የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ በአጀንዳነት ተይዟል፤ ዐሥር አህጉረ ስብከት ተለይተዋል፡፡ በተጭበረበረ የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ማስረጃና የዶክትሬት መመረቂያ ጥናትን አስመስሎ መቅዳት/plagiarism/ ክሥና ወቀሳ እየቀረበባቸው የሚገኙት፣ ሓላፊነትን በተገቢው ኹኔታ ባለመወጣትና በትጋት ባለመሥራት የተገመገሙት ዶ/ር አባ ኃይለ ማርያም መለሰ፣ በከባድ እምነት ማጉደል በተቀሰቀሰባቸው የካህናትና ምእመናን ተቃውሞ ከቅ/ላሊበላ ደብር አስተዳዳሪነት የሚነሡት አባ ገብረ ኢየሱስ መኰንንና የመሰሏቸው ቆሞሳት ከታሳቢ ዕጩዎች መካከል …

ጥቅምት ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የልማት ኤጀንሲው የስራ ሃላፊ ለዘጋቢያችን እንደነገሩት ድርጅቱ በተሰጠው ስልጣን እና ሃላፊነት የተለያዩ የመንግስት ይዞታ የነበሩ ተቋማት በጥናት ለህዝብ ጥቅም የመሸጥ የመለወጥ ፤ ስልጣን ተሰጥትቶታል፡፡ ይህን ስራ ተግባራዊ ለማድረግ አዳጋች ሁኖብኛል ሲሉ ገልጸዋል፡፡ እስካሁንም የአዋሺ አግሮ ኢንዱስትሪ ቲብላ እርሻ፣ የመካከለኛ አዋሺ የእርሻ ልማት፣  በሰሜን ኦሞ እርሻ ልማት ውስጥ የሚገኘው …

ጥቅምት ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ብርሀንና ሰላምን ለ20 አመታት የመሩት የኢህአዴግ ደጋፊ የሆኑት ወ/ሮ ሙሉወርቅ ገብረህይወት  ጡረታ ወጥተው በእርሳቸው ምትክ የህወሀት አባሉ አቶ ተካ አባዲ ዛሬ ስራስኪያጅ ሆነው ተሹመዋል። የአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት ስራ አስኪያጅ ሆነው የቆዩት አቶ ተካ፣ ከሰራተኛው ጋር ከፍተኛ ውዝግብ ውስጥ በመግባትና በአስተዳደራቸው ብልሹነት ይታወቃሉ። ዛሬ ከሰአት ሹመቱ ይፋ ሲሆን የብርሀንና …

ጥቅምት ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዊ ዞን ቻግኒ ከተማ የሚገኘው ትልቁ የእስልምና ሀይማኖት ትምህርት ቤት በመንግስት ትእዛዝ እንዲታሸግ ተደርጓል፡፡ በትምህርት ቤቱ ውስጥ ከ600 በላይ ተማሪዎች የእስልምና ሀይማኖት አስተምሮዎችን ይማሩበት ነበር። መንግስት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ የሀይማኖት ተቋማትን እያሸገ ነው። መንግስት  ድርጅቶቹ የአክራሪነት መፈልፈያ ሆኗል በማለት ይከራከራል። የመንግስትን እርምጃ የሚቃወሙ ሙስሊሞች በበኩላቸው …

ጥቅምት ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቤይሩት ኢትዮጵያዊቷ በመኪና አደጋ  ደርሶባት አስቸኳይ ህክምና ማግኘት ባለመቻሏ ህይወቷ አለፈ። ኢትዮጵያዊቷ አስቸኳይ ህክምና ማግኘት ያልቻለችው- ቆንስላ ጽፈት ቤቱ ሀላፊነት አልወስድም በማለቱ እንደሆነ ተዘግቧል። በዚህም ሳቢያ መዳን ስትችል የነበረችው ወጣት  ህክምና ባለማግኘቷ ለህልፍት መብቃቷ፤ ዜናውን በማህበራዊ መገናኛዎች የተከታተሉትን ሁሉ አሳዝኗል። የቆንጽላ ጽህፈት ቤት ሠራተኞች፤  ለግድብና ለተለያዩ ነገሮች እያሉ …

ጥቅምት ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰሜን ወሌ በራያ ቆቦ ወረዳ ከ40 በላይ መንገደኞች ይዞ ሲጓዝ የነበረ አውቶቡስ በመገልበጡ ከ30 በላይ ሰዎች ሲሞቱ በርካቶችም ቆስለዋል። መኪናው ከጭንቱ ልክ በላይ ሰዎችን ጭኖ መጓዙ ታውቋል። በኢትዮጵያ የመኪና አደጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨ መ ረ መሄዱ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወቃል።

