በቃሊቲ እሥር ቤት የሚገኙት አቶ በቀለ ገርባና አቶ ኦልባና ሌሊሳ “የሕክምና እርዳታ እንዳያገኙ ተደርገዋል” ሲል ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አሳስቧል፡፡

በተለይ የአቶ ኦልባና ሌሊሣ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን የድርጅቱ የኢትዮጵያና የኤርትራ መርማሪ ክሌር ቤስተን ለቪኦኤ በሰጡት መግለጫ ገልፀዋል፡፡

ድርጅቱ ባለፈው ዓርብ ባወጣው የአፋጣኝ እርምጃ ጥሪው መልዕክቱን የሚያዩ ሁሉ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተመሣሣይ ጥሪ እንዲያስተላልፉ አሳስቧል፡፡

ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚገኙ የኦሮሚያ ከተሞችን በአዲስ አበባ ማስተር ችላንውስጥ አካትቶ ለማልማት በሚል የተያዘውን ዕቅድ የኦሮሚያ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች በተለያዩ ከተሞች ተቃውሞዎቻቸውን እያሰሙ ነው፡፡

በጂማ፣ በነቀምት፣ በሃሮማያ፣ በአምቦና በሌሎችም ከተሞች ያሉ የኦሮሚያ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች የአዲስ አበባ ዙሪያ ከተሞችን በማስተር ፕላኑ ውስጥ መካተት እየተቃወሙ ያሉት በሰላማዊ ሰልፎች ነው፡፡

በጂማና በነቀምቴ የፀጥታ ኃይሎች የኃይል እርምጃ መውሰዳቸው የተሰማ ሲሆን በሌሎቹ ከተሞች ግን ከማስፈራራት ወይም ከሥጋት የዘለቀ እንቅስቃሴ እንዳልነበረ ተማሪዎቹ ተናግረዋል፡፡

የኦሮሚያን የአስተዳደርና የፀጥታ ዘርፍ፣ እንዲሁም የክልሉን የፖሊስ ኮሚሽን አግኝተን ለማነጋገር ጥረት እያደረግን ነው፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የወባ ወረርሽኝ በዓለም ዙሪያ በእጅጉ ቢቀንስም አሁንም ቢሆን በየዓመቱ ሁለት መቶ ሚሊየን ሰው እንደሚያዝ የተባበሩት መንግሥታት የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡

ዛሬም ቢሆን በዓመት ከስድስት መቶ ሺህ በላይ ሰው እንደሚሞትም ድርጅቱ የዘንድሮን የወባ ቀን አስታክኮ ባወጣው ሪፖርቱ አመልክቷል፡፡

በሌላ በኩል ግን ኢትዮጵያ ላለፉት አምስትና ስድስት ተከታታይ ዓመታት የወባ ወረርሽን ተከስቶባት እንደማያውቅ የኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የሃገርአቀፍ የወባ መከላከያ መርኃግብር አስተባባሪ ወ/ት ሕይወት ሰሎሞን ለቪኦኤ በሰጡት ማብራሪያ ባለፉት አሥር ዓመታት ውስጥ በወባ የመያዝ አጋጣሚ በ67 ከመቶ መቀነሱን፣ የሞት መጠኑ በ48 ከመቶ መውረዱንና ዕድሜአቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናት የወጣ ሞት መጠን…

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

በአራት ዪኒቨርሲቲዎች የሚገኙ የኦሮሞ ተማሪዎች የአዲስ አበባ አዲሱን ማስተር ፓልን በመቃወም ተቃዉሞውውቸዉን አሰሙ። በዉጭ አገር የሚገኘውና በቅርቡ የተቋቋመው የኦሮሞ ሜዲያ ንቴዎርክ ማስተር ፓልኑን በመቃወም ከፍተኛ ቅስቀሳ እያደረገ የነበረና የሚገኝ ሲሆን፣ በዶር መራራ ጉዳናን የሚመራዉ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስን ጨመሮ በርካታ የኦሮሞ ድርጅቶች በርካታ የኦሮሞ ድርጅቶች ፕላኑን አዉግዘዋል። የኦሮሞ ተማሪዎች ም በአምቦ፣ በወለጋ፣ በጂማና በሃረማያ ሰላማዊ በሆነመንገድ […]

ዩኤስ አሜሪካ እና የአውሮጳ ህብረት ሩስያ በዩክሬይን ቀውስ ላይ እያካሄደችው ነው ባሉት ሕገ ወጥ ጣልቃ ገብነት ሰበብ ካሁን ቀደም የጣሉትን ማዕቀብ አጠናከሩ።

