የውጭ ሀገር ሠዎች ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ከሚደነቁባቸውና ከሚደነግጡባቸው ጉዳዮች አንዱ ኢትዮጵያዊያን ጥሬ ስጋን ጐመድ ጐመድ እያደረጉ (እየመተሩ) ሲመገቡ ማየት ነው። ጥሬ ሥጋ መብላት በኢትዮጵያ በብዙ ማኅበረሰቦች ውስጥ በስፋት የሚዘወተር ነው።

በብዙ ሀገሮች ደግሞ ጥሬ ሥጋን መመገብ እምብዛም ስለማይታወቅ የባህር ማዶ ሰዎች ጥሬ ሥጋ የሚበላ ሰው ሲያዩ ይደነግጣሉ፣ ይፈራሉ፣ እንዲሁም ሊቀፋቸውም…

በ   [ሰንደቅ]

አስረኛው ዙር የኮንደሚኒየም ዕጣ ከወጣ ሳምንታት ተቆጠሩ። ቀደም ባሉት ጊዜያት በኮንደሚኒየም ቤቶች ላይ ዕጣ ከወጣ በኋላ ቤቶቹን ለባለእድለኞች በማስተላለፉ በኩል እሰከ ሁለት ዓመት…

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ሚያዝያ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፍሪደም ሀውስ  ይህን ያለው-በዩናይትድ ስቴትስ  ምክትል የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ  ወንዲ ሸርማን ስለ ኢትዮጵያ ምርጫ አስመልክተው ለተናገሩት ንግግር በሰጠው ምላሽ ነው። ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ሀገር እንደኾነች የጠቀሱት ወንዲ ሸርማን  ሀገሪቱ በመጪው ግንቦት  የምታደርገው ምርጫ  ነጻ፣ፍተሀዊና ተዓማኒ እንደሚሆን  በእርግጠኝነት  ተናግረዋል። “ወንዲ ሸርማን የተናገሩት ነገር መሉ በሙሉ በመረጃ …

ሚያዝያ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኮሚሽኑ ሊቀመንበር ዶክተርን ኮሳዛና ድላሚኒ  የተፈጸመው ጥቃት በፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን በመጥቀስ፤ በጥቃቱ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች ሀዘናቸውን ገልጸዋል። “ምንም ዓይነት ችግር ቢጋረጥብንም፣ ሟቾቹ የሀገሬው ሰው ይሁኑ አልያም የውጪ ሀገር ዜጋ፤ በህዝብ ላይ የሚፈጸምን ጥቃት በምንም ዓይነት ምክንያት ማስተባበል አይቻልም” ብለዋል- ሊቀመንበሯ። የደቡብ አፍሪካ መንግስትና  የኩዋ ዙሉ  አካባቢ …

ሚያዝያ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፓርቲው ፦«ከራሳችን ውጪ ለችግራችን ደራሽ መንግስት የለንም!»በሚል ርእስ በየመንና በደቡብ አፍሪካ በሚገኚ ኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጥቃት አስመልክቶ ባወጣው ወቅታዊ መግለጫ ፣የኢትዮጵያውያን የውርደት ዘመን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ሰሞኑን ከተከሰተው እጅግ አስከፊ ሁኔታ ላይ አድርሶናል ብሏል። “የመን ውስጥ በተከሰተው ጦርነት ተጎጂ የሆኑትን የውጭ ዜጎች መንግስታቶቻቸው ቀድመው ሲያስወጡ …

