የሠማያዊ ፓርቲ ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ባካሄደው ሠላማዊ ሠልፍ መንግሥት እየተከተለው ነው ያለውን ብልሹ የአስተዳደር ሥርዓት፣ ሙስናና ደካማ የመሠረተ-ልማት አቅርቦት ያሻሽል ሲል ጠየቀ።

በአካባቢያቸዉ የሚገኝና ለእነሱ የዕለት ተዕለት ህይወት ትርጉም ያለዉ የደን ሃብት የምንጠራ አደጋ ባንዣበበበት ወቅት ዶቼ ቬለ ያነጋገራቸዉ የመዠንገር ማኅበረሰብ አባላት «መዠንገሮች ዉሃ ብቻ ሳይሆን ደግም ህይወት ነዉ» የሚል መመሪያ እንዳላቸዉ ገልጸዉልን ነበር።

5. መዝየም

ኢትዮጵያውያን አባቶችና ምእመናን በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም መንፈሳዊ ተጋድሎ ለመፈጸምና መንፈሳዊ ርስትን ለትውልድ ለማኖር ታላቅ መሥዋዕትነት ከፍለዋል፡፡ ይህንን የዘመናት ተጋድሎ የሚያሳይ አንዳች ሙዝየም ግን የለንም፡፡ የገዳሞቻችንን ታሪክ፣ የተጻጻፍናቸውን ደብዳቤዎች፣ በየጊዜው ከሀገር ቤት የተላኩትን መጻሕፍትና ሌሎች ንዋያተ ቅድሳት፣ የዘመናቱን አሻራ የሚያሳዩ የሥዕልና የፎቶ ግራፍ መረጃዎች፣ ካርታዎች፣ ተጓዦችና ታሪክ ጸሐፊዎች የከተቧቸው ማስረጃዎች፣ በየዘመናቱ የተሰጡ ስጦታዎችን የሚያሳዩ መዛግብት፣ የተሾሙ ራይሶችንና ሊቃነ ጳጳሳትን የሚያሳዩ ዝርዝሮችና ፎቶዎች፣ የተሳላሚዎችን ሁኔታ የሚያሳዩ ፎቶዎችና መዛግብት የተከማቹበት፤ ከዚያም አልፎ የእናት ቤተ ክርስቲያንን ማንነት፣ ታሪክና ቅርሶች የሚያሳይ አንድ ታላቅ ሙዝየም በደብረ ገነት ኪዳነ ምሕረት ግቢ ውስጥ ወይም በአካባቢው ያስፈልገናል፡፡

ይህ ሙዝየም ሦስት ጥቅሞች ይኖሩታል፡፡ በአንድ በኩል ከሁለት ሺ ዓመታት በላይ ያስቆጠረውን የቅድስት ሀገር ርስታችንን ታሪክ በተጨባጭ የምናሳይበት፣ ከንግግር የዘለለ ማስረጃ እንዲኖረንና ያንንም ለዓለም ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንድናሳይ ያደርገናል፡፡ ከኢየሩሳሌም ከተማ አንዱ የቱሪስት መዳረሻ በመሆንም የኢትዮጵያውያንን የተጋድሎ ታሪክ ለጎብኝዎች እናሳይበታለን፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ኢየሩሳሌም የመላው ዓለም አማኞች መናኸሪያ በመሆኗ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ለማስተዋወቂያ ወሳኝ መድረክ ይሆናል፡፡ ቀደም ብለን እንዳየነው ኢትዮጵያንና ቤተ ክርስቲያንዋን በተለይ ለምዕራቡ ዓለም ያስተዋወቋት የኢየሩሳሌም(በተለይም የዴር ሡልጣን) ገዳማት አባቶች ነበሩ፡፡

ሦስተኛ ደግሞ ለገዳሙ ተጨማሪ የገቢ ምንጭ ይሆናል፡፡ የዓመቱን ፋሲካ ጠብቆ ጧፍ ከመሸጥ ይልቅ ራቅ አድርጎ አስቦ ታሪካችንን የሚያሳዩ ፖስት ካርዶችን፣ ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱና ስለ ኢየሩሳሌም ገዳማት የተጻፉ መጻሕፍትን፣ የጎብኝዎች መመሪያዎችን(Tourist Guide)፣ ኢትዮጵያዊ ትውፊት ያላቸው ቅዱሳት ሥዕላትን፣ የላንቲካ ዕቃዎችን(የሀገሪቱን ባሕል፣ የእምነት ሥርትዓቷንና ታሪኳን የሚያሳዩ ሰሐኖች፣ ቲሸርቶች፣ ኩባያዎች፣ የወግ ዕቃዎች፣  ጌጣ ጌጦች) ለቱሪስቶች በመሸጥ ከፍተኛ ገቢ ለማግኘት ያስችላል፡፡

እስካሁን በታየው ልማዳችን ዕቃ ቤት እንጂ ሙዝየም በብዛት የለንም፡፡ በሀገር ቤት እንኳን ያሉን ሙዝየሞች ከታሪካችንና ከቅርሳችን ጋር ሲወዳደሩ ዓባይን በጭልፋ የሚያስብሉ ዓይነት ናቸው፡፡ በኢየሩሳሌም የሚገኙ አብዛኞቹ አብያተ ክርስቲያናት ሙዝየም ብቻ ሳይሆን የጥናትና ምርምር ተቋማት ጭምር እንዳሏቸው የኢየሩሳሌም የቱሪዝም መሥሪያ ቤት የሚያሳትማቸው የቱሪስት መርጃ መጻሕፍት ያሳያሉ፡፡ ሌላው ቀርቶ የቅርብ ዘመን ታሪክ ያላቸው አብያተ ክርስቲያናት እንኳን ቱሪስት እንደ ጎርፍ የሚፈስበት ሙዝየም አላቸው፡፡ ለተመራማሪዎችም ኢየሩሳሌምን የተመለከቱ መረጃዎችን በመሸጥ ገቢ ያገኛሉ፡፡

የአርመን ሙዝየም ሕንጻ
ወደ ኢየሩሳሌም ምእመናንን የሚያጓጉዙ ተቋማት ከገዳማቱ አስተዳደር ጋር በመመካከር ሊያከናውኗቸው ከሚገቡ ነገሮች አንዱ የሙዝየሙ ጉዳይ ነው፡፡ ‹ታሪክ እንደ ነጋሪው ነው› በሚል ያረጀ ብሂል ስለ ራሳችን ታሪክ ለእኛ እንኳን የሚገርመንን ዓይነት ያልነበረ ታሪክ እንደነበረ እየተደረገ፣ የነበረውም እየተዘነጋ እየቀረበልን መሆኑን ካየን ለቱሪስቶችማ ምን ሊነገር እንደሚችል መገመት ነው፡፡

ይህንን ሙዝየም እንዴት ባለ መንገድ ልናቋቁመው፣ ልናካሂደው ምን ምን እንዲሠራ ልናደርገው እንደምንችል በሚገባ በዓይን ዓይቶ ለመረዳት በግሪክ ፍጥሞ ደሴት የሚገኘውን የቅዱስ ዮሐንስ ገዳም መጎብኘቱ እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡ ያም ካልተቻለ በኢየሩሳሌም አሮጌው ከተማ የሚገኙትን የአርመንንና የግሪክን ፓትርያሪኬት ሙዝየሞች ማየቱ በቂ ሊሆን ይችላል፡፡

6. ሴሚናሪ

ምንም እንኳን የገዳማቱ መነኮሳት የቀድሞ አባቶች ገዳሙን የጠበቁት ተምረው አይደለም ቢሉም አባባሉም ስሕተት ነው፣ ትምህርትም የግድ ነው፡፡ የቀድሞ አባቶች አልተማሩም የሚለው ብሂል ከሁለት ነገሮች የሚመነጭ ነው፡፡ አንድ ካለማወቅ ሁለትም ከንቀት፡፡ የቀድሞ አባቶች ለትምህርት ታላቅ ቦታ እንደነበራቸው ባከማቿቸው መጻሕፍት ብቻ እንኳን ማወቅ ይቻላል፡፡ እንኳን የክርስትና መጻሕፍት የአይሁድ፣ የግሪክ፣ የሂንዱስታንና የእስልምና መጻሕፍትን ሳይቀር ወደ ግእዝ እየተረጎሙ አስቀምጠውልናል፡፡ ተተኪዎቻቸው እንደነ እርሱ ዕውቀት ወዳጆች መስለዋቸው፡፡ ታላቁ ንጉሥና የዴር ሡልጣን ገዳም ባለ ውለታ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ‹‹መጽሐፈ ብርሃን›› በተሰኘው መጽሐፉ ‹‹እስመ ጽሙዐን ለትምህርት ብሔረ ኢትዮጵያ ኄራን – ምርጦቹ የኢትዮጵያ ሰዎች ትምህርትን የተጠሙ ናቸው›› እንዳለው ኢትዮጵያውያን ትምህርትን የተጠሙና ለዕውቀት ማንኛውንም ዓይነት ዋጋ የሚከፍሉ ነበሩ፡፡

ዛሬ ባለው ዓለም ድጓ፣ ጾመ ድጓ፣ ቅኔ፣ ቅዳሴ፣ ዝማሬ፣ ትርጓሜና አቋቋም እጅግ አስፈላጊዎች ቢሆኑም ብቻቸውን ግን ወንዝ ሊያሻግሩን አይችሉም፡፡ ዛሬ በልዩ ልዩ የሀገራችንና የዓለም ቋንቋዎች ማስተማርና መጻፍ የሚያስፈልግበት፣ ጥንታዊ ሀብታችንን በዘመናዊ መንገድ ማቅረብ የሚጠየቅበት፣ ሕዝቡን ለመድረስ ልዩ ልዩ ሚዲያዎችን መጠቀም የግድ የሚልበት፣ ከትውልዱ ጋር ለመግባባትና የትውልዱን ጥያቄ ለመመለስ ሁለገብ ዕውቀት የሚያሻበት፣ ዘመን ነው፡፡

የኢየሩሳሌም ገዳማት አባቶችና እናቶች ከላይ በተጠቀሱት ነገሮች የሠለጠኑ፣ በሚገባ የታጠቁና በሁለት በኩል የተሳሉ ሰይፎች እንዲሆኑ ግድ ይላቸዋል፡፡ አንድም ‹‹መልክ ከእግዚአብሔር ሞያ ከጎረቤት›› ነውና ከጎረቤቶቻቸው ልምድ ለመቅሰም ስለሚችሉ፤ አንድም የትምህርት መርጃዎችን ከልዩ ልዩ ተቋማት ለማግኘት ቀላል ስለሆነ፤ አንድም በአንድ አካባቢ መኖራቸው በፈረቃ ለመማር ስለሚያስችላቸው፤ አንድም ልዩ ልዩ ቋንቋዎችን ለመማር ኢየሩሳሌም አመቺ በመሆኗ፡፡ ሌላው ቀርቶ በሀገር ቤት የሚገኙ መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶቻችንንም ከኢየሩሳሌም ትምህርት ቤት ጋር በማቀናጀት የተሻሉ ለሚባሉ ተማሪዎች ስኮላርሺፕ መስጠት ይቻላል፡፡

