(ፋኑኤል ክንፉ) ከ26 ዓመታት በፊት የደርግ መንግሥት በትግራይ ክልል በሐውዜን ሕዝብ ላይ ያካሄደው የአውሮፕላን ድብደባ በስተጀርባ የእሥራኤል መንግሥት እጅ እንዳለበት የቀድሞ የህወሓት ሊቀመንበር አቶ ስብሃት ነጋ ይፋ አደረጉ። አቶ ስብሃት ይህን የገለፁት በሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ የደርግ 604 ኮር የተደመሰሰበትን የወታደራዊ ሳይንስ ጥበብ አስመልክቶ ሰሞኑን በሽረ ከተማ በተሰናዳ የውይይት መድረክ ላይ ነው። አቦይ ስብሃት ሲያስረዱ፣ “የቀዝቃዛው ጦርነት ማክተምን ተከትሎ ታላቋ ሶቪየት ሕብረት መፈራረስ ጀመረች። ይህን ክስተት ተከትሎ ሶቪየት ሕብረት ከኢትዮጵያ እየወጣች መጣች። በእሷ እግር የተተካውም የሩሲያ ፌዴሬሽን ለደርግ አገዛዝ ከዚህ በፊት ይደረግ የነበረውን ወታደራዊ እርዳታ አቋረጠ። ይህን ዓለም ዓቀፍ የፖለቲካ ዳይናሚዝም ተከትሎ አሜሪካ መራሹ የምዕራብ ዓለም እና የእሥራኤል መንግስት ከደርግ ጋር ወዳጅ ሆኑ። የደርግ አገዛዝን መውደቅን ተከትሎ ሊፈጠር የሚችለውን የጂኦ-ፖለቲካል ኃይል አሰላለፍ በመፍራት የምዕራቡ ዓለምና እሥራኤል  ደርግን ወዳጅ አድርገው በእኛ የትግል እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ እርምጃዎች መውሰድ ጀመሩ” ብለዋል። አያይዘውም፣ “በወቅቱ ሕወሓት ወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅሙ እየጠነከረ እየመጣ በመሆኑ አሜሪካና እሥራኤል ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገብተዋል። የአዲስ አበባው መንግስት ወዳጅ ስለሆኑ እንዴት ከተጀመረው የትጥቅ ትግል ሊያድኑት እንደሚችሉ ብዙ መንገዶችን ሞክረዋል። በጊዜው ደርግን ለማትረፍ ያልሞከረ የምዕራብ ሀገር አልነበረም። ሁሉም የሚችለውን አድርጓል። አሜሪካ ለማደራደር ስትሞክር እሥራኤል ግን የተለየ ሚና ወሰደች” ሲሉ ወንጅለዋል። “አሜሪካ አንዴ ወደ ሮማ ሌላ ጊዜ ወደ ለንደን እንድንመጣ ጠራችን።  ሮማ ላይ ጂሚ ካርተር አስጠርቶን የነበረ ቢሆንም፣ የደርግ ልዑካን ቡድን እናንተ ስለኢትዮጵያ ምን […]

ኢህአዴግ አይገዛንም!›› ተማሪዎቹ ፖሊስ የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠናን የተቃወሙ የደብረማርቆስ የመለስተኛ ሁለተኛ እና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ (መሰናዶ) ተማሪዎችን እያፈሰ እያሰረ እንደሚገኝ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ ተማሪዎቹ በትናንትናው ዕለት ኢህአዴግን የሚተቹ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን በማንሳታቸው ይሰለጥኑበት ከነበረው ሰፊ አዳራሽ ወጥተው 20፣ 20 ሆነው በጠባብ ክፍል እንዲሰለጥኑ ከመደረጉም ባሻገር ጥያቄ የሚያነሱት ላይ ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ዛሬ ጠዋት […]

በመጪው የካቲት ከሚከበረውን የህወሓት 40ኛ አመት የልደት በዓል ይከበራል፡፡ ከበዐሉ አከባበር ዝግጅት አንዱ የሆነው፤ ከትጥቅ ትግሉን ዋነኛ ሥፍራዎች የተወሰኑት ከታህሳስ 13 -16 ቀን 2007 በታዋቂ አርቲስቶች እና ጋዜጠኞች እንዲጎበኙ ተደርጓል፡፡ ጉብኝቱ የተጀመረው በደደቢት ሲሆን፣ በዚያው ቦታ ላይ በተዘጋጀ ግዜያዊ የሣር ዳስ ውስጥ ገለጻ ተሰጥቶ ነበር፡፡ በዕለቱ ተናጋሪ የነበሩት የህወሓት መሥራቾች አባይ ፀሐዬ፣ ስብሐት ነጋ፣ ስዩም መስፍን እና አቦይ ካህሳይ እንዲሁም የብአዴን መሥራች በረከት ስምዖን ነበሩ፡፡ የገለጻቸውን ቅጂ ከታች ካለው የድምጽ ፋይል ያዳምጡ፡፡ —— *********** More from Horn Affairs AmharicAudio | በኦሮሞ ተማሪዎች ስለተካሄዱት ተቃውሞዎች የአሜሪካ ድምጽ ሬድዮ ዘገባAudio| የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ አመራር በአዲሱ ማስተር ፕላን ላይ የሰጡት መግለጫAudio| ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ በመቐለ ያደረጉት ንግግርበደቡብ ሱዳን ያሉ ኢትዮጵያዊያን መንግስታቸው እንዲታደጋቸው ይሻሉሚኒስትር ሽፈራው:- በቅርቡ ለሚመረቀው ተንዳሆ ስኳር መዘግየት ህንዶችን ወቀሱዓባይ ወልዱ፡- ህወሓትን ለድል ያበቃው የውጭና የሌሎች ድጋፍ ሳይሆን የጠራ ሕዝባዊ መስመር ነው

 

(በብዙ አንባቢያን ጥያቄ በድጋሚ የታተመ)

 
የገና እና የጥምቀት በዓላት ሲደርሱ በምእመናኑ ዘወትር የሚጠየቁ ጥያቄዎች አሉ፡፡ እነዚህን እና መሰል የሕዝቡን የዘወትር ጥያቄዎች መልስ የያዘ የማያዳግም ጥራዝ ማውጣት ከሊቃውንት ጉባኤ የሚጠበቅ ነው፡፡ አብዛኞቹ ጉዳዮች አበው ቀድመው ሥርዓት የሠሩባቸው እና ማብራርያ ብቻ የሚያስፈልጋቸው ናቸውና፡፡ ለዛሬ ሦስቱን ብቻ እንመልስ፡፡
 
ገና እና ጥምቀት ዓርብ እና ረቡዕ ቢውሉ ይበላባቸዋል ወይስ ይጾማሉ?
ፍትሐ ነገሥት፡ ዳግመኛ በየሳምንቱ ዓርብ እና ረቡዕን መጾም ነው፡፡ በዓለ ሃምሳ፣ የልደት እና የጥምቀት በዓል የተባበሩባቸው ጊዜ ካልሆነ በቀር /ዐንቀጽ 15፣ ቁ566/

የዓርብን እና የረቡዕን ጾም ግን ከልደት፣ከጥምቀት እና ከበዓለ ሃምሳ በቀር ዘወትር ይጹሙ /ዐንቀጽ 15፣ቁ 603/
የገና እና የጥምቀት ቅዳሴ ስንት ሰዓት ነው?
ፍትሐ ነገሥት፡ ስለ ልደት እና ጥምቀት ግን በዚያ ዘመን በኒቂያ የተሰበሰቡ ሊቃውንት ቅዳሴው በሌሊት ይሆን ዘንድ አዘዙ /ዐንቀጽ 15፣ ቁ 595/
ልደት ጋድ አለው?
ፍትሐ ነገሥት፡ የልደት እና የጥምቀት በዓላት ጋድ አላቸው /ዐንቀጽ 15፣ ቁ 566/
     ትንታኔ፡ የገና ጾም 44 ቀናትን ይይዛል፡፡
                   40 ጾመ ነቢያት
                     3 ጾመ አብርሃም ሶርያዊ
                    1 ጋድ
               ድምር 44
የገና ጋድ ከጾሙ ተያይዞ የተቀመጠ እንጂ ለብቻው የተቀመጠ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ሰሙነ ሕማማት ለብቻው የሚቆጠር ጾም ነው፡፡ /ዐንቀጽ 15፣ቁ 565/ ነገር ግን አንድ ሰው ዐቢይ ጾምን ሳይጾም ከርሞ ሕማማትን ለብቻው መጾም አይችልም፡፡ የገናም ጋድ እንዲሁ ነው፡፡
ይህንን ጋድ የልደትን ጾም የማይጾሙ ሰዎች እንዲጾሙት የተሠራ ነውን?
መልስ፡ በቤተ ክርስቲያን ላልተጠመቁ፣ ለማይቆርቡ፣ ንስሐ ለማይገቡ፣ ለማያስቀድሱ፣ ለማይጾሙ ሰዎች ተብሎ የተሠራ ልዩ ሥርዓት የለም፡፡ በፍትሐ ነገሥት ዐንቀጽ 15፣ ቁ 565 እንደተገለጠው ሰባቱ አጽዋማት «ለክርስቲያን ሁሉ» የታዘዙ ናቸው፡፡ ስለዚህም የገናን ጾም ክርስቲያን ሁሉ ጾመው በበዓለ ልደት ሊገድፉ ይገባቸዋል፡፡ ፍትሐ ነገሥት ስለ ገና ጾም ሲገልጥ «መጀመርያው የኅዳር እኩሌታ ፋሲካው የልደት በዓል ነው» ይላል /ዐንቀጽ 15፣ ቁ 568/፡፡ ይህም ከገና ጾም ተሸርፎ የሚጾም ነገር እንደሌለው ያሳያል፡፡
መልካም በዓል

የኢሳያስ አፍወሪቂ ጋዜጣዊ መግለጫ እና ወያኔ ከውጪ የሚኖሩ ተቃዋሚዎች ጋር የድርድር ጥያቄ እንዲያዣንብብ እየሰራ መሆኑ ታውቋል:: ተወካዩን አስመራ ለማስገባት ዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ ቀጥሏል:: ከአውሮፓ ወደ ኤርትራ ለውህደቱ ስብሰባ እንዲሄድ የተወከለው በጀርመን የሚኖረው አቶ ካሳዬ መርሻ ወደ አስመራ እንዳይገባ በሻእቢያ መከልከሉ ሲታወቅ ከፊል ኤርትራዊ እንደሆነ የሚታወቀው እና ከአውስትራሊያ የተወከለው የወልቃይት ተወላጅ አቶ አለልኝ ከሻእቢያ ፈቃድ ማግኘቱ ታውቋል:: […]

ክፍል ሁለት (በእውቀቱ ሥዩም) እንደምነሽ ሸገር የከሰመው ወንዝሽ የከሰመው ወዝሽ የሚታየው ነጥፎ እንደምነው ጣፎ እንዴት ነው ቀበና እስቲ ድንጋይ ላጥምድ መረብ ልጣልና፡፡ በነገራችን ላይ በኣዲስ ኣበባ የሚገኙ ካፌዎችና ምግብ ቤቶች“ ኒውዮርክ”“ ዴምቨር” “ወዘተረፈ ተብለው የሚጠሩትን ያክል ባውሮፓና በኣሜሪካ ያሉ ሬስቶራንቶች ደግሞ ”ዱከም“ ፤ ኣራትኪሎ ፤ ፒያሳ በሚል ተሰይመዋል፡፡ የዚህ ምክንያቱ ምንድር ነው ፡፡ ኣዲስ ኣበባ […]

ፖሊስ የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠናን የተቃወሙ ተማሪዎችን እያፈሰ እያሰረ ነው

• ‹‹ኢህአዴግ አይገዛንም!›› ተማሪዎቹ
ፖሊስ የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠናን የተቃወሙ የደብረማርቆስ የመለስተኛ ሁለተኛ እና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ (መሰናዶ) ተማሪዎችን እያፈሰ እያሰረ እንደሚገኝ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡

ተማሪዎቹ በትናንትናው ዕለት ኢህአዴግን የሚተቹ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን በማንሳታቸው ይሰለጥኑበት ከነበረው ሰፊ አዳራሽ ወጥተው 20፣ 20 ሆነው በጠባብ ክፍል እንዲሰለጥኑ ከመደረጉም ባሻገር ጥያቄ የሚያነሱት ላይ ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ዛሬ ጠዋት ጥያቄ ያነሳሉ የተባሉት ተማሪዎች ስልጠና ወደሚሰጡባቸው ትምህርት ቤቶች ግቢ እንዳይገቡ ከመደረጉም ባሻገር የድብዛ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ስልጠናውን መቃወማቸውን ተከትሎ ፖሊስ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የሰሙ የተክለሀይማኖት መልስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እርምጃውን በመቃወም ለድብዛ ተማሪዎች ድጋፍ መስጠታቸው ተገልጾአል፡፡

