ሠማያዊ ፓርቲ ያካሄደው ሠላማዊ ሰልፍ
የሠማያዊ ፓርቲ ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ባካሄደው ሠላማዊ ሠልፍ መንግሥት እየተከተለው ነው ያለውን ብልሹ የአስተዳደር ሥርዓት፣ ሙስናና ደካማ የመሠረተ-ልማት አቅርቦት ያሻሽል ሲል ጠየቀ።
የሠማያዊ ፓርቲ ዛሬ አዲስ አበባ ላይ ባካሄደው ሠላማዊ ሠልፍ መንግሥት እየተከተለው ነው ያለውን ብልሹ የአስተዳደር ሥርዓት፣ ሙስናና ደካማ የመሠረተ-ልማት አቅርቦት ያሻሽል ሲል ጠየቀ።
በአካባቢያቸዉ የሚገኝና ለእነሱ የዕለት ተዕለት ህይወት ትርጉም ያለዉ የደን ሃብት የምንጠራ አደጋ ባንዣበበበት ወቅት ዶቼ ቬለ ያነጋገራቸዉ የመዠንገር ማኅበረሰብ አባላት «መዠንገሮች ዉሃ ብቻ ሳይሆን ደግም ህይወት ነዉ» የሚል መመሪያ እንዳላቸዉ ገልጸዉልን ነበር።
![]() |
|
የአርመን ሙዝየም ሕንጻ
|
በነገው ስልፍም ይፈቱ ዘንድ ድምጹን ያሰማል!
ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹የተነጠቁ መብቶቻችን እናስመልሳለን›› በሚል ሚያዝያ 19 ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱ ይታወቃል፡፡ በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት ከምናነሳቸው ጉዳዮች አንዱና ዋነኛው ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሰልፉ ገዥው ፓርቲን ላይ የሠላ ትችት ስለሰነዘሩና ለህዝባቸው መረጃ ስለሰጡ ብቻ የሚደርስባቸውን ህገ ወጥ እርምጃ ያወግዛል፡፡
በሳምንቱ ውስጥ የህዝብን መብት ለማስመለስ ለጠራነው ሰልፍ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ 50 ያህል አመራሮችና አባላት በህገ ወጥ መንገድ ታስረዋል፡፡ በትናንትናው ዕለት የፓርቲያችን ሊቀመንበር (ማታ ተፈትተዋል)፣ ምክትል ሊቀመንበር፣ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በህገ ወጥ መንገድ መታሰራቸው ይታወቃል፡፡ በተመሳሳይ ወቅት የዞን ዘጠኝ አክቲቪስቶችና ሌሎች ጋዜጠኞችም ታስረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ሌሎችን ለማሰር ጥረት እየተደረገ እንደሆነ ይታወቃል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ይህን የገዥው ፓርቲ ከፍርሃት የመነጨ አምባገነናዊ እርምጃ በጽኑ ይቃወማል፡፡ በነገው ዕለትም በእነዚህ አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች ላይ የተደረገውን እስር የሚያወግዝ መሆኑን መግለጽ ይወዳል፡፡
ኑ ራሳችን ነጻ በማውጣት የአገራችን እጣ ፈንታ እንወስን!
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
ዜና 26.04.2014
በደቡብ አፍሪቃ አፓርታይድ ከተገረሰሰበ በነገው ዕለት 20 ዓመት ይሆናል። የፀረ ዘር አድልዎው ትግል ታሪክ እና ስለ ሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ምን ይመስላል?
