መንግስት የግል መጽሄቶች የህትመት ቁጥር መጨመር ስጋት ላይ እንደጣለው ታወቀ::

መንግስታዊዎቹ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና በአሁኑ ወቅት በመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት ስር በአንድ መመሪያነት የሚሰራውና በአዋጅ በፈረሰ ስም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እየተባለ የሚጠራው ድርጅቶች በጋራ አጥንተናል ባሉትና ሰባት ያህል መጽሄቶች ሕግና ስርዓትን በመተላለፍ እየሰሩ መሆኑን የሚያውጀው ጥናት መነሻ የመጽሄቶቹ ቁጥር መጨመር ገዢውን ፓርቲ ስጋት ላይ በመጣሉ መሆኑን የኢሳት ምንጮች ገለጹ።

ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች እንደጠቆሙት በጽንፈኝነት ከተፈረጁት ሰባቱ መጽሔቶች ማለትም ሎሚ፣ፋክት፣አዲስጉዳይ፣ዕንቁ፣ቆንጆ፣ሊያ እና ጃኖ መጽሔቶች መካከል አብዛኛዎቹ ሳምንታዊ የህትመታቸው መጠን ከጊዜ ወደጊዜ እያደገ መምጣትና የሚጽፉአቸውም ርዕሰ ጉዳዮችም ገዥውን ፓርቲ አጠንክረው የሚተቹ መሆን በተለይ ከመጪው ዓመት አገር አቀፍ ምርጫ ጋር በተያያዘ ኢህአዴግን ስጋት ላይ ጥለውታል፡፡

መጽሄቶቹ ለጥናት ሲመረጡ ቀድሞውኑ ውጤቱ ይታወቅ ነበር ያሉት ምንጮቹ ፣ በጥናቱ ተገኘ የተባለው ውጤት ባለስልጣናቱ በየጊዜው ሲሉት የነበረና በአዲስዘመን ጋዜጣ አጀንዳ ኣምድ ላይ በተከታታይ ሲጻፉ የነበሩ ትችቶች ናቸው ብለዋል፡፡ መንግስታዊ ተቋማቱ የጀመሩት ጥናት ገና አለመጠናቀቁንና ከጅምሩ ተቆንጥሮ እንዲለቀቅ የተደረገው በሁዋላ መንግስት ለሚወስደው እርምጃ ከወዲሁ ህጋዊነትን ለማላበስ ታስቦ ነው ሲሉ አስረድተዋል፡፡ ጥናቱ ገና ሳይጠናቀቅና ድምዳሜው ሳይታወቅ ውጤቱ ይፋ መደረጉም መንግስት ሚዲዎቹን ለመወንጀል የቱን ያህል እንደቋመጠ የሚያሳይ ነውም በማለት አክለዋል፡፡

ባለፈው ሳምንት ረቡዕ በአዲስዘመን ጋዜጣ የፊት ገጽ ላይ የታተመው ዘገባ እንደሚሳየው ሰባቱ መጽሔቶች ከመስከረም እስከ ህዳር 30/2006 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት ባወጡዋቸው ዘገባዎች የጽንፈኛ ድርጅቶች ልሳናት መሆናቸውን፣ሕገመንግስቱን እንደሚጥሱ፣ሽብርተኝነትን እንደሚያበረታቱ፣የተሳሳቱ መረጃዎች ሕዝቡ በስርዓቱ ላይ እምነት አጥቶ ለአመጽ እንዲነሳሳ እንደሚደርጉ በጥናት ደርሰንበታል መባሉና ኢሳትም ይህንኑ በዕለቱ መዘገቡ ይታወሳል፡፡
የብሮድካስት ባለስልጣን በታህሳስ ወር 2006 ባወጣው ሪፖርት መሰረት ፋክት መጽሔት በወር 62 ሺ ኮፒ በማሳተም የሚመራ ሲሆን ሎሚ 55ሺ፣ አዲስጉዳይ 51 ሺ ኮፒዎችን በማሳተም ይከተላሉ፡፡ ቆንጆ 7ሺ፣ ዕንቁ 6ሺ 400፣ጃኖ 4ሺ ሲያሳትሙ ሊያ የተባለችው መጽሔት በታህሳስ ወር ምን ያህል ኮፒ እንደታተመች ባለስልጣኑ በመረጃው አላካተተም፡፡
ምንም አይነት ግሳጼ ካልደረሰባቸው ሳምንታዊ ጋዜጦች መካከል ሪፖርተር የእሁድ እትሙ 11 ሺ፣ ፣ አዲስ አድማስ 8 ሺ 700፣ ሰንደቅ 1 ሺ 933፣ ኢትዮ ቻናል፣ 1 ሺ 737 ያሳትማሉ። ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና

የመከላከያ መኮንኖች በአ.አ ፖሊስ ተመደቡ::
የአዲስ አበባ ፖሊስ ከጨዋታ ውጭ እንደሚደረግ ምንም ጥርጥር የለውም ::
በአዲስ አበባ ለጤና አገልግሎት የተሰሩ ክሊኒኮች ወደ እስር ቤትነት ተቀየሩ ::

በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስሩ ክፍለ ከተሞች የመከላከያ መኮንኖች ተዛውረው መመደባቸውን ታማኝ የቅርብ ምንጮች ገለፁ። የሕወሐት አባላት የሆኑትና ከመቶ አለቃ እስከ ሻለቃ ደረጃ ያላቸው የመከላከያ መኮንኖች የአዲስ አበባን ፖሊስ በበላይነት እንዲቆጣጠሩ በአስሩም ክፍለ ከቶሞች የመምሪያ ሃላፊ ተደርገው መሾማቸውን ምንጮቹ አስታውቀዋል።

ከዚሁ ጎን ለጎን በአዲስ አበባ በሚገኙ ወረዳዎች “ኮሚኒቲ ፖሊስ” በሚል አዳዲስ የፌደራል ፖሊሶች እንደመተደቡ ምንጮቹ አያይዘው ገለፀዋል። በአዲስ አበባ ፖሊስ ሃይል እምነት ያጣው ገዢው ፓርቲ ሕወሐት/ኢህአዴግ ታማኝ በሚላቸው መኮንኖችና የፌደራል ፖሊሶች እየተካና አፈናውን እያጠናከረ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮቹ አክለውም አሁን በተጀመረው የክልሉን ፖሊስ የማፍረስ ተግባር በቅርብ ጊዜ የአዲስ አበባ ፖሊስ ከጨዋታ ውጭ እንደሚደረግ ምንም ጥርጥር የለውም ብለዋል።

ገዢው ፓርቲ ራሱ በደነገገው ሕገ-መንግስት ላይ ፖሊስ ፀጥታውን እንደሚቆጣጠር እንዲሁም መከላከያ ገለልተኛ ሆኖ የአገሩን ሉአላዊነት እንደሚጠብቅና ከማንኛውም ፖለቲካ ድርጅት ነፃ ሆኖ እንደሚቆም አዋጁ የሚገልፅ ቢሆንም ነገር ግን ራሱ ላወጣው ሕገ መንግስት ተገዢ መሆን እንዳልቻለ የሕወሐት መኮንኖች ከመከላከያ ተዛውረው የአዲስ አበባን ፖሊስ በበላይነት እንዲመሩና እንዲቆጣጠሩ መመደባቸው የህግ ጥሰት እያካሄደ እንደሆነ በቂ ማስረጃ ነው ብለዋል ምንጮቹ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአዲስ አበባ ለጤና አገልግሎት የተሰሩ ክሊኒኮች ወደ እስር ቤትነት እየተቀየሩ መሆኑን ምንጮች አጋልጠዋል። በአዲስ አበባ የካና አራዳ ክፍለ ከተሞች “ኬርና ፕላን” በተባሉ ግብረሰናይ ድርጅቶች የተሰሩት ጤና ጣቢያዎች ወደ ፖሊስ ጣቢያነት ተቀይረው እስረኞች እየታሰሩባቸው መሆኑን አረጋግጠዋል። በየካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 06/07 ቤላ፣ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ቀበሌ 11 እንዲሁም ጃንሜዳ ቀበሌ 05 የሚገኙ ጤና ጣቢያዎች በከፊል እንደሚጠቀሱ ያስታወቁት ምንጮቹ በተጠቀሱት ቦታዎች እስረኞች በብዛት ታስረው እንደሚገኙ አያይዘው ገልፀዋል።

የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር በእንግሊዝኛ ምህጻሩ «ኦ ዲ ኤፍ» ወደ ኣገር ቤት ተመልሶ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል መወሰኑን ኣስታወቀ። ‪የግንባሩ ፕሬዝደንት አቶ ሌንጮ ለታ እንደገለጹት ግንባሩ ከምስረታው ኣንስቶ ወደ ኣገር ቤት ለመመለስ ግልጽ አቐም ይዟል። ለኢትዮጵያ ህዝቦች አዲስ ራዕይ ኣለኝ የሚለው የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ህጋዊ መሰረት ያለው ኣገራዊ ኣንድነትን ለመመስረት እንደሚሰራም ኣስታውቐል። «ኦ ዲ ኤፍ» በይፋ ከተመሰረተ ገና ኣንድ ዓመቱ ሲሆን ፕሬዝደንቱ አቶ ሌንጮ ለታ ለረጅም ጊዜ የዓማጺው ኦሮሞ ነጻነት ግንብር ከፍተኛ ዓመራር አባል እንደነበሩ ኣይዘነጋም።

object Podcast

ያደግነው/የተነገረን እና ካደግን በኋላ/የምናየው/የምንሰማው ስለአገራችን የውጭ ዜጎች ይኖራቸዋል ብለን የምናስበው አመለካከት አናት የሚበጠብጥ ነው፡፡ እኛ ጀግና ሕዝቦች፣ የድንቅ ቅርስና የተፈጥሮ ሀብት ባለቤት፣ እንግዳ ተቀባይ፣ ኩሩ፣ ምናምን… እንባላለን ብለን ስናስብ ኢትዮጵያን ከጎበኟትም፣ በስም ብቻ ከሚያውቋትም ሰዎች የምንሰማው (ወይም የአገራችንን ስም ሲሰሙ ወደህሊናቸው የሚመጣው) ድህነታችንን፣ በዚሁ ሳቢያ በየሰዉ አገር ስደት መሰማራታችን፣ በጦርነት መባላታችንን … ነው፡፡  ሌላው ቀርቶ ዘወትር የምንዘምርላቸውን ሥነ-ሕንፃዎቻችንን እንኳ የሚያውቁ ጥቂቶች ናቸው፤ እነርሱን ሊጎበኙ መጥተው ዘግናኝ ድህነታችንን እና የከተማ ስርዓታችንን ስርዓት አልበኝነት ብቻ በትዝብት እያስታወሱ የሚኖሩ እልፍ ናቸው፡፡
ምናልባት ብዙ የውጭ ዜጎች የሚስማሙበት ሁለት ነገሮች ቢኖሩ የሴቶቻችንን ቁንጅና እና የቡናችንን አሪፍነት ነው፡፡ በነገራችን ላይ፣ የኢትዮጵያ እና ሊቢያ ጨዋታ በደቡብ አፍሪካ ሲካሄድ ‹ኮሜንታተሩ› ስለኢትዮጵያውያን ደጋፊዎች መልካምነት (ብሎም መልከ መልካምነት) ሲያወራ ስሰማ ምንም እንኳን ለኳስ እምብዛም ብሆንም ከዕለት ዕለት በልቤ እየደደረ የመጣውን የመልካም ስም ናፍቆት ቆሰቆሰው – “ምናለ ኳሱን በድል ወጥተው ረሀባችን ባይረሳም እንኳ ከጎኑ፣ መልከ መልካምነታችን፤ ልክ እንደሩጫው ኳስ ተጫዋችነታችን ገጽታችን (brand) ቢሆንልን?” እያልኩ የዋህ ምኞት እመኛለሁ!
ኢትዮጵያውያን ለውጭ ዜጎች
ለዚህ ጽሑፍ ማሳያ የሚሆነኝን ነገር ከጉግል ፍለጋ ላይ ነው ይዤ የመጣሁት፡፡ Ethiopia እና Ethiopian People የሚሉትን ሁለት ቃላቶች በጉግል ምስል ውስጥ አስሳችሁ የምታገኙት የማታውቋትን (ቢያንስ የማታስቧትን) ኢትዮጵያ ቢሆንም እንኳ – የውጭ ዜጎች የሚያስቧትን ኢትዮጵያ ነው፡፡ ከካርታው ውጪ ራቁታቸውን ያሉ ሰዎች፣ የተራቡ ሰዎች፣ የተጎሳቆሉ መንደሮች ምስል ነው፡፡ ማነፃፀር ካሻችሁ ደግሞ ብዙም ሳትርቁ የዛሬ ጎረቤታችን የKenyaን እና Kenyan People የጉግል ምስል ሐሰሳ ውጤት ተመልከቱ – የሚያምሩ የመሬት አቀማመጦች እና የዱር እንስሳት፣ በሚያማምሩ የባሕል ልብሶች ያጌጡ ሕዝቦች ይመጡላችኋል – የዛሬ ሃምሳ ዓመት ነጻ የወጣችው፣ የኛን ግማሽ ሕዝብ ብቻ ያላት ኬንያ የጉግል ገጽታ የእኛን ያስከነዳል፡፡

በይነመረብ ላይ የተለያዩ ወደኢትዮጵያ ለሚደረጉ ጉዞዎች የተሰጡ ምክሮችን  ሳነብ ይህንኑ ነው የሚነግሩኝ፡፡
ይህ የሆነው ለምንድን ነው? ገጽታችንን በአግባቡ ስላልገነባን? የእኛን መልካም ገጽታ ሊያጠፉ የሚፈልጉ ስላሉ? ወይስ፣ እኛ ውስጡ ስላለን የማይታወቀን (የማይሸተን) እውነታ ስለሆነ?
በግሌ በጉግል ምስል ሐሰሳ ላይ የምትመጣዋን ኢትዮጵያ ያክል የከፋን ነን ብዬ አላስብም፣ ነገር ግን ያንን ያክል ያልከፋን ነን ብዬ ለማለት የሚያስችለኝ በቂ መረጃ የለኝም፡፡ እያደግን ነው እንዳልል፣ ዛሬም ገበሬው ከበሬ ትከሻ ላይ አልወረደም፡፡ እያደግን አይደለም እንዳልል ከተማ ውስጥ ብልጭልጭ አያለሁ፡፡ የብልጭልጩንም ባሰብኩ ቁጥር የኔ ሰፈር (ፈረንሳይ ለጋሲዮን) እና ቦሌን ሳወዳድር አሁንም ያው የድሮው ይሆንብኛል፡፡ ልጅ እያለሁ ቦሌ የሀብታም ሰፈር ነው፣ አሁንም የኔ ልጆች ለሚሆኑ የሰፈሮቼ ልጆች ቦሌ የሀብታም ሰፈር ነው፡፡ ከፈረንሳይ ለጋሲዮን እስከ አራት ኪሎ በቅርብ ጊዜ (እንበል በሁለት ዐሥርት ዓመታት) የተገነባ ሕንፃ የለም፣ የተሠራ አዲስ መንገድ የለም (አሁን አንዱ ተስተካክሎ እየታደሰ ነው)፣ የነዋሪው ቁጥር ግን ከእጥፍ በላይ ጨምሯል፡፡ የሚያሳዝነው ጉዳይ በከተማችን ካሉ ቦሌዎች ቁጥር የፈረንሳይ ለጋሲዮኖች ቁጥር ይበልጣል፡፡ ቦሌዎችም ወደላይ መመንደጋቸውን ሌሎቹም ወደታች መቆርቆዛቸውን የሚያስረግጡ እንጂ የማያስረግጡ መረጃዎች የሉኝም፡፡

ቦሌ እና ሌሎችም አካባቢዎች የሚሠሩ ሕንፃዎችን ሳይ ተስፋ ይታየኛል፤ የባቡር መንገድ ዝርጋታው፣ ሌላው ሌላውም እንደሚታከክ ቁስል ያለ ደስታ ይሰጠኛል፤ የማያድን ብቻ የሚያስታምም ዓይነት! ቢያንስ ለገጽታችን እንኳን አሪፍ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ውስጤ ግን እውነቱን ያውቀዋል፤ ሕዝብ ገጽታ እየበላ አይኖርም፡፡ ያ – የጉግል ሐሰሳ ላይ የሚመጣው የተራበ ሰው ሆድ በመስታወት ሕንፃ አይሞላም፡፡ በተለይ ደግሞ ባለሥልጣናት እንደነጋዴ ሕንፃ እንደሚገነቡ ትዝ ባለኝ ቁጥር የዚያ ሰው ረሀብ ለጥቂት ጥጋበኞች ሕንፃ ያቆማል እንጂ መቼም እንደማይቆም ይገባኛል፤ ተስፋ ያስቆርጠኛል፡፡

‹‹ዐይናችን፣ ጆሯችንና ልባችን የቤተ ክርስቲያናችንን ህልውና በሚወስነው የአደረጃጀትና አሠራር ለውጥ ተግባራዊነት ላይ ነው፤ የቤተ ክርስቲያናችን ትንሣኤ ደርሷል ብለን እናምናለን፡፡›› /ምእመናን/ ‹‹ከእውነተኛ የቤተ ክርስቲያኒቷ ጥቅም ወዲያና ወዲህ አልልም፤ አትጠራጠሩ! ሕጉ የጠራ ኾኖ በትክክሉ ይወጣል፤ ቤተ ክርስቲያናችን ወደቀደመ ክብሯ ትመለሳለች፡፡›› /ፓትርያርኩ/ *                              *                             *  (ሰንደቅ ጋዜጣ፤ 9ኛ ዓመት ቁጥር 436፤ ጥር 07 2006 ዓ.ም.) …

ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ አማካሪ የሆኑት አቶ በረከት ስምዖን በቅርቡ ከሚኒስትሮች እና ከኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ባደረጉት ውይይትና ግምገማ ላይ ” ህዝቡን ለመምራት የሚነደፉ ንድፈ ሀሳቦች ( ቲዮሪዎች) በየጊዜው ካልተሻሻሉ የሚዝጉ በመሆናቸው አብዮታዊ ዲሞክራሲ በልማታዊ ዲሞክራሲ እንዲተካ ተደርጓል ብለዋል። የኢህአዴግ መንግስት ይበልጥ የሚገለጸው በአብዮታዊ ዲሞክራሲ አስተሳሰብ …

ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መንግስታዊዎቹ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና በአሁኑ ወቅት በመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት ስር በአንድ መመሪያነት የሚሰራውና በአዋጅ በፈረሰ ስም የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እየተባለ የሚጠራው ድርጅቶች በጋራ አጥንተናል ባሉትና ሰባት ያህል መጽሄቶች ሕግና ስርዓትን በመተላለፍ እየሰሩ መሆኑን የሚያውጀው ጥናት መነሻ የመጽሄቶቹ ቁጥር መጨመር ገዢውን ፓርቲ ስጋት ላይ በመጣሉ መሆኑን …

ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኮሚሽኑ በደብዳቤው የኢህአዴግ መንግስት ሰፊ የሆነውን የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት የሚያደርገውን እንቅስቃሴ የመንግስትታቱ ዋና ጸሀፊ እንዲያዩት ጠይቋል። ገዢው ፓርቲ በሱዳን ውስጥ ተቃዋሚዎች የመደራጃ ቦታ እንዳያገኙ በሚል ከሱዳን ጋር ተቀባይነት የሌለው የድንበር ውል እያደረገ መሆኑንም ኮሚሽኑ ገልጿል። የአፍሪካ ቀንድ በዚህ መሬት የተነሳ ለሌላ ግጭት ሊዳረግ እንደሚችል …

ጥር ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት በመተረክ ላይ ባለው በታጋይ መዝሙር ፈንቴ ተርጓሚኒት  በአቶ ዳንኤል ግዛው ጸኃፊነት የቀረበው መጽሀፍ  በአማራ ህዝብ  ላይ  ጥላቻ እንዲፈጠር እያደረገ ነው በማለት የብአዴን አባላት ተቃውመውታል። አባላቱ በብር ሸለቆ በመካሄድ ላይ ባለው ስልጠና ላይ  እንደተናገሩት ሬዲዩ ፋና ታሪካዊ ስህተት እየፈጸመ ነው ፡፡ “የህውሃት ድብቅ አላማ …

«በሕገ መንግስቱ የመደራጀት መብታቸው የተጠበቀላቸው ፓርቲዎችን አልከሰስንም።ፓርቲዎችን ግን ሽፋን አድርገዉ ስርዓቱን ወይንም ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን ለመናድ እንቀሳቀሳለን የሚሉ ኃይሎችን ግን ዛሬም ፣ ነገም ፣ ሕጉን የማስከበር ግዴታና ሃላፊነት ስላለብን ከመከሰስ አያመልጡም ማለት ነዉ።» ኢቲቪ በቅርቡ በ«ሽብርተኝነት» ላይ፣ በቅርቡ ባቀረበዉ አሳዛኝ ዶኩሜንተሪ ላይ ፣ የፌደራል መንግስት አቃቤ ሕግ፣ አቶ ብርሃኑ ወንድማገኝ የተናገሩት ነበር። እኝህ የሕግ ባለሞያ […]

ከ7 ሳምንት በፊት ነበር ሶስት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የቤልጄምን ጦር ኃይል በፍርድ ቤት የከሰሱት። ይህም እኢአ በ2011 መጋቢት ወር ከሊቢያ ትሪፖሊ 72 ሰዎችን አሳፍራ ወደ ላምፔዱዛ ስትጓዝ የነበረች አንዲት ጀልባ የማዕበል አደጋ ከደረሰባት በኋላ በአካባቢዉ ከነበሩ ኃይሎች ርዳታ ባለማግኘታቸዉ ነው።

የደቡብ ሱዳን መንግሥት ጦር ሠራዊት ቃል አቀባይ ከጦርነት በመሸሽ ላይ የነበሩ 200 ሰዎች መስጠማቸውን ገለጡ። የጦር ሠራዊቱ ቃል አቀባይ ኮሎኔል ፊሊፕ አጉዔር፤ ነጭ ዐባይን ስታቋርጥ በሰጠመችው ጀልባ ተሣፍረው የነበሩት አብዛኞቹ ሴቶችና ሕጻናት ነበሩ።

የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር በእንግሊዝኛ ምህጻሩ «ኦ ዲ ኤፍ» ወደ ኣገር ቤት ተመልሶ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል መወሰኑን ኣስታወቀ።

የግንባሩ ፕሬዝደንት አቶ ሌንጮ ለታ እንደገለጹት ግንባሩ ከምስረታው ኣንስቶ ወደ ኣገር ቤት ለመመለስ ግልጽ አቐም ይዟል።

በደ/ጎንደር ፎገራ ወረዳ ሻጋ ቀበሌ በ2007 ዓ.ም ለሚደረገው ምርጫ ዝግጅት ሲባል የአካባቢውን የወልና የግጦሽ መሬት ለወጣቶች እንዲሰጥ ብአዴን በደብዳቤ አዝዞ ነበር፡፡ እንደአሰተያየት ሰጪዎች የክልሉ መንግስት ከዚህ በፊት ባወጣው አዋጅና መመሪያ መሰረት የወልና የግጦሽ መሬት ለማከፋፈል 80% የማህበረሰብ ክፍል ፈቃደኛ መሆን እንዳለበት ይገልፃል፡፡ በአማራ ክልል የመንግስት መስሪያ ቤት ሰራተኛ የሆኑ ግለሰብ ለፍኖጸ-ነፃነት እንደገለፁት ለምርጫ ሲባል በህገወጥ […]

የማለዳ ወግ … የመረጃዎች እውነት ፣ እውሸት ፍልሚያ ጅማሮ ! የተመላሾች ጉዳይ … በርካታ ከሳውዲ ወደ ሃገር ቤት የተመለሱ ዜጎችን በሚመለከት የጀርመንና የአሜሪካ ራዲዮን ጨምሮ በርካታ የመገናኛ ብዙሃን አንድ አይነት የሚመስል መረጃ ግፉአን ተመላሾችን እማኝ እያደረጉ መረጃ አቀብለውናል ።http://www.rappler.com/world/regions/africa/45783-ethiopia-s-colossal-human-airlift-from-saudi-arabia ” ራፕለር ” በታዝነው ሳምንት ባቀበለን መረጃ ሻንጣቸው ጠፍቷቸው በአንድ የሻንጣ ማጠራቀሚያ ግቢ ሻንጣቸውን ሲፈትሹ የሚያሳየውን […]

የቀድሞ የአራና ትግራይ አመራር አባል፣ አቶ ገብሩ አሥራት፣ ከባለቤታቸው ጋር በመኢካን እይሄዱ እንዳለኡ ድንገት መኪናቸው በእሳት መቃጠሏ በስፋት ተዘግቧል። «የአቶ ገብሩ አስራት መኪና በእሳት ነደደች» በሚል ርእስ ሥር በአስራት አብርሃም የተጻፈ ዘገባ በፌስ ቡክ ተለቋል። ዘገባዉን እንደሚከተለው አቅርበናል፡ የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት እና የዓረና ሊቀመንበር አቶ ገብሩ አስራት ከባለቤታቸው ከወ/ሮ የውብማር አስፋው ጋር በመሆን በመኪና […]

ግርማይ ገብሩ የቀድሞ የህወሓት ታጋይና የአሁን የቪኦኤ (VOA) ዘጋቢና ደራሲ ነው። ዓላማዬ ስለ ግርማይ ገብሩ ለመፃፍ አይደለም፤ ግርማይ በፌስቡክ ገፁ ስላሰፈረው መረጃ ለመዋስ እንጂ። መረጃው ከዚህ በፊትም አውቀው ነበር። ግን ለማስረጃ ያህል ግርማይን ልጥቀስ: ምክንያቱም ግርማይ የህወሓት ታጋይ ነበርና። ግርማይ በ1969 ዓም የህወሓት (ተሓህት) ሦስቱ መፈክሮች ሲጠቅስ የመጀመርያውና ዋነኛው አድርጎ የፃፈው “አፄነት፣ መስፍንነትና የአማራ የበላይነት […]

Image

«በሕገ መንግስቱ የመደራጀት መብታቸው የተጠበቀላቸው ፓርቲዎችን አልከሰስንም።ፓርቲዎችን ግን ሽፋን አድርገዉ ስርዓቱን ወይንም ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን ለመናድ እንቀሳቀሳለን የሚሉ ኃይሎችን ግን ዛሬም ፣ ነገም ፣ ሕጉን የማስከበር ግዴታና ሃላፊነት ስላለብን ከመከሰስ አያመልጡም ማለት ነዉ።»ኢቲቪ በቅርቡ በ«ሽብርተኝነት» ላይ፣ በቅርቡ ባቀረበዉ አሳዛኝ ዶኩሜንተሪ ላይ ፣ የፌደራል መንግስት አቃቤ ሕግ፣ አቶ ብርሃኑ ወንድማገኝ የተናገሩት ነበር።