ዩኤስ አሜሪካ እና የአውሮጳ ህብረት ሩስያ በዩክሬይን ቀውስ ላይ እያካሄደችው ነው ባሉት ሕገ ወጥ ጣልቃ ገብነት ሰበብ ካሁን ቀደም የጣሉትን ማዕቀብ አጠናከሩ።

በትናንትናዉ ዕለት ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሁለት ርዕሳነ ሊቃነ ጳጳሳትን የቅድስና ሥርዓት አካሂዳለች። በቤተ ክርስቲያኒቱ ቅዱሳን የተባሉት ዮሐንስ 23ኛ እና ዮሐንስ ጳዉሎስ ዳግማዊ የተባሉት በርዕሳነ ሊቃነ ጳጳሳትነት ያገለገሉ አባቶች ናቸዉ።

የደቡብ ሱዳን ግጭት እስካሁን በሺህዎች የሚቆጠሩ የሀገሪቱ ነዋሪዎችንለሞት ዳርጓል። ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሰዎችም ቀዬያቸውን ጥለው እንዲሰደዱ አስገድዷል። ከወራት በፊት በሁለቱ የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ኃይላት መካከል አዲስ አበባ ውስጥ የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተፋላሚዎችን ደም ከመፋሰስ አልታደገም።

ዩናይትድ ስቴትስ በሲና በረሃ አካባቢ ለገጠማት የሽብር ስጋት እንዲዉሉ በሚል አስር አፓቼ ሄሊኮፕተሮችን ለግብፅ ልትሰጥ መሆኗን ሰሞኑን አስታዉቃለች። ይህንኑ ድጋፍ ተከትሎ የግብፅ መንግስት ወታደራዊ አቅሙን እያጠናከረ የሚገኘዉ

ማዕከላዊን በከፊል አውቀዋለሁ፡፡ ትናንት ሰባት የሚሆኑ ጋዜጠኞች፣ ብሎገሮችና አክቲቪስቶች መታሰራቸውን ተከትሎ ወደ ማእከላዊ መወሰዳቸውን ሰምተናል፡፡ በቀጣዮቹ ቀናት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ጨለምተኛ ልመስል እችል ይሆናል፤ እውነታው ግን ይኸው ነው፡፡ መጀመሪያ ክሱ ምን ሊሆን ይችላል የሚለው አጓጊ ጥያቄ ነው፡፡ ይህን ለማወቅ ወሳኝ ፍንጭ የሚሰጠው የቤት ፍተሻው ነው፡፡ የታሰሩትን ሰዎች ቤት የሚፈትሹት ፖሊሶችና መርማሪዎች ቤቱን […]

ሰማያዊ በመባል የሚታወቀውና የወጣቶች ፓርቲ እንደሆነ አዘወትሮ የሚናገረው ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው ሳምንት በወጣ ልሳኑ ‹‹ነገረ ኢትዮጵያ›› ላይ ታዋቂውን ኢትዮጵያዊ ምሁርና በተቃውሞ ጎራ እድሜ ሳይገድባቸው ትግል እያደረጉ ያሉትን ምሁር ዶ/ር ኃይሉ አርአያን አሰደበ፡፡ የፓርቲው ልሳን ዶ/ር ሃይሉን ለመሳደብ የተገደደው የሚል ጠንካራ አቋም ስላላቸው ሲሆን ሳሙኤል አወቀ በተባለ ጎረምሳ ፀኃፊ በኩል ተብለው መገለፃቸው ብዙዎችን ያሳዘነ ሲሆን ከኢትዮጵያዊ […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም የመንግስታቸውን የዘጠኝ ወራት ሪፖርት ለፓርቲያቸው የፓርላማ አባላት ባቀረቡበት ወቅት(ሁለት ወንበር ከማጣታቸው ውጪ) ‹‹ዴሞክራሲያዊነት ለመንግስታቸው የህልውና ጉዳይ ››እንደሆነ አውስተው ነበር፡፡ልማታዊ በመሆናችን ዴሞክራሲን እንደ ትርፍ ነገር የምንቆጥር የሚመስላቸው ተሳስተዋል ለማለት አስረግጠው ሲናገሩ አድምጬ ነበር፡፡ ኢህአዴግ በየጊዜው የፖለቲካ አክሮባት እየሰራ ንፋሱ እንደወሰደው ከአንዱ ርዕዩተ ዓለም ወደ አንዱ እንደፌንጣ እየዘለለ ‹ልማታዊ ወ ዴሞክራሲያዊ ነኝ› እያለን ነው፡፡ድርጅቱ […]