የሁለቱም ትምህርት ቤት ተማሪዎች በጋር በመሆን ከተማው አደባባይ ላይ በመውጣት ‹‹አህአዴግ አይገዛንም፣ ኢህአዴግ ሌባ፣…›› የመሳሰሉ መፈክሮችን በማሰማት ተቃውሟቸውን መግለጻቸውን ተከትሎም ፖሊስ ተማሪዎቹን እያፈሰ ወዳልታወቀ ቦታ መውሰዱ ተሰምቷል፡፡ ከዚህም ባሻገር ጥያቄ የሚጠይቁና ፖሊስ ተቃውሞውን አደራጅተዋል ብሎ የሚጠረጥራቸውን ተማሪዎች እየፈለገ እያሰረ መሆኑን ተማሪዎቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በምስራቅ ጎጃም ዞን በ17ቱም ወረዳዎች የሚገኙ ተማሪዎች ስልጠናውን ካልወሰዱ ከትምህርት ቤት እንደሚባረሩና ፈተና ላይ እንደማይቀመጡ ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም ስልጠናውን መቃወማቸውን ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡

The Indian Folktales በተሰኝ ከዛሬ 100 ዓመት በፊት በ1919 እኤአ በታተመ መጽሐፍ ላይ እንዲህ ይላል፡፡
አንድ የሕንድ ጠቢብ ደቀ መዝሙሮቹን ሥራ እንዲሠሩ አዘዛቸውና ራቅ ብለው በከፍታ ቦታ ላይ ይመለከታቸው ጀመር፡፡ ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ተመልሶ ደቀ መዝሙሮቹን ሰበሰባቸው፡፡ ከዚያም እንዲህ አላቸው ‹‹ከእናንተ መካከል የተወሰናችሁ እንደ ሰው የተወሰናችሁት ደግሞ እንደ እንስሳ ስትሠሩ ነበር›› ተማሪዎቹም ተገርመው ጠየቁት፡፡ መምህሩም ‹‹እንደ እንስሳ መሥራት ማለት አንድን ነገር መጎተት፣ መሸከም፣ መግፋት፣ ማዞር ወይም የሚደርስበት ቦታ ማድረስ ማለት ነው፡፡ ምን እየሠራ እንደሆነ፣ ለምን እየሠራ እንደሆነ፣ የሚመጣው ውጤት ምን እንደሆነ፣ ዓላማው ምን እንደሆነ አያስብም፡፡ በሥራው ላይም ከራሱ አስቦ አንዳች አይጨምርም፡፡ የዛሬ ሺ ዓመት አንድ ዝሆን የሠራውን ዛሬም ሌላ ዝሆን በተመሳሳይ መልኩ ይሠራዋል፡፡(አንድ ሊቅ ‹ዕብደት ማለት አንድ ውጤት እንደማያመጣ እየታወቀ በተደጋጋሚ መሥራት ነው› ብሎ ነበር) አያሻሽለውም፡፡ ምናልባት ከሰው በላይ ተሸክሞ፣ ስቦ፣ ገፍቶ፣ ቆፍሮ፣ ሮጦ፣ ደክሞ፣ ይሆናል፡፡ ያ ግን እንስሳውን ጠንካራ ያስብለዋል እንጂ ጎበዝ አያስብለውም፡፡ጉብዝና አእምሮ አለበት፡፡ እንደ እንደስሳ የሚሠሩ ሰዎች እንጂ እንደ ሰዎች የሚሠሩ እንስሳት የሉም የተባለውም ለዚህ ነው፡፡ 

እንደ እንስሳ የሚሠሩ ሰዎች እንደዚህ ናቸው፡፡ የተሰጣቸው ሥራ ያለ መለገም ይሠራሉ፡፡ ሲቆፍሩ፣ ሲገነቡ፣ ሲያመላልሱ፣ ሲያርሱ፣ ሲያጭዱ፣ ሲሸከሙ፣ ሲሰፉ፣ ሲፈጩ ይውላሉ፡፡ የሚሠሩት ያለ የሌለ ጉልበታቸውን ሁሉ ተጠቅመው ነው፡፡ ነገር ግን ጉልበታቸው እንጂ አእምሯቸውን አያሠሩትም፡፡ አርባ ዓመት፣ ሃምሳ ዓመት ተመሳሳይ የሆነን ሥራ ያለ ምንም ማሻሻል ሲያከናውኑ ታያላችሁ፡፡ የጻፉት ወረቀት፣ የሰፉት ልብስ፣ ያመረቱት እህል፣ የሠሩት ቤት ምን እንደሚሆን አያስቡም፡፡ እስኪ ቀየር አድርገን፣ አሻሽለን፣ ለውጠን፣ በተለየ መንድ እንሥራው አይሉም፡፡ ስለዓላማው፣ ስለሚከተለው ነገር፣ ስለሚያደርጉት ጥንቃቄ፣ ስለ ዕውቀት መሻሻል ምንም ነገር አያስቡም፡፡ እንዲያውም አእምሮ ያለው መጥቶ ለውጥ ሲያመጣባቸው ዓለም ያለፈች ይመስላቸዋል፡፡ ታላቅነታቸውን የሚያስመሰክሩት ያንን ብቻ በማድረግና ያን ጠብቆ በመኖር ነው፡፡ ለምን እንደሚያደርጉትና ለምን እንደሚጠብቁት ግን አያውቁም፡፡ብቻ ያ ነው ሥራቸው፡›› አላቸው፡፡
ተማሪዎቹም ራሳቸውን ነቀነቁ፡፡ ‹‹ከእናንተ መካከል አንዳንዶቻችሁ እንደ ሰው አንዳንዶቻችሁም እንደ እንስሳ ስትሠሩ አየኋችሁ፡፡›› አለ መምህሩ፡፡ ተማሪዎቹም ‹‹እንደ ሰው መሥራት ምንድን ነው? መለኪያውስ ምንድን ነው?›› ሲሉ ጠየቁት፡፡ መምህሩም እንዲህ አላቸው፡፡ ‹‹እንደ ሰው መሥራት ማለት ቢያንስ እነዚህን አራት ነገሮች ለማድረግ መቻል ነው፡፡
1.       ሥራን ሲሠሩ የሚያስከትለው ውጤት ዐውቆ መሥራት፡- ሥራን ስትሠሩ ምን ውጤት ያመጣል? ዓላማው ምንድን ነው? የእኔ ድርሻ ምንድን ነው? የሚያስከትለው በጎና ክፉ ነገር ምን አለ? የዚህ ሥራ ትልቁ ሥዕል ምንድን ነው? ብላችሁ አስቡ፡፡ ድንጋይ ፍለጡ ስለተባላችሁ፣ ጉድጓድ ቆፍሩ ስለተባላችሁ ወይም ልብስ ሥሩ ስለተባላችሁ በቻ አትሥሩ፡፡ እናንተ የምትሠሩት ሥራ የመጨረሻው ውጤቱ ምን እንደሆነ አስባችሁ ሥሩ፡፡ ያ ከሆነ ለጥራት ትጨነቃላችሁ፤ለውበት ታስባላችሁ፤ ሀገራችሁን፣ ሕዝባችሁን እያሰባችሁ ትሠራላችሁ፡፡ ራሳችሁን የታላቅ ዓላማ አካል እንጂ የአንዲት ቁራጭ ሥራ ሠራተኛ አታደርጉትም፡፡
2.     በጥንቃቄ መሥራት፡– ማንኛውም ሥራ የሚያመጣው በጎና ክፉ ነገር ይኖራል፡፡ ሰው ማለት ክፉን ነገር እየቀነሰ በጎን ነገር እያበዛ የሚሄድ ፍጡር ነው፡፡ የምትሠሩት ሥራ ጥፋት እንዳያስከትል፣ ጉዳት እንዳያመጣ፣ ሌሎችን እንዳይረብሽ፣ ሌሎች የሠሩትን እንዳያበላሽ፣ አስባችሁ ሥሩ፡፡ የእናንተን ሥራ መሥራትና የተሰጣችሁን መጨረሳችሁን ብቻ የምታዩ ከሆነ ሰዎች ሳትሆኑ እንስሳት ሆናችኋል ማለት ነው፡፡ እያሰባችሁ አይደለም ማለት ነው፤ ጡንቻችሁ እንጂ አእምሯችሁ አላደገም ማለት ነው፡፡ ለተሰጣችሁ ዕቃ፣ ለሰውነታችሁ፣ ለጤናችሁ፣ ለአካባቢያችሁ፣ ለሌሎች ሰዎች፣ ለእንስሳት፣ ለዕጽዋት፣ ጥንቃቄ አድርጉ፡፡ ስትሠሩ ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳታስከትሉ ተጠንቀቁ፤ ጉዳት ቢመጣ እንኳን ለመቀነስ ጣሩ፡፡ ግዴለሾ አትሁኑ፡፡ ግዴለሽ ሰው ሠራተኛ አይባልም፤ አጥፊ እንጂ፡፡
3.     ከሚጠበቀው በተሻለ መሥራት፡ የተሰጣችሁን ሥራ ከተሰጣችሁ በተሻለ መልኩ በመሥራት ከሚጠበቅባችሁ የበለጠ ውጤት አስመዝግቡ፡፡ ያንኑ የተሰጣችሁን ብቻ የምትሠሩ ከሆነማ ከእንስሳ ምኑን ተሻላችሁት፡፡ አንድን ዝሆን ዕቃ አሸክመን ብንልከው፤ በዝሆን ፍጥነት ተጉዞ ዕቃውን ያደርሳል እንጂ ፍጥነቱን ስለማሻሻልና በአቋራጭ መንገድ ስለ መጠቀም አያስብም፡፡ እናንተም እንዲሁ የተሰጣችሁን ብቻ የምትሠሩ ከሆነ ጠንካራ ልትሆኑ እንጂ ጎበዝ ልትሆኑ አትችሉም፡፡ ጎበዝ ማለት ስለ ተሻለ ነገር ለማሰብ የሚችል ማለት ነው፡፡
4.     በዕውቀት ላይ ተመሥርቶ መሥራት፡- ሥራን ስትሠሩ ዐውቃችሁት ሥሩ፤ መለካት ካለባችሁ በመለኪያ ተጠቀሙ፤ መመዘን ካለባችሁ በመመዘኛ ተጠቀሙ፤ እናውቀዋለን፣ ለምደነዋል ብላችሁ በግምት አትሥሩ፡፡ የተሰጣችሁ መመሪያ ካለ እርሱን ተከተሉ፤ የተሰጣችሁን ዝርዝር ሥራ ተመልከቱና የጎደለ ወይም የማያስፈልግ ካለ አስተክክሉ፤ መቼ ጀምራችሁ መቼ መጨረስ እንዳለባችሁ አስቡ፡፡ ምንም የተማራችሁና ዐዋቂዎች ብትሆኑ ስለምትሠሩት ሥራ መጀመሪያ ጠይቁና ተረዱ፤ አስፈላጊ መሣሪያ ሳትይዙ አትሥሩ፡፡ እናውቀዋለን ከምትሉ ላናውቀው እንችላለን ብላችሁ ለማወቅ ሞክሩ፡፡
እንስሳ ዕውቀት የለውም፤ የሚሠራውን በዕውቀት ተመርቶ አይሠራም፡፡ ስለ ጫኑት ይጫናል፤ ስለ ጎተቱት ይሄዳል፤ ስላረሱበት ያርሳል፡፡ እናንተ ግን ጉልበታችሁን አእምሯችሁ ይምራው፡፡ ይህ ነው እንደ ሰው መሥራት ማለት፡፡››
እኛስ እንዴት እየሠራን ነው? እንደ ሰው ወይስ እንደ እንስሳ?

ጸሐፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
—–
  “ሻዕቢያ” የሚለው ስም ሲነሳ የዑስማን ሳልህ ሳቤ ስምም አብሮ ይነሳል፡፡ በእርግጥም “ሻዕቢያ” የሚለውን ስያሜ በስራ ላይ ከማዋል ጀምሮ ድርጅቱን በሁለት እግሩ እንዲቆም ያደረገው ሳልህ ሳቤ በመሆኑ እርሱን እንደ ሻዕቢያ መስራች መመልከቱ አግባብ ነው፡፡ የ“ጀብሃ” ስም ሲጠቀስ ደግሞ ብዙዎች የሚያስታውሱት ሓሚድ ኢድሪስ አዋቴን ነው፡፡ ሆኖም ስህተት ነው፡፡ ሃሚድ ኢድሪስ አዋቴ በታሪክ የሚታወሰው ጀብሃ የትጥቅ ትግል በጀመረበት ጊዜ የመጀመሪያውን ጥይት የተኮሰ ሰው በመሆኑ ነው፡፡ “ጀብሃት ታሕሪረል ኤርትሪያ” (በአጭሩ “ጀብሃ”) ወይንም በትግርኛ ስሙ “ተጋድሎ ሓርነት ኤርትራ” (ተ.ሓ.ኤ) የሚባለው የኤርትራ አንጋፋ የፖለቲካ ድርጅት የተመሰረተው ግን ሃሚድ አዋቴ ትግሉን በባርካ በረሃ ከመጀመሩ ከአንድ ዓመት አስቀድሞ ነው፡፡ የድርጅቱ መስራቾች በአብዛኛው በካይሮ የሚማሩ ተማሪዎች ሲሆኑ የቀድሞው የኤርትራ ፓርላማ አባላት የሆኑ ጥቂት ሰዎችና ነጋዴዎችም ተቀላቅለቸዋል፡፡ ከመስራቾቹ መካከል ሙሐመድ ሳሊህ ሁመድ፣ ሙሐመድ አደም ኢድሪስ፤ ሰዒድ ሁሴን፣ ጣሓ ሙሐመድ ኑር፣ ወዘተ…ይጠቀሳሉ፡፡ ይሁንና እነዚህን ሰዎች አሰባስቦ የድርጅቱን መሰረት በመጣል ከፍተኛ ሚና የተጫወተው ሰው ኢድሪስ ገላውዴዎስ ይባላል፡፡

ኢድሪስ ዑሥማን ገላውዴዎስ በ1934 በከረን ከተማ አቅራቢያ በነበረችው “በይት ጀክ” በተባለች አነስተኛ ከተማ ነው የተወለደው፡፡ ኢድሪስ የቤኒአምር (ትግረ) ብሄረሰብ ነው፡፡  አባቱ ሀብታም ነጋዴ የነበሩ ከመሆኑም በላይ በተጨማሪም በምዕራባዊው ኤርትራ ሰፊ እርሻ ነበራቸው፡፡ በመሆኑም ኢድሪስ መደበኛ ትምህርቱን የጀመረው በ1942 የአባቱ እርሻ በሚገኝባትና በኢትዮጵያና ኤርትራ ድንበር ላይ ባለችው የአሊጊደር ከተማ ነው፡፡ በ1947 የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ወደ ከሰላ (ሱዳን) ተላከ፡፡ የፖለቲካ ተሳትፎውንም የጀመረው በከሰላ ከተማ በነበረበት ወቅት ነው፡፡

  እንደሚታወቀው በዚያ ዘመን ኤርትራ በእንግሊዞች አስተዳደር ስር ነበረች፡፡ በዘመኑ ኤርትራ ነጻ መውጣት አለባት የሚሉና ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ትቀላቀል የሚሉ ሁለት ጎራዎች ነበሩ፡፡ የመጀመሪያውን ጎራ የሚያንቀሳቅሰው “ራቢጣ አል-ኢስላሚያ” የሚባል ፓርቲ ሲሆን ሁለተኛውን ጎራ የሚመራው ደግሞ “ማሕበር ሀገር ፍቕሪ” የሚባለው ቡድን ነው፡፡ የኢድሪስ አባት የራቢጣ አባል የነበሩ እንደመሆናቸው “ኤርትራ ነጻ ትሁን” በማለት ከሼኽ ሱልጣን ኢብራሂም ጋር ብዙ ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ኢድሪስም በአባቱ ላይ ባየው የትግል መንፈስ በጣም ተማረከ፡፡ መሆኑም “የራቢጣ” የወጣቶች ክንፍ አባል ሆነ፡፡

ኢድሪስ በ1951 ትምህርቱን በከፍተኛ በማዕረግ በማጠናቀቁ ከካይሮ ዩኒቨርሲቲ የስኮላርሺፕ እድል አገኘ፡፡ ወደ ዩኒቨርሲቲው ገብቶም የህግ ትምህርት ማጥናት ጀመረ፡፡ ከዓመት በኋላም የኤርትራ ተማሪዎች ማህበር ሲመሰረት የማህበሩ ሊቀመንበር ሆኖ ተመረጠ፡፡ ኢድሪስ በዚህ ማህበር ኤርትራዊያ ስደተኞችን ለማሰባሰብ በሰፊው ተጠቅሞበታል፡፡

   *****

ኢድሪስና ጓዶቹ በስደት ላይ ሆነው የሀገር ቤቱን ሁኔታ በቅርበት ይከታተሉት ነበር፡፡ በተለይም የተባበሩት መንግሥታት ለኤርትራ የሰጠው የፌዴሬሽን መብት እየተሸረሸረ ነው በማለት ተቃውሞአቸውን ያሰሙ ነበር፡፡ በ1957 የኤርትራ ሰንደቅ ዓላማ ታገደ፡፡ ከዓመት በኋላም ትግርኛና ዐረብኛ የስራ ቋንቋ መሆናቸው አብቅቶ በአማርኛ ሲተኩ ደግሞ “ሐረካ” (Eritrean Liberation Movement) የተባለው ድርጅት በሚስጢር ተመሰረተ፡፡ ”

  የሐረካ ዓላማ ፌዴሬሽኑ በተቀመጠለት ደንብ መሰረት እንዲሰራ መጠየቅና ለዚህም እስከ መጨረሻው መታገል ነበረ፡፡ በተጨማሪም የትጥቅ ትግልን እንደ አማራጭ አልወሰደም፡፡ ይህ ድርጅት በካይሮ የነበሩትን ተማሪዎች በአባልነት ለማሳተፍ ሲሞክር ግን ተቃውሞ ገጠመው፡፡ እነ ኢድሪስ ገላውዴዎስ የሐረካ ዓላማና የትግል ስልት አዋጪ መስሎ ስላልታያቸው ድርጅቱን እንደ ከንቱ ማህበር ነበር ያዩት፡፡

   *****

 በ1960 ነው፡፡ ኤርትራዊያን በፌዴሬሽኑ አሰራር ሙሉ በሙሉ ተስፋ ቆርጠዋል፡፡ በርካቶቹም በአጼ ኃይለ ሥላሤ መንግሥት የተሾሙት ቢትወደድ አስፋሓ ወልደሚካኤል ለባርነት ሊዳርገን ነው እያሉ መነጋገር ጀምረዋል፡፡ ከዓመት በፊት የኤርትራ ሰራተኞችና ተማሪዎች ሰላማዊ ሰልፍ ባደረጉበት ወቅት የጸጥታ ሃይሎች በወሰዱት እርምጃ ሳቢያ በሀገር ቤት ተቃውሞ ማድረጉም ብዙ እንደማያራምድ አምነዋል፡፡ በዚህም የተነሳ በርካቶች የመንግሥትና የፓርላማ ስልጣናቸውን በመተው ወደ ውጪ መሰደድ ጀመሩ፡፡ እነዚህ ስደተኞች ካይሮ ከሚገኙት ተማሪዎች ጋር ከተቀላቀሉ በኋላ ስለ ድርጅት ምሥረታ መነጋገር ጀመሩ፡፡ ውይይቱም ፍሬያማ ሆኖ በመውጣቱ በጁላይ ወር 1960 ከነጻነት በስተቀር የፌዴሬሽንን ፎርሙላ የማይቀበል አዲስ ድርጅት ተመሰረተ፡፡ ይህም ድርጅት “ጀብሃት ታሕሪረል ኤሪቲሪያ” ወይንም “ተጋድሎ ሓርነት ኤርትራ” (ተ.ሓ.ኤ) ተብሎ ተሰየመ፡፡
     
   “ጀብሃ” ሲመሰረት የድርጅቱ ሊቀመንበር ሆኖ የተመረጠው የቀድሞ የፓርላማ አባል የነበረው ኢድሪስ ሙሐመድ አደም ነው፡፡ የድርጅቱ ዋና ጸሐፊ ደግሞ ኢድሪስ ገላውዴዎስ ነው፡፡ የድርጅቱ ላዕላይ ምክር ቤት (Supreme Council) አባላት ኢድሪስ ሙሐመድ አደም፤ ኢድሪስ ገላውዴዎስ፣ ሙሐመድ ሳሊሕ አሕመድ፣ ዑሥማን ኢድሪስ ኪያር፣ ሙሐመድ ሰዒድ ኪያር፣ ሲሆኑ ከአንድ ዓመት በኋላም ዑሥማን ሳልህ ሳቤ ተቀላቅሎአቸዋል፡፡
  
 “ጀብሃ” ከተቋቋመ በኋላ በምዕራብ ኤርትራ በረሃ በተበታተነ ሁኔታ ከሚታገሉት እነ ሃሚድ ኢድሪስ አዋቴን መከሳሰሉ ፋኖዎች ጋር ተገናኘ፡፡ ለአዋቴም የግንባሩን ወታደራዊ ክፍል እንዲመሩ ውክልና ሰጣቸው፡፡ በመስከረም 1/1961 በሃሚድ አዋቴ አዝማችነት በጀብሃ ስም የትጥቅ ትግሉ ተጀመረ፡፡ ሃሚድ ኢድሪስ አዋቴ ከአንድ ዓመት በኋላ ሲገደሉ ደግሞ የወታደራዊውን ክንፍ የመምራቱ ስልጣን ለኢድሪስ ገላውዴዎስ ተሰጠ፡፡ በዚህም የኢድሪስ ገላውዴዎስ መቀመጫ ከካይሮ ከተማ ወደ ሱዳኗ ከሰላ ከተማ ተቀየረ፡፡

ኢድሪስ ገላውዴዎስ ከሰላ ከደረሰ በኋላ በሱዳን ውስጥ የሚገኙ ኤርትራዊያን ስደተኞችን እያሰባሰበ ወታደራዊ ስልጠና እንዲያገኙ አድርጓል፡፡ በኋላ ላይ ደግሞ ለድርጅቱ ድጋፍ ለማግኘት ወደ ልዩ ልዩ ሀገራት ተጉዟል፡፡ በዚህም ውጤት አግኝቶበታል፡፡ ለምሳሌ በ1967 ወደ ቻይና ተጉዞ እነ ማኦ ዜዱንግን በማሳመን ለጀብሃ የመሳሪያና የስልጠና ድጋፍ አስገኝቷል (በዚያን ጊዜ ወደ ቻይና ሄደው ስልጠና ካገኙት መካከል አንዱ የአሁኑ የኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ናቸው)፡፡ ወደ ኩባ በመሄድም የጀብሃ ተዋጊዎች የፓራ-ኮማንዶ ስልጠና እና የመሳሪያ ድጋፍ እንዲያገኙ አድርጓል፡፡ ከሶሪያና ከኢራቅም ብዙ እርዳታ አስገኝቷል፡፡ የእስያ-አፍሪቃ የወዳጅነት ኮንፈረንስ በተካሄደበት ጊዜም ድርጅቱን በመወከል ተሳትፏል፡፡

   *****

ከዚህ ቀደም በጻፍኳቸው ጽሑፎች እንደገለጽኩት “ጀብሃ” የሚባለው ድርጅት በኤርትራዊያን ክርስቲያኖች ላይ ውገና ያካሄድ ነበር፡፡ የዚህም መነሻ “ለኃይለ ሥላሤ መንግሥት አሳልፈው የሸጡን ክርስቲያኖቹ ናቸው” የሚለው የተሳሳተ ፍረጃው ነው፡፡ እርግጥ የኃይለ ሥላሤ መንግሥት ኤርትራዊያን ሙስሊሞች ወደ ስልጣነ-መንግሥቱ እንዳይቀርቡ አድርጓል፡፡ በመንግሥት ስልጣንም ሆነ በፓርላማው ውስጥ የተሰገሰጉት በአብዛኛው ደገኛ ክርስቲያኖች ነበሩ፡፡ ይሁንና የእነዚህ ጥቂት ሰዎች ምግባር ሁሉንም የኤርትራ ህዝበ ክርስቲያን አይወክልም፡፡ ስለዚህ ጀብሃ ኤርትራዊያን ክርስቲያኖችን በጥርጣሬ ማየቱና በድርጅቱ ውስጥ የነበሩትንም እያሳደደ መምታቱ ትክክል አልነበረም፡፡ ድርጅቱንም ለውድቀት ያበቃውም ይህ የውገና አቋሙ ነው፡፡

  ይህ ወገንተኛ አቋም የሁሉም የጀብሃ አባላት አቋም አልነበረም፡፡ በመሆኑም በ1969 በወታደራዊ ግንባር የተሰለፉት አባላት ፓርቲው ራሱን እንዲፈትሽና እንዲያሻሽል የሚቀሰቅሰውን የአዶብሃ ኮንፈረንስ ጠሩ፡፡ በኮንፈረንሱ ማጠቃለያም ድርጅቱ ራሱን እስካላሻሻለ ድረስ ካይሮ የሚገኘው ላዕላይ ምክር ቤት የሚያወጣቸውን መመሪያዎች እንደማይቀበሉ አስታወቁ፡፡ የካይሮው ምክር ቤት ኮንፈረንሱን በህገ-ወጥነት ፈረጀው፡፡ ሆኖም በከሰላ የሚገኘው ኢድሪስ ገላውዴዎስ የተነሱትን ጥያቄዎች እንደሚቀበል አስታወቀ፡፡ በዚህም የተነሳ ኢድሪስ ገላውዴዎስ ከአመራሩ ጋር ተጋጨ፡፡ በድርጅቱ ውስጥ የነበረውንም ከፍተኛ ስልጣን አጣ፡፡ ይሁንና የወታደራዊ ኮሚቴ ሊቀመንበርነቱን አልተወውም፡፡
 