እኝህ የሕግ ባለሞያ እየደጋገሙ ሕግን ስለማክበርና ስለ ሕገ መንግስቱ ነግረዉናል። ስለሕገ መንግስት ካነሳን አይቀር አንድ ነገር ጣል ላድርግ። የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 29 ንኡስ አንቀጽ 4 «በመንግስት ገንዘብ የሚካሄድ ወይንም በመንግስት ቁጥጥር ሥር ያለ መገናኛ ብዙሃን የተለያዩ አስተያየቶችን ለማስተናገድ በሚያስችለው ሁኔታ እንዲመራ ይደረጋል» የሚል ድንጋጌ ያካትታል። ኢቲቪ በሕዝብ ገንዘብ የሚተዳደር እንደመሆኑ ይህ የሕገ መንግስት አንቀጽ ይመለከተዋል። ነገር ግን ኢቲቪ በቀጥታ፣ ሕግ መንግስቱን ሲንድ፣ ገለልተኛነት በጎደለው መልኩ የአንድ ድርጅትን የፖለቲክ ፕሮፖጋንዳ መጠቀሚያ ሲሆን ነው እያየን ያለነዉ። እነ አንዱዋለም አራጌ ላይ፣ ኢቲቪ የአንድ ወገንን አቋም የያዘ፣ የስም ማጥፋት ዘመቻ ሲያዥጎደጉድ፣ ቢያንስ ቢያንስ ጥቂት ሰኮንዶች፣ የአንዷለምን ጠበቃዎች፣ ወይንም ቤተሰብ፣ አሊያም የትግል አጋሮቹ የሆኑት የአንድነት አመራር አባላትን ለማነጋገር አልተሞከረም። እንግዲህ ከዚህ የምንረዳዉ፣ ሕግን በማክበር አኳያ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴጎችና ኢቲቪ፣ አንድ ጣታቸዉን ወደሌሎች ሲጠቁሙ፣ አራቱ ጣቶቻቸው ወደ እነርሱ መዞራቸውን፣ ሕገ መንግስቱን እየጣሱ ያሉ እነርሱ መሆናቸውን ነዉ።

«አንዱዋለም አራጌን በተመለከተ፣ የግንቦት ሰባትን ተእልኮ ለማስፈጸም አገር ዉስጥ በሕቡእ (ስዉር) ይንቀሳቀሳል በሰላማዊ ትግል እንታገላለን የሚሉ የፓርቲዎችን ሽፋን አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረ በመሆኑ በቂ ማስረጃ አቅርበናል» ሲሉ ነበር የፌደራል አቃቤ ሕጉ ለኢቲቪ አክለው የገለጹት። ምን አይነት መረጃ እንዳቀረቡ ግን አልነገሩንም። ለምን ቢባል ምንም ስለሌለ።

አንዱዋለም ያደርጋቸው የነበሩ እንቅስቃሴዎች በሙሉ ሲያደርግ የነበረው በግልጽና በገሃድ ነዉ። ለተለያዩ ፓልቶክ ክፍሎች፣ አገር ዉስጥና በዉጭ ለሚገኙ ሜዲያዎች በርካታ ቃለ መጠይቆችን ሰጥቷል። በአገር ቤት፣ በአንድነት ፓርቲ ዉስጥ ሆነ በተለያዩ ቦታዎች በተደረጉ ዉይይቶችና ስብሰባዎች ያቀረባቸው ንግግሮች በሙሉ የተደበቁ አይደሉም። ዉጭ ካሉ ኢትዮጵያዊያን ጋር (አንዱም እኔው ነበርኩ) ፣ ብዙ ጊዜ በስልክ ሃሳቦችን ተለዋዉጧል። በስልክ ያደረጋቸው ንግግሮችም፣ 24 ሰዓት የሰላማዊ ተቃዋሚ መሪዎችን ስልክ በሚጠልፈው ቴሌ ዘንድ የተሰሙ ናቸው። ቤቱና ቢሮዉ ከላይ እስከ ታች ተበርብረዉ ፣ የሚስጥራዊ የኮሚኒኬሽን መሳሪያዎች፣ ቦምቦች፣ ፈንጂዎች፣ ሚስጥራዊ ሰነዶች አልተገኙም። ኤሜሎቹ በሙሉ ተነበዋል። አንዱዋለምን ከግንቦት ሰባት ጋር የሚያገናኝ፣ በሕቡእ እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሆነ የሚያመለክት አንዳች መረጃ አቃቤ ሕግ አላቀረበም። መረጃዎች ቢኖሩ ኖሮ፣ «እንኳን ዘንቦብሽ ድሮም ጤዛ ነሽ» እንደተባለ፣ ዜጎችን በማዋረድና በማሳነስ የሚታወቀዉ ኢቲቪ፣ ይሄን ጊዜ በስፋት ያወራልን ነበር።

ኢቲቪ ግን አንዱዋለምን ለመክሰስ ያቀረበው፣ አንድ የአንድነት አባል የነበሩ፣ ተስፋሁን አናጋዉ የተባሉ ሰው የተናገሩትን ነዉ። አንዱዋለም ከታሰረ በኋላ አቃቤ ሕጎች መረጃ ማቅረብ ባለመቻላቸው፣ የዉሸት መረጃዎች ማሰባሰቡ የግድ ሆነባቸው። የታሰሩ ሌሎች የአንድነት አባላትን ማግባባት ጀመሩ። «በአንዱዋለም ላይ እኛ ተናገሩ የምንላችሁን ከተናጋራችሁ እንፈታቹሃለን» ብለው እጆቻቸዉን ጠመዘዙ። ብዙዎች በአንዱዋለም ላይ የዉሸት መረጃ ማቅረቡ ሕሊናቸውን ስለከበደው ፍቃደኛ አልሆኑም። ነገር ግን እንደ ተስፋሁን አናጋው፣ የሚባሉ ደካማ ሰዎች ተገኙና የዉሸት ምስክርነት ቀረበ። እንግዲህ በአገዛዙ ካድሬዎች ተቀናብረው ከቀረቡ የዉሽት ምስክርነቶች ዉጭ፣ ቅንጣት የምታክል፣ አንዱዋለምን ሽብርተኛ ወይንም ከግንቦት ስባት ጋር የሚሰራ መሆኑን የሚያሳይ መረጃ አልቀረበም።

«ግንቦት ሰባት ፣ ግንቦት ሰባት ……» እንባላለን። ከጅምሩ በግንቦት ሰባት ላይ ጠንካራ ተቃዉሞ ያለኝ ሰው ነኝ። የግንቦት ሰባት ፖለቲካ አይመቸኝም፣ ለአገርም ይጠቅማል ብዬ አላስብም። ግንቦት ሰባቶች ከያዙት የተሳሳተ መንገድ እንዲመለሱ፣ በሻእቢያ ድጋፍ ሳይሆን፣ በሕዝብ ጉልበት በመተማመን ወደ ሰላሙ መንገድ እንዲመጡ መክሪያለሁ። በተለያዩ ጊዜያት ለአንባቢያን ያቀረብኳቸውን ጽሆፍችን መመልከት ይቻላል።

ከቅንጅት ጊዜ ጀምሮ በአገር ዉስጥ በሰላም ለዉጥ ለማምጣት የሚሰሩ ድርጅቶችን ደግፊያለሁ። በተለይም የአንድነት ፓርቲ በጣም የሚመቸኝ ፓርቲ እንደመሆኑ፣ አንዱዋለም አራጌን ጨምሮ፣ ከፓርቲዉ አመራር አባላት ጋር ሃሳብ የተለዋወጥኩባቸው በርካታ ጊዜያት ነበሩ። አንዱዋለም አራጌ፣ እግዚአብሄርን የሚፈራ፣ የልጆች አባት፣ የሰላማዊ ትግል አርበኛ ነዉ። አንዱዋለም ስለ ትጥቅ ትግል ያለዉን አመለካከት አውቃለሁ። በየትኛዉም መድረክና ፍርድ ቤት፣ መጽህፍ ቅዱስ ላይ እጄን ጭኜ የምመሰክረዉ ነዉ። አንዱዋለም አራጌ የግንቦት ስባት አባል ወይንም ሽብርተኛ ነው የሚለውን፣ በምን መስፈርትና መልኩ ልቀበለው አልችልም። በርግጥ አንዱዋለም የግንቦት ሰባት አባል ከተባለ፣ እኔም የግንቦት ሰባት አባል ነኝ እንደ ማለት ነዉ።

በጣም ያሳዝናል። እንደ አንዱዋለም አራጌ አይነት አገር ወዳድ ዜጎች፣ አገራቸዉን በመዉደዳቸው፣ የሕዝብ መብት ይከበር በማለታቸው፣ «ሽብርተኞች» በሚል አሳዛኝ ክስ ሲታሰሩ ማየት፣ አገራችን ኢትዮጵያ ዜጎች ቀና ብለው የሚራመዱባት ሳይሆን ፣ አሳፋሪ ድራማ የሚካሄድባት፣ ሕግ መቀለጃ የሆነባት አገር መሆኗ፣ በርግጥ ልብን የሚያደማ ነው።

እንግዲህ፣ ሁሌ እንደማደርገዉ፣ ጥሪ ለኢሕአዴጎች አስተላልፋለሁ። ኢሕአዴግ ዉስጥ፣ ለአገርና ለሕዝብ የሚያስቡ ካሉ፣ በድርጅታቸው ዉስጥ እየተደረገ ያለውን አፈናና ግፍ በቃ የማለት አቅምና ጉልበት ሊኖራቸው ይገባል ባይ ነኝ። ድርጅታቸው ዉስጥ ያሉ ጥቂቶች ድርጅታቸውን ይዘው ገደል እንዲወስዱ ሊፈቀድላቸው አይገባም። እነ አንዱዋለምን በማሰር ኢሕአዴግ ምንም የሚጠቀመው ነገር የለም። እነ አንዱዋለምን በዉሸት ክስ ከሶ፣ በቴለቭዥኝ ደግሞ ስማቸውን ማጉደፍ፣ ነዉር ነዉ። ኢሕአዴግ የበለጠ እንዲጠላ የሚያደርግ ነዉ። የአረና ትግራይ አመራር አባል አብርሃ ደስታ አንዴ ሲጽፍ፣ የሕወሃት እምብርት በነበረችው የትግራይ ክልል፣ አንዱዋለም አራጌ በጣም ተወዳጅ ፖለቲከኛ እንደሆነ ገልጾ ነበር። አንዱዋለም አራጌ፣ በክልሎች ሁሉ ሕዝብ የሚያውቀዉ ጀግና መሪ ነዉ። በርሱ ላይ እየተደረገ ያለው ዘመቻ፣ የበለጠ አንዱዋለምን ከፍ የሚያደርግ፣ ኢሕአዴግን ደግሞ የሚያሳንስ ነዉ። አንዱዋለምን እና ሌሎች የሕሊና እስረኞች፣ አለመፍታት በቀጥታ ከሕዝቡ ጋር እንደመላተም ነው። አይጠቅምም። ጉዳት አለው።

ለኢሕአዴጎች ጥሪ ባቀርብም፣ የነአንዱዋለም ጉዳይ፣ የኢሕአዴጎች ጉዳይ ብቻ ግን አደለም። ኢሕአዴጎች ወደ ሕሊናቸው ተመልሰው መልካም ነገር ያደርጉ ዘንድ እነርሱን ማነጋገርና ለማሳመን መሞከር፣ ማበረታታት ተገቢ ነዉ የሚል እምነት ቢኖረኝም፣ ሁሉንም ነገር ከነርሱ ጠብቆ ቁጭ ማለቱ ግን፣ እጅግ በጣም ትልቅ ስህተት ነው። እነርሱ ቢሰሙ መልካም ነዉ፤ ካልሆነ ግን እያንዳንዳችን መብታችንን የማስከበር ሃላፊነት ያለብን ይመስለኛል። ዛሬ እነ አንዱዋለም ናቸው። ነገ እያንዳንዳችን ቤት ይንኳኳል ። ዛሬ ሊመቸን ይችላል። ነገር ግን ለሕይወታችን ምንም ዋስትና አይኖረንም። አንድ የመንግስት ባለስልጣን ፊታችንን አይቶ ከጠላን፣ በቀላሉ ወደ ወህኒ ሊወረወረን የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ ማወቅ አለብን። አለን የምንለውን ቢዝነስ አንዱ ከፈለገዉ፣ «ያለ የሌለዉን እያመጡ፣ ይሄን ያህል ግብር ክፈል» ተብለን ከጨዋታ ዉጭ በቀላሉ ልንሆን የምንችልበት አገር ነዉ ያለችን። አቤት የምንልበት የሕግ ስርዓት የለም። አብዛኞቹ ዳኞች በመመሪያ የሚፈርዱ ካድሬዎች ናቸው። በመሆኑም፣ ኢትዮጵያ፣ ሕግ የበላይ የሆነባት፣ ለሁሉ ዜጎቸ እኩል የሆነች፣ ኢትዮጵያዊያን ሳይፈሩና ሳይሸማቀቁ ሃሳባቸውን በነጻነት መግለጽ የሚችሉባት፣ መቀባባል፣ ይቅርታ፣ ፍቅር፣ ሰላም ፣ ፍትህና ወንድማማችነት የሰፈነባት፣ የበለጸገች አገር እንድትሆን፣ እያንዳንዳችን የድርሻችንን መወጣት አለብን። ዳር ሆኖ ተቀመጦ ማውራት ይብቃ። ሌሎች ለምን እንዲህ አላደረጉም ብሎ መክሰስ ይብቃ። ሌሎች ሞተው በነርሱ አስክሬን ላይ ተረማመደን ለመሻሻል መሞከር ይብቃ። አገራችን የእስክንደር፣ ወይንም የአንዱዋለም፣ ወይንም የበቀለ ገርባ፣ ወይንም የርዮት አለሙ ብቻ ሳትሆን የሁላችንም ናት፣ ሁላችንም ተስፋ ሳንቆርጥ፣ ሌሎች ነጻ እንዲያወጡን ሳንጠብቅ፣ የድርሻችንን እንወጣ።

መከላከያ ሰራዊት የተለያዩ ወቅታዊ ጥያቄዎች እያቀረቡላቸው መሆኑ ታወቀ::

የሃያሰዎስተኛ ክ/ጦ ኣዛዥ ብ/ጀነራል በላይ ስዩም፤ የሰላሳ ኣንደኛ ክ/ጦ ኣዛዥ ብ/ጀነራል ድሪባና፤ የሰላሳ ሰዎስተኛ ከ/ጦር ኣዛዥ ብ/ጀነራል ከበደ ፍቃዱ እኛ ኣዲስ ቶሻሚ በመሆናችን ብዙ ተቀባይነት የለንም::

የማእከላዊ እዝ የበላይ ኣመራሮች በተገኙበት ስብሰባ ላይ እንደ ኣንድ ትልቅ ኣጀንዳ ሆኖ የቀረበ። ኣብዛኛው የሰራዊቱ ኣባል ማግኘት የሚገባው ጥቅም ባለማግኘቱ በሰራዊቱ ውስጥ የመቀጠል ፍላጎቱ ያበቃና የሞተ በመሆኑ ምክንያት ክውትድርና ኣለም ተሰናብቶ የግል ሂወቱ መምራት እንደሚፈልግ ላቀረቡት ጥያቄ በስብሰባው ውስጥ የተካፈሉት የበላይ ኣመራሮች የቀረበው ጥያቄ ሰምተው እንዳልሰሙ በመምሰል ተገቢ መልስ ሳይሰጡበት እንዳለፉ ለማወቅ ተችለዋል::

መረጃው በማስከተል በስብሰባው ውስጥ የተገኙ የሃያሰዎስተኛ ክፍለጦር ኣዛዥ ብርጋዴል ጀነራል በላይ ስዩም፤ የሰላሳ ኣንደኛ ክፍለጦር ኣዛዥ ብርጋዴል ጀነራል ድሪባና፤ የሰላሳ ሰዎስተኛ ከፍለጦር ኣዛዥ ብርጋዴል ጀነራል ከበደ ፍቃዱ እኛ ኣዲስ ቶሻሚ በመሆናችን ብዙ ተቀባይነት የለንም ኣታስቸግሩን ብለው መልስ እንደሰጥዋቸው ለማወቅ ተችለዋል::

ይህ በንዲህ እንዳለ ከሰራዊቱ ውስጥ ለመኪና ሾፌርነት ስልጠና ተመልምለው ኣዲ ቡኽራይ ወደ ተባለው ቦታ የታላኩ ወተሃደሮች ስልጠናውን በመተው ወደ ክፍላቸው ተመልሰው የ 7 ኣመት ኣገልግሎታችን ስለ ጨረስን ከሰረዊት የመሰናበት መብታችን ይረጋገጥልን ብልው ጥያቄ ማቅረባቸው ተገለጸ::

ወደ ስልጠናው ከተላኩ ቦሃላ ተመልሰው ወደ ክፍላቸው ከተመለሱ ምልምል ወተሃደሮች ስም ለመጥቀስ። ወ/ር ማእርግ ሰፍየ፤ ወ/ር ተሻለ ኣየነው፤ ወ/ር ክብሮም ኣስረስና ሌሎች ሲሆኑ። በተለይ ከ 1990 ኣ/ም ባሃላ የተቀጠሩ የሰራዊቱ ኣባላት የደሞዝ ይሁን የማእርግ እድገት መብታቸው እንዳላገኙና በላዩ ላይ ለኣባይ ግድብ፤ ለትምህርት ቤትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች እየተባለ ደሞዛቸው እየተቆረጠ በመሆኑ ምክንያት ተማርረው ከሰራዊቱ ለመልቀቅ ስንብት እየጠየቁ መሆናቸው መረጃው ኣክሎ ኣስረድተዋል::

የኢሕኣዴግ ፍራቻ የወለደው እቅድ ምርጫውን ሊያጭበረብር ነው::የድምጽ ማጭበርበሮች እንኳን ቢከሰት ተቃዋሚዎች የተቃውሞ ሰልፍ እንዲያደርጉ አይፈቀድላቸውም።
ኢህአዴግ ከምርጫ 2007 በሁዋላ ረብሻ ሊነሳ ይችላል አለ::

ኢትዮጵያን ላለፉት 23 ዓመታት የገዛው ኢህአዴግ መጪውን ምርጫ ተከትሎ በአዲስ አበባና በዋና ዋና የአገሪቱ ከተሞች ረብሻዎች ሊነሱ እንደሚችሉ ፓርቲው ድምዳሜ ላኢ መድረሱን አስታውቋል።

የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት በኢትዮጵያ መንግስት አሸባሪ ተብለው የተፈረጁት በተለይ ግንቦት7 እና ኦነግ ምርጫውን ተከትሎ በምርጫ 97 የታየውን አይነት የህዝብ አመጽ ለማስነሳት እየሰሩ ነው የሚል ድምዳሜ ላይ የደረሰው ኢህአዴግ፣ ከአሁኑ ጀምሮ በአንድ ለአምስት አደረጃጀትና የከተሞችን ነዋሪዎች ስለ አሸባሪዎች አላማ እና ግብ በማስረዳት ህዝቡ በአመጹ ተሳታፊ እንዳይሆን እንደሚያስተምር አስታውቋል።

አሸባሪ የተባሉ ድርጅቶች በመልካም አስተዳደር፣ በሙስና እና በኢኮኖሚ ዙሪያ የሚታዩ ክፍተቶችን ተጠቅመው ህዝቡ በመንግስት ላይ እንዲነሳ ሊያደርጉ ይችላሉ አለው ኢህአዴግ፣ ለዚህ አላማ እንዲረዳቸው ደግሞ ኢሳትንና ቪኦኤን የመሳሰሉ የመገናኛ ብዙሀንን በአገር ውስጥ ደግሞ አንዳንድ ጽንፈኛ አስተሳሰብ ያላቸውን መጽሄቶች ሊጠቀሙ ይችላሉ ብሎአል። በአገር ውስጥ በሰላማዊ ትግል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ድርጅቶች ፣ ለአመጽ ጥሪው ህጋዊ ሽፋን ለማሰጠት ሊንቀሳቀሱ ይችላሉ ።

በተለይ የአዲስ አበባ ህዝብ የአሸባሪዎች ኢላማ እንዳይሆን ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ኢህአዴግ ገልጿል።

በሚቀጥለው አንድ አመት ውስጥ በአዲስ አበባ እና በክልል ዋና ዋና ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎች እና የመንግስት ሰራተኞች በሽብረተኝነት ዙሪያ ተከታታይ ትምህርት የሚሰጣቸው ሲሆን፣ ግንባሩም ከእዚህ ስልጠና የአካባቢ የሰላም ጠባቂዎችን እንደሚመለምል ፣ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው ገዢውን ፓርቲ አይደግፉም የሚባሉትን የመለየት ስራም እንደሚሰራ ታውቋል።

ኢህአዴግ ምርጫውን ተከትሎ ሊነሳ የሚችል ማንኛውም ተቃውሞ ሽብርተኝነት ነው ሲል ድምዳሜ ላይ ደርሷል። በምርጫ ሂደቱ ላይ ፍትሀዊ ያልሆኑ አሰራሮች እንዲሁም የድምጽ ማጭበርበሮች እንኳን ቢከሰት ተቃዋሚዎች የተቃውሞ ሰልፍ እንዲያደርጉ አይፈቀድላቸውም። ኢሳት ዜና

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች እሁድ ጥር 4 ቀን 2006 ቅሊንጦ ማረሚያ ቤት በመሄድ የህዝበ ሙስሊሙን መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን እና አብረዋቸው የታሰሩትን የኢስላም ልጆች መዘየራቸውን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡ በዚያራውም ከኮሚቴው አባላት ጋር የተነጋገሩ ሲሆን የፓርቲው አመራሮች በኮሚቴው አባላት ላይ የሚታየውን ፅናት አድንቀዋል፡፡

በህዝብ ግንኙነት ክፍሉ የተመራው የከፍተኛ አመራር አባላት
– የፓርቲው ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር አቶ ተክሌ በቀለ
– የፓርቲው ዋና ፀሐፊ አቶ ስዩም መንገሻ
– የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው
– የፓርቲው የውጭ ጉዳይ ሀላፊ ኢንጂነር ዘለቀ ረዲ
በማረሚያ ቤቱ በመገኘት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈው ከኮሚቴው አባላት ጋር የሀሳብ ልውውጥ አድርገዋል፡፡ ከሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ የቅሊንጦ እስረኞች –
1-ሼህ መክት ሙሄ – የሼሪዓ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ የነበሩ
2- አቡበከር አህመድ
3- ካሚል ሸምሱ
4- አቡበከር አሊ
5- ሙባረክ አደም
6-አህመድ ሙስጠፋ
7- አብዱራዛቅ አክመል
እና ሌሎችም ሲሆኑ እነ አቡበከር ከፍተኛ የመንፈስ ጥንካሬ የሚታይባቸው ዛሬም ዛሬም ከፊታቸው ፅናት የሚነበብባቸው እንደነበር የአንድነት አመራሮች ገልፀዋል፡፡
የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጠንከር ያለ ምክርና መልዕክትም አስተላልፏል፡፡ ሀገሪቷ በነፃነት ደረጃ እንዲህ ባለ ሁኔታ ላይ መድረሷ እንዳሳዘናቸውም ለፓርቲው አመራሮች ገልፀዋል፡፡

ኮሚቴዎቻችንን ህጋዊ ወኪሎቻችን መሆናቸውን ሳር ቅጠሉ የመሰከረው ጉዳይ ቢሆንም ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል ግን በእስር ቤት እንዲማቅቁ እየተደረጉ ይገኛሉ፡፡

አላህ ፍትህን ያስፍንላቸው!!!
ፍትህ ለኢትዬጲያ ሙስሊሞች !!!

