የአፍጋኒስታኑ የቀድሞ የገንዘብ ሚኒስትር አሽራፍ ጋኒና የቀድሞዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱላህ አብዱላህ ምንም እንኳን ሁለቱ ተፎካካሪዎች ስለምርጫዉ ዉጤትና ስለወደፊት የስልጣን ክፍፍል ሲወዛገቡ ቢቆዩም በመጨረሻ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ለመመስረት ተስማምተዋል። ይህ ለአፍጋኒስታን የስልጣን ፉክክር መጨረሻ ይሆን ይሆን?

ከአምስት ወራት ገደማ በፊት የተመረቀው የአዳማ አዲስ አበባ የፍጥነት መንገድ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ አንድ ሳምንት ሆነው። አዲሱ መንገድ የባለአሽከርካሪዎችን ጊዜ መቆጠብ ማስቻሉንተገልጋዮች በደስታ ገልጸዋል።

ደራሲ – እንዳለ ጌታ ከበደ

ዋጋ – 49 ብር

አታሚ – ኤች ዋይ ማተሚያ ቤት

እንዳለ ጌታ የጻፈውን እምቢታ መጽሐፍ ከአዲስ አበባ ወደ አውስትራልያ እየተጓዝኩ አውሮፕላን ውስጥ ነው ያነበብኩት፡፡ መጽሐፉ ለገበያ ሲቀርብ እንደማልኖር ስላወቀ ቀድሜ እንዳገኘው በማድረጉ አመሰግነዋለሁ፡፡ ይኼ በታሪክና በሥነ ቃል(ፎክሎር) ላይ የተመሠረተ ልቦለድ በአንዲት ብዙዎቻችን በማናውቃት ከዘመን የቀደመች ሴት ጀግና ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡

ቃቄ ወርድወት ትባላለች፡፡ በነገራችን ላይ ቃቄ የአባቷ ስም ነው፡፡ የእርሷ ስም ወርድወት ነው፡፡ በጉራጌ ባሕል የአባትን ስም ከልጅ የሚያስቀድም ጥንታዊ ሥርዓት ነበረ ማለት ነው፡፡ ምናልባትም በዕውቀቱ ስዩም ‹በኢትዮጵያ ከልጅ ስም በፊት የአባት እንደሚቀድም ማስረጃ አለኝ› ያለው አንዱ ይኼንን ሳይሆን አይቀርም ብዬ ገምቻለሁ፡፡ የመጽሐፉን ረቂቅ መመልከቱን መግቢያው ላይ ያሳያልና፡፡

ቃቄ ወርድወት በ1840ዎቹ አካባቢ ከጉራጌ ማኅበረሰብ የፈነጠቀች ኢትዮጵያዊት ኮከብ ነበረች፡፡ በሴቶች ላይ የነበረውን አድሏዊ ልማዳዊ ሥርዓት ለመታገል፣ በጋብቻ ሥርዓት ወንዶቹ ከሴቶቹ ይልቅ ሥልጣን ለማደላደል፤ ሴቶች ከለፉበት ትዳራቸው ያለ አንዳች ንብረት በፍቺ መባረራቸውን ለማስቀረት የታገለች ጀግና፡፡ ዛሬ እንኳን ለብዙ ኢትዮጵያውያን ሴቶች አስቸጋሪ የሆነውን ‹ሴት ልጅ ተመርጣ ብቻ ሳይሆን መርጣም ማግባት አለባት› የሚለውን ሐሳብ ይዛ የታገለች፤ ታግላም በራሷ ላይ የፈጸመች ጀግና ሴት ናት፡፡

በዚያ የሴቶች መብት፣ የጾታ እኩልነት የሚሉ ዘመናዊ ሐሳቦች ባልዳበሩበት፤ ለሴቶች መብት ቆመናል የሚሉ ተቋማት ባልነበሩበት ዘመን ከዘመኗ ቀድማ ችግሩን የተረዳች፤ የሴቶችን ችግር ለመቅረፍና እናቶቻችን ፍትሕ እንዲያገኙ ለማድረግ በጉራጌ ማኅበረሰብ ባሕል ከፍተኛው ሸንጎ እስከሆነው ኧጆካ አደባባይ ድረስ የተሟገተች ጀግና ናት፡፡

እንዳለ ጌታ የዚህችን የማናውቃትን ጀግናችንን የተጋድሎ ታሪክ ከልዩ ልዩ ምንጮች ሰብስቦ፣ ሥነ ቃሉን አስማምቶ፣ ከሀገራችን ታሪካዊ መዛግብት ጋር አዋሕዶ በልቦለድ መልክ አቅርቦልናል፡፡ ወጥ ልቦለዶች እያነሡ፣ የትርጉም ሥራዎች ቦታችንን እየወሰዱ ባሉበት ዘመን የራሳችንን ታሪክ መልሰን እንድናይ የሚያደርግ እንዲህ ያለውን ሥራ ማግኘት ለሥነ ጽሑፋችን አንድ እመርታ ነው፡፡

ሰው የሚያውቀውን ሲያቀርብ፣ የሚያቀርበውንም ሲያውቅ ደስ ይላል፡፡ የኖረበትን፣ የተሠራበትንና የተዋሐደውን ነገር ሲተርክ ከውስጡ ስለሚመነጭ ከዛፍ ሥር የሚመነጭን ውኃ እንደመጠጣት ይቆጠራል፡፡ አንድን ማኅበረሰብ በዕንግዳ ዓይን ማየት ተለምዶ የሚመስሉትን ነገሮች በሚገባ ለማንጠር ይረዳል፡፡ የውስጡ ሰው ለምዶት የሚያልፈውን ዕንግዳ ሰው ትኩረት ይሰጠዋል፡፡ አንድን ማኅበረሰብ በውስጥ ሰው ማየት ደግሞ የሚያውቁትን፣ የኖሩበትንና ትርጉሙንም በሚገባ የሚያውቁትን ነገር እንደ ልብ ምት አዳምጦ ለማቅረብ ይረዳል፡፡ የቃቄ ወርድወት ታሪክ እንዲህ ሆኖ ነው የቀረበው፡፡ ማኅበረሰቡ የተሰፋበትን እያንዳንዷን ሰበዝ ታዩበታላችሁ፡፤ ያውም ሳይታወቃችሁ፡፡

የእንዳለ ጌታ መጽሐፍም የኖረበትንና ያጠናውን ማኅበረሰብ ያቀረበበት ስለሆነ ሁለት መቶ ዓመታትን ተሻግራችሁ ትነጉዱና ከቃቄ ወርድወት ጋር ለመብት ትታገላላችሁ፣ ጉራጌ ገብታችሁ ደመራ ታበራላችሁ፣ መስቀል ታከብራላችሁ፣ ክትፎ ትበላላችሁ፣ ከነገሥታቱና መኳንንቱ ጋር ትዋጋላችሁ፡፡ ኧጆካ ትወጣላችሁ፣ ጀፎረ ላይ ትቀመጣላችሁ፡፡

በጉራጌ ማኅበረሰብና በማዕከላዊው መንግሥት መካከል፣ በጉራጌ ማኅበረሰብና በሌሎች የአካባቢው ማኅበረሰቦች መካከል ፍቅርም፣ ጠብም፣ ጦርነትም፣ ዕርቅም ነበረ፡፡ እነዚህ ግንኙነቶች በማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጥሩትን አሉታዊና አዎንታዊ ነገሮች በእንዳለ ጌታ ዓይን ስናያቸው አንድን ታላቅ ማኅበረሰብ በመፍጠር ሂደት ውስጥ የተከናወኑ የሂደቱ መገለጫዎች እንጂ የቂም መቋጠሪያዎች ሆነው አናገኛቸውም፡፡ በአንድ ቤተሰብ ውስጥ በሚገኙ ልጆች መካከል የሚኖር መጣላትና መዋደድ የልጆቹ የዕድገታቸው ሂደት አካል እንደሚሆነው ማለት ነው፡፡

በየአካባቢው የሚገኘውና የማናውቀው ታሪካችንና ባሕላችን እንዲህ ለነገዋ ሀገራችን መቀመሚያ በሚሆን፣ ያለፈውንም ለማወቂያና ለማረሚያ በሚያገለግል፣ በሌላ በኩል ደግሞ አቃፊ እንጂ አግላይ ባልሆነ መንገድ ቢቀርብልን የአንዱ አካባቢ ታሪክ የሁላችንም እየሆነ ‹የኢትዮጵያ› ስንል የሚጎድለን አይኖርም ነበር፡፡ አሁን አሁን ግን ‹የኢትዮጵያ› ስንል የሚጎድሉን ነገሮች አሉ፡፡ አንድም አንዳንዶች ‹የኼማ የራሳችን ብቻ ነው› ብለው ቆርጠው በማስቀረታቸው፣ አንድም ደግሞ ‹የኢትዮጵያ› የተባለው ነገር አንዳንዶችን አግልሎ በማስቀረቱ፡፡ ሁለቱም ግን እኩል ነው የሚጎዱት፡፡ የጉራጌ ክትፎ የሁላችንም እንደሆነው ሁሉ የየአካባቢው ሥነ ቃል፣ ታሪክ፣ ባሕልና ቅርስ እየወጣ የሁላችንም እየሆነ መሄድና ወደ ዋናው አካል እየተቀለቀለ፣ ለዋናው አካል ግንባታም አስተዋጽዖ እያደረገ መሄድ አለበት፡፡ ማግለልም መገለልም አንድ ናቸው፡፡