ሚያዝያ ፱(ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከዛሬ ሚያዝያ 9/2007 ዓ.ም ጀምሮ ለሁለት ቀን በሚከበረው ‹‹የመምህራን ቀን›› የኢህአዴግ አባል የሆኑ መምህራን ብቻ መሸለማቸውን ነገረ ኢትዮጵያ በዝግጅቱላይ የነበሩ መምህራንን ዋቢ  አድርጎ ዘገበ፡፡ በተማሪዎች ዘንድ ብቃት የላቸውም ተብለው ቅሬታ የሚነሳባቸው መምህራን የገዥው ፓርቲ አባል በመሆናቸው ብቻ ‹‹ምርጥ መምህራን›› ተብለው እንደተሸለሙ የገለጹት መምህራኑ ‹‹ከመቶው 90፣ 80…. አግኝተዋል ተብለው ከመሸለማቸውውጭ መስፈርቱም ግልጽነት የጎደለውና ወገንተኛ እንደሆነ በግልጽ ተገንዝበናል›› ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ በታህሳስ ወር 2007 ዓ.ም በፈጠራ ውጤታማ የሆኑትን መምህራን ሸልመው እንደነበር ያስታወሱት መምህራን ‹‹በአገር ደረጃ በጠቅላይ ሚኒስትሩ በፈጠራ ሙያቸው የተሸለሙት መምህራን አሁን በከተማደረጃ ለተደረገው ሽልማት እንደማይበቁ ተደርጎ ከሽልማቱ መገለላቸው መምህራኑን አነጋግሯል›› ብለዋል፡፡ ዛሬ በተከበረው በዓል በአገር አቀፍ ደረጃ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሸለሙት እንዳይካተቱ የተደረገበት ዋነኛ ምክንያት የኢህአዴግ አባል ባለመሆናቸው እንደሆነ፣ በሌላ በኩል የኢህአዴግ አባል የሆኑትና በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም የተሸለሙትአሁንም መሸለማቸው የድርጅቱ አባል ያልሆኑትን መምህራን ሆን ተብሎ ለማግለል ያለመ ነው ብለዋል፡

የኢኮኖሚ ችግር ሲፈጠር ስደተኛዉን ኢላማ ኣድርጎ ጥቃት መሰንዘር በደቡብ ኣፍሪካ ብቻ የታየ ችግር ኣይደለም። ግሪክ፣ ጀርመን፣ ጣልያን፣ ሩስያ እና በብዙ ኣገሮች የታየ የተለመደ ክስተት ነው። ህንዳውያን በግሪክ ጎዳና ለመንቀሳቀስ ኣዳጋች እየሆነባቸው እንደሆነ ሁሉ ሞስኮም ኣሁን የውጭ ዜጋ እንደልቡ እማይንቀሳቀስባት ከተማ ሁናለች፤ ለምን ቢባል የኢኮኖሚ ችግር።በነዚህ ኣገሮች ከፈተኛ የፀረ ስደተኛ ጥቃትም እሚፈፀምባቸው ኣገሮች እየሆኑ ነው:: ይሄ ነገር ከዘር እና ከጥቁረት እያገናኙ ደቡብ ኣፍሪካውያንን የቀኝ ገዢዎች ንድፈ ሃሳቦች እየተጠቀሙ “ድሮስ ጥቁር….ለነፃነት ኣቅም ያልደረስ እንስሳ” ምናምን እያሉ የትምክህት ቃል መሰንዘር የጉዳዩን ትክክለኛ ገፅታ ኣለመረዳትን ነው እሚያሳየው። የኢኮኖሚ ችግር ወደ ፖለቲካዊና የፀጥታ ችግር እንደሚቀየር ሳይታለም የተፈታ ሃቅ ነው። በሩዋንዳም በሌሎች ኣገራትም የታየው ይህ ነው። እንዲህ ኣይነት ሁኔታ ለሰነፍ ፖለቲከኞች ጥሩ ኣጋጣሚ ይፍጥራል፤ የሰነፍ ፖለቲካ ደግሞ ቀላል ግን ኣውዳሚ ስለሆነ ዉጤቱ ኣሁን ደቡብ ኣፍሪካ ላይ እያየን ያለነው ኣይነት እልቂት ያስከትላል።ኣንዱን በማስወገድ “መፍትሄ” ለመሻት መጣር ነው የሰነፍ ፖለቲካ ማለት።ለዚህ መዋቅራዊ መደላድል እሚፈጥረው ግን የኢኮኖሚ ችግር ነው። ሁቱዎች ቱትሲዎች ላይ ገጀራቸውን ከማሳረፋቸው በፊት የዋጋ ንረት እና ስራ ኣጥነት ሂወታቸው ላይ ገጀራዉን ኣሳርፎ ነበር። ይህ ቀቢፀ ተስፋነት ሰለፍ ፖለቲከኞች ተመቻቸው እና ዘርን ለማጥፋት ተጠቀሙበት። ደቡብ ኣፍሪካ ላይ እየተፈፀመ ያለ ነገርም ከጄኔቲክ ሳይሆን ከኢኮኖምያዊ ሁኔታ መመሰቃቀል እሚመነጭ ነገር ነው። የደቡብ ኣፍሪካ ለየት እሚያደርገው የኣፓርታይድ ስርኣት በፖለቲካው ረገድ “ሲገረሰስ” የኢኮኖሚው ሁናቴ በነጮች እንደተያዘ እንዲቀጥል መፈቀዱ ነው። ማንዴላ ከዚ ዉጪ ኣማራጭ […]