ቁጥራቸው ወደ 40 የሚጠጋ የእሕኣፓ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች የሕወሓት/ኢሕኣዴግ ሰራዊት ጎንደር እና ጎጃምን በተቆጣጠረ ጊዜ በውጊያ ከተማረኩ በኋላ በ1983/84( በ1991)ከተረሸኑ በኋላ በጣና በለስ ፕሮጀክት አቅራቢያ በጅምላ መቀበራቸውን ምንጮች ለኢትዮ ሚዲያ ገልጸዋል::

የጅምላ መቃብሩን የቆፈረው ቡልዶዘር የጣና በለስ ፕሮጀክት ንብረት የነበረ ሲሆን ቡልዶዘሩን ሲያንቀሳቅስ የነበረውም ኦፕሬተር ግድያውን እና የጅምላ መቃብሩን በተመለከት ህዝብ ጆሮ እንዳይደርስ ምስጢር ለመጠበቅ ሲባል ወዲያው የተገደለ መሆኑ ምንጮቹ ገልጸው የግድያው ትእዛዝ የሰጡት እና እንዲፈጸም ያደረጉት ሟች መለስ ዜናዊ እና አኦ ስብሃት ነጋ መሆናቸውን አክለው ተናግረዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ በተመሳሳይ ሁኔታ ስምንት የኢሕኣፓ ሰራዊት አመራሮች የነበሩት በሕወሓት ሰራዊት ተይዘው በ ባዶ 6 እስር ቤት ትግራይ መታሰራቸው እና የግድያ ቅጣት ተላልፎባቸው እንደነበር ይታወሳል:: ይህ የኢሕኣፓ ከፍተኛ አመራሮች ጸጋዬ ደብተራው ሃጎስ በርሄ ይሳቅ ደብረጺሆን እና ሌሎችም የተላለፈባቸው የግድያ ቅጣት የተፈጸመው በትግራይ ይሁን በጎንደር አሊያም በጎጃም እስካሁን መረጃው እንዳሌላቸው ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል::
http://www.ethiomedia.com/14store/5563.html

click here for pdf

ሰንደባ ኢየሱስ – ከሩቁ

ከባሕርዳር ወደ ጎንደር ስትጓዙ አርኖ የምትባል አነስተኛ ከተማ ታገኛላችሁ፡፡ የከተማዋና የወንዟ ስም አንድ ነው፡፡ አርኖ ላይ ወርዳችሁ ወደ ቀኝ ለአንድ ሰዓት ተኩል ያህል በእግራችሁ ስትጓዙ ሜዳውን ትጨርሱና ገደሉን ፊት ለፊት ትጋፈጡታላችሁ፡፡ በገደሉ መካከል እንደ ሞሰበ ወርቅ በተሸለመች ተራራ አናት ላይ የሰንደባ ኢየሱስ ወተክለ ሃይማኖትን ጥንታዊ ደብር ታገኙታላችሁ፡፡
የደብሩ ካህናት የቤተ ክርስቲያኑ ታሪክ ከአንድ ሺ ዓመት በላይ እንዳለፈው ይናገራሉ፡፡ በአካባቢው የምናገኛቸው የሥነ ሕንጻና አካባቢያዊ ማስረጃዎች ደግሞ ታሪኩ ቢያንስ ሰባት መቶ ዓመት ሊሆነው እንደሚችል ይጠቁማሉ፡፡
የሰንደባ ኢየሱስ ወተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ሥነ ሕንጻው ከዛግዌ ዘመን፣ አካባቢያዊ መረጃዎቹ ደግሞ ከ13ኛውና 14ኛው ዘመን ጋር የሚገናኙ ናቸው፡፡

ቤተ ክርስቲያኑ ክብ ሆኖ ውጩ በጭቃ የተገረፈ ነው፡፡ የጭቃ ግርፉ በቤተ ክርስቲያኑ ላይ የደረሰውን የመፍረስ አደጋ ለመታደግ በአካባቢው ባለሞያዎች የተገነባ ነው፡፡ ወደ ውስጡ ሲዘልቁ ግን ሁለት ጥንታዊ ክፍሎችን ያገኛሉ፡፡

ሰንደባ ኢየሱስ – ከቅርብ ሲታይ

የደብሩ መስኮቶች እንደ ይምርሐነ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ከአንድ ወጥ እንጨት የተሠሩ ናቸው፡፡ እያንዳንዱ መስኮት ያራሱ ቅርጽ ያለው ሲሆን፣ አንደኛው ከሌላኛው የተለየ ዲዛይን አለው፡፡ ብዙዎቹ መስኮቶች ለውበት የተሠሩ እንጂ የሚከፈቱ  አይደሉም፡፡ የመስኮቶቹ መቃኖች ከአንድ ወጥ እንጨት ወጣ ብለው የተሠሩ፣ በአራቱም መዓዝን ወጣ ወጣ ያሉ ጌጦች ያሏቸው ናቸው፡፡ ይህ አሠራራቸው ከይምርሐነ ክርስቶስ አሠራር ጋር ያዛምዳቸዋል፡፡
               
ሰንደባ ኢየሱስ ወተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያንን ከይምርሐነ ክርስቶስ ጋር የሚያዛምዳቸው መስኮታቸው ብቻ አይደሉም፡፡ የመቅደሱ ግድግዳ አሠራርም ተመሳሳይ ነው፡፡ ግድግዳው በቀጫጭን ጠፍጣፋ ድንጋዮች እየተሰካካ፣ በኖራ መሰል ነገር እየተያያዘ ቀጥ ብሎ የተሠራ ነው፡፡ እጅግ የሚገርመው ግን ድንጋዮች የተያያዙበት ኖራ መሰል ነገር የተለሰነበት መንገድ ነው፡፡ የደብሩ ሊቃውንት ኖራ ከተነከረ ቆዳ ጋር እየተያያዘ እንደተሠራ ይናገራሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ከውጭ ክብ ቢሆንም ሁለቱ የውስጥ ክፍሎቹ ግን አራት መዓዝን ናቸው፡፡ መዓዝኖቹ በርግጠኝነት 90 ዲግሪ ናቸው፡፡ ወደ ላይም በቱምቢ ሲለካ ቀጥ ብሎ የወጣ ወጣ ገባ የሌለው ነው፡፡

በተሰካኩ ድንጋዮች የተሠራው ግድግዳ

በግድግዳው አማካይ በሐረግ የተጌጠ ነው፡፡ ጌጡ ከጥግ እስከ ጥግ በሁለት ወይም በሦስት መሥመር እየተዘረጋ ተገጥግጧል፡፡ ከመስኮቶቹ በላይ ደግሞ ሌላ ጌጥ አለ፡፡ በመስኮቶቹ መቃን ርዝመት ልክ ከአንድ ወጥ እንጨት የተሠራ ሐረግ፡፡ ይህ ሐረግ በመስኮቱ ላይ በቻ ሳይሆን ከበሩ በላይም እንዲሁ በየመዓዝናቱ ተሰክቶ ይታያል፡፡

የተጌጠው መስኮት

አራት መዓዝኑ የመቅደሱ ግንብ ለስድስት ሜትር ያህል ወደ ላይ ከወጣ በኋላ መቅደሱን ከጣራው ጋር በክብ ግድግዳ ያያይዘዋል፡፡ ወደ ቅድስቱ መግቢያው በር የጥንቱን ይዘት አልለቀቀም፡፡ በአራት ደረጃ የተሠራው መቃን በሥዕል የተሞላ ነው፡፡ በመጨረሻው መቃን ላይ ደግሞ የአሥራ አምስቱ ነቢያት ሥዕል በትንንሹ ተሥሎ ይታያል፡፡

የአሥራ አምስቱ ነቢያት ሥዕል- የበሩ ላይኛው መቃን
ከበሩ በላይ ሌላ ጌጠኛ መስኮት አለ፡፡ መስኮቱ ባለ ሦስት መቃን ሲሆን ሦስቱም በሥዕል ያጌጡ ናቸው፡፡ የሚገርመው ግን መስኮቱ ለውበት የተሠራ እንጂ የሚከፈት መስኮት አይደለም፡፡ ከአንድ ወጥ እንጨት የተቀረጸው መስኮት የመስኮቱ ውስጣዊ አካል ራሱ በቀለም ያሸበረቀ ነው፡፡ የመስኮቱ ውስጣዊ አካል ደግሞ እርስ በርሳቸው በተያያዙ ክቦች ቅርጽ የተሠራ ነው፡፡ እያንዳንዱ ክበብም የየራሱ ቀለም ተቀብቷል፡፡

ዋናው በር በበሩ ላይ የቅዱሳን መላእክት ሥዕል በትልቁ ተሥሎበታል፡፡ ሥዕሉ እንዳይበላሽ በመጋረጃ የተጋረደ ሲሆን ሥዕሉን ባለ ሦስት ደረጃ መቃን አጅቦታል፡፡ ወደ በሩ የመግቢያው ደረጃ ከእንጨት የተሠራ ባለ ሰባት እርከን ነው፡፡ ሊቃውንቱ የሰባቱ መዓርጋት፣ የሰባቱ ሰማያትም ቢሉ ምሳሌ ነው ይላሉ፡፡ ከበሩ ግራና ቀኝ ቢያንስ አራት መቶ ዓመታትን የዘለቁ፣ የሥዕል አጣጣላቸው ከጎንደር ዘመን ቀደም ያሉ ዓመታትንና የጎንደርን ዘመን አሻራ ያዙ ሥዕሎች አሉ፡፡

ባለ ሰባት ደረጃው በር

በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ መንበር የሚመስሉና የቤተ ክርስቲያኑን ቅርጽ የያዙ ወጥ ከሆነ እንጨት የተቀረጹ ሳጥኖች አሉ፡፡ አንዳንድ ሊቃውንት ቅዱስ ላሊበላ ሕንጻዎቹን ከመውቀሩ በፊት ዲዛይኑን በእንጨቶቹ ላይ ማስቀመጡን ይናገራሉ፡፡ በሰንደባ ኢየሱስ ወተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያንም የመቅደሱን ቅርጽና የመቅደሱን ሐረጎችና በሮች ቅርጽ ያዘ አነስተኛ መንበር መሰል ነገር አለ፡፡ እንደ እኔ ግምት ቤተ ክርስቲያኑ ሲታነጽ የቤተ ክርስቲያኑ ቅርጽ አራት መዓዝን የነበረ ይመስላል፡፡ በኋላ ሲፈርስ ለማደስ ሳይሆን አይቀርም ውጩ ክብ የሆነው፡፡

የቤተ ክርስቲያኑን ቅርጽ የያዘው ጥንታዊው አንድ ወጥ ‹መንበር›

የመቅደሱ ታችኛው ግድግዳ በዕውቅ ጠራቢ ተስተካክለውና አምረው በተጠረቡ ግዙፍና አራት መዓዝን በሆኑ ዐለቶች የተገነባ ነው፡፡ የዚህ ግድግዳ አሠራሩ በአኩስም ከተገኙ የጥንት መቃብሮች አሠራር ጋር የተዛመደ ነው፡፡ ዐለቶቹ እርስ በርስ የተገጣጠሙበት መንገድ ትኩረት ቢደረግበት ለዛሬውም የግንባታ ችግሮቻችን መፍትሔ የሚሰጡ ናቸው፡፡

በግዙፍ ጥርብ ድንጋዮች የተገነባው ግድግዳ

የሰንደባ ኢየሱስ አስደናቂ ታሪክ የሚጀምረው አሁን ቅድስት የሆነውን ክፍል ሲገልጡት ነው፡፡ ቅድስቱ ሁለት ክፍል ያለው እጅግ ሰፊ ክፍል ነው፡፡ ምናልባትም በጥንቱ አሠራሩ ይኼ መቅደሱ ሳይሆን አይቀርም፡፡ በቅድስቱ ውስጥ ያለው ውስጠኛው ክፍል ባለ ሦስት በር ሲሆን የግራና ቀኙ በር ቅስት መልክ ሲኖረው፣ የመካከለኛው በር ግን የከፊል ክብ መልክ ያለው ነው፡፡ ግድግዳው ከጥርብ ድንጋይ የተሠራ፣ በዓምዱ መጨረሻ ላይ ዓምዱን ከቅስቱ የሚያያይዙ መከዳዎች የተሠሩለት ጌጠኛ ግድግዳ ነው፡፡


በውስጠኛው ክፍል ውስጥ የሚገኙት ሦስት መናብር ለየት ያሉ ናቸው፡፡ መካከለኛው መንበር እጅግ ግዙፍ ከመሆኑም በላይ አሠራሩ የላሊበላን መናብርት የመሰለ ነው፡፡ በግራና በቀኝ ያሉት መናብርት እስካሁን በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ካየኋቸው መናብርት ለየት ያሉ ናቸው፡፡ ቅርጻቸውም የኦሪቱን መንበረ ታቦት የሚመስሉ ሲሆኑ ካህናቱ መሥዋዕተ ኦሪት ሲሠዋባቸው የነበሩ ናቸው በማለት ይገልጣሉ፡፡ በላያቸው ያለውን ጌጥና ቅርጽም ጊዜ ወስዶ ማጥናት ይጠይቃል፡፡

አስደናቂው ቅድስት

በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ጥንታዊ ሚዛን፣ ከድንጋይ የተሠራ አገልግል፣ ከአንድ ወጥ እንጨት የታነጸ የመብራት ማብሪያ፣ ከአንድ ወጥ እንጨት የተሠራች አገልግል፣ የኦሪቱን የመሰለ የዘይት ማብሪያ ይገኛል፡፡ አሁን አገልግሎት የማይሰጥ ‹ተሰማ ጎንደር› የሚባል ከበሮም ነበራቸው፡፡ ይህ ከበሮ በማኅሌት ጊዜ ሲመታ እስከ ጎንደር ከተማ ይሰማ ስለነበር ‹ተሰማ ጎንደር› ተብሎ መሰየሙ ይነገራል፡፡
ሰንደባ ኢየሱስ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ ብቻ ሳይሆን አካባቢውም ከመካከለኛው ዘመን ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በአካባቢው አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ የሚነገረው ታሪክ፣ የአሥራ ሁለቱ ንቡራነ እድ ቦታዎች ናቸው ተብለው የሚነገሩት ቦታዎች፣  ደብሩ ከአቡነ ታዴዎስ ዘጽላልሽ ጋር ተያይዞ የሚነገርለት ታሪክ፣ ጠለቅ ብለው ቢጠኑ በሀገራችን የሕዝቦች መስተጋብርና በቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን አገልግሎት ላይ ተጨማሪ ዕውቀት የሚሰጡን መረጃዎችን ልናገኝ እንደምንችል መገመት ይቻላል፡፡ የአካባቢው ሽማግሌዎችና የየደብሩ ታሪክ

ከአንድ ወጥ እንጨት የተሠራው አገልግል
ሰንደባ(ታዴዎስ)፣ ጉርሐች(ኤልሳዕ)፣ ቀልቀል (ገብረ ዮሐንስ)፣ ምጓዕ(በርሶማ)፣ ጥቃራ(መርሐ ክርስቶስ)፣ ደብረ ቅድስት(ጳውሎስ)፣ ዳንጉሬ(ቀሌምንጦስ)፣ ሰውበዳ(ዮሐንስ ከማ)፣ ዋሻ(እንድርያስ)፣ ገረገራ(አኖሬዎስ)፣ አግድ(እጬ ፊልጶስ)፣ ውሻ ጥርስ(እጬ ፊልሞና) ቦታቸው መሆኑን ይገልጣል፡፡ የሰንደባ ኢየሱስ መጽሐፍ ‹ቡራኬ ዘሰንደባ ታዴዎስ፣ ሲመት ዘኤልሳዕ፣ ወመጽዑ ፲ወ፪ ንቡራነ ዕድ ዘሀገረ ሴዋ ዘደብረ ሊባኖስ – ቡራኬ የሰንደባ ታዴዎስ፣ ሹመት የኤልሳዕ ነው፤ አሥራ ሁለቱ ንቡራነ ዕድ በሀገረ ሸዋ ከምትገኘው ደብረ ሊባኖስ መጡ› ይላል፡፡

‹ከኦሪት ዘመን ጀምሮ‹ አገልግሎት ላይ የነበረው የመብራት ማብሪያ
እጅግ አስደናቂው ነገር አዲስ የሆነ የንቡራነ ዕድ ዝርዘር እዚህ ማግኘታችን፣ ከንቡራነ ዕዱ መካከልም ታዴዎስ፣ ኤልሳዕ፣ አኖሬዎስ፣ ፊልጶስ በሌሎች መጻሕፍት ከሚገኙት ዝርዝሮች ጋር ተመሳሳይ ሲሆኑ – ገብረ ዮሐንስ፣ መርሐ ክርስቶስ፣ ጳውሎስ፣ ቀሌምንጦስ፣ ዮሐንስ ከማ፣ እንድርያስ፣ እጬ ፊልሞና በንቡራነ ዕድ ዝርዝር የምናገኛቸው አዳዲስ ስሞች ናቸው፡፡ እነዚህን አድባራት በእነዚህ ቅዱሳን ርስትነት ቢጠሩም የየደብሩ ታቦታት ግን በሌሎች ቅዱሳን ስም የሚጠሩ ናቸው፡፡

ከአንድ ወጥ ድንጋይ የተቀረጸው አገልግል
ይህ ጉዳይ ሁለት ነገሮችን እንድንገምት ያደርጋል፡፡ በዛሬው ወሎና ኤርትራ እንደነበረው የአሥራ ሁለት አበው ሥምሪት በጎንደር አካባቢም ነበር ማለት ነው? ይህ ከሆነ ደግሞ የጥንቷን ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ሥምሪት የሚያጠናክርልን ተጨማሪ ነገር አገኘን ማለት ነው፡፡ ወይስ ደግሞ የአካባቢው ቃላዊና ጽሑፋዊ መረጃ እንደሚገልጠው ከደብረ ሊባኖስ የተነሡ አሥራ ሁለት ንቡራነ ዕድ ወደዚህ አካባቢ መጥተው ነበርን? ያ ከሆነ ደግሞ በዚህ ዝርዝር ያገኘናቸውን አዳዲስ ንቡራነ ዕድ ታሪካቸውን መፈለግ የግድ ይለናል ማለት ነው፡፡

ሁሉም ተጨማሪ ጥናት የሚጠይቁ ፍንጮች ናቸው፡፡ ፍላጎትና ዕውቀት ያለው ሰው አጥንቶ ቢነግረን እንመርቀዋለን፡፡

ጥር ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢትዮጵያን ላለፉት 23 ዓመታት የገዛው ኢህአዴግ መጪውን ምርጫ ተከትሎ በአዲስ አበባና በዋና ዋና የአገሪቱ ከተሞች ረብሻዎች ሊነሱ እንደሚችሉ ፓርቲው ድምዳሜ ላኢ መድረሱን አስታውቋል። የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት በኢትዮጵያ መንግስት አሸባሪ ተብለው የተፈረጁት በተለይ ግንቦት7 እና ኦነግ ምርጫውን ተከትሎ በምርጫ 97 የታየውን አይነት የህዝብ አመጽ ለማስነሳት እየሰሩ ነው …

ጥር ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአፍሪካ ቀንድ የሂውማን ራይትስ ሊግ ለኢሳት በላከው መግለጫ ከነሐሴ እስከ ታህሳስ ባለው ጊዜ ውስጥ የኦሮሞ ህዝብ ፌደራሊስት ኮንግረስ አባላት ናቸው የተባሉ 45 ሰዎች በጉጂ ዞን በነገሌ እስር ቤት ውስጥ ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ ታስረው ይገኛሉ። ከታሰሩት መካከልም የሁለተኛ ደረጃ፣ የኮሌጅና የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና መምህራን ይገኙበታል። በጉጂ ወረዳ በሀርኬሎ ከተማ …

ጥር ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ ዩነቨርሲቲ የሥነ ምድር ትምህርት ክፍል የከርሰ ምድር ውኃን በተለያዩ መንገዶች  ሲያጠኑ የቆዩ አንድ ምሁር ባወጡት ጽሁፍ  አብዛኛው የአዲስ አበባ ወንዞች  ለመጠጥም፣ ለእርሻም፣ ለኢንዱስትሪም መዋል የሚችል አይደለም። በአገር አቀፍ ደረጃ የሚገኙ  አዋሽ፣ ቦረከናና ሌሎች ወንዞች ከኢንዱስትሪዎችና ከከተሞች በሚወጡ ቆሻሻዎች መበከላቸው ተመልክቷል፡፡ ከሽንት ቤት ጉድጓዶች የሚወጡ ፍሳሾች፣ …

ጥር ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሚኒስትር አለማየሁ ተገኑ ይህን የተናገሩት አንድ የግብጽ ጋዜጣ የአገሪቱን ከፍተኛ ባለስልጣን በመጥቀስ የዘገበውን ዜና ተከትሎ ነው። ጋዜጣው ፣ ኢትዮጵያ ለፖለቲካ ፍጆታ ለማዋል በማሰብ ግድቡ 30 በመቶ እንደተጠናቀቀ እያስወራች መሆኑዋንና ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት እንዳጋጠማት” መዘገቡ ይታወቃል። የአባይ ግድብ ግንባታ የገንዘብም ሆነ የቴክኒክ ችግር አላጋጠመውም ያሉት ሚኒስትሩ፣ በተያዘለት የጊዜ …

ጥር ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን ተቋርጦ የነበረው የደቡብ ሱዳን የሰላም ድርድር ዛሬ በጋዝ ላይ የምሽት ክበብ ውስት መጀመሩን ቢቢሲ ዘግቧል። ቀደም ብሎ በሸራተን አዲስ የነበረው የድርድር ቦታ የተቀየረው ቦታውን አትዮጵያን በመጎብኘት ላይ ያሉት የጃፓኑ ጠ/ሚኒስትር ሾኒዝ አቤ በመያዛቸው ነው። ድርድሩ በምሽት ክለብ ውስጥ መሆኑ አንዳንድ ተደራዳሪዎችን አላስደሰተም። በቤቱ ውስጥ የሚሰማው ጫጫታ …

በዚህ በጀርመን ሀገር ፤ በስፋት የ 4ኛነቱን ደረጃ በያዘችው ከተማ

በኮሎኝ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተቋቋመው የእስፖርትና ባህል ማሕበር ፤

ከትናንት በስቲያ ፣ ረዘም ላለ ጊዜ የከተማይቱ ኑዋሪዎች የሆኑና

በቅርብ ጊዜም የመጡ በጠቅላላ 250

የምርጫ 97ን ቀውስ ተከትሎ ወደ እስር ቤት ከገቡት የቀድሞዎቹ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ (ቅንጅት) አመራሮች መካከል አንዱ የነበሩት ኢንጂነር ግዛቸው ሺፈራው፣ በቅርቡ የአንድነት ለፍትሕና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል፡፡ ስለአዲሱ ሊቀመንበርነታቸው፣ ስለመጪው ዓመት ምርጫና ሌሎች ጉዳዮች ነአምን አሸናፊ አጋግሯቸዋል፡፡