ጥቅምት ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኬንያው ዴይሊ ኔሽን እንደዘገበው ኢትዮጵያውያኑ የተያዙት ሙታሬ በምትባለውና ከሞዛምቢክ ጋር ድንበርተኛ በሆነችው ከተማ በኩል አድርገው ወደ ደቡብ አፍሪካ ሲያቀኑ በፖሊስ እንደተያዙ ማክሰኞ ማምሻውን ተዘግቧል፡፡ ተጠርጣሪ ስደተኞቹ በግምት ከ20 እስከ 30 ባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ እንደሚገኙ የተገለጸ ሲሆን፣ ከዚምባቡዌ በሕገወጥ መተላለፊያ በኩል መግባታቸውን ያስታወቁት፣ በዚምባቡዌ ቤት ብሪጅ ዲስትሪክት የፖሊስ …

ሬይክያቪክ ጂዖ-ተርማል ​​
ኢትዮጵያ ሌላ ባለአራት ቢሊየን ዶላር የኃይል ማመንጫ ሥራ ልትጀምር ነው
የኢትዮጵያ ጂዖ-ተርማል ኢነርጂ መገኛ የስምጥ ሸለቆ ክልል ​​የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ሬይክያቪክ ጂዖ-ተርማል ከሚባል ኩባንያ ጋር የኩርቤቲን የከርሰ-ምድር እንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለማከናወን ውል ተፈራርሟል፡፡

ፕሮጀክቱ አራት ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ወይም ወደ ሰማንያ ቢሊዮን ብር እንደሚፈጅ ተገልጿል፡፡

ጂዖ-ተርማል ኢነርጂ ​​
ሬይክያቪክ ጂዖ-ተርማል በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ግዙፍ የውጭ ቀጥታ መዋዕለ ነዋይ እና የግል የኤሌክትሪክ ኃይል አመንጭ ኩባንያ መሆኑ ነው፡፡

ይህንንና ሌሎችም በተፈጥሮ አካባቢ፣ ሣይንስና ሕይወት ላይ የተቀናበሩ ዘገባዎችን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Prof. Al Mariam ፕ/ር ዓለማየሁ ገብረማርያም ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ)
ታላላቅ የአፍሪካ መሪዎች ህልም አላቸው፤ ቀሪዎቹ በቅዠት የተሞሉ ናቸው።

በቅርቡ የአፍሪካ መሪዎች ቢያንስ በአፍሪካ ህብረት ስልጣን ያላቸውና የእነርሱ ጋሻ ጃግሬዎች ስለህግ ልዕልና፣ ስለዘር ማደን (ማሳደድ) የማያቋርጡ አስደንጋጭ የቅዠት ሪፖርቶች በገፍ እያቀረቡ ነው። ቅዠታቸውም የፍትህ ጎራዴ ስያሳድዳቸው በላብ ተጠምቀው ከእንቅልፍ ይነቃሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ኢትዮጵያ ውስጥ ‘ዴሞክራሲ አለ’ ለማለት ያስቸግራል – ክቡር ገና
የፓርላማ አባላት ከተመረጡበት አካባቢና ሕዝብ ፍላጎት ይልቅ የፓርቲያቸውን ያስቀድማሉ ሲሉ አቶ ክቡር ገና አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

“ኢትዮጵያ ውስጥ ‘ዴሞክራሲ አለ’ ለማለት ያስቸግራል” ብለዋል የኢኒሽየቲቭ አፍሪካ ዋና ዳይሬክተር አቶ ክቡር ገና፡፡

“አብዛኛው ተቃዋሚ ኃይልም ከመንግሥት የተሻለ መሆኑን አላሣየም ወይም እስከአሁን በግልፅ አልወጣም” ብለዋል አቶ ክቡር አክለው፡፡

አቶ ክቡር ስለአዲሱ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት በአንድ መፅሔት ላይ ያሠፈሩትን ፅሁፍ መነሻ አድርጎ እስክንድር ፍሬው አነጋግሯቸዋል፡፡

የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

የጀርመን መራሂተ-መንግስት አንጌላ ሜርክል የእጅ ስልክ በዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት የስለላ ተቋም ተጠልፏል የሚለዉ ዜና እያነጋገረ ነዉ። ዩናይትድ ስቴትስ ድርጊቱን እንዳልፈፀመች በመጥቀስ አስተባብላለች። ጉዳዩ በአውሮጳ መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶታል።

