ይድነቃቸው ከበደ (የሰማያዊ ፓርቲ የሕግ ጉዳይ ኃላፊ)ይድነቃቸው ከበደ (የሰማያዊ ፓርቲ የሕግ ጉዳይ ኃላፊ)

ነኀሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ሰማያዊ ፓርቲ ታላቅ የተቃውሞ ሠልፍ መጥራቱ የሚታወቅ ነው፤ ይሁን እንጂ በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት እንደሰፈር ጉልበታኛ ድንኳን ሰባሪ ዘው ብሎ በኃይማኖት ሰበብ ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ቀንና ሰዓት እንዲሁም ቦታ በሕግ አግባብ ሣይሆን በጉልበት ሠልፍ መሰል ሠልፍ ማካሄዱ የሚታወቅ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፈቃዱ በቀለ

መግቢያ
በዚህ አርዕስት ላይ ለመጻፍ ከአሰብኩ ረዥም ጊዜ ሆነኝ። እንደሚታወቀው አንድ ጥናታዊ ጽሁፍ ለማቅረብ ቀላል አይደለም። የመንፈስ ርጋታን የሚጠይቅ ብቻ ሳይሆን፣ ለአንባቢ የሚቀርበው ጽሁፍ ከርስ በርስ ቅራኔዎች የተላቀቀና አሳማኝ እንዲሆን አድርጎ ለመጻፍና ለማስነበብ ረዥም ጊዜን ይፈጃል። ብዙ ዕውቀትንና ምርምርን ይጠይቃል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ እና ከፍተኛ ባለስጣኖቻቸዉ የአሜሪካ ምክር ቤት ለፕሬዝደንቱ ሶርያ ላይ ወታደራዊ ጥቃት የመፈጸም መብት እንዲሰጣቸዉ ጥያቄ ማቅረባቸዉን ቀጥለዋል።

በ100 ሺዎች የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ቤተ እስራኤላዉያን ባለፉት ሠላሣ ዓመታት እስራኤል ገብተዋል። ይሁንና ቤተ እሥራኤላውያኑን ከሀገሪቱ ኅብረተሰብ ጋ የማዋሀዱ ተግባር ዛሬም ትልቅ እክል ይታይበታል።

የኬንያ ባለስልጣናት በዓለም ዓቀፉ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት (ICC) ክሳቸው ሊታይ ጥቂት ሳምንታት ሲቀረው፤ የሀገሪቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኬንያ የICC መቋቋሚያ ዉል ፈራሚነቷን ታነሳ ዘንድ ትናንት ሲከራከር ውሏል።

ሰዎች ካለፈ እጅግ መጥፎ ድርጊት ፣ እስከምን ድረስ ትምህርት ይቀስማሉ? በተለያዩ ዘመናት ያጋጠሙ ሁኔታዎችን ፤ ጦርነቶችን ፤ ወረራዎችን ፤ ውዝግቦችን ስንመረምር ፣ ሰው፤ ጭካኔ የሚያሳይባቸው መሣሪያዎች በሥነ ቴክኑኒክ ተሻሽለው ተሠርተው ከመቅረባቸው

በቅስቀሳ ስራ ላይ የነበሩ አራት የአንድነት ፓርቲ አባላት አዳማ ከተማ ውስጥ መታሰራቸው ታወቀ፡፡ ፖሊስ ከ5ሺ በላይ በራሪ ወረቀቶችን ቀምቷቸዋል፡፡ ፖሊስ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ እውቅና ተሰጣችሁ እንጂ በራሪ ወረቀት የመበተን ፍቃድ የላችሁም በሚል ዳንኤል ፈይሳ፣ደረጄ መኮንን፣አስናቀ ሸንገማና ደረጄ ክበበው የተባሉት አባላት ወረዳ አንድ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ታስረው ከሰዓታት በኋላ መለቀቃቸውን የቅስቀሳ ቡድኑ አባላት አስታውቀዋል፡፡ ከትራፊክ ፖሊስ፣ከፖሊስ፣ከደህንነት፣ከደንብ […]

ሰልፈኞቹ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የማያባራ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በመቃወም በደቡብ ኮርያ ፕሬዚደንት ጽ/ ቤት ፊት ለፊት ፕሬስ ኮንፈረንስ በማድረግ የኮርያ መንግስት በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫና እንዲፈጥር ተማጽነዋል። ለ ደቡብ ኮርያ ፕሬዚደንት ፓርክ ግን-ሄ ደብዳቤም ኣስገብተዋል። ሰልፈኞቹ ለደቡብ ኮርያ UNHCR ተወካይና የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ደብዳቤዎችን ያስገቡ ሲሆን በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫና እንዲፈጥሩ ተማጽነዋል። ከሰልፈኞቹ መሃል ኣብዛኛዎቹ […]

በአበሾቹ መንደር ፉት ስክሬይ በአንዱ የሐበሻ ሆቴል ቁጭ ብዬ አንድ ወገን ወደ እኔ መጣ፡፡ መጥቶም አልቀረ ወንበር ሳበና ቁጭ አለ፡፡

‹‹ዐውቅሃለሁ መሰል››

‹‹ይሆናል፣ የሰው መተዋወቂያው ብዙ ነው›› አልኩት፡፡

‹‹ዳንኤል ነህ አይደል›› አለኝ፡፡ አረጋገጥኩለት፡፡ እኔ በቀን አራት ጊዜ የሚፈራረቀው የሜልበርን አየር አልገባኝ ብሏል እርሱ ጃቦኒ ነው ያደረገው፡፡ ራሱን አስተዋወቀኝ፡፡ መጽሐፎቼን ማንበቡን ነገረኝ፡፡ መቼም በውጭ ሀገር ሰማሁ የሚል እንጂ አየሁ፣ እገሌ ነገረኝ የሚል እንጂ አነበብኩ የሚል ሰው ማግኘት ዋድላና ደላንታ ሄዶ ኦራል እንደማግኘት ብርቅ ነው፡፡ አመሰገንኩት፡፡

‹‹እንግሊዝኛ ብችል ኖሮ አንዳንዱን ጽሑፍ እተረጉመው ነበር›› አለኝ እየሳቀ፡፡

‹‹ታድያ ምን ችግር አለው፡፡ አውስትራልያ የእንግሊዝኛ ሀገር ናት፡፡ ተርጉመው›› አልኩት፡፡

‹‹እንደመጣሁ ቋንቋ ትምህርት ቤት ገብቼ ነበር፡፡ ለስደተኞች የሚሰጥ ኮርስ ስላለ ለመውሰድ፡፡ እንግሊዝኛና ብስክሌት በልጅነት ካልጀመሩት ጉድ ይሠራል››

ሳቅኩና ‹‹እንዴት?›› አልኩት››

‹‹ሞከርኩትና ቋንቋውን ትቼ ፈገግታውን ብቻ ተምሬው ወጣሁ›› አለኝ፡፡

‹‹የትኛውን ፈገግታ?››

‹‹አለች የእነርሱ ፈገግታ፤ እንደ ፍሬቻ ብልጭ ድርግም የሚያደርጓት፡፡ ቢገባህም ባይገባህም ከሳቅክ ፈረንጅ ደስ ይለዋል፡፡ ታድያ ሥራ ስገባ ቢገባኝም ባይገባኝም ሳቅ ስል ከአፍንጫ በታች ከአገጭ በላይ በሆነ ፈገግታ ያጅቡኝ ነበር፡፡ እኔ ደግሞ ሥራዬን ከሠራሁ የእነርሱ እንግሊዝኛ ቢገባኝ ባይገባኝ ብዬ ተውኩላቸው፡፡ አንድ ቀን ግን ጉድ ሆንኩ፡፡›› ጉጉቴ ከሳቅ ጋር ጨመረ፡፡