* ይድረስ ለክቡር ዶር ቴዎድሮስ አድሃኖም … * ኢህአዴግን እንዴት እንምረጥ ? ትናንት በሁከት ፣ ዛሬ በመፈራረስ በሚመስል አደገኛ የለውጥ ሂደት ውስጥ ባለችው የመን የኢትዮጵያውያን የድረሱልኝ ድምጽ ከነኡኡታው ሰላም ይነሳል ። በደቡብ አፍሪካ በኢትዮጵያውያን ስደተኛ ወገኖቻችን ላይ ከኢራቅና ሶርያ አይ ኤስ አይ ኤስ ISIS ጽንፈኞች ባላነሰ ከፍ ሲል በሰብአዊው ዜጋ ፣ ዝቅ ሲል ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ሚያዝያ ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ አፍሪካ የውጪ ሀገር  ዜጎች ላይ የተፈጸመው ጥቃት  ያስቆጣቸው በርካታ ደቡብ አፍሪካውያን  ደርጊቱን  ለማውገዝ  በደርባን  ታላቅ ሰልፍ  ማድረጋቸውን የአገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ደቡብ አፍሪካውያን እና የውጭ አገር ዜጎች በሰልፉ ላይ  ተገኝተዋል። “የውጪ ሀገር ዜጎችን ማጥቃትና ማሳድድ ይቁም!” የሚል መፈክር ያነገቡት የደርባን ነዋሪዎች፤ በጥቃት ፈጻሚዎቹ ላይ …

ባለፈው እሑድ፣ የትንሣኤ ዕለት ማልዳ ነው ከዕንቅልፏ የተነሣቺው፡፡ እናቷ ቤተ ክርስቲያን አድራ፣ አባቷ ደግሞ ሌሊት ከውጭ ሀገር ገብቶ ደክሟቸው እንደተኙ አልተነሡም፡፡ እርሷም በጠዋት የተነሣቺው ጓደኛዋ አደራ ስላለቻት ነው፡፡ ‹‹የቴሌቭዥን የትንሣኤ ፕሮግራም የተቀረጸው እኛ ቤት ነው›› ብላ አጓጉታታለቺ፡፡ የተነሣቺው ጓደኛዋን በቴሌቭዥን ለማየት ስትል ነው፡፡ ደግሞ ‹ዘፈን ምናምን አቅርቤያለሁ› ብላታለቺ፡፡ የጓደኛዋ አባት ‹ፍቅር እዚህም እዚያም›፣ ‹ትሄጅብኛለሽ› እና ‹ፍቅር በኪችን ውስጥ› የተሰኙ ሦስት አስቂኝ የፍቅር ፊልሞች ላይ የሠራ ‹ታዋቂ አርቲስት› ነው፡፡ ጓደኛዋ እንደነገረቻት ከሆነ የበዓሉ ፕሮግራም እነርሱ ቤት ሲቀረጽ የቀረ አርቲስት የለም፡፡ በዓሉ ራሱ ሕዝቡን ሊያዝናና ስለማይችል ‹ዘና እንዲያደርጉት› ተብሎ ቀልደኞቹ ሁሉ እነርሱ ቤት መጥተው ነበር፡፡ 