ብዙዎች በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ መስሪያ ቤት አስፈላጊውን አገልግሎት በአፋጣኝ አልሰጠንም በማለት እንደሚያማርሩ እና ስጋት እንደገባቸው የጅዳዉ ወኪላችን ገልጿል። የሳውዲ መንግስት ሕገ ወጥ ስደተኞችን አስመልክቶ ያወጣውን መስፈርት ለሚያሟሉ ዜጎች የመኖሪያ ፈቃድ ለመስጠት የሰጠው የተራዘመ የምህረት አዋጅ፤

በሚቀጥለው ወር ፖላንድ ውስጥ በሚደረገው ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ የአፍሪቃን አቋም ለማንፀባረቅ ይረዳል የተባለለት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ አዲስ አበባ ውስጥ በአፍሪቃ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ስብሰባ ተካሂዷል።

የጀርመን መራሂተ-መንግስት የእጅ ስልክ በዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት የስለላ ተቋም ሳይጠለፍ አይቀርም መባሉ ዩናይትድ ስቴትስና ጀርመንን እያነጋገረ ነው። ዋሽንግተን ሜርክል አልተሰለሉም፣ አይሰለሉምም ብላለች።

መዲና አዲስ አበባ ፤ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ትምህርት ቤት፤ የባቡር ጣብያ ፤ የአዉሮፕላን ማረፊያ፤ የማተሚያ ቤት ሆቴሎች የስልክ ቤት፤ የመሳሰሉ ህንጻዎችን የገነባች፤ ታሪካዊ ሃዉልቶችን ያቆመች እና በኢትዮጵያ ዘመናዊነትን ከተቀበሉት የኢትዮጵያ ከተሞች በቀደምትነት ትጠቀሳለች።

በደቡብ ኦሞ ጂንካ ከተማ በ2003 ዓ.ም የተሰራ ሁለገብ ስታዲየም መፍረሱ ተሰማ፡፡ ስታዲየሙ ለ13ኛው የአርብቶ አደር ጉባኤ ወደ ዞኑ ላቀኑት የቀድሞ ጠ/ሚ/ር አቶ መለስ ዜናዊ ጉብኝት እንዲደርስ ተብሎ የተወጠነ እንደ ነበር ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ በዚህ ሁኔታ ጥር 13 ቀን 2003 ዓ.ም የዋለው የአርብቶ አደር ቀን በስታዲየሙ እንዲከበር ለማድረግ ስራው ሙሉ በሙሉ በ20 ቀናት ውስጥ እንደተጠናቀቀ ለማወቅ ተችሏል፡፡ […]

ጥቂት ቀደም ሲል “አጼ ሚኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱ በደራሲ ተስፋዬ ገ/አብ አይን” በሚል ርእስ በለቀቅሁት ጽሁፍ ሳቢያ በርካታ አንባቢያን የተለያዬ አስተያየት ልከውልኛል። አንዳንዱ “ይህን እየወጣ ያለ ደራሲ ወደታች ባትጎትተው ምናለ?” ሲል ሌሎችም “አበጀህ” ብለውኛል። መጽሃፍትን አነባለሁ ብዬ አስባለሁ–በተለይ የአማርኛ ስራዎችን። አሁን አሁን የሚወጡትን ካልሆነ በቀር ብዙም ያመለጠኝ ስራ አልነበረም። አንድ መጽሃፍ አጀማመሩ ካላስደሰተኝ ለመጨረስ ራሴን […]

‹‹ሀገሬ ናይጄሪያ ኢትዮጵያን ለማሸነፍ ምትችልበት ብቸኛው መንገድ አንድም ጸሎት አሊያም ዕድል ነው፡፡›› የቀድሞው ዝነኛውና ኮከብ የናይጄሪያ ብሔራዊ ቡድን ተጨዋች የሆነው ካኑ ለአንድ ታዋቂ የስፖርት ድረ ገጽ በሰጠው አስተያየት ነበር እንዲህ ያለው፡፡ በጨዋታው ላይ የሆነው ሁሉ እንዳለ ሆኖ በእውነትም ካኑ እንደገመተው የናይጄሪያዎቹ ፈጣን ንስሮች ‹‹በጸሎትም ወይም በዕድል›› ሊባል በሚችል ሁኔታ የኢትዮጵያ አቻዎቻቸውን 2-1 በማሸነፍ ለ2014 የብራዚሉ […]

