ሰሞኑን ለዓለም አቀፍ ሰብሰባ ወደ አገራችን የገቡ ግብረ ሰዶማውያን በገንዘባቸው ኃይል በሀገራችን የረከሰና የተወገዘውን በተለይም የቤተሰብ ጠንቅ የሆነውን ወንድ ለወንድ የሚደረግ ሩካቤ ሥጋን ዜጎች አጥብቀው እንዲያወግዙ የኃይማኖት አባቶች ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ እነዚሁ ስማቸው እንዳይገለፅ የፈለጉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ የሆኑ አባቶች በእምነቱ አስተምህሮትና ደንብ መሠረት ፈጣሪ የተናገረው ትንቢት በዚህ ዘመን እየተፈፀመና እየተደረገ ለመሆኑ ለኃይማኖቱ ተከታዮች […]

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ቅዳሜ ሕዳር 30 እና እሁድ ታህሳስ 1 ቀን 2004 ዓ.ም 2ኛውን መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ እንደሚያካሂድ አስታወቀ፡ ፡ በጠቅላላ ጉባዔውም አባላት፤አንድነት ፓርቲ ከብርሃን ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ጋር ያደረጉትን ውህደት እና ከመድረክ አባላት ፓርቲዎች ጋር የተፈጠረውን ግንባር እንደሚያፀድቁት ይጠበቃል፡፡ በተጨማሪም ለሚቀጥሉት ዓመታት የብሔራዊ ም/ቤት አባል በመሆን የሚያገለግሉ አባላትን እንደሚያስመርጥ ተጠቁሟል፡፡ ይህ በእንዲህ […]

“በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሠላማዊ ትግል ለማፈን የተሠራ ድሪቶ ነው” አንዱዓለም አራጌ “የሚነገረው ድርሰት ነው ሠላማዊ ትግል ወንጀል ካልሆነ በስተቀር ወንጀል አልፈፅምኩም” ናትናኤል መኮንን “የፃፉትን ተረታ ተረቶች አልፈፀምኩም” ክንፈሚካኤል ደበበ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/ም/ሊቀመንበርና ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አንዱዓለም አራጌ፣ የአንድነት ማዕከላዊ ም/ቤት አባል ናትናኤል መኮንን፣ ዮሐንስ ተረፈ፣ የሸዋስ ይሁንዓለም /ሻምበል/፣ ክንፈ ሚካኤል ደበበ፣ ምትኩ […]

ምክር ቤቱ እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር ዛሬ ሰኞ ዲሴምብር 5 ቀን 2011 ዓ.ም፣ ባደረገዉ ስብሰባ የኤርትራ መንግስት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለሽብር ፈጣሪዎች በተለይም በሶማሊያ ለሚገኘዉ የአልሻባብ አሸባሪ ቡድን የሚሰጠዉን ድጋፍ፣ በአስቸኳይ እንዲያቆም ያስጠነቀቀ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያና ከጅቡቲ ጋር ኤርትራ ያላትን የድንበር ግጭትም በሰላም እንድትፈታ ጥሪ አቅርቧል። ምክር ቤቱ ባወጣዉ ሕግ 2023 ፣ የኤርትራ መንግስት ከጅቡቲ ጋር ከአራት […]

በዚህ ሳምንት እንደተለመደው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅት አፍዝዝ አደንግዝ የሆነውን ዘጋቢ ፊልም አቀርቧል፡፡ ርዕሱንም አኬልዳማ ብለውታል፡፡ “አኬልዳማ” የሚለው ርዕስን የተጠቀሙት የርዕሰ ጉዳዩን አሳሳቢነት ለማስመር በመፈለግ ይመስላል፡፡ የዚህ ፊልም ጭብጥ ዋነኛ ማጠንጠኛ በዚህ ወቅት ለእስር የተዳረጉትን ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪና አባላት የሆኑ ግለሰቦች በሽብር ሾል ተሳታፊ መሆናቸውን ለማረጋገጥ አስረጅ መረጃ ይዘው ለመቅረብ ቢሆንም ፊልሙ ከብዙ አተያይ […]

ፖለቲካ የሚለዉ ቃል እንደ ጸያፍና አስፈሪ ቃል ነዉ በብዙ ኢትዮጵያዉያን ዘንድ የሚታየዉ። እንደዉም በተለምዶ ፖለቲካ ከኮረንቲ ጋር ይመሳሰላል። ነገር ግን፣ ይመስለናል እንጂ፣ ከፖለቲካ ነጻ የሆነ ሰዉ የለም። በአዎንታዊነት ሆነ በአሉታዊነት «ፖለቲካ አያገባንም» የሚሉ ዜጎችን ጨምሮ ፣ ምን ያህል የፖለቲካ ዉሳኔዎች፣ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ላይ እያደረሱ ያለዉን ተጽእኖ በስፋት ለማብራራት በርካታ ምሳሌዎችን መዘርዘር ይቻላል። ለጊዜዉ ግን አራት […]