ከቀረፃው ማግሥት ጓደኛዋ ትምህርት ቤት ስትመጣ የታዋቂ አርቲስቶችን ፊርማ በየደብተሯ ሰብስባ መጥታ ጓደኞቿን ሁሉ ስታስቀናቸው ነበር፡፡ በርግጥ ክፍል ውስጥ እርሷና ጓደኞቿ ትምህርታቸውን ረስተው የአርቲስቶችን ፊርማ ሲያደንቁ ያዩዋቸው መምህራቸው እንደ መገሰጽ ቢያደርጉም፣ እንደመስማት ያላቸው ተማሪ ግን አልነበረም፡፡ ምክንያቱም እርሳቸው ታዋቂ አይደሉማ፡፡ ደግሞ መምህር ከመቼ ወዲህ ነው ታዋቂ የሚሆነው፡፡ ይኼው ስንቱ አርብቶ አደርና አርሶ አደር ሲሸለም መምህር መቼ ተሸልሞ ያውቃል፡፡ በተለይ ደግሞ ብዙዎችን ተማሪዎች ያናደዳቸው ‹‹የዘፈነም፣ የተወነም፣ ፊልም የሠራም፣ ማስታወቂያ የሠራም አርቲስት አይባልም›› ያሉት ነገር ነው፡፡ ‹‹አርቲስት የሚለው ስም ለሰዓሊዎች የሚሰጥ ስም ነው፡፡  ያውም ስካልፕቸርና ፔይንቲንግ ለሚሠሩት ብቻ፡፡ እርሱም ቢሆን እንደ ደጃዝማችና ግራ አዝማች ማዕረግ ሳይሆን የሞያ መጠሪያ ነው፡፡ እስኪ አሁን አርቲስት ማይክል ጃክሰን፣ አርቲስት ቢዮንሴ ሲባል ሰምታችሁ ታውቃላችሁ? ሰው ማዕረግ የሚያበዛው ስሙ ብቻውን ለመቆም ዐቅም ስለሚያጣ ነው፡፡ እስኪ ተመልከቱ፡፡ ዳቪንቼ፣ ሼክስፒር፣ ሞዛርት፣ ፒካሶ የሚለው ስምኮ ብቻውን የሚቆም ነው፡፡ ዕዝል ቅጽል አያስፈልገውም፡፡›› ያሉትን ነገር ተማሪዎቻቸው ‹‹እርሳቸው ከቴሌቭዥን ሊበልጡ ነው እንዴ›› ብለው ሙድ ያዙባቸው፡፡
ለነገሩ እርሳቸውም አብዝተውታል፡፡ ‹አርሶ አደርና አርብቶ አደር፣ ሠልጣኝና የትራፊክ ፖሊስ፣ ታራሚና ፍርደኛ፣ ጋዜጠኛና ጎዳና ተዳዳሪ ማዕረግ ሆነው ከስም በፊት በሚቀጸሉባት ሀገር ‹አርቲስት› ማዕረግ አይደለም ብለው ተማሪን ማሸበር በአሸባሪነት የሚያስከስስ እንዳይሆን ያሰጋል፡፡ እንዲያውም ኢቲቪ ቢሰማቸው ‹በአሸባሪነት ሊያስከስስ ይገባል ሲሉ አንዳንድ የሕግ ምሁራን አስገነዘቡ› ብሎ ለዜና ጥብስ ያውላቸው ነበር፡፡
እርሷ ሶፋ ወንበር ላይ ተቀምጣ ይኼንን ሁሉ ስታስብ ጓደኛዋ በቴሌ ቭዥን ዘገየች፡፡ እስኪጀመር ድረስ ያቺ የ12 ዓመት የሰባተኛ ክፍል ተማሪ ማሰቧን ቀጠለች፡፡ ‹‹ቆይ ግን አባዬ ምንድን ነው? አንድም ቀንኮ በቴሌቭዥን ታይቶ አያውቅም፡፡ ይኼው ኤልዳና እንኳን ስንት ጊዜ በቲቪ ልትታዪ ነው፡፡ አባዬ ግን ዶክተር ምናምን ከሚሆን አርቲስት ቢሆን ነበር ጥሩ፡፡ እርሱ ዶክተር ሆኖ ምንም አልጠቀመንም፡፡ አንዴ አሜሪካ አንዴ ጃፓን፣ አንዴ ጀርመን ለወርክ ሾፕ መሮጥ ብቻ ነው፡፡ በርግጥ የኤልዳናም አባት ውጭ ይኼዳል፡፡ ግን እርሱ ሲሄድም ሲመጣም በሚዲያ ይነገርለታል፡፡ ሊሄድ ነው፣ እየሄደ ነው፣ ሊደርስ ነው፣ ደረሰ ይባልለታል፡፡ የኔን አባት መሄድና መምጣት ግን እኛና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ ነን የምናውቀው፡፡
ደግሞ የኤልዳና አባት ውጭ ሲሄድ ሰው ይከበዋል፣ ጉርድ ቀሚስ ያደረጉ ሴቶች፣ ቁጥርጥር የተሠሩ ወንዶች፣ አጅበውት ፎቶ ይነሣሉ፡፡ የኔ አባት ግን ፎቶዎቹን ሁሉ ሳይ ወይ ከራሰ በራ ሰው ጋር ወይ ድክምክም ካሉ ሴቶች ጋር ነው የሚነሣው፡፡ ደግሞኮ የኤልዳና አባት ሁልጊዜ የአበባ ጉንጉን ሲቀበል ነው የሚታየው፡፡ የኔ አባት ግን ሯጭ ይመስል ሜዳልያ ሲቀበል ነው የምናየው፡፡ ኤልዳና ቪዲዮውን በስልኳ ስታሳየን ሰው ሁሉ ኡኡ እያለ አዳራሽ ውስጥ ለአባቷ ይጨፍርለታል፡፡ የኔ አባት ግን አንድ ጠረጴዛ ነገር አጠገብ ይቆማል፤ የሆነ ነገር በፓወር ፖይንት ያሳያል፤ አንድ ጊዜ ይጨበጨብለታል፡፡ በቃ፡፡ አንድም የሚጨፍር ሰው አይታይም፡፡ አባዬ ግን ምንድን ነው?
ቆይ ግን እኛ ቤት ኢቲቪዎች የማይመጡት ለምንድን ነው? አባቴ አርቲስት ስላልሆነ ነው አይደል፡፡ የኔ አባትኮ እንኳን ለፋሲካ ለአርሂቡ ቀርቦ አያውቅም፡፡ እውነታቸው ነው፡፡ በአርሂቡኮ አርቲስቶች ሲቀርቡ ‹እንትናዬ አድናቂህ ነኝ፣ እወድሃለሁ፤ ቀጣዩ አልበምህ መቼ ነው የሚወጣው? ምን ፊልም ልትሠራልን ነው?›› የሚል ሰው ይደውልላቸዋል፡፡ አሁን አባዬ አርሂቡ ላይ ቢቀርብ ምን ሊባል ነው? ምን ተብሎ ሊጠየቅ ነው? ደግሞ ማንም አድናቂ አያገኝም፡፡ አልበም የለው፤ ፊልም የለው፣ ሰዎች በምን ያውቁታል፡፡