የአካባቢውን ሥነ ቃል፣ ታሪክና ባሕል ከምናገኝባቸውና የራሳችን ከምናደርግባቸው መንገዶች አንዱ ኪነ ጥበባዊ በሆነ መንገድ ማግኘታችን ነው፡፡ ‹የእገሌ ብሔረሰብ ታሪክና ባሕል› እየተባሉ ብቻ የሚወጡ፣ ሲጀምሩ ሌላውን አውግዘው፣ ኮንነውና ጠልተው የሚነሡ ‹መጻሕፍት› አጥሩን በአደገኛ አጥር ከማጠናከር ያለፈ ፋይዳ አይኖራቸውም፡፡ ቁስሉን ማሳየት እንጂ ማሻርም አይፈልጉም፡፡ ምናልባትም የጉዳዩ ባለቤት ነኝ ብሎ ከሚያስበው አካል በቀር የሌላውን ልብ ለመማረክም አይችሉም፡፡ ጎጣዊ ጀግና ከመፍጠር ባለፈ ሀገራዊ ጀግና አያስገኙም፡፡ በላይ ዘለቀን የጎጃም፣ ዐፄ ዮሐንስን የትግሬ፣ ቃቄ ወርድወትን የጉራጌ ብቻ አድርገው ለማስቀረት የሚያልሙ ናቸው፡፡

ኢትዮጵያዊ ጀግና፣ ሀገራዊ ታሪክ፣ ሀገራዊም ማንነት ሊፈጠር የሚችለው እንዲህ የአንዱ አካባቢ ታሪክ የሌላው እንዲሆን አድርጎ በማቅረብና ለታሪኩና ሥነ ቃሉ ብቻ ሳይሆን ለአቀራረቡም ጭምር በመጨነቅ ነው፡፡ ‹ሲያዩት ያላመረ ሲበሉት ያቅራል› ይባል የለ፡፡ የእንዳለ ጌታን መጽሐፍ አንብቡት የምላችሁም ለዚህ ነው፡፡ በሞቴ አንብቡት፡፡  

ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

መግቢያ

ለአዘማሪ ሙያ ተስማሚ የግብር መግለጫ መሆን ያለበት የቱ ነው? አዘማሪ ወይስ አርቲስት? በሚል በአቶ ዓለም ነጻነት ሬድዮ የቀረበው ውይይት ለዚህች ጦማር መነሻ ሆኖኛል። ከቀደሙ አባቶች እንደሰማሁት አዘማሪ ብቻውን የቆመ አይደለም። ከብዙ ነገሮች ጋራ ከቅኔያችን፣ ከዜማችንና ከስሜታችን ጋራ የተያያዘ ነው። አዘማሪ የሚለውን ቃል ከነዚህ ነጥሎ ለማቅረብ መሞከር ያዘማሪን ክብርና ቦታ ዝቅ ያደርገዋል የሚል ስጋት አለኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ወንድሙ መኰንን

የለንደኖቹልማታዊካኅናትወያኔያዊዘጋቢፊልምአቀናበሩብን!

ኢንግላንድ መከረም ፯ቀን ፪፲፻፯ ዓ.ም

መግቢያ

እንኳን ለአዲሱ ዓመት አደረሳችሁ። መባል ስላለበት ነው። ያለፈውማ ዓመትአንደኛውን ጥቁር ዓመት ተብሏል። ሲያንሰው ነው። ወያኔ ከመቼው በበለጠ ጥቃቷን በኢትዮጵያ ልጆች ላይ በሁሉም አቅጣጫ ያጧጧፈችበት ዓመት ነበር። ነጻውን መገናኛ ብዙሀን ከጨዋታ ውጪ አድርጋለች። ብዙ ጋዜጠኞች በማሠሯ ወህኔ ቤቱ ጠቧል መሰለኝ፣ አሁን አሁን የያዘችው ዜዴ፣ በቁጥጥሯ ሥር ከሌሉ፣የፋሺን ጋዜጠኞችም ሳይቀሩ ማዘዣ ሳይደርሳቸው፣ በሬዲዮዋና በጋዜጦቿ “ከስሼአቸዋለሁ!” በማለት ፣ ነጭ ሽብር እየነዛችባቸው በርግገው ከአገር እንዲጠፉ ማሳደዷን በሰፊው ተያይዛቸዋለች።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የአይሲል ( Islamic State of Iraq and the Levant – ISIL ) እንቅስቃሴ ከሰማይ ዱብ ያለ አዲስ ክስተት አይደለም። አይሲል ( አንዳንዶቹ ISIS ይሉታል – Islamic State of Iraq and Syria ) በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው የፖለቲካ ውጥንቅጥ ሀቅ ውጤት ነው። ለአነሳሱ፣ ለዕድገቱና ለሂደቱ ብዙ ነባሪ ምክንያቶች አሉት። በርግጥ የአይሲልን እንቅስቃሴ ከሀይማኖትና ከዘይት ሀብት ለይቶ ማየት […]

ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ

                                                       
—-

 እነሆ ነፍስ የሆነውን አርቲስት ልናነሳው ወደድን!! ተወዳጅ፣ ጥበበኛ፣ ባለ ተሰጥኦ ከያኒ!! እውነተኛ የሙዚቃ ቀማሪ! ሱዳን ያፈራችው የምንጊዜም ጌጥ!! ከካይሮ እስከ ዑጋንዳ፣ ከጅቡቲ እስከ ማሊ ምንጊዜም እንደተወደደ ያለ የጥበብ ዋርካ!! ሙሐመድ ወርዲ!!

  “ወርዲ” ማለት ለሱዳኖች ንጉሥ እንደማለት ነው፡፡ እኛም ከአንጋፋ አርቲስቶቻችን ነጥለን አናየውም፡፡ በድሮ ጊዜ ወርዲን በፍቅር ሰምተነዋል፡፡ ዛሬም ወርዲን በመደጋገም እየሰማነው ነው፡፡

*****

ወርዲ ከልቡ ዘፋኝ ነው፡፡ ዘፈኖቹ ከኛ ጋር ከመዛመዳቸው የተነሳ እኛን እኛን ይሸታሉ፡፡ በርካታ ዜማዎቹ እኛ የምንጊዜም ምርጦች አድርገን ለምንወዳቸው ታዋቂ ዘፈኖቻችን መነሻ ለመሆንም በቅተዋል፡፡ ለምሳሌ አንጋፋው ድምጻዊ ጥላሁን ገሠሠ ያዜመውን “አንቺ ከቶ ግድየለሽም”ን ውሰዱት፡፡

አንቺ ከቶ ግድ የለሽም

ስለፍቅር አይገባሽም

ሁሉን ነገር እረስተሽው

ችላ ብለሽ ስለተውሽው

ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ፡፡

አዎን! ዛሬም ድረስ የዚህ ዜማ ተወዳጅነት አልቀነሰም፡፡ ለዚህ ዜማ መሰረቱ የሙሐመድ ወርዲ “አነ ዐርፈክ ያ ፉአዲ” ነው፡፡ ሙሐመድ ወርዲ ዘፈኑን ሲያዜመው እንዲህ ነበር ያለው፡፡

“አነ ዐርፈክ ያ ፉአዲ

ጠል ዐዛበክ ዋ ሱሃዲ

ዋ ሽጃያ አነ ዐዛቢ”

ታዲያ ሙሐመድ ወርዲ የተጫወተውን ዜማ ጋሽ ጥላሁን ወደ አማርኛ የመለሰው እንዲሁ በጋጠወጥነት አይምሰላችሁ፡፡ በነገሩ ውስጥ  የወርዲ ሙሉ ቡራኬ አለበት፡፡ በቀዳማዊ ኃይለሥላሤ ዘመን የካርቱም መንገድ ለኛ አርቲስቶች የውሃ መንገድ ነበረ፡፡ ለሱዳኖችም ከዋዲ ሃልፋ ይልቅ ሸገር ነበር የምትቀርባቸው፡፡ እናም በዚህ ምልልስ መሀል የኛዎቹ አንጋፋዎች (ጥላሁን ገሠሠ፣ ምኒልክ ወስናቸው፣ አለማየሁ እሸቴ፣ ዓሊ ሸቦ፣ ዓሊ ቢራ ወዘተ..) እና የሱዳኖቹ አንጋፋ አርቲስቶች (አሕመድ አል-ሙስጠፋ፣ ሰይድ ኸሊፋ፣ ሙሐመድ ወርዲ፣ አብዱልከሪም አል-ካብሊ፣ አብዱል ዓዚዝ አል-ሙባረክ ወዘተ…) የአንድ ቤተሰብ ልጆች ሆነው ነበር፡፡ ሱዳኖቹ ያዜሙትን የኛዎቹ ወደ አማርኛ፣ ኦሮምኛና ሶማሊኛ እየመለሱ ይጫወቱታል፡፡ የኛንም ዘፈኖች ሱዳኖች በቋንቋቸው እየተረጎሙ ይዘፍኑታል፡፡ አንዳንዴ ዕድል ሲገጥማቸው ሁለቱም ዘፋኞች አንዱን ዜማ በአንድ መድረክ ላይ በየቋንቋቸው ይጫወቱታል፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት ነው እንግዲህ የሙሐመድ ወርዲ “አነ ዐርፈክ ያ ፉአዲ” ወደ አማርኛ የተመለሰው፡፡