ጥቅምት ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ህግ አንድ ግለሰብ ከመንግስት በማስፈቀድ አንድ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ እንዲይዝ ቢፈቀደልትም ፣ በተግባር ግን አብዛኛው ህዝብ በመሳሪያ አሰሳ ስም የግል መሳሪያውን መቀማቱን በተለያዩ የመገናኛ ብሀን ሲዘገብ ቆይቷል። በ1997 ምርጫ ወቅት የአንድ ብሄር አባላት በገዢው ፓርቲ ህወሀት  ራስን የመጠበቂያ መሳሪያ እንዲታደላቸው መደረጉ በስፋት መዘገቡ ይታወቃል። የፌደራል አቃቢ ህግ …

ጥቅምት ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ 13ኛውን የአርብቶ አደሮች ቀን ለማክበር ደቡብ ኦሞ ዞንን ለማክበር በተገኙበት ወቅት ለእርሳቸው ክብር መገለጫ እንዲሆን እስከ 20 ሚሊዮን ብር እንደፈጀ የሚነገርለት ስታዲያም  በጅንካ ከተማ ተስርቶላቸው ነበር። ይሁን እንጅ ስታዲየሙ ሶስተኛ አመቱን ሳይደፍን ለሁለተኛ ጊዜ ፈርሷል። በመጀመሪያ ከክቡር ትሪቡኑ በስተቀኝ በኩል ያለው ክፍል ፈርሶ ጥገና …

ጥቅምት ፲፫(አስራ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኩባንያው ከ230 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ እቃዎችን ታክስ ሳይከፍል በቴሌ ስም ሲያስገባ በመገኘቱ ንብረቱ እንዲወረስ እንደሚደረግ ፎርቹን ጋዜጣ ዘግቧል። ቴሌ ለኩባንያው እቃዎችን እንዲያስገባ ፈቃድ አለመስጠቱን በመግለጹ ችግሩ ይፋ መውጣቱን ጋዜጣው ዘግቧል። ሁዋዌ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው በአይነት ከ235 በላይ እቃዎችን አስገብቷል፤ ይኸው ኩባንያ ከሶስት ወር በፊት የማስፋፋት ስራ ለመስራት በሚል …

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ካለፈው ስህተታቸው በመማር ከአጉልና ማስረጃ አልባ ፍረጃ እንዲላቀቁ አሳሰበ። ፓርቲው ከትናንት በስትያ ባወጣው መግለጫ እንደገለፀው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ባለፈው ሳምንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በመሪ ደረጃ በማይጠበቅ መልኩ የአንድነትን እንቅስቃሴ ስም ለማጥፋት በመሞከራቸው ከዚህ ድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል ብሏል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የራሳቸው አጀንዳ የላቸውም፣ የሻዕቢያ መልእክት አድራሾች […]

የቅሪተ አፅም እድሜ መለክያዉ እንዴት ነዉ፤ ረጅም እድሜ እንዳለዉ የሚነገረዉ ቅሪተ አፅምስ መገኛ ቦታዉ እንዴት ይታወቃል? ከመቶ ሽ በላይ እድሜ ያላቸዉን ቅሪተ አፅሞች እድሜ መለክያ ዘዴ እጅግ ቀላሉ ነዉ ያሉን ዶክተር ብርሃኔ አስፋዉ ሉሲ «ድንቅነሽ» ስትገኝ ከነበሩ ተመራማሪዎች መካከል አንዱ ነበሩ።

የዩናይትድ ሴቴትስ የአፍሪቃ እዝ አፍሪኮም ዋና አዛዥ ዴቪድ ሮድሪገዝ እና በአሜሪካን የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ሊንዳ ግሪንፊልድ አሜሪካ ከሰሃራ በስተደቡብ ከሚገኙ የአፍሪቃ ሃገራት

«የጀርመንና ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ጉባኤ » የተሰኘ ውይይት እዚህ ጀርመን ኮሎኝ ከተማ ውስጥ ባሳለፍነው ሣምንት ተሰናድቶ ነበር። በውይይቱ የኢትዮጵያ እና የጀርመን መንግሥት ባለስልጣናትን ጨምሮ የተለያዩ ባለሀብቶች እና እንግዶች ተሳትፈዋል።

ዕቃ ለማውጣት ቦሌ ወደሚገኘው የካርጎ ተርሚናል ሄጃለሁ፡፡ መቼም ዘመድ ውጭ ሀገር ያለው ሰው ደጋግሞ የሚሄደው አንድም ለወዳጁ እድሜ ከጤና ለመለመን ቤተ ክርስቲያን፣ አንድም የተላከለትን ዕቃ ለመውሰድ ካርጎ ተርሚናል፣ አንድም የዓመት በዓል ብር ለመቀበል ባንክ ቤት ነው፡፡

