ ክብራቸውን ለማስጠበቅ የሚያደርጉት ጥረት የሌሎች ሀገር መንግስታት የሚያደርጉትን ጣልቃ ገብነት በዓለም አቀፍ ስምምነቶችም ሆነ በተለይ በሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ጥላ የሚያጠላ መሆኑን ግንዛቤ አለመወሰዱ እጅግ የሚያሳዝን ድርጊት ነው፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከተያዙ በኋላ ላለፉት 16 ቀናት በምን አይነት ሁናቴ እንደቆዩ ህዝብና ቤተሰቦቻቸው እንዲያውቁት አለመደረጉ፤ ስለ አያያዛቸው ሁኔታም በማህበረሰቡና በፓርቲያችን ውስጥ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንዲኖር አድርጓል፡፡ሰማያዊ ፓርቲ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሰብዓዊ አያያዝ እያሳሰበው ህወሓት መራሹ የኢህአዴግ አገዛዝ አያያዛቸውን ግልፅ እንዲያደርግ ሰብዓዊ ክብራቸውም እንዲጠበቅ በጥብቅ ያሳስባል፡፡
2. በዚሁ ሳምንት ገዢው ፓርቲ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ የአምባገነኑን መንግስት ህወሓት/ኢህአዲግን ሲታገሉ የነበሩ ፖለቲከኞችን በስመ አሸባሪ ከያሉበት እየለቀመ ህገ-ወጥ እስራት መፈፀሙ ይታወቃል፡፡ ህወሓት/ኢህአዲግ ይህ ግብታዊ ተግባሩ ምንም እንኳን አዲስ ባይሆንም በአሁኑ ወቅት ለውጥን ለማምጣት በቆራጥነት እየታገሉ ያሉ ሰላማዊ ታጋዮችን ማሰሩ በሀገር ውስጥ በህጋዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ፓርቲዎችን ከአማፂ ቡድኖች ጋር ግንኙነት ያላቸው በማስመሰል ሰላማዊ ትግሉን ለማዳከምና መጪውን 2007 ዓ/ም ምርጫ ያለ ተቀናቃኝ ለማለፍ የሚደረግ ህገ ወጥ እንቅስቃሴ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ የፓርቲያችን ብ/ም/ቤት ምክትል ሰብሳቢ የሆነው አቶ የሺዋስ አሰፋ በሰላማዊ ትግሉ በቁርጠኝነት እየተሳተፈ ባለበት ሁኔታ ለእስር መዳረጉ፤ የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው፤ የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሀላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄን በመፍጠር ላይ ያለው የአረና /ትግራይ/ ፓርቲ አመራር አባል የሆኑትን አቶ አብረሃ ደስታ ለእስር መዳረጋቸው ህወኃት/ኢህአዴግ የመጨረሻው መጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ያረጋግጣል፡፡ በመሆኑም አገዛዙ እያካሄደ ያለውን መንግስታዊ ሽብር አቁሞ ለሀገርም ሆነ ለራሱ የሚበጀውን መንገድ እንዲከተል እያሳሰብን የታሰሩት የፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን፡፡

በመጨረሻም ፓርቲያችንን መንግስት እያደረገ ያለው ሽብርን የመንዛትና ህግን የመጣስ ተግባሩ መቼም ቢሆን ከሰላማዊ ትግሉ እንደማያቆመውና ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በአፅንኦት እየገለፀ እነዚህንና ከላይ የተጠቀሱትን የገዢውን ፓርቲ መርህ አልባነት፣ ህገ-ወጥነት እና የለየለት አምባገነንነትን አሁን ካለው ነባራዊ እውነታ ጋር አጣምሮ የትግል ስልቱን ደረጃ ከፍ ወዳለ ምዕራፍ ማሸጋገር እንዳለበት አምኗል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ ለምናደርጋቸው ሀገር አቀፍ ንቅናቄዎች መላው የሀገሪቱ ህብረተሰብ በንቃት ተዘጋጅቶ እንዲጠብቅ ጥሪውን እያስተላለፈ ለዚህም ቁርጠኛ አመራር ለመስጠት ዝግጁነቱን ለመግለፅ ይወዳል፡፡በዚህ አምባገነንነትን ለመታገል በሚደረገው ንቅናቄም በሀገር ውስጥ የሚገኙ ህጋዊና ሰላማዊ ፓርቲዎች፤አለም አቀፍ ተቋማት፤የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፤ሲቪክ ማህበራት፤መላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከሰላማዊ ትግሉ ጎን በጋራ እንድንቆም እንጠይቃለን፡፡