አዎን!! እነ ጋሽ ጥላሁን እንደ አሁኖቹ ዘፋኞች (አንዳንዶቹን ማለቴ ነው) የሱዳንና የፈረንጅ ዜማን ወደ አማርኛ እየገለበጡ “የራሴ ድርሰት ነው”  ብለው ሊያሞኙን አይከጅሉም፡፡ ዋናው አርቲስት ባለበት ጭምር እየዘፈኑ ያሳዩትና “እንዴት ነው! አበላሽቼብህ ይሆን?” በማለት ምክርና እገዛ ይጠይቁታል፡፡ ሱዳናዊው አርቲስትም በሰማው ነገር ላይ የራሱን አስተያየት ይሰጣል፡፡ የኛዎቹም ከሱዳናዊያኑ አርቲስቶች የሚሰጣቸውን አስተያየት ተንተርሰው እጅግ የተሻለ ስራ ይሰሩና ህዝቡን እንካችሁ ይሉታል፡፡ ለዚያም ነበር ስራው የሚዋጣላቸውና ዘመን ተሻጋሪ የሚሆንላቸው፡፡

በዚህ ስሌት ወደኛ ቋንቋዎች ከተቀየሩት ተወዳጅ የሱዳን ዜማዎች መካከል የጥላሁን ገሠሠ “እዩዋት ስትናፍቀኝ” (ሰይድ ኸሊፋና ኢብራሂም አውድ በጋራ ከዘፈኑት ዘፈን የተወሰደ)፣ የአሰፋ አባተ “ሸግዬ ሸጊቱ” (ከአሕመድ አል-ሙስጠፋ “ሐቢቢ በኪቱ” የተወሰደ)፣ የምንሊክ ወስናቸው “ስኳር” (ከአብዱልከሪም አል-ካብሊ “ሱከር” የተወሰደ) የዓሊ ቢራ “ኦፊ ረፋ ቡልታ” (ከሙሐመድ ወርዲ “ያ ኑረል-ዐይን” የተወሰደ) ይጠቀሳሉ፡፡

                                                                          *****

    በርካታ የሀገራችን የሙዚቃ ወዳጆች ከመሐመድ ወርዲ ዜማዎች መካከል ለ“ገመር ቦባ” እና ለ“ቲስዐተ ዐሸር ሰና” (ብዙዎች የሚያውቁት  “ሰበርታ” በሚለው ስም ነው) ልዩ ፍቅር አላቸው፡፡ ሆኖም ሱዳኖች በአንደኛ ደረጃ የሚያሰልፏቸው ሌሎች በርካታ የወርዲ ዜማዎች አሉ፡፡ በተለይም “ሱድፋ”፣ “ቃሲ ቀልበክ”፣ “አልሀወል አወል”፣ “አነ ማ በንሳክ”፣  “አንናስ አል-ጊያፋ”፣ “ሐረምተ አድ-ዱንያ”፣ “ያ ኑረል ዐይን”፣ “ሸተል ዘማ”፣ “አል-ሙርሳል” የመሳሰሉት ከምርጥ የወርዲ ዜማዎች መካከል ይሰለፋሉ፡፡ እኔ በግሌ በጣም ከምወዳቸው የሱዳን ዜማዎች መካከልም አንዱ የሙሐመድ ወርዲ “አዚብኒ ወተፈነን” ነው፡፡

ዐዚብኒ ወዚድ ዐዘባ ዩምኪን ገልቢ ይግሳዚይክ

ዜይመን ሳኒ ገልበክ ዩምኪን ገልቢ ይግሳዚክ፡፡

አዚብኒ ወተፈነን ፊ አልዋን ዐዛቢ

ማ ቲምሳሕ ዲሙዒ ማ ቲርሐም ሸባቢ፡፡
ኸሊኒ ፊሹጁኒ ዩምኪን ገልቢ ይክሳዚይክ

ዜይ መንሳኒ ገልበክ ዩምኪን ገልቢ ይክሳዚይክ፡፡

ወርዲ በዚህ ዘፈን ለወዳጁ “ልብሽ ጨክኖብኝ ፍቅርሽ አቃጥሎ እየጨረሰኝ ነው፤ መጥተሸ እምባዬን የማታብሺልኝ ልበ-ደረቅ ነሽ” የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ ነው የፈለገው፡፡ ወርዲ ይህንን ዜማ የዛሬ 20 ዓመት ገደማ በአዲስ አበባ ስታዲየም እጅግ ባማረ ሁኔታ የተጫወተው ሲሆን የሀገራችን አድናቂዎችም በጋለ ስሜት ተቀብለውታል ( ቪዲዮውን በሚከተለው ሊንክ ላይ ተመልከቱት፡፡  https://www.youtube.com/watch?v=WkegFEEwjjM&feature=related

                                                                          *****

ታዲያ የወርዲ ፍቅረኛ በ“አዚብኒ-ወተፈነን” ውስጥ እንደተገለጸው በጭካኔዋ አልዘለቀችም፡፡ ወርዲ በጉንጮቹ ላይ የሚያፈሰው እምባ አሳዝኖአት ከፍቅር በረከቱ ልታቀምሰው መጥታለታለች፡፡ ወርዲም ፍቅረኛውን ያገኘበትን ቀን “የቀኖች ሁሉ ረጢብ፣ እጅግ በጣም ገዳም፣ የምኞቴን ያሳካሁበት ቀን መጥቶልኛል” በማለት ገልጾታል፡፡

“ሱድፋ” የሚለውን የሙሐመድ ወርዲን ዘፈን እናውቀው የለ?.. በዚያ ዘፈን ውስጥ ወርዲ ለወዳጁ ያለውን ፍቅር ብቻ ሳይሆን ከናፈቁት ወዳጅ ጋር መገናኘቱ የሚሰጠውን ደስታ በተዋቡ ቃላት ገልጾታል፡፡ እኔ በበኩሌ እጅግ በጣም የምወደው የወርዲ ዘፈን ይኸው ሱድፋ ነው፡፡ እነሆ የሱድፋን ሙሉ ግጥም ተጋበዙልኝ፡

ሱድፋ… ሱድፋ

ሱድፈ ወ አጅመል ሱድፈነ የውም ላቄታ

አስዓድ የውም የውሚል ሐዬታ

ኑረ ዐይነያ አያም ሓቤታ

ይህ አዝማቹ ነው እንግዲህ፡፡ “ሱድፋ” ማለት አስገራሚ ዕድል ማለት ነው (በእንግሊዝኛ fortunate የሚለው ቃል ይቀርበዋል)፡፡ ተከታዮቹ ግጥሞች የሚከተሉት ናቸው፡፡

አን-ነዘራት በሪዓ ገመም ዘውፍጀል ኸጀል

አልበሰማት ተበዊ ዘይ ኑረል ዐመል

ወጅሂክ ቤን መዛህሪክ ዘይ በድሪ-ክ-ከመል

ወሽሻመክ ኺዴድክ ዘይ ጠዕመል ኹበል

ተስኪር ገልቢ

ወተሽዒል ሑቢ

ኢሽሀክ ረብቢ

አነ በህ ዋ

—–

ማ ቃዲር አጉል ሊክ አን ሑብቢል ከቢር

ወስፉ ዓለይያ ቃሲ መዓዪሽ ፊ-ድ-ደሚር

ቀድረል ከውን ተኩልሉሁ አክበር ቤ ከቲር

ማሊክኒ ሙሐዪይርኒ ሹፍከል ቢል ኣሲር

አስአሊ ቀልቢ

ኢኪኒ ዪቅደር

ኢሽራሕ ሑቢ

አነ ሙሕታር

——

ሱድፈ ዑዩኑ ሻፈክ ሌይሊ ባቂ ይነዊር

ያ አይያም ረቢዒ ዑምሪ መዓኪ አዝሐር

ፊሃ አጥ-ጤይር ይገኒ ሚን አል-ሓኒ ዪዝከር

ቀልቢ ፈራሸ ሐውሊ ወኢንቲ ሸባቢከ አኽደር

ያ መበሒብቢ

ባዕቡድ ሑብቢክ

አለሻን ሑብቢክ

ሩሒ ፈዳክ

*****

ለመሆኑ መሐመድ ወርዲ ማን ነው?