ወረፋውን ጠብቄ መስኮቱ ጋ ደረስኩና ስሜን አስመዘገብኩ፡፡ እስክትጠራ ጠብቅ ተብዬም ወንበር ፈልጌ ተቀመጥኩ፡፡ ከጎኔ አንድ ጎልማሳ ተቀምጦ ይቁነጠነጣል፡፡ አንዴ ፀጉሩን አንዴ ዓይኑን ያሻል፡፡ ኩኩሉ እንደሚል አውራ ዶሮ አንገቱን ከወዘወዘ በኋላ ወደ እኔ ዞር አለና ‹‹ስምህ ናፍቆህ ያውቃል›› አለኝ፡፡

ገረመኝና ‹‹ስሜማ አብሮኝ ነው የሚኖረው፤ ምን ብሎ ይናፍቀኛል›› አልኩት፡፡

‹‹ስምህን ሰጥተህ አታውቅም፤ አሁን ስምህን አልሰጠህም እንዴ›› አለኝ፡፡

ይበልጥ ግራ ገባኝና ‹‹እና ወሰዱት ማለት ነው›› አልኩት ሳቅ እያፈነኝ፡፡

‹‹ታድያስ፤ አሁንኮ ወሳኙ እነርሱ ጋር ያስመዘገብከው ስምህ እንጂ አንተ ጋ ያለው ስምህ አይደለም፡፡ አንተ እገሌ መሆንህ ቁም ነገር የለውም፡፡ እነርሱ ‹እ-ገ-ሌ› ብለው ሲጠሩህ ነው ሕይወትህ የሚንቀሳቀሰው፡፡ እኔ አሁን ስሜ ናፍቆኛል፡፡ ስሜ ሲጠራ መስማት፣ ስሜ ሲጠራ አቤት ማለት ናፈቀኝ፡፡››

የእርሱን ስሰማ እኔም ስሜ ይናፍቀኝ ጀመር፡፡ ‹‹ትጠራላችሁ›› አይደል ያሉን፤ እውነትም ስማችንን ወስደውታል ማለትኮ ነው፡፡ ካልጠሩን ቁጭ ብለን መቅረታችን ነው፡፡ የተጠሩት ደግሞ እየተፍነከነኩ ወደ መስኮቱ እየተጠጉ ነው፡፡ ሰልፉ ሲረዝም፣ ጊዜው ሲሄድ፣ መቀመጥም ሲሰለቻችሁ ደግሞ ስማችሁ ይበልጥ ይናፍቃችኋል፡፡

‹‹እዚህ ብቻ ነው ወይስ ሌላውም ቦታ ወረፋ አለው›› አልኩት፡፡

‹‹ምን እዚህ ብቻ ኑሮህኮ እንደዚሁ ነው፡፡ ስም ትሰጣለህ፣ ትጠብቃለህ፣ ስምህን ትናፍቃለህ፣ እድለኛ ከሆንክ ትጠራለህ፣ አቤት ትላለህ፣ ወደ ሌላው ምእራፍ ትሻገራለህ፡፡ እዚያም ስም ትሰጣለህ፣ ስም ትናፍቃለህ፣ ትጠራለህ፣ አቤት ትላለህ፣ እንዲህ እያልክ ትኖራለህ፡፡ አቤት ካላልክ ደግሞ ችግር ነው፡፡ ያልፍሃል፡፡ አሁን ያ ሰውዬ ስልክ እያወራ አለፈው፡፡ ‹አቤት› ማለት ነበረበት፡፡ አሁን እንደገና ስሙ እየናፈቀው ነው፡፡ ያኛው ደግሞ ስሙ ቢናፍቀው፣ ቢናፍቀው የሚጠራው አጥቷል፡፡እየደጋገመ ‹ጥሩኝ እንጂ› ይላል፡፡‹ቆይ እንጠራሃለን› ይሉታል፡፡ አሁን አንተን በስልክ ጠርተውህ ነው አይደል የመጣኸው? አሁን ይኼ ጋቢ ነገር የለበሰው ሰው ለምን አትጠሩኝም ብሎ ነው ከክፍለ ሀገር የመጣው፡፡ ስሙ ናፍቆት፡፡ ልጁ ደውላ ዕቃ ልኬልሃለሁ አለቺው፡፡ እርሱ ካሁን አሁን ስሜ በስልክ ይጠራል ብሎ ቢጠብቅ ቀረበት፡፡ ስሙ ሲናፍቀው መጣና ‹እባካችሁ ጥሩኝ› አለ፡፡ እነርሱ ደግሞ ‹ሀገርህ ተመለስና ስንጠራህ ትመጣለህ› ይሉታል፡፡ ስሙ የናፈቀው ሰው መች እንዲህ በቀላሉ ይመለሳል፡፡››

