በደቡብ ሱዳን የዩኒቲ ግዛት የነዳጅ ዘይት የሚያወጣ « ግሬተር ፓየኔር » የተባለ አንድ የቻይና ኩባንያ በዚሁ የነጭ ዓባይ ዳርቻ የሚገኙ ከአምስት መቶ ሺህ የሚበልጥ ሕዝብ ለራሱ ደህንነት ሲል አካባቢውን እንዲልቅ እና ራቅ ወዳለ ቦታ እንዲሄድ የሁለት ወራት ጊዜ ሰጥቶዋል።

በአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት የተዘጋጀው የ5 ሳምንት ስልጠና ዛሬ ተጀመረ፤ ስልጠናው በሰላማዊ ትግል ላይ ጥልቅ ጥናት ባደረጉት በአቶ ግርማ ካሳ ነው፡፡ አቶ ግርማ ሞገስ ኢትዮጵያ ረዥም የነፃነት ታሪክ ቢኖራትም በስልጣኔ ለምን እንዳልገፋች? እስከዛሬ ሰላማዊ ትግል ተደርጓል ወይ? የሚሉ ጭብጦች ላይ አተኩረዋል፡፡ በተለይ የሀገሪቷ ባህል ቀራፂ በነበሩ አካላት ዘመናዊ ስልጣኔ ሲያጥላሉ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ በመቀጠልም ሀገሪቷ የጦርነት […]

የቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ጉዳዩን በጥብቅ ይነጋገርበታል በመንግሥት ባለሥልጣናት ስለሚፈጸሙ በደሎች ከአህጉረ ስብከት የሚቀርቡ አቤቱታዎች የፍትሕ አካሉን አፋጣኝ ውሳኔ ያገኙ ዘንድ ቅ/ሲኖዶሱ ግፊት እንዲያደርግ አጠቃላይ ጉባኤው ዐደራ ጥሎበታል አህጉረ ስብከት ያቀረቧቸውን የአስተዳደር፣ የፍትሕና የጸጥታ አካላት በደሎችና ተጽዕኖዎች አጣርቶ መፍትሔ የሚሰጥ÷ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ ከሃይማኖት ተቋማት ጉባኤና ከፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የተውጣጣ ኮሚቴ እንዲዋቀር አጠቃላይ ጉባኤው በአቋም መግለጫው …


Ethiopia’s constitution is one of the world’s generous constitutions in giving rights. It gives ‘the nations, nationalities and peoples the right to self determination to secession.’ So, it is no wonder that it gives the ultimate right for freedom of expression and the right to privacy. However, the question is that ‘are the rights granted on the constitution applicable in reality?’
It is universally true that rights are always granted with restrictions. These restrictions are applied usually for ‘national security issues’ or even to protect the well being of certain society members and also in cases where the right conflicts with other rights. For example, the right for freedom of expression should not exceed the right to privacy and leave individuals in physical and psychological insecurity. In consideration of this, I have been challenging myself to answer the question ‘is Ethiopia over writing constitutional rights for one of these reasons or just to protect the power of its rulers?’
Article 29 of the constitution in its sub article 2, gives the right to ‘everyone’ to express him/herself without interference. “This right shall include freedom to seek, receive and impart information and ideas of all kinds, regardless of frontiers, either orally, in writing or in print, in the form of art, or through any media of his choice.” On sub article 3/a, it approves the prohibition of any form of censorship; on sub article 3/b, that citizens have the freedom to access information of public interest.
There is also article 26 of the constitution which gives the people the right to privacy. Section 2 of this article reads:
“Everyone has the right to the inviolability of his notes and correspondence including postal letters, and communications made by means of telephone, telecommunications and electronic devices.”
I will forward three major problems to make my point. 

Problem #1:

All Proclamations are NOT constituted in the Constitution
In Ethiopia, the government bothers little to listen to alternative voices of the people before passing bills. Among these bills are there the infamous Anti-Terrorism Proclamation No. 652/2009 and others were passed in the same way without giving the people a chance to reflect on the draft to recommend improvements on how it can protect the country from danger of any kind without violating rights of the people.  
Article 14/1/a of the Anti-Terrorism proclamation reads as:
“[upon getting court warrant, National Intelligence and Security Office may] intercept or conduct surveillance on the telephone, fax, radio, Internet, electronic, postal and similar communications of a person suspected of terrorism”. This grants National Intelligence and Security officials, who are more concerned about protecting power than the people, the ultimate right to violate the right to privacy of citizens especially the dissidents.
Similarly, the Telecom Fraud Offence No. 761/2012 in its article 14 gives Police the right “for covert search” upon court warrant where among others the Police “has reasonable ground that a telecom fraud is likely to be committed.”
We may think this contradiction between the proclamations and the constitution is OK for the sake of the big picture – which is ‘National Security’. But, we know it is not OK when we learn about who the victims are. According to Article 19, Ethiopia’s submission to the Universal Periodic Review, 12 journalists are prosecuted in relation to “terrorism act” since the proclamation was passed in 2009. To mention a few among these convicted journalists:
  1. Eskinder Nega – is blogger who is convicted and is serving 18 years of imprisonment in Kality;
  2. Abiy Tekelemariam and Mesfin Negash – are editors of  addisnegeronline.com and are sentenced 8 years of imprisonment in absentia;
  3. Abebe Belew – is a journalist on an internet based radio called Addis Dimts. He is convicted of “terrorism” and sentenced in absentia;
These are not the only ones who were convicted on their activities on the cyber; there are also other journalists on whom digital information were presented as “evidences of crime” against them. Reeyot Alemu, a young woman journalist and a university lecturer who is convicted of “supporting terrorism” is now serving her imprisonment in Kality. She was accused for reporting to ethiopianreview.com, US based website whose owner is also convicted in “terrorism.” Among the “evidences” presented against Reeyot Alemu, there was a picture that she was tagged in a facebook status by a facebook friend she doesn’t recognize in person.
In the same way, Wubshet Taye, editor-in-chief of Awramba Times – currently defunct newspaper, is serving 14 years of imprisonment in Zeway, is also convicted of “terrorism” acts. Among witnesses presented against him included a phone conversation he had. The conversation was about the suit color choices on which he was supposed to wear as a best man for a wedding of his best friend but it was interpreted as “code” by police.
PROBLEM #2:
Why Filter the ‘Worst Penetration’?
In 2012, Open Net Initiative, called the Ethiopian internet penetration as the 2nd lowest penetration in Sub-Saharan Africa; however, having this lowest penetration, Ethiopia, instead of encouraging the connectivity, it is discouraging it. Ethiopia is listed as “Not Free” in both 2012 and 2013 reports of Freedom on the net 2013 that Freedom House is sponsoring.
Since 2006, following the controversial Ethiopian election of 2005, Ethiopia blocked news websites – some of these are operating locally (e.g. website the former ‘Fitih’ newspaper), opposition parties’ and affiliated entities’ websites, individual blogs, audio-video tubes and many others from being accessed in the country. Websites of Aljeezira, CNN, Economist and and IMF are among internationally recognized websites that were blocked and again unblocked in Ethiopia when the sensation of the news or story they published dies. My comment is that, if Aljazeera, CNN and Economist were Ethiopian media houses, their journalists would either exile or get imprisoned and the media houses would eventually shut down.
PROBLEM #3:
The Surveillance is More Sophisticated than What the Internet can Offer
Security researchers of Rapid7, an international security firm, scanned the Internet in 2012 for finFisher – internet surveillance software and discovered IP addresses of only 11 countries among which Ethiopia is one.
In February 2013, Citizen Lab – a research organization on the area, found that ‘a finSpy campaign in Ethiopia uses Ginbot 7 as bait to infect users.’ Ginbot 7 is a “terrorist group” according to Ethiopia and infected pictures with spyware of its leader, Dr. Birhanu Nega, were released on social networks to spy cyber activities of citizens who might download those pictures.
Ethiopia accepts universal conventions of Human Rights; its constitution provides the right for freedom of expression and the right to privacy. The problem is that the law provisions contradict the constitution and even if they don’t, they will be interpreted in a way they are used against journalists and innocent dissent citizens and on behalf of power.