አባዬ ግን አርቲስት መሆን ነበረበት፡፡ ዶክተርነት ምን ያደርግለታል፡፡ አርቲስት ቢሆን ኖሮ በኋላ ሲያረጅ ‹የክብር ዶክትሬት› ተብሎ ይሰጠው ነበር፡፡ ‹የክብር አርቲስት› ብሎ ግን ማንም አሁን አይሰጠውም፡፡ ዶክተርነት ይደረስበታል፡፡ አርቲስትነት ግን አይደረስበትም፡፡ እንዲያውም እነርሱ ሲጠሩ ‹ክቡር ዶክተር› ነው የሚባሉት የኔ አባት ግን ‹ዶክተር› ብቻ ነው፡፡
እርሷ ይህንን ስታወጣና ስታወርድ የቴሌቭዥኑ ፕሮግራም ጀመረ፡፡ ጋዜጠኛውም ‹እያዝናናን እናስተምራለን› ብሎ የጓደኛዋን ቤት አሳየ፡፡ ምንም እንኳን የተቀረጸው በጾም ጊዜ ቢሆን ዶሮው፣ በጉ፣ ክትፎው፣ ቅቤው፣ ዕንቁላሉ ይታያል፡፡ ለነገሩ እንደ ኢቲቪ አቆጣጠር ጾሙ አንድ ሳምንት ሲቀረው ያልቃል፡፡ ከዚያ በኋላ ቀረጻ ይቻላል፡፡ ጓደኛዋን አየቻት፡፡ ቤታቸው እየታየ ነው፡፡
እየሮጠች አባቷን ቀሰቀሰቺው፡፡
‹‹ጓደኛዬ በቴሌቭዥን እየታየች ነው›› ስትለው ድካሙ ባይለቀውም እርሷን ለማስደሰት ተነሥቶ ዓይኑን እያሸ ወደ ሳሎን መጣ፡፡ ‹እያት ኤልዳናን› አለቺው፡፡ ኤልዳና እየተጠየቀቺ ነው፡፡ ቃለ መጠይቁ ሲያልቅ ‹አባዬ አንተ መቼ ነው በቲቪ የምትቀርበው› አለቺው ልጁ፡፡
‹‹ሚዲያችን ከታዋቂ ይልቅ ለዐዋቂ ቦታ ሲኖረው›› አላት አባቷ፡፡
‹‹አንተ ግን ለምን ታዋቂ አልሆንክም››
‹‹ልጄ እኔኮ ታዋቂ ነኝ፡፡ የኢቲቪ ጋዜጠኞች ግን አያውቁኝም፡፡ የቢቢሲ፣ የሲኤንኤን፣ የአልጀዚራ ጋዜጠኞች ያውቁኛል፡፡ እኔ አንድ ነገር ስለ ግብርና ከተናገርኩ ወይም ከጻፍኩ ያ ዜና ይሆናል፡፡ እዚህ አገር ግን ዕውቀት ዜና አይሆንም ልጄ፡፡ እዚህ ሀገር ዜና የሚሆነው ፖለቲካና ቀልድ ነው፡፡››
‹‹እሺ ለምን አርሂቡ ላይ አትቀርብም››
‹‹ያማ ጋዜጠኛውን ማሰቃየት ነው ልጄ››
‹‹ለምን ይሰቃያል?››
‹‹ምን ይጠይቀኛል? ጥናታዊ ጽሑፎቼን ማንበብ ሊኖርበት ነው፡፡ ምርምሮቼን መቃኘት ሊኖርበት ነው፡፡ ስለ እኔ የተሰጡ የሌሎች ሳይንቲስቶችን ምስክርነት ማገላበጥ ሊኖርበት ነው፡፡ ይሰቃያል ልጄ፡፡ ቀልድ የለመደን ሰው ዕውቀት ያሰቃየዋል፡፡በቀለላሉ የመጀመሪያ አልበምህ መቼ አወጣኸው? የመጀመሪያው ፊልምህ ምን ነበር? ገጠመኝህ ምንድን ነው? እያለ ሰዓቱን መሙላት ሲችል ምን በወጣው ሳይንቲስ አቅርቦ ይሰቃያል፡፡ ጋዜጠኞቹ መዘጋጀት ስለማይችሉም ስለማይፈልጉም አይደል እንዴ ‹እስኪ ራስሽን ለአድማጮች አስተዋውቂ› የሚሉሽ፡፡ ይኼኮ የጋዜጠኛው ሥራ ነበር፡፡ አንብቦ፣ ፕሮፋይል ሠርቶ ቢመጣ ኖሮ እንዲህ አይልም፡፡ ደግሞም አለቆቹም ላይወዱለት ይችላሉ፡፡ ዕውቀት የመለወጥ ኃይል አለው፡፡ ሕዝቡ ደግሞ እንዲዝናና እንጂ እንዲለወጥ አይፈለግም፡፡››
‹‹ተዪው እኔን፡፡ አንድ ገበሬ በዓል እንዴት ነው የሚያከብረው? ድንበር ላይ ባሉ ወታደሮች ዘንድ እንዴት ይከበራል? ተረኛ ሆነው ሆስፒታል ወይም እሳት አደጋ መከላከያ ውስጥ ባሉ ባለሞያዎች ዘንድ ፋሲካ ምን ዓይነት በዓል ነው? በዕለቱ አየር ላይ በሚሆኑ የአውሮፕላን አብራሪዎችና አስተናጋጆች፣ መርከብ ላይ በሚሠሩ ኢትዮጵያውያን፣ ሆስፒታል በተኙ ሕሙማን፣ በዓል እንዴት ይከበራል? የሚለውን እንኳን መች ያሳዩናል፡፡ ለምን ይመስልሻል?
‹‹እነርሱ ታድያ አርቲስት ናቸው እንዴ?››
››ልጄ የኑሮ አርቱማ ያለው እዚያ ውስጥ ነበር፡፡ የኛነታችንን ሌላ ገጽታ የምናየውማ እዚያ ውስጥ ነበር፡፡ ግን ይኼ ማሰብ ይጠይቃል፤ መመራመርን፣ ማንበብን፣ መዘጋጀትን ይጠይቃል፡፡ ማሰብ፣ ማንበብና መዘጋጀት ደግሞ እዚያ ቤት የሚወደዱ አይመስሉኝም››
‹‹እሺ ታድያ መቼ ነው የኛ ቤት በቴሌቭዥን የሚቀርበው?››
‹‹ወይ እኔ መቀለድ፣ ወይ እነርሱ ማወቅ ሲጀምሩ››
  