‹‹አንድ አብሮኝ የሚሠራ ልጅ አለ፡፡ በጉሮሮ እንግሊዝኛው ሲያወራኝ ስቄ ነበር የማሳልፈው፡፡ ‹እንግሊዝኛንና ስደትን ስቆ ማሳለፍ ነው› የሚል ጓደኛ ነበረኝ፡፡ ታድያ አንድ ቀን ሥራ እየሠራን የሆነ ነገር ያወራኛል፡፡ ልብ አልሰጠሁትም፡፡ ሲጨርስ ቀና ብዬ በፈገግታ ሳየው ተናደደ፡፡ በማውቃት እንግሊዝኛ ‹‹ምን ሆንክ›› አልኩት፡፡ ‹‹እንዴት እናቴ ትናንት ሞተች ስልህ ትስቃለህ›› አይለኝም፡፡ እኔ ራሴ ደነገጥኩ፡፡ ቀዥቃዣ ፈረንጅ፤ እናቱ ሞታ እስኪ ከፍራሽ አስነሥቶ ሠለስት እንኳን ሳይደርስ ምን ያመጣዋል፡፡ እኛ ድሮ የተማርነውን ሁሉ አጣመው አጣመው ድምጻቸው ሊያዝልኝ አልቻለም፡፡ አሁን ሲገባኝ ግን እነርሱ የጉሮሮ እኛ የከንፈር እንግሊዝኛ ነው የተማርነው፡፡››

‹‹ደግሞ እንግሊዝኛ የከንፈርና የጉሮሮ የሚባል አለው?››

‹‹ታድያስ፡፡ እስኪ ስማቸው፡፡ እኛ ‹ዋተር› ብለን ረገጥ አድርገን ስንጠራ እነርሱ ‹ዋር› ብለው በአየር ላይ ያልፉታል፡፡ እኛ ‹ገርል› እየተባልን ጫን ብለን ስንናገር እነርሱ ‹ገ – ል› ብለው በስሱ ያቆላምጧታል፡፡› አሁን ያለን አማራጭ በአማርኛ እያለቀስን በእንግሊዝኛ መሳቅ ነው፡፡›› እኔ ግን በአማርኛ ሳቅኩ፡፡

‹‹ለምን ትምህርት ቤት አልሄድክም(ውጭ ‹አልገባህም› አይባልም) እዚያ የግድ ከቋንቋው ተናጋሪዎች ጋር ስትቀላቀል ትለምደው ነበር››

‹‹ድመት ጅራቷ የተቆረጠበት ቦታ ተመልሳ አትሄድም› ሲባል ሰምተሃል፡፡ እኛም መቀመጫችንን (እርሱ ሌላ ነበር ያለው) የተገረፍንበት ስለሆነ ነው መሰል ወጣ ስትል እዚያ አይመራህም፡፡ እንጂ እዚህ ሀገርማ ብትማር ብዙ ይረዱሃል፡፡ አየህ ድሮ እንማር የነበረው ለእንጀራ ነበር፡፡ እዚህ መጥተን ሳንማር እንጀራ አገኘን፡፡ ታድያ ለምን እንማራለን? ደግሞ በየስደተኛው ካምፕ ፀጉራችንንና ልባችንን ጨርሰን መጥተን ነው መሰል እዚህ ሀገር ማስታወስ የሚባል ነገር የለም፡፡ ቶሎ ትረሳለህ፡፡ 

‹‹ምን ያህል ጊዜ ቆየህ አውስትራልያ››

‹‹በሃሳብ ዘጠኝ ዓመት፣ በአካል አሥራ ስድስት ዓመት›› አለመረዳቴን ለመግለጥ አንገቴን ሊወድቅ እንደተዘጋጀ ብርጭቆ አወዛወዝኩ፡፡


‹‹ሱዳን ነበርኩ፡፡ ሱዳን ዘጠኝ ዓመት ቆየሁ፡፡ እዚያ እያለሁ በተስፋ አውስትራልያ ነበርኩ፡፡ ነገ ትሄዳላችሁ፣ አልቋል፤ ተጠናቋል፤ ፎርም ሙሉ፤ ተዘጋጁ፤ አሻራ ስጡ፤ ፎቶ ተነሡ ስንባል ዘጠኟን ዓመት ጠጣናት፡፡ እኛስ ይሁን በልጅነታችን ወጥተን ነው፡፡ አረጋውያን አባቶች ነበሩ እዚያ፡፡ ስደትና እብደት ካረጁ በኋላ አያምርም፡፡ የአብርሃም ቤት አዛውንቶች ሲባል ሰምተሃል?››

‹‹አልሰማሁም›› አልኩት፡፡

ቀጠለ፡፡ ‹‹እነዚህ አዛውንቶች ከ1966 ዓም ጀምሮ በኢዲዩ፣ በከፋኝ፣ በምናምን እየተደራጁ ሲዋጉ የኖሩ ናቸው፡፡ በኋላ ግን ሁሉም ነገር አልሆን አላቸው፡፡ አረጁ፡፡ መጀመሪያ በተለያዩ ቦታዎች፤ በኋላ ደግሞ አብዱል ረከም በሚባል የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ከሃያ ዓመታት በላይ በሱዳን አሳለፉ፡፡ በመጨረሻም ከዛሬ ሰባት ዓመት በፊት ወደ 350 የሚጠጉ አዛውንቶች አውስትራልያ መጡ፡፡ መንግሥት ጡረታ ይሰጣቸዋል፡፡ ቋንቋው ግን መከራ ያሳያቸዋል፡፡ ቤት የመጣ ፖስታ ለማንበብ፣ ከማኅበራዊ አገልግሎት ሠራተኞች ጋር ለመግባባት ችግር አለ፡፡ አውስትራልያ ብር እንጂ ቋንቋ አትረዳ፡፡

የዘመድ ሰላምታ ሲመጣ ደብዳቤ

አንብቡልኝ ብዬ ለሰው አስነብቤ – የሚል ዘፈን ትዝ ይልሃል (በዜማ ነው ያለልኝ) እዚህ ተወዳጅ ዜማ ነው፡፡››

‹‹እዚህ ሀገር ከሱዳን የመጡ ይበዛሉ ልበል፡፡››

‹‹ልክ ነህ፤ በተለይ በኢሕአፓና በኢዲዩ ጊዜ ወጥተው፤አሥርና ሃያ ዓመት ሱዳን ኖረው የመጡ ናቸው አብዛኞቹ፡፡ ያልተቀየጠ ንጹሕ የኢሕአፓ ዘር እዚህኮ ነው ያለው፡፡ ጓድ ሲባባሉ ትሰማቸዋለህ፡፡ 

‹‹ ለመሆኑ ግን ከወጣህ በኋላ ወደ ሀገር ተመልሰህ ታውቃለህ?››

‹‹አንድ ጊዜ ብቻ››

‹‹ምነው፤ ጥፊም ይደገማል ይባል የለ እንዴ››

‹‹ታክሲ ነጅ ከሆንክ መደጋገምህ አይቀርም››

ታክሲው አያደርሳቸው››

‹‹ትርፊክ እየጣስክ ትነዳ ትነዳና ነጥብ ትሰበስባለህ፤ ከዚያ ወደ ዘጠኝ አካባቢ ስትደርስ መንጃ ፍቃድህን ነጥቀው እንዳትነዳ ይሉሃል፡፡ እዚህ ሀገር እንዴት ትዘልቀዋለህ፡፡ ሀገር የናፈቀህ መስለህ ኢትዮጵያ ትሄድና አንድ ሦስት ወሯን ቅጣት እዚያ ታሳልፋታለህ፡፡ ‹ለዕረፍት የመጣ ፍቅር›› በሚለው ፋንታ ‹ለዕረፍት የመጣ ሾፌር›› የሚል ፊልም ሠርተህ ትመለሳለህ፡፡››

ቢሆንም አገር አይደል››

‹‹ወዳጄ ሀገር ቤት ደርሶ የመጣና ቤቱ የተቃጠለበት አንድ ነው››

‹‹እንዴት››

‹‹ሙልጭህን ነዋ የምትቀረው፡፡ እዚያ ዝንጥ እያለ የምታየው ዳያስጶራ ሁሉ ከሀገሩ ሲመለስ ስልክ አያነሣ፣ ከሰው አይገናኝ፣ ኢሜይል አይከፍት፤ ይመንናል፡፡ ከሆስፒታል መውጣት በለው፡፡ በተለይ ኢምፖርት ሊያደርጉ የሚሄዱትማ››

‹‹ምንድን ነው ኢምፖርት የሚያደርጉት››

(ይቀጥላል)

ካሮላይን ስፕሪንግስ፣ ሜልበርን፣ አውስትራልያ


Zone9 is an informal group of young Ethiopian activists and bloggers working together to create an alternative independent narration of the socio-political conditions in Ethiopia and thereby foster public discourse that will result in emergence of ideas for the betterment of the Nation. 

In an effort to meet our objectives, we have conducted three different online campaigns that we believe have informed citizens and called for good governance. The fourth and last of the Ethiopian year 2005 campaign will be held under the motto “Ethiopian Dream – Let us all dream it together” between 5th-7th of September, 2013. 

