ማሊ እና የምክር ቤታዊው ምርጫ ዝግጅት

ምዕራብ አፍሪቃዊቱ ሀገር ማሊ እአአ የፊታችን ህዳር 24 አዲስ ምክር ቤት ትመርጣለች። የምርጫው ዘመቻ በሳምንቱ መጀመሪያ የተጀመረ ሲሆን፣ ለ147 የብሔራዊ ምክር ቤት መንበሮች 1141 ዕጩዎች በተወዳዳሪነት ቀርበዋል።