ስድስት ጦማሪያን እንዲሁም አንድ ጋዜጠኛ ትናንት ከቀትር በኃላ አዲስ አበባ ውስጥ መታሰራቸው ተሰማ። ዞን «9» በመባል የሚታወቀዉ የጦማርያን ስብስብ አባላት ላይ ላለፉት ሰባት ወራት ከፍተኛ ክትትል ሲደረግ መቆየቱም ተመልክቶአል።
የአውሮጳ የደኅንነትና የትብብር ድርጅት በእንግሊዝኛ ምኅፃሩ «ኦሴ» ታዛቢ ቡድን አባላት እንዲፈቱ የጀርመን ፌዴራል መንግሥት ጥሪ አቀረበ።
መፍቀሬ-ሩስያ ታጣቂዎች ይዘው ያቆዩዋቸውን የተወሰኑ የ«ኦሴ» ታዛቢ ቡድን አባላት ለመገናኛ ብዙኃን እይታ አቀረቡ። ከተያዙት ታዛቢዎች መካከል አንድ ስዊድናዊ የስኳር ህመም ስላለበት መለቀቁን ታጣቂዎቹ አስታውቀዋል።
የአቡነ ማትያስ የመነጋገርና የመደራደር አቅም ለጉብኝቱ መሰረዝ በምክንያትነት ተጠቅሷል የግብፁ ፓትርያርክ በስድስት ወራት ውስጥ ሦስት ጊዜ የጉብኝት ጥያቄ አቅርበዋል የአቡነ ታዎድሮስ ተደጋጋሚ ውትውታ ጉዳዩ ከሕዳሴው ግድብ ጋራ መያያዙን አመላክቷል የጉብኝቱ መሰረዝ በአቡነ ታዎድሮስ ጥያቄ እንደኾነ መዘገቡ ከመቅለል መጥቅለል እንዲሉ ነው ‹‹መንግሥት የግብፆችን ያህል ቤተ ክርስቲያኒቱን የዲፕሎማሲው አካል አላደረገም›› (ፋክት፤ ቅጽ ፪ ቁጥር ፵፫፤ ፳፻፮ ዓ.ም.) …![]()
According to the latest information we got, Journalist, campaigner and close friend of Zone9 have been arrested and her house was searched this late morning. For the last few months Edom had been in serious interrogation and surveillance from “Intelligence officers” questioning her details on the activities of the Zone9. Zone Nine again wants to confirm that Edom and other Bloggers has never been a part of any illegal activity and we request the government to release all immediately.
በድጋሚ የዞኑ አባላትና ወዳጆች ምንም አይነት ህገ ወጥ ስራ ላይ ያልተሰማሩ በመሆናቸው መንግስት እርምት ወስዶ በአስቸኳይ አንዲፈታቸው እንጠይቃለን!
Zone9 has confirmed that Six Zone9 bloggers and journalist Tesfalem Woldeyes are in Addis Ababa central investigation center (meakelawi) since their arrest last night. during the arrest their house was searched and police took laptops, Newspapers and books from their home. Families were not allowed to meet them.We believe members and friends of Zone Nine have nothing to do with any illegal activities and we again request the government to release them immediately.
ቀን 18/08/ 2006 ዓ.ም
ውድ የሚዲያ ማህበረሰብ አባላት፡- ባለፉት 23 ዓመታት ህወሓት/ኢህአዴግ በህገ መንግስቱ የሚዲያ ነጻነት እንደሚፈቀድ ቢደነግግም በተግባር ግን የራሱን ፕሮፖጋንዳ ከሚነዛባቸው ሚዲያዎች ውጭ ሌሎቹን ሲዘጋና ሲያሸማቅቅ ኖሯል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ህዝባችን ከገዥው ፓርቲ ፕሮፖጋንዳ ውጭ አማራጭ መረጃ ማግኘት አልቻለም፡፡ ጋዜጠኞች እየታሰሩ፣ እየተሰደዱ፣ ሚዲያዎች እየተዘጉም ቢሆን የተቻላችሁን ያህል ለህዝብ መረጃ ለማድረስ የሚዲያው ማህበረሰብ አባላት ለምታደርጉት ሁሉ ከፍ ያለ ክብር አለን፡፡ የታፈነውን የህዝብ ድምጽ ለማሰማት የምታደርጉትን ጥረትም እናበረታታለን፡፡ ሆኖም አሁንም ቢሆን በገዥው ፓርቲ አፋኝነት ምክንያት ህዝባችን የሚገባውን መረጃ እያገኘ አይደለም፡፡ እናንተም በሰበብ አስባቡ ጫና እየደረሰባችሁ እንደሆነ ፓርቲያችን ይገነዘባል፡፡