Our country Ethiopia is home of rich history, beautiful cultures and identities. Having and recognizing our differences, the presence of an all-inclusive shared national dream is a crucial element in the nation building effort. It is in this view that the 4th online campaign will try to create a stage for all Ethiopians to envision a better Ethiopia. 

Among the major objectives of the campaign are: · 

a) to envision an all-inclusive country, equal to Ethiopians from all walk of life and background and accommodative of all cultures and identities, 

b) to seek for ways that encourage and look for just economic, social and political progress in the country, 

c) to preach for religious tolerance and 

d) to envision Ethiopia that all Ethiopians aspire to live in and none desire to leave behind. 

The campaign mainly will be held on Twitter and Facebook. Articles, that motivate citizens to question themselves and discuss their dream for the country, will be published on our blog. Status updates and tweets (containing unique hashtag #EthiopianDream is developed for the purpose) will be circulated. Banners will be developed to be used as a profile picture throughout the campaign period.

Dear all Ethiopians who want to see Ethiopia an even more proud nation that is equal to all, where citizens work together focusing on human and national development without any negative feeling for each other; you all are invited to join the campaign to sharing your dream and sharing others’ dream. 

Zone9 
We blog because we care!!!


ዞን 9 ኢ-መደበኛ የአራማጆች እና የጦማሪያን ቡድን ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ማኅበረሰባዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታ የተለየ እና ወገናዊ ያልሆነ ተረክ ለመፍጠር እየሰራ የሚገኝ የወጣቶች ስብስብ ነው፡፡ ይህንን የምናደርግበት ዋና አላማ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሀገሪቷ ጉዳይ ያገባኛል ብለው ውይይት የማድረግ ባህል እንዲያሳድጉ በማድረግ ሀገሪቷን በሁሉም መስኮች ወደተሻ ለደረጃ የሚያደርሱ ሃሳቦች እንዲወለዱ ለማመቻቸት ነው፡፡ 

የተከበራችሁ የዞን9 ነዋሪዎች፣ በ2005 ዓ.ም ሊደረጉ ከታቀዱት አራት የበይነ መረብ ዘመቻዎች አራተኛው እና የመጨረሻው ዘመቻ ነገ ሐሙስ ነሐሴ 30 ቀን 2005 ዓ.ም እስከ ቅዳሜ ጳጉሜን 2 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል፡፡ አራተኛው ዘመቻ ‹‹#ኢትዮጵያዊ_ሕልም፤ ኑ አብረን እናልም!›› በሚል ርዕስ መላው ኢትዮጵያውያንን ኢትዮጵያ ሆና ማየት የሚፈልጉትን እና እዚያ ለመድረስ መደረግ አለበት የሚሉትን የሚያካፍሉበት ይሆናል፡፡ 

የረጅም ታሪክ፣ የውብ ባሕል እና ማንነቶች ባለቤት በሆነችው ሀገራችን ኢትዮጵያ፤ ዜጎቿ እርስ በርስ ተስማምተው እና ሁሉንም ዕኩል ባሳተፈ መልኩ ሀገሪቷን ለመገንባት ከሚያስችሉት ግብዓቶች መሐከል የጋራ ሕልም መኖሩ ዋነኛው ነው፡፡ ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ አራተኛው የበይነመረብ ዘመቻ ኢትዮጵያዊያን ለኢትዮጵያ ያላቸውን የወደፊት ተስፋ እንዲጋሩ መድረክ ለመፍጠር ይጥራል፡፡ 

የዘመቻው ዋና ዓላማዎችም፤ ሁሉንም አካታች፣ ለሁሉም ምቹ፣ ለሁሉም ዕኩል ዕድል የምትሰጥ ኢትዮጵያን ለማመለካከት፣ የቋንቋ እና ባሕላዊ ኅብርን አስፈላጊነት እና ጥቅም ለማመላከት፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ፍትሕን ለማምጣት የሚበጁ አመለካከቶችን ለማስረጽ፣ ሃይማኖታዊ መቻቻልን ለመስበክ እና በተለይም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊኖርባት የሚፈልጋት፣ ተሰዶ የማይወጣባት፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ዕኩል የሚታዩባት፣ የሚጠቀሙባት እና የሚጠቅሟት ኢትዮጵያን ማለም እንዲቻል ማድረግ ይሆናሉ፡፡

ዘመቻው በዋነኛነት የሚካሄደው ‹‹ፌስቡክ›› እና ‹‹ትዊተርን›› በመጠቀም ይሆናል፡፡ ዜጎች ለሀገሪቷ ያላቸውን ሕልም በተመለከተ እራሳቸውን እንዲጠይቁ እና እንዲወያዩ የሚያስችሉ የተለያዩ ጽሑፎች በጦማራችን ይወጣሉ፡፡ በሁለቱ ማኅበራዊ አውታሮች ላይ ለዚሁ ዘመቻ ሲባል የተዘጋጁ አጫጭር ጽሑፎች ይሰራጫሉ፡፡ ዘመቻውን የሚመለከት ‹ባነር› ተዘጋጅቶ ዘመቻው በሚቆይባቸው ቀናት የተለያዩ ፕሮፋይል ምስሎችም ተዘጋጅተው የሽፋን ምስል እና የፕሮፋይል ፎቶ ይሆናሉ፡፡

ኢትዮጵያ ለሁሉም ዜጎቿ ምቹ፣ ሁሉም ዜጎቿ ካለምንም የጥላቻ ስሜት እርስ በርስ ተደጋግፈው ሰብኣዊና ቁሳዊ የሀገር ግንባታ ላይ ብቻ የሚያተኩርበት እና የበለጠ የምታኮራ ሀገር ሆና ማየት የምትፈልጉ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በዚህ ዘመቻ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ ሕልማችሁን እንድታጋሩ እና የሌሎችን ሕልም እንድትጋሩ እንጋብዛለን፡፡

ስለሚያገባን እንጦምራለን!!! 
ዞን9

ስፖርት በጣም እወዳለሁ፤ ወቅታዊ ዜናና ጥናታዊ ፊልምም አዘወትራለሁ። ከሁለቱ ዉጭ ግን ኢትዮጵያ እያለሁም ሆነ ዛሬ በስደት ኑሮዬ ከቴሌቪዥን ጋር ብዙም አልዋደድም . . . ግን አንዳንዴ እበድ ሲለኝ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም ቴሌቪዥን ሆኖ ከመተኛቴ በፊት ኢቲቪ እየከፈትኩ አብዳለሁ። አዎ . . . አብዳለሁ። ሆዴ ያመቀዉ ቁጣና ልቤ የተሸከመዉ የ22 አመት በደል ቀለል የሚለኝ ሳብድ ነዉና ኢቲቪ […]

ነሃሴ ፳፰(ሃያ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው አዲስ ራእይ በሚባለው ልሳኑ ” ፣ በሀይማኖት ሽፋን የሚካሄዱ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች እየተዳከሙና እየተጋለጡ መሄዳቸው ባይቀርም ባለፉት ሁለት አመታት ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ ስርአቱን በሐይል ለመፈታተን ከመከሩት የሁከት ሀይሎች ዋነኞቹ ነበሩ ማለት ይቻላል” ብሎአል። ኢህአዴግ ከአክራሪዎች ጎን በመቆም አመጽ ለማነሳሳት ሞክረዋል ካላቸው ድርጅቶች መካከል ድምጻችን ይሰማ፣ ግንቦት 7 አሜሪካ ድምጽ …

ነሃሴ ፳፰(ሃያ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው እሁድ በአዲስ አበባ ሰማያዊ ፓርቲ ሊያደርገው የነበረውን የተቃውሞ ሰልፍ በሀይል የጨፈለቀው የ ኢህአዴግ መንግስት፤ በርካታ የፓርቲውን አባላት እንዳሰረ ፣ እንደደበደበና እና የጽህፈት ቤቱን ንብረት እንደመዘበረ ፓርቲው መግለጹን ቢቢሲ በትናንት ዘገባው አመልክቷል። የፓርቲውን  ሊቀመንበር ይልቃል ጌትነትን በመጥቀስ የዜና አውታሩ እንደዘገበው፤ እሁድ ሊካሄድ ለነበረው ሰላማዊ ሰልፍ በፓር ቲያቸው የተዘጋጁ …