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር
ሰማያዊ ፓርቲ
ሀምሌ 3/2006ዓ/ም

አቡጊዳ – እነ ሃብታሙ ፍርድ ቤት አልቀረቡም – አብርሃ ደስታ የት እንዳለ አይታወቅም « ከትላንት በስቲያ የተያዙት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በዛሬው እለት አራዳ ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ የፍኖተ ነፃነት የፖሊስ ምንጮች የፍኖተ ነፃነት የፖሊስ ምንጮች እንደጠቆሙት የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወጣት ሀብታሙ አያሌው፣ የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ም/ኃላፊ የሆነው አቶ ዳንኤል ሺበሺ እንዲሁም […]

ከመኢአድ/አንድነት ውህደት አመቻች ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ………………………………………………………… የውህደት አመቻች ኮሚቴውን በማሰር ውህደቱን ማደናቀፍ አይቻልም!!! ኢህአዴግ ሰሞኑን የጀመረው እስር የአንድነት/መኢአድን ውህደት የማደናቀፍ አቅም እንደሌለው ለኢትዮጵያ ህዝብ ማረጋገጥ እንወዳለን …………………………………………… በኢትዮጵያችን በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለማምጣት እየታገሉ የሚገኙት አንድነትና መኢአድ ከጥልቅ ውይይት በኋላ ወቅታዊው የፖለቲካ ሁኔታ የሚፈልገውን በመገንዘብ፤ የህዝቡን ጥያቄ መመለስ የሚችል የበተባበረ የፖለቲካ ሃይል ለመፍጠር እንዲቻል […]

አገር ቤት ያሉ መሪዎች ቁርጠኝነት ያስደንቀኛል። ግርማ ሰይፉ «ለመታሰር እንዘጋጅ» አለ። ዳንኤል ተፈራ «ገዥዎች፣ እመኑኝ ባሮጌው መንገዳችሁ በርካቶችን ነፃነት ናፋቂዎች በሰፋፊ እስር ቤታችሁ ታጉሩ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የዚህን ትውልድ የነፃነት መንፈስ ግን ልታስሩት አትችሉም» አለ። የፍኖት ዋና አዘጋጅ ነብዩ «ጨቋኞችን መታገል ፅድቅ እንጂ ኩነኔ እንደሌለው አምናለሁ፤ ጭቆናን እምቢ በማለቴ የምጠጣት እያንዳንዷ ፅዋ በፈጣሪ ዘንድ ወሮታ […]

ግፍና ሰቆቃ ወልዶናል – የአዲስ አበባ አንድነት ሕዝብ ግንኙነት ያሬድ አማረ ************************************************************ እንታሰራለን ስንል አንፈታም ማለት አይደለም ፤ በትግል ውስጥ አልፈን እናሸንፋለን ስንልም ላንሞት እንችላለንም ለማለት አይደለም ፡፡ ሊሰመርበት የሚገባው ግን በሰላማዊ ትግሉ ማሳ ላይ ዘር ሆነን ተዘርተን ብዙ ፍሬ እንዳፈራን በተራዳን ወቅትና ወደ ጎተራ በአንድነት ተሰባስበን በገባን ወቅት የተነሳንለት ዓላማ ጥልቅና ምጡቅ እንደሆነ ልባችን […]