በማዕከላዊ የሚገኙ የዞን ዘጠኝ አባላትን ከተፈቀደልን ለመጠየቅ ካልሆነም የታሰሩበትንና ፍርድ ቤት የሚቀርቡበትን ቀን ለማወቅ ወደ ስፍራው ዛሬ ማለዳ አምርተን ነበር፡፡የጦማርያኑ ቤተሰቦች ያመጡትን ምግብ ከማቀበል ውጪ ማንንም ሊያናግሩ እንደማይችሉ ተነግሯቸው በሐዘን እንዲመለሱ ተደርገዋል፡፡ መቼ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ለሚለው ጥያቄም ኃላፊነት ወስዶ የሚናገር አካል በመጥፋቱ ማወቅ አልተቻለም፡፡ለምን ታሰሩ ለሚለው ጥያቄ ግን መልስ ከተባለ‹‹ ተረጋጉ መስማታችሁ መቼ ይቀራል››ተብሏል፡፡ […]

ከአዲስነገር ጋዜጣ አባላቶች መሰደድ እንዲሁም ከውብሸት እስክንድር እና ርእዮት አለሙ መታሰር በሁዋላ ለእኔ መንግስት በሚዲያ ሰዎች ላድ በጅምላ የወሰደው ትልቅ ክስረት ነው። ፅሀዮ መንግስታችንም የኢትዮጵያውያን በነፃነት የመኖር ህልም ማጨናገፉን ስራዮ ብሎ ተያዞታል ምን ያህል እንዳዘንኩኝ አላውቅም ብዙ ሰው ስለሀገሬ አያገባኝም ባሉበት ሰአት ስለሚያገባን እንጦምራለን( እንፅፋለን) በማለት ለሀገራቸው ያላቸውን ቀና ነገር በበሳል ብእራቸው ሲፅፉ ነው የማውቀው። […]

ከአርብ ሚያዚያ 17 ቀን ጀምሮ ኢሕአዴግ ዞን ዘጠኝ ተብለው በሶማል ሜዲያ ምህበረሰቡ የሚታወቁ ወጣት ጦማሪያንን ( ብሎገርስ) እንዲሆም ሌሎች ጋዜጠኞችን አይሰረ ሲሆን፣ እስረኞቹ ትልናት እሁድ ሚያዚያ 19 ቀን ፍርድ ቤት እንደቀረቡ ታወቀ። የታሰሩ የዞን9 አባላትና ጋዜጠኞች ትላንትና እሁድ ሚያዝያ 19 አራዳ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት ቤተሰብ ሳይወቅ እና የሕጝ ባለሞያ በሌለበት ሁኔታ ሲሆን፣ […]

ትላንት ሚያዝያ 17 2006 አመሻሽ ላይ ዞን 9 በተሰኘ ድረ ገጽ (ብሎግ) ላይ በሳል ፖለቲካዊና ማህበራዊ ትችቶችን በማቅረብ ከሚታወቁት ፀኀፍት መሀከል 6ቱ ማለትም ማህሌት ፋንታሁን፣ በፍቃዱ ሀይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ዘላለም ክብረት፣ አጥናፍ ብርሀን፣ አቤል ዋበላ እንዲሁም ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣ ጋዜጠኛ አስማመው ኃ/ጊዎርጊስ እና ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል፡፡ ግለሰቦቹ በተለያየ […]

በመድረክ እና በአንድነት መካከል ስላለው ግንኙነት ሁለት ኢትዮጵያዊያን የጻፉትን አነበብኩ። ዶር መሳይ ከበደ፣ መድረክ ዉስጥ ባሉ የዘዉግ ደርጅቶች እና በአንድነት ፓርቲ መካከል ያሉት የፖለቲካ ፕሮግራም ልዩነቶች የማይታረቁ መሆናቸውን በመገልጽ፣ አንድነት ጊዜዉን እና ጉልበቱን እነዚህ የዘዉግ ድርጅቶችን በማባበል ላይ ከማጥፋት፣ ከሌሎች አገር አቀፍ ድርጅቶች ጋር አብሮ እንዲሰራና እንዲዋሃድ ይመክራሉ። አቶ ዳዊት ተሾመ በበኩላቸው፣ ለዶር መሳይ መልስ […]

መፍቀሬ-ሩስያ ታጣቂዎች ይዘው ያቆዩዋቸውን የተወሰኑ የ«ኦኢሲዲ» ታዛቢ ቡድን አባላት ለመገናኛ ብዙኃን እይታ አቀረቡ። ከተያዙት ታዛቢዎች መካከል አንድ ስዊድናዊ የስኳር ህመም ስላለበት መለቀቁን ታጣቂዎቹ አስታውቀዋል።

የታሰሩ የዞን9 አባላትና ጋዜጠኞች ትላንትና እሁድ ሚያዝያ 19 አራዳ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው እነደነበር ታወቀ