ገዥው ፓርቲ ላይ የሰላ ትችት የሚያደርሱ ጋዜጠኞች ‹‹አሸባሪ›› ተብለው ታስረዋል፡፡ ጋዜጦችና መጽሄቶች በስርዓቱ ተዘግተዋል፡፡ በርካታ ጋዜጠኞች አገራቸውን ጥለው ተሰደዋል፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ድብደባ፣ ማስፈራሪያና ዛቻ ደርሶባቸዋል፡፡ እየደረሰባቸውም ነው፡፡ ገዥው ፓርቲ በሚያደርስባቸው ቀጥተኛም ሆነ ተዘዋዋሪ ጫና ከገበያ ወጥተዋል፡፡ በአጠቃላይ በአሁኑ ወቅት ለህዝባችን አማራጭ መረጃ የሚያደርሱ ሚዲያዎችና የሚዲያው ማህበረሰብ መብቶቻቸውን ተነጥቀው አደጋ ላይ ወድቀዋል፡፡
አማራጭ መረጃ ለዴሞክራሲና ለልማት ቀዳሚውን ሚና እንደሚጫወት የሚያምነው ፓርቲያችን ይህን የመብት ረገጣና አፈና ሲቃወምና ሲታገል ቆይቷል፡፡ አሁንም በጠነከረ መልኩ ይቃወማል፡፡
ፓርቲያችን ሀሳብን በነጻነት የመግለጽን ጨምሮ የተነጠቁትን መብቶቻችን ለማስመለስ በመጣሩ አመራሮቹና አባላቱ በህገ ወጥ መንገደ እስር ቤት በሚገኙበት ተመሳሳይ ወቅት የዞን ዘጠኝ ወጣቶች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህም ከመቸውም ጊዜ በላይ ጭቆናው እንደመረረ እና ሁሉን ማህበረሰብ ያቀፈ ትግል እንደሚያስፈልግ ዋነኛ ማሳያ ነው፡፡ ከዚህ የመረረ ጭቆና ህዝባችንን ነጻ ማውጣት የምንችለው እኛ ህዝቡን ማደራጀትና ማንቀሳቀስ የሚዲያ ማህበረሰቡም መደረጃውን ለህዝባችን ማድረስ ሲችል ብቻ ነው፡፡
ፓርቲያችን ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ጨምሮ ገዥው ፓርቲ ከኢትዮጵያውያን የነጠቃቸውን መብቶች ለማስመለስ ተቃውሞ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ የሚዲያው ማህበረሰብ ይህን የተቃውሞ ሰልፍ ሂደት ለህዝብ በማስተላለፍ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የታመነ ነው፡፡ በመሆኑም መብቶቻችን በህዝብ ትግል ይመለሱ ዘንድ እናንተም የተለመደው የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ ጥሪያችን እናስተላልፋለን፡፡
መረጃ ኃይል ነውና በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ የህትመትም ሆነ የብሮድካስት ውጤቶች የተነጠቁትን መብቶቻችን፣ የሰላማዊ ሰልፉን ሂደት፣ በሂደቱ በፓርቲያችንና በህዝቡ ላይ የሚደርሰውን በደል እና ሰላማዊ ሰልፉን ለህዝብ በማድረስ ግዴታችሁን እንድትወጡ አደራ እንላለን፡፡ በተለይ ሌሎች ሚደያዎች በታፈኑበት በአንጻራዊነት የህዝብ ድምጽ በመሆን ላይ በሚገኘው ፌስ ቡክ በኩል መረጃዎችን ለህዝብ በማድረስ ቀላል የማይባል ጫና መፍጠር የሚቻል በመሆኑ አጋጣሚውን በመጠቀም መብታችን ለማስመለስ እንድንታገልና በሰልፉም እንድንገኝ አደራችን እናስተላልፋለን፡፡
ኑ ራሳችን ነጻ በማውጣት የአገራችን እጣ ፈንታ እንወስን!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ልጅ ተክሌ (ቶሮንቶ)
ዘመቻ ነቀምትና ዘመቻ ኢትዮጵያ