In conclusion: Ethiopia MAYBE doing well in economic progresses; but it is NOT doing ANYTHING at all in human and democratic rights.

ኢትዮጵያን ለረጅም ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትርነት የመሩትና ሰፊ ስልጣን የነበራቸው መለስ ዜናዊ በነሃሴ ወር በድንገት መሞት በሃገር ውስጥም ሆነ በኢትዮጵያ ዓለማቀፍ አጋሮች ዘንድ የሀገሪቱን ፖለቲካዊ ሽግግር የሚመለከቱ ጥያቄዎችንና አጠራጣሪ ሁኔታዎችን አስነስቶ ነበር።በኢትዮጵያ ያለው የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በተለይ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ እየከፋ ሄዷል።አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በመስከረም ወር ስልጣኑን የተረከቡ ቢሆንም መንግስት በርሳቸው አመራር ሰብአዊ […]

ጥቅምት ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦጋዴን የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብት ጥሰትና የጦር ወንጀል የሚያሳየው ዘጋቢ ፊልም በቅርቡ በስዊድን ቴሌቪዥን መለቀቁን ተከትሎ ዛሬ አርብ፣ የስዊድን የጦር ኮሚሽን ማስረጃዎችን ተረክቧል። ማስረጃዎችን ለኮሚሽኑ ያስረከቡት ሂደቱ ዋና ተወናይ የሆነው ወጣት አብዱላሂ የሱፍና የአለማቀፍ የህግ ባለሙያዎች ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት ስቴላ ጋርደ ናቸው። የጦር ኮሚሽኑ የቀረበለትን ማስረጃ በማየት አፋጣኝ ውሳኔ እንደሚሰጥ …

ጥቅምት ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰብአዊ መብት ድርጅቱ ” በማዕከላዊ የሚገኙት መርማሪ ፖሊሶች ታሳሪዎች ጥፋታቸውን እንዲያምኑ፣ እንዲናገሩ ወይም ሌላ መረጃ እንዲያወጡ የሚያደርጉት በሃይል የማስፈራራት መንገድን በመጠቀም ሲሆን ይህም እስከ ማሰቃየት እና ሌላ ጎጂ አያያዝ እስከ መፈጸም ይደርሳል፡፡ ” ብሎአል። ከ2002 ዓም እስከ 2005 ዓም ባለው ጊዜ ውስጥ በማእከላዊ እስር ቤት የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን …

ጥቅምት ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ ከሙስና መንሰራፋት ጋር በተያያዘ የገጠመውን ፈተና በድል ለመወጣት ሕዝቡን ማሳተፍ እንዳለበትና ያለሕዝቡ ተሳትፎ የሚደረጉ ነገሮች ሁሉ የማይመለስ ጥፋትን ያስከትላሉ ሲሉ አቶ ስብሃት ነጋ ለኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮችን ምክር ለግሰዋል። የጸረ ሙስና ኮምሽን በሸራተን ሆቴል ያዘጋጀውና በምክትል ጠ/ሚኒስትር ማዕረግ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር የሆኑት አቶ ሙክታር ከድር እና የፓርላማው አፈጉባዔ አቶ …

ጥቅምት ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከመንገድ ጋር በተያያዘ ከዋግ ህምራ ዞን ርዕሰ ከተማ ሰቆጣ የሚሰማው የተቃውሞ ድምጽ በሁሉም የዞኑ ወርዳዎች መዳረሱን በስፍራው ያሉ ወኪሎች ገልጸዋል፡፡ ” የልማት ጥያቄያችን አልተመለሰም ፤  መንግስት ሰቆጣን እረሰቱዋል ፤ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ትግራይ መሄድ ግድ ብሎናል” ሲሉ ነዋሪዎች ለመንግስት ባለስልጣናት  ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ በቅርቡ ከሰቆጣ ፤ አበርገሌ ፤ ዝቋላ፤ ስሃላ …

ነገ በሚጠናቀቀው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ፴፪ኛ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ ‹‹የሃይማኖት መቻቻል›› በሚለው መርሐ ግብር ‹‹የብዝኃነት አያያዝ፣ አክራሪነት/ጽንፈኝነት ዝንባሌዎቹና መፍትሔዎቹ›› በሚል ርእስ አቶ ገዛኸኝ ጥላሁን፣ አቶ ታዴዎስ ሲሳይ እና አቶ ጣሰው ገጆ በተባሉ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሦስት ከፍተኛ አማካሪዎችና ባለሞያዎች ጽሑፍ መቅረቡና ውይይት መካሄዱ ተዘግቧል፡፡ በውይይቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ከየአህጉረ ስብከታቸው ተጨባጭ ኹኔታ …

ጥቅምት ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ባለስልጣናት የፓለቲካ እስረኞች ላይ ምርመራ ሲያካሂዱ ስቃይ እንደሚፈጽሙ ተቀማጭነቱን በአሜሪካ ያደረገው ሂዩማን ራይትስ ዎች ዛሬ ይፋ አደረገ፡፡ መንግስት በበኩሉ የቀረበውን ውንጀላ አስተባብሎ ሪፖርቱ ከእውነት የራቀና ተአማኝነት የሌለው ነው ብሏል፡፡ ድርጅቱ ታስረው የነበሩ እማኞች ዋቢ በማድረግ ባወጣው ሪፖርት ባለስልጣናት ከእስረኞች ቃል ለመቀበል ሲሉና ምርመራ ሲያካሂዱ ድብደባ እንደሚፈጽሙ አመልክቷል፡፡ …

ጥቅምት ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያና ኬንያ በግልገል ጊቤ ሶስተኛ የሀይል ማመንጫ ግድብ ላይ ያላቸውን አለመግባባት እልባት ለመስጠት የተባበሩት መንግስታት የአካባቢ ፕሮግራም ሁለቱንም ሀገራት በማግባባት ላይ እንደሆኑ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ በኦሞ ወንዝ ላይ በመገንባት ላይ ያለችው የሀይል ማመንጫ ፕሮጀክት በቅርብ የሚገኘውን የኬንያን ቱርካና ሀይቅ ይጎዳል በሚል የኬንያ መንግስት የአካባቢ ተቆርቋሪ ድርጅቶች ቅሬታቸውን ሲያሰሙ ቆይተዋል፡፡ …

ጥቅምት ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኢትዮጵያዊውን የእርሻ ሳይንቲስት አዲስ ለተቋቋመ የሳይንቲስቶች አማካሪ ቦርድ አባልነት መረጠው፡፡ ሳይንቲስቱ ፕሮፌሰር ገቢሳ ኢጀታ 26 አባላትን ላካተተው የተባበሩት መንግስታት የሳይንቲስቶች አማካሪ ቦርድ ሲመርጥ ብቸኛ የእርሻ ሳይንቲስት እንደሆነ ኢሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡ አዲሱ የተባበሩት መንግስታት የሳይንቲስቶች አማካሪ ቦርድ በአለም አቀፍ በተለያዩ ዘርፍ የታወቁ ሳይንስቶችን በአባልነት ይዞ ይገኛል፡፡ …