ከ፲ ፱ ፻ ፷ ፮ ዓመተ ምህረቱ የየካቲት ሕዝባዊ መነሳሳት ጀምሮ፤ ለመብት፣ ለነፃነትና በሰላም ሠርቶ ለመኖር ያለው ትግል፤ ሳያርፍ በተከታታይ አሁንም እየተካሄደ ነው። በነዚህ ባለፉት ፵ ዓመታት፤ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን፤ በትግሉ ከሕዝብ ጎን ተሰልፈው ሕይወታቸውን ሠጥተዋል። ቆራጥ የሕዝብ ጠበቃዎች ወጥተዋል፤ ሕይወታቸውን ላመኑበት ዓላማ በቆራጥነት በመሥጠት በጀግንነት ተቆጥረዋል። ትውልድ አልፎ ትውልድ ተተክቷል። በግለሰብ ደረጃ፤ አጥንት የሚሰብሩ፣ […]

ወቅቱ ለክርስቲያኖች የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል ሰሞን እንደመሆኑ በዓሉ የሚመለከታቸውን አንባቢ ወገኖቼን “እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው [በሰላም] አደረሳችሁ” ማለትን እወዳለሁ፡፡ የደርግ ጊዜ አንድ ትዝታ አለኝ፡፡ በአብዛኛው በሀገር ወዳድ ደናቁርት የታጨቀው የደርግ መንግሥት ሠለጠንኩ ብሎ ሃይማኖተቢሱንና ሃይማኖተኝነትን ከልካዩን የሶሻሊዝም ሥርዓት ካወጀባት ጠማማ ዕለት ጀምሮ በዓል በመጣ ቁጥር በተለይም የአብዮቱ በዓል በሚከበርበት ወቅት “እንኳን ደረሳችሁ” ይል ነበር – […]