 ኢድሪስ ገላውዴዎስ የጀብሃን ወታደራዊ ክንፍ በሚመራበት ወቅት ነበር በዑሥማን ሳልህ ሳቤ እና በኢሳያስ አፍወርቂ የሚመሩት ቡድኖች ከድርጅቱ ተንገጥለው የወጡት፡፡ የጀብሃ አመራር እነዚህን ቡድኖች በወታደራዊ ጥቃት የማጥፋት ውሳኔ አሳለፈ፡፡ ኢድሪስ ገላውዴዎስ ግን ውሳኔው ኤርትራዊያንን የበለጠ ይከፋፍላል በማለት ተቃወመው፡፡ ወታደራዊ ዘመቻዎችንም እንደማያስፈጽም ለድርጅቱ መሪዎች ቁርጡን ነገራቸው፡፡ በዚህም የተነሳ የድርጅቱ መሪዎች ኢድሪስን ከወታደራዊ መሪነቱ አስነሱትና በውጪ ጉዳይ ላይ ሾሙት፡፡

ኢድሪስ ገላውዴዎስ ድርጅቱን በውጪ ጉዳይ ሃላፊነት በሚመራበት ወቅት ድርጅቱ በጣም እየተዳከመ ነበር፡፡ ቢሆንም ኢድሪስ በውጪው ዓለም የድርጅቱን ስም የሚያስጠሩ ስራዎችን ሰርቷል፡፡ ለምሳሌ እ.ኤ.አ. በ1978 ታላቋ ሶቭየት ህብረት ጀብሃ ከደርግ መንግሥት ጋር እንዲወያይ በፈጠረችው መድረክ ላይ ድርጅቱን ወክሎ ተገኝቷል፡፡

 ከጥቂት ዓመታት በኋላ ጀብሃ ፍርስርሱ ወጣ፡፡ በኤርትራ ምድር የቀረው ትርፍራፊ ጦሩ በሻዕቢያ ተደመሰሰ፡፡ ድርጅቱም በስም ያለ በተግባር ግን የሌለ ሆኖ ቀረ፡፡ ይህንን የተመለከተው ኢድሪስ ገላውዴዎስ በድርጅቱ መሪዎች ላይ ከፍተኛ ሂስ ጽፎ አቀረበ፡፡ ድርጅቱ ሁሉንም ኤርትራዊያን በእኩል ሁኔታ አለማየቱና ዲሞክራሲያዊ አሰራር የሌለው መሆኑ ለሞት እንዳበቃው አሰመረበት፡፡ በመሆኑም ከጀብሃ አመራር ራሱን አገለለ፡፡

   በ1991 ሻዕቢያ ኤርትራን ሙሉ በሙሉ ሲቆጣጠር ኢድሪስ ገላውዴዎስ ለአዲሱ መንግሥት እውቅና እንደሚሰጥ አስታወቀ፡፡ እነ ኢሳያስ አፈወርቂም ወደ ሀገር መጥቶ በስራ እንዲረዳቸው ጥሪ አቀረቡለት፡፡ ኢድሪስም ግብዣውን ተቀብሎ ወደ ሀገር ውስጥ ገባ፡፡ ከ1991-1993 በነበሩት ዓመታትም ከዶ/ር በረከት ሃብተ ሥላሴ ጋር የሪፈረንደም ኮሚሽን ሃላፊ ሆኖ ሰራ፡፡ በተከታዮቹ ዓመታት ደግሞ የህገ-መንግሥት አርቃቂ ኮሚሽን አባል ሆኖ በመስራት ላይ እያለ እ.ኤ.አ በ1998 አረፈ፡፡ የቀብር ስርዓቱም በብሄራዊ ደረጃ ተፈጸመለት፡፡

   *****

   የጀብሃ አባላት ለኢድሪስ ገላውዴዎስ ሁለት ዓይነት እይታዎች ነው ያላቸው፡፡ ኢድሪስ ድርጅቱን ለመመስረትና የወታደራዊ ክንፉን መሰረት ለመጣል ያደረገውን አስተዋጽኦ በበጎ ዐይኑ ይመለከቱታል፡፡ ከዚያ በኋላ ግን አድርባይ ሆኖ ድርጅቱን ከድቷል በማለት ይኮንኑታል፡፡ የሻዕቢያ አባላትና ደጋፊዎች ግን ኢድሪስ ገላውዴዎስን በበረሃ ውስጥ የተገኘ ተክል አድርገው ነው የሚያዩት፡፡ “ጀብሃ ከውጥኑ ጀምሮ በርሱ ቢመራ ኖሮ ኤርትራዊያን እርስ በራሳቸው አይጋደሉም ነበር” በማለትም ያምናሉ፡፡ ሐቁ የትኛው እንደሆነ ታሪክ ነው የሚፈርደው፡፡ ከብዙ በጥቂቱ ግን ኢድሪስ ገላውዴዎስ ማለት ከላይ የተገለጸው ሰው ነው፡፡
—–
ምንጮች

1.      www.awate.co,

2.     www.asmerino.com

3.     Tekste Negash: Ethiopia and Eritrea: The Federal Experience, 1997

የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ ኢህደግ በመጪው ግንቦት ወር የሚካሄደውን ምርጫ ነጻና ሰላማዊ ከማድረግ ጋር በተያያዘ የአስልጣኞች ስልጠና ለከፍተኛ አመራሮቹ እየሰጠ ነው።

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የየመን አገር ውስጥ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው ኢትዮጵያውያኑ  ሞቻ በሚባለው የወደብ ከተማ አቅራቢያ  ሲደርሱ የተሳፈሩበት ጀልባ በመስጠሙ 24ቱም አትዮጵያውያን አልቀዋል። የሁሉም አስከሬን መገኙቱን ባለስልጣኑ ሲናገሩ፣ የተረፉ ካሉም በማፈላለግ ላይ መሆኑን አስታውቋል። ባለፈው ወር ከ79 ያላነሱ ኢትዮጵያውያን ባህር ላይ ማለቃቸው ሲታወስ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ባህር ላይ የሞቱ ኢትዮጵያውያንን ቁጥር …

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ተማሪዎች ኢህአዴግን እንዲመርጡ በሚል በግዳጅ በተዘጋጀው የፖለቲካ ስልጠና ላይ ተማሪዎች ፈታኝ የሆኑ ጥያቄዎችን አስተያየቶችን ሰጥተዋል ። ኢህአዴግ እነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋን የመሰሉ ሰዎችን አሸባሪዎች ማለቱ ትክክል አለመሆኑን የሚገልጹት ተማሪዎች፣ ኢህአዴግን የሚበልጡት በመሉ  አሸባሪ እያለ እንደሚፈርጃቸው ተናግረዋል ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የሚኖርበት ቤት 400 ሺ ብር እንደሚከፈልበት የተናገሩት ተማሪዎች፣ …

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ ከመላው አገሪቱ ለተውጣጡ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች መጪውን ምርጫ በተመለከተ ስልጠና እየሰጠ ሲሆን፣ ከስልጠናው በፊት ማንኛውም ባለስልጣን ስልክ ይዞ መግባት እንደማይችል ጥብቅ የሆነ መልእክት በመተላለፉ፣ ሁሉም ባለስልጣናት ስልካቸውን መኪናቸው ውስጥ እየተዉ ወይም ለሹፌሮቻቸው እየሰጡ መግባታቸው ታውቋል። ወደ ስብሰባው የሚገባ ሰው ማንኛውንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን መያዙንና አለመያዙን ለማረጋገጥ  …

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ጥቅምት ወር በጎንደር፣ በትግራይና በጎጃም አካባቢዎች የተያዙ የተቃዋሚ ድርጅት አመራሮች ፍድር ቤት ቀርበው የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል። ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው የሰማያዊ፣ የአንድነትና የመኢአድ ፓርቲዎች የዞን አመራሮች  ታህሳስ 21 ቀን 2007 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት ቀርበው ፣ አመራሮቹ ለ3ኛ ጊዜ የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል፡፡ “ፖሊስ ምርመራየን አልጨረስኩም፣ …

ታኀሳስ ፳፩(ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኦሮምያ ክልል  በተለይም በአምቦ፣ በአለማያና በሌሎችም ዩኒቨርስቲዎች ለተፈጸሙ ግድያዎችና  በሌሎች  አካባቢዎች ለደረሱ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተጠያቂ የሆኑት ኮማንደር ፣ ታህሳስ 17 ቀን 2007 ዓም ሲያሽከረክሩት የነበረው መኪና ተገልብጦ ከ3 ጠባቂዎቻቸው ጋር በሂርናና አሰበ ተፈሪ መካከል በሚገኝ አንድ ገደላማ ቦታ ላይ ገብተው ህይወታቸው ወዲያውኑ አልፎአል። ኮማንደሩ የተሳፈሩበት …

የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ ኢሀደግ በመጪው ግንቦት ውር የሚካሄደውን ምርጫ ነጻና ሰላማዊ ከማድረግ ጋር በተያያዘ የአስልጣኞች ስልጠና ለከፍተኛ አመራሮቹ እየሰጠ ነው።

(አቶ እያስፔድ ተስፋዬ የሰማያዊ ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚና የወጣቶች ክፍል ሃላፊ ናቸው። በቅርቡም ከሚሰሩበት መስሪያ ቤት/ባንክ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው ምክንያት ተባረዋል። በነገረ ኢትዮጵያ ብዙ ጊዜ ጽሁፎችን የሚያቀርቡ ወጣት ፖለቲካኛ ናቸው። በጋራ ህዝቡን ማታገል እንደሚገባ በመገልጽ በተለትም ለሰማያዊና ለአንድነት ፓርቲ ጥሩ ያቀረቡበት ጽሁፍን ያንብቡ) ለውጡ ይመጣል! ጥያቄው ግን ተዘጋጅተናል ወይ? ————————————————- ስለ 1966ቱ ለውጥ ብዙ ተብሏል፡፡ በለውጡ ወቅት […]

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

የአንድነት፣ የሰማያዊና የመኢአድ አባላት ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ! ለጥር 19/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው! በሽብር ክስ ተጠርጥረው የመኢአድ፣ የሰማያዊና የአንድነት አመራሮች በዛሬው እለት አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡ ሲሆን የአንድነት ፓርቲ ጠበቃ አቶ ገበየሁ እንደገለፁት ከዚህ ቀደም በነበረው ሰነድ፣ አሻራ እና ቃላቸውን ወስደዋል እንዲሁም አስረላጊ ምርመራም አካሂደዋል፡፡ ተጨማሪ ምንም ምርመራ ያደረጉት ነገር ስላልተገኘ ደምበኞቼን የዋስትና መብታቸው […]

አምና ሊባል አንድ ቀን የቀረዉ ጎርጎሪዮሳዊዉ 2014ዓ,ም በጤናዉ ረገድ ዓለም ያደናገጡ በሽታዎች የተከሰቱበት ነበር። በዚህ ዓመት ከታዩት በሽታዎች ሳርስ፣ ማርቡርግ እና የወፍ ጉንፋን በየተቀሰቀሱበት አካባቢ ሲወሰኑ፤ ኤቦላ ግን መነሻዉ ምዕራብ አፍሪቃ ሃገራት ቢሆንም የተሐዋሲዉ ስርጭት በርካታ ቦታዎችን ነካክቷል።

ጥር
በልዩ ቅናሽ የመጻሕፍት ሽያጭ ወር
አግዮስ ኅትመትና ጠቅላላ ንግድ ሥራ ሐላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ያሳተማቸውን
የዲያቆን ዳንኤል ክብረትና የሌሎችንም መጻሕፍት፤ የንባብ ባህላችንን ለማሳደግ እና አንባብያንን ለማበረታታት፤ ከ25% እስከ 50% (ከሃያ አምስት እስከ ሃምሣ በመቶ) ቅናሽ በማድረግ፤
ከጥር 1 እስከ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ባሉት ቀናት ውስጥ ለአንድ ወር
የሚቆይ ልዩ የመጻሕፍት ቅናሽ ሽያጭ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል፡፡
ቦታ፡- አግዮስ መጻሕፍት መደብር
አድራሻ፡- መገናኛ ለም ሆቴል አጠገብ፣ ማትያስ ሕንፃ ምድር ቤት (G – 06)
             ስልክ ቁጥር፡- 011 663 9902 / 0930098254
በተለይ ‹አራቱ ኃያላንን ላልገዛችሁ ይኼ መልካም አጋጣሚ ነው

ውድ አንባብያን መጻሕፍቱን በአዲስ አበባ ሌሎችም አካባቢዎች በወኪሎቻችን አማካኝነት በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ፤
      ለጉርድ ሾላ፣ ሲ ኤም ሲ ሚካኤል እና አካባቢው፤
መዝገቡ መጻሕፍት መደብር፤ ጉርድ ሾላ ቴሌ ፊት ለፊት፣ ዲ ኤም መንጃ ፈቃድ ት/ቤት ሕንፃ ሥር፤
                               ስልክ ቁጥር፡- 0912 951732
      አራት ኪሎ / ቅድስት ማርያም / አካባቢ፤
ፍሬው መጻሕፍት መደብር፤ ዐፄ ናዖድ ት/ቤት አጠገብ ስልክ ቁጥር፡- 0911 685232

      ፒያሳ አራዳ ጊዮርጊስ አካባቢ፤
ጌታቸው መጻሕፍት መደብር፤ አራዳ ጊዮርጊስ ጤና ጣቢያ ፊት ለፊት፤ ስልክ ቁጥር፡- 0911 469954
መኮንን መጻሕፍት መደብር፤ ስልክ ቁጥር፡- 0913 108312