ሪፖርተር፡- አንድነት የወጣቶች ፓርቲ ነው ይባላል፡፡ ነገር ግን አመራሩ ላይ ወጣቶች አይታዩም በማለት የሚተቹ አሉ፡፡ የእርስዎን ዳግም ሊቀመንበር ሆኖ መመረጥንም እንደ ምሳሌ ያነሱታል፡፡ ለምንድነው ወጣቶች ወደ አመራር የማይመጡት?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- ይህንን ጥያቄ መጠየቅ ያለባቸው መራጮች ናቸው፡፡ መራጮችንና የአንድነት አባላትን መጠየቅ ነው፡፡ በመሠረቱ አንድነት የወጣቶች ፓርቲ ነው፡፡ ባለፈው ሥራ አስፈጻሚም ሆነ በብሔራዊ ምክር ቤቱ የወጣቱ ተሳትፎ ከፍተኛ ነበር፡፡ በጠቅላላ ጉባዔው ሰባ በመቶ አካባቢ ወጣት ነው፡፡ የተወዳደርኳቸው ሰዎችም ወጣቶች ናቸው፡፡ ስለዚህ ይህ ነገር መጠየቅ ያለባቸው አባላትና ጉባዔው ናቸው፡፡
መጠየቅ ያለበት እኔ ፍላጎት ኖሮኝ ወጣቶችን ወደታች ገፍቼ ድርጅታዊ ሥራ ሠርቼ ብመጣ ኖሮ ነበር፡፡ ወጣቶችን ወደታች ተጭነሃል ማለት ይቻል ነበር፡፡ ዋናው ማየት ያለብን ጠቅላላ ጉባዔውና አጠቃላይ ሒደቱ ዲሞክራሲያዊ ነበር ወይስ አልነበረም ነው፡፡ በእኔ ግምት አንድነት ፓርቲ ለዲሞክራሲያዊ አሠራር ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ ፓርቲዎች የሚበልጠው ያለ አይመስለኝም፡፡ ለዚህም የምገልጸው በምክር ቤታችንም በሕገ ደንባችን መሠረት የምንሰበሰበው በሦስት ወር አንዴ ነበር፡፡ ምክር ቤቱ ግን በዓመት እስከ 20 ጊዜ ይሰበስባል፡፡ ምክንያቱም የጀመርነውን አጀንዳ በምናደርገው ሰፊ ውይይት መጨረስ አንችልም፡፡ አጀንዳ ጨርሰን አናውቅም፡፡ አራት አጀንዳዎች ቀርበው እንደሆን ሁለቱን ጨርሰን ሁለቱን ደግሞ ለሚቀጥለው ጊዜ እናስተላልፋለን፡፡ ይህ ደግሞ የዲሞክራሲያዊ ውይይት ነፀብራቅ ነው፡፡
እኔ እንዲያውም ቅስቀሳ አላደረግኩም፡፡ የእኔ ተወዳዳሪዎች ቅስቀሳ አድርገዋል፡፡ ስለዚህ ምርጫው ዲሞክራሲያዊ ነው ወይም አይደለም? የሚለው ነው ጥያቄው፡፡ ዲሞክራሲያዊ ነበር፡፡ ለምን ወጣቶች አልመጡም ለሚለው የእነሱ ምርጫ ነው፡፡ እኔ በአብዛኛው የተመረጥኩት በወጣቶች ነው፡፡ ምናልባት ከዚህ በፊትም እንዳደረግኩት ወጣቶችን የማሳተፍ አመለካከትና ባህሪ አለኝ፡፡ እኔ አመራር በነበርኩበት ጊዜ በሕገ ደንቡ መሠረት በሥራ አስፈጻሚ 13 አባላት ነው የሚኖሩት፡፡ እኔ ግን ወጣቶች ወደፊት እንዲቆጠሩ ስድስት አባላት ድምፅ የመስጠት ሥልጣን ሳይኖራቸው አስገብቻለሁ፡፡ ደንቡ ስለማይፈቅድልኝ ነው እንጂ ባለድምፅ ሆነው መግባት ይችሉ ነበር፡፡ ደንቡ ግን አይፈቅድም፡፡ ስለዚህ ድምፅ አልባ ከመሆናቸው በስተቀር ሙሉ በሙሉ የአመራር አባል ነበሩ፡፡
አቶ ግርማ ሰይፉም የዚያ አባል ነበሩ፡፡ ሌላው ወጣቱን ለዚህ ቦታ ማንም አልከለከለውም፡፡ አንዳንድ ጊዜ የተሳሳተ አመለካከት አለ፡፡ ሜካኒካል ይሆናል፣ ኮታ ይሆናል፡፡ ወጣቶች መምጣት አለባቸው፡፡ የኮታ ጉዳይ አይደለም፡፡ ይህ የመብት ጉዳይ ነው እንጂ የሚሰጣቸው ስጦታ አይደለም፡፡ ስለዚህ በአንድነት ፓርቲ ለወጣቶችም ሜዳው ክፍት ነው፡፡ ነገ ጠዋት የላቀ ከመጣ ምክር ቤቱ በወጣት ሊተካ ይችላል፡፡ ከፖለቲካም አንፃር መታየት ያለበት ስብጥሩ ነው፡፡ ከወጣቶችም፣ ከጐልማሶችም፣ ከአዛውንትም ያ ስብጥር ነው መሆን ያለበት፡፡ ወጣትም ሆኖ ሽማግሌም ሆኖ የራሱ የሆነ ችግር አለበት፡፡ ያንን የሚያቻችለው መቀላቀሉ ነው፡፡
ሪፖርተር፡- በተቃዋሚውም ሆነ በገዥው ፓርቲ ውስጥ ያሉት የ60ዎቹ ትውልድ አባላት አመራርነት የሚያበቃውና ወጣቶች በሰፊው ወደ መሪነት የሚመጡት መቼ ነው?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- በእኔ በኩል በአመዛኙ በአንድነት ፓርቲ ውስጥ የ60ዎቹ ትውልድ ፖለቲካ የሚለው አይሠራም፡፡ ባለፈው አላየነውም አሁንም አይታይም፡፡ የአንድነት ዕድሜ ስድስት ዓመት ነው፡፡ በስድስት ዓመት ጊዜ ውስጥ አራት ፕሬዚዳንቶችን ለውጧል፡፡ የመጀመሪያዋ ብርቱካን ሚደቅሳ ነበረች፡፡ የወጣቶች ተወካይ ነበረች፣ የ60ዎቹ አይደለችም፡፡ ከዚያ እርሷ ስትታሰር እኔ ተጠባባቂ ሆኜ ኃላፊነቱን ተረከብኩ፡፡ ከዚያ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ሆነ፣ አሁን እኔ መጣሁ፡፡ ማንም ፓርቲ በስድስት ዓመት ውስጥ አራት ፕሬዚዳንት የቀየረ የለም፡፡ ይህ የሚያሳየው የአንድነትን ዲሞክራሲያዊነት ነው፡፡ በመሠረቱ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ብቃት ባለው ከ60ዎቹ በኋላ ባለው ትውልድ መተካት አለበት፡፡ ያ የእኔ እምነት ነው፡፡ የ60ዎቹ ፖለቲከኞች መጪውን ትውልድ አብቅተው መተካት እንዳለባቸው እምነቴ ነው፡፡
ሪፖርተር፡- አሁን አንድነትን እንደ ምሳሌ ከወሰድነው መጀመሪያ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ወጣት መሪ ነበሩ፡፡ ከዚያ እሳቸው ሲታሰሩ እርስዎ መሪ ሆኑ፡፡ ቀጥሎ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ አሁን ደግሞ ተመልሰው እርስዎ መጡ፡፡ በአንድነት ውስጥ ከወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ውጪ ያው የ60ዎቹ ትውልድ አባላት ስለሆናችሁ ከዚያ አንፃር ለማለት ፈልጌ ነው?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- ትክክል ያልሆነ ምዘና ነው፡፡ ምንድነው የ60ዎቹ ፖለቲከኞች ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ቅድም እንዳልኩህ ስብጥሩን ነው ማየት ያለብን፡፡ ብርቱካን በነበረችበት ጊዜም ሆነ አሁን ሥራ አስፈጻሚ ውስጥ የነበሩ ግለሰቦች ጥቂት ናቸው፡፡ ምናልባት በጣት የሚቆጠሩ [እኔ፣ ነጋሶ፣ አስራት]፡፡ ነገር ግን ሥራ አስፈጻሚ ውስጥ የነበሩት አብላጫዎቹ ከ60ዎቹ በኋላ የመጡ ትውልዶች ናቸው፡፡ በአሁኑ ብሔራዊ ምክር ቤት ውስጥ ከ35 ዓመት ዕድሜ በታች ያሉት 72 በመቶ ናቸው፡፡ የ60ዎቹ አሉበት፡፡ ነገር ግን በአብላጫው ወጣቶች ናቸው፡፡ በእኔ ካቢኔ ውስጥ የ60ዎቹ ትውልድ ያለነው ሁለት ሰዎች ነን፡፡ ከ15 ሰዎች አንድ ሰው የ60ዎቹ ሆኖ ላይ ስለተቀመጠ የ60ዎቹ ተፅዕኖ አለ ለሚባለው ምዘናው ትክክል አይመስለኝም፡፡ መታየት ያለበት ይዘቱ ነው፡፡ የ60ዎቹ ትውልድ አባላት እንዲያውም የት እንዳሉ ግራ ይገባኛል፡፡ አንዳንድ ቦታ መሪ ስለሆነ ብቻ ነው፡፡ የፓርቲው መዋቅር መፈተሽ ካለበት የ60ዎቹ የፖለቲካ ተሳፊዎች ወጥተው ዳር የቆሙ ይመስለኛል፡፡ ደግሞም የተፈጥሮ ሒደት ነው፣ የፖለቲካም ሒደት ነው፣ የታሪክም ሒደት ነው፡፡ መታየት ያለበት የግለሰቦች የ60ዎቹ ትውልድ መሆን ሳይሆን ስብጥሩ ውስጥ ስንት አሉ የሚለው ነው፡፡
ሪፖርተር፡- አሁን እንደ አዲስ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ሆነው መጥተዋል፡፡ ለፓርቲው ምን አዲስ ነገር ይዘው መጡ?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- እኛ ፓርቲያችንን የምንመራው በሥርዓት ነው፡፡ ፓርቲው በ2002 ዓ.ም. የስትራቴጂ ዶክመንቱንና የአምስት ዓመት ዕቅዱን በመጽሐፍ መልክ አውጥቶታል፡፡ የአነድነት ፓርቲ መሠረታዊ ራዕይና ግብ በዚያ ውስጥ ነው የሚታየው፡፡ እዚያ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ነው ሁላችንም በቀጣይነት እየገነባን የምንሄደው፡፡ ነገር ግን በ2002 እና በ2003 ዓ.ም. ያወጣነው የስትራቴጂ ግንባታ ከወቅቱ ሁኔታ ጋር መዛመድ አለበት፣ መቀነባበር አለበት፡፡ ስለዚህ በዚያ መንገድ አንዳንድ ለየት ያሉ ሙከራዎች አካሂዳለሁ፡፡
የመጀመሪያው ሙከራዬ አንድነት ምናልባት ካሉት ፓርቲዎች በጉልህ ጠንክሮ የሚታይና መዋቅሩ ታች ድረስ የወረደ ነው፡፡ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ እንዲያው እንደ ሌላው ጉልበት ወይም አቅም አለን ባንልም በቂ የመንቀሳቀስ ችሎታ አለን የሚል ግምት አለኝ፡፡
ይህንን የአመራር መርህ ከአንድነት አቅምና ሕዝባዊ ገጽታ አንፃር የተለየ (Rebranding) እንዲሆን አደርጋለሁ፡፡ ለምሳሌ አንዱ ያደረግኩት ሥራ አስፈጻሚውን በአብዛኛው ወጣትና አዲስ ነው ያደረግኩት፡፡ በትምህርታቸው ብቁ የሆኑ ናቸው፡፡ በትምህርት ብትሄድ አሁን ከ15 ሰዎች ስድስቱ ሁለተኛ ዲግሪ አላቸው፡፡ ሰባቱ የመጀመርያ ዲግሪ አላቸው፡፡ ሁለቱ ደግሞ ዲፕሎማ አላቸው፡፡ አሁን ይኼ አዲስ ምልክት (New Branding) ነው፡፡ ሁለተኛ እነዚህን ሰዎች ስመድብ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ችሎታ እንዲኖራቸው አንዱ መሥፈርት ነበር፡፡ አሁን ዘመኑ ወደዚያው እያመራ ነው፡፡ ስለዚህ በኢንፎርሜሽን ግንኙነታችን ከውጭው መረጃ እኩል አንድነት መራመድ አለበት፡፡
ሌላው ትኩረት የምሰጠው ወጣቶችን የማብቃት ሥራ ነው፡፡ ወጣቶች በቅተው ፓርቲውን እንዲመሩ አደርጋለሁ፡፡ አሁን እኔ እዚህ ሆኜ ወጣቶችን ነው ወደፊት እንዲሮጡ የማደርገው፡፡ ይህን ካደረግኩ በኋላ በእኔ እምነት ክርክርም መካሄድ አለበት፡፡ እስካሁን የተካሄደው የተቃዋሚ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ውጤት አላስገኘም፡፡ ይኼ ምንም የምንክደው አይደለምና ይህ ለምንድን ነው የሚለው ብዙ ጊዜ ይረብሸኛል፡፡ ወይ ማቆም አለብን ወይ መሥራት አለብን፡፡ እስካሁን ኢትዮጵያ ውስጥ የተበጣጠሱ ዘጠና ፓርቲዎች አሉ፡፡ ከዘጠናዎቹ ደግሞ ጉልህ የሆኑት አሥር አይሆኑም፡፡ አሥሩም አብረው መሥራት አልቻሉም፡፡ በጥምረትም በግንባርም አልተቻለም፡፡ ለምንድን ነው? ለአሥሩም ቢሆን አሥር መሪዎች አሉ፣ አሥር ፕሮግራሞች አሉ፡፡ አሥሩም እንግዲህ አሥር መሪ ኖሮዋቸው ፖለቲካ ይመራሉ የሚል እምነት የለኝም፡፡ ስለዚህ በብሔራዊ ምክር ቤትና በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ውሳኔ አስገኛለሁ የሚል እምነት አለኝ፡፡
በእኔ እምነት እንግዲህ አንድነት ፓርቲ ግንባርና ጥምረት ውስጥ አይገባም፡፡ ወደ ውህደት አንድ አመራር አንድ ፕሮግራም ወዳለው እንቅስቃሴ እንገባለን የሚል እምነት አለኝ፡፡ ይህ የእኔ ሐሳብ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ስብሰባ ላይ ፈንጥቄያለሁ፡፡ ይህ መሆን አለበት፡፡ የተጀመሩት ውህደቶች በሚቀጥሉት ሦስት ወራት ማለቅ አለባቸው ብሎ ጠቅላላ ጉባዔው ወስኗል፡፡ ወይ እንዋሀዳለን ወይ እንለያያለን፡፡ ስለዚህ በዚህ ሁኔታ አንድ የማየው እስከ 2007 ዓ.ም. ወይም በዚህ ዓመት ለእኔ የውህደት ዓመት ነው ብዬ የምገምተው፡፡ ወይ እንዋሀዳለን አለበለዚያ በሰላም ተለያይተን ሁላችንም ጉልበታችንን በየአካባቢው በትብብር እናጠናክር የሚል አመለካከት አለኝ፡፡
ይህን ካደረግኩ በኋላ ከኢሕአዴግ ጋር ገንቢ ግንኙነት (Constructive Engagement) እንዲኖረን እፈልጋለሁ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የጥላቻ ፖለቲካ ማብቃት አለበት፡፡ ኢሕአዴግ ተቃዋሚዎችን የሚያያቸው እንደ ጠላት ከዚያም አልፎ እንደ ሽብርተኛ ነው፡፡ ይኼንን ነገር ለሚያስብ ሰው እኮ በጣም ነው የሚያስደነግጠው፡፡ በእኛም በኩል ኢሕአዴግን የምናየው እንደ አውሬ ነው፡፡ ምናልባት የሠራውን ሥራ ሁሉ ዋጋ (Credit) ያለመስጠት አለ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ፖለቲካችን ኢሕአዴግን መቃወም ብቻ ሆኖአል፡፡ ያ መቆም አለበት፡፡ ትልቁ ኳስ ያለው ኢሕአዴግ ዘንድ ነው፡፡ እኔ በበኩሌ ወደፊት በማደርገው እንቅስቃሴ ገንቢ ግንኙነት አድርገን ያለውን የፖለቲካ ምኅዳር ለሁላችንም እኩል ማድረግ አለበት፡፡ ኢቴቪ የኢትዮጵያ ሕዝብ ቴሌቪዥን ጣቢያ ነው፡፡ ለምንድነው የኢሕአዴግ ብቻ የሚሆነው? መብት እኮ አለን፡፡ ለኢቴቪ ደብዳቤ ጽፈናል፡፡ የጻፍነው ምንድነው የኢሕአዴግን ኮንፈረንስ ከባህር ዳርና የኢሕአዴግን ብሔራዊ ምክር ቤት በቀጥታ ስታስተላለፉ ነበር፡፡ የእኛን ግን አልዘገቡም፡፡ ለኢሕአዴግ 99 በመቶ ሰጥተው ለእኛ ግን አንድ በመቶ እንኳን አይሰጡንም፡፡ ይኼ ሁሉ ቁልጭ አድርጐ የሚያሳየው የኢሕአዴግን ድክመትና ስህተት ነው፡፡
ሪፖርተር፡- ለብዙ ፓርቲዎች የእንዋሀድ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ነገር ግን ከዚህ ቀደም እንደታየው ብዙ ውህደቶች ምርጫ ሲደርስ ከመሰባሰብ በዘለለ ብዙም ሲገፉበት አይስተዋልም፡፡ የ97ቱን ቅንጅት ማስታወስ ይቻላል፡፡ ከዚህ አንፃር አሁን እርስዎ የሚያቀርቡት ሐሳብ በምን ይለያል? ከዚህ ቀደም ተሞክረው እንደከሰሙት እንደማይሆንስ ማረጋገጫው ምንድነው?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- የቅንጅት ራሱን የቻለ ጉዳይ አለው፡፡ ቅንጅት አልተዋሀደም ነበር፡፡ ለዚህም ነው ቅንጅት ግንባር ደረጃ አልደረሰም የሚባለው፡፡ ለቅንጅት ከፍተኛውን ድቀት ያስከተሉት የኢሕአዴግና የቅንጅት መሪዎች ናቸው፡፡ በወቅቱ ኢሕአዴግ ያልጠበቀው የፖለቲካ አድማስ ነው የመጣበት፤ በ97 ምርጫ አልጠበቀውም ነበር፡፡ አራቱ ፓርቲዎች ማለትም መኢአድ፣ ኢዴፓ፣ ቀስተ ደመናና ኢዴሊ ሆነው ቅንጅት የተመሠረተው ኅዳር ላይ ነበር፡፡ ኅዳር ላይ ተመሥርተን ግንቦት ላይ ነው ከፍተኛ ዕርምጃ ያሳየነው፡፡ ያ ሁኔታ ኢሕአዴግ ያለውን ግምት በጣም ነው ያዛባው፡፡ ኢሕአዴግ አቅም አይፈጥሩም የሚል ግምት ነበረው፡፡ ገና ስንፈጠር በምርጫው አካባቢ አዲስ አበባን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጠርን፡፡ የምርጫው ዕለት ምሽት በአጠቃላይ የምርጫው ሒደት ተናጋ፡፡ በዚያ ምክንያት ቅንጅት ከፍተኛ ውድቀት ውስጥ ገባ፡፡ ኢሕአዴግ ትኩረት አደረገብን፡፡
በዚያ ምክንያት እኛም ወደ እስር ቤት ገብተን ከዚያ ደግሞ ወጣን፡፡ ያው ነገሩ ትክክል ስላልነበር መውጣት እንደነበረብን እኔ አምናለሁ፡፡ ከወጣን በኋላ ደግሞ እኛ አንድ መሆን አልቻልንም፡፡ በእስር ቤት ውስጥ ብሶት ተፈጠረ፡፡ እንደገና ቅንጅትን ለአቶ አየለ ጫሚሶ ሰጡት፡፡ በዚያ በዚያ በመካከላችን ችግሩን በሰከነ ሁኔታ ለማራመድ አልቻልንም፡፡ በዚህ በኩል የራሱ የኢሕአዴግም የእኛም ድክመት ነበር፡፡ ከዚያ በፊትም በተፈጠሩት ስብስቦች እንደዚሁ የመሪዎች ብዛት ነው ችግሩ፡፡ አሁን እኔ የምለው ውህደት ከሆነ አንድ መሪ ሊኖር ይችላል፡፡ ውህደቱም መፈጸም ያለበት በዲሞክራሲያዊ መርሆዎች መሆን አለበት፡፡ ውህደት ላይ ዲሞክራሲያዊ ባህል መፍጠር አለብን፡፡ አመራር አንድ መሆን አለበት፡፡ ሕግ፣ ሥነ ሥርዓትና ደንቡ መታየት አለበት፡፡ እናም ዲሲፕሊን ሊኖረን ይገባል፡፡ የባህሪ ለውጥም ያስፈልገናል፡፡ ከዚህ አንፃር አንደኛ እኛ አመራሮች የባህሪ ለውጥ ያስፈልገናል፡፡ ያ እስከሆነ ድረስ እኔ ውህደት ይወድቃል ብዬ አላስብም፡፡ አልተሞከረም፡፡ በተጨባጭ ብሔራዊ ዕይታ ያለው ውህደት እኮ እስካሁን አልተካሄደም፡፡
ሪፖርተር፡- ከዚህ ከውህደቱ ጋር በተያያዘ የርዕዮተ ዓለም ጉዳይስ እንዴት ነው የሚታየው? ብሔራዊ የሆነ ፓርቲ ይኖራል፤ ኅብረ ብሔራዊ የሆኑ ፓርቲዎችም ይኖራሉ፡፡ ይህስ ለውህደቱ እንቅፋት አይሆንም?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- እኔ ሁላችንም ወደ ብሔራዊ ምክክር መምጣት አለብን የሚል እምነት አለኝ፡፡ ለምሳሌ ብሔር ተኮር የሆነ ፓርቲ ከእኛ ጋር ሲዋሀድ ብሔራዊ ቅርፅ መያዝ አለበት፡፡ አለበለዚያ ብሔር ተኮርና ኅብረ ብሔር ሊዋሀዱ አይችሉም፡፡ ምንድነው ጠቃሚው ነገር? ዲሞክራሲ እስከሆነ ድረስ ለምሳሌ የእኛ ፕሮግራም የግለሰብንም የቡድንንም መብት ያከብራል፡፡ የብሔረሰብ ጉዳይ ከሆነ የቡድን ጉዳይ ነው፡፡ ያ እስከተጠበቀ ድረስ ማንኛውም የብሔር ፓርቲ እኛን ይቀላቀላል የሚል እምነት አለኝ፡፡ ያ ነው ጠቃሚው ነገር፡፡ የፕሮግራሙ ዕይታ ብሔር ተኮር የሆኑትን ፓርቲዎች ፍላጐት ማሟላት አለበት፡፡ የብሔረሰቡ ቋንቋ፣ የብሔረሰቡ የመወሰን መብትና ባህል ማሟላት አለብን፡፡ ይኼ የኢትዮጵያ ነፀብራቅ ነው፡፡ አንዴ ወደ ላይ አንዴ ወደ ታች የምንልበት ጉዳይ አይደለም፡፡ እኩልነት እስካለ ድረስ የብሔረሰብ ጉዳይ አይነሳም ባይ ነኝ፡፡ ፍትሕ፣ እኩልነት፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እስካሉ ድረስ ችግር ያለ አይመስለኝም፡፡
ሪፖርተር፡- አንድነት አሳካዋለሁ ወይም በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ አመጣዋለሁ የሚለው የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም ምንድነው?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- የእኛ ሊበራል ዲሞክራሲ ነው፡፡ ሊበራል ዲሞክራሲ ሆኖ የቡድንና የግለሰብ መብትን አንድ ላይ እናከብራለን፡፡
ሪፖርተር፡- በሊበራል ዲሞክራሲ የቡድንም የግልም መብት ይከበራል ብለዋል፡፡ ነገር ግን የፍላጐት መጋጨት አይኖርም? በቡድን መብትና በግለሰቦች መብት መካከል ማለት ነው?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ነው የሚወሰነው፡፡ በዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ስንት ሰዎች ናቸው እንደዚህ የሚሉት? ሊኖርም ይችላል፡፡ ይህ ተፈጥሮአዊ ነው፡፡ አሥር ሰዎች ሁለቱን አባረው ማካሄድ አይችሉም የሚል ይኖራል፡፡ 90 በመቶ ከደገፈው የ90 በመቶ ይሆናል ለሚለው የዲሞክራሲ ውሳኔ ነው የሚጠይቀው፡፡ እኛም ተወያይተንበታልና የሚወሰነው በዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መሠረት ነው፡፡
ሪፖርተር፡- በሚቀጥለው ዓመት የሚካሄድ አገር አቀፍ ምርጫ አለ፡፡ አንድነት እንደ አንድ ተቃዋሚ ፓርቲ በምርጫው ለመሳተፍና ተጨባጭ ውጤት ለማስመዝገብ ምን ምን ሥራዎችን እየሠራ ነው?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- አንደኛ የራሳችንን አቅም እየገነባን ነው፡፡ ከጠቅላላ ጉባዔያችን ዕይታ አግኝተናል፡፡ በዚያ ዕይታ ለምሳሌ የውህደቱ አንዱ ዓላማ በምርጫ የማሸነፍ ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም አንድነት ብቻውን ከሚሮጥ ሦስትና አራት ፓርቲ ሆነን ልክ እንደ ቅንጅት ብንሮጥ የተሻለ ውጤት እናገኛለን በማለት፣ በውህደቱ ለምርጫው አንድ የጐለበተ አቅም ለመፍጠር የምናደርገው ስትራቴጂ ነው፡፡ ሁለተኛው ፕሮግራማችንንና ርዕዮተ ዓለማችንን ልክ እንደ ሚሊዮኖች ንቅናቄ ወደታች እናወርደዋለን፡፡ አንድ የሕዝብን ዕይታ የሚስብ ከምርጫ 2007 ጋር የሚገናኝ ፕሮግራም እናወጣለን፡፡ ሕዝብን ለማንቀሳቀስ ከዚህ በተጨማሪ አንድነት የዲሞክራሲ ምርጫ ፓርቲ ነው፡፡ ለማንኛውም ሁልጊዜ ለምርጫ ይዘጋጃል፡፡ አሁን ስትራቴጂያችንን ከልሰን ከወቅታዊ ሁኔታ ጋር አማራጭ ፖሊሲዎችን እንቀርፃለን፡፡ ከአማራጭ ፖሊሲዎች በመነሳት የምርጫ ማኒፌስቶ እናዘጋጃለን፡፡ በእኔ ዕይታ እስከ ሰኔ ድረስ ካለፈም እስከ ነሐሴ ድረስ አንዱና ትልቁ ሥራችን ይህንን የምርጫ ፖሊሲና ማኒፌስቶ ማዘጋጀት ነው፡፡ ከዚያ ብቁ የሆኑ ዕጩዎችን ከካቢኔያችን ውስጥ እንመለምላለን፡፡ ከየቦታው ብቁ የሆኑ ታዛቢዎችንም እንመርጣለን፡፡ ይህ ሒደት ነው፡፡ ሕዝባዊ ስብሰባ እናካሂዳለን፡፡ እንደዚሁም ሕዝባዊ ንቅናቄ ይኖረናል፡፡ እየሄድን ራሳችንን ወደ ሕዝብ የምናወርድበት፡፡ ይህን ሁሉ ለማድረግ ግን የምርጫ ፓርቲ ብንሆንም ምርጫ ውስጥ ጥልቅ ብለን አንገባም፡፡ ሜዳው ለሁላችን እኩል መሆኑን እናረጋግጣለን፡፡ ስለዚህ ከላይ እንዳልኩት ለዚህ ነው ገንቢ ግንኙነት (Constructive Engagement) ከገዥው ፓርቲ ጋር የምናደርገው፡፡ ይኼ ሜዳ ለሁላችንም እኩል እንዲሆን ነው የምንፈልገው፡፡ ኢትዮጵያ የጋራችን ነች፡፡ ኢሕአዴግ አንድ ፓርቲ ነው፡፡ እኛም አንድ ፓርቲ ነን፡፡
የምርጫው ሕግ በሕገ መንግሥቱና በምርጫ ቦርድ ሕግ መሠረት መካሄድ ስላለበት ያንን እንጠይቃለን፡፡ ምርጫ ቦርድ የኢሕአዴግ ከሆነ፣ ሚዲያው የኢሕአዴግ ከሆነ፣ የፍትሕ አካላቱ የኢሕአዴግ ከሆኑ እኛ ያን ጊዜ የምንወስነው ውሳኔ ይኖራል፡፡ ነገር ግን ከትዝብትም ጭምር እስካሁን ያሉት ተቋማት ለእኔ ዲሞክራሲያዊ አልነበሩም፡፡ የ2002 ምርጫ በጣም ያዘንኩበት ምርጫ ነበር፡፡ በ21ኛው ክፍለ ዘመን 99.6 በመቶ የሚያገኝ ፓርቲ የለም፡፡ በዓለም ላይ ዲሞክራሲያዊ በሆነና ውድድሩ በእኩል ሜዳ ላይ ተካሂዶ በእዚህ ውጤት ማሸነፍ አይቻልም፡፡ በዓለም ዙሪያ በአብዛኛው መንግሥት በቅንጅት እየተፈጠረ ነው፡፡ እንግሊዝን ውሰድ የኮንሰርቫቲቭና የሌበር ፓርቲ ቅንጅት ነው፡፡ ጀርመን፣ ጣሊያንና ኖርዌይም እንዲሁ ቅንጅት ነው፡፡ ምክንያቱ በዲሞክራሲያዊ ሥርዓቱ ውድድሩ ነፃ ነው፡፡ እናም ስለዚህ 99.6 በመቶ በጭራሽ ሊሆን አይችልም፡፡ እንኳን እንደ ኢትዮጵያ ያለ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦችና የኅብረተሰብ ክፍል ባህሪ ባለበት አገር ይኼ አይቻልም፡፡ ይኼ ነገር መለወጥ አለበት፡፡ እናም ለምርጫ እንዘጋጃለን፡፡ ነገር ግን ሜዳው ሁላችንንም እኩል ማስተናገድ አለበት፡፡
ሪፖርተር፡- የመጫወቻ ሜዳው ለሁላችሁም እኩል መሆኑን እንዴት ማረጋገጥ ትችላላችሁ?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- ለምሳሌ በምርጫ 97 ሚዲያው ትንሽ ወደ ኢሕአዴግም ቢያደላ ተከፍቶ ነበር፡፡ እንዲያውም የእነሱ ሜዳ ከፍ የእኛ ሜዳ ዝቅ ቢልም፣ ነገር ግን የመወዳደርያ ቦታ ነበረው፡፡ የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ክርክሮች ለሕዝብ የወጡት በ97 ምርጫ ነበር፡፡ በ2002 ምርጫ ሚዲያው ታፍኖ ነበር፡፡ ሚዲያው የሕዝብ ጥያቄ አላስተናገደም፡፡ ዝም ብሎ ለይስሙላ ቴሌቪዥን ጣቢያ ተሂዶ አንዳንድ ነገሮች መነጋገራችንን ሕዝብ ሊሰማው ይችላል፡፡ ነገር ግን በሆነ እጅ ቁጥጥር ሥር የወደቀ ነበር፡፡ ያ መሆን የለበትም፡፡ እናም ትልቁ ምሳሌ የ97 ምርጫ የሚዲያ ጉዳይ ነበር፡፡ ሚዲያው ያን ጊዜ ተከፍቶ ነበር፡፡ በእኩልነትም ባይካሄድም ያን ጊዜ እንደ እኩል ነው የወሰድነው፡፡ እንደዚያ መሆን አለበት፡፡
ሪፖርተር፡- ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ አንድነት የፀረ ሽብር ሕጉ ይሰረዝ የሚል አቋም ይዞ እየተከራከረ ነው፡፡ አሁን ደግሞ በመላው ዓለም ሽብርተኝነት ትልቅ ሥጋት ሆኗል፡፡ በእኛ አገር የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ አጠቃቀም ተቃዋሚዎችን ፀጥ ለማሰኘት ነው የሚለው እንዳለ ሆኖ፣ አንድነት እንደ ፓርቲ አማራጭ የፀረ ሽብር ሕግ አለው ወይ ይሰረዝ ሲል ምን ማለት ነው?
ኢንጂነር ግዛቸው፡- መጀመርያ ሽብርተኝነትን መዋጋት የኢሕአዴግ ብቻ አይደለም፡፡ የማንኛውም ዜጋ ነው መሆን ያለበት፡፡ ይኼ ሽብርተኝነት ዓለም አቀፍ እንቅስቃሴው አስከፊ፣ ከሰው ልጅ ባህሪ በተለየ የሰው ልጅን መንፈስ የሚሰብር፣ የሰው ልጅነትን የሚቀንስ ነው፡፡ አንድነትም ሆነ እኔ እንደ አንድነት አመራር እንደዚሁም እንደ ዜጋም እንዋጋለን&#496

በአሁኑ ወቅት 30 በመቶ ግንባታው የተጠናቀቀውና በሦስት ዓመታት ውስጥ ግንባታው ሙሉ ለሙሉ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በተመለከተ፣ ‹‹ቴክኒካዊ›› በሆኑ ጉዳዮች ላይ ተከታታይ ድርድሮች እየተደረጉ ነው፡፡