ጥቅምት ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን በጋምቤላ ክልል ንዌር ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ሚኒኛንግ ከተማ የተፈጠረው ግጭት ተባብሶ የሞቱ የመከላከያ ሰራዊት ቁጥር መጨመሩና በርካታ መሳሪያዎች ከመከላከያ ካምፕ መወሰዳቸው ተገለጸ፡፡ ባለፋው እሁድ አንድ መሳሪያ የታጠቀ ሰው እግር ኳሱን ሲመለከቱ በነበሩ ሰዎች መካከል ባስነሳው አለመግባባት የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና ነዋሪዎች ግጭት ውስጥ ገብተው ሰንብተዋል፡፡ ግጭቱ …

ጥቅምት ፰(ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል ዳውሮ ዞን ከሁለት ዓመት በፊት ተቀስቅሶ የነበረው የመልካም አስተዳደር እጦት ጥያቄ በአዲስ መልክ መቅረብ በመጀመሩ በዞኑ ውጥረት መንገሱን ተገለጸ፡፡ በዞኑ የሚኖሩ ማህበረሰብ ከፍተኛ የሆን የመልካም አስተዳደር ችግር እንዳለባቸው በመግለጽ ላይ መሆናቸውን የዳውሮ ዞን አካባቢ ተወላጅ የሆኑት አቶ ፍሰሀ ተስፋዬ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ አመልክተዋል፡፡ አዲስ …


‹‹በእግዚአብሔር ስም እምልላችኋለሁ የማውቀው ነገር የለም…›› አለ እየጮኸ፡፡
‹‹ገልብጡት›› አለ ኮማንደሩ፤ አላመነውም ነበር፡፡
ከግራና ቀኙ ቆመው የነበሩት ሁለቱ ፖሊሶች ገፍትረው በአፍጢሙ ደፉት፡፡ ወለሉ የአፈር ስለነበር ብዙም አልተጎዳም፡፡ እግሮቹ ቋንጃ ላይ ወፈር ያለ ቧንቧ ብረት አስገብተው እግሮቹን የኋልዮሽ በመጎተት በጠፍር መሳይ ገመድ ከወገቡጋ አሰሯቸው፡፡ የቧንቧ ብረቱን ዳርና ዳር ይዘው ሲያነሱት ቁልቁል ተዘቀዘቀ፡፡ አንጠልጥለው ግድግዳው ላይ የተሰኩ ሁለት አግድም ምሰሶዎች ላይ ሰቀሉት፡፡
‹‹አሁንስ አትናገርም?›› አለው ኮማንደሩ፡፡
‹‹ኧረ እኔ ምንም የማውቀ…›› የጀመረውን ሳይጨርስ በፊት አንደኛው ፖሊስ በያዘው ደረቅ ጎማ ጀርባውን አደረቀው፡፡
‹‹እውነቱን ትናገራለህ ወይስ አትናገርም?›› አለው ኮማንደሩ በድጋሚ፤ ከመናገር ይልቅ ዝም ማለት ያዋጣል በማለት ዝም አለ፡፡
‹‹ትናገራለህ፣ አትናገርም›› አለው ኮማንደሩ፤ ዝም አለ!
ሁለቱም ፖሊሶች በደረቅ ጎማቸው ተፈራረቁበት፤ ‹‹እናገራለሁ፣ እናገራለሁ…›› አለ በጩኸት፡፡ ዱላውን አቆሙለት ነገር ግን የሚናገረው ስላልነበረው ዝም አለ፡፡
‹‹ተናገራ፣…›› አለ ኮማንደሩ በብስጭት ጩኸት እያምባረቀ ከጥቂት ደቂቃዎች ዝምታ በኋላ፡፡
‹‹እ…ግ…ዚ…አ…ብ…ሔ…ር…ን… ምንም የማውቀው ነገር የለም፡፡›› አለ የመሐላውን እያንዳንዷን ድምፅ አጥብቆ እየጠራ፡፡ ቁጥሩን ለማያስታውሰው ጊዜ ሁለቱ ፖሊሶች በደረቅ ጎማቸው ጀርባው ላይ ተረባረቡበት፡፡
‹‹አትናገርም፣… ›› አለ ኮማንደሩ፡፡
‹‹ምን ልናገር…? በእግዚአብሔር አታምኑም… ኧረ እባካችሁ…››
‹‹እስከ ጥዋት ድረስ አስብበት… እስክትናገር ድረስ ከዚህ አትወርድም›› ብሎት ኮማንደሩ ክፍሉን ለቆ ወጣ፡፡ ሁለቱ ፖሊሶች እጆቹን በካቴና ጠርንፈው ሲያበቁ ኮማንደሩን ተከትለው ከወጡ በኋላ በሩ በላዩ ላይ ተጠረቀመ፡፡ ቤቱ ዓይን በሚያወጣ ጨለማ ተዋጠ፡፡ እንደዘቀዘቁት ይቆያሉ ብሎ አላመነም ነበር፡፡ ከአሁን አሁን አንዳቸው ተመልሰው ይመጣሉ ብሎ አሰበ፣ ተመኘ፣ ፀለየ – ምንም የተለወጠ ነገር የለም፡፡