፩- የሲያትሉ ባተሌ ወዳጄ ደውሎ፤ “አንድነት የአዲስ አበባውን ሰልፍ ፈቃድ ተከልክሏል፡፡ ስለዚህ ምን ርምጃ ይውሰድ” በሚል ጥያቄ ሲያደርቀኝ ነበር፡፡ ሳንግባባ ተለያየን፡፡ ከሞላ ጎደል እሱ የሚለው፤ “ቢከለከሉም ገፍተው ይውጡ፡፡ ምክንያቱም፤ በተከለከሉ ቁጥር እሺ ብለው የሚገቡ ከሆነ፤ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያጣሉ፡፡ ገፍተው ከወጡ ግን፤ መንግስትም ጨክኖ ርምጃ አይወስድም፤ ቢወስድም ግን፤ ትግሉን ያበረታል፤ ሌሎችንን ይቀሰቅሳሉ” ነው፡፡ ኢፍትሀዊ ህግን መጋፈጥ ፍትሀዊነት ነው የሚለውን ይትበሀል ይዞ መሰለኝ የሞገተኝ፡፡ እኔ ደግሞ “የለም ሁሉንም ሰብስቦ ያስራቸዋል፤ ካሰራቸው ደግሞ ሌሎች ሰልፈኞች መውለድ አመታት ይፈጃል፡፡ ስለዚህ ይታገሱ፤ ሲሆን ሲሆን ወደፍርድቤት ይሂዱ፤ ወይም ሌላ ጥበብ ፈጥረው ሂደቱን ያጡዙት፡፡ እንጂ፤ አሁን ገፍተው ሰልፍ ቢወጡ ትግሉን ማጨናገፍ፤ ማስወረድ ነው” ብዬ ሞገትኩ፡፡ አልተስማማንም፡፡ የዚህ ጽሁፍ አብይ ዓላማም ማስታወቂያና ማስታወሻ ቢሆንም፤ የኛ የወጤዎቹ (ዳያስፖራ) ሚና የት ድረስ ነው? ድርጅቶቻችንስ ከመፈክር የዘለለ አመራር ለመስጠት ምን ሸበባቸው? በማለት፤ ከቅዳሜ ኤፕሪል 26ቱ የቶሮንቶ-ነቀምት ዝግጅት ማስታወሻ ጎን ለጎን፤ ሌሎች ጉዳዮችን በስሱ ያሻሻል፡፡ ከዚያ በፊት ግን፤
![]() |
|
ከመቶ ዓመታት በፊት ወደ ኢየሩሳሌም የመጡ አባቶች
|
Zone9.
ሰሞኑን ናይሮቢ ውስጥ እየታየ ያለውን በስደተኞች ላይ የሚካሄድ አፈሣና እሥራት ተከትሎ ወደ ሰባ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ መደረጉን በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡
ከቪኦኤ ጋር የስልክ ቃለ ምልልስ ያደረጉት በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የቆንስላና የዳያስፖራ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ መለስ ዓለም ተክኤ የኬንያ መንግሥት እርምጃውን እየወሰደ ያለው ስደተኞችን ለማሳደድ ብሎ ሳይሆን በፀጥታ ችግሩ ምክንያት ነው – ብለዋል፡፡
ኬንያ ውስጥ ኢትዮጵያዊያን በተለያየ መንገድ እንደሚኖሩ የገለፁት አቶ መለስ እስከአሁንም ጥቃት የተፈፀመበት ኢትዮጵያዊ መኖሩን እንደማያውቁ አመልክተዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡
“በአራቱ የፖለቲካ እሥረኞች ላይ የቀረቡ ክሦች እንዲሠረዙ ትዕዛዝ የሰጠሁት የደቡብ ሱዳኑን የሰላም ንግግር ሂደት ለማፋጠን ነው” ሲሉ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር አስታውቀዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ ጁባ ላይ በተጠራ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሲናገሩ በአራቱ እሥረኞች የቀረቡ ክሦች እንዲሠረዙ ከአካባቢው ሃገሮች ጫና ሲደረግባቸው መቆየቱንም ተናግረዋል፡፡
ለዝርዝሩ የተያያዘውን ዘገባ ያዳምጡ፡፡
Leaders of Blue Party detained
Addis Peripheral towns and Oromo political parties
Juba released detatined formenr officials
Ethiopian refugees in Kenya – Ethiopian Embassy reaction
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
«የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ» የሚል ስያሜ እንዳለው የጠቀሰው ማኅበር ሕጋዊ ምሥረታ ባካሂድም የፌዴራል በጎ-አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ኤጀንሲ ሕጋዊ ዕውቅና ነፈገኝ ሲል አማሯል።
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ-መንግሥት በኢትዮጵያናኤርትራ ላይ ከፍተኛ ትኩረት አድርጎ እንደሠራ ይጠቀሳል። አማርኛና ትግርኛን ጨምሮ የተለያዩ ቋንቋዎችም ሊቅ ነበር፤ ስዊድናዊዉ ዶ/ር ዮሐንስ ኮልሞዲን።
በዩክሬን የምዕራቡ ዓለም ፍጥጫ እያየለ መምጣቱ ተዘግቧል። የዩክሬይን ባለሥልጣናት ሩስያ «ሦስተኛው የዓለም ጦርነትን» ለማጫራል ትሻለች ብለዋል።
የደቡብ አፍሪቃ ህዝብ ነፃነቱን ካገኘ ከ20 ዓመት በኋላ የሀገሪቱ ወጣቶች ለመሆኑ ምን ያህል ተዋህደው እየኖሩ ነው? ብዙዎችእንደሚሉትግን ከሆነ አሁንም በሀብታም እና ደሀ ፣ በጥቁር እና ነጭ መካከል ልዩነቱ በሰፊው ይስተዋላል።
ፖሊስ የሰልፉን ኃላፊነት እንደማይወስድ አስታወቀ የአዲስ አበባ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነሩ በትናንትናው ዕለት ‹‹እንነጋገር!›› ያላቸውን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች በዛሬው ቀን ቢሮው በሄዱበት ወቅት ‹‹ሙሉ በሙሉ የሰፉን ኃላፊነት ትውስዳላችሁ!›› እንዳላቸው የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴዎች ገልጸዋል፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ በኩል የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ብርሃኑና ምክትል ሰብሳቢው አቶ ስለሽ ፈይሳ የቀረቡ ሲሆን ‹‹እኛ ለፖሊስ ያሳወቅነው በሰልፉ ወቅት ሊፈጠሩ የሚችሉ ችግሮችን እንዲቆጣጠር ነው፡፡ እኛ ሀላፊነት ልንወስድ የምንችለው ይዛናቸው ለምንወጣው ጽሁፍና ለምናስተላልፈው መልዕክት ብቻ ነው፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት ሰልፉን ሊያደናቅፉ የሚመጡ አካላት ቢኖሩ ይህን ኃላፊነት ሊወስድ የሚገባው ፖሊስ ነው›› የሚል መከራከሪያ አቅርበዋል፡፡ አስተባባሪዎቹ ፖሊስ ይህን ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ሰልፉን ለማደናቀፍ ሴራ እየተሸረበ ስለመሆኑ አመላካች ነው ሲልም የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴ አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ምክትል ኮሚሽነሩ ‹‹ሰልፉ ከሚካሄድበት 3 ሰዓት እስከ ስድስት ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ አንድ ደቂቃ ቢያልፍ ህገ በህገ ወጥነት እንከሳችኋለን›› እንዳሏቸው ተግልጻል፡፡ በተመሳሳይ የታሰሩት ወጣቶች ‹‹ህገ ወጥ ወረቀት ነው ሲበትኑ የተገኙት፡፡ ህገ ወጥ ወቀረት በመበተናቸውም ሊታሰሩ ይገባቸዋል፡፡›› ማለታቸውን ገልጸዋል፡፡
በተያዘ ዜና ፖሊስና የደህንነት አባላት የሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ አካባቢ የሚገኘውን ህዝብ በር እያንኳኩ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲን በድምጽ ብክለት ክሰሱት!›› እያሉ እየቀሰቀሱ ነው፡፡ ነገር ግን አብዛኛዎቹ የሰፈሩ ነዋሪዎች ‹‹እስካሁን አልረበሹንም፣ ሊረብሹንም አይችሉም፡፡›› እያሏቸው ነው፡፡ ከዚህ በፊት ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ በዝግጅት ላይ እያለ አመራሮቹ ጃን ሜዳ ፖሊስ ጣቢያ በታሰሩበት ወቅት ፖሊስ ‹‹ህዝቡ ነው የድምጽ ብክለት አድርሰውብናል በሚል›› የከሰሳችሁ ማለቱ ይታወሳል፡፡