  ሙሉ ስሙ ሙሐመድ ዑስማን ሳሊሕ ወርዲ ነው፡፡ እርሱ ግን “ሙሐመድ ወርዲ” ወይንም በአጭሩ በቤተሰቡ ስም “ወርዲ” ተብሎ ነው የሚታወቀው፡፡ የተወለደው እ.ኤ.አ. በ1932 “ዋዲ ሀልፋ” በተሰኘው ሰሜናዊው የሱዳን ክፍለ ሀገር፣ “ሱወርዳ” በተባለች ትንሽዬ የገጠር መንደር ውስጥ ነው፡፡ እናቱ የኑቢያ ተወላጅ ስትሆን አባቱ ዐረብ ነው፡፡

ወርዲ የሙት ልጅ ነው፡፡ ሁለቱንም ወላጆቹን በልጅነቱ ነው ያጣው፡፡ በመሆኑም በዘመዶቹ ጥበቃ ስር ሆኖ ነው ያደገው፡፡ ትምህርቱን በዋዲ ሀልፋ እና በካርቱም ተከታትሏል፡፡ የተወለደበትን ሀገር እስከ 1956 በመምህርነት ሙያ ካገለገለ በኋላ በወቅቱ ይሞካክራቸው የነበሩት ዘፈኖች በኦምዱርማን ሬድዮ ጣቢያ ተቀርጸው በመተላለፋቸው በህዝብ ልብ ውስጥ ገባ፡፡ ያገኘው የሞራል ድጋፍ ማነሳሻ ስለሆነው መምህርነቱን ትቶ የአርቲስትነቱን ጎራ ተቀላቀለ፡፡ ከዚያም ሱዳኖች ከሚያፈቅሯቸው ቁንጮ ዘፋኞቻቸው አንዱ ለመሆን በቃ፡፡

 

    ወርዲ በህይወቱ የተረጋጋ ኑሮ አልኖረም፡፡ በሱዳን የተለዋወጡት መንግሥታት በተቃዋሚነት እየፈረጁት አንገላተውታል፡፡ በመሆኑም ለሀያ ዓመታት ያህል በካይሮና በለንደን ነው የኖረው፡፡ በ2002 ግን ወደ ሀገሩ በክብር ተመልሷል፡፡ ወርዲ በሙዚቃው ዕድገት ላደረገው አስተዋጽኦ ከካርቱም ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሸልሟል፡፡ ከልዩ ልዩ የአውሮጳ፣ አፍሪቃና እስያ ሀገራትም ሽልማቶችን ተቀብሏል፡፡

 መሐመድ ወርዲ በመጨረሻዎቹ ዓመታት በደረሰበት የጤና መታወክ ሁለት ኩላሊቶቹ ከጥቅም ውጪ ሆነው ነበር፡፡ ይኸው የኩላሊት ህመም ፋታ ነስቶት በየካቲት ወር 2012 ከዚህች ዓለም አሰናብቶታል፡፡

*****

ከመግቢያዬ እንደገለጽኩት የሀገራችን የሙዚቃ አፍቃሪዎች በጣም የሚወዱት የመሐመድ ወርዲ ዘፈን “ሰበርታ” ነው፡፡ እኔም “ሱድፋ”ን ከሁሉም እንደማስበልጥ ገልጫለሁ፡፡ በሱዳኖች ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆነው የመሐመድ ወርዲ ዜማ ግን “ገመር ቦባ” ነው፡፡ ሱዳኖች እ.ኤ.አ. በ2000 ባደረጉት ምርጫ “አል-ገመር ቦባ” የተሰኘው ዘፈን የክፍለ ዘመኑ ምርጥ “ነጠላ ዜማ” ተብሎ ተመርጧል፡፡እኔም ገመር ቦባን በድምጽ (ኦድዮ) ልጋብዛችሁና ላብቃ፡፡

ቦባ ዐሌክ ተጊል… ቦባ ዐሌክ ተጊል

አል-ገመር ቦባ ዐሌይክ ተጊል፡፡

አስ-ሰጊሩን አል-ማ-ከቢር

አር-ሪጌበት-ጊዛዛት አሲር

አስኑን በርራጊን የሺል

አል-ዑዩን መሥለል ፈናጂል

ቢንተ-ሱዳን አሲል

ያ ገመር ቦባ ዐሌክ ተጊል፡፡

(ገመር ቦባን በዚህ ሊንክ ላይ ይስሙት https://archive.org/details/MohammedWardi-AlQamarBoeba )

——

አፈንዲ ሙተቂ

መጀመሪያ ታሕሳስ 6/2006 ተጻፈ፡፡

እንደገና ተሻሽሎ መስከረም 9/2007 ተጻፈ፡፡

The writer, Afendi Muteki, is a researcher and author of the ethnography and history of the peoples of East Ethiopia.

 You may like his facebook page and stay in touch with his articles and analysis: Just click this link to go to his facebook page.

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ባለፈው ሳምንት እሑድ በክፍል አንድ ውይይታችን ፣ የገባውን አዲሱን ዘመን 2007 ዓ ም ን መንስዔ በማድረግ፤ በኢትዮጵያ ፣ ከገሐዳዊው ይዞታ ጋር ምኞትና ተስፋ እንዴትና ምን ቢደረግ እውን ሊሆኑ እንደሚችሉ 3 ቱ ተጋባዥ እንግዶቻችን ፣ ከአዲስ ዓመት

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በኬንያ መዲና ናይሮቢ የሚገኘው ዌስትጌት የተባለው ትልቅ የገበያ ማዕከል በአሸባሪዎች ጥቃት ከተሰነዘረበት በነገው ዕለት ልክ አንድ ዓመት ይሞላል። ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደው የሶማልያ አክራሪ ታጣቂ ኃይል ታጣቂዎቹ እአአ መስከረም 21፣ 2013 ዓም ማዕከሉን በማጥቃት ለቀጠሉት አራት ቀናት በመያዝ ሕዝቡን ማሸበራቸው የሚታወስ ነው።

በኬንያ መዲና ናይሮቢ የሚገኘው ዌስትጌት የተባለው ትልቅ የገበያ ማዕከል በአሸባሪዎች ጥቃት ከተሰነዘረበት በነገው ዕለት ልክ አንድ ዓመት ይሞላል። ለጥቃቱ ኃላፊነቱን የወሰደው የሶማልያ አክራሪ ታጣቂ ኃይል ታጣቂዎቹ እአአ መስከረም 21፣ 2013 ዓም ማዕከሉን በማጥቃት ለቀጠሉት አራት ቀናት በመያዝ ሕዝቡን ማሸበራቸው የሚታወስ ነው።

በጄኔቭ የሚገኘዉ የተ.መ የስደተኞች ርዳታ ሰጭ ጉዳይ መሥርያ ቤት እንዳስታወቀዉ፤ በ24 ሰዓታት ዉስጥ ብቻ ወደ 70 ሺ የሚጠጉ ሰዎች ጥገኝነት በመፈለግ ቦታዉ ላይ ደርሰዋል።

በጄኔቭ የሚገኘዉ የተ.መ የስደተኞች ርዳታ ሰጭ ጉዳይ መሥርያ ቤት እንዳስታወቀዉ፤ በ24 ሰዓታት ዉስጥ ብቻ ወደ 70 ሺ የሚጠጉ ሰዎች ጥገኝነት በመፈለግ ቦታዉ ላይ ደርሰዋል።

ቱርክ በሺዎች የሚቆጠሩ እና ከሶርያ የሸሹ ኩርዶች ድንበሯን ተሻግረው እየገቡ መሆኑን አስታወቀች። ከአማፂው አይ ኤስ ቡድን የሸሹ 45 ሺ የሚጠጉ ሰዎች ከዓርብ ዕለት አንስተው የቱርክ -ሶርያን ድንበር አልፈዋል ሲሉ የቱርክ ምክትል ጠ/ሚኒስትር ኑማን ኩርቱልሙስ ለCNN ቱርክ የመገናኛ ብዙኃን ገልጸዋል።