በእያንዳንዱ ድርድር ከሚስተዋሉ አቋሞች ግን ለዘመናት የቆዩ ሴራዎች መልካቸውን ቀይረው እየመጡ ይመስላል፡፡

በታላቁ የዓባይ ግድብ ላይ የዓለም አቀፍ ባለሙያዎች ቡድን ጥናት ውጤት የያዘው ሪፖርት አሁን እየተደረጉ ላሉት ድርድሮች መሠረት የሚጥል ነው፡፡ ሪፖርቱ እንደሚለው፣ የግድቡ ግንባታ እንዲቋረጥ ምንም መሠረታዊ ምክንያት ባለመኖሩ፣ በተቻለ መጠን በታችኛው የዓባይ ተፋሰስ አገሮች ላይ ሊያስከትለው የሚችለው የውኃ ፍሰት መጠን መቀነስና ቴክኒካዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሦስቱም አገሮች ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ሱዳን በጋራ ተቀራርበው መሥራት እንዳለባቸው ነው፡፡ በተረፈ የግድቡ ግንባታ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን ሪፖርቱ አጽንኦት ይሰጣል፡፡

የግብፅ ዥንጉርጉር አቋሞች

ኢትዮጵያና ሱዳን ሪፖርቱን በፀጋ የተቀበሉት በመሆናቸው ሚስጥርነቱ እንደተጠበቀ እንዲቆይም የሚቻላቸውን ጥረት አድርገዋል፡፡ በሌላ በኩል ግብፅ በሪፖርቱ ላይ የተዘበራረቀ አቋም እያንፀባረቀች በመሆንዋ ሪፖርቱ ይፋ በሆነበት ወቅት በተጠራው ብሔራዊ ምክክር፣ በተለይ የግብፅ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በኢትዮጵያ ላይ ጦር ኃይሉ እንዲዘምት ድምፃቸው ተሰምቷል፡፡ ግብፅ ባጋጠማት ቀውስ ምክንያት እየተደረጉ ያሉት የባለሥልጣናት መቀያየር የግብፅ መንግሥት አቋም ለትንተና የማይመች ቢሆንም፣ አንዱ የሌላውን ስህተት እየደገመ ይመስላል፡፡ አንዱ ከሌላው ስህተት እየተማረ አይመስልም፡፡ አሁን ሥልጣን ላይ ያለው የሽግግር መንግሥት ከአንድ ዓመት የሥልጣን ቆይታ ጊዜ በኋላ የተባረረውን የፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲ መንግሥት በኢትዮጵያና በዓባይ ግድብ ላይ የተለሳለሰ አቋም መያዙ ለውድቀቱ ምክንያት መሆኑን እየተናገረ ነው፡፡

ሁለተኛ ከላይ ከተጠቀሰው ምክንያት ጋር ተያያዥነት ያለው ቢሆንም፣ ግብፅ በአንድ በኩል የባለሙያዎቹ ሪፖርትን አለመቀበልዋና በሌላ በኩል የቡድኑን ምክረ ሐሳብ ለመተግበር ድርድር እንዲደረግ መስማማቷ እርስ በርስ የሚጣረሱ አካሄዶች ናቸው፡፡

ሦስተኛ ሪፖርቱን በተመለከተ በሚስጥር ተይዞ መቀመጥ በነበረበት ጊዜ አንዳንድ ተፅዕኖ ያሳርፋሉ ተብለው ለሚገመቱ አገሮችና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተላልፎ እንዲሰጥ ማድረጓ ይነገራል፡፡ እንዲሁም ዋሽንግተን ፖስትን ጨምሮ አንዳንድ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሪፖርቱን ድምዳሜ በተሳሳተ መንገድ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ጥረት ተደርጓል፡፡ ይህ እንግዲህ በአገር ውስጥ የሚደረገውን አሉታዊ የሚዲያ ቅስቀሳን ጨምሮ ማለት ነው፡፡

ያም ሆነ ይህ ግብፅ የሪፖርቱን ውጤት መቀበሏን በግልጽ ባታሳውቅም፣ የባለሙያዎች የቡድንን ምክረ ሐሳብ ለመተግበር በቅርቡ ያለውጤት የተበተነውን ጨምሮ ሦስት ጊዜ ድርድር ተቀምጣ ነበር፡፡

ከኢትዮጵያ የውኃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር የተገኙ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ የባለሙያዎች ቡድን ያቀረበውን ምክረ ሐሳብ ተግባራዊ ለማድረግና ይህንን ተግባራዊ የሚያደርግ ኮሚቴ ለማቋቋም በሁለቱም የመጀመርያ ድርድሮች ግብፅ ተስማምታ ነበር፡፡

በኮሚቴው አወቃቀር ላይ አንዳንድ ውዝግቦች የነበሩ ቢሆንም፣ በመጨረሻ በኮሚቴው ውስጥ ሦስቱን አገሮች የሚወክሉ ዜጐች ብቻ እንዲካተቱ ስምምነት ላይ ተደርሶ ነበር፡፡ ይህ የኢትዮጵያ አቋም ነበር፡፡ ኮሚቴውም ምክረ ሐሳቡን ተግባራዊ በማድረግ ረገድ የውጭ አማካሪ ድርጅትን የመቅጠርን ሥራ ጨምሮ አማካሪው የሚያቀርበውን ሐሳብ ይገመግማል ይላል፡፡

ባለፈው ሳምንት በካርቱም በተደረገው ሦስተኛው የድርድር ዙር ግን የግብፅ ተወካዮች ዓለም አቀፍ አማካሪ ድርጅት እንዲቀጠር ይጠይቃሉ፡፡ የውኃ፣ የመስኖና የኢነርጂ ሚኒስቴር የድንበር ተሻጋሪ ወንዞች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፈቅ አህመድ ግብፆች እንዲቀጠር የፈለጉት የውጭ አማካሪ ድርጅት ቀደም ሲል ስምምነት ከተደረሰበት መንፈስ ውጪ የሚቋቋመውን ኮሚቴ በበላይነት የመቆጣጠር ኃላፊነት እንዲኖረው የሚል ድብቅ አጀንዳ የያዘ መሆኑን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ድርድሩ ያለውጤት ሲበተን በቀጣይነት ግን ለመነጋገር ቀጣሮ ተይዟል፡፡

የኢትዮጵያ ተደራዳሪ ቡድን አባል የሆኑት በዓባይ ወንዝ ፖለቲካ ላይ ግንባር ቀደሙ ተመራማሪው ዶ/ር ያዕቆብ አርሳኖ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በግብፅ የቀረበው የዓለም አቀፍ ባለሙያዎች ቡድን እንዲመሠረት ብትቀበልም በሁለት ነገሮች አለመግባባት ተፈጥሯል፡፡ አንደኛው የባለሙያዎቹ ቡድን በሦስቱ አገሮች የጋራ መግባባት (ሙሉ በሙሉ) መመሥረት አለበት የሚል የኢትዮጵያ አቋምን ግብፅ መቀበል አለመቻሏ ነው፡፡

ሁለተኛው የባለሙያዎቹ ቡድን የሚመሠረተው ከሦስቱም አገሮች የተውጣጡ አባላትን ያቀፈው የምክረ ሐሳቡን አስፈጻሚ ኮሚቴ ባለሙያዎች ቀጥሮ ሥራውን ሲያስፈጽም ድንገት አለመግባባት ከተፈጠረ እንጂ፣ አሁን የሚመሠረትበት አመክንዮ የለም የሚለው የኢትዮጵያ አቋም ነው፡፡

ሌላው ስብሰባው ያለ ውጤት እንዲበተን ምክንያት የሆነው ሦስቱም አገሮች የጋራ መግባባት እንዲኖራቸው ግብፆች ሰባት መርሆች ይዘው መቅረባቸው ነበር፡፡ የመግባባት ሰነድ መፈራረም የዚሁ ስብሰባ አጀንዳ ካለመሆኑም ባሻገር፣ ቀደም ሲል በተለይ የውኃ አጠቃላይ የስምምነት ማዕቀፍ ላይ ሲፈራረሙ፣ ከአሥር ዓመት በላይ ከቆዩ በኋላ አሁን እንዲህ ዓይነት አጀንዳ ላይ መነጋገር ዋናውን ጉዳይ ወደ ጐን ለመግፋት ያለመ በመሆኑ ኢትዮጵያ ያልተቀበለች ምክንያት መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ እንደ ዶ/ር ያዕቆብ እምነት፣ ጥያቄው ሒደቱን ወደ ኋላ የሚመልስ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት የተደረገውን የሚቃረን መርህ ነው፡፡

ዴይሊ ኒውስ የተባለ ጋዜጣን ጨምሮ አብዛኞቹ የግብፅ ሚዲያዎች ግን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸውን ዋቢ አድርገው የዘገቡት ከዚህ በተቃራኒ ነው፡፡ ‹‹ከሦስቱም አገሮች የተውጣጣ አንድ ኮሚቴ እንዲቋቋም ግብፅ ያቀረበችው ሐሳብ በኢትዮጵያ ተቀባይነት አላገኘም፤›› በሚል፡፡

ምን ማለት ነው?

ዓለም አቀፍ የውኃ ኤክስፐርቶች ያሉበት ቡድን ግድቡን አጥንቶ ሪፖርቱን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ ያቀረበውን የምክረ ሐሳብ ለመተግበር ተደጋጋሚ ድርድር እየተደረገ ቆይቷል፡፡ አሁን ግን ድርድሩ እንከን እያጋጠመው ይመስላል፡፡

ዶ/ር ያዕቆብ፣ ‹‹ወደፊት ድርድሩ ምን የሚሆን ይመስልዎታል?›› በማለት ከሪፖርተር ለቀረብላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ ‹‹አሁን እየተሠራ ያለው ሥራ በባለሙያዎች ደረጃ ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ጥናት እንዲደረግ ነው፡፡ በቁጥር ተለክቶ ተወስኖ የሚገለጽ ነገር ነው፡፡ ግብፆች ያንን ነገር መቀበል አይፈልጉም፤›› ብለዋል፡፡

እንደተደራዳሪም እንደ የፖለቲካል ሳይንስ ተመራማሪም የጀመሩትን ምላሽ በመቀጠል፣ ‹‹በቴክኒክ ደረጃ ያለውን ነገር ወደ ላይ ወደ መሪዎች ግብፆች ተመልሶ እንዲሄድና ፖለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ይፈልጋሉ፡፡ እስካሁን የተሠራውንና የተለፋበትን መና የሚያስቀር ነው፡፡ እንዳልተሠራ ሆኖ ወደ ኋላ የሚመለስ ከመሆኑም በላይ፣ በዚያውም ግብፆች የፖለቲካ ውዝግቡን ለሚዲያ ቀልብና ትችት ይዳርጋሉ፤›› ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ በኩል እያንዳንዷ እንቅስቃሴ በጥንቃቄ የምትታይ መሆኗን፣ ድርድሩ በዝርዝርና በቴክኒክ አፈጻጸም ጉዳዮች ላይ እንጂ ወደ ፖለቲካ ተመልሶ የሚሄድበት መንገድ በሩ ዝግ ነው ብለዋል፡፡

በዲላ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ መምህርና በዓባይ ውኃ ውዝግብ ላይ ጥናት ያካሄዱት አቶ ዘሪሁን አበበ በበኩላቸው፣ በአብዛኛው የኢትዮጵያ ተደራዳሪውን ዶ/ር ያዕቆብ ሐሳብ ይደግፋሉ፡፡ ‹‹በግብፅ በኩል ለማድረግ የሚፈለገው አንድና አንድ ነው፡፡ የግድቡ ሥራ እንዲቋረጥ ወይም በጣም ትንሽ ሆኖ እንዲገነባ ነው፡፡ ያ እስካልተሳካላቸው ድረስ ጉዳዩ ሁሌም ፖለቲካዊ መልክ ይዞ በሚዲያ እንዲራገብና ኢትዮጵያን ለማስተቸት ይፈልጋሉ፤›› ብለዋል፡፡ ዞሮ ዞሮ ፍላጐታቸው ቀደም ሲል በብቸኝነት የተፈረመውን እ.ኤ.አ. የ1959 ‹‹ውል›› ማሽከርከር እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ እንደ አቶ ዘሪሁን ገለጻ፣ ግብፆች በአንድ በኩል የተፋሰሱን አገሮች የውኃ ትብብር ማዕቀፉን በጀርባ እየመጡበት ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት የያዘው መንገድ እንዳለ ሆኖ፣ በዓባይ ተፋሰስ አገሮች ሥራ ላይ የዋለውንና ሕግ ሆኖ የፀደቀውን የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት በፈራሚ አገሮች ፓርላማ እንዳይፀድቅ ጥረት ያደርጋሉ፡፡

የተመናመነው የመደራደር አቅም

በዓባይ ግድብ ዙሪያ የሚደረጉ ድርድሮች በሦስት አገሮች መካከል ብቻ የሚደረጉ የሦስትዮሽ ድርድር ሆነዋል፡፡ ቀደም ሲል በግድቡ መገንባት ተቃውሞ ቢጤ አሰምታ የነበረችው ሱዳን ከተወሰነ ጊዜ በኋላ አቋሟን ለመከለስ ተገዳለች፡፡ በመሆኑም አሁን በጉዳዩ ላይ በሚደረጉ ድርድሮች ጐልተው እየወጡ ያሉት ጫፍ የረገጡ ውዝግቦች በሁለቱ አገሮች ማለትም በግብፅና በኢትዮጵያ መካከል ሆነዋል፡፡ ይኼውም ከ80 በመቶ በላይ የዓባይን ውኃ ጥቅም ላይ በምታውለው ግብፅና ለዓባይ ውኃ 86 በመቶ አስተዋጽኦ በምታደርገው ኢትዮጵያ መካከል ነው፡፡ ውዝግቡ በተለያዩ መንገዶች የሚገለጽ ሲሆን፣ የሱዳን አቋም መለወጥ የግብፅን የመደራደር አቅም እየተመናመነ እንዲመጣ ምክንያት መሆኑን አንድ ሪፖርተር ያነጋገራቸው ስማቸው እንዲገለጽ የማይፈልጉ የውኃ ዲፕሎማሲ ተመራማሪ ተናግረዋል፡፡ እሳቸው እንደሚሉት፣ የግብፅ የመደራደር አቅም የተመናመነው ግብፅ ውስጥ ባለው ቀውስ ምክንያት ብቻም አይደለም፡፡ እንዲያውም ሚዲያዎቻቸው ከሚዘግቡት ማስተዋል እንደሚቻለው፣ የግብፅ ፖለቲከኞች አገራቸው ከገባችበት ቀውስ መውጣት የምትችለው አንድ ትልቅ ውጫዊ የሆነ አጀንዳ በመፍጠር መሆኑን የተስማሙ ይመስላሉ፡፡ እሱም የዓባይን ጉዳይ በማቀንቀን ሲሆን፣ ኢትዮጵያ የተባለችውን ‹‹ነባር ጠላት›› ማስቀደምና የውስጥ ጉዳያቸው በድርድር እንዲቆይ ማድረግ ነው፡፡ እንደ ዲፕሎማቱ እምነት ሱዳን በግድቡ ላይ የነበራት አቋም ሲለወጥ በግብፅ ላይ ከፍተኛ መደናገጥ ነበር የፈጠረው፡፡

የዓባይን ግድብ በተመለከተ የሱዳን አቋም መለወጥ ብቻ ሳይሆን፣ የግድቡን ተፅዕኖ ያጠኑት የውኃ ባለሙያዎች ቡድን ሪፖርት የግብፅ ፖለቲከኞች በኢትዮጵያ ላይ ያነጣጠሩትን ሴራ አክሽፎባቸዋል፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት ግብፆች በኢትዮጵያ ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያደርጉት ጉትጐታ ተቀባይነት እንዳይኖረው አድርጐታል፡፡ በተቃራኒው የኢትዮጵያን አቋም በይፋ ሙሉ ለሙሉ ተሰሚነት አገኘ ባይባልም፣ አንዳንድ ትልልቅ መገናኛ ብዙኃን ሚዛኑን በጠበቀ አኳኋን መዘገብ ጀምረዋል፡፡ አሁን ቴክኒካዊ የሆነ ድርድር ወደ ፖለቲካ ደረጃ ከፍ ብሎ ውዝግብ እንዲፈጥር የሚፈለግበት ምክንያት ይኸው ነው፡፡

ቀደም ሲል ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ የምታራምደውን የማዳከም ስትራቴጂ የተገነዘበው የኢትዮጵያ መንግሥት ግድቡን ሙሉ ለሙሉ በራሱ ወጪ ለመገንባት ነበር ያቀደው፡፡ በመሆኑም በፕሮጀክቱ ተፈጥሮም ሆነ ፕሮጀክቱን በተመለከተ የወጣው ዓለም አቀፍ ሪፖርት ግብፅ በውጭው ዓለም ልታሳርፍ የነበረውን ተፅዕኖ በእጅጉ ቀንሶታል፡፡

‹‹በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ›› እንዲሉ፣ በቅርቡ ለግብፅ የውጭ ፖሊሲ ማስፈጸሚያ እንዳትውል ትሰጋ የነበረችው ሱዳን አቋም መለወጥ ብዙ ነገሮችን በግብፆች ላይ ያወሳሰባቸው ይመስላል፡፡ እዚህ ላይ ሁለት ነገሮች ማስታወስ ግድ ይላል፡፡

አንደኛው ከሁለት ዓመት በፊት የአሜሪካ አንድ የደኅንነት ድርጅት (Stratford) እና ዊኪሊክስ ይፋ እንዳደረጉት፣ ግብፅንና ሱዳን ኢትዮጵያንና ታላቁን ግድብ ለማጥቃት ሐሳብ ነበራቸው ተብሎ ነበር፡፡

ሁለተኛው ሱዳን ሥጋት በሚፈጥረው የሁለቱ አገሮች ጦርነት ውስጥ በቀጥታ ትሳተፋለች የሚል ግምት ያልነበረ ቢሆንም፣ ግብፅ ኢትዮጵያን ለማጥቃት የቅርብ ጐረቤት የሆነችው የሱዳንን ግዛት እንደ መንደርደርያ ልትጠቀምበት ትችላለች የሚል ግምት ነበር፡፡

ግብፅ የዓባይን ውኃ በብቸኝነት ለመጠቀም ታዋቂና በአብዛኛው የውኃው ባለቤት ከሆነችው ኢትዮጵያ ውጪ የተደረጉት እ.ኤ.አ. የ1929ና የ1959 አሮጌ ስምምነቶች በአዲሱ ሁለገብ የውኃ አጠቃቀም ማዕቀፍ (CFA) በስድስት አገሮች ፈራሚነት መተካታቸውና ሕግ ሆነው መፅደቃቸው ይታወሳል፡፡

ሪፖርተር

በሃገራችን ውስጥ እየተከሰተ ያለው የሰብኣዊ መብት ጥሰት እኛ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን የአለም ህዝብ ትኩረት በመሳብ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን በገሃድ እየታየ ነው:: ይህ የሰብኣዊ መብት ጥሰት የሚፈጸመው ቁልፍ ባለስልጣናት የፖሊስ መኮንኖችን በመጠቀም የህዝብን ሰላም ማደፍረስ እና ሽብር መንዛት የእለት ተግባራቸው አድርገው ተያይዘውታል::

ብልሃት በሌለው መልካም አስተዳደር የፖሊስ ባለስልጣናት የሚፈጽሙት ኢሰብኣዊ ተግባራት የህዝብን የመኖር ሁኔታ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከቶታል::ከጥያቄ ምልክትም አልፎ ከባባድ ወንጀሎች በህዝብ የእለት ተለት ሂደት ውስጥ ራሱን መንግስት ያሰኛው ሕወሓት እየፈጸመ ነው::የኢትዮጵያ ህዝቦች ሃይማኖት እና የፖለቲካ አስተሳሰብ ሳይለያቸው በጋራ የሚያቀርቡትን ጥያቄ
ላይ መልስ መስጠት እየተቻለ በጉልበት እና በማስፈራራት በመግደል እና በማሰር የሚመጣ ለውጥ የለም:; የህዝቦች ትግል በየፈርጁ እየቀጠለ ይሄዳል::ማንኛውም ህዝብ ለለውጥ እስከተነሳ ድረስ የሚሞትለት አላማ እንዳለውም ማሰብ ያስፈልጋል::

ባለስልጣናት ህጋዊ የሆኑ ዜጎች እንዲታሰሩ እንዲገላቱ የሚያደርጉት ከተጠያቂነት አያድናቸውም:; ህገመንግስታዊ መብቶችን በመጣስ ዜጎችን በአገራቸው እና ህጋዊ የሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማዋከብ ስልጣን ላይ ያለው ጁንታ ህግን እንደማያከብር ፍንትው አድርጎ ያሳየበት ህገወጥ ተግባር በተደጋጋሚ እያየን ነው:: ራሳቹህ ያወጣችሁትን ህግ ያላከበራችሁ እኛ እንዴት እናክብርላችሁ?? መጀመሪያ አንድ መንግስት ባለስልጣኖቹ ህግን አክብረው ለህዝቡ አርኣያ መሆን አለባቸው:: እያየን ያለነው ግን ሕግ አውጪው እና አስፈጻሚው አካል ህግን እየጣሰ መሆኑን ነው:: ስለዚህ ብልሃት አልባ ዲሞክራሲ በሞላባቸው እና የሰውን ልጅ መብት ትርጉም በማያቁ ባለስልጣናት ከመመራት ሞትን መርጦ መታገል አማራጭ እየሆነ ያለበት ዘመን ላይ ደርሰናል::

ከማናችንም ኢትዮጵያውያን በፊት ባለስልጣናት ህግ አውጪዎች ህግ አስፈጻሚዎች እና የጸጥታ ሃይሎች ለህግ ተገዢ ይሁኑልን::ለእኛም አርኣያ ይሁኑ::በጉልበት እና በሃይል በብልሃት አልባ ዲሞክራሲ ሽብር እየነዙ ሃገር አይመራም!!!ምንሊክ ሳልሳዊ