ዛሬ ዛሬ ከፍ አድርጎ ማሰብ እየጠፋ ነው መሰል የአባቶቻችን ሃሳብ አሜሪካና አውሮፓ መሄድ፣ ከግሪክ ንዋያተ ቅድሳት ማምጣት፣ ቤት መሥራት፣ ዘር መዝራት እየሆነ ነው፡፡ ነገ ቤተ ክርስቲያኒቱ ትፈልገኛለች፣ ነገ ወደ ኢትዮጵያ ኮሌጆች ሄጄ አስተምራለሁ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን እተረጉማለሁ፣ ሕዝቡን በወንጌል እደርሳለሁ፤ የመነኮስኩበትን ገዳም ኑሮና አሠራር አሻሽላለሁ፣ ቤተ ክርስቲያኔን በዓለም መድረክ አስጠራለሁ፣ ብሎ ከፍ አድርጎ የሚያስብ እያጣን ነው፡፡ ይህ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያናችን ጉዳት ነው፡፡

በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ የኢየሩሳሌም መነኮሳት የነበራቸውን ቦታ ባለፈው ጊዜ በመጠኑ ጠቅሰነዋል፡፡ የኢትተጵያ ታላላቅ ገዳማት አባቶች አብዛኞቹ ኢየሩሳሌም መጥተዋል፡፡ እዚህ ያዩትንና የሰሙትን ይዘው በሀገራቸው ተግብረውታል፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትንና ንዋያተ ቅድሳትን ወደ ሀገር አምጥተዋል፡፡ ሌላው ቢቀር አፈሩንና የዮርዳኖስን ጠበል እየያዙ በመምጣት ከገዳሞቻቸው አፈርና ጠበል ጋር አዋሕደውታል፡፡ እንደ ቅዱስ ላሊበላ ያሉትም ምድራዊትና ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን ከተመለከቱ በኋላ ‹ከመዝ ግበር› በተባሉት መሠረት የኢየሩሳሌምን አምሳል በሀገራቸው ሠርተዋል፡፡

ዛሬም ቤተ ክርስቲያን ከኢየሩሳሌም መነኮሳትና መነኮሳዪያት ብዙ ትጠብቃለች፡፡ በዕውቀት የበሰሉ፣ በቋንቋ የተካኑ፣ ዓለም ዐቀፋዊ ልምድ ያላቸው፣ በሁለት በኩል የተሳሉ ሆነው እንዲያገለግሏት፡፡ ለዚህ ደግሞ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሴሚናሪ ያስፈልጋል፡፡ የተቋሙን አመሠራረትና አሠራር ለመረዳት ከሌሎቹ ልምድ መቅሰም ነው፡፡ ወጭውን ለመሸፈን ደግሞ ምእመናን አንድም ሁለትም ተማሪ ስኮላርሺፕ እንዲሰጡ ማስረዳት ነው፡፡ ዛሬ ሰው ያጣንበት ዘመን ስለሆነ ሰው ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት ለመርዳት ምእመናን ዝግጁ ናቸው፡፡ ብቻ የቆረጠ፣ የገባውና፣ ዓላማ ያለው ሰው ይኑረን እንጂ፡፡

አሁን አሁን በዓለም ዐቀፍ መድረኮች ቤተ ክርስቲያንን ወክሎ በብቃት ሊሳተፍ የሚችል ሰው እያጣን ነው፡፡ በአብያተ ክርስቲያናት መካከል የእምነት ውይይት (Inter – church dialogue) ይደረጋል፤ በልዩ ልዩ እምነቶች መካከልም ውይይት ይደረጋል(Inter – faith dialogue)፣ የአፍሪካና የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ይደረጋል፤ የመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ጉባኤ ይደረጋል፤ በሌሎች የዓለም መድረኮችም የሃይማኖት አባቶች ይጋበዛሉ፤ ቅዱሳት መጻሕፍትን በመተርጎም ሥራም ከግሪክ፣ ከዕብራይስጥ፣ ከላቲንና ዐረብ ጋር ማነጻጸር ይጠይቃል፤ ለዚህ ሁሉ ትምህርትና ሥልጠና ወሳኝ ነው፡፡ ለዚህ ነው ኢየሩሳሌም ላይ አንድ ደረጃውን የጠበቀ፣ ሰው ሊያፈራ የሚችል፣ ሴሚናሪ ይኑረን የምለው፡፡

(ይቀጥላል) 

ኢየሩሳሌም

በነገው ስልፍም ይፈቱ ዘንድ ድምጹን ያሰማል!

ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹የተነጠቁ መብቶቻችን እናስመልሳለን›› በሚል ሚያዝያ 19 ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱ ይታወቃል፡፡ በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት ከምናነሳቸው ጉዳዮች አንዱና ዋነኛው ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሰልፉ ገዥው ፓርቲን ላይ የሠላ ትችት ስለሰነዘሩና ለህዝባቸው መረጃ ስለሰጡ ብቻ የሚደርስባቸውን ህገ ወጥ እርምጃ ያወግዛል፡፡

በሳምንቱ ውስጥ የህዝብን መብት ለማስመለስ ለጠራነው ሰልፍ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ 50 ያህል አመራሮችና አባላት በህገ ወጥ መንገድ ታስረዋል፡፡ በትናንትናው ዕለት የፓርቲያችን ሊቀመንበር (ማታ ተፈትተዋል)፣ ምክትል ሊቀመንበር፣ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በህገ ወጥ መንገድ መታሰራቸው ይታወቃል፡፡ በተመሳሳይ ወቅት የዞን ዘጠኝ አክቲቪስቶችና ሌሎች ጋዜጠኞችም ታስረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ሌሎችን ለማሰር ጥረት እየተደረገ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ይህን የገዥው ፓርቲ ከፍርሃት የመነጨ አምባገነናዊ እርምጃ በጽኑ ይቃወማል፡፡ በነገው ዕለትም በእነዚህ አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች ላይ የተደረገውን እስር የሚያወግዝ መሆኑን መግለጽ ይወዳል፡፡

ኑ ራሳችን ነጻ በማውጣት የአገራችን እጣ ፈንታ እንወስን!

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ስድስት ጦማሪያን እንዲሁም አንድ ጋዜጠኛ ትናንት ከቀትር በኃላ አዲስ አበባ ውስጥ መታሰራቸው ተሰማ። ዞን «9» በመባል የሚታወቀዉ የጦማርያን ስብስብ አባላት ላይ ላለፉት ሰባት ወራት ከፍተኛ ክትትል ሲደረግ መቆየቱም ተመልክቶአል።

መፍቀሬ-ሩስያ ታጣቂዎች ይዘው ያቆዩዋቸውን የተወሰኑ የ«ኦሴ» ታዛቢ ቡድን አባላት ለመገናኛ ብዙኃን እይታ አቀረቡ። ከተያዙት ታዛቢዎች መካከል አንድ ስዊድናዊ የስኳር ህመም ስላለበት መለቀቁን ታጣቂዎቹ አስታውቀዋል።

የአቡነ ማትያስ የመነጋገርና የመደራደር አቅም ለጉብኝቱ መሰረዝ በምክንያትነት ተጠቅሷል የግብፁ ፓትርያርክ በስድስት ወራት ውስጥ ሦስት ጊዜ የጉብኝት ጥያቄ አቅርበዋል የአቡነ ታዎድሮስ ተደጋጋሚ ውትውታ ጉዳዩ ከሕዳሴው ግድብ ጋራ መያያዙን አመላክቷል የጉብኝቱ መሰረዝ በአቡነ ታዎድሮስ ጥያቄ እንደኾነ መዘገቡ ከመቅለል መጥቅለል እንዲሉ ነው ‹‹መንግሥት የግብፆችን ያህል ቤተ ክርስቲያኒቱን የዲፕሎማሲው አካል አላደረገም›› (ፋክት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፵፫፤ ፳፻፮ ዓ.ም.) …

 ዞን ዘጠኝ  አሁን  በደረሰው መረጃ መሰረት ጋዜጠኛ እና የዞን9 ዘመቻዎች ንቁ ተሳታፌ የነበረችው የቅርብ ጓደኛ ኤዶም ካሳዪ በፀጥታ ሃይሎች ቤቷ ተፈትሾ ወደ ማእከላዊ ምርመራ ትወስዳለች ! ዞንዘጠኝ የኤዶም ካሳየ በምንም አይነት ህገወጥ ተግባር ውስጥ ተሳትፋ እንደማታውቅ ነገር ግን ከደህንነት ሃይሎች ከፍተኛ ወከባ ሲደርስባት እንደቆየች እያረጋገጠ መንግስት እሷንም ሆነ ሌሎች አባላትን በአስቸኳይ እንዲፈታ በድጋሚ ጥሪውን ያስተላልፋል!

According to the latest information we got, Journalist, campaigner and close friend of Zone9 have been arrested and her house was searched this late morning. For the last few months Edom had been in serious interrogation and surveillance from “Intelligence officers” questioning her details on the activities of the Zone9. Zone Nine again wants to confirm that Edom and other Bloggers has never been a part of any illegal activity and we request the government to release all immediately.


 

ትላንትና ማምሻውን በመንግስት የጸጥታ ሃይሎች በቁጥጥር ስር ዋሉት 6 የዞን 9 አባላትና ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ማእከላዊ ምርመራ እንደሚገኙ ተረጋግጧል፡፡ ታሳሪዎቹን ቤተሰብ ማየት የማይችል ሲሆን ስንቅ በማቀበል ብቻ ተመልሰዋል፡፡ በተያዙበት ሰአት ቤታቸውና ቢሮአቸው የተፈተሸ ሲሆን መጽሃፍት ጋዜጦች እና ላፕፖቻቸውም ጭምር እነደተወሰዱ ማወቅ ችለናል፡፡ 

በድጋሚ የዞኑ አባላትና ወዳጆች ምንም አይነት ህገ ወጥ ስራ ላይ ያልተሰማሩ በመሆናቸው መንግስት እርምት ወስዶ በአስቸኳይ አንዲፈታቸው እንጠይቃለን! 

Zone9 has confirmed that Six Zone9 bloggers and journalist Tesfalem Woldeyes are in Addis Ababa central investigation center (meakelawi) since their arrest last night. during the arrest their house was searched and police took laptops, Newspapers and books from their home. Families were not allowed to meet them.We believe members and friends of Zone Nine have nothing to do with any illegal activities and we again request the government to release them immediately. 