Befekadu Hailu

There was a time in my life when I used to think a lot about revolution in Ethiopia. In fact, in 2011 during the so called ‘Arab Spring’ I wrote a rejoinder article when Ethiopian democracy activists (especially those who are based in diaspora) planned a ‘Day of Rage’ using Facebook and aimed at ending EPRDF’s two-decade authoritarian rule. Just after a year I wrote one more rejoinder titled “Revolution is Ephemeral ’. In this article I tried to highlight what Ethiopians truly lack to launch a genuine social revolution using social media. In these couple of articles it appeared that I went up against proponents of revolution but I was trying to explain the traceable causes and conditions of social revolution. In a nutshell, I was saying that the significant portion of the Ethiopian population, the opposition politicians, and the intellectuals and generally the elite and social ideals and social reality were not sufficiently prepared to kick-start an authentic and organic social change.
Yet again in 2012, I was inspired enough to write a series of articles under a general title ‘Concerning Change’ on our own blog Zone9. In the first of my series of articles titled “Will EPRDF hand over power by means of election?”  I tried to explain why EPRDF will keep on clinging to power. I argued that EPRDF is not yet ready for an electoral democracy. In a bid to demonstrate an alternative yet constitutional means of possible social change such as civil disobedience I wrote further articles as a follow up to my critique and highlighted different elements of social change across a spectrum of societal issues. As much as I can  I tried to kindle genuine public conversations in bringing these issues to the public’s attention through my articles such as ‘Fear and Social Change’ ‘Regime Change and Religion’, ‘The Role of Civil Society in 1974 Ethiopian Revolution’ and “Revolution or Sluggish Change”  It was during this time that I contemplated deeply about revolution. It was one phase of my life in which I have tried to articulate my comprehension of revolution into pieces of writings but it was also a stage of my life in which my belief on revolution was dropped off significantly.  But I have to confess here that my belief on revolution plummeted to its all-time low merely in 2013. Subsequently, I found myself turned into an activist of an organic social change through processes (not a transient revolution) from an avid reader and advocate of revolutionary ideas.  I have to put in plain words that what made me skeptic of transient revolutions; I have to explain at length that how I progressed (say it regress if you like) from being optimistic revolutionary to a proponent of an organic and authentic social change through processes, as the 1960s Ethiopian Marxist revolutionaries put it, what turned me from being ‘Revo’ (revolutionary) to ‘Sabo’ (Saboteur). Please note that I was only an enthusiastic reader of revolutionary ideas.  
  At some stage while I was grappling with the revolutionary ideals of intending to bring fundamental structural change in favor of the mass but unexpectedly might turn to be like unrestrained wildfire which could be destructive; Mohamed Morsi was ousted in Egypt’s second revolution just in two years. The second Egyptian rebellion (revolution) made me feel perplexed about revolutions. But I thought in his short-lived presidency Morsi operated against basic principles of democracy and hence I believed the second revolution was born in resistance to another form of dictatorship. Certainly the second revolution even made me assert “A Conscious public will not be a possession of a despot and Egyptians are a proof”. I genuinely took the idea seriously that Egyptians would thrive in protesting until they get their preferred form of government; just like the 18th century series of French Revolutions which profoundly affected modern history. However, I realized that this is not the case when I observe the Egyptian army suspended the constitution and took control the revolution. In a similar manner of the 1974 Ethiopian Revolution during which the Ethiopian army  hacked the revolution the Egyptian army did the same. After that I even went as far as asking “If Revolutions are inherently similar?” 
In the meantime the Ethiopian social media sphere and the private press spontaneously embarked on entertaining a sort of peculiar conversations. These conversations were prompted by Jawar Mohamed’s public comment on Al Jazeera’s English daily television program called The Stream. On the show when Jawar was pressed by the host of the show what he prefers, flanked by his ethnic and national identity; he declared his ethnicity comes first over his national identity and acknowledged himself as ‘Oromo First’. Many consider the public discussion which followed the Jawar incident as a pointless exercise of talking past each other but I think of this spectacle in a different way.  I consider this incident as one of fascinating things because it really helped many people to re-examine their understanding of Ethiopia’s historical and political phenomenon. For me that incident was an excellent opportunity and serves as an evidence that we need a ground for long-running debates and a continuous scholarship on Ethiopia’s historical and political phenomenon. The spectacle should be an eye opening and insightful opportunity especially for those of us who are a loosely-knit community of dissents, oppositions groups, writers and activists whose organizing purpose is only to triumph over EPRDF. It was an incident that tasked all of us to find a possible way and build a system that can maintain a consensus among opponents. Furthermore, the incident made it clearer than ever that most of us only know what we do not want but we do not clearly know what we really want. To conclude on this, the incident exposed that Ethiopians struggle for democracy is not principled but rather it is based on indignation and grudge.  
As difficult as this issue to contemplate I started to realize the fact that despotic leaders are generally results of broader and yet fundamental societal flaws. For me this was like the aha! moment. So when revolution is conceived in a society with a high degree of authoritarianism, the end result is usually more authoritarianism. I think it comes down to individual elite who appeared liberal and revolutionary from authoritarian society are either concealed  authoritarian themselves or the society is not yet ready to allow  them to exercise their liberty. This is like a classic causality dilemma, which one came first a chicken or the egg.  But I think one should change first and it should be the society. It is with this eureka effect that I tried to revisit the revolutions in the Arab world. Tunisia, Egypt, Libya, and Syria… and I tend to think that the revolutions in these countries have done more harm than good. They caused a great deal of human suffering. Removing a despot does not necessarily guarantee a change. In similar manner the 1974 Ethiopian Revolution which removed HaileSelassie’s rule and replaced with the Dergue, a Marxist military junta is just as bad (If not worse) than the revolutions of the Arab world. It is even worse if we consider the human suffering that was caused by the infighting and power struggle of the political parties of the time. I have watched when the storied Ukraine for its Orange revolution of 2004 back to revolution all over again in 2014. I even tweeted about it ‘to revolution then calmness and back’. The February 2014 Ukrainian revolution culminated (I am not sure if I can say it is culminated) in turning over its own State Crimea to pro-Russian forces even though it appeared the Russian involvement in Ukrainian affairs cited as one of the cause of the revolution. I also wrote a commentary on my personal blog asking Are revolutions meant to be betrayed? ››My point in this particular blog post was showing reasons why elite citizens who usually initiate revolutions would end up in brawl and infighting after they started revolutions. I used the old Amharic saying to illustrate my point ‘Thieves usually do not fight when they steal but they brawl when they divide what they robbed”.  I intentionally used the word ‘thieves’ to illustrate the context of Ethiopian political reality. I am referring to Ethiopian astroturf political originations (formal or informal) that are organized in the name of interest group to bring social change. Beyond their being astroturf in their nature they fight each other. We have numerous such groups and their sole propose is to get hold of political power and harvest the benefits from it not brining genuine revolution.
For this reason I truly believe we can bring change without going through an instantaneous revolution. We can take a good lesson from the history of English people. The English people have a lot of exemplary deeds. Rule of law, discussion and public engagement though grass root organizations can bring the desired form of government and we can also achieve social change peacefully.
An acquaintance of mine who knows my stance of instantaneous social change came to visit me in prison after I was unjustly accused of inciting revolution.  He looked at me and said ” Aha, what did I told you, there will never be a change without revolution’. But remarkably even in the injustices and sufferings me and my zone9 blogging collective colleagues have been through I still see the need for an authentic social change. Had the society have had the consciousness; they would have seen the impunity of the Ethiopian government (police) enjoy and the injustice we are suffering from. Apparently the Ethiopian government does not have the slightest concern for legitimate questions of Ethiopians but rather they are deeply bothered by the ‘noise of foreign powers’.   Suffering the consequence of using the right to freedom of expression has become a social reality because the society sits silently and watches all the injustice. Society should start to speak up against injustice but to do so we should embark on educative and liberating process through grassroots activism and peaceful disobedience which are yet not happened in Ethiopia. Once a society has become conscious of the benefits of liberating social change and developed a test for liberty there is no way back. I believe consciousness comes first then liberty follows. We have failed spectacularly because as a society we havethe cart before the horse in mostof our projects.  That is how explained for my acquaintance who visited me in prison as well. However, as Kiflu Tadesse put it on the first of two volumed books “That Generation” which dealt with the 1974 Ethiopian Revolution Haile Fida one of the iconic figures of the storied Ethiopian Socialist Movement never predicted Ethiopians would revolted just one year ahead of the 1974 Ethiopian Revolution. According to Kiflu, in 1973 Haile said for Ethiopians to start a revolution it would take them a minimum of twenty five years. Unless I blunder like Haile I don’t think there will be a revolution in Ethiopia in the foreseeable future. Finally like the Ethiopian satirist Abebe Tola usually say if I screw-up on this screw me over. 

የምርጫ አመት ነው። ነጻ ጋዜጦጭ በሙሉ ተዘግተዋል። አገዛዙ በሕዝብና በመንግስት ገንዘብ በየተቋማቱና መስሪያ ቤቶች ስብሰባ እየጠራ ፣ በኢቲቪ ህዝቡን የሚያደነቁረው አንሶት፣ እንደገና በስብሰባ ዜጎችን እያደነቆረ ነው። ኢትዮጵያዊያን የዲሞክራሲያዊ እና ሰብአዊ መብታቸው ተረግጦ በግድ ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረጉ ናቸው። አንዳንዶች “ዉሸት ነው። ኢሕአዴግ ለዲሞክራሲ የቆመ ተራማጅ ድርጅት ነው” ሊሉ ይችላሉ። ይችን አብራ የተያያዘቸውን ማስታወቂይ እንዲያነቡ እናበረታታለን። ይህ […]

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የህሊናና የፖለቲካ እስረኞችን በአደባባይ ሻማ ማብራት ፕሮግራም ለማሰብ፣ የአዲስ አበባ አስተዳደርን በደብዳቤ መጠየቁንና የአስተዳደሩ የሕዝባዊ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ለፕሮግራሙ የተመረጠውን ቦታ የተለያዩ ምክንያቶችን በመስጠት ዕውቅና እንደነፈገው ፓርቲው አሳውቋል፡፡ በመሆኑም ድርጊቱ የተለመደ የሕገ-መንግስታዊና የሕግ ጥሰት መሆኑን በመገንዘብ በጥልቀት ተወያይቶበታል፡፡ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ህብረተሰቡን በግዳጅ ስልጠና ወጥሮ በፈለገበት ቦታ ላይ […]