በወያኔ ዘርኝነት፤ ጎጠኝነትና ወደር የለሽ ጭቆና ከሁለት አስርተ አመታት በላይ ጀርባዉ የጎበጠዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ባለፉት ሁለት ወራት ዉስጥ በሁለት እጅግ አስቀያሚና ዘግናኝ በሆኑ የታሪክ ምዕራፎች ዉስጥ አልፏል። ለወትሮዉ በወርሃ ህዳርና ታህሳስ፤ ህዳር ሚካኤልንና የገና በዐልን እያከበረ አጆቹን ወደ ፈጣሪዉ የሚዘረጋዉ የኢትዮጵያ ህዝብ፤ ዘንድሮ ከእነዚህ ሁለት የቆዩ ባህሎቹና ወጎቹ ፈቀቅ ብሎ በሁለት ክብሩን ባዋረዱና ማንነቱን ጥያቄ ዉስጥ በከተቱ ከስተቶች ልቡ ቆስሎ ከራሱ ጋር ሲነታረክ ሰንብቷል። የፈጠረዉን አምላክ መለምን እንጂ በፈጣሪዉ አማርሮ የማያዉቀዉ የኢትዮጵያ ህዝብ . . . የሚያስብልኝ መንግስት እንደለሌለኝ አዉቃለሁ፤ አምላኬ ግን በፍጹም አይረሳኝም። ምነዉ ቅዱስ ሚካኤል አንተና ሰይፍህ እያላችሁ እንዴት እንዲህ ይደረጋል አንዴ . . . እያለ በምድራዊዉም በሰማያዊዉም መንግስታት ላይ የመረረ ጩኸቱን አሰምቷል።
በህዳር 2006 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ አገራቸዉ ዉስጥ የስራ ዕድል ተነፍገዉ ስራ ፍለጋ ወደ ሳዑዲ የተሰደዱ ወገኖቹ በሳዑዲ ፖሊስና ህዝብ ከፍተኛ በደል ሲፈጸምባቸዉ ተመልክቶ በኃዘንና በቁጭት ልቡ በግኗል። በተለይ ወንዶች ልጆቹ ፈለጊ እንደሌለዉ እንስሳ በየአደባባዩ ሲረገጡና ሲደበደቡ፤ ሴቶች ልጆቹ ደግሞ በየማጀቱ ሲደፈሩ ተመልክቶ ለህዝብና ለአገር ለሚያስቡ አስተዋይና ጨዋ መሪዎች ባለመታደሉ በባዕድ አገር ዉስጥ በደረሰበት ዉርደትና መከራ በአለም አቀፍ ደረጃ ጩኸቱን አሰምቷል።በዚሁ በ2006 ዓም በታህሳሰ ወር አጋማሽ ላይ ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይ ብርድ ልብስ ተጠቅልሎ የተጣለ የሰዉ ልጅ አጽም ቀርቶ በስመአብ ተብሎ የታረደ በሬ ስጋም ማየት በማይፈልግበት በገና ፆም ወቅት የገዛ ወገኖቹ አጽም በመንገድ ቆፋሪዎች ከመሬት ዉስጥ እየተጎተተ ሲወጣ አይቶ በቆሰለ ልብና በነደደ አንደበት “እባክህ ፈጠሪ ወይ ዉረድ ወይ ፍረድ” እያለ ከወያኔ ጋር ከመኖር የፈጣሪን ፍርዱን አለዚያም ዳግም ምጽአቱን ተመኝቷል።
ባለፉት ሁለት ወራት ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ በሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰዉ ግፍና መከራ ድፍን ህዳርንና ታህሳስን በአለም ዙሪያ በአራቱም ማዕዘን የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንን ያሰባሰበ፤ ያነጋገረ፤ ያበሳጨ፤ ያስቆጨና አንጀት ያሳረረ ጉዳይ ነበር። አዎ የ2006 ህዳርና ታህሳስ አገር ዉስጥም ካገር ዉጭም ለምን መጡ የሚያሰኙ የቀን ጎደሎዎች ነበሩ። የወገኖቹ በባዕድ አገር አላግባብ መታሰር፤መደብደብና መገደል ያበሳጨዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ከዚህ ሀዘኑና ብስጭቱ ሳይላቀቅ ነበር ባለፈዉ ታህሳስ 18ትና 19 ቀን ሌላ አሳዛኝና አስደንጋጭ ዜና የጭንቅና የመከራ ጓዳ የሆነችዉን መዲናችን ከአዲስ አበባን አንደ ሐምሌ ጨለማ የከበባት። ደርግን አሸንፈዉ ስልጣን ሲይዙ ደርግ ገድሎ የቀበረዉን አስከሬን መቃብር እየቆፈሩ ያወጡት የወያኔ መሪዎች እነሱም በተራቸዉ በጅምላ ገድለዉ በብርድ ልብስ እየጠቀለሉ የቀበሯቸዉን ኢትዮጵያዉያን አስከሬን ዬት እንደቀበሩት እንኳን ሰለማያዉቁ እነሱ እራሳቸዉ እየቆፈሩ አዉጥተዉ ወንድሞቹና እህቶቹ እንደወጡ የቀሩበትን የኢትዮጵያን ህዝብ አንጀት እንደገና አቁስለዋል።
እዚህ ላይ አንድ እጅግ በጣም ሊያሳስበንና ሊያስጨንቀን የሚገባ ነገር ቢኖር ባለፈዉ ሳምንት ከስድት ኪሎ ወደ ፈረንሳይ ለጋሲዮን በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው የጃንሜዳ ጦር ካምፕ አካባቢ በብርድ ልብስ እንደተጠቀለለ የተገኘዉ የ6 ሰዎች አጽም ሊገኝ የቻለዉ ሆን ተብሎ የጅምላ መቃብር ለማግኘት በተደረገ ቁፋሮ ሳይሆን በአጋጣሚ ነዉ። ይህ የሚያሳየን አዲስ አበባን ጨምሮ በብዙ የአገራችን አካባቢዎች ዉስጥ መረጃ የተሰበሰባበቸዉንና የሚጠረጠሩ ቦታዎችን የኢትዮጵያ ህዝብ ከአለም አቀፉ ህብረተሰብ ጋር ተባብሮ እየቆፈረ መፈተሽ ቢጀምር ወያኔ ጭካኔዉን ሊያሳየን ከሞከረዉ ከደርግ ስርዐት ጋር ምንም የማይለያይ ጨካኝና አረመኔ ስርዐት ለመሆኑ ማንም ማስተባበል የማይችለዉ ተጨባጭ ማስረጃ ይገኛል ብለን እናምናለን።
የወያኔ ዘረኞች አዲስ አበባን በተቆጣጠሩ ማግስት ስራችን ብለዉ የጀመሩት ደርግ የሰለበዉን የኢትዮጵያን ህዝብ ሞራል ማደስ ወይም በሶሻሊዝም ስም የደቀቀዉን የአገራችንን ኤኮኖሚ መገንባት አልነበረም። የደርግ ሰርዐት አንደ ገለባ ሲበተን አብሮት የተበተነዉ የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያሰራዊትም ቢሆን እንደጠላት የሚመለከቱት ኃይል ስለነበር ይህ ለእናት አገሩ ዳር ድንበር መከበር ደሙን ያፈሰሰ ሰራዊት የሚበላና የሚቀመስ አጥቶ ወደ መንገድ ላይ ለማኝነት ሲቀየር ሌላ ቢቀር ጡረታዉን እንኳን ለማስከበር ያደረጉለት ምንም ነገር አልነበረም። ወያኔዎች ስልጣን እንደጨበጡ የደረጉት አቢይ ነገር ቢኖር ከክፍለ ሀገር ክፍለ ሀገረ እየዞሩ ደርግ በቀይ ሽብርና በሌላም ሌላ ግዜ ገድሎ የቀበራቸዉን ሰዎች መቃብር እየቆፈሩ አጽም መሰብሰብ ነበር። በወቅቱ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በተከታታይ እንደተመለከትነዉ የወያኔ ጉድጓድ ቆፋሪዎች የሰነበተ መቃብር እየከፈቱና አጽም እየሰበሰቡ ደርግ ምን አይነት ጨካኝ ነብሰ ገዳይ እንደሆነ ለአመታት የምናዉቀዉን እዉነት እንደገና እንድናዉቀዉ አድርገዉናል። በዚህ ከአንድ አመት ከመንፈቅ በላይ በዘለቀዉ የወያኔ መቃብር ቁፋሮ ወያኔ የቀድሞዉን ንጉስ የቀዳማዊ ኃ/ስላሤን ጨምሮ የብዙ ሰዎችን የመቃብር ቦታ እየቆፈረ እሱ ለፖለቲካ ፍጆታዉ የሚፈልጋቸዉንና በተለይ ደግሞ የኔ ናቸዉ የሚላቸዉን ሰዎች አጽም እየለቀመ አንደገና በክብር እንዲቀበሩ ሲያደርግ ሌሎቹን የደርግ ሰለባዎች ደግሞ ምሶ ያወጣዉን አፈር አንደገና መልሶባቸዋል። እንደዚህ አይነት ጉድ የተመለከትነዉ ከሃያ ሁለት አመታት በፊት ወያኔ ኢትየጵያን ሲቆጣጠር ነበር።
ባለፈዉ ሳምንት አዲስ አበባ ዉስጥ መንገድ የሚሰሩ ሰዎች ለራሳቸዉ ጉዳይ መሬት ሲቆፍሩ ከተጠቀለሉበት የደብረ ብርሀን ብርድ ልብስ ዉስጥ እየዘለሉ ወጥተዉ “የፍትህ ያለህ” እያሉ ሲጮኹ የሰማናቸዉ አጽሞች ወያኔ በእኔ ዘመነ መንግስት ሰዉ በሰዉነቱ ይከበራል እንጂ እየተጎተተ አየገደልም ብሎ ከማለ በኋላ በራሱ በወያኔ በግፍ እየተጎተቱ ተገድለዉ የተጣሉ ዜጎች አጽም ነዉ። ይህንን በታሪካችን ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ጉድ በስፍራዉ ተገኝተዉ የተመለከቱ የአይን ምስክሮች እንደተናገሩት ቦታዉ ዘመናዊ የመቆፈሪያ ማሽኖች በመቆፈር ላይ እያለ በመጀመሪያ አራት አስከሬኖች በብርድልብስ እንደተጠቀለሉ ተንከባለዉ ወደላይ ሲወጡ የታዩ ሲሆን፤ በሁኔታዉ የተደናገጡት ቆፋሪዎች ስራቸዉን አቋርጠዉ ወደ ቤታቸዉ ከሄዱ በኋላ በነጋታው ረፋዱ ላይ በሌላ አቅጣጫ ሌላ ቁፋሮ ሲያደርጉ አሁንም እንደገና በተመሳሳይ ሁኔታ በብርድ ልብስ የተጠቀለሉ ስድስት አስከሬኖች አግኝተዋል።
አንድ አስከሬኖቹ በተገኙበት አካባቢ በብዛት ተገኝቶ ሁኔታዉን ይመለከት የነበረዉን ህዝብ ለማባረር ወታደሮቹን አስከትሎ የመጣ ከፍተኛ ወታደራዊ የጦር መኮንን “ይህ ግቢ ሶስት ስርዓቶችን ያገለገለ በመሆኑ የማናቸው እንደሆነ ለማወቅ አይቻልም፤ ሆኖም ሰዎች በመሆናቸው ክቡር ናቸውና አፈር አልብሷቸው” በማለት የዘረኞቹን የወያኔ መሪዎች አይን ያወጣ ወንጀል ለመደበቅ ሲሞክር ተደምጧል። ሆኖም ሁኔታዉን በቅርብ ሆኖ የተከታተለዉም ሆነ በርቀት ሆኖ በምስል የተመለከተ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ወንጀሉ የሌሎቹ መንግስታት ሳይሆን የወያኔ መሆኑን ለመገንዘብ ግዜ አልወሰደበትም። አስከሬኖቹ በጅምላ የተጠቀለሉበት የደብረ ብርሀን ብርድ ልብስም ቢሆን እንኳን መሬት ዉስጥ ተቀብሮ ምስጥ፤ እርጥበትና ዘመን ተፈራርቀዉበት፤ አልጋ ላይ ህያዉ ሰዉ ለብሶትም ቢሆን ሃያ አመት ቀርቶ አምስት አመትም የሚቆየዉ የዛሬዎቹ የወያኔ መሪዎች ለብሰዉት አንደመጡት ቁምጣ በመርፌ ከተጠቋቆመ ብቻ ነዉ። ባለፈዉ ሳምንት አርብና ቅዳሜ አስር አስከሬኖችን እንዳቀፈ ከመሬት ዉስጥ ሲወጣ ያየነነዉ ብርድል ልብስ የሚያሳየን ነገር ቢኖር ወያኔ በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ ኢትዮጵያዉያንን በሚስጢር እየገደለ እንደ ቆሻሻ ዕቃ ዬትም ቦታ መጣሉን እንዳማያቆም ነዉ።
የአገራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ለሀይማኖት የሚሰጠዉ ቦታ እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ። በእስልምናዉ፤ በክርስትናዉም ሆነ በአይሁድ ሀይማኖቶች አስተምህሮ በሀይማኖት ዉስጥ ሁለቱ ዋና ዋና አካሎች እግዚአብሄርና ሰዉ ናቸዉ፤ ይህ የሚያሳየን ሰዉ ክቡር ፍጡር መሆኑን ነዉ። ወደዚህ አለም ሲመጣም ሆነ ይህችን አለም ሲለይ በከብር መጥቶ በክብር የሚሸኝ የሰዉ ልጅ ብቻ ነዉ። የኢትዮጵያ ክርስትና እምነት መሰረት ከሆነችዉ ከትግራይ ክልል የመጡት የዛሬዎቹ የኢትዮጵያ መሪዎች ግን ክርስትናዉን ብቻ ሳይሆን የራሳቸዉንም ሰዉ መሆን የረሱ ይመስላል። ሰዉን የመሰለ ክቡር ፍጡር በጅምላ ተገድሎ፤ በጅምላ ከተቀበረበት ቦታ በኮንስትራክሺን ሠራተኞች ከመሬት ዉስጥ እየተጎተተ መዉጣቱን የሰሙ የወያኔ መሪዎች ጉዳዩን አስመልክቶ አንድም ትንፍሽ ያሉት ቃል የለም። እነሱ ብቻ ሳይሆኑ በእነሱ ቁጥጥር ስር ያሉት የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥንም እነማን እንደሆኑ፤ መቼ እንደሞቱና ማን እንደገደላቸዉ የማይታወቅ ሰዎች አስከሬን በብርድልብስ ተጠቅልሎ ሲገኝ ያንን ለስድብና ህዝብን ለመኮነን ቀኑን ሙሉ የሚከፍቱትን አፋቹዉን መክፈት አልፈለጉም። የሚገርመዉ እንደ አለባሌ ነገር ከተጣሉበት ቦታ ተጎትተዉ የወጡት አስከሬኖች ሁኔታና የተጠቀለሉበት ብርድልብስ ሙሉ በሙሉ ወንጀሉን ወያኔ ላይ ስለሚያመለክት ነዉ እንጂ የእነሱ እጅ የሌለበት ወንጀል ቢሆን ኖሮ የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሳምንት ሙሉ ሌላ ዜና አይሰማም ነበር።
አገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ አገሮች የሚኖረዉ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ባለፈዉ ሳምንት እንደ ዋዛ ከመሬት ዉስጥ እየተጎተቱ የወጡ ወገኖቹን አስከሬን ጉዳይ በቀላሉ መመልከት የለበትም። ወያኔ ስልጣን እጁ ከገባ ጀምሮ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያንን እያፈነ በየማጎሪያ ቤቱ አጉሯቸዋል። ከሰሞኑ ጃንሜዳ አካባቢ ያየነዉ ዘግናኝ ክስተት ስለእነዚህ ወያኔ በየድብቅ አስር ቤቶች አስሮ አድራሻቸዉ ስለጠፋ ዜጎቻችን ብዙ የሚለዉ ነገር ያለ ይመስለናል። እኛ ነን አድራሻቸዉ የጠፋ ሰዎች እያልን የምንጨነቀዉ እንጂ እነዚህ ወያኔ አስሯቸዉ አድራሻቸዉ የጠፋ ሰዎች ዬት እንዳሉ ጃንሜዳ አፉን ከፍቶ ነግሮናል። አዲስ አበባና በየከተማዉ የሚኖረዉ ህዝብ ስለወያኔ የጅምላ ግድያ የሚያዉቀዉ ብዙ ሚስጢር ይኖራል፤ በጅምላ ተገድለዉ በጅምላ የሚቀበሩ ሰዎችንም ጉዳይ በተመለከተ ማንም ሰዉ ሳያየዉና ሳያዉቀዉ የሚፈጸም ነገር አይመስለንምና ከአሁን በኋላ ጥረታቻን ሁሉ የወያኔ የጅምላ ግድያዎች በብሄራዊና በአለም አቀፍ አካላት እንዲመረመሩና ወንጀለኞቹ ለፍርድ እንዲቀርቡ ማድረግ መሆን አለበት። በዚህ ጉዳይ ላይ መረጃ ያላቸዉ ዜጎች መረጃዎቻቸዉን ማሰባሰብ፤ማደራጀትና ለሚመለከተቸዉ አካላት መስጠት ይኖርባቸዋል። ዬት እንደደረሱ ሳናዉቅ ባለፈዉ ሳምንት ሳይተሳብ በደብረህርሃን ብርድ ልብስ እንደተጠቀለሉ ከመሬት ዉስጥ የወጡ ዜጎቻችን ፍትህ ሳያገኙ ማንም ኢትዮጵያዊ እንቅልፍ ሊወስደዉ አይገባም።

ካለመታደል ሀገራችን ዛሬም ሰላም ፍትህና ዲሞክራሲ የሰፈነባት በልማትና በእድገት ጎዳና የምትራመድ ሀገር አልሆነችም። ለዚህም በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩም እንደ ዓቢይ ምክንያት ተደርጎ የሚቀርበው የህዝብን ይሁንታን ያገኘ፡ ህዝብን በእኩልነት የሚዳኝ፡ ህዝባዊና ዲሞክራሲያዊ የሆነ መንግሥት አለመመስረቱ፡ አገርና ህዝብ የሚተዳደሩበት ዲሞክራሲያዊ ህገ መንግሥት አለመኖሩ ነው።

እስከዛሬ በተጨባጭ እንደታየው በ ኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ የተፈራረቁበት ገዥዎቹ በየበኩላቸው አንዱ ከሌላው የሚለዩባቸው ባህርያት ቢኖራቸውም ሁሉንም ግን አንድ የሚያስመስሏቸው ባህርያትም አሏቸው። እነሱም ሁሉም በኃይል ሥልጣን መያዛቸው፡ አምባገነንነታቸው፡ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ ማራመዳቸው፡ በህዝብ መካከል የጋራ መተማመንና ከበሬታን ለመፍጠር፡ ሁሉም ዘላቂ ሰላምና መረጋጋትን በሀገሪቱ ለማስፈን አለመቻላቸው ደግሞ ዛሬ ለሁሉም በግልጥ እየታየ ያለ ነው። በዚህም የተነሳ በሀገራችን ለብሔራዊ ክብርና ነፃነት፡ ለዲሞክራሲ፡ ለማህበራዊ ፍትህ፡ ለሰላምና ለእኩልነት የሚታገሉ ኃይሎች የሰላማዊ ለውጥ በሮች ስለተዘጉባቸው የአ መፅን ጎዳና እንዲከተሉ የሚጋብዝ በር ተቀዶ ይገኛል።

በሌላ በኩል ደግሞ በሀገሪቱ ውስጥ የፖለቲካ መረጋጋት ንእዲፈጠር፡ ሕዝቡም አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ አግኝቶ ያለስጋት ለመኖር እንዲችል፡ የዳኝነት ተቋሞች ነፃ ሆነው የሚሠሩበት፡ የህግ የበላይነት የተረጋገጠበት ሁኔታ እንዲፈጠርና፡ ህዝቡም በህግና ሥርዓት መኖር ላይ እምነት እንዲያድርበት ለማድረግ እንዲቻል፡ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት የሚታገሉ ኢትዮጵያዊ ተቃዋሚ ኃይሎች በተናጠልም ሆነ በኅብረት በርካታ ጥረቶች ተደርገዋል። ሆኖም እስከዛሬ የተደረጉት ጥረቶችን ሁሉ በማምከን ወያኔ የሰላምና የእርቅ መሰናከል ከመሆኑም ባሻገር በንፁሃን ዜጎች ደም ሰላምን አጠልሽቶታል። ወያኔ ስለ ሰላምና እርቅ ሊሰማም ሊነጋገርም እማይችልበት የደም ስካር ላይ ደርሷል።

ብአዴን ቢመጣ ኦህዴድ ቢመጣ ደህዴን ቢመጣ የሚለወጥ ነገር አይኖርም። ጠንከር ያለ ለለውጥ የተዘጋጀ – አስከ ሞት የቆረጠ -ጠቅላይ ሚኒስተር ስልጣን አገኘ ማለት የህወሃት የበላይነት እና ፈላጭ ቆራጭነት ፍላጎት ፈተና ይገጥመዋል ማለት ስለሆነ! ህወህት የበላይነቱን ለማሰጠበቅ የፈጠራቸው የመንግስት ስልጣን አደረጃጀት አና ተቋማት ዛሬም በሙሉ ሃይላቸው አሉ። የህወሃት ፈላጭ ቆራጭነት ሳይዳከም ለውጥ አይመጣም። የህወሃት ፈላጭ ቆራጭነት መሰረቱ ደሞ ከምንም በላይ ወታደራዊ ሃይሉ ላይ የተመሰረተ አንደሆነ የአደባባይ ሚስጥር ነው። በደህነንት ቢሮ ያሉትን የህወሃት አመራሮች ከታች ያሉት ማዳክም የሚችሉበትን አጋጣሚ አና ሁኔታ ተጠቅመው አስካላዳከሙት ደረስ የህወሃት የስልጣን የበላይነት ትርጉም ባለው ሁኔታ እክል ሊገጥመው አይችልም።

ሌላ ሌላውን ትተን መሰረታዊ የሆነ ህገ-መንግስታዊ ማሻሻያ ያስፈልጋል፣ የፍትህ ስርዕቱ የፍትህ ስርእት መመስልም መሆንም አለበት፣ የነጻው ፕሬስና ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ህዳሴ አንመራለን አየተባለ በመካከለኛው ዘመን አና ከዛ በፊት ከነበረው አንደነበረው በሰይፍ አና በሰደፍ መያዝ የለበትም። አነኚህ ወሳኝ ርምጃዎች በአዝጋሚ ለውጥ ይመጣሉ ብየ አላስብም። የአዝጋሚ ለውጥ ዲስኩር (ፍላጎት ካለ ፍላጎትም) ጭራሽ ወደማይቀልበስ የባርነት ዓለም አና ዘመን የመውሰጃ ከፓለቲካ ዘዴ ሊሆን ይችላል። ጋዜጠኞችና የተቃዋሚ ፓለቲካ መሪዎች ዘብጥያ ሲጣሉ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን የፈጠሩትን ዓይነት ጫና መፍጠር ስላልተቻለ አንኳን መሰረታዊ የፕሬስ ነጻነት አና በነጻነት ያለገደብ የመደራጀት መብት የሚከበርበት ፍንጭ ሊገኝ ቀርቶ የታሰሩትን ጋዜጠኞች አና የፓለቲካ መሪዎች ማስፈታት አንኳን አልተቻለም። ጭራሽ መብታቸው ተረግጦ ያላግባብ አስር ቤት የተጣሉ ኢትዮጵያውያን ዛሬ ድረስ “አሸባሪ” አየተባሉ አየተፌዘባቸው ነው ያለው። አቶ ኃይለማርያምም ፌዙን በጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ አያስተጋቡት ነው።

ከበቀለበት የተጋጋበት አንዲሉ የ”በሳሉ መሪ ራዕይ” ዜማ ከህወሃት አባላት በእህት ድርጂቶች የፓለቲካ አላዋቂዎች አና መሪዎች ይበልጥ ተዜመ! በአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝም ተሰማ። ችግሩ የለውጥ ጥያቄ ማድበስበሻ ሆኖ ለረዢም ጊዜ ሊቆይ አይችልም። በውሽት ላይ የተመሰረተ ፐሮፓጋንዳ ስር ሊይዝ አይችልም።አንዴት ይሄን ማየት አቃታቸው?!የሕዝባችን መከራና ሰቆቃ እየከፋ ሄደ። የተጨቆነዉ ሕዝብ ተነሳስቶ ለመብቱ ሲታገል ጨቋኝ መንግሥታት ለዉጥ እንዲያደርጉ ይገደዳሉ፤ ካለዚያ በተባበረዉ የሕዝብ ኃይል ተንኮታኩተዉ ይወድቃሉ። የታገለዉ ለዉጥ ያመጣል፤ ያልታገለዉ ቁጭ ብሎ በባርነት ሲገዛ ይኖራል፤ ቁጭም ባለበት ይሞታል ማለት ነው። የለዉጥ ባለቤት ሁሌ ሕዝብ መሆን አለበት። ህዝቡ ትግሉን በሚገባ እንዲያቀናጅ የትግል መሪ ይፈልጋል።

ስለዚህ የተቃዋሚ የፖሊቲካ መሪዎች ታላቅ ኃላፊነት ይጠበቅባቸዋል። ያገራችንን ጭብጥ ሁኔታ ስንመረምር ግን በሁለቱም በኩል ታላላቅና ተደጋጋሚ ድክመቶች ታይተዋል። አምባገነን መንግሥታት ለዘለዓለም ካልገዛን ሲሉ የተቃዋሚ ድርጅቶች ኅብረታቸዉን ማጠናከር ስላልቻሉ የጨቋኝ መንግሥታትን ዘመናት ሲያራዝሙ ቆይተዋል።ወያኔ/ኢሕአደግ ለዘለዓለም ሊገዛ አይችልም፤ ለሁሉም ጊዜ አለዉና።ትግሉ ይበልጥ መፋፋም፡ ይበልጥ መጨስ፡ መጋጋም፡ መንደድ ይጠበቅበታል። ትግሉን ለማፈንና አቅጣጫውን ለማሳት የወያኔ መንጋ እየተሯሯጠ ነው። በውጭ ያለውንም የሕዝብና የድርጅቶችን ተቃውሞ ቢቻለው ለማዳፈን፡ ካልሆነለት ደግሞ ለማዳከም፡ በአሁኑ ወቅት የወያኔ ከፋፋይ ቡድን በየቦታው በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ እያየን ነው። ይህ ቡድንም፡ ምሁር ነን፡ አስታራቂ ነን፡ ሽማግሌ ነን ወይም ታጋይ ነን በሚሉ መሰሪዎችም እየተደገፈ ነው።

የሕዝብ ክንድ ይላላ፡ ይደክም ዘንድ፡ በከፋፋይ ሴራ የተሰማሩትን ነቅቶ መጠበቅ፡ ትግሉን መከላከል ብቻ ሳይሆን ወያኔ ለባሾችን፡ ሰላዮችን ሳንፈራ እየመነጠርን ማጋለጥ ይኖርብናል። ዘረኛው ቡድንና ጭፍሮቹ የሕዝቡን ትግል ለመከፋፈል ከመቼውም ጊዜ በበለጠ እየጣሩ ናቸውና። ሕዝብ አንድነቱን ጠብቆ፡ የወያኔን ቡድን ለአንዴም ለሁሌም ለማስወገድ አስፈላጊውን መስዋእ ትነት እየከፈለ ባለበት ወቅት የፖለቲካ ድርጅቶችን እገዛና አመራር ይጠይቃል። የሕዝብ አሸናፊነት አጠራጣሪ ባይሆንም፡ አሸናፊ ለመሆን ግን መታገል መቅደም እንዳለበት ምን ጊዜም መረሳት የለበትም። ለዚህ መሠረቱ ግን ከራስ ጋር እየታረቁ፡ ከወገን ጋር እየተስማሙ በጋራ ዓላማና ብሔራዊ እጅንዳ ዙሪያ ተሰባስቦ በጋራ መታገል ብቻ ነው።

በዓለም ታላቅ ዝና ያተረፉት የግ/ቀ/ኃ/ሥና በአፍሪቃ አህጉር መሬትን ያንቀጠቀጠዉ የደርግ መንግሥት ቀናቸዉ ሲደርስ እንዴት እንደመነመኑና እንደከሰሙ መዘርዘር አይኖርብኝም፤ በታሪክ ፊት ተቀምጧልና። በሩቁም በእነ አሜሪካ ለረዥም ዓመታት ሲረዱና ሲደገፉ በነበሩት በእነ ሞቡቱ፤ የሻህ ንጉሥ፤ ሆስኒ ሙባረክ፤ ወዘተ ላይ በመጨረሻ የደረሰዉን ዉርደት መገንዘብ ያስፈልጋል። ተቃዋሚ የፖሊቲካ ድርጅቶች ነን የሚሉትና በተግባር ግን የጭቆናን ዘመን የሚያራዝሙ በሙሉ ካለፉት ስህተቶች ገና ሊማሩ አልቻሉም፤ ・ድር ቢያብር እንበሳ ያስር・ የተባለዉን ቅዱስ አሳብ ደጋግመዉ መናቃቸዉ ያስተዛዝባል። ቁርጥ ያለ አቋም ያስፈልጋል፤ ከዛፍ ዛፍ መዝለል ዬትም አያደርስም። ለጊዜያዊ ጥቅማ ጥቅሞች በርካሽ መገዛትና አገርን መሸጥ በሰማይም በምድርም ያስጠይቃል። ቀኑ ሲደርስ ራቆታችንን ወደምድር እነደመጣን ሁሉ ራቆታችንን ወደዚያዉ እነደምንመለስ አንርሳ!!!

ነገርግን በህብረት ለሀገር ታሪክ ሰርቶ ማለፍ ዘላለማዊ የትዉልድና የሀገር ክብር ነዉ!!!