#FreeZone9bloggers #FreeTesfalem #Ethiopia

ቀን 18/08/ 2006 ዓ.ም

ውድ የሚዲያ ማህበረሰብ አባላት፡- ባለፉት 23 ዓመታት ህወሓት/ኢህአዴግ በህገ መንግስቱ የሚዲያ ነጻነት እንደሚፈቀድ ቢደነግግም በተግባር ግን የራሱን ፕሮፖጋንዳ ከሚነዛባቸው ሚዲያዎች ውጭ ሌሎቹን ሲዘጋና ሲያሸማቅቅ ኖሯል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ህዝባችን ከገዥው ፓርቲ ፕሮፖጋንዳ ውጭ አማራጭ መረጃ ማግኘት አልቻለም፡፡ ጋዜጠኞች እየታሰሩ፣ እየተሰደዱ፣ ሚዲያዎች እየተዘጉም ቢሆን የተቻላችሁን ያህል ለህዝብ መረጃ ለማድረስ የሚዲያው ማህበረሰብ አባላት ለምታደርጉት ሁሉ ከፍ ያለ ክብር አለን፡፡ የታፈነውን የህዝብ ድምጽ ለማሰማት የምታደርጉትን ጥረትም እናበረታታለን፡፡ ሆኖም አሁንም ቢሆን በገዥው ፓርቲ አፋኝነት ምክንያት ህዝባችን የሚገባውን መረጃ እያገኘ አይደለም፡፡ እናንተም በሰበብ አስባቡ ጫና እየደረሰባችሁ እንደሆነ ፓርቲያችን ይገነዘባል፡፡

ገዥው ፓርቲ ላይ የሰላ ትችት የሚያደርሱ ጋዜጠኞች ‹‹አሸባሪ›› ተብለው ታስረዋል፡፡ ጋዜጦችና መጽሄቶች በስርዓቱ ተዘግተዋል፡፡ በርካታ ጋዜጠኞች አገራቸውን ጥለው ተሰደዋል፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ድብደባ፣ ማስፈራሪያና ዛቻ ደርሶባቸዋል፡፡ እየደረሰባቸውም ነው፡፡ ገዥው ፓርቲ በሚያደርስባቸው ቀጥተኛም ሆነ ተዘዋዋሪ ጫና ከገበያ ወጥተዋል፡፡ በአጠቃላይ በአሁኑ ወቅት ለህዝባችን አማራጭ መረጃ የሚያደርሱ ሚዲያዎችና የሚዲያው ማህበረሰብ መብቶቻቸውን ተነጥቀው አደጋ ላይ ወድቀዋል፡፡

አማራጭ መረጃ ለዴሞክራሲና ለልማት ቀዳሚውን ሚና እንደሚጫወት የሚያምነው ፓርቲያችን ይህን የመብት ረገጣና አፈና ሲቃወምና ሲታገል ቆይቷል፡፡ አሁንም በጠነከረ መልኩ ይቃወማል፡፡

ፓርቲያችን ሀሳብን በነጻነት የመግለጽን ጨምሮ የተነጠቁትን መብቶቻችን ለማስመለስ በመጣሩ አመራሮቹና አባላቱ በህገ ወጥ መንገደ እስር ቤት በሚገኙበት ተመሳሳይ ወቅት የዞን ዘጠኝ ወጣቶች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህም ከመቸውም ጊዜ በላይ ጭቆናው እንደመረረ እና ሁሉን ማህበረሰብ ያቀፈ ትግል እንደሚያስፈልግ ዋነኛ ማሳያ ነው፡፡ ከዚህ የመረረ ጭቆና ህዝባችንን ነጻ ማውጣት የምንችለው እኛ ህዝቡን ማደራጀትና ማንቀሳቀስ የሚዲያ ማህበረሰቡም መደረጃውን ለህዝባችን ማድረስ ሲችል ብቻ ነው፡፡

ፓርቲያችን ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ጨምሮ ገዥው ፓርቲ ከኢትዮጵያውያን የነጠቃቸውን መብቶች ለማስመለስ ተቃውሞ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ የሚዲያው ማህበረሰብ ይህን የተቃውሞ ሰልፍ ሂደት ለህዝብ በማስተላለፍ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የታመነ ነው፡፡ በመሆኑም መብቶቻችን በህዝብ ትግል ይመለሱ ዘንድ እናንተም የተለመደው የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ ጥሪያችን እናስተላልፋለን፡፡

መረጃ ኃይል ነውና በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ የህትመትም ሆነ የብሮድካስት ውጤቶች የተነጠቁትን መብቶቻችን፣ የሰላማዊ ሰልፉን ሂደት፣ በሂደቱ በፓርቲያችንና በህዝቡ ላይ የሚደርሰውን በደል እና ሰላማዊ ሰልፉን ለህዝብ በማድረስ ግዴታችሁን እንድትወጡ አደራ እንላለን፡፡ በተለይ ሌሎች ሚደያዎች በታፈኑበት በአንጻራዊነት የህዝብ ድምጽ በመሆን ላይ በሚገኘው ፌስ ቡክ በኩል መረጃዎችን ለህዝብ በማድረስ ቀላል የማይባል ጫና መፍጠር የሚቻል በመሆኑ አጋጣሚውን በመጠቀም መብታችን ለማስመለስ እንድንታገልና በሰልፉም እንድንገኝ አደራችን እናስተላልፋለን፡፡

ኑ ራሳችን ነጻ በማውጣት የአገራችን እጣ ፈንታ እንወስን!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ልጅ ተክሌ (ቶሮንቶ)

ዘመቻ ነቀምትና ዘመቻ ኢትዮጵያ

፩-      የሲያትሉ ባተሌ ወዳጄ ደውሎ፤ “አንድነት የአዲስ አበባውን ሰልፍ ፈቃድ ተከልክሏል፡፡ ስለዚህ ምን ርምጃ ይውሰድ” በሚል ጥያቄ ሲያደርቀኝ ነበር፡፡ ሳንግባባ ተለያየን፡፡ ከሞላ ጎደል እሱ የሚለው፤ “ቢከለከሉም ገፍተው ይውጡ፡፡ ምክንያቱም፤ በተከለከሉ ቁጥር እሺ ብለው የሚገቡ ከሆነ፤ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያጣሉ፡፡ ገፍተው ከወጡ ግን፤ መንግስትም ጨክኖ ርምጃ አይወስድም፤ ቢወስድም ግን፤ ትግሉን ያበረታል፤ ሌሎችንን ይቀሰቅሳሉ” ነው፡፡ ኢፍትሀዊ ህግን መጋፈጥ ፍትሀዊነት ነው የሚለውን ይትበሀል ይዞ መሰለኝ የሞገተኝ፡፡ እኔ ደግሞ “የለም ሁሉንም ሰብስቦ ያስራቸዋል፤ ካሰራቸው ደግሞ ሌሎች ሰልፈኞች መውለድ አመታት ይፈጃል፡፡ ስለዚህ ይታገሱ፤ ሲሆን ሲሆን ወደፍርድቤት ይሂዱ፤ ወይም ሌላ ጥበብ ፈጥረው ሂደቱን ያጡዙት፡፡ እንጂ፤ አሁን ገፍተው ሰልፍ ቢወጡ ትግሉን ማጨናገፍ፤ ማስወረድ ነው” ብዬ ሞገትኩ፡፡ አልተስማማንም፡፡  የዚህ ጽሁፍ አብይ ዓላማም ማስታወቂያና ማስታወሻ ቢሆንም፤ የኛ የወጤዎቹ (ዳያስፖራ) ሚና የት ድረስ ነው? ድርጅቶቻችንስ ከመፈክር የዘለለ አመራር ለመስጠት ምን ሸበባቸው? በማለት፤ ከቅዳሜ ኤፕሪል 26ቱ የቶሮንቶ-ነቀምት ዝግጅት ማስታወሻ ጎን ለጎን፤ ሌሎች ጉዳዮችን በስሱ ያሻሻል፡፡ ከዚያ በፊት ግን፤

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከመቶ ዓመታት በፊት ወደ ኢየሩሳሌም የመጡ አባቶች

click here for pdf

ከዚህ በፊት ለኢየሩሳሌም ገዳማችን ሊደረጉ የሚገቡ ዐሥር ነገሮችን አቀርባለሁ ባልኩት መሠረት ሦስቱን አቅርቤያለሁ፡፤ አራተኛውን እነሆ

4. ጠንካራ የምልመላ መሥፈርት ይኑር

አባቶቻችን ወደ ኢየሩሳሌም ጉዞ ሲያደርጉ ሁለት ሺ ዓመት አልፏቸዋል፡፡ በየዘመናቱ ከአውሮፓና ከእስያ የመጡ ተጓዦችና ታሪክ ጸሐፊዎች የኢትዮጵያውያን መነኮሳትን የፈቃድ ድህነት፣ የጸሎት ትጋት፣ ተአምር አድራጊነት፣ ሊቅነት፣ መንፈሳዊነትና ፍጹማዊ ምናኔ በአድናቆት ጽፈውታል፡፡ እነዚያ መነኮሳት ወደ ቅድስት ሀገር የመጡት ለአራት ዓላማዎች ነበር፡፡

  1. ከቅዱሳን ቦታዎች በረከት ለማግኘት፣

  2.  ፍጹም የሆነ ምናኔን ለመኖር፣

  3. ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ዕውቀትን ለመገብየትና

  4. የኢትዮጵያውያንን ቅዱሳት መካናት ለመጠበቅ፡፡

ያኔ የዐረብ ሀገሮችን፣ የሱዳንንና የሳዑዲን በረሃዎች፣ የዐረቦችንና የቱርኮችን አገዛዝ፣ ውኃ ጥሙንና መከራውን አልፎ ለመምጣት መንፈሳዊ ጽናትና የጸና እምነት ያስፈልግ ስለነበር ለክፉ የሚሰጥ ሰው ይህንን ሁሉ ችሎ ወደ ኢትዮጵያውያን ገዳማት አይመጣም ነበር፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን በመነኮሳቱ መካከል መለያየትና መከፋፈል እንደነበረ እቴጌ ጣይቱ መነኮሳቱን ‹‹እባካችሁ አትጣሉ፣ አንድ ሁኑ›› እያሉ የጻፉት ደብዳቤ ይነግረናል፡፡ ለገዳሙ በጎ የሠሩ አንዳንድ አባቶችም ዕጣ ፈንታቸው መሰደድ፣ መገፋትና መባረር እንደነበረ የነ አባ ወልደ ሰማዕት ታሪክ ይነግረናል( በነገራችን ላይ የአባ ወልደ ሰማዕትን አስደናቂ ታሪክና በገዳሙ መነኮሳት የደረሰባቸውን ግፍ በቀጣይ ሳምንት እመለስበታለሁ፡፡ በዘመናቸው የዓይን ምስክሮች የነበሩ ሁለት ሰዎች የጻፉትን፣ ሁለት ሌሎች ሰዎች ደግሞ ከእርሳቸው ሰምተው ለትውልድ ያስቀመጡትን ታሪክ አግኝቻለሁ)

ዛሬ መነኮሳትን ለኢየሩሳሌም ገዳማት የሚመድበው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ነው፡፡ ስለዚህም በመንገድ የሚደርስ ፈተና፣ በኑሮ የሚደርስ ችግር፣ ረሃብና እርዛት የለም፡፡ መከራ የሚያጠራው ሰውም የለም፡፡ ለዚህም ነው ወደ ኢየሩሳሌም ገዳማት ለሚመደቡ አባቶችና እናቶች ጠንካራ የምልመላ መሥፈርት ያስፈልጋል የምንለው፡፡ መንፈሳዊነታቸው፣ ለጸሎት ያላቸው ትጋት፣ ዐቅመ ደካሞችን ለመርዳት ያላቸው ፍላጎትና ብርታት፣ ለመማርና ዕውቀት ለመሸመት ያላቸው ጉጉትና ዐቅም፣ በዓላማቸው ለመጽናትና የመጡበትን ግዳጅ ለመፈጸም ያላቸው ዝግጁነት መታየት አለበት፡፡

ከዘረኛነት የነጹ፣ ነጋ ለኪዳን መሸ ለቁርባን የሚሉ፣ ቅዳሴና ሰዓታት የማይሰለቻቸው፣ በሕይወት ለሌሎች ምሳሌ የሚሆኑ፣ ንጽሕናቸውንና ቅድስናቸውን ጠብቀው በመኖር ነገ ቤተ ክርስቲያኒቱ ለምትፈልጋቸው መዓርግ ዝግጁ የሆኑ፣ አፍቅሮ ነዋይ የራቀላቸው፣ ቤት ልሥራ ዘር ልዝራ የማይሉ እንዲሆኑ ጠንካራ የመመልመያ መሥፈርት ያስፈልጋል፡፡