ይህንን ደብዳቤ ስጽፍ ፊት ለፊቴ የቤተሰባችንን ፎቶ ግድግዳው ላይ እያየሁ ነው፡፡ ‹‹ይናገራል ፎቶ›› አሉ፡፡ አቤት በፎቶማ እንዴት ያምርብናል፡፡ ፎቶ ላይ ያለው ፈገግታ እንዲሁ ትዳር ውስጥም ቢቀጥል እንዴት ጥሩ ነበር፡፡ ግርም ይላልኮ፡፡ፎቶ አንሺዎች ሁሉ ከአንድ እናት የተወለዱ ይመስል ለምንድን ነው በግድ ‹‹ፈገግ በሉ›› የሚሉት፡፡ በቃ ፎቶ ማለት ደስታን ማሳያ ብቻ ነው እንዴ፡፡ የከፋው ሰው ፎቶ አይነሳም ማለት ነው፡፡ አንዳንድ ፎቶ አንሺዎችና ቪዲዮ ቀራጮችኮ በገዛ ሠርጋችን ተዋንያን ያደርጉናል፡፡ እንደ ራሳችን ሳይሆን እንደ እነርሱ ፈቃድ ያስኬዱናል፣ ያሳስሙናል፣ ያስተቃቅፉናል፣ ያሰልፉናል፣ ያጣምሙናል፣ ያቃኑናል፡፡ እነርሱ ግን የፊልም ዳይሬክተር ናቸው ወይስ የሠርግ ቪዲዮ ቀራጮች? እኛስ ሙሽሮች ነን ወይስ ተዋንያን?

ከተለያየን ጀምሮ ይህንን ፎቶ ደጋግሜ እያየሁ ደጋግሜ አስባለሁ፡፡ ለብቻ መሆን አንድ የሚጠቅመው ነገር ቢኖር የማሰቢያ ጊዜ መስጠቱ ነው፡፡ ሰው ለመኖር ለካ ከምግብና መጠለያ እኩል የማሰቢያ ጊዜም ያስፈልገዋል፡፡ እንዲሁ ስንዞር፣ እንዲሁ ስንወጣና ስንወርድ፣ እንዲሁ ቀዳዳ ለመሙላት ወዲህ ወዲያ ስንል፣ እንዲሁ ጠዋት ወጥተን ማታ ስንገባ አይደል እንዴ የኖርነው? አሁን ሳስበውኮ የኑሮ ወንዝ ወደወሰደን ፈሰስን እንጂ አስበን አልኖርንም፡፡

እስኪ ልጠይቅሽ ለመሆኑ ለኛ ትዳር ምንድን ነበር? አንድ ቤት መኖር፣ አንድ አልጋ ላይ መተኛት፣ ልጆች መውለድ፣ ወላጆቻችን ቤት አንድ ላይ መሄድ፣ መጎራረስ፣ <ከባለቤትዎ ጋር> ተብሎ መጠራት፣ ምንድን ነው ግን ትዳር? ለመሆኑ ሠርገን ነበር ወይስ ተጋብተን ነበር? ጋብቻ ነበረን ወይስ ትዳር? አቤት ለሠርጋችን እንዴት ነበር የለፋነው፡፡ ‹‹ጋብቻ የትዳር መጀመሪያው ሥነ ሥርዓቱ ነው፤ ሠርግ ማጀቢያው ድግስ ሲሆን፣ ትዳር ደግሞ በዚህ በኩል ተገብቶ የሚኖረው ኑሮ ነው›› የሚል ካነበብኩ በኋላ ይህንን ጥያቄ መጠየቅ ጀምሬያለሁ፡፡ አዳራሽ ለማግኘት፣ መኪና ለማግኘት፣ የሠርግ ልብስ ለመምረጥና ለማሰፋት፣ ድግሱን ለማሣመር፣ የሚጠሩ ሰዎችን ለመምረጥ፣ ሚዜዎቻችንን ለመምረጥ ስንቴ ነበር ያሰብነው፤ ሰሐንና ብርጭቆ እንኳን ሳይቀር አስበንበት፣ ሰው አማክረን፣ ዙረን መርጠን፣ ከሌሎች ልምድ ወስደን ነበር የተከራየነው፡፡

በእኔና ባንቺ ሠርግ ስንት ሰዎች ተሳተፉ፣ ስንቶች ለፉ፣ የስንት ሰዎች ሐሳብ ተዋጣ፣ የስንቶች ልምድ ተቀሰመ፣ የስንቶች ጉልበትስ ፈሰሰ፡፡ በያንዳንዱ ጉዳይ እንወያይ፣ እንከራከር፣ እንጨቃጨቅ፣ እንለያይ ነበር፡፡ በያንዳንዱ ጉዳይ እንደገና እንገናኝ፣ እንግባባ፣ እንስማማና እንታረቅ ነበር፡፡ በብዙ ሰዎች ታግዘን አግብተን ትዳርን ብቻችንን ገጠምነውና አልቻልነውም፡፡ ሠርግ ላይ ያለው እገዛ ትዳር ላይ ቢሆን እንዴት ጥሩ ነበር፡፡

