የአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ

የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ለአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ አዲስ አበባ ስታዲየም ውስጥ በአልጄሪያ 2 ለ1 ተሸንፏል። በአውሮጳ የእግር ኳስ ማኅበራት ኅብረት ጨዋታ ፖርቹጋል ባልተጠበቀ ሁናቴ በሜዳዋ በአልባኒያ ስትረታ፤ ማኅበሩን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀላቀለችው አዲሲቷ አባል ጂብራልተር በፖላንድ የግብ ጎተራ ሆናለች። ጀርመን ስኮትላንድን ረትታለች።