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

በቅርቡ የሽንጎው ከፍተኛ አመራር አካል የሆነው ምክር ቤት ባካሄደው የሁለት ቀን ስብሰባ ሀገራችን ኢትዮጵያ የምትገኝበትን ሁኔታ በሰፊው መርምሮ ለቀጣዩም ትግል ምን መደረግ እንዳለበት መመሪያ በመሰጠት ተጠናቋል። በተጨማሪም የሽንጎው የተለያዩ የስራ ክፍሎች የስራ አፈጻጸምን በተመለከተ የቀረቡለትን ሪፖርቶች መርምሮ ትግሉ ተጠናክሮ የሚቀጥልበትን ተጨማሪ መመሪያ በመስጠት ተጠናቋል። በተለይም ደግሞ ሽንጎው በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚያካሂደው ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ የተገኙትን መልካም […]

ሚያዝያ ፮(ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የከተማዋ የኢሳት የመረጃ ምንጮች እንደገለጹት ከትናንት ሰኞ ምሽት ጀምሮ እስከ ዛሬ ማክሰኞ እኩለቀን ድረስ ከተማዋ በተኩስ ስትናወጥ ውላለች። አንዳንድ ነዋሪዎች እንደሚሉት የተኩሱ ልውውጡ የተካሄደው በመከላከያ ሰራዊት አባላት እና በሶማሊ ክልል ልዩ ሚሊሺያዎች መካከል ነው፡፡ የመከላከያ ሰራዊት አባላት አንድ የክልል 5 ጠባቂ መግደላቸውን ተከትሎ፣ የክልሉ ልዩ  ሃይል ሚሊሺያዎች …

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ ኣቆጣጠር ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ የ60 ደቂቃ ሥርጭቱ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች ያስተላልፋል።