ያጠፋው ጥፋት ምን እንደሆነ አልገባውም፡፡ ድምፁን አውጥቶ ጮኸ፣ ተለማመነ… ነገር ግን መጥቶ የሚረዳው ሰው ቀርቶ የሚሰማው ሰው መኖሩን እስኪጠራጠር ድረስ መልስ አጣ፡፡ በካቴና የታሰሩትን እጆቹን የሚያረግበት ቦታ አጣ፡፡ ወደላይ ሲያደርጋቸው በደቂቃ ውስጥ ክንዱ ይዝላል፡፡ ወደታች ሲለቃቸው ሰውነቱን ከመጎተትም በተጨማሪ ጣቱን የሚቆጠቁጥ ድንዛዜ ይሰማዋል፡፡ ከላይ እግሮቹ መሐል ያለው ብረት ጉልበቱን ለሁለት በጥሶ ሊወጣ የደረሰ ይመስል ወጥሮ ይዞታል፡፡
እያንዳንዷ ደቂቃ የሰዓት ያክል ረዘመችበት፡፡ እልፍ የስሜት መለዋወጦችን በደቂቃዎች ውስጥ ያስተናግዳል፡፡ ድንገት የማቅለሽለሽ ስሜት ተሰማው፡፡ እዚያው የተዘቀዘቀበት ሊያስመልሰው እንደሆነ ገባው፤ ነገር ግን ውጦ ሊመልሰው አይችልም – ተዘቅዝቋል፡፡ ሆዱ ውስጥ ያለው ምግብ ወጣ፡፡ በተዘቀዘቀው ፊቱ፣ በግንባሩ ላይ ቁልቁል ፈሰሰ፡፡
‹‹አምላኬ ካላዳንከኝ ቶሎ ግደለኝ…›› ብሎ ፀለየ፡፡ ያጠፋውን ጥፋት አያውቅም፡፡ ፖለቲካ አይወድም፤ ‹ፖለቲካና ኮረንቲን ከሩቁ› ባይ ነው፡፡ ፖሊሶቹ ተመልሰው ሲመጡ ምን እንደሚላቸው ግራ ገብቶታል፡፡ ካልሆነ መዋሸት እንደሚሻል እያሰበ ነው፡፡ ምን ብሎ ይዋሻል? ውሸቱንስ እንዴት እውነት ማስመሰል ይቻላል? ሕመሙ… በአግባቡ ማሰብ አላስቻለውም፡፡ በክፍሉ ውስጥ የሚሰማው ብቸኛ ድምፅ እምባው በግንባሩ ላይ ፈሶ መሬት ላይ ሲንጠባጠብ የሚወጣው ድምፅ ብቻ ነው፡፡ አፍንጫው እየተዝረከረከ የሚያወጣው ፈሳሽ ዓይኑ ውስጥ እየገባ ያሰቃየው ጀመር፡፡ ከእግር ጥፍሩ እስከራስ ፀጉሩ ድረስ ሕመም ይሰማዋል፡፡
ቀስ በቀስ ግን ሰውነቱ እየቀዘቀዘ መጣ፡፡ መጀመሪያ እግሮቹን አጣቸው እንደተዘቀዘቀ ነው፡፡ እግሮቹ ከላይ መታሰራቸው ይታወቀዋል፡፡ ግን ሕመሙ አይሰማውም፡፡ ደንዝዟል፡፡ ሊያንቀሳቀሳቸው ሲሞክር አይችልም፡፡ እግሮቹ ከላይ ይኑሩ አይኑሩ እርግጠኛ መሆን አቃተው፡፡ ጨለማ ነው፣ ምንም ዓይታየውም፡፡ አዕምሮውም እግሮቹን ማዘዝ አቅቶታል፡፡
ወደታች የተንጠለጠሉት እጆቹ ጣቶች ደም አርግዘው በማበጣቸው ሊፈነዱ የደረሱ ይመስላሉ፡፡ ጥዝጣዜያቸው እከኩኝ፣ እከኩኝ ቢያሰኝም የሚያክበት ትርፍ እጅ አልነበረውም፡፡ ከላይ እየቀዘቀዘ፣ ከታች እየተቃጠለ ነው፡፡ ሕይወቱ ቀስ በቀስ እየወጣች እንደሆነ ተሰማው፣ ፈራ፡፡ ቀድሞ ግደለኝ ብሎ የለመነውን አምላኩን ደግሞ ‹‹አትግደለኝ›› እያለ በሹክሹክታ ይለማመነው ጀመር፤ ከዚያ በኋላ የሚያስታውሰው ነገር የለም፡፡
—-
—-
ቅዝቃዜ ይሰማዋል፡፡ ሙሉ ሰውነቱ ይቀዘቅዛል፡፡ ጭው ባለ ሜዳ ላይ ብቻውን በጀርባው ተንጋሏል፡፡ ዝናብ እየዘነበ ነው፡፡ ዝናቡ ግን የሚንጠባጠብ ዝናብ አይደለም፡፡ ሰማዩ የተቀደደ ይመስል ጎርፍ ነው እላዩ ላይ የሚወርደው፡፡ ዝናቡ ይቋረጥና፣ ጥቂት ቆይቶ መልሶ ይደፋበታል፡፡ ሰውነቱ ዝሏል፡፡ በትግል ዓይኖቹን ገለጣቸው፡፡ አንዱ ፖሊስ የውኃ ባልዲ ይዞ ቁልቁል ይመለከተዋል፡፡ አዎ፣ ትዝ አለው፡፡ ታስሮ ነበር፡፡ ተዘቅዝቆ ሲገረፍ ነበር፡፡ ዘቅዝቀው ሰቅለውት ጥለውት ሄደው ነበር፡፡ አዎ፣ ትዝ አለው፡፡ ያ ሁሉ ስቃይ፡፡ አሁን ወርዷል፡፡ መሬት ላይ ተዘርሯል፡፡ ውኃ እየደፉበት ነበር፤ ዝናብ አይደለም ማለት ነው፡፡ ድጋሚ ሊጠይቁኝ ነው የመጡት ብሎ አሰበ፤ ምን ሊላቸው ነው?
‹‹ተነስ!›› አለው ፖሊሱ፡፡
መነሳት አልቻለም፡፡ እጁን ዘረጋለት፡፡ ‹‹እንኳን ደስ አለህ፤ ነጻ መሆንህ ተረጋግጧል፡፡ ስለዚህ ከሁለት ቀን በኋላ ትለቀቃለህ›› አለው፡፡ ‹‹እንደዚያ ካሰቃያችሁኝ በኋላ…?›› ብሎ መጠየቅ አልቻለም፡፡ ፈርቷቸዋል፡፡ ለሁለት ቀናት እንዲያገግም እዚያው ‹‹ማረሚያ›› ቤት ውስጥ አቆዩትና ነጻ ወጣ፡፡ ‹‹አገሪቷን ለቅቄ መጥፋት›› አለብኝ እያለ ነው በልቡ፤ ሁሉንም ነገር በጥርጣሬና በፍርሐት እየተመለከተ ነው፡፡ ነጻ መውጣቱን እንኳ ማመን አልቻለም፡፡ ምናልባት ቅዠት ቢሆንስ?!
ሁለት፣ ሦስት እያለ አንድ ሳምንት ሞላው፡፡ መረጋጋት ጀመረ፡፡ ገጠመኙን ለማንም መናገር አልፈለገም፡፡ የገዛ ጥላውን ሳይቀር እየተጠራጠረ ነው፡፡
ብዙ ነገር አሰኘው፡፡ እንደሰው መሳቅ፣ መጫወት፣ በቀን ክፉ ያቋረጠውን ኑሮ መቀጠል አማረው፡፡ ከቤቱ ወጥቶ መንገዱ ይዞ ዝም ብሎ ይጓዝ ጀመር፡፡ በጠንካራ ሐሳብ የታጀበ መንገድ፡፡ እመንገዱ ላይ ያገኘው አንድ ኢንተርኔት ካፌ ዘው ብሎ ገባ፡፡ ኢሜይሉን ከፈተው፡፡ ምንም ያላነበበው ኢሜይል የለም፡፡
‹‹እንዴ?…›› አለ ለራሱ፡፡
የመጨረሻው ኢሜይል ከቀድሞው የሥራ ባልደረባው እሱ የታሰረ ዕለት የተላከ ነበር፡፡ አላነበበውም፤ ግን የተነበቡ ኢሜይሎች ውስጥ ተቀምጧል፡፡ ትዝ ሲለው የኢሜይል አድራሻውን እና የይለፍ ቃሉን ለኮማንደሩ ተናግሮ ነበር፡፡ ‹አንብበውታል ማለት ነው› አለ፤ የሥራ ባልደረባው የፌስቡክ ፖለቲከኛ ስለነበር በዚያ ጉዳይ አይስማሙም ነበር – በእሱ ጉዳይ ይሆን ያሰሩኝ ብሎ ጠረጠረ፤ ነገር ግን ከሱጋ የነበራቸው ግንኙነት የሩቅ ነበር፡፡ አሁን ግን ወደውጭ አገር ሄዶ ነው እየተባለ ቢወራም በድንገት ከሥራ ቀርቶ መልቀቁን ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡ እንዲያውም ወደውጭ አገር መሄዱን ሲሰማ ‹‹ለካስ ፌስቡክ ላይ ፖለቲካ የሚጽፈው ጥገኝነት ለመለመኛ ነው?›› ብሎ ነበር፡፡ ምን ብሎ ጽፎልኝ ይሆን ብሎ ቢያስብም መክፈት ግን አስፈራው፡፡ ፖሊሶቹን መልሶ እንደመጥራት አስፈራው፡፡
ብዙም አላስቻለውም፤ ብዙ ካመነታ በኋላ መልሶ ኢሜይሉን ከፈተው፡፡ እንዲህ ይነበባል፡-
‹‹አሁን ለምጽፍልህ ነገር ይቅርታ እንድታደርግልኝ እለምንሃለሁ፡፡ ሆኖም፣ ነፍሴን ለማትረፍ ከዚያ ውጪ አማራጭ አልነበረኝም፡፡ ፖሊስ በማላውቀው ነገር ይዞ ሲያሰቃየኝ ነበር የከረመው፡፡ አብረውህ የሚሠሩትን አጋልጥ እያሉ ሲቀጠቅጡኝ እና ምስጢር ካወጣሁ እንደሚለቁኝ ቃል ሲገቡልኝ፥ አንተንና ሌሎችም ስማቸው የመጡልኝን የሥራ ባልደረቦቼን እና ጓደኞቼን ስም ዘርዝሬ ነገርኳቸው፡፡… ከለቀቁኝ በኋላ በሌላ ስቃይ ድንበር አሳብሬ ጎረቤት አገር ገብቻለሁ፡፡ አሁን የምመክርህ ነገር፣ ማቄን ጨርቄን ሳትል አገር ለቀህ እንድትወጣ ነው፡፡ አለበለዚያ አንተንም ይይዙህና ምንም የማያቁ ሰዎችን ስትጠቁም… ተጠቋቁመን ማለቃችን ነው…››
ያነበበውን ማመን አቃተው!
—-
ይህ አጭር ልቦለድ የተጻፈው ዛሬ በተለቀቀው የሰብኣዊ መብቶች ታዛቢ የማዕከላዊ ፖሊስ ጣብያ የማሰቃየት ተግባር ማጋለጫ ሪፖርት ላይ በወጡ ሐሳቦች ላይ በመመርኮዝ ነው፡፡

ማዕከላዊ ተብሎ በሚታወቀው የፌደራሉ የምርመራ ጣቢያ ሶስት የተለመዱ ስፍራዎች አሉ።አንደኛው ሰዎች ያለመብራት የሚታሰሩበት እና ጭለማ ቤት የሚባለው ነው።ሁለተኛው ለግርፋት የተመቻቸው ጣውላ ቤት የሚባለው ሲሆን ሶስተኛው ደግሞ በተሻለ ደረጃ የሚታሰሩበት እና ከዚሁ የተነሳ በሌስሊ ኣባባል «ሸራተን» ተብሎ የሚታወቀው ነው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ከተፎካካሪው የናይጀሪያ ብሔራዊ ቡድን ጋ በአዲስ አበባ ስታዲየም ግጥሚያ ያካሄደው ባለፈው እሁድ ዕለት ነበር። ይህንኑ የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ዋና ምክንያት በማድረግ ወጣቱ ያሳየዉ ሥነ ምግባር በዛሬው የወጣቶች ዓለም ባጭሩ እንቃኛለን።

ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደዉ የዓመቱ የመጀመሪያ ስብሰባዉ አዲሱ ፕሬዝደንት ባለፈዉ ሳምንት ባቀረቡት የዓመቱ የመንግሥት የትኩረት አቅጣጫ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በእንግሊዘኛው ምህፃር «ፍሮንቴክስ» የተባለው ለአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት የድንበር ጥበቃ ድጋፍ ሰጭ ድርጅት ፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በጀልባ ወደ አውሮፓ ለመሻገር የሚሞክሩ ስደተኞችን በመመለስ የደረሰበትን ወቀሳ አመነ ።

አቶ ምኅረት ደበበ – የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ​​
ኅዳሴ ግድብ እና የዓለምአቀፉ ቡድን ሪፖርት
ታዋቂ የሆኑ ጋዜጦችና የዜና ወኪሎች ስለናይል ወይም ስለአባይ ወንዝ እና ስለኅዳሴ ግድብ እየፃፉ ነው፡፡

የኒው ዮርኮቹ ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙኃን ብሉምበርግ፣ ዘ ዋል ስትሪት ጁርናል፣ ዘ ናሽናል ከእነዚያ መካከል ይጠቀሳሉ፡፡

ዘ ዋል ስትሪት ጁርናል በረቡዕ፣ ጥቅምት 6/2006 ዓ.ም ዕትሙ ባሠፈረው ዘገባው ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብፅ በመጭው ሣምንት ማክሰኞ፣ ጥቅምት 12/2006 ዓ.ም እንደሚሰበሰቡ የኢትዮጵያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በምንጭነት ጠቅሶ ፅፏል፡፡
Ethiopia, Sudan, Egypt, Eritrea ​​
ይህ ስብሰባ የሚካሄደው በሦስቱ ሃገሮች የተመሠረተው የኤክስፐርቶች ቡድን የቅኝት ሪፖርቱን ካስገባ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ …

ጥቅምት ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በጋሞጎፋ ዞን በጨንጫ ወረዳ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ቤት መምህራን ለአባይ ግድብ ማሰሪያ በሚል ከደሞዛቸው ላይ ገንዘብ መቆረጡን ተከትሎ ካለፉት 3 ቀናት ጀምሮ የስራ ማቆም አድማ እያደረጉ ነው፡፡ የጨንጫ ፣ ጭነቶ፣ ጦሎላ፣ ጨፌ፣ ጺዳ እና ቱክሻ  ትምህርት ቤቶች መምህራን በአድማ ላይ መሆናቸውን ተከትሎ ትምህርት ቤቶች ተዘግተው ተማሪዎች ቤታቸው …

ጥቅምት ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚ ሀይለማርያም ዛሬ በተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ከፓርላማ አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ መንግስት የጎዳና ላይ ነውጥ ከሚያሰቡት ሀይሎች ጋር ለመነጋገር የማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ተናግረዋል። አቶ ሀይለማርያም በተቃዋሚዎች በኩል የሚቀርበው ቅጥ ያጣ ፍረጃ እና የጥላቻ ፖለቲካ እንዲቆም  እንዲሁም የጎዳና ላይ ነውጥ እናደርጋለን በማለት የሚያስቡ ሀይሎችም ሀሳባቸውን እንዲያቆሙ ጠይቀዋል። “የጎዳና …

ጥቅምት ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በስብሰባው ላይ የተሳተፉ አባቶች ለኢሳት እንደገለጹት በዛሬው ስብሰባ የልማት ኮሚሽኑ ሪፖርት ሰፊ ሽፋን የተሰጠው ሲሆን፣ መንግስት በቤተክርስቲያኑዋ ገቢ ላይ እየተጠቀመ መሆኑ ተነግሯል። የኮሚሽኑ መሪ ” በጭንቅ ውስጥ ነው እየሰራን ያለነው ፣ በመኖርና ባለመኖር ውስጥ እንገኛለን ያሉ” ሲሆን፣ ስሜታቸውን በድፍረት ሲናገሩ ከዋሉት ጳጳሳት መካከል ብጹዕ አቡነ ቄርሊዎስ ” ዛሬ ጀመርነው፣ …

ጥቅምት ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ ኃ/ማርያም ዛሬ ጠዋት የአገር አቀፍ የጸረ ሙስና ጥምረት 2ኛ መደበኛ ስብሰባ በሸራተን አዲስ በተካሄደበት ስነስርኣት ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር አንዳንዶቹ ባለሃብቶች ከከፍተኛ መንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር ሳይቀር የጠበቀ ቁርኝት ፈጥረው እንደነበር አምነው በዚህም ምክንያት ሰዎቹን መንግስት አይደፍራቸውም ተብሎ በህብረተሰቡ ዘንድ እስከመገመት ደርሶ ነበር ሲሉ ተናግረዋል፡፡ እንደዚህ ዓይነት የመንግስት …