ነሃሴ ፳፰(ሃያ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከአራት ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የወጣበትና በኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት የኪነጥበባት ባለሙያዎች፣ ምሁራንና የሚዲያ ባለሙያዎች ቡድን የተሳተፉበት የጉብኝት ፕሮግራም ከግንቦት 24 እስከ ሰኔ 4/2005 ዓ/ም በኢትዮጵያ ሶማሊ ክልል መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ይህንን መነቃቃትና የገጽታ ግንባታ አጠናክሮ ለመቀጠል ያስችላል የተባለ ታላቅ ድግስ ጳጉሜ 3 ቀን 2005 በሸራተን …

ነሃሴ ፳፰(ሃያ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦባማ አስተዳደር በዜጎቹ ላይ የኬሚካል መሳሪያዎችን በመጠቀም ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል ባለው የባሽር አላሳድ መንግስት ላይ እርምጃ እንደሚወስድ ሲያስጠነቅቅ ከቆ በሁዋላ በመጨረሻም ፕሬዚዳንቱ፣ ጉዳዩን ለኮንግረስና ለሴኔት አቅርበው ለማስወሰን በመፈለጋቸው ባለፈው ሳምንት የታየው  የጦርነት ደመና ዝናቡን ሳያርከፈክፍ መጥፋቱ ይታወቃል። ይሁን እንጅ ፕሬዚዳንት ኦባማ የዲሞክራት እና የሪፐብሊካን መሪዎችን ከአነጋገሩ በሁዋላ ፣ …

  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

የግብጽ የጦር ፍርድ ቤት በ52 የሙስሊም ወንድማማቾች አባላትና ደጋፊዎች ላይ ከአምስት ዓመት እስከ እድሜ ልክ እስራትን በየነ። ከተከሰሱት መካከል አንዱ የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸዋል።

በተከታታይ የሚፅፉና አስተያየት የሚሠጡት አፍሪቃዉያን ምሁራን እንደሚሉት የቀድሞ አዉሮጳዉያን ቅኝ ገዢዎች ተመልሰዉ አፍሪቃን ቢገዙ የአሕጉሪቱን ሕዝብ በራሱ ወገኖች አሁን ከሚያየዉ ስቃይ ይገላግሉታል

UNAIDS በመድሃኒት ስርጭትና ቁጥጥር ረገድ ኢትዮጵያ ከሌሎች የአፍሪቃ ሀገሮች ጋ ስትነፃፀር በተሻለ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ የገለጸዉ በያዝነዉ ዓመት ግንቦት ወር ነዉ። እንደድርጅቱ ዘገባም በቫይረሱ አዲስ ከሚያዙት ይልቅ መድሃኒት የሚወስዱ ወገኖች ቁጥርም ከፍ ማለቱን ያመለክታል።

አብርሃ ደስታ Abreha Destaአብርሃ ደስታ ከመቐለ

የህወሓት ደጋፊዎች የአቶ አርከበ ሚና መቀነስ በአቶ አባይ ምክንያት እንደሆነ ያስባሉ። እንደኔ ግን አርከበ የተገለለው በአባይ ወልዱ ሳይሆን በመለስ ነው። መለስ ሥልጣን በጣም ከመውደዱ የተነሳ ሥልጣኑን የሚፎካከሩና አደጋ የሚደቅኑ አቅም ያላቸው የህወሓት ሰዎች ሲያርቅና ሲያጠፋ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ክንፉ አሰፋ
በተንጣለለ ቪላ ውስጥ ከበድ ያሉ እንግዶች “ጸዳ” ባሉ ምግብና መጠጦች እየተስተናገዱ ነው። ታዋቂ ግለሰቦች፤ ባለሥልጣናት እና አርቲስቶች የቀረበላቸውን ቡፌ በልማታዊ ወጋቸው እያወራረዱ ሳሉ፤ አንድ እንግዳ ነገር በመሃላቸው ተከሰተ። ሞቅ ባለው የአይቴ ነጋ ገብረእግዚአብሔር ድግስ ላይ ያልተጋበዙ ሁለት ሰዎች ዘው ብለው ከግብዣው ክፍል ገቡ። የፌዴራል ፖሊስ አባላት ነበሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ Journalist Temesgen Desalegnተመስገን ደሳለኝ
“በአፍሪካ ትልቁ አምባገነን” የሚል ተቀፅላ የተሰጣቸው የሊቢያው ኮሎኔል መሀመድ ጋዳፊ እና የግብፁ ሆስኒ ሙባረክ በህዝባዊው እምቢተኝነት ከሥልጣን መነሳታቸው በመሰል አገዛዞች ስር ያደሩ ሕዝቦችን ለለውጥ ማነቃቃቱ የሚጠበቅ ነው። በተለይም ከራሳቸው መንግሥት ተኳርፈው አስተማማኝ የዲሞክራሲ ተቋማትን በገነቡ የምዕራብ ሀገራት በብዛት የሚኖሩ ዜጎች ላሏት ኢትዮጵያ ንቅናቄው የፈጠረው ተመሳሳይ መነሳሳት ቀላል ባለመሆኑ ኢህአዴግን ሊወጣው ከማይችለው ቅርቃር ውስጥ ከቶታል። የዚህ ተጠየቅም ቀድሞ እንዲህ አይነት ችግሮች ሲፈጠሩ ድርጅቱ ‘እሳት ማጥፊያ’ ያደርጋቸው የነበሩ አጀንዳዎቹ ያለፈባቸው (Expired) መሆናቸውን ማሳየት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጁ ላይ ኢህአዴግ ከተቃዋሚ ፓርቲዎቹ ከአንድነት፣ ከሰማያዊ፣ ከመድረክ እና ከኢዴፓ ጋር በቴሌቭዥን ውይይት አካሂዷል። ውይይቱን ሊመለከቱት ይገባል ብለን እናምናለን። ሁለተኛውን ክፍል ቪዲዮ ከክፍል አንድ ቪዲዮ በታች ያለውን “ሙሉውን አስነብበኝ”ን በመጫን ያገኙታል። የማጫወቻ ቁልፉን በመጫን ይመልክቱ!

ክፍል ፩

ሙሉውን አስነብበኝ …

በተንጣለለ ቪላ ውስጥ ከበድ ያሉ እንግዶች “ጸዳ” ባሉ ምግብና መጠጦች እየተስተናገዱ ነው። ታዋቂ ግለሰቦች፤ ባለስልጣናት እና አርቲስቶች የቀረበላቸውን ብፌ በልማታዊ ወጋቸው እያወራረዱ ሳሉ አንድ እንግዳ ነገር በመሃላቸው ተከሰተ። ሞቅ ባለው የአይቴ ነጋ ገብረእግዚአብሄር ድግስ ላይ ያልተጋበዙ ሁለት ሰዎች ዘው ብለው ከግብዣው ክፍል ገቡ። የፌዴራል ፖሊስ አባላት ነበሩ። በዚህ ያልተለመደ ክስተት የአቶ ነጋ እንግዶች አልተደናገጡም ነበር። […]

ሰሞኑን ከፀረ አሸባሪነት ህግ በማስቀጠል የአዲስ አበባን ከተማ ነዋሪን በተለ ሲያምስ ከርሞ አሁንም በማመስ ላይ ያለው የመኖሪያ ቤት ጉዳይ ነው፡፡ በእዲስ አባባ የመኖሪያ ቤት ችግር እንዳለ አሌ የሚባል አይደለም፡፡ ይህ ችግር እዚህ እንዲደርስ ደግሞ ዋናው ተዋናይ መንግሰት እንደሆነ መዘንጋት የለበትም፡፡ ምክንያቱም ለቤት መስሪያ የሚሆነውን ቦታ በቁጥጥሩ ስር አድርጎ ለዜጎች እንዳይደርስ በማድረጉ ነው፡፡ አንደኛው በቁጥ-ቁጥ ቦታ […]

The Secret ሚስጢሩ ወለላዬ ከስዊድን
ስለተከሰተው ሚስጥርና የሚስጥሩን ቀላል መደረግ አሁን የሚጠይቁኝ አይመስለኝም። ይልቁንም አጠቃቀሙ እንዴት ነው? ይሉኝ ይሆናል። ለዚህ በክፍል ሦስት ጽሁፌ መልስ ይዣለሁ። ከዛ በፊት ግን ታላቁ መጽሐፍ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ይላል? የሚስጥሩ ተጠቃሚዎችስ ምን ይነግሩናል? ይሄን አንብበው ወደ ሚስጥሩ አጠቃቀም ይሻገሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሰማያዊ ፓርቲ ቅዳሜ ጳጉሜን 2 ቀን በመስቀል አደባባይ ህዝባዊ የሰላማዊ ሰልፍ ጠራ