አርብ አመሻሹን እና ቅዳሜ ጠዋት የታሰሩት የዞን9 አባላትና ጋዜጠኞች ትላንትና (እሁድ ጠዋት) ፍርድ ቤት መቅረባቸው ታወቀ፡፡ ቤተሰብም ሆነ የህግ ባለሞያ ባላወቀበት ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን የጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀባቸው ክስ ላይ 

“ውጨ ሃገር ከሚገኙ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ነን ከሚሉ ጋር በገንዘብና በሃሳብ በመተባበር በማህበረሰብ ሚዲያ ሃገርን ማሸበር” ወንጀል መጠርጠራቸው የተገለጸ ሲሆን 

1. ማህሌት ፋንታሁን አቤል ዋበላ እና በፍቃዱ ሃይሉ ለሚያዚያ 30
2. ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ጋዜጠኛ አስማማው ሃይለግዮርጊስ ዘላለም ክብረት ለሚያዝያ 29
3. አጥናፍ ብርሃኔ ኤዶም ካሳየ ናትናኤል ፈለቀ ሚያዝያ 30 ተቀጥረዋል፡፡

The journalists and bloggers are charged of “Working with foreign human right activist organizations agreeing with idea, finance and inciting violence through social media to create instability in the country” with three different files.

Hence;
1. Mahlet Fantahun
2. Abel Wabela
3. Befeqadu Hailu are appointed for May 8 2014 

1. Tesfalem Weldyes 
2. Asmamaw W/Giorigis
3. Zelalem Kebret are appointed for May 7 2014

1. Atenaf Berahene
2. Edom Kassaye
3. Natnael Feleke are appointed for May 8 2014

#FreeZone9bloggers #FreeEdom #FreeTesfalem#FreeAsemamaw #Ethiopia

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሶስተኛ አመት የምህንድስና ተማሪ የሆነው ዮናስ ከድር ሰማያዊ ፓርቲ ለጠራው ሰልፍ ሲቀሰቅስ ተይዞ ጉለሌ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ ይገኛል፡፡ እስር ቤት ውስጥ ያለ ተማሪ በፖሊስ ታጅቦ ፈተናውን የመፈተን መብት ቢኖረውም ዮናስን ግን ‹‹አንተ የፖለቲካ እስረኛ ነህ፣ አንተን አጅበን ማስፈተን አንችልም፣ አንተን የሚያጅብ ፖሊስ የለንም!›› የሚሉ የተለያዩ ምክንያችን በመደርደር ለፈተና እንዳይቀርብ ተደርጓል፡፡

የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች (እደግመዋለው) የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ህገመንግስቱን ተመርኩዘው የሃይማኖት ነጻነት ጥያቄዎችን በመያዝ ወኪሎቻቸውን በመምረጥ ህጋዊ ውክልን በመስጠት ወደ ገዢው መንግስታዊ ቡድን ህግን አንብበው ለይተው አውቀው መብታቸውን እና ግዴታቸውን ተረድተው አቤቱታቸውን ለማሰማት በሄዱበት የወይኔው ስርአት እንኳን ደህና መጣችሁ በሚል የህሰት ወንበዴያዊ ፈገግታ በአስመሳይ ሰላም እና ፍቅር አቅርቦ እውቅና የሰጠ በማስመሰል ደም በተለወሱ ጥርሶቹ ነክሶ ለመያዝ እና ለአገዛዙ […]

መብራት ውሃ የስልክና የኢንተርኔት ኔትወርክ አገልግሎቶች መብቶች የህዝብ ናቸው!!!!! -ምንሊክ ሳልሳዊ አቤቱታችን ከፖለቲካ ነጻነት እና ዲሞክራሲያዊነት ጎን ለጎን የመሰረታዊ አገልግሎቶች ጥያቄ ነው …ይህ ደሞ ለየት ባለ መልኩ አብዮታዊ ነው:: እኛ በሰው አገር የምንኖር ዲያስፖራዎች በወገናችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ከማውራት እና መኖሪያ ፍቃዳችን ሲታደስ ከመቀዝቀዝ ዉጪ በወያኔ ላይ የምናሳድረው ጫና እምብዛም ጉልፍ ስፍራ የለውም:: እርስ በርሳቸው […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

የሠማያዊ ፓርቲ ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ባካሄደው ሠላማዊ ሠልፍ መንግሥት እየተከተለው ነው ያለውን ብልሹ የአስተዳደር ሥርዓት፣ ሙስናና ደካማ የመሠረተ-ልማት አቅርቦት ያሻሽል ሲል ጠየቀ።