በዩክሬን የሰፈነው ውጥረት ተባብሶ ዛሬ ወደ ግጭት ተሸጋግሯል ። በዛሬው እለት የዩክሬን ወታደሮች ምሥራቅ ዩክሬን ከሚገኙት መፍቅሬ ሩስያ ኃይሎች ጋር ተጋጭተው ቢያንስ ሁለት ሚሊሽያዎችን መግደላቸውን መንግሥት አስታውቀዋል ።
የሰው ልጅ ግላዊና ማህበራዊ ህይወቱን ለማሻሻል እንዲሁም የለት ተለት ህይወቱን የተሻለ ለማድረግ በአካባቢው ወይም በሚኖርበት ሃገር ያለውን አካባቢያዊና መንግስታዊ ስርዓት ጤናማ መሆኑ ግድ ነው። የማህበረሰቡም የለት ተለት ህይወት ከግዜ ወደ ግዜ አስቸጋሪ እየሆነ ሲሄድ የዛ ማህበረሰብ መንግስት ወይም አገዛዝ መቀየሩ አንደኛው መፍትሄ ነው። እንደሁለተኛ አማራጭ መፍትሄ የሚወሰደው ደግሞ የነበረውን አገዛዝ ለአነስተኛና ከፍተኛ ለውጦች ካለው ምቹነት […]
ጸጋዬገ ብረመድኅን አርአያ
“ መኳንንቶቼ፣ ልጆቼና ሕዝቦቼ ሆይ! እኔ ስለ እናቴ ኢትዮጵያ ሕይወቴን ልሰዋላት ሙሉ ፈቃድ አለኝ። በእኔ ልብ ያለው አሳብ በትክክል በእናንተም ልብ በመታሰቡ በጣም ደስ ብሎኛል። “ እንግዲህ አሳባችን አንድ ከሆነ ጠንክሩ እንጂ አትፍሩ። ለዘመቻውም አዋጅ አናግራለሁና አይዞአችሁ አትፍሩ! “ አገሬ ሆይ ስሚ! መኳንንቶቼ፣ ወታደሮቼ፣ ሕዝቦቼ ስሙ…..ወደፊት ገስግሱ እንጂ ወደኋላ አትቅሩ! “ የኢትዮጵያ ልጅ ሆይ! ልብ አድርገህ ተመልከት ኢትዮጵያ የተባለችው አንደኛ እናትህ ናት! ሁለተኛ ዘውድህ ናት! ሦስተኛ ሚስትህ ናት! አራተኛ ልጅህ ናት! አምስተኛ መቃብርህ ናት! እንግዲህ የእናት ፍቅር፣ የዘውድ ክብር፣ የሚስት ደግነት፣ የልጅ ደስታ፣ የመቃብር ከባቲነት እንደዚህ መሆኑን አውቀኸው ተነሳ!”
አንበሳው አጼ ዮሐንስ- ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ

ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ!
የተነጠቁ መብቶቻችንን እናስመልሳለን!!!
እሁድ ሚያዚያ 19 ቀን ከጠዋቱ 3 – 8 ሰኣት
ቦታ ከፓርቲው ጽ/ቤት ተነስቶ በአዋሬ፣ አድዋ ድልድይ፣ ባልደራስ አድርጎ መድረሻው ወረዳ 8 ሜዳ የካ ሚካኤል ታቦት ማደርያ ይሆናል፡፡
ኑ ራሳችንን ነፃ በማውጣት የሀገራችንን እጣ ፈንታ እንወስን!
ሰማያዊ ፓርቲ
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሕገመንግሥታዊ መብቴን በመጣስ ቅስቀሳ እንዳላካሄድ ታግጃለሁ፤ አባላቶቼ ያለ አግባብ ታስረውብኛልና ያቀረብካቸው አማራጭ ቦታዎች ወደጎን ተደርገው ህጉ በማይፈቅድለት አካባቢ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳደርግ ተነግሮኛል በሚል በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ በአዲስ አበባ ከንቲባ ጽ/ቤት እና በአዲስ አበባ ፖሊስ ላይ በመሰረተው ክስ የቀረቡትን የክርክር ሃሳቦች ያደመጠው የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 8ኛ […]
የአዲስ አበባና የኦሮምያ ግንኙነት የፌደራል ስርዓቱ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ጊዜ አንስቶ እያወዛገበ ያለ ጉዳይ ነው። በቅርቡ ደግሞ የአዲስ አበባ አስተዳደር የ10 እና የ25 ዓመት የተቀናጀ የጋራ ልማት ፕላን በማዘጋጀት በተለምዶ “ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ ከተሞችን ከአዲስ አበባ ጋር ለማቀናጀት ጥረት መጀመሩ ተድበስብሶ ያለፈውን የፌደራሊዝም ጥያቄ እንደገና እንዲያገረሽ አድርጎታል። የተቀናጀ የጋራ ልማት […]