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ባለፈዉ መጋቢት 28 በተደረገዉ ምርጫ የመላዉ ለዉጥ አራማጆች ኮንግረስ (APC) ዕጩ የቀድሞዉ ጄኔራል መሐመዱ ቡኸሪ አሽንፈዋል።ከቡኻሪ ማሸነፍ እኩል በሥልጣን ላይ ያሉት ፕሬዝዳንት ጉድላክ ጆናታን ሽንፈታቸዉን አምነዉ መቀበላቸዉ በናጄሪያ በብዙ የአፍሪቃ ሐገራትም ብዙ ያልተለመደ ዓይነት ዴሞክራሲያዊ የሥልጣን ሽሽግር ነዉ የሆነዉ።

ናይጄሪያ በ1960 እጎአ ከብሪታንያ ቅኝ አገዛዝ ነፃ ከወጣችበት ጊዜ ጀምሮ እንደ ዲሞክራሲያዉ ይትበሐል በምርጫ መሪዎችዋን ለመሾም የተለያዩ ሙከራዎች ተደርገዉባት ነበር።ይሁንና እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር እስከ 1999 ድረስ የተመረጠ የሲቢል አስተዳደር ተደላድሎ ሥልጣን ይዞባት አያዉቅም።

ብዙ ጊዜ በጦር ጄኔራሎች መፈንቅለ መንግሥት፤ አልፎ፤ አልፎ በርስ በርስ ጦርነትና ግጭት ሥትታበጥ አርባ ዓመት ያሕል ያስቆጠረችዉ ምዕራብ አፍሪቃዊት ሐገር አነሰም በዛ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ማስተናገድ የጀመረችዉ እጎአ በ1999 ነዉ።ከ1999 እስካሁን ድረስ የሚገዛት ግን ሕዝባዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (PDP) የተሰኘዉ ነዉ።

ባለፈዉ መጋቢት 28 በተደረገዉ ምርጫ ግን አራት የፖለቲካ ፓርቲዎችን ያጣመረዉ የመላዉ ለዉጥ አራማጆች ኮንግረስ (APC) ዕጩ የቀድሞዉ ጄኔራል መሐመዱ ቡኸሪ አሽንፈዋል።ከቡኻሪ ማሸነፍ እኩል በሥልጣን ላይ ያሉት ፕሬዝዳንት ጉድላክ ጆናታን ሽንፈታቸዉን አምነዉ መቀበላቸዉ በናጄሪያ በብዙ የአፍሪቃ ሐገራትም ብዙ ያልተለመደ ዓይነት ዴሞክራሲያዊ የሥልጣን ሽሽግር ነዉ የሆነዉ።

እርግጥ ነዉ ከቀዝቃዛዉ ጦርነት ፍፃሜ በሕዋላ ለወትሮዉ በመፈንቅለ መንግሥት፤ በነፍጥ ትግል ወይም በዉርስ መሪዎች ሲፈራረቁባቸዉ የነበሩት ብዙ የአፍሪቃ ሐገራት ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እናስተናግዳለን ማለታቸዉ አልቀረም።ይሁንና በትክክለኛ ምርጫ ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር የተደረገባቸዉ ፤ ደቡብ አፍሪቃ፤ቦትስዋና፤ሞዛምቢክ፤ ጋና፤ ታንዛኒያ እያልን የምንቆጥራቸዉ የአንድ ዕጅ ጣቶችን እንኳ የማይሞሉ ሐገራት ናቸዉ።

ያሁኑ የናጄሪያ ምርጫ ሒደትና ዉጤት ለአፍሪቃዉያን ምን ያስተምራል ነዉ?የሚለዉ ጥያቄ የዉይይታችን አብይ ጭብጥ ነዉ።

‹‹ቅጽ አራት ከተሞላ በኋላ ራስን ማግለል አይቻልም›› ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በወላይታ ዞን በቦሎሶሶሬ 2 የምርጫ ክልል ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ለውድድር ከቀረቡት ዕጩ ተወዳዳሪዎች መካከል፣ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ)ን ወክለው ለውድድር ቀርበው የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኃይሌ ራሳቸውን ከምርጫው ማግለላቸውን ለሪፖርተር አስታወቁ፡፡ ‹‹ከምርጫው ራሴን ለማግለል ስወስን ምንም […]