ወጣቷ የግእዝ መምህርትና ደራሲ

ሀሳብን በስፋትና በጥልቀት የመግለፅ አቅሙ እጅግ የዳበረ እንደሆነ ይነገርለታል፤ ጥንታዊው የግእዝ ቋንቋ። አንዳንዶች ግእዝ ሞቷል መቀበር ብቻ ነው የቀረው ሲሉ ይደመጣል። ሌሎች ደግሞ የለም፤ ቋንቋው በቤተክህነትና በሌሎችም ቦታዎች አገልግሎት ላይ እየዋለ ነው አልሞተም፤ እንደውም አሁን እያንሰራራ ነው በማለት ለማስረዳት ይሞክራሉ።