በአካባቢያቸዉ የሚገኝና ለእነሱ የዕለት ተዕለት ህይወት ትርጉም ያለዉ የደን ሃብት የምንጠራ አደጋ ባንዣበበበት ወቅት ዶቼ ቬለ ያነጋገራቸዉ የመዠንገር ማኅበረሰብ አባላት «መዠንገሮች ዉሃ ብቻ ሳይሆን ደግም ህይወት ነዉ» የሚል መመሪያ እንዳላቸዉ ገልጸዉልን ነበር።

5. መዝየም

ኢትዮጵያውያን አባቶችና ምእመናን በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም መንፈሳዊ ተጋድሎ ለመፈጸምና መንፈሳዊ ርስትን ለትውልድ ለማኖር ታላቅ መሥዋዕትነት ከፍለዋል፡፡ ይህንን የዘመናት ተጋድሎ የሚያሳይ አንዳች ሙዝየም ግን የለንም፡፡ የገዳሞቻችንን ታሪክ፣ የተጻጻፍናቸውን ደብዳቤዎች፣ በየጊዜው ከሀገር ቤት የተላኩትን መጻሕፍትና ሌሎች ንዋያተ ቅድሳት፣ የዘመናቱን አሻራ የሚያሳዩ የሥዕልና የፎቶ ግራፍ መረጃዎች፣ ካርታዎች፣ ተጓዦችና ታሪክ ጸሐፊዎች የከተቧቸው ማስረጃዎች፣ በየዘመናቱ የተሰጡ ስጦታዎችን የሚያሳዩ መዛግብት፣ የተሾሙ ራይሶችንና ሊቃነ ጳጳሳትን የሚያሳዩ ዝርዝሮችና ፎቶዎች፣ የተሳላሚዎችን ሁኔታ የሚያሳዩ ፎቶዎችና መዛግብት የተከማቹበት፤ ከዚያም አልፎ የእናት ቤተ ክርስቲያንን ማንነት፣ ታሪክና ቅርሶች የሚያሳይ አንድ ታላቅ ሙዝየም በደብረ ገነት ኪዳነ ምሕረት ግቢ ውስጥ ወይም በአካባቢው ያስፈልገናል፡፡

ይህ ሙዝየም ሦስት ጥቅሞች ይኖሩታል፡፡ በአንድ በኩል ከሁለት ሺ ዓመታት በላይ ያስቆጠረውን የቅድስት ሀገር ርስታችንን ታሪክ በተጨባጭ የምናሳይበት፣ ከንግግር የዘለለ ማስረጃ እንዲኖረንና ያንንም ለዓለም ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንድናሳይ ያደርገናል፡፡ ከኢየሩሳሌም ከተማ አንዱ የቱሪስት መዳረሻ በመሆንም የኢትዮጵያውያንን የተጋድሎ ታሪክ ለጎብኝዎች እናሳይበታለን፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ኢየሩሳሌም የመላው ዓለም አማኞች መናኸሪያ በመሆኗ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ለማስተዋወቂያ ወሳኝ መድረክ ይሆናል፡፡ ቀደም ብለን እንዳየነው ኢትዮጵያንና ቤተ ክርስቲያንዋን በተለይ ለምዕራቡ ዓለም ያስተዋወቋት የኢየሩሳሌም(በተለይም የዴር ሡልጣን) ገዳማት አባቶች ነበሩ፡፡

ሦስተኛ ደግሞ ለገዳሙ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ይሆናል፡፡ የዓመቱን ፋሲካ ጠብቆ ጧፍ ከመሸጥ ይልቅ ራቅ አድርጎ አስቦ ታሪካችንን የሚያሳዩ ፖስት ካርዶችን፣ ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱና ስለ ኢየሩሳሌም ገዳማት የተጻፉ መጻሕፍትን፣ የጎብኝዎች መመሪያዎችን(Tourist Guide)፣ ኢትዮጵያዊ ትውፊት ያላቸው ቅዱሳት ሥዕላትን፣ የላንቲካ ዕቃዎችን(የሀገሪቱን ባሕል፣ የእምነት ሥርትዓቷንና ታሪኳን የሚያሳዩ ሰሐኖች፣ ቲሸርቶች፣ ኩባያዎች፣ የወግ ዕቃዎች፣  ጌጣ ጌጦች) ለቱሪስቶች በመሸጥ ከፍተኛ ገቢ ለማግኘት ያስችላል፡፡

