የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን እና የቅዱሳን ስያሜ

በትናንትናዉ ዕለት ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሁለት ርዕሳነ ሊቃነ ጳጳሳትን የቅድስና ሥርዓት አካሂዳለች። በቤተ ክርስቲያኒቱ ቅዱሳን የተባሉት ዮሐንስ 23ኛ እና ዮሐንስ ጳዉሎስ ዳግማዊ የተባሉት በርዕሳነ ሊቃነ ጳጳሳትነት ያገለገሉ አባቶች ናቸዉ።