Ethiopia Zare (ሰኞ ነኀሴ 27 ቀን 2005 ዓ.ም. September 2, 2013)፦ እሁድ ነኀሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. ታላቅ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ በዝግጅት ላይ የነበረው የሰማያዊ ፓርቲ ቅዳሜ ነኀሴ 25 ቀን ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ሲቪል በለበሱ ግለሰቦች መሪነት በፖሊሶች ጽሕፈት ቤቱን ጥሰው በመግባት አመራሮቹ መታሰራቸውንና ንብረቶች መወረሳቸውን ፓርቲው ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ግርማ ሠይፉ ማሩ
ሰሞኑን ከፀረ-አሸባሪነት ሕግ በማስቀጠል የአዲስ አበባን ከተማ ነዋሪን በተለይ ሲያምስ ከርሞ አሁንም በማመስ ላይ ያለው የመኖሪያ ቤት ጉዳይ ነው። በአዲስ አባባ የመኖሪያ ቤት ችግር እንዳለ አሌ የሚባል አይደለም። ይህ ችግር እዚህ እንዲደርስ ደግሞ ዋናው ተዋናይ መንግሥት እንደሆነ መዘንጋት የለበትም። ምክንያቱም ለቤት መስሪያ የሚሆነውን ቦታ በቁጥጥሩ ስር አድርጎ ለዜጎች እንዳይደርስ በማድረጉ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ …

“ከአድባይነት እርግማን ይሰውረን!”

ታክሎ ተሾመ

የኃይማኖት መሪው ቡድሐ የሚሰጠን አንድ እንቆቅልሽ የሚከተለውን ይመስላል። አንድ ነጋዴ ሩቅ ሄዶ ሲመለስ፤ ቤቱ በሽፍቶች ተዘርፎና ተቃጥሎ ይደርሳል። ከቤቱ ከተረፈው ረመጥ – መካከል አንድ ተቃጥሎ የከሰለ የሰው ገላ ያያል። “ይሄ ትንሹ ልጄ መሆን አለበት” አለ። በዚህ ምክንያት ምርር ብሎ አለቀሰ። ደረቱን መታ። ፀጉሩንም ነጨ። ገላውን እንደገና የማቃጠል፤ የሐዘን ሥነ-ስርዓት እንዲካሄድም አደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምክር ቤት፤ የትላንት እሁድ ሰልፍ
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ከተመሠረቱት አዲሶቹ የፖለቲካ ድርጅቶች ወገን የሚመደበው የሰማያዊ ፓርቲ አሁንም የተቃውሞ ድምጹን የሚያሰማበት ሰላማዊ ሰልፍ የሚያደርግ መሆኑን ገለጠ።

Marthe Van der Wolf ከአዲስ አበባ ለአሜሪካ ድምጽ ባጠናቀረችው ዘገባ እንደጠቆመችው፤ ሰማያዊ ፓርቲ ከመቶ በላይ አባሎቹ ከታሰሩበት በኋላ ለትላንት እሁድ ጠርቶት የነበረውን ሕዝባዊ ትዕይንት መሠረዙን አስታውቋል።

የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምክር ቤት፤ የትላንት እሁድ ሰልፍ
 የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘት ከአክራሪነት ጋር ተባብረዋል የተባሉ የፖለቲካ ኃይሎች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ፤ ወጣቶችም “ሥልጣን ፈላጊ” ላሏቸው መሣሪያ እንዳይሆኑ ማሳሰቢያ ተሰጠ፡፡

ማሳሰቢያው የተሰማው የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ላይ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ነው፡፡

  ESAT Radio Daily Broadcast to Ethiopia. Frequency Details: 7 days a week Short Wave (SW) from 8:00 pm to 9:00 pm (Local Ethiopian Time) 19 Meter Band 15355 kHz, 15360 kHz, 15365 kHz, 15370 kHz, 15380 kHz, 15385 kHz and 15390 kHz Download/Listen

ከየክልሉ የተውጣጡ የአስተዳደር አባላት እና የሃይማኖት ተጠሪዎች ባለፈው ሳምንት ከማክሰኞ እስከ ኀሙስ በአፍሪቃ ሕብረት አዳራሽ ተገኝተው ሀገር አቀፍ ጉባኤ ማካሄዳቸው ይታወሳል።

ፕሬዝዳት ኦባማ የሚተማመኑበትን እቅዳቸዉ ለማስፈፀም-የሚተማመኑበትን ዘመናይ ጦር ከምርጥ መሳሪያዎቹ ጋር አዝምተዋል።የሶሪያ የቅርብ ወዳጆች ሩሲያ፥ ቻይና እና ኢራን የድብደባዉን ዕቅድና ዘመቻ አጥብቀዉ ይቃወማሉ።የሩሲያዉ ፕሬዝዳት ቭላድሚር ፑቲን ከዚሕም አልፈዉ አሜሪካና የተባባሪዎችዋን አቅድ አጣጥለዉ ነቅፈዉታል።

ለረጅም ጊዜ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ አዘጋጅ ሆኖ ያገለገለዉና የጋዜጣዉ ህትመት ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ የኢቦኒ መፅሔት ዋና አዘጋጅ ሆኖ በመስራት ላይ የሚገኘዉ ጋዜጠኛና ብሎገር ብስራት ወልደ ሚካኤል ሰሞኑን በ4 የደህንነት ኃይሎች ታግቶ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እንደተፈፀመበት ተናገረ ፡፡ ድርጊቱ የተፈፀመዉ ባሳለፍነዉ ሰኞ (ነሐሴ 20 – 2005ዓ.ም) ከምሽቱ 2፡35 ላይ ከስራ ወደ ቤቱ በጉዞ ላይ እያለ ነበር፡፡ […]

አመራሩ በታገደበት ቆይቶ የኑፋቄ ውዝግቡ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ ጠይቋል አመራሩ ኑፋቄው በአግባቡ እንዳይጣራ የተለያዩ ተጽዕኖዎችን ሲፈጥር ቆይቷል ብዙኀኑ የሀ/ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ አባላት በውሳኔው ቃለ ጉባኤ ላይ አልፈረሙም ‹‹ከዚህ በኋላ ለሚፈጠረው ችግር ሓላፊነቱን የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት ይወስዳል፡፡›› /ሰበካ ጉባኤው/   በፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ሕዋስ በመጠለፉና በቃለ ዐዋዲው ድንጋጌ መሠረት ለሰበካ ጉባኤው መመሪያ ባለመገዛቱ የመዘጋት ርምጃ የተወሰደበት የድሬዳዋ ደብረ …

የኢትዮጵያን ነጻነት ስናስብ ልንዘክራቸው የሚገቡ፣ ለሀገሪቱ ደማቸውን ያፈሰሱ፣ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ የታገሉ፤ ለነጻነቷ ሲሉ ከገዛ መንግሥታቸው ጋር የተሟገቱ፣ ዕውቀታቸውንና ገንዘባቸውን የከሰከሱ አያሌ የሌላ ሀገር ሰዎች አሉ፡፡ በተለይ ዛሬ ኢትዮጵያዊነት ቆሻሻ እንደ ነካው ልብስ በሚገፋበት ጊዜ ለኢትዮጵያዊነታችን ዋጋ የከፈሉትን ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ሰዎች ማስታወስ ግድ ይለናል፡፡

እዚህ አውስትራልያ መጥቼ ካገኘኋቸው መጻሕፍት አንዱ ‹ተልዕኮ 101 – Mission 101› የተባለ ዱንካን ማክናብ(Duncan Mcnab) በተባለ ሰው የተጻፈ መጽሐፍ ነው፡፡ ማክናብ መርማሪ(detective) ፖሊስ፣ የግል የምርመራ ሥራ (Investigator) ባለሞያ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ የነበረ አውስትራልያዊ ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ በእንግሊዝ ወታደራዊ ተልዕኮ ውስጥ በመሰለፍ ለኢትዮጵያ ነጻነት የታገሉ አራት አውስትራልያውያን ወታደሮች ታሪክ ቀርቧል፡፡ ከአራቱ አንዱ የዱንካን ማክናብ አጎት ነበረ፡፡