እስካሁን በታየው ልማዳችን ዕቃ ቤት እንጂ ሙዝየም በብዛት የለንም፡፡ በሀገር ቤት እንኳን ያሉን ሙዝየሞች ከታሪካችንና ከቅርሳችን ጋር ሲወዳደሩ ዓባይን በጭልፋ የሚያስብሉ ዓይነት ናቸው፡፡ በኢየሩሳሌም የሚገኙ አብዛኞቹ አብያተ ክርስቲያናት ሙዝየም ብቻ ሳይሆን የጥናትና ምርምር ተቋማት ጭምር እንዳሏቸው የኢየሩሳሌም የቱሪዝም መሥሪያ ቤት የሚያሳትማቸው የቱሪስት መርጃ መጻሕፍት ያሳያሉ፡፡ ሌላው ቀርቶ የቅርብ ዘመን ታሪክ ያላቸው አብያተ ክርስቲያናት እንኳን ቱሪስት እንደ ጎርፍ የሚፈስበት ሙዝየም አላቸው፡፡ ለተመራማሪዎችም ኢየሩሳሌምን የተመለከቱ መረጃዎችን በመሸጥ ገቢ ያገኛሉ፡፡

የአርመን ሙዝየም ሕንጻ
ወደ ኢየሩሳሌም ምእመናንን የሚያጓጉዙ ተቋማት ከገዳማቱ አስተዳደር ጋር በመመካከር ሊያከናውኗቸው ከሚገቡ ነገሮች አንዱ የሙዝየሙ ጉዳይ ነው፡፡ ‹ታሪክ እንደ ነጋሪው ነው› በሚል ያረጀ ብሂል ስለ ራሳችን ታሪክ ለእኛ እንኳን የሚገርመንን ዓይነት ያልነበረ ታሪክ እንደነበረ እየተደረገ፣ የነበረውም እየተዘነጋ እየቀረበልን መሆኑን ካየን ለቱሪስቶችማ ምን ሊነገር እንደሚችል መገመት ነው፡፡

ይህንን ሙዝየም እንዴት ባለ መንገድ ልናቋቁመው፣ ልናካሂደው ምን ምን እንዲሠራ ልናደርገው እንደምንችል በሚገባ በዓይን ዓይቶ ለመረዳት በግሪክ ፍጥሞ ደሴት የሚገኘውን የቅዱስ ዮሐንስ ገዳም መጎብኘቱ እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡ ያም ካልተቻለ በኢየሩሳሌም አሮጌው ከተማ የሚገኙትን የአርመንንና የግሪክን ፓትርያሪኬት ሙዝየሞች ማየቱ በቂ ሊሆን ይችላል፡፡

6. ሴሚናሪ

ምንም እንኳን የገዳማቱ መነኮሳት የቀድሞ አባቶች ገዳሙን የጠበቁት ተምረው አይደለም ቢሉም አባባሉም ስሕተት ነው፣ ትምህርትም የግድ ነው፡፡ የቀድሞ አባቶች አልተማሩም የሚለው ብሂል ከሁለት ነገሮች የሚመነጭ ነው፡፡ አንድ ካለማወቅ ሁለትም ከንቀት፡፡ የቀድሞ አባቶች ለትምህርት ታላቅ ቦታ እንደነበራቸው ባከማቿቸው መጻሕፍት ብቻ እንኳን ማወቅ ይቻላል፡፡ እንኳን የክርስትና መጻሕፍት የአይሁድ፣ የግሪክ፣ የሂንዱስታንና የእስልምና መጻሕፍትን ሳይቀር ወደ ግእዝ እየተረጎሙ አስቀምጠውልናል፡፡ ተተኪዎቻቸው እንደነ እርሱ ዕውቀት ወዳጆች መስለዋቸው፡፡ ታላቁ ንጉሥና የዴር ሡልጣን ገዳም ባለ ውለታ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ‹‹መጽሐፈ ብርሃን›› በተሰኘው መጽሐፉ ‹‹እስመ ጽሙዐን ለትምህርት ብሔረ ኢትዮጵያ ኄራን – ምርጦቹ የኢትዮጵያ ሰዎች ትምህርትን የተጠሙ ናቸው›› እንዳለው ኢትዮጵያውያን ትምህርትን የተጠሙና ለዕውቀት ማንኛውንም ዓይነት ዋጋ የሚከፍሉ ነበሩ፡፡

ዛሬ ባለው ዓለም ድጓ፣ ጾመ ድጓ፣ ቅኔ፣ ቅዳሴ፣ ዝማሬ፣ ትርጓሜና አቋቋም እጅግ አስፈላጊዎች ቢሆኑም ብቻቸውን ግን ወንዝ ሊያሻግሩን አይችሉም፡፡ ዛሬ በልዩ ልዩ የሀገራችንና የዓለም ቋንቋዎች ማስተማርና መጻፍ የሚያስፈልግበት፣ ጥንታዊ ሀብታችንን በዘመናዊ መንገድ ማቅረብ የሚጠየቅበት፣ ሕዝቡን ለመድረስ ልዩ ልዩ ሚዲያዎችን መጠቀም የግድ የሚልበት፣ ከትውልዱ ጋር ለመግባባትና የትውልዱን ጥያቄ ለመመለስ ሁለገብ ዕውቀት የሚያሻበት፣ ዘመን ነው፡፡