አሁን ሳስበው የለፋነው ለሠርጋችን እንጂ ለትዳራችን አልነበረም፡፡ እስኪ ትዝ ይበልሽ፡፡ ከኛ በፊት የተጋቡ ሙሽሮችን ልምድ የወሰድው ስለ ሙሽራ ልብስ፣ ስለ ቬሎ፣ ስለ ሚዜ፣ ስለ መኪና፣ ስለ ድግስ፣ ስለ አዳራሽ፣ ስለ መጥሪያ ካርድ፣ ስለ ባንድ፣ ስለ ቪዲዮ እንጂ ስለ ኑሯቸው አልነበረም፡፡ እነርሱምኮ ‹ዲል› ባለ ድግስ፣ የሁላችንንም ቀልብ በማረከ ሥነ ሥርዓት ተጋብተው ይሆናል፡፡ ከዚያስ? ነው ጥያቄው፡፡ የኛስ ሠርግ ጉ-ድ የተባለ አልነበረም፡፡ እስካሁን ድረስ የእኔና የአንቺን ሠርግ እንደ ትንግርት የሚያወሩት አሉኮ፡፡ ከሠርጉ በኋላ የሆንነውን ስለማያውቁ፡፡

አንድ ወዳጄ ትዳርና ችግኝ አንድ ነው ብሎኛል፡፡ ሁለቱም ክብካቤ ይፈልጋሉ፡፤ ሁለቱም በየጊዜው መኮትኮትና ማሳደግን ይጠይቃሉ፡፡ ሁለቱም መከርከምና ድንጋይና አረሙን እንዲያስወግዱላቸው ይፈልጋሉ፡፡ ሁለቱም የዕለት ተዕለት ትኩረት ይሻሉ፡፡ እኛ ግን እንደዚያ ያደረግን አይመስለኝም፡፡ ጉልበታችን ሁሉ ለሠርጉ ፈሰሰና ትዳሩ ላይ አቅም ጠፋ፡፡ ‹‹ዳገት ላይ ሰው ጠፋ›› አሉ ፕሮፌሰር መስፍን፡፡ ድሮ ልጆች ሆነን

ገንዘባችን ሁሉ አለቀ በሻይ

ሚስት ሳናገባ ዓለምን ሳናይ – እንል ነበር፡፡ ከየት የመጣ ግጥም እንደሆነ እንጃ፡፡ የኛም ጉልበታችንና ዐቅማችን ሁሉ ሠርጋችን ላይ ፈሰሰና ‹ዓለምን ሳናይ› ቀረን፡፡ ይገርምሻል፡፡ በቴሌቭዥን ሰሞኑን የችግኝ ተከላ ዜና ሲነገር ትዝ የሚለኝ የእኔና የአንቺ ትዳር ነው፡፡ ድሮ በሠፈራችን በሚገኝ ጋራ ላይ ሰኔ በመጣ ቁጥር በቀበሌ ትእዛዝ እየወጣን የምንተክለው ችግኝ ነበር፡፡ ከተከልነው በኋላ ግን ዞር ብሎ የሚያየው የለም፡፡ ሰኔና ሰኞ የገጠመለት  ችግኝ ይጸድቃል፡፡ ሌላው ግን ደርቆ ይቀራል፡፡ ቀበሌውም ማስተከል እንጂ ማሳደግ አያውቅበትም፡፡ የብዙዎቻችን ትዳር እንደዚያ ይመስለኛል፡፡ ልክ አንድ አገር ሰው ተሰብስቦ ችግኝ እንደሚተክለው ሁሉ አንድ አገር ሰው ተሰብስቦ ትዳር የሚባለውን ችግኝ የሠርግ ቀን ይተክለዋል፡፡ ችግኙን ማንም ዞር ብሎ እንደማያየው ሁሉ ትዳርን የሚከባከበው፣ ውኃ የሚያጠጣው፣ አረም የሚነቅልለት፣ አፈር የሚያደርግለት፣ ፋንድያ የሚደፋለት፣ አውሬ እንዳያበላሸው አጥር የሚቀጥርለት የለም፡፡ ልክ ያደለው ችግኝ በዕድል አድጎ እንደሚገኘው ሁሉ፣ ያደለው ትዳርም አድጎ ተመንድጎ እናየው ይሆናል፡፡ ‹‹አፍራ ያለው ተኝቶም ያፈራል›› ይባል የለ፡፡ ብዙ ትዳሮች ግን እንደ ብዙዎቹ ችግኞች ከስመው ቀርተዋል፡፡