በዚህ መጽሐፍ ላይ ከአራቱ ወታደሮች ጋር ታሪኩ ተያይዞ የቀረበ አንድ ሌላ ሰው አለ፡፡ ይህ ሰው የተወለደው እኤአ ኖቬምበር 25 ቀን 1877 ዓም በደቡብ ብሪዝበን(አውስትራልያ) ነው፡፡ አያት ቅድመ አያቶቹ ትንግርታዊ ጉዞ የሚወዱ(adventurers) ነበሩ፡፡ አያቱ ከእንግሊዟ ዌልስ በ1800ዎቹ ነበር ወደ አውስትራልያ የገባው፡፡ በምሥራቅ አውስትራልያ ከ117ሺ ሄክታር በላይ መሬት የነበረው ሀብታም አሳራሽ ነበረ፡፡ በኋላ ግን ወደ እንግሊዝ ተመልሶ በሄርፎርድ ሻየር ኑሮውን ቀጠለ፡፡ ልጁን አርኖልድንም በአዳሪ ትምህርት ቤት አስተማረው፡፡

በ1896 አርኖልድ እንግሊዝን ተወና ወደ አውስትራልያ መጥቶ በቤተሰቡ እርሻ ላይ መሥራት ጀመረ፡፡ በከተማ በሚገኘው ዘመናዊ ቤት ከመኖር ይልቅ በገጠር በነበረው የገበሬዎች ቤት ውስጥ በመኖርና አኗኗሩን ሁሉ እንደ ገበሬዎቹ በማድረግ የተለየ ሕይወት የመኖርን ዘይቤ እንደ አያቶቹ ተካነበት፡፡ ‹ቋረኛው› አርኖልድ ዊንሆልት እንግዲህ የዚህ ሰው ልጅ ነበር፡፡

ዊንሆልት ሲፈጥረው የትግል ሰው ነው፡፡ መከራ ባለበት ቦታ ገብቶ መታገል የሚወድ፡፡ በ1899 እኤአ በደቡብ አፍሪካ የቦር ጦርነት ሲፈነዳ የቤተሰቡን ሀብት ትቶ እንዲያውም ለፈረስ መግዣ እንዲሆነው የተወሰነውን ሽጦ በኩይንስ ላንድ ጦር ወስጥ በመመዝገብ በ1900 ወደ ደቡብ አፍሪካ ሄደና ለለስምንት ዓመት በውጊያ ላይ ቆየ፡፡ ጦርነቱ ሲፈጸምም ወደ አውስትራልያ ተመልሶ የቤተሰቡን ሀብት ማስተዳደር ጀመረ፡፡ ከሀብቱ ጎን ለጎን በኩዊንስ ላንድ ፖለቲካ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ለግዛቲቱ ሕግ አውጭ ምክር ቤት በ1909 ተመርጦ ነበር፡፡ ከዚያም በኋላ በ1913 እኤአ ወደ አፍሪካ ተመልሶ በደቡብና በደቡብ ምእራብ አፍሪካ ውጊያዎች ላይ በፈቃደኛነት ተሳትፏል፡፡ እንዲያውም በናሚቢያ በረሃ እያለ በአንበሳ እስከ መነከስ ደርሶ ነበር፡፡

በዚህ መካከል በ1928 ዓም ሞሶሎኒ ኢትዮጵያን ወረረ፡፡ ዊንሆልት ይህ ነገር በጣም ነበር ያሳሰበው፡፡ በአንድ በኩል የኢትዮጵያ መወረር፤ በሌላ በኩል ሞሶሎኒ በአፍሪካ ለነበሩ የእንግሊዝ ቅኝ ግዛቶች አደጋ መሆኑ ልቡን ገዝቶታል፡፡ ጦርነቱን በቅርብ ለመረዳት እንዲችል የብሪዝበኑ ኮርየር ሜይል ጋዜጣ የጦርነት ሪፖርተር አድርጎ ወደ ምሥራቅ አፍሪካ እንዲልከው አደረገ፡፡ በኖቬምበር 22 ቀን 1935 እኤአ ከአውስትራልያ ወደ አፍሪካ በመርከብ አመራ፡፡ በኤደን በኩል አድርጎ ጅቡቲ፣ በጅቡቲ በኩልም በባቡር ተሣፍሮ አዲስ አበባ ገባ፡፡ ኢምፔሪያል ሆቴልም ዐረፈ፡፡

አርኖልድ ዊንሆልት

ዊንሆልት በኢትዮጵያ አርበኞች የአልበገር ባይነት ውጊያ መንፈሱ ተማርኮ ነበር፡፡ እርሱ በደቡብ አፍሪካ፣ በናሚቢያና በአንጎላ የተዋጋው የደፈጣ ውጊያ ስልት በኢትዮጵያ አርበኞች ሲተገበር ማየቱ እንዲቀላቀላቸው ይገፋፋው ነበር፡፡ ዊንሆልት ስለ ደፈጣ ውጊያ አንብቧል፣ ሠልጥኗል፤ በተግባርም ሠርቶበታል፡፡ የደፈጣ ውጊያም ይማርከዋል፡፡ ይህንን የአርበኞች ውጊያ ለመረዳትና ለመዘገብ ግን አልቻለም፡፡ ጣልያኖች ጋዜጠኞች ከአዲስ አበባ እንዲወጡ አይፈቅዱም ነበር፡፡
ዊንሆልት ይህ ነገር መንፈሱን አላረካው ሲል የቀይ መስቀል ሾፌር ሆኖ በመቀጠር ወደ ገጠሮች ለመሄድ ወሰነ፡፡ በ1936 እኤአ የፈለገውን ሥራ አገኘው፡፡ በዚህ ሥራው አማካኝነት በአዲስ አበባ ለነበረው የእንግሊዝ ሌጋሲዮን መረጃ ከማቀበሉም በላይ ጦርነቱን በቅርብ ለመረዳትም ቻለ፡፡ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ጦርነቱ ዜና መሆኑ አበቃ፡፡ ዊን ሆልትም ወደ አውስትራልያ ተመለሰ፡፡

ዊንሆልት በአንዳንድ ኢትዮጵያውያን ጠባይ ባይደሰትም የኢጣልያ ወረራ ግን ትክክል አልነበረም ብሎ ያስብ ነበር፡፡ በወቅቱ የነበሩት ኃያላን ሀገሮች ለኢትዮጵያ ጥያቄ ተገቢ መልስ አለመስጠታቸውም አሳዝኖታል፡፡ ይህንን ስሜቱን ኮርየር ሜይል ለተሰኘው ጋዜጣ እየጻፈ ቢልክም ዋና አዘጋጁ ግን ለማተም ፈቃደኛ አልነበረም፡፡ ዊንሆልት ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሞሶሎኒንና የእንግሊዙን ጠቅላይ ሚኒስትር ቻምበርላይንን ያወግዝ ነበር፡፡ ጋዜጦች የነፈጉትን ዕድል የተለያዩ መድረኮችን በማዘጋጀት ይወጣ ነበር፡፡ ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ስለ ኢትዮጵያ ይናገራል፡፡

በ1937 እኤአ ዊንሆልት አውስትራልያን ለቅቆ እንደገና ወደ የመን አመራ፡፡ በየመን ዋና ከተማ ኤደን ያገኛቸውን የእንግሊዝ ታላላቅ ወታደራዊ ባለ ሥልጣናትንም ኢትዮጵያን ለማገዝ እንግሊዝ ጦር ማዝመት እንዳለባት መወትወት ጀመረ፡፡ በተለይም የአርበኞችን የደፈጣ ውጊያ በመጠቀም ጣልያንን ሰላም መንሣትና በመጨረሻም ማስወጣት አለብን የሚለውን ሃሳቡን በተደጋጋሚ ለማሳመን ይጥር ነበር፡፡ የየመን ቆይታው አልሳካ ሲለውም ወደ ለንደን አምርቶ ከእንግሊዝ የዲፕሎማሲና ወታደራዊ ባለሥልጣናት ጋር በሃሳቡ ተነጋገረ፡፡ ማንም ግን ትኩረት ሊሰጠው አልወደደም፡፡ ዊንሆልት በዚያ እያለ ታዋቂዋ የኢትዮጵያ ወዳጅ ሲልቭያ ፓንክረስት ለምታሳትመው New Times – Ethiopian News ዋና የጽሑፍ አበርካች ሆኖ ነበር፡፡