ከጎልጉል የተወሰደ

ኢትዮጵያዊነት የሚለው ቃል እኮ የኢያንዳንዳችን መከበሪያ እና መኩሪያ እንጂ ማፈሪያ አይደለም::ለአመታት ታገልን የሚሉ ከወያኔ ጎን እየፈሉም ያሉ እና የከሰሙ የብሄር ድርጅቶች በታገሉባቸው አመታቶች ከወሬ ውጭ ለሃገሪቱም ይሁን ለሚጠሩት ብሄር ምንም የፈየዱት ነገር የለም:: ያመጡትም ነጻነት የለም ይብሱኑ እርስ በእርስ ከማጨፋጨፍ ውጪ እና ህዝብን ለእልቂት ከመዳረክ ውጪ ምንም ያመጡት ውጤት የለም:: በብሄር ስም መታገል እና ዘረኝነት ማራመድ ለብሄራዊ ጭቆና በር መክፈት ነው :: ገዢው ፓርቲን ሕወሓትን እንኳን ብትመለከቱት ለትግራይ ህዝብ የፈጠረው አዲስ ነገር የለም:: የትግራይ ህዝብ በዘመናዊ ጭቆና ፍዳውን እያየ ነው::

እኛ በጋራ እስካልታገልን ድረስ ለውጥ አይመጣም:: ከሃገር ሲወጡ የወያኔን ጽዋ ጠጥተው እዚህ ከመጡ በኋላ የሚከረበቱ አስመሳይ ተለጣፊ ፖለቲከኞችን ማስወገድ ግዴታችን ነው:: ኢትዮጵያዊነት የሚለው ቃል እኮ የኢያንዳንዳችን መከበሪያ እና መኩሪያ እንጂ ማፈሪያ አይደለም:: ከሌላው አለም የምንወስደው ትምህርት ምንድን ነው??ሌላው ዜጋ ሃገሩን እና ሌላውን ወገኑን እንዴት ነው የሚወደው?? የዘር እና የቀለም ልዩነት እየተወገደ በሚሄድበት በዚህ በሰለጠነው አለም ላይ ትላንትን እያሰብን የምንኖር ሰዎች ግንዛቤያችንን ማስፋት ይጠበቅብናል::

ኢትዮጵያ ምን አደረገችልኝ የሚል አነጋገር የሚናገሩ ጠባብ ብሄርተኞች አላማቸው የት ላይ እንደሚያርፍ ራሳቸው አያውቁትም::ኢትዮጵያ እኮ አንዲት ግኡዝ አካል ነች :: ተንቀሳቅሳ ላንተ ላንቺ እና ለእናንተ የምትፈይደው ነገር የለም ምድሯን እየረገጥን እየተማርን እየኖርን ያለነው እኛ ነን ::የእኛ ስራ ደሞ አገርን ከክፉ ገዢዎች አድነን ራሳችንን ነጻ በማውጣት የወገንን እምባ ማበስ እንጂ በወገን እንባ እና ደም መነገድ አላስፈላጊ ኪሳራ ያስከትልብናል ለኢትዮጵያ ምን ሰራሁላት ለወገኔ ምን አደረኩለት ብለህ ጠይቅ እንጂ እንደ ከብት አታጓራ:: በህዝብ ጥያቄ ስም ተደብቆ ጠባብነትን ማራመድ ክሽፈትን ያመጣል እና እንጠንቀቅ:: በየትኛውም አገር ያለን ኢትዮጵያውያን በጡት ነካሾች የታሰበውን ጸረ ኢትዮጵያ ዘመቻ ልንቃወም ይገባል::ምንሊክ ሳልሳዊ

አምስተኛው ዙር አገር አቀፍ ‹‹ምርጫ›› እንደወትሮው ሁሉ በቀጣዩ ዓመት ሊደረግ በዕቅድ ተይዟል፤ ወሬውም ከወዲሁ ለፖለቲካ ፍጆታነት እየዋለ ነው፤ ኢህአዴግም በበኩሉ ‹አውራ ፓርቲ›ነቱን ከቀደመው በበለጠ አጠናክሮ የሚቀጥልበትን ሴራ ፈትሎ በመግመድ ውሎ ማደሩን ገና በማለዳ እያቀላጠፈው መሆኑን እየታዘብን ነው፡፡ አቶ መለስ ዜናዊ (ከልቡ ባይሆንም) በ1996 ዓ.ም ወርሃ ሐምሌ ላይ በተደረገ የግንባሩ ጉባኤ ‹‹የሚቀጥለው ምርጫ እንከን-አልባ ይሆናል›› ሲል ‹ቃል› ገብቶ የነበር ቢሆንም፣ ከስድስት ዓመት በኋላ በተካሄደው አራተኛው ዙር ‹‹ምርጫ›› በግላጭ ‹እንከን-አልባ ድል› በሚል ሲቀይረው ቅንጣት ታህል ሀፍረት

አልተሰማውም ነበር፡፡ ግና! ‹አንድ ለእናቱ› እንዲል አቤ ጎበኛ፣ የተቃውሞውን ስብስብ የምትወክል አንዲት ወንበር ሾልካ ወደ ምክር ቤቱ በመግባቷ፣ ፓርቲው ዛሬም ድረስ እንደ እግር እሳት እያንገበገበችው መሆኑን በተለያየ መንገድ እያሳየን ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ኢህአዴግ ከዚህ ትምህርት በመውሰድ በሚቀጥለው ዓመት በሚደረግው ‹‹ምርጫ›› እንዲህ አይነት ‹እንዝህላልነትን› ለማረም በከፍተኛ ዝግጅት መጠመዱን የሚጠቁሙ መረጃዎች እያፈተለኩ ነው፡፡ መቼም የጉዳዩ እውነትነት ከተረጋገጠ፣ ምናልባትም በ2012 ዓ.ም ልክ እንደ ኤርትራ ወይም እንደ ቻይና ‹ልማታዊ መንግስት እንጂ ምርጫ የሚባል ነገር አያስፈልግም! የምርጫ ፖለቲካ የኒዎ-ሊበራሊስቶች አጀንዳ ነውና!!› ከማለት የሚመለስ አይመስለኝም፡፡ ማን ያውቃል? …እንዲህ እንደዛሬው የሶስት ሺ ዓመት ታሪክ ያላትን እና የዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ አገርን ፍርሃት በመንዛት አሸንፎ ከቆየ የምናየው ይሆናል፡፡

ከዚህ ባለፈ ቀጣዩን ‹‹ምርጫ›› በፍፁማዊ ጠቅላይነት ለመጨረስ እያደረገ ያለው መሰናዶ በሶስት የተከፈለ ነው፤ የመጀመሪያው ለመላው የድርጅቱ አባላት (የመንግስታዊ ተቋማት ኃላፊዎችን ጨምሮ) የተዘጋጀው ፓኬጅ ነው (ሰሞኑን በተለያዩ ከተሞች ስለ ‹አውራ ፓርቲ› አስፈላጊነት እና የ‹ልማታዊ መንግስት›ን ጠቀሜታ በተመለከተ እየተሰጠ ያለው ሥልጠናም የዚሁ አካል እንደሆነ ሰምቻለሁ)፤ ሁለተኛው መራጩ ሕዝብ ላይ በተናጥል አተኩሮ ለመተግበር እየተሞከረ ካለው ቀመር ጋር የሚያያዝ ሲሆን፤ ይህም እንደ ቀድሞው ሁሉ ለአቅመ-ምርጫ የደረሰውን ህዝብ በኮንዶሚንየም፣ በመልካም አስተዳደር እና በማይጨበጡ የተስፋ ፕሮፓጋንዳዎች ማማለልን የሚያካትት ነው፤ የመጨረሻው ደግሞ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና የግሉ የህትመት ሚዲያ ላይ ያነጣጥራል፤ በዚህ ፅሁፍም አጀንዳ የምናደርገው አገዛዙ በዚህኛው ግንባር ከሚያስወነጭፋቸው የ‹ጦር መሳሪያዎች› በዋነኛነት በዘጋቢ ወይም በዶክመንተሪ መልክ የሚያዘጋጃቸው ፊልሞችን የተመለከተ ነው፡፡

ስውሩ አጀንዳ…
በርግጥ ይህ አይነቱ አሰራር ዛሬ የተጀመረ አይደለም፤ ባለፉት ሃያ ዓመታት በሙሉ ሲተገበር የነበረ ነው፡፡ በተለይ ሕዝባዊ ተቃውሞን

የመሰለ ለሥልጣን የሚያሰጋ ድንገቴ አጋጣሚ ሲከሰት የሚመረቱት ፊልሞች ቁጥርም እንዲሁ ይጨምራል፤ እንደ ምሳሌም የ1993ቱን የህወሓት ክፍፍልን ተከትሎ በየአካባቢው የሕዝብ ማጉረምረም በበረታበት ወቅት፣ የሰሜን አፍሪካ አብዮት በጋመበት ማግስት እና የእስልምና እምነት ተከታዮች ሕገ-መንግስታዊው የኃይማኖት ነፃነት እንዲከበርላቸው በአደባባይ በጠየቁባቸው ጊዜያት በ‹‹ዘጋቢ ትዕይንት›› ስም የተሰራጩትን ብቻ መመልከቱ በቂ ነው ብዬ አስባለሁ (በነገራችን ላይ እንዲህ አይነት ጭብጥ ያላቸው ፊልሞች ደራሲያን፣ የስርዓቱ ዋነኞች ‹ኤጲስ-ቆጶሳት› እንጂ ተቋሙ የሰበሰባቸው ብላቴና ልማታውያን ጋዜጠኞች አይደሉም)

ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የመረጃ ምንጮቼ እንዳረጋገጥኩት ‹ዶክመንተሪ ፊልሞች› የሚዘጋጁት በሁለት መንገድ ነው፤ የመጀመሪያው በኢቲቪ ባልደረቦች ሃሳብ አመንጪነት በፕሮፓጋንዳ ላይ የሚያተኩር ሲሆን፣ በሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ይሁንታን ሲያገኝ እንዲተላለፍ የሚደረግ ነው፡፡ ሌላኛው ደግሞ፣ በጉምቱ የፓርቲው መሪዎች የጭብጥ አሰናጅነት ሙሉ ድራማው አልቆለት በቀጥታ አየር ላይ እንዲውል ወደ ጣቢያው የሚላከው ነው፡፡ በዚህ ዘውግ የሚመደቡት አብዛኛዎቹ ፊልሞች ተቃዋሚ ፓርቲዎችን፣ በግል ሚዲያ ላይ የተሰማሩ ጋዜጠኞችን፣ የኃይማኖት መሪዎችን እና ዓለም-አቀፍ ተቋማትን በመወንጀልና በመዝለፍ ላይ የሚያውጠነጥኑ ናቸው (የቅርቦቹን እንኳ ለማስታውስ ያህል ብንጠቅሳቸው ይህንኑ ያስረግጣሉ፡- ‹አዲስ አበባን እንደ ባግዳድ›፣ ‹አኬልዳማ›፣ ‹ጀሀዳዊ ሀረካት›፣ ‹ሽብርተኝነት በኢትዮጵያ› እና የመሳሰሉት)

በጥቅሉ እስከ 2004 ዓ.ም መገባደጃ ድረስ የእነዚህ ፊልሞች ደራሲ አቶ መለስ ዜናዊ የነበረ ሲሆን፤ ከእርሱ ህልፈት በኋላ የኮሚኒኬሽን መ/ቤት (ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የጠቅላይ ሚንስትሩ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር አማካሪዎች) በደህንነት እና ፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል ስም

እንደሚያዘጋጁት ውስጥ-አወቅ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ኢቲቪ በእንዲህ አይነት ጭብጥ ዙሪያ በሚያውጠነጥኑ ፊልሞች ላይ ምንም አይነት ተሳትፎ አያደርግም፤ ሳይቀንስና ሳይጨምር ለሕዝብ ማስተላለፍ አማራጭ ያልተተወለት ብቸኛ ግዴታው ነው፤ የህወሓቱ ሰው ገራገሩ የተቋሙ ስራ አስኪያጅ ዘርዓይ አስግዶምም ቢሆን ይህ ኃላፊነት ሲሰጠው ትጉህ አገልጋይነቱ ለማን እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቀዋልና፣

በፍፁም ፈቃደኝነት ሥራውን ከማሳለጥ በቀር የሚቃወምበት ወይም የኤዲቶሪያል ነፃነቴን አላስገፋም ብሎ የሚቀብጥበት አንዳች ምክንያት የለውም፡፡ በግልባጩ ውዳሴ መለስ፣ ስደት፣ የአባይ ቁጭት፣ የኮንዶሚንየም ቤቶችንና መሰል ጉዳዮችን በተመለከተ ደግሞ ሩቅ አላሚዎቹ ‹‹ልማታዊ ጋዜጠኞች››፣ እንቅልፍ አጥተው የሚጨነቁበትና እርስ በእርስ ለመቀዳደም የሚተጉበት አጀንዳ ስለመሆኑ ራሱ በረከት ስምዖንም ገና ድሮ የገባው ይመስለኛል (በነገራችን ላይ በየጊዜው ጥቂት የጣቢያው የተለያዩ ፕሮግራም አዘጋጆች እና የዘጋቢ ፊልም ባለሙያዎች የቻይናን የሚዲያ ተሞክሮ አጥንተው እንዲመጡ እንደሚደረግ ይታወቃል)

ለዚህ ፅሁፍም እንደ ማሳያ የምጠቅሰው፣ ባለፈው ሳምንት ‹‹ሽብርተኝነት በኢትዮጵያ›› በሚል ርዕስ ለተመልካች የቀረበው ዘጋቢ ፊልም፣ ሙሉ በሙሉ በብሔራዊ መረጃ መ/ቤት ስም የተዘጋጀ ሲሆን፣ በንባብ የተሳተፉት ሁለቱ ‹‹ጋዜጠኞች››ም የኢቲቪ መደበኛ

ባልደረቦች እንዳልሆኑ ከምንጮቼ አረጋግጫለሁ፡፡ ምንም እንኳ የፊልሙ ‹ባለቤት› የሆነው የደህንነት ቢሮ በሽብርተኝነት ዙሪያ የሚያውጠነጥን ነው ቢለንም፣ እንዲተላለፍ የተፈለገው ዋነኛ መልዕክት በቀጥታ ከቀጣዩ ምርጫ ጋር የተያየዘ ነው ወደሚል ጠርዝ የሚገፉንን ማሳያዎች መምዘዝ የሚቻል ይመስለኛል፡፡ እንዴት ሆኖ? የሚለውን ጥያቄ በአዲስ ርዕስ ሥር እናፍታታው፡፡

ከፍርሃት ጋር ወደፊት!

በዚህ ፊልም ላይ ዋነኛ አጋፋሪ ሆነው የቀረቡት ሶስት ሰዎች ናቸው፤ የኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስቴር ሚንስትር ዲኤታ ሽመልስ ከማል (ከጥቂት ዓመታት ወዲህ በእንዲህ አይነት ፊልሞች ላይ የመሪ-ተዋናይነትን ገፀ-ባህሪ ወክሎ መጫወቱን እየተካነው እንደሆነ እኔም ራሴ እመሰክርለታለሁ¡)፣ የፌደራሉ ዋና ዓቃቢ-ሕግ ብርሃኑ ወንድማገኝ እና አቶ ዘሪሁን ተሾመ (ይህ ሰው ደግሞ አሉባልታና ጠቀሜታቸው ረብ-የለሽ የሆነ ወሬዎችን በማቅረብ የሚታወቀው የ‹ዛሚ-90.7› ሬዲዮ ባለቤት ሚሚ ስብሃቱ የትዳር አጋር ነው) ከትዕይንቱ መካከል የሚታወሱ ፊቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች ድራማው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ ተሰፍሮ የተሰጣቸውንና በፈጠራ ታሪክ የተሞላውን ‹ስክሪፕት› ቃል-በቃል ሸምድደው መምጣታቸውን በግልፅ በሚያሳይ መልኩ ሲያነበንቡ ላስተዋላቸው ተመልካች ‹‹ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች›› የጣሉባቸውን ግዴታ በቁርጠኝነት ለማስፈፀም ‹ቀራኒዮ› ድረስ የሚጓዙ ሊመስለው ቢችል አይፈረድበትም¡ መቼም አገዛዙ ዓለማዊ ፍላጎታቸውን እስካሟላላቸው ድረስ ሀገር፣ ሕገ-መንግስት፣ ሕሊና… ደንታ ሳይሰጧቸው ሕዝብን በማሸበር የስርዓቱ ዕድሜ ይረዝም ዘንድ ‹ከፍርሃት ጋር ወደፊት!!› ለማለት የማያመነቱ ሰዎችን በዙሪያው የኮለኮለው ለእንዲህ አይነቱ ጊዜ ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ፊልሙ ከቀድሞዎቹ አንፃር እንኳ ሲመዘን የወረደና አሰልቺ ቢሆንም፣ ያን ያህል ከተደሰኮረለት የ‹‹ሽብርተኝነት ጉዳይ›› ባሻገር ሁለት ያደፈጡ ስውር ዓላማዎች ያሉት ይመስለኛልና፣ እነርሱን ነጣጥለን እንመልከት፡፡

የቀደሙ ልምዶችን ተንተርሰን ስናብሰለስለው፣ የዘጋቢ ትዕይንቱ ድብቅ ዓላማ ተደርጎ ሊጠቀስ የሚችለው የመጀመሪያው የቢሆን ሃሳብ፣ ኢህአዴግ ከምርጫው መዳረሻ በፊት በተቃውሞ ፖለቲካው ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ ያሉ የተወሰኑ የአመራር አባላትን እና ጥቂት ጋዜጠኞችን እንደተለመደው ከግንቦት 7 ጋር አቆራኝቶ ለማሰር እየተዘጋጀ ነው የሚል ይሆናል፡፡ በርግጥም ይህንን መከራከሪያ ከመቀበል ሌላ አማራጭ የሚያሳጡ ሁለት ገፊ ምክንያቶች አሉ፤ አንዱ ፓርቲው ቀጣዩን ምርጫ ከትግል ዘመኑ ጀምሮ ይመራው ከነበረው ጉልበታሙ አቶ መለስ ውጪ የሚያደርገው መሆኑ ያሳደረበት ስጋት ወደ ጭፍን አምባገነንት እንዲቀየር ከማስገደድ አልፎ፣ ይህንኑ የሰውየውን ህልፈት ተከትሎ የተከሰተው የኃይል መከፋፈል ያነበረው የመሳሳት ተፅእኖ ይመስለኛል፤ እነዚህ ኩነቶችም ስርዓቱ ህልውናውን ካፀናበት አምባገነናዊ ባህሪው አኳያ ድንገቴ እርምጃ እንዲወስድ መግፋታቸው የሚጠበቅ ነው፡፡

ሁለተኛው ደግሞ ካደረ ተሞክሮው የሚነሳ ነው፤ ይኸውም በ2002ቱ ምርጫ ዋዜማ በተልካሻ ምክንያት የአንድነት ለፍትሕና ዴሞክራሲ ሊቀ-መንበር የነበረችውን ብርቱካን ሚደቅሳን እስር ቤት በመክተት ፓርቲውን እና የተቃውሞ ደጋፊ ኃይሉን እስረኛ በማስፈታት አጀንዳ እንዲጠመድ ያደረገበት ስልት እና ሁነቱ የፈጠረው ማሕበረሰባዊ የፍርሃት ድባብ ያስገኘለት ጠቀሜታን ሊከልሰው መሞከሩ አይቀሬ መሆኑ ነው፡፡ በአናቱም በወቅቱ ከፍተኛ ተነባቢነት የነበራትን የ‹‹አዲስ ነገር›› ጋዜጣ አዘጋጆች ምርጫው አራት ወር ብቻ ሲቀረው በግልፅና ስውር ጫና ጋዜጣውን ዘግተው ከሀገር እንዲሰደዱ ያደረገበት መንገድም የዚሁ አፈና ጉትያ እንደነበረ አለመዘንጋቱ፣ በቅርብ ከሚፈጠሩ ተመሳሳይ ክስተቶች ጋር ለማያያዝ ያስችላል፡፡

ሌላኛው የዘጋቢ ፊልሙ ዓላማ በቀጣዩ ምርጫ ለውጥ ፈላጊውን የህብረተሰብ ክፍል ወደ ተቃውሞ ጎራ ሊያሰባስብና መነቃቃት ሊፈጥር ይችላል የሚል ብርቱ ጥርጣሬ ያሳደረበትን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ጣቢያን በመርገም (በሽመልስ ከማል አነጋገር ‹‹ውጉዝ ከመአርዮስ›› በማለት) የተቀናቃኝ ድምፆች በተከበበላቸው ሞገድ ብቻ እንዲሰሙ ማስገደድ ነው፡፡ ይህ ሁናቴ አገር ውስጥ ያሉ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች እና ጋዜጠኞች ለጣቢያው ቃለ-ምልልስ እንዳይሰጡ በፍርሃት ቆፈን መሸበብንም ያከተተ ነው፡፡ አስደንጋጩ ጉዳይ ደግሞ መከራከሪያ ሆኖ የቀረበው ሕገ-መንግስታዊው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ሳይሆን፣ ለሚዲያ ተቋሙ የብሶት መግለጫዎችን መስጠትም ሆነ ኢ-ፍትሀዊ አሰራርን ማጋለጥ በሽብርተኝነት እንደሚያስከስስ የሚተርክ ‹‹ዶክመንተሪ ፊልም››

መሆኑ ነው፡፡ በርግጥ ለዚህ ማስፈራሪያ እንደ መደገፊያ የተጠቀሙት ፀረ-ሽብር ሕጉ በግብረ-አበርነት ተጠያቂ የሚያደርግበትን የተለጣጭነት ባህሪውን አፅንኦት በመስጠት እንደነበረ ታዝበናል፡፡

በፊልሙ ላይ አቶ ዘሪሁን ምሬት በዋጠው ድምፅ ‹‹ኢሳት የግንቦት 7 ወፍጮ ነው!›› የሚል መፈክር ሲያሰማ፣ ሽመልስ ከማል ደግሞ የአዋጁ ዋነኛ ዓላማ ከዚህ ቀደም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ‹አሸባሪ› ተብለው ከተፈረጁት ድርጅቶች ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንዳይኖር ለማድረግ እንደሆነ ምሎ-እየተገዘተ ተመልካቹን በፍርሃት ለማንበድበድ ሲሞክር ተስተውሏል፡፡ ይሁንና የአቶ
ሽመልስን እርግጠኛነት ለማመን አመክንዮ መጠቀም የግድ ይሆናል፤ እናም ኢሳት የእነዚህ ድርጅቶች ዓላማ አራማጅ መሆኑን ለማሳየት ምን ተጨባጭ ማስረጃ አቀረባችሁ? ለሚለው ጥያቄ እየነገሩን ካለው እንቶ-ፈንቶ ባለፈ በማስረጃ የተደገፈ መልስ መስጠት የሚኖርባቸው ይመስለኛል፡፡ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የኤርትራ መንግስት ከሰጠው አምስት መቶ ሺህ ዶላር ውስጥ ሁለት መቶ ሺውን ለኢሳት ሥራ ማኪያሄጃ እንዲውል መወሰኑን በስልክ ሲናገር ከማሰማት በዘለለ ማለቴ ነው፡፡

እግረ-መንገድ ለመጥቀስ ያህል የዚህ ፅሁፍ ዓላማ ኢሳትን መንግስት ለምን ወነጀለው በሚል ግብረ-መልስ መስጠት አለመሆኑን ማስገንዘቡ አስፈላጊ ይመስለኛል፤ መነሻ ምክንያቴ እንደ ሚዲያ ተቋምነቱ ከእኔ ሞያ ጋር በቀጥታ መገናኘቱ ሲሆን፤ ለምን ይህ ሆነ? ያልኩበት ተጠየቅም የሕግ የበላይነት ጉዳይ ብቻ በመሆኑ ነው፡፡ ምክንያቱም የተመለከትነው ፕሮግራም ኢሳት እስከ ዛሬ ባሰራጨው ዘገባ ላይ ‹አሸባሪ› ሊያስብለው የሚያስችል ትዕዛዝ ያስተላለፈበትን ወይም ንፁሃን ኢትዮጵያውያንን በተጠመደ ፈንጂ ዶግ-አምድ እንዲሆኑ መቀስቀሱን የሚያጋልጥ ሳይሆን፣ በሰላማዊም ሆነ በትጥቅ ትግል ከተደራጁ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላት ጋር ያደረገውን ቃለ- መጠይቅ ብቻ በመደጋገም ነው፡፡ ለዚህም ይመስለኛል የዘጋቢ ፊልሙ ድብቅ ዓላማ ስርዓቱ በሀገር ውስጥ ያሉትን ጥቂት የግል የሕትመት ሚዲያዎች በፈርጣማ የፖለቲካና ቢሮክራሲ ክንዱ ደቁሶ ካኮሰመነ በኋላ፣ በተወሰነ መልኩም ቢሆን ድምፅ ላጡት ድምፅ መሆን እየቻለ የመጣውን እና ለተፎካካሪ ፓርቲዎች አማራጭ የሚዲያ ምህዳር የፈጠረውን የቴሌቪዥን ጣቢያ ከተለመደው የአፈና መንገድ /ጃሚንግ/ በተለየ ስልት ከጨዋታ ውጪ ለማድረግና በቀጣዩ ምርጫ ‹አውራ ፓርቲ›ነቱን ለማስጠበቅ የሚያደርገው ዝግጅት ነው እንድንል የተገደድነው፡፡

ከዚህ ቀደም እነ እስክንድር ነጋ በግንቦታ 7 አባልነት ተወንጅለው በታሰሩበት ወቅት አቶ መለስ ዜናዊ ለፓርላማው ‹‹ክምር ማስረጃ አለን›› ቢልም፣ ጉዳዩ ፍርድ ቤት ሲቀርብ ግን በጨበጣ እንደገባበት ማየታችን አደባባይ የወጣ ሀቅ ነበር፤ በርግጥም ማስረጃ ሆኖ የተቆጠረው ራሱ ያዘጋጀው ‹‹አኬልዳማ›› የሚል ‹‹ዘገቢ ፊልም›› እንደነበረ ስንመለከት፣ ይህ ስርዓት አስቀድሞ የተናገረበት ጉዳይ ስህተት መሆኑ እንዳይጋለጥ ምንም ነገር ከማድረግ እንደማይመለስ እንታዘባለን (በነገራችን ላይ በወቅቱ በፍትህ ጋዜጣ ‹‹አኬልዳማው! የአይሁድ ወይስ የኢህአዴግ?›› በሚል ርዕስ የዘገባውን ፈጠራነት በተጠናከረ ማስረጃ ለማጋለጥ ከተሞከረ በኋላ እንዲህ የሚል ምክር አዘል ቁም-ነገር ተላልፎ እንደ ነበር አይዘነጋም፡-

‹‹ሆሊውድ የሚሰሩ አስፈሪ (ሆረር) ፊልሞች እንኳ ቢያንስ ከ16 ዓመት በታች ያሉ ልጆች እንዳያዩአቸው የሚከለክል ሕግ አለ፣ ኢቲቪ ግን የተበጠሰ አንገት፣ የተገነጠለ ክንድ፣ የተቆረጠ እጅ፣ የተፈረከሰ ጭንቅላት… እያሳየ፣ ‹13 ዓመት የሞላው ሕፃን በሙሉ ሊያየው ይችላል› ማለቱ ኃላፊነት የጎደለው አሰራር ነው››

ባለፈው ሳምንት በቀረበው ፊልም ላይ ቢያንስ ይህ ሁኔታ ታርሞ ከ16 ዓመት በታች ያሉ ልጆች ሊያዩት እንደማይገባ ከሚያስጠነቅቅ መልዕክት ጋር መተላለፉ ስርዓቱ ምክር መስማት ጀመረ እንዴ? እንድንል የሚያጭር ነው፡፡ በርግጥም በሌሎች ጉዳዮችም እንዲህ ቢያዳምጡን ኖሮ፣ እየዋጣቸው ካለው ጥልቅ ጨለማ ራሳቸውን መታደግ የሚችሉበት በርካታ ዕድል ነበር፡፡)

የሆነው ሆኖ በዚህና መሰል ፊልሞች ላይ የሚነሳው ሌላው ለትዝብት የሚያጋልጠው ጉዳይ የደህንነት ተቋሙ ሁሉንም ዜጋ አብጠርጥሬ አውቃለሁ የሚለው ማንአህሎኝነቱ ነው፡፡ አስቂኙ ጉዳይ ግን በአዋጅ የተቋቋሙት የመረጃው መስሪያ ቤት እና የፀረ-ሽብር ግብረ-ኃይል፣ ያሻቸውን ዜጋ ቤት (በስውርም በግልፅም) መበርበር፣ ስልክ መጥለፍ፣ የኢ-ሜል እና የማሕበራዊ ሚዲያዎችን አካውንት ‹የሚስጥር ቁልፍ ቃላት› ሰብሮ መፈተሽ… ከሚያስችል ያልተገደበ ሥልጣን ጋር የሚንቀሳቀሱ ቢሆንም፣ ሽብርተኝነትን ለመከላከል እንደ አዋጭ መፍትሄ የወሰዱት ‹ዶክመንተሪ ፊልም›ን እስኪመስል ድረስ በሳምንት አንዴ መመልከቱ የተለመደ መሆኑ ነው፡፡ ርግጥ እንዲህ አይነት ትዕይንቶች ተጨማሪ ስርዓታዊ ጠቀሜታቸው ማህበራዊ ተቀባይነታቸው የጎላ ዜጎችን በስቅየት (ቶርቸር) እያንበረከኩ በቴሌቭዥን መስኮት አንገት አስደፍተው በማቅረብ ትውልዱ ተጠራጣሪና ድንጉጥ እንዲሆን ያላቸው አስተዋፆኦ አንዱ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ ይህው ቃል በሚከሰሱት ንፁሀን ላይ ተመልሶ እንደ ማስረጃ ተቆጥሮ፣ ከአስር ዓመት እስከ ዕድሜ ልክ የሚደርስ ቅጣት በ‹ካንጋሮው› ፍርድ ቤት እንዲጣልባቸው የሚያደርገው ግፈኝነት ነው፡፡ ለዚህም ቅጥ ያጣ አምባገነንነት አይደፈሬ ሥልጣኑ የሰጠውና ገና ሲረቅቅ ጀምሮ ጠንካራ ተቃውሞ ሲቀርብበት የነበረውን የፀረ-ሽብር አዋጅን የሕጋዊነት ከለላ አድርጎ እየተባባሰ በመጣ መልኩ መጠቀሙን መቀጠሉ ነው፡፡ ከጥቂት ሳምንታት በፊት የታተመው ‹‹ኒውስ ዊክ›› መፅሄት ‹‹Ethiopia declares war on [deleted] men›› በሚል ርዕስ ባስነበበው አደገኛ መጣጥፍ አዋጁን ያብጠለጠለበት ሀረግ የትችቶቹን ሙሉ መንፈስ የሚጠቀልል ይመስለኛልና እዚህ ጋር ልጥቀሰው፡-

‹‹የፀረ-ሽብር ሕጉ መንግስት ሽብርተኝነት ብሎ የሚያስበውን ጉዳይ በ‹መፃፍ፣ ማቀናበር፣ ማተም ወይም ማሰራጨት› የሚከሰውን ዜጋ በሃያ ዓመታት እስር እንዲቀጣ ፈቅዶለታል፡፡››

እነዚህን ነገሮች ጠቅልለን ስንመለከት ገዥው ፓርቲ ለሀገሪቱ ስጋት እንደሆነ የሚነግረንን ሽብርተኝነት ራሱ ባዘጋጀው ሕገ-መንግስት ሳይሆን፣ በዶክመንተሪ ፊልም ጎርፍ ለመግታት ነው የተዘጋጀው ወደሚል ጠርዝ ይገፋናል፡፡ በርግጥ የፓርቲው አላማ ሥልጣኑን መጠበቅ ነውና ሕገ-መንግስቱን ወዲያ ጥሎ ዘጋቢ ፊልሞች ላይ ቢንጠለጠል እንዴት ልንገረም እንችላለን?!