ከትምህርት ቤትና ከመጻሕፍት ያገኙት ዕውቀት አራት ዓይና ያደረጋቸው ሊቁ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታዬ በተጠያቂነት ደረጃ የሚገኙና አገልግሎታቸውም ሙሉ ነበር፡- ቀዳሽና መዘምር፤ ጋዜጠኛና ሰባኬ ወንጌል፤ ጸሐፊና ተርጓሚ፤ አስተዳዳሪና መምህር፤ የአውራጃ አብያተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ፤ ኤርትራን ጨምሮ የአህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የስምንት መምሪያዎች ምክትልና ዋና ሓላፊ፡፡ ሊቁ በሓላፊነት በተመደቡባቸው ቦታዎች …

ለውጡ ይመጣል! ጥያቄው ግን ተዘጋጅተናል ወይ? ነው፡፡
————————————————-
ስለ 1966ቱ ለውጥ ብዙ ተብሏል፡፡ በለውጡ ወቅት የነበሩትን ሰዎችም ሆነ ሌሎቹን የሚያስማማ አንድ ነገር ቢኖር የለውጡ ግብታዊነት እና ለውጡን ሊሸከም የሚችል ድርጅት በወቅቱ አለመኖሩ ነው፡፡ ዛሬ ላይ ቆመን ለውጡ ገና ነው ብለን ብንዘናጋ እንደ ኃይሌ ፊዳ ልንሳሳት የምችልባቸው አጋጣሚዎች ብዙ ይመስሉኛል (ሀይሌ ፊዳ ከብርሀነ መስቀል ጋር ባደረጉት ውይይት ለውጡ ገና ነው ብዙ አመታትንም ይፈልጋል ብሎ ነበረ)፡፡ ከዚያ ይልቅ ለውጡን ለመቀበል በሚያስችል ተክለ ሰውነት ላይ ለመገኘት ምን እናድርግ የሚለው ላይ መዘጋጀት አስፈላጊ ነው፡፡

ብዙዎች በመኢሶን እና በኢህአፓ መካከል የነበረው ልዩነት ያለፈውን ትውልድ ዋጋ እንዳስከፈለው ሲናገሩ ይደመጣሉ፡፡ አንዳንዶች የሁለቱ ልዩነት የእናቸንፋለን እና የእናሸንፋለን የቃላት ጨዋታ ነበረ ሲሉ በሚያነሱት ሀሳብ ባልስማማም (ልዩነታቸው መሰረታዊ ነበር ብዬ ስለማምን) የሁለቱ ልዩነት ግን ትውልዱን ዋጋ ማስከፈሉን የማይቀበል ማንም ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡

ስለሁለቱ ልዩነት ሲነሳ ቢያንስ በሁለት ወቅቶች ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡
የመጀመሪያው ከለውጡ በፊት የነበረው እና ከለውጡም በኋላ እስከተወሰነ ድረስ አብሮ የዘለቀው የሁለቱ ፓርቲዎች የመደጋገፍ ጊዜ ነው፡፡ በአልጀርስ የነበረው የኢህአድ/ኢህአፓ መስራች ቡድን ከሀይሌ ፊዳው የመኢሶን መስራች ቡድን ጋር በአንዳንድ ነጥቦች ሳይስማሙ ቢለያዩም ልዩነታቸው ሰፊ የሚባል አልነበረም፡፡ ለዚህም ማሳያው የኢህአፓ ልሳን የነበረችው የዴሞክራሲያ የመጀመሪያ ዕትሞች እና የመኢሶን ልሳን የነበረችው የሰፊው ህዝብ ድምፅ ጋዜጣ የመጀመሪያ ዕትሞች በይዘት መመሳሰል እና በሀሳብ መደጋገፍ ነው፡፡ ይህ ሂደት እነ ሀይሌ ፊዳ ከውጪ ወደ ሀገር ቤት እስኪገቡ ድረስ የቀጠለ እንደነበርም ታሪክ መዝግቦ ያስቀመጠው ሀቅ ነው፡፡

ሁለተኛው ወቅት ደግሞ ለውጡ ከመጣ በኋላና እነ ሀይሌ ፊዳ ሀገር ቤት ከገቡ በኋላ ያለው እና በሁለቱ ድርጅቶች መካከል ያለው ልዩነት መሰረታዊ እየሆነ የሄደበት እና በጣም የተለጠጠበት ወቅት ነው፡፡ በዚህ ወቅት በመኢሶን እና በኢህአፓ አመራሮች መካከል ግንኑነት ለማድረግ የተሞከረ ቢሆንም (ለአብነትም ዶ/ር ተስፋዬ ደበሳይ ከዶ/ር ሀይሌ ፊዳ ጋር፤ ነገደ ጎበዜ ከአለማየሁ ሀይሌ(ደርግ ውስጥ ሰርጎ የገባ የኢህአፓ ሰው ነው ይባል ነበር) ጋር ተገናኝተው አውርተዋል) ከረፈደ በኋላ የተደረገ ውይይት በመሆኑ ያመጣው ለውጥ አልነበረም፡፡

በእኔ እይታ ለሁለቱ ድርጅቶች አለመስማማት አቢዩ ምክንያት ከለውጡ በኋላ ኢህአፓ ሰፊ ህዝባዊ መሰረት (ማስ ቤዝ) ማግኘቱ በመኢሶን በኩል ለደርግ ሂሳዊ ድጋፍ እየሰጡ መቀጠል ይሻላል ወደሚለው ሀሳብ እንዲሄዱ የገፋቸው ይመስለኛል፡፡ ከመነሻው የነበራቸውን አነስተኛ ልዩነት አጥብበው በጋራ ቢሄዱ ኖሮ አንዳቸው ተለይቶ ህዝባዊ መሰረት የሚገነባበት እና ሌላኛቸው ህዝባዊ መሰረት ለመያዝ ከወታደሩ ጋር የሚሰለፍበት ሁናቴ አይኖርም ነበር፡፡

ለማንኛውም ይህን ያነሳሁት በታሪኩ ላይ ለመነታረክ ሳይሆን ዛሬም ከታሪክ ሳንማር ያለፈውን ስሀተት እንዳንደግም ካለኝ ፍርሀት ነው፡፡
ዛሬ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተለይም ሰማያዊ እና አንድነት በጋራ ሆነው ለሚመጣው ለውጥ ራሳቸውን ካላዘጋጁ በስተቀር ከለውጡ በኋላ ልዩነታቸውን አጥብበው ለውጡ ተፈጥሯዊ ይዘቱን ጠብቆ ለሀገር በሚጠቅም መልኩ ለማስቀጠል ይችላሉ ማለት ዘበት ነው፡፡ ልዩነታቸውን አሁን ላይ ማጥበብ እና በጋራ መቆም ካልቻሉ ከለውጡ በኋላ እንደ ጠላት የሚተያዩበትም እድል እጅግ በጣም የሰፋ ሊሆን እንደሚችል እገምታለሁ፡፡ በተለይም ደግሞ ለውጡን ተከትሎ ከሁለት አንዳቸው ከፍ ያለ መስዋዕትነት የከፈሉ እንደሆነ፡፡

የተቃዋሚዎች በአንድ መቆም ለለውጡ ተዘጋጅቶ ለመጠበቅ ብቻ ሳይሆን ለውጡን ለማምጣትም የተሻለው እና አጭሩ መንገድ ነውና የየፓርቲዎቹ አመራሮች(በተለይም የሰማያዊ እና የአንድነት) ዛሬ ነገ ሳይሉ ቁጭ ብለው በመነጋገር ወደ አንድ የሚመጡበትን እና በጋራ ህዝቡን የሚያታግሉበትን መንገድ እንዲፈጥሩ ጥሪዬን አቀርባለሁ ፡፡
Image

በደብረማርቆስ፣ ባሶ ሊበንና ሞጣ መረር ያለ ተቃውሞ ተነስተዋል::
በጎጃም የመሰናዶ ተማሪዎች የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ላይ ተቃውሙ አሰሙ
በምስራቅ ጎጃም ዞን ሁሉም ትምህርት ቤቶች የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል መሰናዶ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቁመው እንዲወስዱ የተደረገውን የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠና ላይ ተቃውሞ ማሰማታቸውን ምንጮን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በስልጠናው ወቅት የህዝቡ አስተሳሰብ፣ የግል ሚዲያ፣ ተቃዋሚዎች ለኢትዮጵያ እድገት ጠንቅ ተደርገው የቀረቡ ሲሆን ተማሪዎች ይህንን አቀራረብ ተቃውመውታል፡፡ በአንጻሩ ከወራት በፊት ስልጠናውን የወሰዱት መምህራንም ዳግመኛ ስልጠናውን እንዲወስዱ ተደርገዋል እየጠደረጉ ሲሆን ዝምታን መምረጣቸው ተገልጾአል፡፡

ተማሪዎቹ ‹‹የምርጫ ቅስቀሳ ከሆነ ለተቃዋሚዎችም ይፈቀድ፣ ለምን ለግጭት የሚጋብዙ ቅስቀሳ ትቀሰቅሳላችሁ፣ የኢህአዴግ ፖሊሲ ምሁራንንም ጭምር ለስደት የዳረገ ነው፣ ከቻይና እና ከኮሪያ የሚያስተሳስረን የታሪክም ሆነ የባህል መሰረት የለንም፣ ኢህአዴግ 23 አመት ያልተገበረውን ዴሞክራሲ ሊያስተምረን አይችልም›› የሚሉ ጥያቄዎችንና አስተያየቶችን አንስተዋል፡፡

በስልጠናው ወቅት ተቃውሞዎች እየተነሱ ሲሆን በተለይም ደብረማርቆስ፣ ባሶ ሊበንና ሞጣ ላይ ተማሪዎቹ ‹‹ኢህአዴግ ሌላ፣ ኢህአዴግ ሌባ›› የሚል ጩኸት በማሰማታቸው ሲሰለጥኑበት ከነበረው ሰፊ አዳራሽ 20፣ 20 ሆነው በየክፍሉ እንዲሰለጥኑ ተደርገዋል፡፡ በተለይ በደብረማርቆስ ከተማ በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹ የካድሬ ስልጠና አንሰለጥንም በማለት መረር ያለ ተቃውሞ እያሰሙ እንደሚገኙ ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡


ታኅሣሥ 19 ቀን 2007 ዓም በቤተ ክርስቲያን ዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ከታወቁት ሊቃውንት መካከል አንዱን አጥተናል፡፡ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየን፡፡ ስለ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን በመቆርቆር፣ በማስተማርና በመጻፍ የምናውቃቸው፤ ቤተ ክርስቲያኒቱን ከጫፍ እስከ ጫፍ ያገለገሉ፤ በተለይም ለወጣቱ ትውልድ ጥያቄዎቹን በመመለስና አስረግጠውም በማስረዳት የምናደንቃቸው ነበሩ፡፡
ዜማ፣ አቋቋም፣ የአማርኛ ሰዋስው፣ ቅኔና የግእዝ አገባብ፣ ብሉይ፣ ሐዲስ፣ ነገረ መለኮት፣ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ በዘመናዊ ትምህርት እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የተማሩ መሆናቸውን ስናይ፤ በአንባቢነታቸው ጥንታውያንና ዘመናውያን መጻሕፍትን የሚያገላብጡ ብቻ ሳይሆኑ በላዔ መጻሕፍት እንደነበሩ በሌሎቹ ሊቃውንት ሲመሰከርላቸው፤ በምሥራች ድምጽ ሬዲዮ ትምህርት በመስጠት፣ በታሪክና ድርሰት ክፍል ለዐሥር ዓመታት በማገልገል፤ የመዝሙር ክፍልን በመምራት፣ የዜና ቤተ ክርስቲያንን በምክትልና በዋና አዘጋጅነት  በማገልገል፣ እንዲያውም ጋዜጣውን የጋዜጣ መልክ በማስያዛቸው በ1962 ዓም መሸለማቸውን  እያዘከርን የተጓዙበትን የዕውቀት ጎዳና ስንመረምር ያጣነው አንድ ሰው ብቻ ባለመሆኑ፡-
አራት ሰው ሞተ ተቀበረ ዛሬ
ድጓ ጾመ ድጓ መዋሥዕት ዝማሬ
ተብሎ ለሊቁ የተገጠመው ሙሾ ለእርሳቸውም ይስማማቸዋል እንላለን፡፡ 

