የሰሃራን ምድረ በዳ አቋርጠው በጀልባ አውሮፓ ለመግባት የሚጥሩ አያሌ ወጣቶችና ጎልማሶች በየጊዜው ስለሚያጋጥሟቸው አያሌ ሕልውና ተፈታታኝ ተግዳሮቶች ያልተነገረበት ጊዜ የለም። ቀደም ባሉት ጊዜያት ከሰሜን ምዕራብ አፍሪቃ በጀልባዎች ወደ ካናሪ ደሴቶች

ተከሳሾች ለፍርድ ቤቱ በሰጡት ቃል አሸባሪዎች እንዳልሆኑ፤ እስር ቤት ዉስጥ እንደተደበደቡ፤ እንደተሰቃዩና ያልተናገሩትንና ያላሉትን እንዳሉ ተደርጎ እንዲፈርሙ መርማሪዎች እንዳስፈራሯቸው ገልፀዋል

ችሎቱ በተከሳሽ በእነ አቶ አቡበከር አህመድ መዝገብ በአሸባሪነት ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች ቃልም ማድመጥ ጀምሯል ። ዛሬ የአንዱን ተከሳሽ ቃል ያደመጠው ችሎቱ የተቀሩትን 18 ተከሳሾች የተከሳሽነት ቃል ለማዳመጥ ለነገ ቀጠሮ ሰጥቷል ።

በጎርጎሮሳውያኑ 2013 ጀርመን ተገን እንድትሰጣቸው የጠየቁ ስደተኞች ቁጥር በኢንዱስትሪ በበለፀጉ ሌሎች ሃገራት ካመለከቱት ቁጥር ጋር ሲነፃጸር ከፍተኛ ነው ። ሆኖም አብዛኛዎቹ ጀርመን እንድትቀበላቸው የጠየቁ አመልካቾች የመኖሪያ ፈቃድ የማግኘት እድላቸው አነስተኛ መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ባለሞያዎች ይናገራሉ ።

በኬንያ መዲና፣ ናይሮቢ በተጣሉ ሦስት የቦምብ ጥቃቶች ቢያንስ ስድስት ሰዎች መገደላቸውን እና 25 መቁሰላቸውን የኬንያ ሀገር አስተዳደር ባለሥልጣናት አስታወቁ። ትናንት ማታ የተጣሉት ጥቃቶች ዒላማ ያደረጉት በብዛት

አቶ አስራት ዛሬ በጠበቃቸው በኩል ለልዩ ችሎቱ ባቀረቡት ይግባኝ በአንድ የግል መፅሄት ላይ ፍርድ ቤቱን በመድፈርና በመተቸት ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የተጣለባቸው የ2 ዓመት ገደብ እንዲነሳላቸው ጠይቀው ነበር ።

የአፍሪቃ መሪዎች ስምምነቱን ላለመቀበል የሚያቅማሙበት ብዙ ምክንያት አላቸዉ።ቀድሞ የሚጠቀሰዉ ግን ማርቲን እንደሚሉት አዉሮፖች ለአፍሪቃ ምርቶች ቀረጥ ሳይጠይቁ ገበያቸዉን ክፍት ካደረጉ፤ አፍሪቃዎችም በምላሹ ለአዉሮጳ ሸቀጦች ቀረጥ ሳያስከፍሉ ገበያቸዉን ክፍት እንዲያደርጉ መጠየቃቸዉ ነዉ።

አዋጁን-።«ለማስከበር እና ቦኩ ሐራምን ለማጥፋት» ተብሎ የዘመተዉ ጦር ሕዝቡን መዉጪያ መግቢያ አሳጣዉ።የጠረጠረዉን በመደዳ-ያስር፤ያሰረዉን ይገርፍ፤ ያሰቃይ፤ እስራት-ስቃዩን ለማምለጥ የሞከረዉን እያሳደደ-ይገድለዉ ያዘ።አምንስቲ ኢንተርናሽናል እንደሚለዉ ይሕ የሁለቱ ሐይላት እርምጃ ከጦር ወንጀል የሚቆጠር ነዉ።