እኔማ አንዳንዴ ‹ለሠርጋችን ከተጨነቅነው ግማሹን እንኳን ለትዳራችን አድርገነው ቢሆን ኖሮ እንደዚህ ባልሆንን ነበር› እላለሁ፡፡ እንዴው ብቻዬን ስለሆንኩ ሰው አያየኝም እንጂ፣ ያበድኩኮ ነው የምመስለው፡፡ ብቻዬን እስቃለሁ፤ ብቻዬንም አወራለሁ፡፡ ባለፉት ዓመታት ያወራናቸውን ሳስባቸው ስለ ቤት ወጭ፣ ስለ ልጆች ትምህርት ቤት፣ ስለ ወላጆቻችን፣ ስለ ጎረቤቶቻችን፣ ስለ ልቅሶና ሠርግ፣ ስለ ርዳታና መዋጮ፣ ስለ መኪናና የቤት ዕቃ፣ ስለ ሥራ ቦታ ችግሮች ሆነው አገኛቸዋለሁ፡፡ እነዚህ ነገሮች ግን ብቻ እንዴት ትዳርን ያሳድጉታል? እንዴትስ ፍሬያማ ያደርጉታል? ስለ እኔና ስለ አንቺ፣ ስለምትወጅውና ስለምትጠይው፣ ስለምንጨምረውና ስለምናርመው፣ አንቺን ይበልጥ ስለማስደሰትና እኔን ይበልጥ ስለማርካት፣ እኔ ላንቺ ማድረግ ስላለብኝና አንቺ ለእኔ ማድረግ ስላለብሽ ነገር ማውራታችንን፣ መወሰናችንንም አላስታውስም፡፡

ደግሞ የሚገርምሽ ነገር፤ ዛሬ ዛሬ ሳስበው ግርም የሚለኝ፣ የምንነጋገረውኮ በሚያጋጥሙን ነገሮች ላይ ብቻ ነው፡፡ አንዳች ነገር ካልገጠመን አንነጋገርም፡፡ ለነገሩማ በዝምታ አድገን እንዴት መነጋገር እንልመድ ብለሽ ነው፡፡ ‹‹ጥፋቱስ አይደለም ካንቺ ወይም  ከእኔ፣

ፍቅር በመሆኑ እንጂ ጽድቅና ኩነኔ፣

አንቺ አንቺን መሆንሽ እኔ እኔን መሆኔ››

አሉ አብዬ መንግሥቱ እውነታቸውን ነው፡፡ እንዴው ጊዜ ወስደን፣ ከሌላው ነገር ወጣ ብለን፣ እየተዝናናንም ቢሉ ወይም ለራሳችን ጊዜ ሰጥተን ስለ ወደፊት ኑሮአችን፣ ስለ እኔና አንቺ ጉዳይ፣ ልናደርገው ስለምንፈልገው ነገር ወይም መሆን ስለምንሻው ጉዳይ አውርተን እናውቃለን ብለሽ ነው? እንዴው ሊመጣልኝ አልቻለም፡፡ አንድ ነገር ይገጥመናል፣ በዚያ ላይ እናወራለን፣ ጉዳዩ ከእኔ ወይንም ካንቺ ጋር ይገናኝና አንዳችን አጥቂ ሌላችን ተከላካይ እንሆናለን፡፡ ከዚያማ ‹‹ጨሰ አቧራው ጨሰ›› ማለት ያኔ ነው፡፡ ግን ለመሆኑ ይህንን ‹‹ጨሰ አቧራው ጨሰ›› የሚል የሠርግ ዘፈን ያመጣው ማነው? መቼም እንደኔ አግብቶ የፈታ ሰው መሆን አለበት፡፡