የየረርና ከረዩ አውራጃ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ፣ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ዋና ጸሐፊ፣ የቀበና አቦ አስተዳዳሪ፣ የካህናት አስተዳደር መምሪያ ጸሐፊ፣ የኤርትራ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ፣ የከፋ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ፣ የትምህርትና ማሠልጠኛ መምሪያ ኃላፊ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ፣ የአስተዳደር መምሪያ ኃላፊ፣ የቁጥጥር አገልግሎት ኃላፊ፣ የበጀትና ንብረት መምሪያ ኃላፊ፣ የስብከተ ወንጌል መምሪያ ኃላፊ፣ የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህት ቤት ምክትል ዲን፣ እየሆኑ ቤተ ክርስቲያኒቱን ማገልገላቸው ስንመለከት፡-
ቀባሪዎቹን
አፈር መልሱ እንጂ ድንጋይ ለምናችሁ
የቀለም ቀንድ ነው ትሰብሩታላችሁ
እንላቸዋለን፡፡
በ1977 በምዕራብ ጀርመን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ያሬዳዊ ዜማ ለማሳየት ከተጓዘው ልዑክ አንዱ ነበሩ፤ በ1995 የዓለም አብያተ ክርስቲያናት በእስክንድርያ ከተማ ባደረገው ጉባኤ ቤተ ክርስቲያንን ወክለው ነበር፣ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ በአዲስ መልክ ሲዘጋጅ በብርቱ ካገለገሉት ሊቃውንት አንዱ ነበሩ፣ የመንና ጅቡቲ የሚገኙ ምእመናንን ለማስተማር በየዓመቱ ይጓዙ ነበረ፡፡ የሊቃውንት ጉባኤ አባል ሆነው ለብዙ ዓመታት አገልግለዋል፡፡ ይህንን ስንመለከትም
እንግዲህ መቃብር ጠንክረህ ተማር
ዕውቀት ተሸክሞ መጣልህ መምር
እንለዋለን፡፡
ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በሚያዘጋጁት ጉባኤ ልጆችን ሳይንቁ፣ ክፍለ ሀገር በሚዘጋጅ ጉባኤ ለመንገዱ ሳይሰቀቁ በመጓዝ ያስተማሩ የዘመናችን ሐዋርያ ናቸው፡፡ ክህነትን፣ ትምህርትንና ጽሕፈትን አንድ አድርገው የያዙ፤ በተለይም ‹‹ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን›› እንደ አንድ የትምህርት ዘርፍ ሆኖ እንዲወጣ በብርቱ የደከሙ ሊቅ ናቸው፡፡ ድካማቸው ፍሬ አግኝቶ በየጊዜው ያዘጋጇቸው መጣጥፎችና መጻሕፍት ዛሬ ከኮሌጆች እስከ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ድረስ የማስተማርያ ዋና መሣሪያዎች ሆነዋል፡፤ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን አንድ የትምህርት ዘርፍ ሆኖ እየተሰጠ ይገኛል፡፡
ሚያዝያ 19 ቀን 1929 ዓም  ይፋት ውስጥ  ደብረ ምሥራቅ ሾተል አምባ በኣታ አጥቢያ ተወልደው፣ በ1941 ዓም ከብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ዲቁና፣ በ1959 ዓም ቅስና ተቀብለው፤ አራት ወንዶችና አራት ሴቶች ወልደው፣ አሥር የልጅ ልጆች አይተው በ78 ዓመታቸው የተለዩን ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል አልታየ በዕለተ ዕረፍታቸውና ቀብራቸው ብዙዎችን ያስደነቁ ሁለት ነገሮች ተከስተዋል፡፡ የመጀመሪያው ክንፈ ገብርኤል ተብለው ተጠርተው በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል(ታኅሣሥ 19 ቀን) ወደ ፈጣሪያቸው መጠራታቸው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ሲከናወን የሕይወት ታሪካቸው በሚነበብበት ጊዜ ከትልቅ ዋርካ ላይ ማንም ሳይነካው አንድ ትልቅ ቅርንጫፍ ተገንድሶ መውደቁ ነው፡፡
ቦታው የነበሩ፣ ይህንንም ነገር የተመለከቱ ሁሉ ታሪኩን በካሜራቸው ሲቀርጹና ከታላቋ ዋርካ ከቤተ ክርስቲያን ብዙዎችን የያዘው አንዱ ታላቅ ቅርንጫፍ ሊቀ ካህናት ክንፈ ገብርኤል ዛሬ መሰናቱን በኀዘን ሲተረጉሙ ነበር፡፡ የቅርንጫፉን ቅጠልም ብዙዎቹ ተሻምተው ወስደውታል
በረከታቸው ይደርብን፡፡  


(አፈንዲ ሙተቂ)
—-
     ጎንደር ካፈራቻቸው ሰዎች መካከል አብዛኛው ኢትዮጵያዊ የሚያውቀው እኝህ ሰው ይመስሉኛል፡፡ እኔ ጸሐፊው ስለርሳቸው የሰማሁት የቋራው መይሳው ካሳን ከማወቄ በፊት እንደሆነ አስታውሳለሁ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በአለቃ ገብረሃና ስም የሚነገሩ ቀልዶችን የነገረን ደግሞ ማን መሰላችሁ….? ከዚህ በፊት ያስተዋወቅኳችሁ የሁለተኛ ክፍል አለቃችን የነበረው አያሌው አብነት  ነው፡፡ ሆኖም እርሱ ያኔ የነገረንን እዚህ መጻፍ አይመችም፡፡ ስለዚህ የአያሌውን ቀልዶች ትተን ስለአለቃ ገብረሃና ከመዛግብት ያገኛቸውን ወጎች እንጨዋወታለን፡፡ ከዚያ በፊት ግን “ዐረፈ ዐይኔ ሐጎስ” “አለቃ ገብረሃ እና አስቂኝ ቀልዶቻቸው” በሚል ርዕስ ካሳተሙት መጽሐፍ ያገኘነውን የአለቃ ገብረሃናን ታሪክ አጠር አድርገን እናወሳለን፡፡
  
አለቃ ገብረሃና በሙሉ ስማቸው “ገብረሃና ደስታ ተገኝ” ይባላሉ፡፡ የተወለዱት በ1814 በጎንደር ክፍለ ሀገር በደብ ታቦር አውራጃ ፎገራ ወረዳ (አሁን ደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ) ውስጥ ነው፡፡ በተወለዱበት አካባቢ የቤተ ክህነት ትምህርት ተምረው በሃያ ስድስት ዓመታቸው የሊቀ-ካህናት ማዕረግ አግኝተዋል፡፡ በዚህ ሹመት ለሰባት ዓመታት ካገለገሉ በኋላ በፍትሐ ነገሥት አዋቂነታቸው ተመርጠው ጎንደር ውስጥ በዳኝነት ተሾሙ፡፡
  አለቃ በካህንነትም ሆነ በዳኝነት ሲያገለግሉ እንደ ሌሎች የዘመኑ መኳንንት ቁጥብ አልነበሩም፡፡ ከተራው ህዝብም ሆነ ከመንግሥት ባለስልጣናት ጋር ይቃለዱ ነበር፡፡ ይህ ቀልደኝነታቸው እየገነነ ሄዶ በትንሹ ራስ ዓሊ ዘንድ ተሰማላቸው፡፡ በመሆኑም ወደ ቤተ መንግሥት ተጠርተው የራስ ዓሊ አጫዋች በመሆን ተሰየሙ፡፡ እንግዲህ ከዚህን ጊዜ ጀምሮ ነው አለቃ ገብረሃና የመኳንንቱና የመሳፍንቱ አጫዋች በመሆን ህይወታቸውን የገፉት፡፡
 
   አለቃ ገብረሃና በአጼ ዮሐንስም ሆነ በአጼ ምኒልክ ዘንድ ክብርና ሞገሥ አግኝተው እንደ ታላቅ ሰው ይታዩ ነበር፡፡ በአጼ ቴዎድሮስ ዘመን ግን ከፍተኛ ችግር ደርሶባቸው ነበር፡፡ ቴዎድሮስ አለቃን ያገኟቸው በቤተ መንግሥቱን ከራስ ዓሊ በተረከቡ ጊዜ ነው፡፡ ቴዎድሮስ አለቃን በዝና ቢያውቋቸውም ቀልድና ባልቱን አልወደዱላቸውም፡፡ ቴዎድሮስ ቀልዱን እንዲያቆሙና በዳኝነቱ እንዲቀጥሉ ቢገስጿቸውም አለቃ በጄ የሚሉ አልሆኑም፡፡ በመሆኑም አለቃን ከዳኝነታቸው ሽረው ትግራይ ውስጥ የሚገኘው የጨለቆት ሥላሤ ገዳም አስተዳዳሪ አድርገው ሾሟቸው፡፡ 
  
የደብሩ ቆይታ የቤተ መንግሥት ኑሮ ለለመዱት አለቃ ገብረሃና የሚመች አልሆነም፡፡ በዚያ ላይ አጼ ቴዎድሮስ ቤተ ክህነትን ርስት አልባ ለማድረግ መሞከራቸው ከሀገሬው ህዝብ ጋር አጣላቸው፡፡ በመሆኑም ካህናቱ ቴዎድሮስን ለመገልበጥ ማሴር ጀመሩ፡፡ አለቃ ገብረሃናም ዱለታውን ተቀላቀሉ፡፡ ይህም ወሬ ለአጼ ቴዎድሮስ ደረሳቸው፡፡ አጼውም አለቃ ገብረሃና ታስረው እንዲቀርቡ አዘዙ፡፡ ሆኖም አለቃ ገብረሃና ሸሽተው ጎጃም ውስጥ ከሚገኘው ዘጌ ገዳም ተደበቁ፡፡
   ከሁለት ዓመት በኋላ አጼ ቴዎድሮስ በመቅደላው ጦርነት ራሳቸውን ገደሉ፡፡ አለቃ ገብረሃናም ከተደበቁበት ወጥተው ወደ ጎንደር ተመለሱ፡፡ በ1864 አጼ ዮሐንስ አራተኛ ሲነግሡ በጎንደር ከተማ የነበራቸውን የቀድሞ ሹመታቸውን አጸደቁላቸው፡፡ በምኒልክ ጊዜ ደግሞ ወደ አዲስ አበባ መጥተው በእንጦጦ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን የአቋቋም እና የመርገድ አስተማሪ ሆኑ፡፡ ከጥቂት ቆይታ በኋላም የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ሆኑ፡፡
  አለቃ ገብረሃና በአዲስ አበባ ኑሮአቸው ከአጼ ምኒልክ ጋር ተዋድደው ይኖሩ ነበር፡፡ ነገር ግን እቴጌ ጣይቱ ቀልዳቸውንና ተረባቸውን አልወደዱላቸውም፡፡ በዚህም የተነሳ ሁለት ጊዜ ተጣልተው ወደ ደብረ ታቦር ሄደዋል፡፡ በሶስተኛው ዙር ግን ከአጼ ምኒልክም ጋራ ተቀያይመው ኖሮ እስከ መጨረሻው ተሰነባብተው ወደ ትውልድ ቄየአቸው ከሄዱ በኋላ እዚያው ኖረው በሰማኒያ አራት ዓመታቸው አርፈዋል፡፡
  አለቃ ገብረሃና መልከ መልካም ቢሆኑም አጭር ሰው ነበሩ፡፡ በዚህ ቁመታቸውም ከሌሎች ጋራ ብዙ ጊዜ ተቋስለዋል፡፡ አንዳንዶች ደግሞ በእግራቸው መንሻፈፍ ሊቀልዱ ሲሞክሩ አለቃ ያልጠበቋቸውን መልሶች እየሰጧቸው “ኩም” ያደርጓቸው ነበር፡፡
   አለቃ ወይዘሮ ማዘንጊያ ከተባሉት ባለቤታቸው ተክሌ የተባለ ልጅ ወልደው ነበር፡፡ ይህ ልጃቸው በትምህርት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ የደብረ ታቦር እየሱስ ጉባኤ ቤተ ክርስቲያን ካህን እስከ መሆን ደርሷል፡፡ ሆኖም ጠላቶቹ ተመቀኝተውት መድኃኒት በጥበጠው በማጠጣት ገድለውታል፡፡
   *****
    በአለቃ ገብረሃና ስም የሚነገሩ ብዙ ጨዋታዎችና ቀልዶች አሉ፡፡ አንዳንዶቹ በርሳቸው የተነገሩ መሆናቸው የተጻፈ ቢሆንም አንዳንዶቹ በጊዜ ሂደት የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ለበረካ ያህል በርሳቸው ስም የሚነገሩ ጥቂት ጨዋታዎችን እንቋደስ፡፡
   አንድ ጊዜ አለቃ ለግብዣ ተጠሩ፡፡ በግብዣው የቀረበው ጎመን ሆዳቸውን ቆዝሮአቸው ኖሮ ወደ እሳት ዳር ተጠጉና ሆዳቸውን ማሻሸት ጀመሩ፡፡ ጋባዣቸው ነገሩ ገርሞት “ምነው አለቃ! ሆድዎትን ምን ሆነው ነው” ሲላቸው “ረ ምንም አይደለም! ጎመኑን እያበሰልኩት ነው” በማለት መለሱላቸው፡፡
  በሌላ ጊዜ ደግሞ አለቃ የታመመ ሰው ሊጠይቁ ይሄዳሉ፡፡ የቤቱ ባለቤት ጠላ ትሰጣቸውና ታቀርብላቸዋል፡፡ አለቃ ጠላውን ፉት እያሉት ሳሉ ሴትዮዋ አመለጣት፡፡ አለቃ ጠላቸውን አገባደው ሲጨርሱ ሴትዮዋ ወደርሳቸው መጣችና “ልድገምዎት እንዴ አለቃ” በማለት ጠየቃቸው፡፡ አለቃም “አዎ! ግን እንደ ቅድሙ ጠረር አታድርጊው” አሏት፡፡
    አለቃ ስንቃቸውን በአገልግል ይዘው ከጥቂት ነጋዴዎች ጋር የዐባይ በረሃን በማቋረጥ ላይ ሳሉ ሽፍቶች በአካባቢው እንዳሉ ይሰማሉ፡፡ ነጋዴዎቹም ለገንዘባቸው አለቃም ለነፍሳቸው ተጨነቁ፡፡ “ምን እናድርግ” እያሉ በመመካከር ላይ ሳሉ አለቃ አንድ ዘዴ ትዝ ይላቸውና ነጋዴዎቹ ገንዘባቸውን እንዲሰጧቸው ይጠይቁአቸዋል፡፡ ነጋዴዎቹም የተጠየቁትን አደረጉ፡፡ አለቃም ገንዘቡን ከአገልግላቸው ውስጥ ከተቱት፡፡
    ጥቂት እንደተጓዙ ሽፍቶቹ ከጫካ ውስጥ ወጥተው “ያላችሁን ቁጭ አድርጉ” ይሏቸዋል፡፡ ነጋዴዎቹ ምንም የለንም ይላሉ፡፡ ሽፍቶቹ ወደ አለቃ ዞረው “በአገልግሉ ውስጥ ያለው ምንድነው” ብለው ጠየቋቸው፡፡ ብልሃተኛው አለቃ “ወላሂ! ወላሂ! ክሽን ያለች የዶሮ ወጥ ናት! ከፈለጋችሁ እዚሁ እንብላ” ብለው መለሱ፡፡ ሽፍቶቹም “በስመ አብ! እኛ የእስላም ስጋ አንበላም” እያሉ በማማተብ ለቀቋቸው፡፡
——
አፈንዲ ሙተቂ)
ታሕሳስ 2007