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የኢየሩሳሌም መነኮሳት የሠሯቸው ሥራዎች የሚያስደንቁ፣ የሚያኮሩና እንኳን እኛ ልጆቻቸውን ሌሎችንም ያስገረሙ ነበሩ፡፡ ዛሬ አንዳንድ መነኮሳት ‹‹እኛ ለጸሎት እንጂ ዕውቀት ለመሸመት ወይም ተግባረ ዕድ ለመሥራት ኢየሩሳሌም አልመጣንም›› ቢሉም በቤተ ክርስቲያናችን ታሪክ ግን ዕውቀትና ገዳማዊ ሕይወት ተለያይተው አያውቁም፡፡ ሌላው ቀርቶ በ13ኛው መክዘ ምርጦቹ ስምንት መቶ መነኮሳት በመንፈሳዊ ሕይወት በስለው፣ በምንኩስና ተክነው፣ በቅዱሳት መጻሕፍት ዕውቀት ተራቅቀው የወጡት ከሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም መሆኑን መርሳት አይገባም፡፡ መካከለኛዋን፣ ምዕራብና ምሥራቅን ብሎም ደቡብ ኢትዮጵያን ተካፍለው ያስተማሩት አሥራ ሁለቱ ንቡራነ ዕድ ተምረውና ተቀርጸው የወጡት ከደብረ ሊባኖስ ነበር፡፡ በኤርትራና በትግራይ ያስተማሩት አምስቱ ከዋክብትና ሰባቱ ከዋክብት የሚባሉት ሐዋርያውያን የተገኙት ከደብረ በንኮል ነበር፡፡


ታላላቅ የቤተ ክርስቲያናችን ቅዱሳት መጻሕፍት ከግሪክ፣ ከዐረብኛ፣ ከዕብራይስጥና ከላቲን ወደ ግእዝ የተተረጎሙት በዴር ሡልጣን መነኮሳት ትጋት መሆኑ ተረስቶ ቋንቋ አለማወቅ ዛሬ አንዳንዶቹን ያኮራቸዋል፡፡ በቅዱሳት መጻፍት የአንድምታ ትርጓሜ ላይ የኢየሩሳሌም ገዳማት መነኮሳትን አስተዋጽዖ ለማወቅ የእሥራኤልን ቦታዎች ከጎንደር ቦታዎች አነጻጽረው የተረጎሙበትን ዘይቤ ማየቱ ብቻ በቂ ነው፡፡ ወደ ኢየሩሳሌም ይመጡ የነበሩት አባቶች ጸሎት ብቻ አልነበረም ተግባራቸው፡፡ ዙሪያ መለስ ነበሩ፡፡ በዐፄ ናዖድ ዘመነ መንግሥት(1487-1500 ዓም) ወደ ኢየሩሳሌም ከመጡት የደብረ ብሥራት ዜና ማርቆስ አሥራ ሁለት አባቶች አንዱ የሆነው አባ በኃይለ ማርያም፣ በተዋሕዶ እምነቱ ምክንያት ለደረሰበት ተዋርዶ ከካቶሊካዊው  ሰው ጋር በኢየሩሳሌም አደባባይ ለመከራከር ሲጠይቅ ዳኛው ‹‹በምን ቋንቋ ትከራከረዋለህ?›› ብሎ ሲጠይቀው ‹‹በዐረብኛ ወይም በዕብራይስጥ›› ሲል መለሰለት፡፡ ዳኛውም ‹‹እንዴት እነዚህን ቋንቋዎች ልታውቅ ቻልክ›› ብሎ በአድናቆት ሲጠይቀው ‹‹ወአነ አአምር በልሳነ ዓረብ ወዕብራይስጥ ፍካሬሆን ለመጻሕፍተ ሕግ ወነቢያት እስመ ተምህርኩ እም ኀበ መምህር ዐቢይ ኢሳይያስ በትእዛዘ ንጉሥ ናዖድ ፈራሄ እግዚአብሔር ዘምስለ ዕንባቆም እኅወ መምህር ዐቢይ ዘስሙ እንድርያስ – እኔም የሕግና የነቢያት መጻሕፍትን ትርጓሜያቸውን በዐረብና በዕብራይስጥ ቋንቋ ዐውቃለሁ፡፡ እግዚአብሔርን በሚፈራ ንጉሥ በናዖድ ትእዛዝ ከታላቁ መምህር ከኢሳይያስ ዘንድ የእንድርያስ ወንድሙ ከሚሆን ከዕንባቆም ጋር ተምሬያለሁና፡፡›› አለው ይላል ገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ከመካከለኛው ዘመን በኋላ የዕብራይስጥና የዐረብኛ ቋንቋ በሦስት ቦታዎች ይሰጡ ነበር፡፡ ደብረ ሊባኖስ(ሸዋ)፣ ደብረ ማርያም(ጎንደር) እና ማኅበረ ሥላሴ(ጎንደር)፡፡ ብዙዎቹ መነኮሳት በእነዚህ ቦታዎች ገብተው ቋንቋውን አጥንተው ነበር ወደ ኢየሩሳሌም የሚመጡት፡፡ የደብረ ማርያሙን የዕብራይስጥ መጽሐፍ እኔም አይቼዋለሁ፡፡


ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ እንደ ጻፉትና ዛሬም በቫቲካን ቤተ መዛግብት እንደምናገኘው ታሪክ በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን የዴር ሡልጣን መነኮሳት በፍሎሬንስ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ተካፍለው ነበር፡፡ ጉባኤው የተካሄደው በላቲን ቋንቋ ነበር፡፡ ኢትጵያውያን መነኮሳትም ጉባኤውን የተሳተፉት በላቲን ቋንቋ ነበረ፡፡ በነገራችን ላይ አርመኖች የራሳቸውን ፊደል እንዲፈጥሩ የረዷቸው በዴር ሡልጣን የነበሩ ኢትዮጵያውያን መነኮሳት ናቸው፡፡ የአርመንን ፊደል የፈጠረው መነኩሴ የኖረው በዴር ሡልጣን ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስን ወደ አርመንኛ ሲተረጉምም የረዱት ኢትዮጵያውያን ነበሩ፡፡ በዚህም ምክንያት የግእዝ ፊደልን የሚመስሉ ፊደሎችና የግእዝ ቃላት በአርመንኛ ቋንቋ ውስጥ በብዛት ይገኛል፡፡

‹‹ቄሱ ዮሐንስ – ፐሪስተር ጆን›› በሚል ስያሜ ኢትዮጵያን ሲፈልጉ የኖሩት የ14ኛው፣ 15ኛውና 16ኛው የአውሮፓ አሳሾች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ መረጃ ያገኙት ከኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት መነኮሳት ነበር፡፡


ይህንን ሁሉ የማነሣው ቀደምት አባቶቻችን እንዴው ሲጸልዩና ርስት ሲጠብቁ ብቻ እንደኖሩ አድርጎ የመመልከት ደካማ አስተሳሰብ በኢየሩሳሌማውያን ላይ ስለሚታይ ነው፡፡ አባቶቻችንና አባቶቻችሁ እንዲያ ብቻ አልነበሩም፡፡ ሌላው ቀርቶ ከራሳቸው አልፈው የሌሎች መመኪያ ለመሆን የበቁና በሌሎች ሀገሮች ገዳማትን የመሠረቱ አባቶችም ነበሩ፡፡ ሶርያውያን ‹‹ሞሰስ – አል – ሐበሽ – ኢትዮጵያዊው ሙሴ›› ብለው የሚጠሩት በ6ኛው መክዘ የነበረው የዴር ሡልጣን መነኮስ በሶርያ ከታወቁት የገዳማት መሥራቾች አንዱ ነው፡፡ ታሪኩ የንጉሥ ልጅ እንደነበር ይገልጣል፡፡ የአርመን ቤተ ክርስቲያን የምታከብራቸው አቡነ ኤዎስጣቴዎስም በዴር ሡልጣን ኖረው ነው ወደ አርመን የተጓዙትና በዚያ ያረፉት፡፡


የኢየሩሳሌም መነኮሳት ለሀገራቸው ያበረከቱት መጻሕፍትን ብቻ አልነበረም፡፡ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችም ወደ ኢትዮጵያ ይገቡ ከነበሩበት መንገድ አንዱ ከኢየሩሳሌም በሚመጡ መነኮሳት አማካኝነት ነበር፡፡ እነ አቡነ ዕዝራ በ16ኛው መክዘ ኢየሩሳሌም ኖረው ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ የውኃ ወፍጮ ይዘው በመምጣት ነበር ለገዳማቱ ያስተዋወቁት፡፡የግራኝ ጦርነት ተከታትሎ ተነሥቶ ተክኖሎጂው ባይስፋፋም አባታችን ግን ጥረት አድርገው ነበር፡፡


የእነዚህን አባቶች ብቃት፣ ዕውቀትና ትጋት ስናይ ዛሬ ያለንበትን ደረጃ መመዘን እንችላለን፡፡ ለዚህም ነው በኢየሩሳሌም ገዳማት የሚመደቡ አባቶች የቀደሙትን ደረጃ የሚያስጠብቁ፣ የቤተ ክርስቲያንን መልካም ገጽታ የሚገነቡ፣ የኢትዮጵያን በረከት ለዓለም፣ በሌሎች የሚገኘውን ልምድ ደግሞ ለኢትዮጵያ የሚያስተላልፉ እንዲሆኑ በሚገባ ተመርጠውና ተመዝነው መመደብ አለባቸው የምንለው፡፡ በኢየሩሳሌም የምንወዳደረው ከግብጾች፣ ከአርመኖች፣ ከግሪኮች፣ ከላቲኖች፣ ከሶርያኖች ጋር ነው፡፡ ለመሆኑ ትናንት ከግሪክ ቀጥላ በፕሮቶኮል ደረጃ 2ኛ የነበረችው ኢትዮጵያ ዛሬ ስንተኛ ናት? የእሥራኤልን የፕሮቶኮል ዶክመንት ያየ ያውቀዋል፡፡  


እንዴት ነው አሁን ለቅዳሴና ለሰዓታት ያለው ፍላጎት? እንዴት ነው ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመማር ያለው ትጋት?  እንዴት ነው የእጅ ሥራ ሠርቶ ገዳሙን ለመርዳት ያለው ሩጫ? (የገዳማውያን አንዱ ተግባር ተግባረ ዕድ አይደለም እንዴ? ለታላቁ እንጦንስ ቅዱስ ሚካኤል ሰኔል መታታት ለምን አስተማረው) እንዴት ነው በኢትዮጵያ የሚገኙ ገዳማትን ለመርዳት ያለው ትጋት? ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ ያለው ጽናት?መንኖ ጥሪት ሆኖ ለመኖር ያለው ተጋድሎ? እውነት ሙሉ በሙሉ በቁሪት ነው ገዳሙ የሚተዳደረው?ለወር ጉርስ ለዓመት ልብስ በዶላር የሚከፈላቸው ባለ ቁሪቶች በኢትዮጵያ ገዳማት አሉ?እነ መምህር ወልደ ሰማዕት በኢየሩሳሌም ከተማ ለገዳማቱ ነበር ቤት የሠሩት፣ ዛሬስ የት ነው ቤቱ እየተሠራ ያለው?የዚህ ሁሉ አንዱ ችግር ከመምረጫ መመዘኛው ነውና እንደገና ቢታይ፡፡