መስከረም ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአካባቢው ምንጮች እንደገለጹት ለቀናት ጋብ ብሎ የቆየው ግጭት ከትናንት ጀምሮ እንደገና አገርሽቷል። የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ጋትሉዋክ ቱት የገዢው ፓርቲ ልሳን ለሆነው ፋና ሬዲዮ ” ኪራይ ሰብሳቢዎችና የመሬት ደላሎች በጠነሰሱት ሴራ ለዘመናት ተቻችሎ የኖረውን ህዝብ ለመከፋፈል ጥረት በማድረጋቸው መስከረም አንድ በሚጤ ከተማ በተፈጠረው ግጭት 13 ሰዎች” መሞታቸውን፣ በገጠር …

መስከረም ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት በመላ አገሪቱ የሚገኙ የትምህርት ተቋማት መስከረም 5 ትምህርት እንዲጀምሩ ቀደም ብሎ ይዞት የነበረውን እቅድ በመሰረዝ አዲሱ የትምህርት ዘመን ከመስከረም 30 በሁዋላ እንዲጀመር ትእዛዝ አስተላልፏል። በትምህርት ሚ/ር ደኤታ ዶ/ር ካባ ኡርጌሳ ዲንሳ ለሁሉም ዩኒቨርስቲዎች መስከረም 5፣ 2007 ዓም የተጻፈው ደብዳቤ   የአንደኛ አመት ወይም አዲስ ገቢ ተማሪዎች ጥሪ ተደርጎ …

መስከረም ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተመድ የሰብአዊ መብት  ኤክስፐርቶች  ኢትዮጵያ  የጸረ ሽብር ህግን  ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ለማፈን እና የማህበራት ነጻነትን ለመጋፋት እየተጠቀመችበት እንደሆነ በመጥቀስ፤ ህጉን አላግባብ መጠቀሙዋን እንድታቆም መጠየቃቸውን-ከጄኔቫ የወጣ መግለጫ ያመለክታል። የተመድ የሰብ ዓዊ መብት ባለሙያዎች አያይሰውም ኢትዮጵያ  በተያሰው ዓመት መጀመሪያ በሰብአዊ መብት ካውንስል አባላት የጸደቀውንና በ 193 ቱም የመንግስታቱ ድርጅት …

መስከረም ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል በቢቸና አውራጃ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ 2 የቀድሞ የቅንጅት አባሎች ተገድለዋል። ገዢው ፓርቲ እንዳደራጀ የሚነገረው ቡችሌ የተባለው ቡድን ክንዳየ አለሙና አባይነህ በተባሉ የቀድሞ የቅንጅት አባላት ላይ ስዋ ወንዝ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ግድያ መፈጸሙን ለማወቅ ተችሎአል። ሁለቱም ሰዎች በተመሳሳይ መንገድ አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ ተደብድበው መሞታቸው ታውቛል። ከ10 …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የዛሬው የወጣቶች ዓለም ዝግጅት የምልክት ቋንቋ ላይ ያተኩራል። ይህንን በተመለከተ ያነጋገርናቸው ሶስት የአካል ጉዳተኛ ያልሆኑ ነገር ግን የምዕልክት ቋንቋን ኢትዮጵያ ውስጥ ተምረው በዚህ ሙያ የተሰማሩ ወጣቶችን ነው።

የፊታችን እሁድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታስቦ የሚዉለዉ «ዓለም አቀፍ የሰላም ዕለት» ዛሪ በአፍሪቃ ሕብረት ታስቦ ዋለ። የተ.መ ተጠሪዎችና ተቀማጭነታ ቸዉ አዲስ አበባ የሆኑ የሕብረቱ አባል ሃገራት አምባሳደሮች ተገኝተዋል።

የታላቅዋ ብሪታንያ አካል ስኮትላንድ ለመገንጠል፤ ወይም በሕብረቱ ታቅፎ ለመቀጠል፤ በቀረበዉ ጥያቄ መሰረት ትናንት ሕዝበ ዉሳኔ ከተካሄደ በኋላ፤ ስኮትላንድ እንዳትገነጠል የሚፈልገዉ ወገን ማሸነፉ ታዉቋል። በድምፅ ቆጠራዉ መሰረት የስኮትላንድን በብሪታንያ ሕብረት መቆየትን የሚሹት 55,3 በመቶ አብላጫ ድምፅን ሲያገኙ፤

በፍቃዱ ዘ ኃይሉ
 

ርዕሱን  አላስታውሰውም ‘ንጂ እ.ኤ.አ በ2011 Arab Uprising በመባል የሚታወሰውን አብዮትተከትሎ፣ ኢትዮጵያውያን ፌስቡከኞችም (በተለይ ዲያስፖራ የሚገኙ) ግንቦት 20 ላይ (ልክ በኢሕአዴግ የ20ኛ አገዛዝ ዕድሜ)   “Anger day” በሚል በፌስቡክ አብዮትመጥራታቸውን ተቃውሜ አንዲት ጽሑፍ ጽፌ ነበር፡፡ በዓመቱ ደግሞ ‹‹ አብዮት ወረት ነው›› በሚል ርዕስ በፌስቡክ አብዮት ለማስነሳት ፍላጎት ያላቸው በርካቶች እንዳሉ ገልጬ ነገር ግን ይጎድላቸዋል የሚባሉትንነገሮች ዘርዝሬ ጽፌ ነበር፡፡ በነዚህ ሁለት ጽሑፎች ላይ፣ ላዩን አብዮትን የተቃወምኩ ቢመስልም እውነታው ግን ጽሑፎቹ በተጻፉበትወቅት ሕዝቡም፣ ተቃዋሚ ልሂቃኑም፣ ሁኔታዎቹም ለአብዮት ዝግጁ አይደሉም የሚል ዝንባሌ ማሳየቱ ነበር፡፡
ከሌላ ዓመት በኋላደግሞ ‹‹ስለለውጥ›› በሚል ርዕስ ተከታታይ ጽሑፎችን በ‹‹ዞን 9›› ላይ በግል ተነሳሽነት ማስፈር ጀምሬ ነበር፡፡ ጽሑፉን የጀመርኩት ‹‹ኢሕአዴግ ሥልጣኑን በምርጫ ይለቃል?›› በሚል ጥያቄ ነበር፡፡ ‹‹አይለቅም›› የምልባቸውን ምክንያቶች ካስቀመጥኩ በኋላ የለውጥ አማራጭ የምላቸውን (አብዮት፣ሰላማዊ አለመታዘዝ /civil disobedience/ የመሳሰሉትን) በየዘርፉ እየቀነጫጨብኩ ለማሳየት ነበር ዓላማዬ ከዚያም ‹‹የለውጥ ፍርሃት››፣ ‹‹የሥርዓት ለውጥ እና ሃይማኖት››፣ ‹‹የ1966ቱ የኢትዮጵያ አብዮት እና የማኅበራት ሚና›› የሚሉ ርዕሶችን በማንሳት በሐሳቦቹ ላይ በሐቀኝነት ለመከራከር ጥረት አድርጌያለሁ (ከዚህ በላይ አልገፋሁበትም እንጂ)፡፡ በበኩሌ ስለአብዮት በደንብ ያነበብኩትም፣ ያሰብኩትም፣ የጻፍኩትም፣ የተረዳሁትም ያኔ ነበር፡፡ ያኔ በአብዮት ላይ የነበረኝ እምነት ተሸርሽሮ ግማሽ ደርሶ ነበር፡፡ ተንጠፍጥፎ ያለቀው ግን አሁንም በዓመቱ (በ2006 አጋማሽ) ነው፡፡ አንባቢ ከአብዮት አድናቂነት ወደ ዝግመተ ለውጥ አራማጅነት (በ ‹‹ያ ትውልድ›› ሰዎች አጠራር ከRevo ወደ Sabo) የተሸጋገርኩበትን የሐሳብ ዳገት (ከፈለጋችሁ ቁልቁለት በሉት) ይረዳ ዘንድ በመጠኑ ዘርዘርአድርጌ ማስረዳት አለብኝ፡፡ (ታዲያ አብዮት አድናቆቱም ቢሆን ከወረቀት እንዳላለፈ ልብ በሉልኝ)፡፡
እነዚያን ተከታታይ ጽሑፎች በጻፍኩበት ሰሞን  ‹አብዮት ‹‹እቆጣጠረዋለሁ›› ብለው ያሰቡትንነገር ግን ድንገት ከቁጥጥር ውጭ ሊሆን የሚችል እሳትን መለኮስ› እንደሆነ እያሰብኩ ባለሁበት ሰሞን ግብጻውያን ሙርሲን ለመጣል ያምጹ ጀመር፡፡ የግብጹ ድጋሚ አመጽ (አብዮት) በጣም የተዘበራረቀ ስሜት ፈጥሮብኝ ነበር፡፡ ሙርሲ እኔ በግሌ ከማምንባቸውና ቋሚም ከሆኑ የዲሞክራሲ መርሆች እያፈነገጠ ነበር፡፡ ስለዚህ የግብጾች ማበይ ምክንያታዊ ነው ብዬ አምኛለሁ፤ እንዲያውም ሕዝብ አንዴ ‹ከነቃ አይሆንም ዕቃ› ብዬ ነበር፡፡ የግብጽ ሕዝብ የሚፈልገውን ዓይነት ሥርዓት እስከሚያገኝ እያበየ ይቀጥላል የሚል ግምት ነበረኝ- ልክ እንደ ፈረንሳዮቹ ተከታታይ አብዮቶች፡፡  ነገር ግን የግብጽ ሕዝብ እያበየ ቢቀጥልም እንኳን የፈለገውን ላያገኝ እንደሚችል የተረዳሁት ወታደራዊ ክንፍ ቀስ በቀስ አገሪቱን በአብዮቱ ተከልሎ ሲጠቀልላት ስመለከት ነበር ፡፡ ከአገራችን የደርግ አመጣጥ አልለይ ብሎኝ ‹አብዮቶች ሁሉ አንድ ናቸው እንዴ?› እስከሚያስብል ድረስ ተመሳስሎብኝም ነበር፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ ማኅበራዊ ሚዲያ እና ፕሬሶች በአንዳች ተዋስኦ ይናጡ ጀመር፡፡ ተዋስኦው የተጀመረው የጃዋር መሐመድን ‹ኦሮሞ ቅድሚያ›(Oromo First) የአልጄዚራ ምላሹን ተከትሎ ነበር፡፡ ብዙዎች ይሄን ወቅት የሚያስታውሱት እንደአላስፈላጊ የንትርክ ወቅት ቢሆንም፣በበኩሌ ብዙዎች ቆም ብለው አቋማቸውን እና የአቋማቸውን መሠረት እንዲፈትሹ፣ በታሪካዊ እና ፖለቲካዊ ኩነቶች ላይ ንባባቸውን እንዲቀጥሉ ያስታወሰ መልካም አጋጣሚ ነው ባይ ነኝ፡፡ ይህ አጋጣሚ በስመ ተቃዋሚ (dissent) የአንድ ኢሕአዴግን ከሥልጣን መውረድ ብቻ እንደ ለውጥ ግብ አድርገን በጋራ ስንንቀሳቀስ የነበርን ተቃዋሚ ግለሰቦች እና ቡድኖች እርስ በርስ ያሉትን ልዩነቶች እና ልዩነቶቻችንን የምናቻችልባቸውን መንገዶች እንድናስተውል መንገድ ፈጥሯል፡፡ ብዙዎቻችን የማንፈልገውን እንጂ የምንፈልገው ምን እንደሆነ በቅጡ እንደማናውቅ፣ትግላችን ከመርሕ ይልቅ በእልሕ እንደሚመራ ያጋለጠ፣ ራሳችንን እንድንገመግም ያስገደደ አጋጣሚ ነበር፡፡