(አፈንዲ ሙተቂ)
—–አንድ–ኡምዱርማን (ሱዳን)—
አሕመድ ያ ሐቢቢ ሰላም ዐለይከ
ያ ሚስኪ ወጢቢ ሰላም ዐለይከ
ሰላም ዐለይከ ዘይነል አንቢያእ
ሰላም ዐለይከ አትቀል አትቂያእ
ሰላም ዐለይከ አስፈል አስፊያእ
ሰላም ዐለይከ ሚን ረብቢ ሰማእ
ሰላም ዐለይከ ዳኢማን ቢላ ኢንቲሃእ
——ሁለት–ገለምሶ—
1.      ሙሐመድ ሰላሙን ዐለይኩም
ሰይዲ ሰላም ዐለይኩም
ሰለዋቱላህ ዐለይኩም
2.     አላሁመ ሰሊ ዐላ ሰይዲና ሙሐመዲን ወዐላ ኩልሊ ነቢዪን
ወሰልሊ ዐላ አቢበክሪን ወዐላ ኩልሊ ወሊዪን
ወሰልሊ ዐላ ጂብሪለን ወዐላ ኩሊ መለክ
—-ሶስት– ጅማ—
አላህ አላህ ላኢላሀ ኢልለላህ
 ሙሐመዱን ረሱሉላሂ ሐቢቡ ዒንደላህ
ዐለይሂ ሰላቱ ወሰላሙ ሚነልላህ
—-አራት– ጅቡቲ—-
ሰላዋቱልላህ ዐለይከ ያ ሙሐመድ
ሰላሙልላህ ዐለይከ ያ ሙሐመድ
ሰላሙልላሂ ያ ኑረል ቁሉቢ
ያ ኑረል ቁሉቢ
—-አምስት– ሐረሪ—–
ሰሊ ያ ረብቢ ዐላ ሙሐመዲን
ሰሊም ያ ረብቢ ዐላ ሙሐመዲን
ባሪክ ያ ረብቢ ዐላ ሙሐመዲን
ኩሉ የውሚን ወለያሊን አልፈ መር
—-ስድስት– ወሎ—– 
ሰላቱ ወተስሊሙ ወ አዝካ ተሒቲን
ዐለል ሙስጠፈል ሃዲ ጣሃ ያ ሙሐመዲን
——————————————–

በሥራ ላይ ያለውን የብሮድካስት አዋጅ የሚሽርና ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም ተንቀሳቃሽ ስልክንበመጠቀም የሚቀርብ የብሮድካስት አገልግሎቶችን ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፡፡
የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለስልጣን ያዘጋጀውና በዚህ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህው የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ አሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን ማለትም ራዲዮ፣ቴሌቪዥን፣ የኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም የሕትመት ሚዲያውን የሚመለከት ነው፡፡ በዚህ አዋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የአንተርኔት ድረገጾች ፈቃድ ማውጣት የግድ መሆኑን ደንግጎአል፡፡
በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል የመረጃ መረብ አማካኝነት ለስርጭት የሚቀርብ ማንኛውም ፕሮግራም በአገር አንድነትና ሉአላዊነት ላይ አደጋ የሚጥል ፣በአገር ደህንነት፣ ክብርና ጥቅም ላይ ጉዳት የሚያደርስ ፣የአገር ሚስጢርን የሚገልጽ ፣ አመጽና ጦርነትን የሚቀሰቅስ፣ የሰው ልጆችን ስብዕና ፣ነጻነት ወይንም ስነምግባር የሚጻረር ፣የሌሎችን እምነት የሚያንኳስስ መሆን እንደሌለበት ደንግጎአል፡፡
በተጨማሪም ሥራዎቹ ማንኛውንም የህብረሰተብ ክፍል፣ ብሔር፣ጎሳ፣ቀለም፣ጾታ፣ዘር፣ቋንቋ፣ሃይማኖት፣ማህበራዊ አመጣጥ፣ ወይንም ሌላ መሰል አቋምንና ክብርን የሚነካ ወይም የሚያዋርድ፣ በህዝቦችና በሃይማኖቶች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት የሚቀሰቅስ ወይንም ጥላቻ የሚያስፋፋ፣ የግለሰብን ስም የሚያጠፋ፣፣ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጆችን አመለካከት ስሜት የሚጎዳና ወደአልተፈለገ አቅጣጫ እንዲያዘነብሉ የሚገፋፋ፣ የህብረሰተቡን ሞራል የሚጥስ ወይንም በሕግ የተከለከለ ማንኛውንም ድርጊት የሚፈጽም መሆን የለበትም ይላል፡፡
ተጠያቂነትም በተመለከተ ረቂቅ አዋጁ እንዳሰፈረው በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል መረጃ መረብ አማካይነት የቀረበ ፕሮግራም ለሚያስከትለው ማንኛውም የወንጀል ድርጊት ወይም የፍትሐብሄር ጉዳት የፕሮግራሙ ሃላፊና የብሮድካስት አገልግሎት ሰጪው በአንድነት ተጠያቂ ይሆናሉ ይላል፡፡
በኢንተርኔት ፣በተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም በመሰል መረጃ መረብ አማካይነት የቀረበ ፕሮግራምን ቁጥጥርን በተመለከተ ከህብረተሰቡ በቅሬታ መልክ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን የመመርመር፣ተቆጣጣሪ የመመደብ ስልጣን ወደፊት ለሚቋቋመው ባለስልጣን መ/ቤት ሃላፊነቱን ይሰጣል፡፡
ረቂቅ አዋጁ የቴሌቪዥንን ከአናሎግ ወደዲጂታል ሽግግርን ለማቀላጠፍና የግል ቴሌቪዥን ለመፍቀድ ይረዳል ተብሎአል፡፡ በዚህ ረቂቅ አዋጅ መሰረት ተጠሪነቱ ለጠ/ሚኒስትሩ የሆነ የኢትዮጵያ የሚዲያ ባለስልጣን የሚባል መ/ቤት ይቋቋማል፡፡
የብሮድካስት አግልግሎት የሚመራበትን ሥርዓት ለመደንገግ ከ15 ዓመታት በፊት የወጣው አዋጅ ቁጥር 178/1991 የግል ቴሌቬዥን ጣቢያ ፈቃድ ለግል ባለሃብቶች የፈቀደ ቢሆንም ይህ ተግባራዊ ሳይሆን አዋጁ በቁጥር 533/1999 የተሻሻለ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተሸሻለውም አዋጅ ቢሆን የግል ቴሌቭዥን ጣቢያ የተፈቀደ ቢሆንም ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ኢትዮጵያ ለዚህ ደረጃ ገና አልበቃችም በማለት አዋጁ እንዳይፈጸም እስካሁን ድረስ መከልከሉ የሚታወቅ ነው፡፡

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ካለፈው እሮብ ጀምሮ ለ3 ቀናት በተካሄደው የመሰናዶና የመምህራን የፖለቲካ ስልጠና ላይ የገዚውን ፓርቲ ካድሬዎች በጥያቄ ከማፋጠጥ ጀምሮ በአገሪቱ ውስጥ በሚታየው ዘረኝነት፣ የፍትህ እጦትና ሙስና ላይ አስተያየቶችን የሰጡ ተማሪዎች ከስብሰባው መጠናቀቅ በሁዋላ ተማሪውንና ህዝቡን ለአመጽ ለማነሳሳት አስባችሁዋል በሚል ማስጠንቀቂያና ባስፈራሪያ እንደደረሳቸው ዘጋቢያችን ገልጻለች። ለተማሪዎች በሚሊኒየም ትምህርት ቤት በፕላዝማ የተደገፈ …

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት ባወጣው የ2014 ሪፖርት ኢትዮጵያ ለግዳጅ ሥራ፣  ለወሲብ ንግድና  ለሕገወጥ የሰዎች ዝውውር የተዳረጉ ወንዶች፣ ሴቶች እና ሕፃናት መነሻ፤ በተወሰነ ደረጃም መዳረሻ አገር ናት ብሎአል። አዲስ አበባ የሚገኘው ዋና የገበያ ማዕከል ከአፍሪካ ቀዳሚው የወሲብ ንግድ ቤቶች መገኛ ነው የሚለው ሪፖርቱ፣  ዕድሜያቸው እስከ 8 ዓመት የሚሆኑ ልጃገረዶች በነዚህ …

ታኀሳስ ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሥራ ላይ ያለውን የብሮድካስት አዋጅ የሚሽርና ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም ተንቀሳቃሽ ስልክንበመጠቀም የሚቀርብ የብሮድካስት አገልግሎቶችን  ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፡፡ የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለስልጣን ያዘጋጀውና በዚህ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህው የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ አሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን ማለትም ራዲዮ፣ቴሌቪዥን፣ የኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም የሕትመት …

(ወልደብርሃን ስሁል) የዛሬ መቶ ሰባ ዓመት አካባቢ አንዲት “ሚጢጢየ” አውሮፓዊት ሃገር ማንም ሳይቀድማት ኢትዮጵያን በጉልበት ይዛ ቅኝ ለመግዛት “ክተት ሰራዊት ምታ ነጋሪት ብላ” ቆርጣ ተሰናዳች። በቆዳ ስፋቷ አንድ ትልቅ ወረዳ እምታክል ናት። አፍሪካ ውስጥ ግን የራሷን መቶ እጥፍ የሚያክል ግዛት መቆጣጠር እሚያስችል አቅምና እብሪት ነበራት። ህልሟን ለማሳካት ፕሮጀክት ቀርፃ feasibility study አካሄደች። እቅዷና ጥናቷ ያነጣጠረውም በዘመነመሳፍንቷ ኢትዮጵያ ላይ ነበር። የቀይ ባህር አካባቢ ደከም ባለ አውሮፓዊ ሃይል እንዲያዝ ትሻ የነበረችው ታላቋ ብሪታንያም ይሁንታ ሰጠቻት፤ በወርራ ቅኝ ልትገዛን ቆርጣ ለተነሳችው ቤልጅየም! ቤልጅየም ለኢትዮጵያ ያሰበችው ፕሮጄክት ብሎንዲል ከሚባል እብሪተኛ ሰው የጀብድ ልክፍት ጋር የተቆራኘ ነበር። ግብፅ በወርኔር ሙዚንጀር፤ ጣልያን በፔትሮ አንቶኖሊ ምን እንዳደረጉን ጠንቅቀን እናውቃለን። ከነሱ በፊት ቀድሞ ስለተሰናዳልን የብሎንዲል Humanitarian Mission ግን ብዙ አናውቅም። ነገሩ ያስገርማል እንጂ አያስቅም። “ገድለ‐ብሎንዲል” በጥቂቱ እንዲህ ነበር፦ የቤልጂግ መንግስት መጀመርያ በ1841 ከፍተኛ በጀት መድቦ ብዛት ያላቸው የስለላ ወኪሎቹን ወደ ግብጽ አሰማራ። ወኪሎቹም “ለሳይንሳዊ ጥናት እና ለሰብአዊ ተልእኮ” በሚሉ ሽፋኖች ካይሮ ላይ ከትመው ስለ ኢትዮጵያ ጥናት ጀመሩ። ማንኛውንም ዓይነት መረጃ በዝርዝር እየቀራረሙ ከሚያቀርቡት ሪፖርት የቤልጂየም ንጉስ ቀዳማዊ ሊዮፖልድ “በውስጧ ሁከት የነገሰባት ኢትዮጵያን” በቀላሉ መውረርና መቆጣጠር እንደሚችል አመነ። ለወረራም ቋመጠናም የሰላዮቹ አስተባባሪ በአካል ወደ ኢትዮጵያ ሂዶ “ሰብዓዊ ተልእኮ” የሚል ስም ያለው ጉብኝት እንዲያካሂድ አዘዘው። ዋናው ተልእኮው ግን ለወረራ ምቹ ሁኔታ እንዲፈጥር እና ባስቸኳይ እሚተገበር የድርጊት መርሃ ግብር እንዲያዘጋጅ ነበር። […]