በተለይማ ልጆች ከመጡ በኋላ ባሰብን፡፡ እኔም ባልሽ መሆኔ ቀርቶ የልጆችሽ አባት ሆንኩ፤ እንቺም ሚስቴ መሆንሽ ቀርቶ የልጆቼ እናት ሆንሽ፡፡ ለመሆኑ ግን ከኛ የሚተርፈንን ጊዜ ነው ለልጆች መስጠት ያለብን ወይስ ከልጆች የሚተርፈውን ጊዜ ነበር እኛ መውሰድ የነበረብን? ለመሆኑ በትዳር ውስጥ ዋናው ጉዳይ ምንድን ነው? ‹ባለቤቴ› የሚለውን ባሕላዊ አጠራር የወደድኩትም ያደነቅኩትም አሁን ነው፡፡ ለምን መሰለሽ? በቀጣዩ ደብዳቤዬ እነግርሻለሁ፡፡

ብንጣላም፣ ብንለያይም፣ ባንግባባም፣ ግን ደኅና ሁኚ፡፡

ያንቺው የቀድሞ ባለቤት

(ሳምንት ይቀጥላል)

 © ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው

በ፲፱፻፹፯ ዓ.ም. ዳግመኛ ከተከፈተ ወዲህ የተመረቁት ደቀ መዛሙርት ብዛት 2175 ደርሷል የተቋማዊ ነፃነት ዕጦትና የበጀት እጥረት ‹‹ጥናትና ምርምር ላይ እንዳላተኩር አድርጎኛል፡፡›› መሠረቱ የወጣው ሕንፃ ሥራ እንዲቆም በጀቱም እንዲመለስ የተላለፈው ትእዛዝ አወዛግቧል ወደ ዩኒቪርስቲ ደረጃ የማሸጋገሩ ሒደት በግንባታ ላይ የሚገኘውን ሕንፃ መጠናቀቅ ይጠብቃል ‹‹ከዛሬው ደስታችኹ የሚበልጥ ደስታ ከፊታችኹ ስለተዘጋጀ ደስታችኹ ዕጥፍ ድርብ ነው፡፡›› /ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ/ …

ሐምሌ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአገር ውስጥ እና በውጭ ከፍተኛ ጫና የተፈጠረበት የኢህአዴግ መንግስት የአቶ አንዳርጋቸውን ምስል በቴሌቪዥን ካቀረበ በሁዋላ የተለያዩ አስተያየቶች በማህበራዊ የመገናኛ መንገዶችና በስልክ እየተሰጡ ነው።አብዛኛው አስተያየት ሰጪ በቴሌቪዥን የቀረበው ምስልና ድምጽ መቆራረጡን ፣ ኢቲቪን የሚያክል ድርጅት ጥራት ያለው  ቀረጻ ለማካሄድ አለመቻሉ ገዢው ፓርቲ ለፕሮፓጋንዳ የሚሆን ነገር ለማግኘት አለመቻሉን ገልጸዋል። ሚኒሊክ ሳልሳዊ  …

ሐምሌ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት ከአገር ቤት በተከታታይ የሚደወሉ ስልኮችን ለማስተናገድ ከአቅሙ በላይ እንደሆነበት እየገለጸ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ደዋዮች አቶ ለአቶ አንዳርጋቸው ያላቸውን ከበሬታ የሚገልጹና ኢህአዴግን በሃይል ለማንበርከክ የሚታገሉትን ቡድኖች ለመቀላቀል እንዴት እንደሚቻል የሚጠይቁ ናቸው። በሌላ ዜና ደግሞ የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የተፈጸመውን የአፈና ተግባር አውግዟል። ትህዴን ” የወያኔ አምባገነን …

ሐምሌ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢህአዴግ  የጸጥታ  ሃይሎች  የአንድነት ፓርቲን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ  የሆነውን ወጣት ሃብታሙ  አያሌውን ፣  የፓርቲውን  የድርጅት ጉዳይ  ምክትል  ሃላፊ  አቶ  ዳንኤል ሽበሺ፣ የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ የሆነውን የሽዋስ አሰፋን እንዲሁም በማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን ከመቀሌ በመጻፍ የሚታወቀውና አረና ፓርቲ አባል የሆነው  መምህር አአብራሃ ደስታን ይዞ አስሯል። እሰረኞቸ ማእከላዊ በሚባለው …