ጥቅምት ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚ ሀይለማርያም ደሳለኝ በአዲስ አበባ የውሀ ቀለም አይቶ የማያውቅ ህዝብ አለ በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ 65 በመቶ የሚሆነው የአዲስ አበባ ህዝብ ውሀ 24 ሰአት እንደሚያገኝ ገልጸው፣ 20 በመቶ የሚሆነው ደግሞ በሳምንት 5 ቀናት፣ ከ10-15 በመቶ የሚሆነው ደግሞ በሳምንት አንድ ቀን ውሀ ያገኛል ብለዋል። በአብዛኛው የአፍሪካ ዋና ዋና ከተሞች የውሀ …

በእንግሊዘኛው ምህፃር FRONTEX የተባለው ለአውሮፓ ህብረት አባል ሃገራት የድንበር ጥበቃ ድጋፍ ሰጭ ድርጅት ፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በጀልባ ወደ አውሮፓ ለመሻገር የሚሞክሩ ስደተኞችን በመመለስ የደረሰበትን ወቀሳ አመነ ።

በዓሉ የሚከበረው ነቢዩ ኢብራሂም ልጃቸውን ለመስዋዕት ያቀረቡበትን ዕለት ለማሰብ ነው፡፡ በዓለም ዙርያ የሚገኙ የዕምነቱ ተከታዮች በአንድነት በመሆን በተለያዩ ሃይማኖታዊ ስርዓቶች የአረፋን በዓል አክብረዋል ።

ዉርሰ ኢትዮጵያ የተሰኘዉ ድርጅት ሰሞኑን በጀርመኗ ታሪካዊት ከተማ ጎታ 16ኛዉን ዓመታዊ ጉባኤዉን አካሂዷል። ጎታ ኢትዮጵያዉ አባ ጎርጎርዮስና ጀርመናዊዉን ሂዮብ ሉዶልፍን ከሶስት መቶ ሃምሳ ዓመታት በፊት ያስተናገደች ከተማ ናት።

የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የሃገሪቱን የበጀት ጣሪያ ከፍ ለማድረግ የሚያስችለውን ስምምነት ትናንት ማታ ካፀደቀ በኋላ ለ16 ቀናት የተዘጉት የተወሰኑ የፌደራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች ዛሬ ሥራ ጀምረዋል ። የሃገሪቱ የበጀት ጣሪያ ከፍ እንዳይል ሲሟገቱ የቆዩት ወግ አጥባቂ ሪፐብሊካኖች ውሳኔውን ሊያስቀሩት ባለመቻላቸው ሽንፈታቸውን አምነዋል ።

የመንበረ ፓትርያርክ 32ኛው ጉባኤ የረቡዕ ዕለት ከሰዓት ውሎ ካለፉት የተለየ ነበር፡፡ ዋና አጀንዳው ‹መቻቻልን› የተመለከተ ሲሆን አቅራቢዎቹም ከፌዴራል ጉዳዮች የተወከሉ አካላት መሆናቸውን በዕለቱ የመርሐ ግብር ዝርዝር ላይ ተገልጧል፡፡ ከሰኞ ጀምሮ ይቀርብ በነበረው የአህጉረ ስብከት ሪፖርቶች ላይ የመብት ጥሰትና ሥልጣንን ለግል ሃይማኖት ማስፋፊያ የመጠቀም አዝማሚያዎች መኖራቸውን፣ በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጠው እምነትን የመያዝ፣ የማስፋፋትና የአምልኮ ቦታ የማግኘት መብት እየተጣሰ መሆኑን የሚገልጡ ዘገባዎች ይሰሙ ነበር፡፡

በትናንትናው የከሰዓት ውሎ ስለ መቻቻል ገለጣ ከተሰጠ በኋላ ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳትና የጉባኤው ተሰብሳቢዎች የየአካባቢያቸውን ችግሮች በዝርዝር ነበር ያነሷቸው፡፡ ‹‹መቻቻል እስከ ምን ድረስ ነው›› ብለው ነበር ብጹዕ አቡነ ቄርሎስ የጠየቁት፡፡ ‹‹አሁን በምዕራብ ወለጋ ያለው ሁኔታ መንግሥት በአገሩ ያለ ይመስላል ወይ? ሰው እግሩን እሳት እየበላው ቻል ይባላል እንዴእንድንቻቻል አድርጉን፣ እንችላለን›› ነበር ያሉት፡፡

የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ሄኖክ ‹በነጆ ወረዳ በሕጋዊ መንገድ ተሠርቶ የነበረው ቤተ ክርስቲያን በአካባቢው ባለ ሥልጣናት ተጽዕኖ እንዲፈርስ መደረጉን፣ ለምን ታፈርሳላችሁ ብለው ድርጊቱን የተቃወሙ ስድሳ ምእመናን መታሠራቸውን›› በኀዘን ነበር የገለጡት፡፡ አያይዘውም ‹‹በባኮ ወረዳ የተመደቡ አንድ ካህን እያረሱ እያሉ የአካባቢው ባለ ሥልጣናት መጡ፤ ካህኑን በሰደፍ እየደበደቡ ‹ከዚህ ሀገር ልቀቁ፣ ይህ የነፍጠኛ መኖሪያ አይደለም› እያሉ አሰቃዩዋቸው፡፡ ካህኑን ሲደበድቧቸው አንበርክከው፣ ለ15 ደቂቃ አተኩረው ፀሐይዋን እንዲያዩ እያስገደዱ ነበር፡፡ ድብደባውን ሰምተው የወጡት ባለቤታቸው በድንጋጤ ታመው ከጥቂት ቀናት በኋላ ሕይወታቸው አለፈ››

‹‹በሰንበትና በቅዱስ ሚካኤል ቀን ምእመናን ሊያስቀድሱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄዱ ‹ለቅዳሴ ካህናቱ ይበቃሉ፤ እናንተ ውጡ›› እየተባሉ እንዳያስቀድሱ ይደረጋሉ፡፡ ከእኛ ቤተ ክርስቲያን 70 ሜትር ርቀት ላይ ሆን ተብሎ እርስ በርስ ለማጋጨት ለፕሮቴስታንቶች የጸሎት ቦታ ተሰጠ፡፡ ለምን ታጨቃጭቁናላችሁ፤ ይህ ቦታ ለእነርሱ አይሆንም ብሎ በመከራከሩ አንድ ዲያቆን ተደብድቦ ሞተ፡፡ የሕክምና ውጤቱም ሆን ተብሎ በወባ በሽታ ሞተ ተብሎ ተሠራ፡፡ ለሁለት ዓመት ያህል ተከራክረን አሁን ቦታው ለእኛ ተወሰነ፡፡

ጊምቢና መንዲ ላይ የምእመናን ልጆች ትምህርት ቤት ውስጥ በፖሊስ ማተባችሁን በጥሱ እየተባሉ ነው፡፡ ለምን ስንላቸው ከላይ የወረደ መመሪያ አለ ይሉናል፡፡››