ለመሆኑ በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ገዳማት ጋብቻ የሚከናወነው በተክሊል ነው? ለመሆኑ የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ከቅዳሴ በኋላ ጋብቻ በቢሮ ውስጥ እንዲደረግ ይፈቅዳል? ቤተ ክርስቲያንስ የኦርቶዶክስ አማኝ ያልሆኑትን ለማጋባት ሥርዓቷ ይፈቅድላታል?የእሥራኤልስ ሕግ ይፈቅዳል? ቤተ ክርስቲያን የማዘጋጃ ቤትን ሥራ መሥራት ትችላለች?ይኼ ሁሉ ለምን መጣ? ለእምነት ሳይሆን፣ ለሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ሳይሆን ለሌሎች ነገሮች ትኩረት ከመስጠት፡፡ ‹‹ሕግ ይወጽዕ እም ጽዮን›› ነበር፡፡ አሁን ግን በጽዮን ሕግ እየጠፋ ነው፡፡ ለዚህ ነው ወደ ኢየሩሳሌም የሚመጡ አባቶችን የመላኪያ መሥፈርቱ ይጥበቅ፣ ቅድሚያ ለሃይማኖት፣ ለሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንና ለጽድቅ የሚሰጡ አባቶችና እናቶች ይምጡ የምንለው፡፡


(ይቀጥላል)


ኢየሩሳሌም

ዛሬ አርብ ሚያዝያ 17 ቀን 2006 አመሻሹ ላይ 11፡20 ገደማ ስድስት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን አባላት የሆኑት ጓደኞቻችን በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች ከያሉበት ተይዘዋል፡፡ እነርሱም ናትናኤል ፈለቀ፣ በፍቃዱ ሀይሉ፣ አጥናፍ ብረሀነ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ ዘላለም ክብረት እና አቤል ዋበላ ናቸው፡፡ ጦማርያኑን ጓደኞቻችን ለማሰር የመጡት አካላት የማሰሪያና የመፈተሻ የፍርድ ቤት ፈቃድ የያዙ መሆናቸውን ሰምተናልአ መደበኛ የሆነው “ዞን 9” የጦማርያን ስብስብ አባላት ሚያዚያ 15፣2006 በዋጣነው መግለጫ ላለፉት ሰባት ወራት የዞኑ አባላት ከፍተኛ የሆነ ክትትል ሲደረግባቸው እንደነበር በጠቅላላው የተጠቆመ ሲሆን ክትትሉ የተወሰኑ የቡድኑን አባላትና የቅርብ ወዳጆችን ጭምር ያካተተ ነበር፡፡ አሁን በመንግስት የተወሰደው እርምጃ የዞኑን ተመልሶ ወደ ስራ መግባት ተከትሎ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል ሆኖም የዞን 9 አባላትና ወዳጆች በምንም አይነት ህገ ወጥ ተግባር ላይ ተሰማርተው እነዳልነበር ለማረጋገጥ እንወዳለ፡፡ በመሆኑም የታሰሩ የዞኑ አባላትና ወዳጆች በአስቸኳይ እንዲለቀቁ እንጠይቃለን፡

Six members of Zone Nine, group of bloggers and activists are arrested today late in the afternoon at 5:20 pm by security. Team members Befeqadu Hailu, Atnaf Berahane, Mahlet Fantahun, Zelalem Kiberet, Natnael Feleke and Abel Wabela are all under custody on arrest warrant.
The arrest comes immediately after the bloggers and activists notified their return to their usual activism on April 23, 2014 after their inactivity for the past seven months. On their return note the group has indicated that they have sustained a considerable amount of surveillance and harassment. They have indicated that one of their reasons for their disappearance from activism is the harassment they have been receiving from government security agents.
We believe members and friends of Zone Nine have nothing to do with illegal activities and we request the government to release them immediately.

Zone9.

ሰሞኑን ናይሮቢ ውስጥ እየታየ ያለውን በስደተኞች ላይ የሚካሄድ አፈሣና እሥራት ተከትሎ ወደ ሰባ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ መደረጉን በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡

ከቪኦኤ ጋር የስልክ ቃለ ምልልስ ያደረጉት በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የቆንስላና የዳያስፖራ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ መለስ ዓለም ተክኤ የኬንያ መንግሥት እርምጃውን እየወሰደ ያለው ስደተኞችን ለማሳደድ ብሎ ሳይሆን በፀጥታ ችግሩ ምክንያት ነው – ብለዋል፡፡

ኬንያ ውስጥ ኢትዮጵያዊያን በተለያየ መንገድ እንደሚኖሩ የገለፁት አቶ መለስ እስከአሁንም ጥቃት የተፈፀመበት ኢትዮጵያዊ መኖሩን እንደማያውቁ አመልክተዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

 

“በአራቱ የፖለቲካ እሥረኞች ላይ የቀረቡ ክሦች እንዲሠረዙ ትዕዛዝ የሰጠሁት የደቡብ ሱዳኑን የሰላም ንግግር ሂደት ለማፋጠን ነው” ሲሉ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ ጁባ ላይ በተጠራ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሲናገሩ በአራቱ እሥረኞች የቀረቡ ክሦች እንዲሠረዙ ከአካባቢው ሃገሮች ጫና ሲደረግባቸው መቆየቱንም ተናግረዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

«የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ» የሚል ስያሜ እንዳለው የጠቀሰው ማኅበር ሕጋዊ ምሥረታ ባካሂድም የፌዴራል በጎ-አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ኤጀንሲ ሕጋዊ ዕውቅና ነፈገኝ ሲል አማሯል።

በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ-መንግሥት በኢትዮጵያናኤርትራ ላይ ከፍተኛ ትኩረት አድርጎ እንደሠራ ይጠቀሳል። አማርኛና ትግርኛን ጨምሮ የተለያዩ ቋንቋዎችም ሊቅ ነበር፤ ስዊድናዊዉ ዶ/ር ዮሐንስ ኮልሞዲን።

የደቡብ አፍሪቃ ህዝብ ነፃነቱን ካገኘ ከ20 ዓመት በኋላ የሀገሪቱ ወጣቶች ለመሆኑ ምን ያህል ተዋህደው እየኖሩ ነው? ብዙዎችእንደሚሉትግን ከሆነ አሁንም በሀብታም እና ደሀ ፣ በጥቁር እና ነጭ መካከል ልዩነቱ በሰፊው ይስተዋላል።

ፖሊስ የሰልፉን ኃላፊነት እንደማይወስድ አስታወቀ የአዲስ አበባ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነሩ በትናንትናው ዕለት ‹‹እንነጋገር!›› ያላቸውን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች በዛሬው ቀን ቢሮው በሄዱበት ወቅት ‹‹ሙሉ በሙሉ የሰፉን ኃላፊነት ትውስዳላችሁ!›› እንዳላቸው የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴዎች ገልጸዋል፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ በኩል የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ብርሃኑና ምክትል ሰብሳቢው አቶ ስለሽ ፈይሳ የቀረቡ ሲሆን ‹‹እኛ ለፖሊስ ያሳወቅነው በሰልፉ ወቅት ሊፈጠሩ የሚችሉ ችግሮችን እንዲቆጣጠር ነው፡፡ እኛ ሀላፊነት ልንወስድ የምንችለው ይዛናቸው ለምንወጣው ጽሁፍና ለምናስተላልፈው መልዕክት ብቻ ነው፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት ሰልፉን ሊያደናቅፉ የሚመጡ አካላት ቢኖሩ ይህን ኃላፊነት ሊወስድ የሚገባው ፖሊስ ነው›› የሚል መከራከሪያ አቅርበዋል፡፡ አስተባባሪዎቹ ፖሊስ ይህን ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ሰልፉን ለማደናቀፍ ሴራ እየተሸረበ ስለመሆኑ አመላካች ነው ሲልም የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ምክትል ኮሚሽነሩ ‹‹ሰልፉ ከሚካሄድበት 3 ሰዓት እስከ ስድስት ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ አንድ ደቂቃ ቢያልፍ ህገ በህገ ወጥነት እንከሳችኋለን›› እንዳሏቸው ተግልጻል፡፡ በተመሳሳይ የታሰሩት ወጣቶች ‹‹ህገ ወጥ ወረቀት ነው ሲበትኑ የተገኙት፡፡ ህገ ወጥ ወቀረት በመበተናቸውም ሊታሰሩ ይገባቸዋል፡፡›› ማለታቸውን ገልጸዋል፡፡
በተያዘ ዜና ፖሊስና የደህንነት አባላት የሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ አካባቢ የሚገኘውን ህዝብ በር እያንኳኩ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲን በድምጽ ብክለት ክሰሱት!›› እያሉ እየቀሰቀሱ ነው፡፡ ነገር ግን አብዛኛዎቹ የሰፈሩ ነዋሪዎች ‹‹እስካሁን አልረበሹንም፣ ሊረብሹንም አይችሉም፡፡›› እያሏቸው ነው፡፡ ከዚህ በፊት ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ በዝግጅት ላይ እያለ አመራሮቹ ጃን ሜዳ ፖሊስ ጣቢያ በታሰሩበት ወቅት ፖሊስ ‹‹ህዝቡ ነው የድምጽ ብክለት አድርሰውብናል በሚል›› የከሰሳችሁ ማለቱ ይታወሳል፡፡