ወደ የፍርሃት ‹ሪፐብሊክ›

ይህች መከረኛ ሀገር በደርግና በኢህአዴግ ከተሠጣት ቅጥያዎች አንዱ ‹‹ሪፐብሊክ›› የሚል እንደሆነ ይታወቃል (የደርጉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሲል፤ ይህኛው ደግሞ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ነች ይለናል)፡፡ ዝርዝር ሃተታውን

ትተን ከዚህ ፅሁፍ አውድ አንፃር የሪፐብሊክን ብያኔ ሕዝባዊ መንግስትነት የሚል ትርጓሜ ሰጥተን ማለፍ ይበቃል፡፡ ይሁንና የተሻገርናቸው ሁለት አስርታት የሚያስረግጡት ብቸኛ እውነት ቢኖር ሀገሪቱ ከዚህ የተጠያቂ መንግስት ምስረታ ተፃራሪ የሆነውን መንገድ መምረጧን ነው፡፡ ከላይ ለማሳያነት የጠቀስኩት ዶክመንተሪ ፊልምም ሆነ ተያያዥ አፋኝ ሕጎቹ እና ፖለቲካዊ አተገባበራቸው በፍርሃት የሚርድ ማሕበረሰብ በመፍጠር፣ ቀጣይ አስርታቱን ካለአንዳች መደነቃቀፍ ረግጦ መግዛትን ዋነኛ ግብ ያደረጉ ናቸው፡፡ ይህን ተቋማዊነትን ተደግፎ የሚካሄደው መንግስታዊ ሽብር፣ በአንዳች ክስተት ብርክ በሚያናውጣቸው ዜጎች ማሕበረሰቡ እየተሞላ እንደሚሄድ ግልፅ ነው፤ ከፌደራላዊ ወደ ፍርሃት ሪፐብሊክ እየተደረገ ባለው በዚህ ጉዞ፣ ሀገሪቱን ከዝግመታዊ ሞት ለመታደግ የበረቱ መዳረሻቸውን ስርዓቱ አዘጋጅቷል፡፡ እናም ዋጋው ምንም ቢሆንም በአደባባዩ ላይ የሚደረግ የተቃውሞን እንቅስቃሴ፣ ኢህአዴግን ከሥልጣን የማውረድ ብቻ ከመሆን መታለፉን በሚገባ ልናስብበት እንደምንገደድ ይሰማኛል፡፡ እነርሱ ከሚቀጥለው ምርጫ በፊትም ሆነ በኋላ ሕዝባዊ ምህዳሩን ምንም አይነት የተቃውሞ ድምፅ የማይሰማበት ምድረ-በዳ ለማድረግ ይህን ያህል ርቀት መጓዛቸውን ስንመለከት ምርጫችን ሁለት ብቻ ይሆናል፡፡ ቀጣዩን ትውልድ በፍርሃት ሪፐብሊክ ውስጥ ትቶ ማለፍ፣ አሊያም አደባባዩን በጨኸት መሙላት፡፡

ኢትዮሚድያ

ይሄ አደጋ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ የግዲያ ሙከራ ይሁን አሊያም በአጋጣሚ የተፈጠረ የእሳት ቃጠሎ ይሁን ማወቅ አልተቻለም።

የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት እና የዓረና ሊቀመንበር አቶ ገብሩ አስራት ከባለቤታቸው ከወ/ሮ የውብማር አስፋው ጋር በመሆን በመኪና እየሄዱ እያለ ድንገት መኪናቸው በእሳት መያያዟን የተመለከቱ ሰዎች ባደረጉላቸው ጥቆማና ርብርብ ከእሳቱ ቃጠሎ ለጥቂት መትረፋቸውን ማወቅ ተችሏል። በመኪናዋን ግን እዚያ የነበረው ሰው ሁሉ ብዙ ርብርብ ቢያደርግም ከቃጠለው ማተረፍ አልተቻለም። በእውነቱ ይህን መረጃ እንደደረሰኝ አላመንኩም ነበር፤

በመሆኑም ወዲያው ወደ አቶ ገብሩ አስራት ስልክ ደውዬ እውነት መሆኑን ማረጋገጥ ችያለሁ። ነገር ግን የአቶ ገብሩ ባለቤት ወ/ሮ የውብማር አስፋው ህወሃት ባካሄደው የትጥቅ ትግል ግንባር ቀደም ሚና ከነበራቸው ጥቂት ሴት ታጋዮች ውስጥ የሚመደቡ እና “ፊኒክስዋ ሞታም ተነሳለች፥ ያልተቋጨው የትግራይ ሴቶች ትግል” የሚለውን መፅሐፍ የፃፉ ናቸው።
ለማነኛውም ለአቶ ገብሩ አስራት እና ለባለቤታቸው ወ/ሮ የውብማር አስፋው እንኳን በህይወት አተረፋችሁ ለማለት እፈልጋለሁ።

ግርማይ ገብሩ የቀድሞ የህወሓት ታጋይና የአሁን የቪኦኤ (VOA) ዘጋቢና ደራሲ ነው። ዓላማዬ ስለ ግርማይ ገብሩ ለመፃፍ አይደለም፤ ግርማይ በፌስቡክ ገፁ ስላሰፈረው መረጃ ለመዋስ እንጂ። መረጃው ከዚህ በፊትም አውቀው ነበር። ግን ለማስረጃ ያህል ግርማይን ልጥቀስ: ምክንያቱም ግርማይ የህወሓት ታጋይ ነበርና።

ግርማይ በ1969 ዓም የህወሓት (ተሓህት) ሦስቱ መፈክሮች ሲጠቅስ የመጀመርያውና ዋነኛው አድርጎ የፃፈው “አፄነት፣ መስፍንነትና የአማራ የበላይነት ይወድማሉ” ይላል።
በትግርኛ “ካብ ጭርሖታት ህወሓት 1969 ዓም: ሃፀይነት፣ መስፍንነትን ናይ አምሓራ ዕብለላን ዓነውቲ እዮም!” ይላል። ግርማይ ገብሩ አልተሳሳተም። ከህወሓቶች ጋር የማልስማማበት ግን ነጥብ አለኝ።

እርግጥ ነው። እኔም አፄነትና መስፍንነትን እንደ ስርዓት አልቀበልም። ምክንያቱም አፄነትና መስፍንነት (እንደ ስርዓት) ላሁኗ ኢትዮጵያ አይመጥኑም። የአፄነትና መስፍንነት ስርዓት በኢትዮጵያ ታሪክ እዚ ግባ የሚባል ለውጥ አላመጣም። ስለዚህ እኛ የሚያስፈልገን ዘመናዊ (ከዘመኑ ንቃተ ህሊናችን ጋር አብሮ የሚሄድ) የህዝብ አስተዳደር (ዴሞክራሲ) እንጂ ንጉስነት (የሰው ገዢነት) አይደለም። የምንፈልገው የሕግ የበላይነት እንጂ የንጉስ የበላይነት አይደለም።

ግን አፄነትና መስፍንነት እንደ ስርዓት ባልቀበለውም የንጉሳውያን ቤተሰቦችና መሳፍንቶች መጥፋት አለባቸው ብዬ ግን አላምንም። እኔ ብሆን እነኚህ የንጉስ ቤተሰቦችና መሳፍንት ቁልፍ የመንግስት ስልጣን አልሰጣቸውም ነበር። በሀገራቸው በሰላም እንዲኖሩ ግን እፈቅድላቸው ነበር። ምክንያቱም እንደማንኛውም ሰው ዜጎች ናቸው፤ ለሀገራቸው በተቻላቸው መጠን አስትዋፅዖ አድርገዋል። ስለዚህ ንጉሳዊ ቤተሰብና መሳፍንት ስለሆኑ ብቻ መጥፋት አለባቸው ብዬ አልፈርድም። እንደ ጠላትም አላያቸውም፣ እንደ ዜጎች እንጂ።

ህወሓት ግን በመፈክር ደረጃ በጠላትነት ፈረጃቸው። በተግባርም አጠፋቸው፣ ገደላቸው። በንጉሳዊ ቤተሰብና መስፍንነት ዝንባሌዎች ሰበብ ብዙ የተምቤን፣ ዓጋመ፣ እንደርታ፣ ዓድዋ፣ ሽረ፣ አክሱም ወዘተ መሳፍንቶች እንዲጠፉ ተደረገ። ‘ትግራይ ከመሳፍንቶች ነፃ ወጣች’ ተባለ። እውነታው ግን ‘ትግራይ ተገደለች’ መባል ነበረበት። መሳፍንቶች ከስልጣን ማውረድ እየተቻለ መግደል ምን አመጣው (ህወሓቶች ከስልጣን ማውረድ እየተቻለ መግደል ለምን ያስፈልጋል)?

ባጠቃላይ መሳፍንቶቹ ሲወድሙ ትግራይ ወደመች። አሁን በትግራይ የተቃውሞ መንፈሱ የተዳከመው በመስፍንነት ሰበብ ብዙ ብቁ ሰው ስለተፈጀብን ነው የሚል እምነት አለኝ። በህወሓት የተገደሉብንን ያህን በሌላ ስርዓት አልተገደሉብንም። ስለዚህ መሳፍንቶች ከስልጣን በማውረድ (መሳፍንቶችን ሳይሆን መስፍናዊ ስርዓቱ) ከህወሓቶች ጋር እስማማለሁ። መስፍናዊ ስርዓቱ ለማጥፋት መሳፍንቶቹ ማጥፋት ከሚል የህወሓት መፈክር ወይ መርህ ግን አልስማማም።

ሌላውና መሰረታዊ የህወሓት ችግር “የአማራ የበላይነት ይውደም!” የሚል መፈክር ነው። እኔም ብሆን የማንም ሰው ወይ ብሄር ወይ ሌላ አካል የበላይነት አልቀበለም። የቴድሮስ ወይ ዮሃንስ ወይ ምኒሊክ ወይ ኃይለስላሴ ወይ መንግስቱ ወይ መለስ ወይ ኃይለማርያም ወይ አማራ ህዝብ ወይ ትግራይ ህዝብ ወይ ኦሮሞ ህዝብ ወይ ሌላ … የበላይነት አልቀበልም። እኔ የምቀበለው የበላይነት ‘የሕግ የበላይነት’ ብቻ ነው። የሌላ የማንም የበላይነት አልቀበልም።

እንደ ፖለቲካ ድርጅት አንድን ህዝብ ዒላማ አድርጎ መነሳት ግን ስህተት ብቻ ሳይሆን በሽታ ነው። ህወሓት (ተሓህት) የአማራን ህዝብ ዒላማ አድርጎ ሲነሳ፣ ሌሎች የህወሓት ተቃዋሚዎች ደግሞ በህወሓት ምክንያት የትግራይን ህዝብ ዒላማ ሲያደርጉ ዉጤቱ ምን ይሆናል? አንድን ህዝብ ከሌላ ህዝብ ጋር የማጣላት ስትራተጂ የፖለቲካ ዕብደት ነው። ህዝብና ገዢው መደብ አለመለያየት (አንድ እንደሆኑ አድርጎ ማሰብ) የፖለቲካ እውቀት ማነስ ዉጤት ነው። ስርዓቱ መቃወምና መታገል እየተቻለ ህዝብን ዒላማ አድርጎ በህዝቦች ላይ መተማመን እንዳይኖር መትጋትና በህዝቦች መካከል ጥላቻ እንዲነግስ መስራት ጠባብነት ነው።

አንድን ህዝብ የበላይነት ሊይዝ አይችልም። አንድን ቡድን ግን በአንድን ህዝብ ስም በመነገድ ሌሎችን ሊበድል ይችላል። የሰው የበላይነት (በህዝቦች ላይ) ሊተገብር ይችላል። ህዝብ እንደ ህዝብ ግን ሌላውን ህዝብ ሊበድል አይችልም። ህወሓት የትግራይን ህዝብ እንደሚወክል ይነግረናል። የትግራይን ህዝብ እወክላለሁ እያለ ሌሎች ህዝቦች (የትግራይን ጨምሮ) ይበድላል። ሌሎች ህዝቦች (የትግራይ ዉጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን) ደግሞ በህወሓት ስርዓት ሲበደሉ በትግራይ ህዝብ የተበደሉ አድርገው ያስባሉ። ግን ስህተት ነው። መታረም አለበት። የትግራይ ህዝብ ለራሱ በህወሓት አገዛዝ የሚበደል ነውና።

“የአማራ የበላይነት” የሚባለው የህወሓት በሽታ እስካሁን ፈውስ አላገኘም። በመርህ ደረጃ ህዝብን ዒላማ አድርጎ ህዝብን ለመታገል መነሳት ስህተት ነው ብያለሁ። በፖለቲካ ህዝብን ዒላማ አይደረግም። ምክንያቱም የፖለቲካ ዓላማ ህዝብን ማገልገል እንጂ ህዝብን መጨቆን አይደለም። ስለዚህ ህዝብን የመበደል ዓላማ መያዝም መተግበርም የህሊና ወንጀል ነው። ህወሓቶች ይህን በሽታ (“የአማራ የበላይነት” መፈክር) አልተዋቸውም። አሁንም “ፀረ አማራ” እንቅስቃሴዎች አሉ። የህወሓት የአሁኑ ስትራተጂ “እኛ ከስልጣን የምንወርድ ከሆነ ከአማራ ጋር አብረን አንቀጥልም” የሚል ገንጣይ አስተሳሰብ እያራመዱ ይገኛሉ። “እኔ ከሌለሁ ሠርዶ አይብቀል …” ዓይነት ስትራተጂ መሆኑ ነው። በጣም የሚገርመው ነገር ፀረ ብአዴንም መነሳታቸው ነው። ለነሱ ከስልጣን ከሚወርዱ ኢትዮጵያ ብትበታተንና ትግራይን አስገንጥለው ትግራይን እየጨቆኑ ቢገዙ ይመርጣሉ።

ግን ይህን “አማራ” የሚባል ህዝብ መቼ ይሆን የበላይነት ይዞ ሌሎች ህዝቦችን የበደለው? አንድን ህዝብ እንዴት ሌላውን ህዝብ ይበድላል? ህዝብ ህዝብን ሊበድል አይችልም። ምክንያቱም አንድን ህዝብ ሌላውን ህዝብ መበደል ከጀመረ (ከቻለ) ህዝብ መሆኑ ቀርቶ ገዢ መደብ (elite) ሁነዋል ማለት ነው። ገዢ መደብ ከሆነ ደግሞ ህዝብ አይደለም። ገዢ መደብ ስርዓት ነው። ህዝብና ስርዓት ደግሞ ይለያያሉ።

ምናልባት የህዝብ የበላይነት አለ የምንለው ህዝብን የሚያስተዳደር (የሚገዛ) ስርዓት ከህዝቡ የወጣ ሲሆን ይሆን? ይህም አሳማኝ አይደለም። ምክንያቱም ገዢ ሁሌ ከህዝቡ ነው የሚወጣው (የቅኝ ግዛት ካልሆነ በስተቀየር)፤ ገዢ ከህዝቡ እንጂ ከማርስ አይመጣም። የኢትዮጵያ መሪ ከኢትዮጵያ ህዝብ ይወጣል። በኢትዮጵያ ብዙ ብሄሮችና ብሄረሰቦች አሉ። ስርዓቱ ከሁሉም ህዝቦች ሰዎች ይኖሩታል። መሪ ግን አንድ ነው የሚሆነው። ያ አንድ ሰው (መሪው) ከአንድ ብሄር ሊሆን ይችላል። ያ አንድ ሰው ስልጣኑ ተጠቅሞ ሌሎች ህዝቦችን ሊበደል (ወይ ሊጠቅም) ይችላል። ሰውየው የፈጠረው ስርዓት ለህዝቡ ቢጎዳም ቢጠምም ከስርዓቱ ይገናኛል እንጂ መሪው ከመጣበት ብሄር ጋር አይገናኝም። ስለዚህ ገዢዎች የሚወክሉት የፈጠሩትን ስርዓት እንጂ የመጡበትን ብሄር አይደለም።

የደርግ ስርዓት ሲበድለን፣ “አማራ በድሎናል” ይሉናል። የኃይለስላሴ ስርዓት ሲበድለን “አማራ በድሎናል” ይሉናል። የምኒሊክ ስርዓት ሲበድለን “አማራ በድሎናል” አሉን። የህወሓት ስርዓት ሲበድለንስ ማን በደለን ሊሉን ነው? የትግራይ ህዝብ? አይሆንም። ምክንያቱም የትግራይ ህዝብ የትግራይን ህዝብ ይበድላል? አንድን ህዝብ ራሱን ይበድላል? በደል ሁሉ ወደ አማራ ህዝብ ለምን? ስርዓትና ህዝብ ማገናኘት የፖለቲካ ኪሳራ ያስከትላል።

ግን እስቲ ይሁን፤ መሪዎች የመጡበትን ብሄር ይወክላሉ እንበል (ስህተት ቢሆንም)። እነሱ (መሪዎቹ) ሲበድሉ የመጡበት ብሄር በበዳይነት ተፈርጆ እንደ ጠላት ይቆጠር እንበል። የአማራ ህዝብ መቼ ይሆን በመሪዎቹ አድርጎ ሌሎች ህዝቦችን የገዛ (የበደለ)? ያለፉ ጨቋኝ ስርዓቶች አማራ ነበሩ ያለው ማነው? አማርኛ የተናገረ ሁሉ አማራ አይደለም። እስቲ የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ መሪዎች እንመልከት።

ብዙ ግዜ የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ የሚጀምረው ከአፄ ቴድሮስ ነው (ወይም ከዚሁ እንጀምር! ምክንያቱም ከአፄ ቴድሮስ በፊት ኢትዮጵያ በመሳፍንቶች ነበር የምትተዳደረው። በዘመነ መሳፍንት መሳፍንቶች የራሳቸውን ህዝብ (ብሄር) ይገዙና ይበድሉ ነበር)። “አማራ” ተብሎ ከተሰየመው አከባቢ የሚወለድ ገዢ ቴድሮስ ነው። አፄ ቴድሮስ ኢትዮጵያ አንድ ለማድረግ በዛን ግዜ የነበሩ መሳፍንቶች ተዋጉ። አፄ ቴድሮስ ዉግያው የጀመሩት በአማራ መሳፍንቶች (የጎጃም፣ ወሎና ጎንደር) ነበር። ቴድሮስ “ከአማራ ስለመጣሁ፣ አማራ ስለምወክል፣ የአማራ መሳፍንቶች ማጥፋት የለብኝም” አላሉም። (ህወሓት ለትግራይ መሳፍንቶች እንዳደረገው ሁሉ)። ስለዚህ አፄ ቴድሮስ አማራን ወክለው ሌላው ኢትዮጵያዊ አልበደሉም (ከበደሉም ለሁሉም ነው)። ስለዚህ “በአማራ ህዝብ ተገዛን” የሚለው ክስ “በአፄ ቴድሮስ ተገዛን” የሚል እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ።

የአማራ ተወላጅ የሆነ የኢትዮጵያ ገዢ ቴድሮስ ብቻ ነው ብዬ አስባለሁ (ጉዳዩ ለታሪክ ተመራማሪዎች ልተወው እንዳልሳሳት፤ ከተሳሳትኩ እታረማለሁ)። ዮሃንስ አማራ አልነበረም፣ ምኒሊክ አማራ አልነበረም፣ ኃይለስላሴ አማራ አልነበረም፣ መንግስቱ አማራ አልነበረም፣ መለስ አማራ አልነበረም፣ ኃይለማርያም አማራ አይደለም። ማነው አማራ?

ምናልባት “የአማራ ገዢዎች” የምንለው ግለሰቦቹ (ንጉሶቹና መሪዎቹ) ሳይሆን ስርዓቱ ነው ካልን ያው ስርዓቱማ ከሁሉም ህዝቦች ተወካዮች አሉበት። አማራ ለብቻው ገዥ ነበር ማለት አንችልም። ምናልባት ገዢዎቹ አማርኛ ስለሚናገሩ ነው ካልን ደግሞ አማርኛ የተናገረ ሁሉ አማራ አይደለም። አቶ መለስም አማርኛ ይናገር ነበር። አፄ ዮሃንስም አማርኛ ይናገሩ ነበር (አማርኛ የኢትዮጵያ ኦፊሽየላዊ የስራ ቋንቋ እንዲሆን የወሰኑት አፄ ዮሃንስ ናቸው የሚል መረጃ አለኝ፤ ‘መረጃ’ እንጂ ‘ማስረጃ’ አላልኩም)።

የአማራ ህዝብ እንደ ማንኛው የኢትዮጵያ ህዝብ በኢትዮጵያ ገዢዎች ሲሰቃይ የነበረ ነው። ባልበላበት በልተሃል፣ ባልገዛበት ገዝተሃል ሲባል ይገርማል፤ ልክ እንደ ትግራይ ህዝብ። የትግራይ ህዝብ ሳይበላ በልተሃል፣ ሳይገዛ ገዝተሃል ይባላል፤ ህወሓት በበላው፣ ህወሓት በገዛው። ህወሓት ትግርኛ ተናጋሪ ስለሆነ ከትግራይ ህዝብ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም (በፖለቲካ መልኩ)። ያለፉ ገዢዎች አማርኛ ስለሚናገሩ ከአማራ ህዝብ ጋር የሚያገናኛቸው ነገር የለም። ህዝብ ሌላ ገዢ ሌላ።

ባጭሩ ፀረ ህዝብ አቋም መያዝ ተገቢ አይደለም (ለማንኛውም ህዝብ)። ሰው የፈለገውን የፖለቲካ አመለካከት መያዝ ይችላል። “የቀድሞ ስርዓት አባላት …” ምናምን እያልን አንፈርጅ። የህወሓት አባላት ለሌሎች ሰዎች የቀድሞ ስርዓት አባላት፣ ናፋቂዎች ወዘተ እያላቹ ስትፈርጁ እናንተም ራሳችሁ ከህወሓት ስርዓት በኋላ “የቀድሞ ስርዓት አባላት ..” ምናምን እየተባላቹ ስማቹ ይጠፋል፣ የፈለጋችሁን የፖለቲካ ፓርቲ አባል የመሆን መብታቹ ይገደባል። አሁን በሌሎች ላይ የምትፈፅሙትን ስም የማጥፋት ተግባር በናንተ (በራሳቹ) ይፈፀማል።

ስለዚህ እናስተውል። ከጥላቻ ፍቅር ይሻለናል። ጥላቻ ይውደም። አሜን!

It is so!!!

እ ጎ አ ከ 2001 – 2006 የእሥራኤል ጠ/ሚንስትር የነበሩትና ፤ ከዚያን ጊዜ አንስቶ የአልጋ ቁራኛ ሆነው የቆዩት አሪዬል ሻሮን ፤ በዛሬው ዕለት በደቡብ እሥራኤል በነጌቭ በረሃ በራሳቸው የአርሻ ቦታ በወታደራዊ ሥነ ሥርዓት ግብዓተ መሬት ተፈጽሞላቸዋል።

አርየል ሻሮን።ሞቱ እንዳይባሉ ይተነፍሳሉ።አሉ እንዳይባሉ አይሰሙም፣ አይለሙም።ስምንት አመት።ሐኪሞች «ከስቃይ መገላገያ» በሚሉት ደንብ እንዳይረዷቸዉ «አይሁድ ነብስ አያጠፋም» የሚለዉ ሕግ አገዳቸዉ።እሳቸዉን ግን በነብስ አጥፊነት የሚወነጅሏቸዉ ብዙ ናቸዉ