ቀጥለው የሀገረ ስብከታቸውን ችግር ያቀረቡት የጋሞጎፋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤልያስ ነበሩ፡፡ ‹‹በጋሞ ጎፋ መቱ ወረዳ፣ ዋጁ ኡቆ ላይ የመስቀል ማክበሪያ ቦታችን ለሱቅ መሥሪያ ቦታ ተሰጠ፡፡ አቤት ብንል የሚሰማን በማጣታችን ዘንድሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ መስቀል ሳናከብር ዋልን፡፡ ሀገሪቱ በችግር ላይ በነበረች ጊዜ እንኳን መስቀል ሳይከበር ቀርቶ አያውቅም ነበር፡፡ የቤተ ክርስቲያን የይዞታ ቦታ ለመንግሥት እየተሰጠ ነው፡፡ በአቡነ ጳውሎስ ዘመን በቅዱስነታቸው በኩል ለክልሉ ደብዳቤ ጻፍን፡፡ ክልሉ ወሰነልን፡፡ ነገር ግን እስካሁን አልተረከብንም፡፡››

ቀጥለው ሃሳባቸውን የሰጡት የባሰ ካልመጣ በቀር ድምጻቸው ማይሰማው ብጹዕ አቡነ ያሬድ የሶማሌ ክልል ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ነበሩ፡፡ ‹‹በሶማሌ ክልል አምስት አብያተ ክርስቲያናት ብቻ ናቸው ያሉን፡፡ ምእመናኑ ብዙ ናቸው፡፡ ሲወልዱ የሚያስጠምቁበት፣ ሲያርፉ የሚቀበሩበት ቤተ ክርስቲያን እንትከል ብንል የሚሰማን አጥተናል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን የሚረዱ ምእመናን በግላቸው ጥቃት እየደረሰባቸው ነው፡፡ ለዚህ መልሳችሁ ምንድን ነው›› ብለዋል፡፡

በገለጻው ላይ ኢትዮጵያ ክርስትናን የተቀበለችው በ4ኛው መክዘ ነው የሚለውን የተቃወሙት ብጹዕ አቡነ ማርቆስ ‹‹ታሪክ ክፉም ሆነ በጎ እንደ ታሪክነቱ መተረክ አለበት፤ አቅራቢው ወንድማችን በ4ኛው መክዘ ክርስትና ገባ ያልከው ተሳስተሃል፡፡ ለመሆኑ ይህንን ለማለት ‹ላይሰንስ አለህ?› አባቱን የሚኮንን ልጅ ምን ያደርጋል? ነገሥታቱን ወቀሳችሁ፣ ቤተ ክርስቲያንን ነቀፋችሁ፤ ለመሆኑ ከማን ነው ይህቺን ሀገር የተረከባችሁት? ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ የገባው ጌታ ባረገ ዓመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 8 ላይ አለ፡፡ ይህንን ዛሬ ‹ግራጁዌት አድርገው›፤ ልዑካኑ ስትመጡ ስለምትናገሩት ነገር ዕወቁ፤››

የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ እንድርያስም ‹‹በቤተ መንግሥት የወርቅ ዕቃ ብቻ አይኖርም፣ የእንጨትም፣ የድንጋይም ዕቃ አለ፡፡ በቤተ ክርስቲያንም ሁሉም ጥሩ አይሆንም፣ መጥፎም ይኖራል፡፡ ነገር ግን እስከ መጨረሻው የጸና ይድናል ብሏል፡፡ በእኔ ሀገረ ስብከት ስድስት አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፡፡ ሦስቱ በአንድ አካባቢ፣ ሦስቱ በሌላ ቦታ፡፡ ይህንን ለክልሉ መንግሥት ብናሳውቅ አልረዱንም፡፡ የተበደለ ሰው ይጮኻል፤ ሲጮህ ደግሞ ፖለቲካ ነው ይባላል፡፡ ድሮ ያስቸገረን የንዋያተ ቅድሳት ዘረፋ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ቤተ ክርስቲያን ወደ ማቃጠል ተዛውሯል፡፡ አንዱ ባለ ሥልጣን እንዲያውም ችግሩን ሳቀርብለት ተቆጣኝ፤ ብዙ ብናገር ነፋስ ስለሚወስደው እዚህ ላይ ይብቃ››

ከብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳት ቀጥሎ የተናገሩት የወላይታ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ‹‹በበዴሳ ወረዳ ያለ አንድ የሌላ እመነት ተከታይ የሆነ ዳኛ ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጋር ቄራ አንካፈልም፤ በመኪና አብረን አንሄድም› ብሎ ዐወጀ፡፡ በጋራ በመቻቻል የኖርንበትን ዕድር ሁሉ ለዩ ብሏል፡፡ ታድያ እንዴት መቻቻል ሊመጣ ይችላል፡፡››

ከጉባኤው የቀረበውን ቅሬታና ሃሳብ ያዳመጡት የፌዴራል ጉዳዮች የሥራ ኃላፊዎች የቀረቡት ቅሬታዎች በሰነድ ተደግፈው ቢደርሷቸው እነርሱም በመፍትሔው ላይ መሥራት እንደሚችሉ፤ ኢትዮጵያ የሃይማኖቶች ጉባኤም ጉዳዩ በየደረጃው ቢቀርብለት መፍታት እንደሚችል፡፡ ቅሬታዎችን እንደዚህ ባለ መድረክ ከሚሆን በየጊዜው እየተገናኙ መፍታት ቢቻል›. የሚሉ ሃሳቦችን ሠንዝረዋል፡፡

የዘንድሮው የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ በአደረጃጀቱ ውበት፣ በተሳታፊዎቹ ብዛት፣ በአህጉረ ስብከቶች ቁጥር(50 ደርሰዋል)፣ በስብሰባው ቁም ነገረኛነት ካለፉት የተለየ ነበር፡፡ እነ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ የሰበካ ጉባኤ ስብሰባ ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን በብርቱ እንደ ደከሙበት ያሳያል፡፡ በየዘገባዎቹ የተሰሙትን የመብት ጥሰቶች፣ ሥልጣንን ተገን በማድረግ የሚፈጸሙ ጫናዎች፣ የአምልኮ ቦታ እጥረቶች፣ በካህናቱ ላይ የሚፈጸሙትን ግፎችና፣ የቤተ ክርስቲያንን ይዞታ የመንጠቅ ርምጃዎች ግን ሊገቱ ይገባቸዋል፡፡ ከአንዳንድ ክልሎች በቀር በብዙዎቹ የዞንና የክልል ባለ ሥልጣናት ችግሩን ተረድተው ለመፍታት እንደሚጥሩ ተገልጧል፡፡ በወረዳ ደረጃ የሚገኙት ግን ሥልጣንን ተገን በማድረግ የግል እምነታቸውን እያስፋፉ መሆኑን ያሳያል፡፡ በደቡብ ጎንደርና በምሥራቅ ጎጃም የተፈጸሙት የአብያተ ክርስቲያናትን የማቃጠል ርምጃዎች በጊዜው ተጣርተው መፍትሔ ካልተሰጣቸው ፍጻሜያቸው አያምርም፡፡

በየአካባቢው በሚገኙ ባለ ሥልጣናት የሚፈጸሙ ትንኮሳዎችም መቆም አለባቸው፡፡ ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳቱ ‹አታስቆጡን› እያሉ ደጋግመው የተናገሩት ነገር የዋዛ አይደለም፡፡ ኃላፊነት የማይሰማቸው አካላት የሚፈጽሙት ገደብ አልባ ትንኮሳና ጫና ወዴት እያመራ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡

ቤተ ክርስቲያኒቱም አደረጃጀቷንና አሠራርዋን ይበልጥ የምትፈትሽበት፣ አሁን ለገጠማት ተግዳሮት ብቁ የሚሆን አሠራና አወቃቀር የምትይዝበት፣ ችግሮችን በስብሰባ ብቻ ሳይሆን በአካባቢያዊ ውይይት፣ በሕግ መሥመርና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ በመሥራት የምትፈታበት መንገድ ሊኖር ይገባል፡፡  