የኢየሩሳሌም ገዳማት አባቶችና እናቶች ከላይ በተጠቀሱት ነገሮች የሠለጠኑ፣ በሚገባ የታጠቁና በሁለት በኩል የተሳሉ ሰይፎች እንዲሆኑ ግድ ይላቸዋል፡፡ አንድም ‹‹መልክ ከእግዚአብሔር ሞያ ከጎረቤት›› ነውና ከጎረቤቶቻቸው ልምድ ለመቅሰም ስለሚችሉ፤ አንድም የትምህርት መርጃዎችን ከልዩ ልዩ ተቋማት ለማግኘት ቀላል ስለሆነ፤ አንድም በአንድ አካባቢ መኖራቸው በፈረቃ ለመማር ስለሚያስችላቸው፤ አንድም ልዩ ልዩ ቋንቋዎችን ለመማር ኢየሩሳሌም አመቺ በመሆኗ፡፡ ሌላው ቀርቶ በሀገር ቤት የሚገኙ መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶቻችንንም ከኢየሩሳሌም ትምህርት ቤት ጋር በማቀናጀት የተሻሉ ለሚባሉ ተማሪዎች ስኮላርሺፕ መስጠት ይቻላል፡፡

ዛሬ ዛሬ ከፍ አድርጎ ማሰብ እየጠፋ ነው መሰል የአባቶቻችን ሃሳብ አሜሪካና አውሮፓ መሄድ፣ ከግሪክ ንዋያተ ቅድሳት ማምጣት፣ ቤት መሥራት፣ ዘር መዝራት እየሆነ ነው፡፡ ነገ ቤተ ክርስቲያኒቱ ትፈልገኛለች፣ ነገ ወደ ኢትዮጵያ ኮሌጆች ሄጄ አስተምራለሁ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን እተረጉማለሁ፣ ሕዝቡን በወንጌል እደርሳለሁ፤ የመነኮስኩበትን ገዳም ኑሮና አሠራር አሻሽላለሁ፣ ቤተ ክርስቲያኔን በዓለም መድረክ አስጠራለሁ፣ ብሎ ከፍ አድርጎ የሚያስብ እያጣን ነው፡፡ ይህ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያናችን ጉዳት ነው፡፡

በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ የኢየሩሳሌም መነኮሳት የነበራቸውን ቦታ ባለፈው ጊዜ በመጠኑ ጠቅሰነዋል፡፡ የኢትተጵያ ታላላቅ ገዳማት አባቶች አብዛኞቹ ኢየሩሳሌም መጥተዋል፡፡ እዚህ ያዩትንና የሰሙትን ይዘው በሀገራቸው ተግብረውታል፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትንና ንዋያተ ቅድሳትን ወደ ሀገር አምጥተዋል፡፡ ሌላው ቢቀር አፈሩንና የዮርዳኖስን ጠበል እየያዙ በመምጣት ከገዳሞቻቸው አፈርና ጠበል ጋር አዋሕደውታል፡፡ እንደ ቅዱስ ላሊበላ ያሉትም ምድራዊትና ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን ከተመለከቱ በኋላ ‹ከመዝ ግበር› በተባሉት መሠረት የኢየሩሳሌምን አምሳል በሀገራቸው ሠርተዋል፡፡

ዛሬም ቤተ ክርስቲያን ከኢየሩሳሌም መነኮሳትና መነኮሳዪያት ብዙ ትጠብቃለች፡፡ በዕውቀት የበሰሉ፣ በቋንቋ የተካኑ፣ ዓለም ዐቀፋዊ ልምድ ያላቸው፣ በሁለት በኩል የተሳሉ ሆነው እንዲያገለግሏት፡፡ ለዚህ ደግሞ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሴሚናሪ ያስፈልጋል፡፡ የተቋሙን አመሠራረትና አሠራር ለመረዳት ከሌሎቹ ልምድ መቅሰም ነው፡፡ ወጭውን ለመሸፈን ደግሞ ምእመናን አንድም ሁለትም ተማሪ ስኮላርሺፕ እንዲሰጡ ማስረዳት ነው፡፡ ዛሬ ሰው ያጣንበት ዘመን ስለሆነ ሰው ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት ለመርዳት ምእመናን ዝግጁ ናቸው፡፡ ብቻ የቆረጠ፣ የገባውና፣ ዓላማ ያለው ሰው ይኑረን እንጂ፡፡