‹‹እውነትምኮ ስም የሚያስናፍቁ አሠራሮች ሞልተዋል›› አልኩት ለመጎትጎት

‹‹ቤት ለማግኘት ትመዘገባለህ፣ ስምህ ይናፍቅሃል፡፡ ጋዜጣ ላይ ወጣ፣ ተለጠፈ፣ በሬዲዮ ተነገረ በተባለ ቁጥር ስምህን ማየት ትናፍቃለህ፡፡ እዚያ ዝርዝር ውስጥ ስታጣው ቅር ይልሃል፡፡ ስኳር ለማግኘት ትመዘገባለህ፣ ከሻሂው ሱስ ይልቅ ስምህን የመስማት ሱስ ይይዝሃል፡፡ ሥራ ለማግኘት ትመዘገባለህ፣ እንጠራሃለን ስትባል ትጠብቃለህ፤ ከዚያ ስልክ ባቃጨለ ቁጥር እመር ብለህ ትነሣለህ፤ የሆነ ሰው ስምህን ሲጠራው፣ አንተም አቤት ስትል ለመስማት ትናፍቃለህ፡፡ ጓደኛህ ደውሎ በቅጽል ስምህ ከጠራህ ትናደዳለህ፡፡ አንተ የምትጠብቀው ‹አቶ እንትና ነዎት› ተብሎ ሲጠራ መስማት ነዋ፡፡ ››

‹‹ቆይ ግን ለምን ይመስልሃል ስማችን እስኪናፍቀን የምንደርሰው››

‹‹አንደኛ ለምዶብናል፡፡ ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ ስም ጠሪ መምህር ተመድቦ ስም መጥራት ተለምዷል፡፡ ዕድር ላይ ይጠራል፤ ፍታት ላይ ይጠራል፤ ዕቁብ ላይ ይጠራል፤ ቡና ለመጠጣት ይጠራል፤ እሥረኛ ለመጠየቅ ይጠራል፤ ቪዛ ለመጠየቅ ይጠራል፤ ስም መጥራት ባህላችን ሆኗል፡፡ ሁለተኛ ደግሞ ስማቸው የሚጠራና የማይጠራ ስላሉ ነው፡፡ ስማቸው ሊጠራ የሚችል፣ ስማቸው የማይጠራና ስማቸው ሳይጠራ እንደተጠራ የሚቆጠሩ አሉ፡፡ ስማቸው ሊጠራ የሚችለው እንደ እኔና አንተ ያሉት ናቸው፡፡ ዕድል ካለህ ስምህ ይጠራል፡፡ ስማቸው የማይጠራው ደግሞ አንዳች ምክንያት የሚኖራቸው ናቸው፡፡ ስማቸው መጠራት የማያስፈልጋቸው ደግሞ ጉዳያቸው በውስጥ የሚያልቅላቸው ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ስማቸው የወርቅ ቁልፍ ነው፤ ብዙ ቢሮዎችን ይከፍታል፤ ወይም ደግሞ የወርቅ ቁልፍ ያንጠለጠለ ስም የሚያውቁ ናቸው፡፡ አንዳንዴኮ ስምን መናፈቅ ይሻላል፡፡ ጭራሽ ስምህ ይጠፋልኮ››

‹‹አንተ ዋናው ክፉ አትሥራ እንጂ ስምህ ቢጠፋ ምን ችግር አለው? ከባሰ በሕግ መጠየቅ ነው››

‹‹ኖ ኖ ኖ ኖ ኖ እንደዚያ አይደለም፤ ስምህ ከነ ጭራሹ ከመዝገብ ላይ ይጠፋል እንጂ፤ ስምህ አልተመዘገበም፤ ‹ዳታ› ውስጥ የለም፡፡ ኮምፒውተር ውስጥ አልገባም፤ መዝገብ ላይ አልተገኘም፤ ፋይሉ ጠፍቷል፤ ትባላለህ፡፡ አንዳንዱ ስምማ ይገርምሃል እንደ ቁልፍ ማንጠልጠያ ወልቆ የሚጠፋ ነውኮ የሚመስለው፤ በተመዘገበበት ቦታ አታገኘውም፡፡ አሁን የእኔ ስም ዕድር ልከፍል ከሄድኩ አንደኛ ነው የሚጠራው፤ ስኳር ልወስድ ከሄድኩ ግን ጭራሽ ሳይጠራ ሊቀር ይችላል፡፡ ለክፍያና ለመዋጮ ብቻ የታደሉ ስሞች አሉ፡፡ ለመቀበል ብቻ የታደሉ ስሞችም አሉ፡፡ ሁለቱንም ስሞች በየመዝገባቸው ነው የምታገኛቸው፡፡ አንተ አንዴ እንኳን ስምህ አልጠራ ብሎህ እየናፈቀህ አንዳንድ ሰዎች ሁለትና ሦስት ጊዜ ስማቸው ሲጠራ ስታይ፣ ስም የሌለህ ሁሉ ይመስልሃል፡፡››