ያለበለዚያ መጋቤ ምሥጢር ወልደ ሩፋኤል የተረተው ተረት መድረሱ የማይቀር ነው፡፡

በጣልያን ጊዜ ነው አሉ፡፡ ጎንደር ላይ ጣልያን በድማሚት አንዱን ተራራ ያናውጠዋል፡፡ ተራራው ‹እድም› እያለ ይፈርሳል፡፡ አንዲት የከብት እረኛ ልጅ ፈርታ ወደ እናቷ ሄደችና ‹እማዬ ኧረ ጣልያን ተራራውን እያፈረሰው ነው›› አለቻት፡፡ እናቷም ‹‹እነ ደጃዝማች እገሌ፣ እነ ፊታውራሪ እገሌ፣ እነ ራስ እገሌ እጅ አንሰጥም ብለው እየተጋደሉ ዐለፉ፡፡ ተራራውንስ ተይው ያፍርሰው፤ እርሱም መቀመጡን አብዝቶት ነበረ፡፡›› አለቻት አሉ፡፡ 

ከጥቅምት ፬ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ጀምሮ እየተካሄደ የሚገኘውና ሦስተኛ ቀኑን ያስቆጠረው ፴፪ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባ በዛሬው ዕለት ከቀትር በኋላ በነበረው ውሎ የተለየ ክሥተት አስተናግዷል፡፡ ‹‹የሃይማኖት መቻቻል›› በሚል ርእስ በ፴፪ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ በተካሄደው ውይይት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ከፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ባለሥልጣናት ጋራ በተለይም በመቻቻልና […]

ጥቅምት ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚገኘው መንበረ ፓትሪያርክ ስብሰባ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ባለው 32ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በቤተክርስቲያኑዋ ታሪክ  ተሰምቶ የማያውቅ ተቃውሞ ተከስቷል። አንድ በስብሰባው ላይ የተሳተፉ አባት እንደገለጹት በስብሰባው ላይ ”  ይህ መንግስት የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ለማፍረስ እንደተነሳ በስፋት ተነግሯል። የፌደራል ጉዳዮች የሀይማኖት ክፍል ሃላፊዎች ዛሬ ስለ አክራሪነትና ጽንፈኝነት …

ጥቅምት ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ልዩ ሀይል እየተባለ በሚጠራው ታጣቂ ሚሊሺያ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት፣ አስገድዶ መድፈርና የሰብአዊ መብቶች ጥሰት መፈጸሙን የሚያመለክት ዛጋቢ ፊልም በስዊድን ቴሌቪዥን መለቀቁን ተከትሎ ፣ የክልሉ መንግስት ምክትል ፕሬዚዳንቱን ቃለመጠይቅ በማድረግ አዲስ ዘጋቢ ፊልም ሰርቶ አቀረበ። የክልሉ መንግስት በለቀቀው አዲስ ፊልም የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አድናቆታቸውን የገለጹበት ክፍል የተካተተ ሲሆን፣ …

ጥቅምት ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከተማሪዎች አለባበስ ጋር  በተያያዘ ከቀናት በፊት የተጀመረው የተማሪዎች ተቃውሞ እልባት ሳያገኝ አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመለከተ፡ ትናንትና ከትናንት ወዲያ ምሽት ላይ ጥይት ሲተኮስ ማምሸቱን የገለጹት አንዳንድ የተማሪዎች ቤተሰቦች፣ የተኩሱ ምክንያት ጩሀት የሚያሰሙ ተማሪዎችን ዝም ለማሰኘት ያለመ ነው ብለዋል። ተማሪዎች በየክፍላቸው ሆነው ተቃውሞ እአሰሙ እንደሚገኙ የገለጹት ቤተሰቦች፣ አንዳንዶች …

ሃገር ውስጥ የተገኙ ዝሆኖች ሁሉ ይታሰሩ የሚል አዋጅ ይወጣል። አንድ አይጥ ከላይ ወደ ታች ትራወጣለች። ምን ሆነሽ ነው ብለው ይጠይቋታል። በሃገር ውስጥ ያሉ ዝሆኖች ሁሉ ይታሰሩ ተብሎ የወጣውን አዋጅ አልሰማችሁም እንዴ? ብላ ትነግራቸዋለች። ታዲያ አንቺ አይጥ እንጂ ዝሆን አይደለሽ ብለው ሲጠይቋት ። እሲኪጣራስ ብላ መለስች አሉ። እሲኪጣራ በዝሆንና በአይጥ መካከል ያለውን ልዩነት ጊዜ ይወስዳል። የተስፋዬ […]

በሀገራችን የስም አወጣጥ ወግና ልማድ እልም ያለችዋ ጥሩራ ባሪያ “አልማዝ” ወይም “ፀሐይ”፣ በነጭናጫነቷና በምግባረ ብልሹነቷ መንደርተኛው ሁሉ የሚያውቃት ሴት ወይዘሮ “ዐመለወርቅ” ወይም “አበቅየለሽ”፣ እልም ያለው ቦቅቧቃ “ደም መላሽ” ወይም “ሺመክት”፣ ቤሣቤስቲን የሌለው የኔቢጤው መናጢ ድሃ “ሀብታሙ” ወይም “አዱኛ”፣ እንዴት ያለው ንፉግና ክፉ ሰው “ቸሩ” ወይም “ደጉ”፣ … ተብሎ ሲጠራ እናውቃለን፡፡ መቼም ‹ስም አይገዛም› ይባላልና በዚህ […]

ክፍል ስድስት በስምምነት ላይ የተመሰረተ የባህል አንድነት (CCU) የእድገት አቅጣጫዎች በዚህ ንድፈ ሃሳብ መሰረት ባህል አዳጊ ነው፡፡ ባህል በተፈጥሮው ዳይናሚክ በመሆኑ በኣንድ ቡድን ህይወት ውስጥ ትውልዶች በራሳቸው ዘመን የየራሳቸውን ፈጠራ እየጨመሩበት ወደላይ ያድጋል:: በሌላ በኩል ደሞ ባህል ወደ ጎን ካለው ሌላ ቡድን ጋር ሲነካካ(interact ሲያደርግ) እሴት እየተጋባ ወደ ጎንም ያድጋል።ወደ ጎን ሲያድግ ብዙ ያጋራ እሴቶችን […]

የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ ስብሰባ÷ በጉባኤው አዘጋጆችና ተሳታፊዎች የተለመደ አነጋገር÷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከእግር እስከ ራሷ በአንድ አዳራሽ የምትገኝበት ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ ዓመታዊ ስብሰባው÷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዓለም አቀፍ ጉባኤ ነው፡፡ ይኸውም ቤተ ክርስቲያናችን በውጭ እና በሀገር ውስጥ ካሏት የመንበረ ጵጵስና ሀገረ ስብከት መንፈሳውያን አስተዳደር ጉባኤያት ተመርጠው የተወከሉ …

ወለላዬ ከስዊድን (ክፍል አራት)

The Secret ሚስጢሩ

ሚስጢሩ አሁን በኃይለኛ ሂደት ላይ ወቷል። እርስዎም የውለታ ምስጋናን፤ የሚፈልጉትን ነገር በዓይነ ህሊና አስቀድሞ ማየትን፤ የተግባር ኃይልን ሂደቶች የሚረዱበት ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል ማለት ነው። ለመሆኑ አስቀድመው ይሄን ሁኔታ የተሸጋገሩ ምን ይላሉ?

ሙሉውን አስነብበኝ …