ከዚህ ድንጋጤ ውስጥነው ‹አምባገነን መሪዎቻችን ከሕዝብ ጉያ የወጡ› የአስተሳሰብ ችግር የወለዳቸው የመሆናቸው ሐቅ ዘልቆ የገባኝ (ወይም genuinely comprehend ማድረግ የተቻለኝ) ስለዚህ አብዮት ሲፀነስ ዓላማው ባልተለወጠ ሕዝብ ላይ የተለወጠ መሪ ማስቀመጥ ቢሆንም ሲወለድ ግን አንድም ያልተለወጠ ሕዝብ የተለወጠ መሪ መውለድ ስለማይችል፣ አንድም ደግሞ የተለወጠ መሪ እና ያልተለወጠ ሕዝብ  መዋሐድ ስለማይችሉ፣ አብዮቱ (ዓላማው) ይጨናገፋል፡፡
በዚሁ ጊዜ ነበር የቅርብጊዜ ምሳሌያችንን የአረብ አብዮትን መልሼ በወፍ በረር ለመገምገም የተገደድኩት፡፡ ቱኒዚያ፣ ግብጽ፣ ሊቢያ፣ ሶሪያ…. ከተሳካው የከሸፈው፣ከለማው የወደመው ይበዛል፡፡ የአምባገነን መገርሰስ ብቻውን ለውጥ አያመጣም፤ ከነዚህኞቹ ለውጦች ይልቅ የእኛው ፊውዳሊዝምን ገርስሶ- ወታደራዊ አምባገነንነትን ያመጣው አብዮት የተሻለ ኪሳራ ነበረው ማለት ይቻላል፡፡ (እዚህጋ በኢሕአፓ፣ መኢሶን እና ሌሎችም የደርግ ፓርቲዎች መካከል የተደረገው የድኅረ አብዮት የሥልጣን ሽኩቻ ሳቢያ የጠፋውን ሕይወት ሳንቆጥር መሆኑ ነው፡፡) ከትንሽ ጊዜ በኋላ ደግሞ በብርቱካናማ አብዮቷ የምትደነቀው ዩክሬን አበየች፡፡(‹“የተውኩትን ነገር ተነግሬ፣ ተመክሬ ባገር ምን ጎትቶ አመጣብኝ፣ የአብዮትን ነገር?” Another revolution? ብዬ ትዊት አድርጌም› ነበር) አብዮቷ ግን በአጭር ጊዜ ውስጥ የአካሏ ክፋይ የሆነችው ክሬሚያን በማሳጣት ይጀምራል፡፡ ምዕራብ ዩክሬናውያን ሲያብዩ ‹የአገራችን መንግሥት ከምዕብራባውያን ይልቅ ምስራቃውያን (ራሺያ….) አደላ› ብለው ቢሆንም በውጤቱ ግን ጭራሽ ራሺያ ክሬሚያን ጠቅልላ አረፈችው፡፡ልብ በሉ! አብዮቱ ከተነሳበት 360 ዲግሪ ዞሮ ተጠናቀቀ፡፡ ለነገሩ አልተጠናቀቀም፤ አሁን ወደ እርስ በእርስ ጦርነት ተሸጋግሯል፡፡
ይኼኔ ነበር በግል ጦማሬ ላይ ጥር 2006 ‹‹Are revolutions meant to be betrayed?›› ብዬ በመጠየቅ የጻፍኩት፡፡ ዜጎች አብዮትን ሲጀምሩት የማይታዩ ችግሮች ሲጨርሱት የሚስተዋለው ‹ሌባ ሲካፈል እንጂ ሲሰርቅ አይጣላም› ነበር የጽሑፌ አንኳር ሐሳብ፡፡ ‹‹ሌባ›› ያልኳቸው  በሕዝባዊ አብዮት ስም የግል ሕልማቸውን የሚያሳኩ አጀንዳ ያላቸውን ቡድኖች (interest groups) ነው፡፡ በኢትዮጵያ ነባራዊ የፖለቲካ እውነታ ደግሞ እነዚህ ዓይነቶቹ interest groups ብዙ ናቸው፡፡ ስለዚህ በአብዮት ለውጥ አማጭነት ተስፋ ስቆርጥ የመጀመሪያ ጥያቄዬ ‹‹ሳያብዩ ለውጥ ማምጣት ይቻላል?›› የሚል ነበር፡፡ የመጀመሪያ መልሴ ‹‹እንግሊዝ›› ነበረች፡፡ የእንግሊዝ ሕዝብና መንግሥት በሕግ የበላይነት ላይ ለማንም ምሳሌ መሆን የሚችል ነው፡፡ የዓለምን ግማሽ በገዙበት ጊዜም አሁንም አብየው አያውቁም- እንግሊዛውያን፡፡ ምክንያቱም ተወያይተው ችግራቸውን መፍታት ይችላሉ፡፡ ሕዝብና መንግሥት ሲለወጡ ሁሉም በሰላም ይካሄዳል፡፡
ይህንን የመጨረሻ አቋሜን ያውቅ የነበረ ወዳጄ፣ ‹‹እህ አሁንስ?›› አለኝ ‹አብዮት ልታስነሳ አሲረሃል› ተብዬ ተጠርጥሬ ከታሰርኩ በኋላ  ሊጎበኘኝ መጥቶ፡፡ ‹‹አየኸው አይደል፣ ያለአብዮት ለውጥ እንደማይመጣ?›› የሚገርመው፣ የኔና የጓደኞቼ በሕገ-ወጣዊ ማንአለብኝነት መታሰርና፣ የመንግሥት (ፖሊስ) ተጠያቂነት ማጣት ውስጥም ሕዝባዊ አለመለወጥ ነው የሚታየኝ፡፡ መንግሥት አሁንም ቢሆን የሚያስጨንቀው ‹‹የውጭ ኃይሎች ጫጫታ›› እንጂ የውስጥ ሰዎች ጥያቄ አይደለም፡፡ በእኛ ላይ የደረሰው (ሐሳብን በመግለጽ ጦስ መታሰር) በሌሎች ላይ ሲደርስ የነበረ፣ እየደረሰ ያለ ፣ ወደፊትም የሚደርስ መሆኑ ቢታወቀውም ሕዝባችን ግን ‹‹መብቴን ማስጠበቅ አለብኝ›› ከማለት ይልቅ ‹‹ዝም ብል ይሻለኛል›› (ጎመን በጤና) mode ውስጥ ነው፡፡ ሕዝብ ገና አልተለወጠም፤ የለውጥ ጣዕሙም የገባው አይመስልም፡፡ ሌሎች ሰላማዊ የትግል አማራጮችም ገና በኢትዮጵያ አልተሞከሩም፡፡ ሕዝቡ ጣዕሙን የማያውቀውን ለውጥ ከመስጠት በፊት ደግሞ የለውጡን ጣዕም አውቆ ለውጡን ራሱ ጠይቆ፣ ራሱ እንዲያመጣው ማንቃት ያስፈልጋል፡፡ አለበለዚያ እንግሊዛውያኑ እንደሚሉት ‹ጋሪው ከፈረሱ ቀድሞ› አይሆንም! ለወዳጄም ይህንኑ ሃሳቤን ነበር የነገርኩት፡፡
ለነገሩ ይህንን ሁሉአልኩ እንጂ ክፍሉ ታደሰ በ‹‹ያ ትውልድ›› (ቅጽ 1) ላይ  ‹ኃይሌፊዳ በ1965 በኢትዮጵያ በ25 ዓመት ጊዜ ውስጥ አብዮት ይነሳል ብዬ አልገምትም ብሎ ነበር› እንዳለው ካልሆንኩ በቀር እኔም በቅርቡ ኢትዮጵያ ውስጥ አብዮት ይነሳል የሚል ምንም ግምት የለኝም፤ በመጨረሻም በአቤ ቶክቻው ዋዘኛ አባባል ‹‹ካጠፋሁ፣ልጥፋ!››