በሽብር ተግባር ተሰማርታችኋል በሚል የፈጠራ ክስ የተከሰሱ፣ በአገር ቤት ሰላማዊ በሆነ መንገድ የኢትዮጵያ ሕዝብ መብቱና ነጻነቱ እንዲረጋገጥለት በመታገል የሚታወቁት የአንድነት ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ አንዱዋለም አራጌ፣ እዉቁ ጋዜጠኛ አቶ እስክንድር ነጋ ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያዉያን የቀረበባቸዉን ክስ እንዲከላከሉ ፍርድ ቤቱ የወሰነ ሲሆን ፣ የቀረበባቸዉ ክስ መሰረት የሌለዉ እንደሆነ በመግለጽ ጥፋተኛ እንዳልሆኑ አረጋግጠዋል። በተለይም አቶ አንዳዋለም አርጌ […]

እኔ ደሞ አገር ያለ መንግስት የሚቆም አይመስለኝም ነበር አለኝ አንዱ ሾለ ቤልጂየም የማእከላዊ መንግስት መዘጋት ስናወጋ:፡ የቤልጂየም ፖለቲከኞች ማእከላዊውን መንግስት ከ ጁን 2010 ጀምሮ በመቀመጫ ንትርክ ጥርቅም አርገው ዘግተውታል። አሁን ግን ቅንጅት ለመፍጠር እየሞከሩ ነው መሰል። ቤልጂየም ደች ፈረንሳይኛ ና ጀርመንኛ ኦፊሺያል ቁዋንቁዋ ሲሆኑ በተፈጥሮዋ ብዙህ ናት። ታዲያ የበልጂየም ፖሊቲከኞች ማእከላዊውን መንግስት ቢዘጉትም ቤልጂየሞች ወይ […]

የአትዮጵያ ሕዝብ ላለፉት አራት አስርት አመታት በላይ ከፍተኛ መስዋትነት የሚጠይቅ ትግል ቢያደርግም ዴሞክራሳዊ ስርዓት መፍጠር አልተቻለም፡፡ ደርግን የተካው ኢህአዴግ ትምህርት ወስዶ የተሻለ ስርዓት ይገነባል ተብሎ ቢጠበቅም፣ እሱም የለየለት አምባገነንና አፋኝ ስርዓት ለመሆን በቃ፡፡ ጭቆና እንዲወገድ፣ እኩልነት እንዲረጋገጥና እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲመሠረት በሚድረግ ጥረት ሁሉም የኢትዮጵያ ልጆች ለሀገራቸው ልማትና ብልፅግና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ ከመስራት ይልቅ ጥላቻና […]

የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢ.ቲ.ቪ.) ለሳምንት ያህል አንድ ማስታወቂያ እየደጋገመ ማሰማት ጀመረ። ‘አኬልዳማ’ የተባለ ልዩ የፊልም ዝግጅት። በአኬልዳማ ማስታወቂያ ፊልሙን ከ13 አመት በታች ያሉ ህጻናት እንዳይመለከቱት ጥብቅ ማስጠንቀቅያም አለለበት። ማስታወቂያውን ከዚህ በፊት ከነበሩት ለየት የሚያደርገው ይህ የማስፈራርያ ማስተንቀቅያው ነው። በማስታወቂያው ውስጥ የአርቲስት ደበበ እሸቱ ምስልም ይታያል። በዚህ ‘ልዩ’ ዝግጅት አርቲስት ደበበ እሸቱ የሚተውንበት ከሆነ ከቀድሞዎቹ የፈጠራ ስራዎች […]

በመርህ ደረጃ የምናውቀውና በትምህርት ቤት የተማርነው ሰዎች ከታሪክ ይማራሉ በዚህም ስህተቶች እየታረሙ ይሄዳሉ፣ አይደገሙም የሚል ነው፡፡ ነገር ግን የሕይወት እንቆቅልሽና በተግባር ስናየው ታሪክ፣ የሚያስተምረን፣ ሰዎች ከታሪክ የማይማሩ መሆናቸውን መሆኑ የሚያስገርም ነው፡፡ ይበልጥ አስገራሚው ደግሞ ሰዎች እንኳን ከአለፈ ከታሪክና በፊት ለፊት ከሚያዩት፣ ከሚሰሙትና ከሚያውቁት እውነታም እንደማይማሩ ነው፡፡ በተለይም አምባገነኖች፤ ጥቂቱንና የቅርቡን ለመጥቀስ፤ የግብፁ ሙባረክ ከቱኒዚያው በንዓሊ […]