አሁን አሁን በዓለም ዐቀፍ መድረኮች ቤተ ክርስቲያንን ወክሎ በብቃት ሊሳተፍ የሚችል ሰው እያጣን ነው፡፡ በአብያተ ክርስቲያናት መካከል የእምነት ውይይት (Inter – church dialogue) ይደረጋል፤ በልዩ ልዩ እምነቶች መካከልም ውይይት ይደረጋል(Inter – faith dialogue)፣ የአፍሪካና የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ይደረጋል፤ የመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ጉባኤ ይደረጋል፤ በሌሎች የዓለም መድረኮችም የሃይማኖት አባቶች ይጋበዛሉ፤ ቅዱሳት መጻሕፍትን በመተርጎም ሥራም ከግሪክ፣ ከዕብራይስጥ፣ ከላቲንና ዐረብ ጋር ማነጻጸር ይጠይቃል፤ ለዚህ ሁሉ ትምህርትና ሥልጠና ወሳኝ ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢየሩሳሌም ላይ አንድ ደረጃውን የጠበቀ፣ ሰው ሊያፈራ የሚችል፣ ሴሚናሪ ይኑረን የምለው፡፡

(ይቀጥላል) 

ኢየሩሳሌም

በነገው ስልፍም ይፈቱ ዘንድ ድምጹን ያሰማል!

ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹የተነጠቁ መብቶቻችን እናስመልሳለን›› በሚል ሚያዝያ 19 ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱ ይታወቃል፡፡ በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት ከምናነሳቸው ጉዳዮች አንዱና ዋነኛው ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሰልፉ ገዥው ፓርቲን ላይ የሠላ ትችት ስለሰነዘሩና ለህዝባቸው መረጃ ስለሰጡ ብቻ የሚደርስባቸውን ህገ ወጥ እርምጃ ያወግዛል፡፡

በሳምንቱ ውስጥ የህዝብን መብት ለማስመለስ ለጠራነው ሰልፍ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ 50 ያህል አመራሮችና አባላት በህገ ወጥ መንገድ ታስረዋል፡፡ በትናንትናው ዕለት የፓርቲያችን ሊቀመንበር (ማታ ተፈትተዋል)፣ ምክትል ሊቀመንበር፣ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በህገ ወጥ መንገድ መታሰራቸው ይታወቃል፡፡ በተመሳሳይ ወቅት የዞን ዘጠኝ አክቲቪስቶችና ሌሎች ጋዜጠኞችም ታስረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ሌሎችን ለማሰር ጥረት እየተደረገ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ይህን የገዥው ፓርቲ ከፍርሃት የመነጨ አምባገነናዊ እርምጃ በጽኑ ይቃወማል፡፡ በነገው ዕለትም በእነዚህ አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች ላይ የተደረገውን እስር የሚያወግዝ መሆኑን መግለጽ ይወዳል፡፡

ኑ ራሳችን ነጻ በማውጣት የአገራችን እጣ ፈንታ እንወስን!

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ስድስት ጦማሪያን እንዲሁም አንድ ጋዜጠኛ ትናንት ከቀትር በኃላ አዲስ አበባ ውስጥ መታሰራቸው ተሰማ። ዞን «9» በመባል የሚታወቀዉ የጦማርያን ስብስብ አባላት ላይ ላለፉት ሰባት ወራት ከፍተኛ ክትትል ሲደረግ መቆየቱም ተመልክቶአል።

መፍቀሬ-ሩስያ ታጣቂዎች ይዘው ያቆዩዋቸውን የተወሰኑ የ«ኦሴ» ታዛቢ ቡድን አባላት ለመገናኛ ብዙኃን እይታ አቀረቡ። ከተያዙት ታዛቢዎች መካከል አንድ ስዊድናዊ የስኳር ህመም ስላለበት መለቀቁን ታጣቂዎቹ አስታውቀዋል።

የአቡነ ማትያስ የመነጋገርና የመደራደር አቅም ለጉብኝቱ መሰረዝ በምክንያትነት ተጠቅሷል የግብፁ ፓትርያርክ በስድስት ወራት ውስጥ ሦስት ጊዜ የጉብኝት ጥያቄ አቅርበዋል የአቡነ ታዎድሮስ ተደጋጋሚ ውትውታ ጉዳዩ ከሕዳሴው ግድብ ጋራ መያያዙን አመላክቷል የጉብኝቱ መሰረዝ በአቡነ ታዎድሮስ ጥያቄ እንደኾነ መዘገቡ ከመቅለል መጥቅለል እንዲሉ ነው ‹‹መንግሥት የግብፆችን ያህል ቤተ ክርስቲያኒቱን የዲፕሎማሲው አካል አላደረገም›› (ፋክት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፵፫፤ ፳፻፮ ዓ.ም.) …