መስከረም ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ ኒክ ኦቻላ ለኢሳት እንደገለጹት በኢትዮጵያ አዲስ አመት ደገኞች በፈጸሙት ጥቃት 8 የመዠንገር ተወላጆች ተገድለው ፣ ከ3 ሺ በላይ የሚሆኑት መሰደዳቸውን ገልጸዋል። 835 መዠንገሮች ቤተክርስቲያን ውስጥ ተጠግተው በምግብ እጥረትና በብርድ ሲሰቃዩ መቆየታቸውን አቶ ኒክ ተናግረዋል። አቶ ኒክ እንደሚሉት ለግጭቱ መንስኤ የኢትዮጵያ መንግስት ያወጣው የመሬት ቅርምት ፖሊሲ ነው። በዚህ …

መስከረም ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከዚህ በላይ የት ሄደን አቤት እንደምንል ግራ ተጋብተናልም በማለት በመንግስት አሰራር ማዘናቸውንም ተናገረዋል፡፡ የቋራ ከተማ ነዋሪዎች ከወራት በፊት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በተገኙበት የጠየቋቸው የመልካም አስተዳደር ፣የመንገድ ፣የመብራት እና ስልክ ችግሮች ይፈታሉ በማለት አመራሮቹ ቃል ቢገቡም በዚህ አመት በተደለደለው የበጀት ቀመር ተጨማሪ በጀት ሳይያዝ መቅረቱ እንዳሳዘናቸው …

መስከረም ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከክልሉ ባለስልጣናት የሚደረሱን መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ፕሬዚዳንቱ አቶ አብዲ ሙሃመድ ወደ አዲስ አበባ እንዲሄዱ ከጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ የቀረበላቸውን ጥሪ ባለመቀበል በክልላቸው የሚገኙ ሲሆን፣ ” በኢትዮጵያ ውስጥ ከህወሃቶች በስተቀር ማንም ከስልጣን ሊያነሳኝ የሚችል ሃይል የለም” በማለት፣ የአቶ ሃይለማርያምን ጥሪ ውድቅ አድርገዋል። በምስራቅ እዝ አዛዥ ጄ/ል አብርሃም ገብረማርያም እንደሚተማመኑ የገለጹት …

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

መምህራኑ በዛሬው ዕለት በመቀሌ ከተማ የተለያዩ አዳራሾች ተሰብስበው በ3 አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያዩ የተገለጸላቸው ሲሆን አጀንዳዎቹም፡- 1 . ስለተሃድሶ መስመራችንና የኢትዮጵያ ህዳሴ 2 . ዴሞክራሲያዊ ሥርዓታችንና ፈተናው 3 . የትምህርት ጥራትና ማነቆዎቹ የሚሉ ሲሆን ስብሰባው የሚቀጥለው ለ 7 ቀን እንደሆነና ቅዳሜና እሁድንም እንደሚጨምር ከመድረኩ መሪዎች ተገለጸላቸው፡፡ መምህራኑም ” እኛ ቅዳሜና እሁድ መሰብሰብ አንፈልግም ማረፍ አለብን:: በተጨማሪም […]

በሰሜናዊው ጫፍ የብሪታንያ ግዛት አካል ስኮትላንድ ፤ እጎአ በ2012 በተደረገ ስምምነት መሠረት፣ ተገንጥላ የራሷን ነጻነት ለማወጅ ወይም ከ 300 ዓመት በላይ ጸንቶ በቆየው ሕብረት፣ ዩናይትድ ኪንግደም በሚባለው ሀገር፣ ማለትም በብሪታንያ በሕብረት ለመኖር፤ ከሁለቱ አንዱን ለመምረጥ፣ ህዝቡ ከዛሬ ጧት አንስቶ እስከማታ ድምፁን በመስጠት ላይ ነው።

በዓለማችን «ግሎባላይዜሽን» ወይም አፅናፋዊዉን ትስስርን ተከትሎ በተለይ በአፍሪቃ ሀገራት ከተሞች የሚደረገዉ ፈጣን የግንባታ ሥራ ታሪካዊ ቅርሶችን እያወደመ መሆኑ አሳሰቢነቱን እያጎላ መጥቶአል።

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ፣ ከፍተኛ የኤኮኖሚና የንግድ ልዑካንን አስከትለው፣ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ፤ ከኢትዮጵያ ከፍተኛ የአመራር አባላትና ከአፍሪቃ ሕብረት ባለሥልጣናት ጋር መወያየታቸው ታውቋል።

ራሱን «እስላማዊ መንግሥት » በማለት የሚጠራው በኢራቅና ከፊል ሶሪያ የሚንቀሳቀሰው አክራሪ ታጣቂ ንቅናቄ ፣ ከዚህ ቀደም የ ሁለት አሜሪካውያን ጋዜጠኞችንና አንድ የብሪታንያ ተወላጅ አንገት ከቀላ ወዲህ፤

ኢትዮጵያ ውስጥ ዘንድሮ በሚካሄደው ብሔራዊ ምርጫ፣ የሲቭል ማሕበራት ድርሻ ሊጠናከር ይገባል ተባለ። ይህ የተገለጠው፤ የኢትዮጵያ ራእይ ም/ቤት ለዴሞክራሲ ግንባታ « ቪዥን ኢትዮጵፕያን ኮንግረስ ፎር ዴሞክራሲ»

የመድረክ አመራር አባል ዶር በየነ ጴጥሮስ ፣ ከአዲስ አድማሷ ጋዜጠኛ ኤልሳቤጥ እቁባይ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ አስተያየት ሰጥተዋል። በተለይም በመድረክ ዉስጥ ስላሉት ችግሮች የተጠየቁት ዶር በየነ፣ ከአንድነት ፓርቲ ጋር ከተፈጠረው ችግር ዉጭ ሌላ ምንም ችግር መድረክ ዉስጥ እንደሌለ ገልጸዋል። በአረና ትግራይ ዉስጥ፣ ታዋቂው ታጋይ አቶ አስገዴን ጨምሮ ከአረና በለቀቁ አባላት ዙሪያ ምላሽ […]

የአንድነት ፓርቲ የመቱ ዞን የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ታመነ መንገሻ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ መስከረም 3 ቀን 2007 ዓ.ም በመቱ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸውን ከአካባቢው የደረሰን ዜና ያመለክታል፡፡ አቶ ታመነ መንገሻ የታሰሩት አማራ ይቀውጣ ብለሃል በሚል ሰበብ እንደሆነና ይህን ተናገሩ በተባለበት ወቅት ታመው አልጋ ላይ እንደነበሩ ምንጮቻችን የገለጹ ሲሆን ፖሊስ በሳቸው ላይ እንዲመሰክር ፖሊስ ጣቢያ ለምስክርነት […]

መስከረም ፯(ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቀድሞው የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት የህዝብ ግንኙነት ስራ አማካሪ እና የክልሉ የወጣቶች ሊቀመንበር በመሆን ካገለገለ በሁዋላ የተለያዩ የቪዲዮ ማስረጃዎችን በመያዝ ከአገር የወጣው ወጣት አብዱላሂ ሁሴን ፣ “ኦ ኦጋዴን” በሚል ኢሳት ያስተላለፈው አጭር የዶክመንታሪ ፊልም፣ በስልጣን ላይ ያሉት ገዢዎች ለሶማሊ፣ ለኢትዮጵያና በአጠቃላይ ለሰው ልጆች ያላቸውን ንቀት ያሳያል ብሎአል። ዘገባውን ከተመለከተ …