‹‹ግን ለሥራና ለስም የታደሉ ሰዎች የሉም››

‹‹ሞልተው፤ አሁን እኛ ሀገር ሊቅ፣ ሳይንቲስት፣ እውነተኛ ነጋዴ፣ ባለሞያ፣ ሥራ ፈጣሪ፣ ገበሬ፣ ምናምን ለስም ያልታደሉ ናቸው፡፡ ስማቸውን የደመወዝ መክፈያና ግብር ሰብሳቢ ብቻ የሚያውቀው፤ አርቲስት፣ ዘፋኝ፣ ቀልደኛ፣ ደግሞ ለስም የታደሉ፡፡ እስኪ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የአንድ ሳይንቲስት ቤት ዓመት በዓል ሲያከብር አይተህ ታውቃለህ? የአንድ የረዥም ርቀት አሽከርካሪ ቤት ገብቶ ኑሮውን ሲያስቃኝ አይተህ ታውቃለህ? እነዚህ ለስም ያልታደሉ ናቸው፡፡ አንዳንዴ ደግሞ ሥራውን የሠሩት፣ የደከሙት፣ የለፉት ስማቸው ሳይጠራ መጨረሻ ላይ የሚጨመሩ ቅመሞች ስማቸው ሲጠራ ትሰማለህ፡፡›› 

ይህንን እያወራልኝ በድምጽ ማጉያ ስም መጥራት ተጀመረ፡፡ አምስት ሰዎች ተጠሩ፡፡ አብሮኝ የነበረው ሰው ግን አልተጠራም፡፡ በድምጽ ማጉያው ‹መሐሪ ተሾመ› የሚል ስም ሲጠራ ከእኛ ፊት ለፊት ባለው ወንበር ላይ የተቀመጠው ሰው ‹ወንድ ከሆንሽ መሐሪ አስቻለው ብለሽ አትጣሪም›› አለ፡፡

‹‹መሐሪ አስቻለው ብሎ መጣራት የወንድነት መለኪያ ሆነ እንዴ›› አልኩት

‹‹መሐሪ አስቻለው እኔ ነኛ››

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የወጣ ነው

ጥቅምት ፲፪(አስራ ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በጉባኤ ላይ የተሳተፉ አንድ የሀይማኖቱ አስተማሪ ፣ የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ  ጉባኤ በ፴፪ኛው ዓመታዊ ስብሰባው ያወጣው መግለጫ ፣ በስብሰባው ላይ የተነሱትን ነጥቦች ዘርዝሮ አቀረበ ነው ብለዋል። ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሀይማኖት አባቶች በድፍረት መናገራቸው ከምን የመጣ ይመስለውታል ተብለው የተጠየቁት መምህሩ፣ ምናልባትም ለውጡ ከፓትርያርኩ ጋር የተያያዘ ሳይሆን …

ጥቅምት ፲፪(አስራ ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነባር የህወሀት ተጋይ የነበሩትና በአሁኑ ጊዜ በገዢው ፓርቲ ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው የሚገኙት ታዋቂው ታጋይ አቶ አስገደ ገብረስላሴ ፣ ልጆቻቸው በከፍተኛ ስቃይ ላይ እንደሚገኙ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ገልጸዋል። የማነ  የተባለው ልጃቸው፣ በእስር ቤት ላይ በደረሰበት ግፍ ምክንያት አካል ጉዳተኛ ሆኗል። አህፎም ደግሞ ከስራ ገበታው ላይ ታፍኖ ከተወሰደ በሁዋላ፣ …