በሶልያና ሽመልስ
በኢህአዴግ መንግስት የመሪነት ሰልጣኑን ከያዘ ከዛሬ 22 አመት ግድም ጀምሮ ቃል ገብቶ ተግባራዊ ባለማድረግ ከሚወቀስባቸው ጉዳየች አንዱ የአገሪትዋ የሰብአዊ መብት አያያዝ ነው፡፡ ሁሉንም አለም አቀፉን የመብቶችን አለማቀፋዊነት የሚያረጋግጡ ጠንካራ እና ግልጽ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችን የያዘ ህገ መንግስት በመጀመሪያዎቹ የስልጣን አመታት መጽደቁም ይታወቃል፡፡
በመጀመሪያዎቹ አስር አመታት የነበረው የሰብአዊ መብት አያያዝ በጣም በአስጊ ሁኔታ ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበበት ቢሆንም የቀጣዩ አስር አመታት አፈጻጸምም ከትችት አላመለጠም፡፡ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሰብአዊ መብት ሪፓርቶችን የሚያወጡ አገር በቀል የማህበረሰብ ድርጅቶች በበጎ አድራጎትና ማህበራት አዋጅ የተነሳ ሽባ በመሆናቸው የሰብአዊ መብት ሁኔታውን ለመገምገም አስቸጋሪ ስለሆነ የአገሪትዋ ሰብአዊ መብት ሁኔታ ” የውጪ ሃይሎች” ድምጽ ብቻ የሚሰማበት ምድረ በዳ ሆኗል፡፡ በአገሪትዋ የተለያዬ ክፍሎች የሚከናወኑ የመብት ጥሰቶችን ለእርምት የሚያቀርብ የአገር ውስጥ ተቋም በሌለበት ሁኔታ በቀጣዩ የፈረንጆች ወር መጀመሪያ የኢትዮጰያ የሰብአዊ መብት ግምገማ (universal periodic review ) ለሁለተኛ ጊዜ በተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ይካሄዳል፡፡
አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ግምገማ (United Nations Human Rights Council Universal Periodic Review)
አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ግምገማ ሁሉም የተባበሩት መንግስታት አገራት በየ4 አመት ተኩል የሚያደርጉት የሰብአዊ መብት ግምገማ ሂደት ነው፡፡ይህ የግምገማ ሂደት አገሮች ያላቸውን የሰብአዊ መብት ችግሮች ለመፍታት እና ችግሮቻቸውን በማስታወስ እነዲያሻሽሉ እንደያግዝ የታሰበ ስርአት ሲሆን እኤአ ከ20006 ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ጀምሯል፡፡ በዚህ ግምገማ የተገምጋሚው አገር መንግስት የሰብአዊ መብት ስራውን አስመልክቶ ሪፓርት ያቀርባል፡፡ መንግሰታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና የሰብአዊ መብት ተቋማትም በተመሳሳይ ተገምጋሚው አገር የሰብአዊ መብት ሁኔታ ላይ ሪፓርታቸውን ለተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ያስገባሉ፡፡ እነዚህ የመንግሰትም መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሪፓርቶችም ተሰብስበው ለአባል አገራት አንዲደርሱ የማድረግ ሃላፌነቱን የተባበሩት መንግስታት ይወስዳል ፡፡ ይህ የግምገማ ሂደት በአጠቃላይ ለ3 ሰአት ከሰላሳ የሚቆይ ሲሆን ተገምጋሚው አገር የራሱን የሰብአዊ መብት ሁኔታ የሚገልጽ ሪፓርት ካቀረበ በሁዋላ የተለያዩ አገራት ጥያቄ ለማቅረብና የማሻሻያ ነጥባቸውን ( recommandations) ለመናገር ቦታ ይይዛሉ ፡፡ በዚህ የግምገማ ሂደት ተገምጋሚ አገር አስፈላጊ ሆኖ ካገኘው የሚቀበለውን የማሻሻያ ነጥብ ተቀብያለው ሲል የማይቀበላቸውን ነጥቦች አልቀበልም በማለት እዚያው መልስ መስጠት ይችላል፡፡ ይህ ካልሆነ ግን አጠቃሎ የተቀበላቸውንና ያልተቀበላቸውን ማሻሻያ ሃሳቦች በሶስት ወራት ገደማ ውስጥ በይፋ ያሳውቃል፡፡ ይህ ሂደት ከተጠናቀቀ በሁዋላ እነዚህን የማሻሻያ ሃሳቦች መተግበር የተገምጋሚው አገር ሃላፊነት ነው፡፡ይህ ሂደት የመጀመሪያው ከሆነ የሰብአዊ መብት ሪፓርትና ጥያቄዎችን የመመለስ ሂደት ሲሆን ለሁለተኛ ዙር ከሆነ ግን ተገምጋሚው አገር በመጀመሪያው ግምገማና በሁለተኛው ግምገማ መካከል ያለውን አፈጻጸምና መሻሻል የማሻሻያ ነጥቦቹ ላይ ያደረገውን ተግባራዊ ለውጥ አብሮ ያቀርባል፡፡ በዚህ መሰረት የኢትየጵያ መጀመሪያው ግምገማ እኤአ በ2009 የተካሄደ ሲሆን ከተለያዩ አገራት 160 የማሻሻያ ነጥቦች አቅርበው ነበር፡፡
አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ግምገማና ኢትዮጲያ
ይህ በየ4 አመቱ የሚካሄድ ግምገማ ላይ አገራችን ከፍተኛ ቁጥር ያለው የማሻሻያ ነጥቦች ከተሰጣቸው አገራት አንዷ ስትሆን በ2009 አ.ም ከተሰጠት የማሻሻያ ነጥቦች መካከል አብዛኛውን ከሲቪክና ፓለቲካዊ መብቶች ጋር የተያያዙ ማሻሻያዎችን ባለመቀበል መንግስት ውድቅ አድርጎአቸዋል፡፡ በወቅቱ ገና በመጽደቅ ላይ የነበሩትን የበጎአድራጉት ድርጅቶች እና የጸረ ሽብር ህግ አዋጆች በተገቢው የአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ደረጃ መሰረት እንድታሻሽል የሚሉ ማሻሻዎች ቢገኘበትም ህጎቹ ምንም መሻሻል ሳይደረግባቸው ሁለተኛው ዙር ግምገማው ከሳምንት በሁዋላ ይደረጋል፡። በመጀመሪያው ግምገማ ወቅት ማሻሻያ ቀርቦባቸው መንግስት ያልተቀበላቸው ጉዳዩች በጥቂቱ የጸረ ሽብር ህጉን ማሻሻል ፣የበጎ አድራጎትና ማህበራት ህጉን መሰረዝ ፣የመንግሰት አስተዳደር አመራር ውስጥ የሚገኘውን የብሄር ተዋእጾ መገምገምና የፌደራሊዝም ስርአቱ መሰረት ሁሉንም ብሄሮች ያማከለ እነዲሆን ማሻሻል፣ኦጋዴን እና ሶማሊያ ክልልን ለሰብአዊ እርዳታ ስራዎች ክፍት ማድረግ፣ የታሰሩ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን መፍታት ፣በሶማሌ ክልል የሚገኝ የሰብአዊ መብት ሁኔታን በገለልተኛ ወገን ማጣራትና የአለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት አባልነት የመሳሰሉት ሲገኙበት ተቀባይነት ካገኙት ማሻሻያ ዎች መካከል የ እኤአ 2010ምርጫን ነጻና ፍትሃዊ ማድረግ፣የገለልተኛ ሚዲያ እድገትን መደገፍ፣ የሴቶችና ህጻናት መብቶች አጠባበቅን ማገዝ የሴት ልጅ ግርዛትና አለእድሜ ጋብቻን ማስወገድ እነዲሁም አገር አቀፍ የሰብአዊ መብት እቅድ ማዘጋጀት ይጠቀሳሉ፡፡
በዚህ የመጀመሪያ ዙር ግምገማ የኢትዮጲያ መንግስት አንዳንድ ጠቅላላ ማሻሻያዎችን ሲቀበል ከነዚህም ውስጥ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ግለሰቦችን ደህንነት መጠበቅ ጠቅላላ የሲቪል ማህበረሰቡ የስራ ከባቢን ምቹ ማድረግ፣ የሚዲያ እድገትን መደገፍ ደረጃውን የጠበቀ ምርጫ ማድረግ የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡
በሁለቱ ግምገማዎች መሃል
ከአራት አመት በፌት የተሰጡ የማሻሻያ ሃሳቦች ያሉበትን ሁኔታ በማሳወቅ የሚጀምረው የአሁኑ የመንግስት ሪፓርት አገሪትዋ በሰብአዊ መብት ረገድ ከፍተኛ መሻሻል እያሳየች እነደሆነ ያትታል፡፡ በተጨማሪም የሰብአዊ መብት እቅድ መዘጋቱን እንደትልቅ ስኬት ያቀርበዋል ፡፡ በሌላ በኩል አገሪትዋ ውስጥ የቀሩት በጣት የሚቆጠሩ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች የእቅዱ ዝግጅት ላይም ሆነ አገራዊ ሪፓርቱ ላይ የነበራቸው ተሳትፎ በጣም ውስን የነበረ ሲሆን ከአራት አመት በፌት የታሰበው የእቅድ ዝግጅት ትግበራው መጀመር ከነበረበት ከሁለት አመት በላይ ዘግይቷል ሲሉ የመንግስትን ሪፓርት ይተቻሉ፡፡ባለፉት አራት አመታት ውስጥ የመንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በፓሊሲ እና በማህበረሰባዊ ንቃተ ህሊና ላይ የሚሰሩት ስራ ተገድቦ ሙከራ የሚያደርጉትም ድርጅቶች ድርጅታዊ ህልውናቸውን በማስጠበቅ ላይ ሲገኙ የሰብአዊ መብት ሁኔታን አስመልክቶ አገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ተቋማትይህ ነው የሚባል ነገር ሲናገሩ አልተሰማም፡፡ይህ በህጉ የተነሳ በተግባር እየታየ ያለው የተቋማት በመብቶች ዙሪያ አለመስራት እግድ በሴቶች መብቶች፣ በህጻናት መብቶችና በአካል ጉዳተኝነት የሚሰሩ ድርጅቶችን ሳይቀር ስራቸውን እንዲቀይሩ አስገድዷቸዋል፡፡ በከፍተኛ ሁኔታ በአገሪቱ ብዙ ክፍሎች ይንቀሳቀሱ የነበሩ እንደ ህግ ባለሞያ ሴቶች ማህበር ያሉ ተቋማት ስራቸውን አዲስ አበባ ላይ ብቻ በማተኮር አንድ ቢሮ ውስጥ ካደረጉ ከራረሙ፡፡ በተጨማሪም ጸረ ሽብርተኛነት አዋጁ በተግባር በመዋል በመቶዎች የሚቆጠሩ የሽብር ክስ ሰለባዎች እነዲፈረድባቸው ያደረገ ሲሆን ጋዜጠኞች የመጀመሪያው ረድፍ ላይ ይገኛሉ፡፡
የጋዜጦች ቁጥርና ጥራት በወረደበት ፣ የእስረኞች አያያዝ ከቶርቸር ጋር መቀላቀሉን የተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲ አመራር እና አራማጅ እስረኞች እየተናገሩ ባሉበት ፣ አሁንም አንድም የግል ቴሌቪዥን እና ገለልተኛ የሚዲያ ተቋም በሌለበት ፣ አሁንም ሰዎች በፓለቲካ አመለካከት ልዩነታቸው እስር ቤት እነደገቡ ብዙዎች እያመኑ፣ አፋኝ ህጎቹ ከስጋት በላይ በተግባር ተጽእኖአቸው በሚታይበትና መጪው ምርጫ አንድ አመት ሲቀረው ሁለተኛው ዙር የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ የኢትዮጲያ ግምገማ ይካሄዳል፡፡ መንግሰት ምን ያህሎቹን የማሻሻያ ሃሳቦች ይቀበል ይሆን ምን ያህሎቹንስ ይቃወም ይሆን ? በዝርዝር ለማየት ፍላጎት ላደረባችሁ ሚያዝያ 28 የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ጉባኤ ድረ ገጽ ላይ መመልከት በቀጥታ ሰርጭታቸው መመልከት ትችላላችሁ፡፡

በዩክሬን የሰፈነው ውጥረት ተባብሶ ዛሬ ወደ ግጭት ተሸጋግሯል ። በዛሬው እለት የዩክሬን ወታደሮች ምሥራቅ ዩክሬን ከሚገኙት መፍቅሬ ሩስያ ኃይሎች ጋር ተጋጭተው ቢያንስ ሁለት ሚሊሽያዎችን መግደላቸውን መንግሥት አስታውቀዋል ።