ያኔ-ከ21ዱ የወታደራዊ ሁንታዉ አባላት ሁሉ ወጣት ነበሩ።ያን ሚስጥር-በመናገራቸዉ የካይሮ ሠልፈኞችን በቁጣ፤ የመብት በተለይም የሴቶች መብት ተሟጋቾችን በዉግዘት ከማንጫጫቱ ባለፍ፤ ድምፀ ለሥላሳዉ ወጣት ጄኔራል የሚፈልጉትን ለማደረግ-የፖለቲካዉን ትኩሳት የለኩበት መግለጫ መሆኑን ያሰበ-ያስተዋል አልነበረም።

በርካታ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የርቀት ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በ2005 ዓም ትምህርታቸውን ቢጨርሱም፣ ጊዚያዊ ዲግሪያቸውን ፣ ማለትም የዲግሪያቸውን ቅጂ ባለማግኘታቸው በስራ ፍለጋ ጥረታቸው ላይ እክል እንደደቀነባቸው በምሬት ገልጸዋል።

የጀርመን የልማት ትብብር ሚንስትር ጌርድ ሚውለር ሰሞኑን ደቡብ ሱዳንን እና ማሊን ጎብኝተውዋል። ሚንስትሩ ወደ ሁለቱ ሀገራት የተጓዙት በቦታው በመገኘት በዚያ ስላለው የመሠረተ ልማት ግንባታ፣

የደቡብ ሱዳን ጦርነት አዲሲቱን ሐገር እያነደደ ደሐ ሕዝቧን እየፈጀ-በገፍ እያሰደደ ነዉ።ተፋላሚ ሐይላት በምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን ( ኢጋድ ) ሸምጋይነት የተኩስ አቁም ሥምምነት ቢፈራረሙም ሥምምነቱ ገቢራዊ አልሆነም።

በፕሬዚደንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት የሚመራው የመንግሥቱ ጦር እና የቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት ሪየክ ማቸርን በሚደግፉት ታጣቂ ኃይላት መካከል በሚካሄደው ውጊያ ሰበብ ሀገሪቱ ለምትገኝበት ውዝግብ መፍትሔ ለማፈላለግ የተጀመረው ጥረት ችግር እንደገጠመው ይገኛል።

ድርጅቱ እንደሚለው በዚሁ ዓመት በዓለማችን በአጠቃላይ 778 ሰዎች በሞት ተቀጥተዋል ። በድርጅቱ መግለጫ መሠረት በይፋ ከተፈፀሙ ከእነዚህ ቅጣቶች በተጨማሪ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በቻይና በድብቅ በሞት ተቀጥተዋል ።

የወጣቶቹ አላማ ጧሪ የሌላቸውን፣ ከጎዳና ላይ የተነሱ አረጋውያንንና የአዕምሮ ህሙማንን መርዳት ነው። ለዚህ ደግሞ 65 በጎ ፍቃደኞች አዲስ አበባ የሚገኘው «ሜቄዶንያ የአረጋውያን እና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከልን ተቀላቅለዋል።ሶስቱን አነጋግረናቸዋል።

ትልቁ የአፍሪቃ ቀንድ ቤተ መፃህፍት እስከመባል በደረሰው በዚህ ተቋም ጥናትና ምርምሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የማድረግ እቅድ መኖሩን ሃላፊው ዶክተር አህመድ ሃሰን ለዶቼቬለ ተናግረዋል ።

ባለፈዉ ሰምወን በኢትዮጵያንና በአካባቢዋ የሚገኙ ሃገራትን የእሥልምና ሥነ-ፅሁፍ ይዘትንና ታሪካዊ ፋይዳዉን የሚቃኝ አንድ ዓለም አቀፍ ጥናታዊ ጉባኤ አዲስ አበባ ዉስጥ መካሔዱ ይታወሳል። በዚህ ጉባኤ የእሥልምና ሥነ-ፅሁፍ በምሥራቅ አፍሪቃ ዉስጥ በሚነገሩ በተለያዩ ቋንቋዎች ለረጅም ጊዜ የተለያዩ አገልግሎቶች ሲስጥ እንደነበር፤

በርስ በርስ ጦርነት በተመሰቃቀለችዉ ደቡብ ሱዳን ዉስጥ በሚሊዮኖች የሚገመቱ ዜጎች ለምግብ እጥረት መጋለጣቸዉ ተገለጸ። የተመድ የዝናቡ ወቅት እየቀረበ በመጣበት በዚህ ወቅት ለእርሻ መዘጋጀት በማይታሰበብት ሁኔታ የገጠመዉ የምግብ እጥረት የከፋ ቀዉስ እንዳያስከትል አስጠንቅቋል።

የግብፅ የጦር ኃይል አዛዥ አበደል ፈታህ አል ሲሲ የወታደራዊ የደንብ ልብሳቸዉን በይፋ የሚቀይሩበት ጊዜ ተቃርቧል። ትናንት ነዉ የጦር አዛዡ ከመከላከያ ሚኒስትርነታቸዉ በይፋ በመልቀቅ ለፕሬዝደንትነት ለመወዳደር መወሰናቸዉን ያስታወቁት።

ለፍጥረተ ዓለም(ዩኒቨርስ)መከሠት ፤ መገኘት ፤ መዘርጋት– መንስዔ ነው ተብሎ የሚጠቀሰው «ታላቁ ፍንዳታ» (BIG BANG) ከ 14 ቢሊዮን ዓመት ገደማ በፊት ማጋጠሙን የሚጠቁም መረጃ በምርምር አግኝተናል ሲል አንድ የጠፈር ሳይንቲስቶች በድን ከወዲያኛው ሳምንት መግለጹ የሚታወስ ነው።

በዓለም ላይ ቁጥራቸው ከአንድ ቢሊዮን የሚበልጥ አካል ጉዳተኞች አሉ ። አብዛኛዎቹም በማደግ ላይ ባሉ ሃገራት ውስጥ ነው የሚኖሩት ። በተለይ በአፍሪቃ አካል ጉዳተኞች ብዙውን ጊዜ አድልዎና መገለል የሚደርስባቸው ሲሆን ብዙዎቹም ስር በሰደደ ድህነት ውስጥ ነው ያሉት ።

የአሸባሪዎች ጥቃት፣ የሐይማኖት ግጭት እና ሙስና ባልተለያት ናይጄሪያ በኢኮኖሚ ከፍተኛ እድገት በማስመዝገብ ላይ እንደሆነች ነው የሚነገረው። ይህ እዕን ከሆነ ደግሞ በነዳጅ ዘይት ሀብታም የሆነችው ናይጄሪያ በቅርቡ በኢኮኖሚ እድገቷ ከአፍሪቃ አንደኛ ከሆነችው ደቡብ አፍሪቃ መቅደሟ አይቀሬ ነው።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ በአዉሮጳ የሚያደርጉትን ጉብኝት ቀጥሎ ዛሬ ብራስል ቤልጅግ ይገኛሉ። በብራስልስ ከአዉሮጳ ኅብረት መሪዎች ጋ ካደረጉት ዉይይት በኋላም ከሰዓት በኋላ በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ምድብ ችሎት በዛሬው ውሎው የሙሥሊም መሪዎችን የክስ ሂደት ተመለከተ። ችሎቱ በነአቶ አቡበከር አህመድ መዝገብ ዓቃቤ ሕግ በአሸባሪነት ክስ የመሠረተባቸውን ተከሳሾች ጉዳይ ከተመለከተ በኋላ

የታዋቂው የጀርመን የእግርኳስ ክለብ ባየር ሚውኒክ ፕሬዝዳንት ኡሊኽነስ የገቢ ግብር በማጭበርበር ወንጀልከ 12ቀናት በፊት 3 ዓመት ተኩል የእስር ቅጣት ተበይኖባቸዋል ። ባለፀጋ ኽነስ ብይኑን ይግባኝ ሳይሉ ወህኒ እንደሚወርዱ አስታውቀዋል። የዛሬው አውሮፓና ጀርመን ዝግጅታችን በኽነስ ላይ የተላለፈው ብይንና አስተምህሮቱ ላይ ያተኩራል ።

የቡድን ሰባት ሀገራት መሪዎች ትናንት በዘ ሄግ፣ ኔዘርላንድ ስለዩክሬይን ውዝግብ ለመምከር በጠሩት ልዩ ስብሰባ ላይ፣ ሩስያ የዩክሬይን ግዛት የነበረችውን ክሪሚያን የግዛቷ አካል አድርጋ በመቀበሏ ፣ ሞስኮ