 በተለይም በአፕሪል 16 ቀን 1938 እንግሊዝና ጣልያን ‹የአንግሎ ጣልያን› ስምምነትን ሲፈራረሙ ዊንሆልት በጣም አዘነ፡፡ ለንደንንም ለቅቆ ወደ የመን ተመለሰ፡፡ ከየመንም አገሩ አውስትራልያ ገባ፡፡ በየሄደበት ሁሉ ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ መናገርና መቀስቀስም ዋና ተግባሩ ሆነ፡፡ የኢትዮጵያ ጉዳይም የመተዳደርያ ሥራውን እስከ ማስረሳት አደረሰው፡፡

በዚህ መካከል እንግሊዝና ጀርመን እየተቃቃሩና ወደ ጦርነት እያመሩ ሄዱ፡፡ የአውስትራልያው ጠቅላይ ሚኒስትር ሮበርት ሜንዝየስም በጀርመን ላይ ጦርነት ዐወጀ፡፡ ዊንሆልት ይህንን እንደ መልካም አጋጣሚ ወሰደው፡፡ ፊቱንም ወደ አፍሪካ ለመመለስ እንዲችል አበቃው፡፡ ሴፕቴምበር 27 ቀን በ1935 እኤአ በ62 ዓመቱ ከአውስትራልያ ለቅቆ ወደ ሲንጋፖር፣ ከዚያም ወደ ኤደን አመራ፡፡ በዚያም አንድ አፓርትመንት ተከራይቶ ዐረብኛና አማርኛ የሚችል ተርጓሚ ቀጠረ፡፡ ለሲልቭያ ፓንክረስት የሚልከውን ጽሑፍ ሳያቋርጥ ያገኛቸውን አካላት ሁሉ የኢትዮጵያ አርበኞችን ስለመርዳትና በእነርሱም አማካኝነት ጣልያንን ድል ስለማድረግ ያማክር ነበር፡፡

ይህ ጥረቱ ውጤት በማምጣቱ የተነሣም በሜይ 1940 ሃሳቡን ተግባራዊ ለማደረግ የሚያስችል ደብዳቤ ከእንግሊዝ ወታደራዊ ባለ ሥልጣናት ደረሰው፡፡ ዊንሆልትም እየፈነደቀ በ62 ዓመት እድሜው እንደገና ወደ ውትድርና ተመለሰ፡፡ በጁን 17 ቀን 1940 እኤአ ከየመን ወደ ሱዳን ካርቱም በረረ፡፡

ምንም እንኳን ለንደን ለሚገኙት ለቀዳማዊ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ የተገለጠ ነገር ባይኖርም እንግሊዞች ግን እያሠጋቸው የመጣውን የጣልያኖችን ኃይል ከምሥራቅ አፍሪካ ለማስወጣት ምሥጢራዊ ዕቅድ በማዘጋጀት ላይ ነበሩ፡፡ ለዚህ ደግሞ የኢትዮጵያን አርበኞች በማገዝ ጣልያኖችን ሰላም መንሣትና በመጨረሻም እንዲወጡ ማደረግ በብዙዎቹ ባለሞያዎቻቸው የታመነበት ዕቅድ ሆነ፡፡ ይህ ዕቅድ ዊንሆልት በተደጋጋሚ ሲወተውተው የነበረ ዕቅድ ነበረ፡፡ እንግሊዞች ይህንን ዕቅድ የተሳካ ለማድረግ በሕንድና በመካከለኛው ምሥራቅ ያገለገለውን በተለይም ደግሞ በምድረ ፍልስጤም እሥራኤልን በመርዳት የተሳከለት ሥራ የሠራውን፣ ከአንደኛው የዓለም ጦርነት ማብቃት በኋላም ወደ ኢትዮጵያ ክርስቲን ከምትባለው ባለቤቱ ጋር መጥቶ ከአዲስ አበባ በስተ ሰሜን ኑሮ የጀመረውን ዳን ሳንፎርድን ነበር የመረጡት፡፡ ሳንፎርድ ስለ ኢትዮጵያ ማወቅ ብቻ ሳይሆን ለሀገሪቱ ይቆረቆር የነበረ፤ ከብዙዎቹ የዘመኑ መሳፍንትና መኳንንት ጋርም መልካም ግንኙነት የነበረው፤ በንጉሠ ነገሥቱ ዘንድም መታወቅንና መከበርን ያተረፈ ሰው ነበር፡፡

ሳንፎርድና(ግራ) ዐፄ ኃይለ ሥላሴ በደምበጫ ግንባር(ጎጃም)
ዳን ሳንፎርድ አዲስ አበባን ለቅቆ ወደ እንግሊዝ የተመለሰው ጣልያኖች ኢትዮጵያን ሲወርሩ ነበር፡፡ አሁን ከጡረታ ተጠርቶ የዚህ የኢትዮጵያ ተልዕኮ መሐንዲስ እንዲሆን ተደረገ፡፡ መጀመሪያ ወደ ካይሮ ከዚያም ወደ ካርቱም በመምጣት ከሌሎች የውትድርና ባለሞያዎች ጋር ዕቅዱን ነደፈ፡፡ ዊንሆልት ካርቱም የደረሰው በዚህ ጊዜ ነበር፡፡ ዳን ሳንፎርድ በጎጃም በኩል ወደ ኢትዮጵያ በመግባት ከአርበኞች ጋር ሆኖ ጣልያንን ለመውጋት ሲያስብ በደቡብ አፍሪካው የደፈጣ ውጊያ ጊዜ አንድ እጁ ጉዳት የደረሰበት ዊንሆልት እዚያው ሆኖ እርሱም ከአርበኞች ጋር ተቀላቅሎ የደፈጣ ውጊያ ለመቀጠል እየተሟሟቀ ነበር፡፡

ሳን ፎርድ በገለባት በኩል ወደ ኢትዮጵያ ለመዝለቅ የነበረው ዕቅድ ጣልያኖች ገለባትን በመያዛቸው ምክንያት ከመተማ 19 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደ ምትገኘው ሌሞና ተዛወረ፡፡ ጣልያኖችና ባንዳዎች ከቋራ እስከ መተማ ያለውን ቦታ መሽገውበት ነበር፡፡ ከእንግሊዝ የምሥራቅ አፍሪካ እዝ የመጨረሻውን መመሪያ ሲጠባበቅ የነበረው ኮሎኔል ሳንፎርድ በኦገስት 6 ቀን ዶቃ ከሚገኘው ካምፕ 54 በቅሎ፣ 36 አህዮች፣ ስድስት ገመድ አልባ መገናኛዎች፣ 13303 ጠመንጃዎች፣ 3 ሪቮልቨሮች፣ 30 አሮጌ ጠመንጃዎች፣ ከአራት የእንግሊዝ ወታደሮች፣ ከአንድ ሐኪምና ከአንድ የራዲዮ ሠራተኛ ጋር ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ተነቃነቀ፡፡ ሳንፎርድ ዊንሆልትን በዶቃ ካምፕ ትቶት ነበር የመጣው፡፡

በአንድ በኩል ይህ የተደረገው እነ ሳን ፎርድ መንገዱን ከጠረጉ በኋላ ዊንሆልት እንዲከተላቸው በማሰብ ነው የሚሉ አሉ፡፡ ያን ጊዜ ዊንሆልት ገና የመጓጓዣ አጋሰሶችን አላዘጋጀም ነበርና፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የዊንሆልት በዶቃ ካምፕ መገኘት ከሌላኛው መኮንን ከሮኒ ክሊችሌይ ጋር አለመጣጣም አስከትሎ ነበር፡፡ የመረጃ ሰው የሆነው ክሊችሌይ ዊንሆልት አርጅቷል ብሎ አስቧል፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ለመዝለቅ ያለውን ጉጉትና ከሲልቭያ ፓንክረስት ጋር ስለሠራው ሥራ ደጋግሞ ማውራቱን አልወደደውም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ እርሱ ራሱ በዚያ ጊዜ ጥቂት በእድሜ ገፍቶ የነበረው ሳን ፎርድ ዊንሆልትን ‹አርጅቷል› ብሎ በማሰብ በተልዕኮው ውስጥ ማካተት አልፈለገም ነበር፡፡ በዚህ ላይ ደግሞ ዊንሆልት አንድ እጁ በሚገባ አይሠራም፡፡

ዊንሆልት ግን ሁሉንም ትቶ 11 አህዮችን፣ ስድስት የታጠቁ የኢትዮጵያ ወታደሮችንና አንድ ሱዳናዊ  ምግብ አብሳይ አዘጋጀ፡፡ በ1940 እኤአ፣ ኦገስት 31 ቀን ሳን ፎርድ የሄደበትን መንገድ በመተው ዊንሆት ከመተማ በስተደቡብ ወደ ቋራ አቅጣጫ የሱዳንን ድንበር ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ጀመረ፡፡ በመንገድ ላይ የተወሰኑትን ኢትዮጵያውያን ወታደሮችና ሱዳናዊውን አብሳይ ቀነሳቸው፡፡ ሁለት አገልጋዮችንና ሦስት አህዮችን ብቻ በመያዝ ጠመንጃውን እንደ አገሬው ሰዎች በትከሻው ወደ ታች አጋድሞ ጉዞ ቀጠለ፡፡ ከመነሣቱ በፊት ሊሄድ ያሰበበት መንገድ ለጣልያን ያደሩ ባንዳዎች የሚገኙበት አደገኛ መንገድ መሆኑን ተነግሮት ነበር፡፡ እርሱ ግን አልተቀበለውም፡፡ እንዲያውም መጣቢያ በምትባል ጣቢያ 50 የጣልያን ወታደሮችና 300 የአካባቢው ተወላጅ ባንዶች ካምፕ መሥርተው አካባቢውን እየቃኙ ነበር፡፡
ጉዞ ወደ ኢትዮጵያ
ዊንሆልት ኦገስት 31 ከሌሎቹ የእንግሊዝ መኮንኖች ተለያይቶ በቋራ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ ከዘለቀ በኋላ ድምፁ ጠፋ፡፡ ሳንፎርድም ዊንሆልት ወደ እርሱ ዘንድ አለመድረሱን ገለጠ፡፡ በገለባትና በካርቱም የሚገኙ የእንግሊዝ ሚሲዮኖች ዊንሆልት የት እንደገባ ለማወቅ አልቻሉም፡፡ የዊንሆልት ዜና ከተሰማ 15 ቀናት አለፉ፡፡ ሴፕቴምበር 15 ቀን 1940 ከዊንሆልት ጋር አብረው ሄደው የነበሩ ሁለት ሰዎች  በዶቃ ካምፕ ተገኙ፡፡ በካምፑ የነበሩት ቴሲገርና ላውሬ የተባሉ ሁለት የእንግሊዝ መኮንኖች የዊንሆልትን ዜና ጠየቋቸው፡፡ ኢሳ አቡ ጂያር እንደተናገረው ከሆነ ይመራቸው የነበረው ሰው የጉሙዝን አካባቢ እያቋረጡ እያሉ ጠፋባቸው፡፡ በዚህም ምክያት በመጣቢያ አካባቢ ካምፕ ሠርተው ተቀመጡ፡፡ በዚህ መካከልም አንድ ቀን በድንገት ከአራቱም አቅጣጫ ተኩስ ተከፈተባቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ዊንሆልት ጠመንጃውን ለአስተርጓሚው አሸክሞት ነበር፡፡

ሁለቱ አገልጋዮቹ ተኩሱን ሲሰሙ እየሮጡ በየአቅጣጫው ጠፉ፡፡ መሣሪያ ያልያዘው ዊንሆልት ብቻውን ቀረ፡፡ ከዚህ በኋላ ያለውን ኢሳ አቡ ጂያር የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ እርሱ አምልጦ ወደ ዶቃ ገብቷል፡፡ ሁለቱ የእንግሊዝ መኮንኖች ይህንን ሪፖርት ሲያስተላልፉ ሌላ ዘገባ ከገለባት መጣላቸው፡፡ ‹‹ሌፍትናንት ዊንሆልት በብዙ ችግር ወደ ሰራቆ ደርሷል፡፡ ፊታውራሪ ወርቁ ስንቄም አስፈላጊውን ነገር ረድተውት ወደ ጎጃም አምርቷል›› ይላል፡፡ ነገር ግን ዊንሆልት ወደ ጎጃም ዘልቆ ሊታይ አልቻለም፡፡ በኋላ እንደተረጋገጠውም የገለባቱ ዘገባ ትክክል አልነበረም፡፡

ከወራት በኋላ እንግሊዞች በአካባቢው ባደረጉት አሰሳ ዊንሆልት ይጠቀምበት የነበረውን  ሄልሜት፣ የተበጫጨቁ ልብሶቹንና ይዞት የነበረውን ቦርሳ(ኪት) አገኙት፡፡ አሳሽ ጓዱም ዊንሆልት መጀመሪያ ተመትቶ ወደ ጫካ በመግባት በዚያው ሳይሞት እንዳልቀረ ገመተ፡፡

ጦርነቱ ከተጠናቀቀ በኋላ የዊንሆልት ባለቤት በካርቱም ያለውን የእንግሊዝን ሚሲዮን የባሏን መጨረሻ እንዲያሳውቃት ጠይቃ ነበር፡፡ በጁላይ 8 ቀን 1941 እኤአ ከጋላባት የተነሡ እንግሊዝ ወታደራዊ አሳሾች ዊንሆልት የሄደበትን መንገድ ተከትለው እነዚያ ሁለት አብረውት የተጓዙ ሰዎች ካምፕ ሠራንበት ወዳሉት ቦታ ተንቀሳቅሰው ነበር፡፡ በአካባቢው የተገኙ መረጃዎች እንደጠቆሙት ጣልያኖች የዊንሆልትን መምጣት በማወቃቸው በመንገዱ ተከትለውታል፡፡ በመጨረሻም ካምፑን በመውረር ተኩስ ሲከፍቱባቸው ዊንሆልትና አብረውት የነበሩት ሰዎች ካምፑን ጥለው ጠፉ፡፡ ጣልያኖችና ባንዶችም ወደ ካምፑ ገቡ፡፡

ከዓይን እማኞችና በጊዜው ከነበሩ የአካባቢው ሰዎች ያገኘውን መረጃ ይዞ አሳሹ ጓድ ከመጣብያ የአራት ወይም የአምስት ሰዓት መንገድ ወደሚርቀውና ከሺንፋ ወንዝ አጠገብ ወደነበረው የዊንሆልት ካምፕ ቦታ ደረሰ፡፡ በአካባቢው በተደረገው ምርመራ የአህዮች አጥንት፣ የተተኮሱ ጥይቶች ቀለሃዎችና የጫማ ቅሬቶች ተለቀሙ፡፡ በአቅራቢያውም የጥርስ መፋቂያና ቦት ጫማ ተገኘ፡፡ ካምፑ ነበረበት ከተባለው 300 ያርድ ርቀት ላይም በመበስበስ ላይ የነበሩ የሰው አጥንቶች ታዩ፡፡ ምናልባትም የቆሰለው ዊንሆልት እዚህ ድረስ ተጉዞ ይሆናል ለሞት እጁን የሰጠው፡፡

ካርቱም የሚገኘው የዊንሆልት የመታሰቢያ ሐውልት 
ይህ ሪፖርት ሲድኒ ሲደርስ የኩዊንስ ላንድ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ኦክቶበር 10 ቀን 1941 እኤአ የዊንሆልትን መሞት በይፋ ዐወጀ፡፡ ቋረኛው የአውስትራልያ ሰውም የኢትዮጵያን ነጻነት ሳያይ ቋራ ላይ ቀረ፡፡ አንደኛው ቋረኛ(ዐፄ ቴዎድሮስ) ለእንግሊዝ እጄን አልሰጥም ብሎ በጀግንነት ሞተ፡፡ ሌላኛው ቋረኛም ኢትዮጵያን ነጻ አወጣለሁ ብሎ በሀገሬው ባንዶች ተገደለ፡፡ ኢትዮጵያ የምትባለው ሀገር እንዲህ ነጭ ከጥቁር ዋጋ ከፍሎባታል፡፡ ኢትዮጵያ እንግሊዞች፣ ኩባዎች፣ አውስትራልያዎች፣ ዐረቦች፣ አይሁድ፣ ሱዳኖች፣ ሩሲያዎች፣ አሜሪካኖች፣ ግሪኮችና ሌሎች ዋጋ ከፍለው ሀገር ያደረጓት ሀገር ናት፡፡ እንኳን የተወለዱባትን ያወቋትን ሰዎች ሕይወት የምታስገብር ሀገር፡፡

 ከፐርዝ ወደ ሜልበርን፣ ኳንታስ አውሮፕላን ላይ