የሰው ልጅ ግላዊና ማህበራዊ ህይወቱን ለማሻሻል እንዲሁም የለት ተለት ህይወቱን የተሻለ ለማድረግ በአካባቢው ወይም በሚኖርበት ሃገር ያለውን አካባቢያዊና መንግስታዊ ስርዓት ጤናማ መሆኑ ግድ ነው። የማህበረሰቡም የለት ተለት ህይወት ከግዜ ወደ ግዜ አስቸጋሪ እየሆነ ሲሄድ የዛ ማህበረሰብ መንግስት ወይም አገዛዝ መቀየሩ አንደኛው መፍትሄ ነው። እንደሁለተኛ አማራጭ መፍትሄ የሚወሰደው ደግሞ የነበረውን አገዛዝ ለአነስተኛና ከፍተኛ ለውጦች ካለው ምቹነት […]

ጸጋዬገ ብረመድኅን አርአያ

“ መኳንንቶቼ፣ ልጆቼና ሕዝቦቼ ሆይ! እኔ ስለ እናቴ ኢትዮጵያ ሕይወቴን ልሰዋላት ሙሉ ፈቃድ አለኝ። በእኔ ልብ ያለው አሳብ በትክክል በእናንተም ልብ በመታሰቡ በጣም ደስ ብሎኛል። “ እንግዲህ አሳባችን አንድ ከሆነ ጠንክሩ እንጂ አትፍሩ። ለዘመቻውም አዋጅ አናግራለሁና አይዞአችሁ አትፍሩ! “ አገሬ ሆይ ስሚ! መኳንንቶቼ፣ ወታደሮቼ፣ ሕዝቦቼ ስሙ…..ወደፊት ገስግሱ እንጂ ወደኋላ አትቅሩ! “ የኢትዮጵያ ልጅ ሆይ! ልብ አድርገህ ተመልከት ኢትዮጵያ የተባለችው አንደኛ እናትህ ናት! ሁለተኛ ዘውድህ ናት! ሦስተኛ ሚስትህ ናት! አራተኛ ልጅህ ናት! አምስተኛ መቃብርህ ናት! እንግዲህ የእናት ፍቅር፣ የዘውድ ክብር፣ የሚስት ደግነት፣ የልጅ ደስታ፣ የመቃብር ከባቲነት እንደዚህ መሆኑን አውቀኸው ተነሳ!”

አንበሳው አጼ ዮሐንስ- ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ

ሙሉውን አስነብበኝ …

ከዚህ ቀደም ባለው ጽሑፍ በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም የሚገኘውን ገዳማችንን በተመለከተ ዐሥር ነጥቦች እንደማነሣ ቀጠሮ ሰጥቼ ነበር ያቆምኩት፡፡ ዛሬ ሦስቱን አነሣለሁ፡፡

  1. ብሔራዊ ኮሚቴ ማቋቋም

የዴር ሡልጣን ገዳማችን ሁለት ዓይነት ችግሮች ተደቅነውበት ይገኛሉ፡፡ የመጀመሪያው የይዞታ ባለቤትነት ያልተፈታ ችግር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ገዳሙ ላለፉት ሁለት መቶ ዓመታት ምንም ዓይነት ጥገና ባለማግኘቱ የተደቀነበት የመፍረስ አደጋ ነው፡፡ የሁለቱም ችግሮች መነሻው ግብጾች በገዳሙ ላይ የሚያቀርቡት የይገባናል ጥያቄና እርሱንም ተከትሎ በመተግበር ላይ የሚገኘው ይርጋ ሕግ(states co)ነው፡፡

ይህንን የገዳማችንን ችግር ለመፍታት በዘላቂነት፣ በተጠናና ዓለም ዐቀፍ ደረጃ ባለው መልክ የሚሠራ ብሔራዊ ኮሚቴ ማቋቋም ያስፈልገናል፡፡ ይህ ኮሚቴ የሃይማኖት፣ የሕግ፣ የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ መንገዶችን ሁሉ በመጠቀም የዴር ሡልጣንን ገዳም ባለቤትነት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚፈታ፣ ገዳሙም ጥንታዊነቱንና ደረጃውን ጠብቆ እንዲጠገንና እንዲገነባ የሚያደርግ መሆን አለበት፡፡

ዛሬ ዓለም በኑሮ ደረጃ የትና የት በደረሰበት ዘመን መብራት፣ ውኃና መጸዳጃ ማግኘት ለዴር ሡልጣን መነኮሳት ፈተና መሆን የለበትም፡፡ በእሥራኤል ሀገር እንስሳ እንኳን በማይኖርበት መልኩ እንዲኖሩ ያስገደዳቸውን የይርጋ ሕግ አስቀርቶ ለደረጃቸውና ለሰብአዊነታቸው የሚመጥን የመኖሪያ አገልግሎት እንዲያገኙ መደረግ አለበት፡፡ በአካባቢው የሚገኙ፣ ቦታንም ከእኛ የወሰዱ አብያተ ክርስቲያናት ሰማይ ጠቀስ ፎቅና ቤተ ክርስቲያን እየሠሩ፣  እነርሱ ግን በጎልጎታ ፍርስራሽ በተሠሩ በኣቶች እንዲኖሩ መገደድ የለባቸውም፡፡ የተቆረጠ ገመድ ለመቀጠል፣ የተሠበረ ቧንቧ ለመሥራት፣ የተበላሸ መጸዳጃ ለማስተካከል፣ የተጣመመ ሚስማር ለማቃናት ሌሎችን ደጅ መጥናት የለባቸውም፡፡

ይህ ነገር ሊፈታ የሚችለው ነገሩን የምር አድርገን ስንይዘው ብቻ ነው፡፡ በየዓመቱ በሚመጡ ተሳላሚዎች ብቻ የሚሠራ አይደለም፡፡ በቀን 24 ሰዓት፣ በሳምንት ሰባት ቀን፣ በወር ሠላሳ ቀናት፣ በዓመት አሥራ ሦስት ወራት የሚሠራ ሥራ ነው፡፡

ለዚህ ደግሞ ከአስጎብኝ ድርጅቶች፣ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከታዋቂ ሰዎች፣ ከምሁራን፣ በውጭ ሀገር ከመኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ ከቤተ እሥራኤላውያን፣ ወዘተ የተውጣጣ አንድ ጠንካራ ብሔራዊ ኮሚቴ መቋቋም አለበት፡፡ ይህንን ኮሚቴ ለማቋቋም የአስጎብኝ ድርጅቶች ኃላፊዎች ተነሣሽነቱን በመውሰድ፣ ከጠቅላይ ቤተ ክህነትና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር መሥራች ጉባኤ መጥራት ይቻላል፡፡

ይህ ብሔራዊ ኮሚቴ በአዲስ አበባ ዋና ጽ/ቤቱን በማድረግ በእሥራኤልና በሌሎች ሀገሮች ቅርንጫፎችን በመክፈት ኢትዮጵያውያንንና የኢትዮጵያን ወዳጆች ማስተባበር ይችላል፡፡ ከግብጽ ቤተ ክርስቲያን ጋር ጉዳዩን የተመለከተ ውይይት እንዲካሄድ ማስቻል፣ ከእሥራኤል መንግሥት ጋር የዲፕሎማሲ ውይይት መጀመር፣ ተጽዕኖ አድራጊ ተቋማትንና ግለሰቦችን በመፈለግ ተጽዕኖ አድራጊነታቸውን መጠቀም፣ ሚዲያዎች ጉዳዩን የተመለከቱ ዘገባዎችን እንዲሠሩ ማስቻል፣ ሕዝቡንም በማስገንዘብ ሀገራዊ ንቅናቄ መፍጠር፣ ደረጃ በደረጃ ሊፈቱ የሚገባቸውን ችግሮች በመለየት ደረጃ በደረጃ መፍታት፣ ሲፈቀድ የጥገናውንና የግንባታውን ሥራ ማከናወን፡፡

ይህንን ጉዳይ አሁኑኑ ማቋቋምና ሥራ መሥራት ካልቻልን ከገዳሙ በላይ በሚደረገው የጥገና ሥራ የድንጋይ መዓት እየዘነበበት የሚገኘው ገዳም፣ የእግዚአብሔር ቸርነት ካልጠበቀው በቀር የመናድ አደጋ ተደቅኖበታል፡፡ ወደፊትም የመፍረስ አደጋ ሊያጋጥመው ይችላል፡፡ አስቀድመን የሕግና የዲፕሎማሲውን ሥራ ካልጀመርነው፣ የፈረሰ ጊዜ ‹‹መልሳችሁ ልትሠሩ አትችሉም›› የሚል ክርክር ያጋጥመንና ፍርስራሽ ታቅፈን መቅረታችን የማይቀር ነገር ነው፡፡ ነገን መቅደም ያለብን ዛሬ ነው፡፡ በተለይ ቁጥራቸው እየጨመረ የመጡት አስጎብኝዎች ይህንን ነገር ፈጥኖ በመከወን ረገድ ሃይማኖታዊም፣ ታሪካዊም፣ ዜግነታዊም ኃላፊነት አለባቸው፡፡


  1. የጋራ የጉዞ ከሚቴ

ወደ ኢየሩሳሌም ለትንሣኤ በዓል፣ ለዳግም ትንሣኤ በዓልና ለገና የሚደረገው የኢትዮጵያውያን ተሳላሚዎች ጉዞ ተጠናክሯል፡፡ የተጓዡም ቁጥር ጨምሯል፡፡ ነገር ግን ይህንን ዕድል በሚገባ አልተጠቀምንበትም፡፡ ተሳላሚዎቹ የሚገናኙበትን፣ ስለ ገዳማቸው የሚመክሩበትን፣ ገዳማቸውን ዘላቂ በመሆነ መንገድ የሚረዱበትን መንገድ አልፈጠርንም፡፡ እንዲያውም በአንዳንዶቹ አስጎብኝዎች መካከል የማይታረቅ የሚመስል ቅራኔ አለ፡፡ በአስጎብኝዋቻቸው ምክንያት ሰላምታ ለመለዋወጥ እንኳን የማይፈላለጉ ተሳላሚዎች አሉ፡፡ ሁሉም በየሆቴሉ ከርሞ፣ በየመኪናው ተጓጓጉዞ፣ በየራሱ ፋሲካን አክብሮ ወደነበረበት ይመለሳል፡፡ ሰማይና ምድር፣ ሕዝብና አሕዛብ፣ ሰውና መላእክት አንድ በሆኑበት ቅዱስ ቦታ ተለያይተን እንመለሳለን፡፡

የኢየሩሳሌም ጉዞ ከመላው ዓለም የሚመጡ ኢትዮጵያውያን የሚገናኙበት፣ የሚተዋወቁበት፣ በአንድ ሊመክሩ የሚችሉበት፣ ፍቅርና ሰላም የሚመሠርቱበት፣ የፖለቲካና የዜግነትን ድንበር ተሻግረው የእምነት አንድነት የሚያሳዩበት መሆን ነበረበት፡፡ ግን አልሆነም፡፡ ትንሣኤን እንኳን በአንድ አዳራሽ ማክበር፣ በአንድነት መመገብ አልቻልንም፡፡ አንድ ቀን ሰጥተን እንኳን መማማር፣ መመካከርና የገዳማችንን ነገር ከገዳማውያኑ ጋር መወያት አልቻልንም፡፡

ይህን ችግር ለመፍታት አስጎብኝዎች የጋራ ኮሚቴ ሊኖራቸው፣ ችግራቸውን በሰከነ፣ በሠለጠነና መንፈሳዊ በሆነ መንገድ ሊፈቱ፣ አንዳንዱንም ችግር ይቅር ተባብለው ተሻግረውት ሊያልፉ ይገባል፡፡ ከችግራችን በላይ የሆነ ጊዜ የማይሰጥ ሌላ አደጋ ከፊታችን ስላለ፣ለባሰው ችግር ሲባል የኛን መለስተኛ ችግር መፍታት አለብን፡፡‹‹ለምጣዱ ሲባል አይጧን ማሳለፍ›› ይገባል፡፡ በጋራ የጉዞ መርሐ ግብራችን ማጣጣም፣ በኢየሩሳሌም ከተማ አንድ ቀን የኢትዮጵያውያንን ቀን ማክበር፣ የጋራ መንፈሳዊ ጉባኤ በማድረግ መማማር፣ ኅብረታችንን በመጠቀም የመጓጓዣ፣ የመኝታና ሌሎች ወጭዎችን እንዲቀንሱልን ማድረግ፣ ለተሳላሚዎቹ ተመሳሳይ መረጃ እንዲሰጣቸው ማድረግ፣ በመካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችንም በጋራ መፍታት ያስፈልጋል፡፡

  1. የጋራ የመታሰቢያ ቀን

በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌምና በአካባቢዋ የሚገኙት ገዳሞቻችን በመሥዋዕትነት ተተክለው በመሥዋዕትነት የጸኑ ናቸው፡፡ እነዚህን ገዳማት ለማቅናትና ለመጠበቅ ሕይወታቸውን፣ ገንዘባቸውንና ዕውቀታቸውን የሠው አያሌ ኢትዮጵያውያን አሉ፡፡ ከዘመናት በፊት መጭው ጊዜ ታይቷቸው ቋሚ ቅርስና ታሪካዊ ሥራ የሠሩ ጠንካራ ቀደምቶቻችን ነበሩ፡፡ እነዚህ ማስታወስ ይገባል፡፡

ብጹዕ አቡነ ማቴዎስ (በረከታቸው ይደርብንና) የነገሥታቱና ንግሥታቱ መታሰቢያ ታኅሣሥ 3 ቀን፣ የሌሎች መኳንንታና መሳፍንት ደግሞ ግንቦት አንድ ቀን በጸሎትና በቅዳሴ እንዲታሰብ በማኅበር አስወስነው ሲሠራበት ይኖራል፡፡ እኛም ተጓዦች ደግሞ በየዘመናቱ ሲጓዙ የኖሩትን፣ ሳይደርሱ በረሃ የቀሩትን፣ በባርነት ተሽጠው የጠፉትን፣ ከመጡ በኋላም በጽናት ያገለገሉትን አባቶችና እናቶች ታሪክ የምንሰማበት፣ በጸሎት የምንዘክርበት፣ ታሪካቸውንም ለትውልድ የምናስተላልፍበት፣ ዛሬም አገልግለው በአረጋዊነት ለሚጦሩ አባቶችና እናቶች አስፈላጊውን ሁሉ የምናደርግበት አንድ ራሱን የቻለ የቀደምቶቻችን መታሰቢያ ቀን ያስፈልገናል፡፡

ቀደም ብሎ የጋራ የጉዞ ኮሚቴ ይኑረን ያልኩትም ይህንን የመሰለውን ለማቀናጀት ነው፡፡ አስጎብኝዎች ተመካክረው አንዱን ቀን በመስጠት፣ ጠዋት የኢትዮጵያ ቀን በኢየሩሳሌም ብለን የገዳማቱን ሁኔታ፣ በብሔራዊ ኮሚቴው የተደረገው ጥረት የደረሰበትን ደረጃ፣ ከእኛ ምን እንደሚጠበቅ፣ ለገዳማቱ በጊዜያዊነትና በዘላቂ ስለሚያስፈልገውን ነገር የምንመክርበት ቢሆን፡፡ ምሳ በአንድነት ከተመገብን በኋላ ደግሞ ‹‹የአባቶቻችን መታሰቢያ ቀን›› ብለን ታሪካቸውን በማስታወስ፣ የመታሰቢያ ሥራ በመሥራት፣ በኢትዮጵያ ለሚገኙ ገዳማትም ርዳታ በመሰብሰብ በትምህርትና በመዝሙር የምናሳልፈው ጊዜ ቢሆን፡፡


የትናንቱ በተረሳ ቁጥር ለዛሬው የምንሰጠው ዋጋ ይቀንሳል፤ ያገኘነው ነገር እንዲሁ የተገኘ ይመስለንና እንዲሁ እናጣዋለን፤ ዛሬ እንደ እነርሱ የሚነሣ ብርቱ ጀግናም እናጣለን፣ ምሳሌ የለውምና፡፡ በተደጋጋሚ የሌሎችን በመስማት ብዛትም የራሳችንን እስከመካድ ልንደርስ እንበቃለን፡፡ በቁጭት ተነሣሥተን ለሃይማኖታችንና ለታሪካችን በጽኑ እንዳንቆምም ማበርቻ እናጣለን፡፡

በቅድስት ሀገር የጉብኝት መርሐ ግብር ውስጥ ለገዳሞቻችን የምንሰጠው ቦታ ውሱን ነው፡፡ የጉዞው መብዛትና የዐቅምም ጉዳይ ገድቦብናል፡፡ ቢያንስ አንዱን ቀን በመሠዋት እና መርሐ ግብራችንን በማሸጋሸግ ግን የቀደሙትን ውለታ መክፈል ባንችል እንኳን ‹‹ዋኖቻችሁን አትርሱ›› የሚለውን ቃል መፈጸም እንችላለን፡፡

(ይቀጥላል)

ጥብርያዶስ፣ እሥራኤል

ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ!
የተነጠቁ መብቶቻችንን እናስመልሳለን!!!
እሁድ ሚያዚያ 19 ቀን ከጠዋቱ 3 – 8 ሰኣት
ቦታ ከፓርቲው ጽ/ቤት ተነስቶ በአዋሬ፣ አድዋ ድልድይ፣ ባልደራስ አድርጎ መድረሻው ወረዳ 8 ሜዳ የካ ሚካኤል ታቦት ማደርያ ይሆናል፡፡
ኑ ራሳችንን ነፃ በማውጣት የሀገራችንን እጣ ፈንታ እንወስን!
ሰማያዊ ፓርቲ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሕገመንግሥታዊ መብቴን በመጣስ ቅስቀሳ እንዳላካሄድ ታግጃለሁ፤ አባላቶቼ ያለ አግባብ ታስረውብኛልና ያቀረብካቸው አማራጭ ቦታዎች ወደጎን ተደርገው ህጉ በማይፈቅድለት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳደርግ ተነግሮኛል በሚል በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአዲስ አበባ ከንቲባ ጽ/ቤት እና በአዲስ አበባ ፖሊስ ላይ በመሰረተው ክስ የቀረቡትን የክርክር ሃሳቦች ያደመጠው የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 8ኛ […]

የአዲስ አበባና የኦሮምያ ግንኙነት የፌደራል ስርዓቱ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ጊዜ አንስቶ እያወዛገበ ያለ ጉዳይ ነው። በቅርቡ ደግሞ የአዲስ አበባ አስተዳደር የ10 እና የ25 ዓመት የተቀናጀ የጋራ ልማት ፕላን በማዘጋጀት በተለምዶ “ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ ከተሞችን ከአዲስ አበባ ጋር ለማቀናጀት ጥረት መጀመሩ ተድበስብሶ ያለፈውን የፌደራሊዝም ጥያቄ እንደገና እንዲያገረሽ አድርጎታል። የተቀናጀ የጋራ ልማት […]

 

የኢትዮጵያ ምጣኔ ኃብት በተያዘው የበጀት ዓመት በ11.3 ከመቶ እንደሚያድግ ተተንብዮ የነበረ ቢሆንም ባለፉት 9 ወራት የታየው የውጪ ንግድ ውጤት ግን እንደተጠበቀው አለመሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ አመልክተዋል።

በሌላ በኩል ደግሞ የግብፅ መንግሥት ወደ ድርድር እንዲገባ ዓለምአቀፍ ጫና እየተደረገበት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ከሱዳን ጋር የተደረገ አዲስ የወሰን ስምምነት እንደሌለም ገልፀዋል።

በኤርትራ ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲቀጥል እንደሚፈልጉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተናገሩት በብሪታንያና በአየርላንድ የኤርትራ አምባሣደር ተስፋሚካኤል ገራህቱ ምላሽ ሰጥተዋል።
 

“ማዕቀቡ ከተጣለ አራት ዓመታት ቢያልፍም በኤርታራ ላይ ምንም ዓይነት ማስረጃ አልቀረበም” ብለዋል አምባሣደሩ።

አምባሣደር…

መንግሥታቸው ካደጉ ሃገሮች ለሚገኝ እርዳታ ሲል የፖሊሲ ለውጥ አድርጎ እንደማያውቅ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ወደፊትም በዚህ መንገድ የሚመጣ ለውጥ እንደማይኖር ገልፀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለፁት ባወጣችው የተመሣሣይ ፆታ ግንኙነት ሕግ ምክንያት በዩጋንዳ ላይ እየተደረገ ያለውን ጫና በማስመልከት ለተነሣ ጥያቄ መልስ ሲሰጡ ነው፡፡

ለዘርዝሩ የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ከአዲስ አበባ ያዳምጡ፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም፣ በአዲስ አበባ ለጠራው ሰላማዊ ሰልፍ፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር እውቅና ሰጠ። አስተዳደሩ፣ ሰማያዊ ፓርቲ፣ አስፈላጊዉን የእውቅና ፎርም በመሙላት ወደ ሰልፍ ተግባራቱ መሰማራት እንደሚችል ትላንት ለፓርቲዉ በላከው ደብዳቤ ማሳወቁ ይታወቃል። በዚያ መስረት የሰማያዊ ከፍተኛ አመራር አባላት፣ በአስተዳደሩ የተጠየቀዉን የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ቅጽ ፎርም በመሙላት፣ ዛሬ ሚያዚያ 16 ቀን አስፈላጊዉን […]

ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች

ሀሳብን በስፋትና በጥልቀት የመግለፅ አቅሙ እጅግ የዳበረ እንደሆነ ይነገርለታል፤ ጥንታዊው የግእዝ ቋንቋ። አንዳንዶች ግእዝ ሞቷል መቀበር ብቻ ነው የቀረው ሲሉ ይደመጣል። ሌሎች ደግሞ የለም፤ ቋንቋው በቤተክህነትና በሌሎችም ቦታዎች አገልግሎት ላይ እየዋለ ነው አልሞተም፤ እንደውም አሁን እያንሰራራ ነው በማለት ለማስረዳት ይሞክራሉ።

ኬንያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ችግር እየተባባሰ መሄዱን እዚያ የሚገኙ ስደተኞች አስታወቁ ። የኬንያ መንግሥት ስደተኞች በሙሉ በሃገሪቱ ወደሚገኙ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች እንዲገቡ ካዘዘ ወዲህ በተለይ በከተሞች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የፍርሃትና የስጋት ህይወት እንደሚገፉ ለዶቼቬለ አስታውቀዋል ።

ከ 14 ዓመት በፊት የተባበሩት መንግሥታት አጠቃላይ ጉባዔ በተለመው መሠረት አዳጊ አገሮች በ ስምንት ዐበይት ነጥቦች ላይ በማትኮር ፤ በተለይ ድህነትን ግማሽ በግማሽ ለመቀነስ፤ መሠረታዊ ትምህርት ለሁሉም ዜጋ ለማዳረስና