ይህ የመጨረሻው ክፍል ነው። የመጨረሻውን ክፍል ከማቅረቤ በፊት የጽሁፌን አሃድ በምስጋና ልጀምር። ሁልጊዜ በህሊናዬ የነበረውን… ነገር ግን ለመጻፍ ጊዜ አጥቼ በነበረበት ወቅት ብርታት ለሆነኝ የእውነት እና የፍቅር አምላክ ምስጋና ይጋባው። ምንም እንኳን ባላነበውም ስለጽሁፉ በሰማሁ ጊዜ… ይህንን ታሪክ ለመጻፍ ምክንያት የሆነኝን የኢትዮ ሚዲያ ባለቤት አብርሃ በላይን በንፁህ ልቤ አመሰግነዋለሁ። ይህንን ጽሁፍ በነጻ ህሊና በድረ ገጾቻችሁና […]

የአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ባለ አክስዮን ድርሻና የጋዜጣው ማኔጂንግ ኢዲተር ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ከሀገር መሰደዱን የመረጃ ምንጮቻችን ገለጹ፡፡ እንደ መረጃ ምንጮቻችን ገለጻ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ሊሰደድ የቻለው “ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ገጥሞት እንደሆነ” ይገልጻሉ፡፡ ምንጮቻችን እንደሚሉት “ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ምርጫ 97 ተከትሎ ከታሠሩት ጋዜጠኞች መካከል አንዱ ነበር፡፡ እድሜልክ ተፈርዶበት በይቅርታ ተፈቶ ነበር፡፡ በጋዜጣ በሚጽፋቸው ጽሑፎች ይቅርታው […]

“ፍትህና ዲሞክራሲ በሌለበት አገር አልኖርም” በሚል ምክንያት ራሱን በእሳት አቃጥሎ በገደለው ጀግናዉ መምህር የኔሰው ገብሬ ላይ የመለስ መንግሰት የከፈተዉ የስም ማጥፋት ዘመቻ የህዝብ ቀልብ አልሳበም። ክህደት፤ ዉሸትና ንቀት የአምባገነኑ መንግስት ተብዬዉ መለያ ጠባይ መሆኑ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ የተሰወረ አይደለም። ከዚህ አሳፋሪና አስነዋሪ ባህሪይ ጋር ከጠ/ሚር መለሾ ጀምሮ እገሌ ከእገሌ ሳይል ሁለት አስርተ አመታትን ያስቆጠረ፤ እጅግ […]

ከሁሉም በፊት በወያኔው ኢሰብኣዊ አገዛዝ ተንገሽግሾ ሰውነቱ ላይ ቤንዚን በማርከፍከፍ ይህችን የደም ምድር ኢትዮጵያ በገዛ ፈቃዱ የተሰናበተውን ወንድማችንና ልጃችንን መምህር የኔሰው ገብሬን የከፈለውን መስዋዕት ፈጣሪ እንደአቤል መስዋዕት ቆጥሮ መንግሥተ ሰማይን ያውርስልን ማለት እፈልጋለሁ፡፡ ካህናት እንዳይታዘቡኝ አንድ ሁለት ቃላትን ልናገር፡፡ ‹የኔሰው ራሱን አጠፋ› ብዬ ለማመን ይከብደኛል፤ አልችልምም፡፡ እርግጥ ነው ራሱን አጥፍቷል፡፡ ግን ለምን? ይህ ወጣት አስተሳሰቡን […]

አንተ ያገሬ ልጅ እስኪ ልጠይቅህ የነጻነት ትርጉም እንደምን አስተዋልህ በመለሰ ዘመን ለጥብሥ ያበቃህ እኔ በሚገባኝ የሱስ ብቻ ነበር ባልሰራበት ሐጢት ራሱን የሰዋ ያውም ለዓመጹበት እጅጉን ይገርማል አንተም መሰዋትህ በኢትዮጵያዊነት ሞትማ ይመጣል ሁሉን አስተካካይ አንተ ያገሬ ልጅ እስኪ ልጠይቅህ የነጻነት ትርጉም እንደምን አስተዋልህ በመለሰ ዘመን ለጥብሥ ያበቃህ ዋጋ ከፍሎዋል አሉ ብዙ ኢትዮጵያዊ ለፍትህ ለነጻነት ያንተ ረቀቀ […]

ስብሰባው ከመደረጉ አስቀድሞ ሕዝብ እንዲያውቀው አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን አንድ መልእክት አስተላልፈው ነበር። ቅዳሜ ኖቨምበር 12 ቀን 2011 በኢንተር ኮንትኔንታል (Intercontinental Hotel) ሆቴል የኦሕዴድ አባል የሆኑት የኢሕአዴግ አምባሳደር አቶ ግርማ ብሩ ስብሰባ አድርገው ነበር። ስብሰባው የእራት ምሽት በሚል የተጠራ ሲሆን። አንድም ተቃዋሚ ተብሎ የተጠረጠረን ሰው ላለማስገባት፤ በግል ደብዳቤ የተጠራ በመሆኑ፤ የዚህ አንባገነን መንግስት ተቃዋሚወች በግርማ ብሩ […]