የዓይን ማዝ በሽታን በቀላሉ መከላከል ሲቻል ዛሬም ለብዙዎ የዐይን ብርሃን ማጣት ምክንያት እየሆነ ነዉ። የድህነት በሽታ በመባል የሚገለፀዉ ይህ የዐይን ህመም በዓለም 21 ሚሊዮን ሰዎችን እንደጎዳ የዓለም የጤና ድርጅት መረጃዎች ያመለክታሉ። ኢትዮጵያ ዉስጥም ይህ የዓይን ሕመም በተለያዩ ክልሎች ተንሰራፍቶ እንደሚገኝ እየተገለጸ ነዉ።

በትናንትናዉ ዕለት የግብፅ ፍርድ ቤት በ529 የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር አባላት ላይ የሞት ቅጣት በይኗል። ዉሳኔዉ በተሰጠበት በዚሁ ችሎት 147ቱ ብቻ ናቸዉ በስፍራዉ ተገኝተዉ ፍርዱን ያደመጡ ሲሆን ቀሪዎቹ ከሚጠብቃቸዉ ፍርድ ለማምለጥ በሽሽት ላይ መሆናቸዉ ተገልጿል።

ደቡብ ሱዳን ከግብፅ ጋ የሁለትዮሽ ወታደራዊ ትብብር ስምምነት መፈራረሟን ዘገባዎች ያመለክታሉ። ጁባ ተመሳሳይ መግባባት ላይ ከሁለት ዓመታት በፊት ከተነጠለቻት ሰሜን ሱዳን ጋም መድረሷ ተገልጿል።

የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ዖባማ፤ ዛሬ ኔድርላንድ እንደገቡ በሰጡት መግለጫ ፣ አውሮፓውያንን ዩናይትድ ስቴትስ ሩሲያ በክሪሚያ በወሰደችው እርምጃ ሳቢያ ዋጋ የሚያስከፍላትን የማዕቀብ ርምጃ በመተባበር ወስደናል አሉ። ሰፊ የጦር ኃይል አንቀሳቅሶ

በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ፣ ባለፈው ቅዳሜ ከቀትር በኋላ በደረሰው የአሳት ቃጠሎ፣ በዋናው ህንጻና ማሺኖች ላይ የደረሰ ጉዳት ባለመኖሩ፤ የማተሚያ ቤቱ መደበኛ ሥራ አለመተጓጎሉን ማተሚያ ድርጅቱ ገለጠ። በቃጠሎው የወደሙት በጓሮ በኩል የነበሩ ትርፈ

የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ፍርንክ ባልተር ሽታይንማየር በአፍሪቃ የሦስት ቀናት ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ አዲስ አበባ ገቡ። ጀርመናዊው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ከኢትዮጵያ ፕሬዚደንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ እና

በሮም አደባባይ ኢትዮጵያውያኑ ጀግኖች አትሌቶች ትናንት ድርብ ድል ተጎናፅፈዋል። በወንዶችም፣ በሴቶችም ማንም ከፊታቸው ደፍሮ መቆም አልቻለም። በእንግሊዝ ፕሬሚየር ሊግ መድፈኞቹን ሰማያዊ ለባሾቹ በገዛ መድፋቸው አፈር ድሜ አብልተዋል። ማን ዩናይትድን ያሳፈረው ባቡር ግን እየተንገታገተ ነው። ሊቨርፑል እና ቸልሲ ተናንቀዋል።

ኢትዮጵያ የጀመረችውን የዕድገትና የለውጥ እቅድ ለማሳካት አስፈላጊ ከሆኑት ጉዳዮች መካከል የኤሌክትሪክ አቅርቦት ትልቁን ሚና ይዞዋል። በኢትዮጵያ የኤሌክትሪኩን አገልግሎት ዘርፍ የማስፋፋቱ ስራ ከተጀመረች ብዙ ዓመታት ቢሆነውም ፣ ውጤቱ እስካሁን የሚፈለገው ደረጃ ላይ ገና አልደረሰም።

ከተመሰረተ ከ70 ዓመታት በላይ ዕድሜ እንዳስቆጠረየሚነገርለት በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኘው የብርሃንና ሠላም ማተሚያ ቤት ዛሬ ቃጠሎ እንደደረሰበት ወኪላችን ከአዲስ አበባ ዘገበ።