የኢትዮጵያ ምጣኔ ኃብት በተያዘው የበጀት ዓመት በ11.3 ከመቶ እንደሚያድግ ተተንብዮ የነበረ ቢሆንም ባለፉት 9 ወራት የታየው የውጪ ንግድ ውጤት ግን እንደተጠበቀው አለመሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ የግብፅ መንግሥት ወደ ድርድር እንዲገባ ዓለምአቀፍ ጫና እየተደረገበት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
ከሱዳን ጋር የተደረገ አዲስ የወሰን ስምምነት እንደሌለም ገልፀዋል።
በኤርትራ ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲቀጥል እንደሚፈልጉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተናገሩት በብሪታንያና በአየርላንድ የኤርትራ አምባሣደር ተስፋሚካኤል ገራህቱ ምላሽ ሰጥተዋል።
“ማዕቀቡ ከተጣለ አራት ዓመታት ቢያልፍም በኤርታራ ላይ ምንም ዓይነት ማስረጃ አልቀረበም” ብለዋል አምባሣደሩ።
አምባሣደር…
መንግሥታቸው ካደጉ ሃገሮች ለሚገኝ እርዳታ ሲል የፖሊሲ ለውጥ አድርጎ እንደማያውቅ የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ወደፊትም በዚህ መንገድ የሚመጣ ለውጥ እንደማይኖር ገልፀዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን የገለፁት ባወጣችው የተመሣሣይ ፆታ ግንኙነት ሕግ ምክንያት በዩጋንዳ ላይ እየተደረገ ያለውን ጫና በማስመልከት ለተነሣ ጥያቄ መልስ ሲሰጡ ነው፡፡
ለዘርዝሩ የእስክንድር ፍሬውን ዘገባ ከአዲስ አበባ ያዳምጡ፡፡
የጦር ሹም ሽር አደረጉ
Salva Kiir, South Sudan, reshuffle, four detainees
Ethiopia, Parliament, gayrights
Hailemariam Desalegn’s report to the Parliament
የሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 ቀን 2006 ዓ.ም፣ በአዲስ አበባ ለጠራው ሰላማዊ ሰልፍ፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር እውቅና ሰጠ። አስተዳደሩ፣ ሰማያዊ ፓርቲ፣ አስፈላጊዉን የእውቅና ፎርም በመሙላት ወደ ሰልፍ ተግባራቱ መሰማራት እንደሚችል ትላንት ለፓርቲዉ በላከው ደብዳቤ ማሳወቁ ይታወቃል። በዚያ መስረት የሰማያዊ ከፍተኛ አመራር አባላት፣ በአስተዳደሩ የተጠየቀዉን የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ቅጽ ፎርም በመሙላት፣ ዛሬ ሚያዚያ 16 ቀን አስፈላጊዉን […]
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
ሀሳብን በስፋትና በጥልቀት የመግለፅ አቅሙ እጅግ የዳበረ እንደሆነ ይነገርለታል፤ ጥንታዊው የግእዝ ቋንቋ። አንዳንዶች ግእዝ ሞቷል መቀበር ብቻ ነው የቀረው ሲሉ ይደመጣል። ሌሎች ደግሞ የለም፤ ቋንቋው በቤተክህነትና በሌሎችም ቦታዎች አገልግሎት ላይ እየዋለ ነው አልሞተም፤ እንደውም አሁን እያንሰራራ ነው በማለት ለማስረዳት ይሞክራሉ።
ኬንያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ችግር እየተባባሰ መሄዱን እዚያ የሚገኙ ስደተኞች አስታወቁ ። የኬንያ መንግሥት ስደተኞች በሙሉ በሃገሪቱ ወደሚገኙ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች እንዲገቡ ካዘዘ ወዲህ በተለይ በከተሞች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የፍርሃትና የስጋት ህይወት እንደሚገፉ ለዶቼቬለ አስታውቀዋል ።
ከ 14 ዓመት በፊት የተባበሩት መንግሥታት አጠቃላይ ጉባዔ በተለመው መሠረት አዳጊ አገሮች በ ስምንት ዐበይት ነጥቦች ላይ በማትኮር ፤ በተለይ ድህነትን ግማሽ በግማሽ ለመቀነስ፤ መሠረታዊ ትምህርት ለሁሉም ዜጋ ለማዳረስና