ትናንት በ19/04/07 ዓ.ም የአንድነት ፓርቲ የኮምቦልቻ ጽ/ቤት መከፈቱን ተከትሎ የማስተዋወቅ ስራ ሲሰሩ ከነበሩት የአንድነት አመራሮች መካከል አቶ ተማም መሀመድ በከተማ አስተዳደሩ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎች ተጠርተው ተጠይቀዋል፡፡ የፀጥታ ዘርፍ ሀላፊዎቹ ‹‹እናንተ ያለጊዜው የምርጫ ቅስቀሳ እያደረጋችሁ ነው፤ የፀጥታ ችግር ለመፍጠር እያሰባችሁ ነው፤ሳታሳውቁ ነው የምትሰሩት›› የሚሉ ጥያቄዎች ያቀረቡባቸው ሲሆን፤ አቶ ተማም እኛ ቢሯችንን ስንከፍት ተገቢውን የማሳወቂያ ደብዳቤ ለሚመለከታቸው […]

የፕሮግራም መግለጫ

ወደ 98 ሚሊየን የሚጠጋ ሕዝብ ባላት ኢትዮጵያ አማርኛ ብሔራዊ የሥራ ቋንቋ ነው፡፡ በቅርብ የተካሄዱ የቅኝት ጥናቶች እንደሚያሳዩት አዋቂ በሚባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ ካለው ሕዝቧ አንድ አምስተኛ የሚሆነው የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያን (የቪኦኤን) ሥርጭቶች ያዳምጣል፡፡ ይህ ቁጥር ቪኦኤ በዓለም ዙሪያ ከሚያሠራጭባቸው ቋንቋዎች ሁሉ ጋር ሲነፃፀር ግዙፍ ከሚባሉት የአድማጭ ብዛት አንዱ ነው፡፡

ቪኦኤ በየዕለቱ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ በአማርኛ፣ በአጭር ሞገድ 22፣ 25 እና 31 ሜትር ባንድ ከሚያሠራጨው የ60 ደቂቃ ዜና፣ አበይት ዜናዎች ትንታኔና ሌሎችም ወቅታዊ መረጃዎችን የያዙ ፕሮግራሞች በተጨማሪ ከሰኞ እስከ ዐርብ ከምሽቱ 1 ሰዓት እስከ 1 ሰዓት ተኩል በአማርኛ የሚተላለፍ የግማሽ ሰዓት ሥርጭት በ1431 መካከለኛ ሞገድ ላይ አለው፡፡

የቪኦኤ የአማርኛ ፕሮግራሞች በተጨማሪም በናይል ሳት ይተላለፋሉ፡፡

ሰኞ፡- ስፖርት፣ አፍሪካ ነክ ርዕሶች፣ ጤና

ማክሰኞ፡- ሐኪሙን ይጠይቁ፣ ንግድ፣ ምጣኔ ኃብትና ግብርና

ረቡዕ፡- ዴሞክራሲ በተግባር፣ ሴቶችና ቤተሰብ፣ አሜሪካና ሕዝቧ፣ ኢትዮጵያዊያን ባሜሪካ

ሐሙስ፡- ባሕልና ማኅበረሰብ፣ ሕይወት በቀበሌ፣ የተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት

ዐርብ፡- እሰጥ አገባ፣ አፍሪካ በጋዜጦች፡ አጥቢያ ኮከብ (የማኅበረሰብ ጀግኖች)

ቅዳሜ፡- ከዚህም ከዚያም፤ የሙዚቃ ቃና

ዕሁድ፡- ራዲዮ መፅሔት፣ መስተዋት (የወጣቶች ፕሮግራም) – ሁለቱ ዝግጅቶች በየሣምንቱ ይፈራረቃሉ፡፡

ለሁሉም የዕድሜ ክልሎች የታሰቡት የሣምንቱ የመጨረሻ ቀናት ዝግጅቶቻችን የሃሣብ ማንሸራሸሪያ መድረኮችንና የመዝናኛ ቅንብሮችን ያካተቱ ናቸው፡፡

የአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ጣቢያ በአሜሪካ መንግሥት በጀት የሚንቀሣቀሱ ትክክለኛና ተዓማኒነት ያላቸውን ዜናዎች እንዲሁም ሰፋፊ ፕሮግራሞችን እያደራጀ በራዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በሞባይል መሣሪያዎችና በኢንተርኔት በ45 የዓለማችን ቋንቋዎች የሚያሠራጭ ዋና መቀመጫው ዋሺንግተን ዲሲ የሆነ የዜና ተቋም ነው፡፡

ቪኦኤ በአማርኛ በሣምንት የዘጠኝ ሰዓት ተኩል ሥርጭት ያስተላልፋል፡፡

«ዓለም ከሁለተኛዉ ያዓለም ጦርነት ወዲሕ የዘንድሮን ያክል ሕዝብ ተሰዶ፤ተፈናቅሎባት አያዉቅም።የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ለበርካታ ሕዝብ አስቸኳይ እርዳታ እንዲያቀርብ የዘንድሮን ያክል ተጠይቆ አያዉቅም።»

የአፋር ነፃ አዉጪ ግንባር (ALF) ከአፋር መስተዳድር ገዢ ፓርቲ ከአፋር ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አብዴፓ)ጋር ያካሄደዉ ዉህደት ህገ ወጥ ነዉ በሚል በዶቼ ቬለ የተላለፈዉ ቃለ መጠይቅ ከሃቅ የራቀ ነዉ ሲል አስተባበለ።

የሶማልያ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን አሸባብ የመረጃ ኃላፊ እንደሆኑ የተነገረላቸዉ ግለሰብ ባሳለፍነዉ ሳምንት መጨረሻ ቅዳሜ በሶማልያ ለሚገኝ የአፍሪቃ ሕብረት ሰላም አስከባሪ ኃይልና ለሶማልያ መንግሥት ጦር እጃቸዉን ከሰጡ በኋላ ግለሰቡ ከዓመት በፊት ቡድኑን ጥለዉ መዉጣታቸዉን አሸባብ ዛሬ አስታወቀ።

Image
ከአውሮፓ ወደ ኤርትራ ለውህደቱ ስብሰባ እንዲሄድ የተወከለው በጀርመን የሚኖረው አቶ ካሳዬ መርሻ ወደ አስመራ እንዳይገባ በሻእቢያ መከልከሉ ሲታወቅ ከፊል ኤርትራዊ እንደሆነ የሚታወቀው እና ከአውስትራሊያ የተወከለው የወልቃይት ተወላጅ አቶ አለልኝ ከሻእቢያ ፈቃድ ማግኘቱ ታውቋል:: ነዋሪነት በጀርመን የሆነው እና ለአርበኞች ግንባር ትግል ታላቅ አስታውጾ እንዳበረከተ የሚነገርለት አቶ ካሳዬ መርሻ በግንባሩ አባላት አስፈላጊዉን ወጪ ተሸፍኖለት ለጉዞ ሲንደረደር በሻእቢያ መከልከሉ በውጪ የሚኖሩ የግንባሩ አባላትን ያሳሰበ ቢሆንም ሁኔታውን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑ ታውቋል::

በዚህ ምክንያት በውጪ የሚኖሩ የአርበኞች ግንባር አባላት እና ደጋፊዎች የተወከለው አቶ ካሳዬ እንዳይመጣ በሻእቢያ መከልከሉን በተመለከተ ያላቸውን ተቃውሞ በደብዳቤ መላካቸው ሲታወቅ በአስመራ የሚገኙ የግንባሩ አመራሮች ሁኔታውን እንዲፈቱ በደብዳቤያቸው ያሳውቁት አባላቱ በአግባቡ የተወከለው ሰው በውህደቱ ጉባዬ ላይ እንዲገኝ ሲሉ አቋማቸውን ገልጸዋል::የወከሉት ሰው በመከልከሉ በውህደቱ ላይ ያላቸውን ጥርጣሬም አስምረውበታል::በቂ ሃይል እና ተንካራ መዋቅር እንዳለው የሚነገርለት አርበኞች ግንባት አባላቱ በኢትዮጵያ ለሚመጣው ለውጥ ተግተው እንደሚሰሩ እና ማንም እንደማያስቆማቸው ተናግረዋል::

አንድ አስተያየት ሰጪ እንደተናገሩት በሃገር ቤት ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሃገራዊ አቋም እንዳይኖራቸው ሕወሓት/ኢሕ አዴግ በሰርጎ ገብነት እየገባ እንደሚያፋልሳቸው ሁሉ በውጪ የሚኖሩ ድርጅቶችንም እንዲሁ ሻእቢያ በውስጥ ጉዳያቸው እየገባ እሱ በሚፈልገው መልኩ እንዲሽከረከሩ ያደርጋል ሲሉ ተደምጠዋል::

ከጀርመን የተወከሉት አቶ ካሳዬ ወደ አስመራ እንዳይገቡ ካልተፈለገበት አንዱ ምክንያት ከዚህ ቀደም በግንባሩ ላይ በሻእቢያ የሚፈጸሙ ግፎችን ለማስቀረት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ የነበሩ ሲሆን የግንባሩ አባላት እና ታጋዮች ይህንን በደንብ ስለሚያውቁ በውህደቱ ላይ እንዲገኝላቸው ፍላጎቱ ቢኖራቸውም ሻእቢያ ግን አንድ ጊዜ ጥርስ ስለነከሰበት እንዳይመጣበት ከልክሏል::እንዲሁም በውጪ የሚኖሩ አባላት ውህደቱ ላይ ችግር ካለ እንዲወገድ ወደፊትም ችግሮች እንዳይፈጠሩ አመራሩን ለማስተካከል እና አማራጮችን መጠቀም በሚል ስልት አቶ ካሳዬ የራሱን የፖለቲካ ልምድ ተጠቅሞ ሊያስተካክል ይችላል እንዲሁም ያሉትን ችግሮች እንዲስተካከሉ በፊትለፊት ይናገራል የሚሉ ፍራቻዎች በሻእቢያ ስላሉ የተወከሉት አባል ወደ አስመራ እንዳይገቡ ከልክለዋል::

አቶ ካሳዬ ወደ አስመራ ሁለት ጊዜ ካሁን ቀደም ሂዶ ካለምንም ፍርሃት ለሻእቢያ ግንባሩን በተመለከተ ያለውን ችግር እና ወደፊት መሆን የለበትን ጉዳይ ካለፍርሃት አፍረጥርጦ ስለተናገረ እንዲሁም አቶ ካሳዬ የአርማጮ ተወላጅ በመሆኑ በአከባቢው ያለውን እና በግንባሩ ታጋዮች ዙሪያ ያለውን ጉዳይ አንስቶ ካለፍርሃት ለሻእቢያ መናገሩ ለአሁኑ መከልከል ምክንያት ቢሆንም ጉዳዩን ለመፍታት አስመራ እና አውሮፓ ያሉ የግንባሩ አመራሮች እየጥሩ መሆኑን ምንጮች ከአስመራ ተናግረዋል:
******************************************************************************
የወያኔ አየር ሃይል ባልደረቦች ይዘውት የገቡትን ሄሊኮፕተር ተከትሎ አቶ ኢሳያስ አፍወርቂ የአዲስ አመትን ጋዜጣዊ መግለጫ አስታከው ይናገራሉ ተብሎ በመጠበቅ ላይ ሲሆን የወያኔ ቃል አቀባዮች ሌመንግስት ታማኝ ለሆነ ጋዜጣ ሄሪኮፕተሩ ለማስመለስ ጥረት አለመደረጉን መግለጻቸው ቢታወቅም የሕወሓት ጦር ጄኔራሎች ግን ካልተመለሰ ምሳችንን አስመራ እንበላለን ሲሉ መደንፋታቸው የወያኔ ባለስልጣናቱን አለመናበብ አመልክቷል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ወያኔ በውጪ ከሚኖሩ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር ለመደራደር ማንዣበቡን ፍንጮች ጠቁመዋል:: ወያኔ በስልጣን የመቆየት እድሉ እንደተመናመነ በማወቁ ድርድር የማድረግ ፍላጎት ማሳየቱ እና በታሪክ ልንከስም ነው ያሉት ባለስልጣንን ተከትሎ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ገዢው ፓርቲ የገባበትን አጣብቂኝ ሊወጣው ባለመቻሉ ውንደለመደው በማዘናጋት ጊዜ መግዣ መፈለጉን ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል:: ‪#‎ምንሊክሳልሳዊ‬