ጥቅምት ፲፪(አስራ ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ መድረክ በስዊድን የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኒታን በተመለከተ በተለይም በቅርቡ በስዊድን ቴሌቪዥን  የኦጋዴን ህዝብ ጭፍጨፋ አስመልክቶ ያሳየውን ዶክመንትሪ ፊልም የተመለከቱ የስዊዲን የህግ ጠበቃና የአለም አቀፍ የህግ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጁሪስት ስቴላ ያርዴት የመንግስት ባለስልጣናትን በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት ለመክሰስ እንደተዘጋጁ በማስታወቃቸው እሳቸውንና ሌሎችን እንግዶች በመጋበዝ ኖቬምበር 2 ቀን 2013 …

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም Prof. Mesfin Woldemariamፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

በአሥራ አምስተኛው ምዕተ-ዓመት ግድም ሆላንድ የታወቀ የባሕር ኃይል ሆኖ ከደቡብ አፍሪካ እስከደቡብ አሜሪካ፣ የኔዘርላንድ የቆዳ ስፋት 41 526 ኪ.ሜ. ካሬ ወይም የትግራይ ግማሽ ነው፤ የሕዝቡም ቁጥር አሥራ ስድስት ሚልዮን ተኩል አይሞላም። የትግራይን ግማሽ በሚሆን መሬት ላይ የትግራይን ሦስት እጥፍ ግድም የሚያህሉ ሰዎች ይኖሩበታል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ፓርቲያችን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ በሀገራችን ላይ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲሰፍንና ፍትሃዊነት እንዲኖር በቁርጠኝነት እየታገለ ይገኛል፡፡ በትግሉ ውስጥም ፓርቲያችን የተጋረጡበትን ፈተናዎች እየተወጣና የሚከፈለውን ዋጋ እየከፈለ ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ በመቀጠል ለህዝቡ ያለውን ታማኝነት እያረጋገጠም ነው፡፡ ፓርቲያችን በመላ ኢትዮጵያ ያለውን አደረጃጀት በመጠቀምና ሕዝቡን በማሳተፍ ለሶስት ወራት የሚቆይ ህዝባዊ ንቅናቄ በማካሄድ የመጀመሪያ ዙር የሆነውን ሰላማዊ […]

በሙሥና የተጠረጠሩ ክሥ ተመሠረተባቸው
የኢትዮጵያ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን አቃቢ ሕግ በሙስና የተጠረጠሩ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና ዕውቅ ነጋዴዎች ላይ ትናንት ክሥ መሥርቷል።

በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አሥራ አምስተኛ የወንጀል ችሎት ትናንትና ዛሬ በዋለው ችሎት የቀድሞ የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታና ምክትላቸው የነበሩት የአቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ፣ የሃገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ የነበሩት አቶ ወልደሥላሴ ወልደሚካኤል፣ እንዲሁም አንዳንድ ከፍተኛ ነጋዴዎች በሃገሪቱ ላይ በመቶዎች ሚሊዮን ብር የሚገመት ጉዳት በማድረስ ተከስሰዋል።

የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በሦስት የተለያዩ መዝገቦች፤ ባጠቃላይ በአርባ ሁለት ተጠርጣሪዎች ላይ ከመቶ በላይ ክሦችን መመሥረቱ ታውቋል።

ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና …

የኢትዮጵያ መንግስት ቢያንስ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ስራ ፈላጊዎችን ወደ ሳውዲ አረቢያ እንዳይገቡ ማገዱን ኣስታወቀ።
በዚሁ መሰረት 40 ሺሽ ያህል ቀደም ሲል የተፈቀዱ ቢዛዎችም ተሰርዘዋል።

የጀርመን መከላከያ ሚኒስቴር የጀርመን የአፍጋኒስታን ኩንዱዝ ተልዕኮ ማብቃቱን ባለፈው ቅዳሜ አስታውቋል። የጀርመን ጦር ኩንዱዝን ሙሉ ለሙሉ ለቆ መውጣት የአካባቢውን ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን ለጦሩ የተለያየ አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ አፍጋናውያንን አስግቷል ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ለአሥር ቀናት በመላ ሀገሪቱ እና ከሀገር ዉጪ የሚገኙ አብያተክርስቲያናት ተወካዮች በተገኙበት የሀገረ ስብከቱን ጳጳሳት ጠርታ በውስጧ ስላሉ ችግሮች አወያይታለች።

በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የካንሰር ታማሚዎች ቁጥር እየጨመረ በመሄድ ላይ መሆኑን የዓለም የጤና ድርጅት ይገልጻል። ድርጅቱ አያይዞም በጎርጎሪዮሳዊዉ 2020ዓ,ም 65 በመቶ የሚሆኑ የካንሰር ታማሚ በአዳጊና በማደግ ላይ በሚገኙ ሃገራት እንደሚገኝ ከወዲሁ ጠቁሟል።