አልጠብቅም ሞትን ተኝቼ ባልጋዬ ፤ እኔው እሄዳልለሁ ፈረሴን ቼ ! ብዬ ፤ በ’ንባ አልታጠብም ቁጭ ብዬ አላለቅስም ፤ ጉልበቴን አጥፌ አልንበረከክም ፤ አልጠብቅም እሱን ወደኔ እስቲመጣ ፤ እኔው እሄዳለሁ ወደሱ እንዳይመጣ ፤ ኩራቴን ይረዳው ድፍረቴን ይወቀው ፤ ተጋድሜ አልሞትም ቆሜነው እምሞተው !! አልፈልግም ዋሻ የምደበቅበት ፤ አያሻኝም ጢሻ የምሸሸግበት ፤ አልሰብርም አንገቴን አላዞርም ፊቴን ፤ […]

በሽብር ተግባር ተሰማርታችኋል በሚል ክስ ከነ አቶ አንዱዋለም ጋር ታስረዉ የነበሩ አቶ ዘመነ ሞላ እና አቶ አሳምነዉ ብረሃኑ ፣ ትላንት ማክሰኞ ኖቬምበር 15 ቀን የተፈቱ ሲሆን፣ አቶ ደበበ እሸቱና አቶ ሾለሺ ሃጎስ ደግሞ፣ ዓርብ ኖቬምበር 11 ቀን እንደተፈቱ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዜና ያለመክታል። እነዚህ ወገኖች በምን ምክንያት እንደተፈቱ ለጊዜዉ የታወቀ ነገር ባይኖርም፣ ገዢዉ ፓርቲ በሽብር […]

ይህን ጥያቄ፤ ለአንድ ጤነኛ ሰው ቢያቀርቡለት፤”እንደዚህ የሚሉት(ያሉት)፤ለትግሬዎች ጥላቻ ያላቸው ናቸው”ሊል እንደሚችል ግልፅ ነው።ይህ አያከራክረንም።አከራካሪ የሚሆነው፤እነዛ፤ ለትግሬዎች ጥላቻ ያላቸው፤ እነማን ናቸው?” የሚለው ተከታይ ጥያቄ ነው። ግን.. ይህን ያለው ማን ይመስላችሁዋል? ቅንጅት? የቅንጅት ደጋፊዎች?ህብረት? የግል ጋዜጦች? ወይስ ሌሎች ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች? “ትግሬን ወደ መቀሌ፤ንብረቱን ወደ ቀበሌ” ብሎ በአደባባይ ያወጀው፤ ህወሀት ቢሆንስ ምን ይሰማችሁዋል?ምንስ ትላላችሁ? በእርግጥ ህወሀት፤በገዛ አባሎቹ […]

ነዋሪው የስብሰባውን አዳራሽ ጥሎ ለመውጣት የተነሳሳው፤በአዲሱ የመሬት ሊዝ አዋጅና በመሬት ይዞታ ማረጋገጫ፣የክፍያ ስርዓትና ባለይዞታዎች በካሬ ሜትር እንዲከፍሉ በተተመነው ገንዘብ ጉዳይ ላይ ለመወያየት ጥያቄ አቅርበው ከመድረክ መላሽ በመነፈጉ ምክንያት ነው፡፡ ዕሁድ ሕዳር 3 ቀን 2004 ዓ.ም በየካ ክ/ ከተማ የቀድሞ ወረዳ 12 ነዋሪ፤ከፈረንሳይ ኤምባሲ ዝቅ ብሎ የሚገኘው ፈረንሳይ መናፈሻ የስብሰባ አዳራሽ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ከ30 ጀምሮ […]

የዳዉሮ ዋካ ህዝብ ቀን 2011-11-15 የኔሰው ገብሬ ይባላል። ዕድሜው ወደ 29 አመት ነው።ሥራው መምህር ነበር።የተወለደው በጂማ ከተማ ዉስጥ ሲሆን የአንደኛም ሆነ የ2ኛ ደረጃ ትምህርቱን የተከታተለው እዚያው ጂማ ከተማ ነበር። ከዚያም ወደ ዋካ ከተማ በመምጣት ታላቅ እህቱ ዘንድ ኑሮዉን አደረገ። ከዚያም ወደ መምህራን ኮሌጅ በመግባት በመምህርነት ሰልጥኖ በዳዉሮ ዞን ዉስጥ በተለያዩ ወረዳዎች ዉስጥ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች […]