የአፍሪቃ መሪዎች የተስማሙበት በወንጀል የማያስጠይቅ መብት
ከ15 ቀናት በፊት በማላቦ ኢኳቶሪያል ጊኒ በተደረገዉ የአፍሪቃ መሪዎች ጉባኤ የሰብዓዊና የሕዝብ መብት ጉዳይ ላይ በተወያዩበት ርእስ ለማብራሪያ ያህል በአፍሪቃ ሕብረት የሕግ መምሪያ ኃላፊዉ ፕሮፌሰር ቪንሰንት ሜኺዮሌ መግለጫ ሰጥተዋል።
ከ15 ቀናት በፊት በማላቦ ኢኳቶሪያል ጊኒ በተደረገዉ የአፍሪቃ መሪዎች ጉባኤ የሰብዓዊና የሕዝብ መብት ጉዳይ ላይ በተወያዩበት ርእስ ለማብራሪያ ያህል በአፍሪቃ ሕብረት የሕግ መምሪያ ኃላፊዉ ፕሮፌሰር ቪንሰንት ሜኺዮሌ መግለጫ ሰጥተዋል።
ለመሆኑ ወጣቱ ፆሙን እንዴት ይጾማል? ያፈጥራልስ? የረመዳን ጾም ከገባ ሁለት ሳምንት ሊሞላው ጥቂት ቀናት ነው የቀሩት። በዚህ በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በፆም ፀሎት የሚታሰበው የቅዱስ ወር ለማን ም ሙስሊም ቢሆን ግዴታ ነው።
ኢህአዴግ በምርጫ ዋዜማ የጀመረው እስር በአምባገነንነት መስመሩ ለመቀጠል የቆረጠ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው!!! በፖለቲካ አመለካከታቸው እና እምነታቸው የታሰሩ ዜጎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ በድጋሚ እንጠይቃለን!! ሕወሓት/ኢህአዴግ ለአለፉት 23 ዓመታት ወደር የሌለው የዴሞክራሲያዊ መብት ገፈፋና የሰብአዊ መብት ረገጣ በዜጎች ላይ ሲፈጽም መቆየቱና አሁንም በዚያው የአፈናና እስር መንገድ መቀጠሉን ዓለም የሚያውቀው እውነታ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በተለይም በሚቀጥለው ዓመት […]
ወያኔ አቶ አንዳርጋቸውን እንዴት ማፈን ቻለ? ለዚህ ጥያቄ መልስ መስጠት ለግንቦት 7 ብቻ ሳይሆን ለሁላችንም የሞትና የሽረት ጥያቄ ነው:: በቂ ማስረጃ እስክሚሰበሰብ ድረስ አራት አቅጣቻዎችን መመርመር ያስፈልጋል:: 1) ለሻቢያ ሁሉ ነገር ከራስ በላይ ነፋስ ነው:: ራሱ ሻቢያ በተዘዋዋሪ ለወያኔ የአቶ አንዳርጋቸውን የበረራ ሰዓታቸውን አሳልፎ ሊሰጥ ይችላል::ይህ እንግዲህ በኤርትራ ውስጥ የሚገኙ የግንቦት 7 መሪዎች ሁኔታውን በደንብ […]
ካሳለፍነው ማክሰኞ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር ውለው በማዕከላዊ በእስር ላይ የሚገኙት ወጣቱ ፖለቲከኛ ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ፣ ወጣቱ ፖለቲከኛ ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት ፓርቲ ድርጅት ጉዳይ ም/ሀላፊ ወጣቱ መምህርና ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታ የአረና ፓርቲ አመራር በትላንትው ዕለት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም ከምሽቱ 12፡16 ላይ የአረና ፓርቲ […]
በዚህ ወር ብቻ እጅግ ከባድ የሆኑ ለጆሮ የሚቅፉ እና ለሰው ልጆች የሚያሰቅቁ የሰብአዊ መብት ገፈፋዎች እና የዜጎች ወደ እስር ቤት መወርወር የበለከተበት ከሃገር ቤትም አልፎ እስከ ጎረቤት አገር ድረስ ተዘልቆ በጉቦ የዜጎች የመዘዋወር መብት በስውር እጆች የተደፈሩበት እሱንም ተከትሎ የተቃዋሚ ድርጅቶች አመራሮች ከየመንገዱ እና ከቤታቸው እየተያዙ ወደ እስር የተወረወሩበት ሁኒታ እያየን እየሰማን ነው። የግንቦት ሰባት […]
በአሸባሪው መንግስታዊ ዘራፊ እና አፋኝ ቡድን የታፈነው አቶ አንዳርጋቸው ጸጌ ወያኔ ለመፍታትም ሆነ ለመግደል ዝግጁ አይደለም ። ግደሉት አሊያም ስቀሉት ቢባሉ እንኳን በፍጹም አያደርጉትም። ምእራባውያኑ ከአፍ ወሬ ውጪ ምንም የሚተገብሩት ነገር የለም ፡ እስክንድር ነጋ በቂ ምሳሌ ሊሆን ይችላል ከሰብአዊ መብት ድርጅቶች ጀምሮ እስከ አሜሪካው የውጪ ጉዳይ አናት ኬሪ ድረስ ድምጻቸውን ቢያሰሙም ለይስሙላ እና ለብሄራዊ […]
የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ በታሰሩ ወጣት ፖለቲከኞች ዙሪያ ያቀረበው ዘገባ
ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ
ኢትዮጵያ ሪቪው ምንጮቹን ጠቅሶ ፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የታፈኑት፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ የሆኑት አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሳያወቁት ፣ በአቶ ጌታቸው አሰፋ የሚመራው የሕወሃት ደህንነት ጽ/ቤት እና በአቶ ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል ዉሳኔ እንደሆነ ዘገበ። ሁለቱ የሕወሃት ባለስልጣናት፣ የሆነውን ነገር ለጠቅላይ ሚኒስተሩ ለመንገር እንኳን ደንታ እንደልነበራቸው ኢትዮጵያ ሪቪው፣ እነ አቶ ጌታቸው አሰፋ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም […]
arrested opoosition leaders not taken to court
Bizuneh Tsigie, report
Bizuneh Tsigie, Interview
ሰላማዊ ሰዎችን ማሰር ቀለቡ ያደረገው መንግስት፣ በትላንትናው እለት ከአንድነት ፓርቲ አቶ ሀብታሙ አያሌው እና አቶ ዳንኤል ሽበሺ፣ ከሰማያዊ ፓርቲ አቶ የሺዋስ አሰፋ፣ ከአረና አቶ አብርሃ ደስታ እንዳሰራቸው ተነግሯል። ይህንን በመቃወም በፌስቡክ ኢትዮጵያዉያን ካሰፈሩት መካከል ጥቂቱን እንደሚከተለው ቀንጭበን አቅርበናል፡ ያሬድ አማረ፡ «ወደኋላ አንመለስምዘመን ተሻጋሪ ወጣቶች በቅለናልና በምንም መልኩ ለሚደረግ ማዋከብ፤እስራት እና ግድያ ከጀመርነው የሰላማዊ ትግል መስመር […]
የህወሓት/ኢህአዲግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ዜጎችን በማፈንና በማሰቃየት ብሎም በመግደል የአፈና አገዛዙን ለረጅም ጊዜ ሲያራምድ መቆየቱ ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ በተለይም ባለፉት 10 ዓመታት የህዝብን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማፈን እስራትና ግድያውን ህጋዊ ለማስመሰል የተለያዩ አፋኝ አዋጆችን አውጥቷል፡፡ እነዚህን አዋጆችንም ተገን አድርጎ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና አባለትን፣ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን፣ እንዲሁም የእምነት ተቋማት […]
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
ሐምሌ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት ሰሞኑን ከአገር ቤት በሚደወሉ ስለኮች የተጨናነቀ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ደዋዮች የኢህአዴግን ስርአት በሃይል ለመፋለም መቁረጣቸውን የሚገልጹ ናቸው። እንደሰሞኑ ሁሉ ” መንገዱን አሳዩን እና አቶ አንዳርጋቸው ይዘውት የተነሱትን ራእይ እውን እናድርገው ” የሚሉ ወጣቶች እየተበራከቱ ሲሆን፣ አንዳንዶች ደግሞ ህዝቡ ራሱን እያደራጀ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባው እያሳሰቡ ነው። አንድ አስተያየት ሰጪ መንግስት …
ሐምሌ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በፌደራል ፖሊሶች እየተደበደበ ወደ አልታወቀ ስፍራ ተወስዶ የነበረው ታዋቂው ፖለቲከኛና ጸሃፊ አብርሃ ደስታ ማእከላዊ እስር ቤት መታሰሩ ታውቋል። የአብረሃ መኖረያ ቤት በፖሊሶች እንደተፈተሸም ለማወቅ ተችሎአል። የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ የፓርቲው ምክትል የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ዳንኤል ሽበሺ እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ ምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ አቶ የሽዋስ …
ሐምሌ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የህወሃት አባል የሆነውና በሶማሊ ክልል የደህንነት ሃለፊ በመሆን ሲሰራ የነበረው መቶ አለቃ አወጣሃኝ በክልሉ ፕሬዚዳንት ትእዛዝ እንዲታሰር ተደርጓል። ግለሰቡ በምን ምክንያት እንደታሰረ ለማወቅ ባይቻልም፣ በክልሉ ፕሬዚዳንት እና በህወሃት የጸጥታ ሰራተኞች መካከል እየተካረረ የመጣው አለመግባባት ማሳያ መሆኑን ከስፍራው የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።
የሶማልያ ጠ/ሚንስትር አብዲዋሊ ሼክ አህመድ ሙሐመድ፣የብሔራዊ ደኅንነት ድርጅት ሹም የነበሩትን በሺር ጉቤንና የፖሊሱን ኃይል አዛዥ አብዲከሪም ዳሒርን በመሻር በምትካቸው፤ በብሪታንያ የሶማልያ አምባሰደር የነበሩት
በብራዚል በመካሄድ ላይ ባለውና ፣ የፊታችን እሁድ በሚያከትመው የዘንድሮው የዓለም የአግር ኳስ ዋንጫ ውድድር፣ ትናንት ማታ በተካሄደው ሁለተኛው የግማሽ ፍጻሜ ውድድር አርጀንቲናና ኔደርላንድ በ9o ው ደቂቃ ጨዋታና 30 ደቂቃም ተጨምሮ ባለመሸና
Press Release by Blue Party Ethiopia / Semayawi Party- Ethiopia/
It is a well known fact that TPLF/EPRDF has slaughtered and oppressed Ethiopian citizens since it came to power. In order to oppress the peaceful struggle, especially within the last 10 years, the regime acclaimed several repressive proclamations and laws to legalize its butchery and tyranny. Many politicians, journalists, bloggers, religious leaders and people who raised question against the regime are victims of these proclamations. Since these controversial laws have been applauded by TPLF/EPRDF, the security institutions that serve the regime have put a lot of politicians, journalists, activists and many who issue its power to jails. The regime also tries to label Medias such as ESAT as terrorists’ medium to threaten politicians in relation to terror act which is ridiculous. Blue likes to stress out that no one should not and cannot choose Medias for anyone in regards to freedom of speech and press.
Accordingly, TPLF/EPRDF’s obsession of power and its negligence to accountability is leading the country in a wrong and chaotic situation. Particularly the last four years have been difficult and the arrest of many peaceful citizens made the political atmosphere very constricted. Nevertheless, countless people are struggling peacefully within the rule of law; many flee abroad to over throw the dictatorial government with whatever way they thought is possible. Thus, Blue Party /Semayawi/ finds it very significant to take this firm position due to the above reasons and more that hasn’t been mentioned here:
1- On June 24 2014, the rebel group Ginbot 7’s General Secretary, Andargachew Tsege was detained by the Yemeni intelligence officers in collaboration with Ethiopian intelligence officers. The officials of both countries knowingly violated international conventions. It is not legal or convenient to intervene in eternal matters of a sovereign country whatsoever. Consequently, the act of Yemeni officials will sure distress the upcoming relationships of the countries. Nonetheless, as the regime didn’t let the public and his family know his whereabouts for 16 days, the matter has been viewed suspiciously in our party, in the public at large and in the international community. It is our concern that he could be ill treated and more. Therefore, Blue Party strongly demands that Andargachew Tsege must be treated moderately and that all his rights under custody are respected.
2- The regime also illegally arrested prominent figures of Ethiopian politicians on July 8. The detainees are members and leaders of parties who are engaged in peaceful struggle. In fact it is not surprising to hear such news; however, we have learned that the regime is anxious and is trying to connect the detainees with rebel forces so that it hopes it can crack down the peaceful struggle before the 2015 election for they could be a threat to its power. It is clear that the dictatorial rule wants to stay in power more through spreading fear among the society. Thus its desperation is leading its ego to arrest one of our members and three other party leaders. Blue Party’s National Council Vice Chairperson Mr. Yeshiwas Assefa, Mr Habtamu Ayalew(Head of Public Relations Affairs of UDJ), Mr. Daniel Shibeshi(Vice Chairman of Organizational Affairs of UDJ) and Arana Tigray’s executive committee member and activist Mr. Abraha Desta are detained for activism and peaceful struggle. All these figures have been engaged in promoting peaceful struggle within the rule of law. Their arrest boldly hints that the regime’s final days in power are counted and change is inevitable in the near future. Hence, Blue Party demands an immediate release of the detainees and as well advocate the regime to stop the state terror. We condemn that TPLF/EPRDF comes to its sense and do what’s right for themselves and the country before it’s too late.
Finally we make sure that the act of state terror by TPLF/EPRDF will not hinder us for an inch from the none-violent struggle we are committed to. We have come into the decision that the offensive and atrocious act of TPLF/EPRDF required us to bring the struggle to the next level. Hence, we call upon the Ethiopian people to be ready to a nationwide movement and make sure that Blue Party is fully committed to provide the leadership needed at its unsurpassed. The Party also calls the peaceful parties, international institutes, human right activists, civic societies for all Ethiopian born and Ethiopians to stand together.
Long live Ethiopia
Blue/Semayawi Party Ethiopia
July 10, 2014
ተማርን የሚሉ ሰዎች አማርኛን ቋንቋ ዉስጥ አንዳንድ የእንግሊዘኛ ቋንቋን እየሰነቀሩ ቋንቋዉ እንዲመነምን እየዳረጉ ናቸዉ ይላሉ ምሁራን። በሌላ በኩል ሃሳብን ለመግለፅ አማርኛ ቋንቋ አስቸጋሪ ነዉ የሚሉም አልጠፉም!የባዕድ ቃላትን የመዋስ ጉዳይ እንዳለ ሆኖ፤ እንግሊዘኛ ቃላትን ጣል እያደረጉ የመናገር አባዜ የተለመደ ይመስላል
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ መንግሥት ለፖለቲካ ፓርቲዎች በሚሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ላይ አድሎአዊ አሰራር ይታይበታል፣ ሕጋዊም አይደለም ሲል ቅሬታውን አሰማ።
የእስራኤል የጦር አዉሮፕላኖች በፍልስጤም ግዛት ጋዛ ላይ ዛሬ ደጋግመዉ ባደረሱት ድብደባ የተጎዱ ሲቪሎች ቁጥር መጨመሩን ዘገባዎች ያመለክታሉ። የተመድ የፀጥታዉ ምክር ቤት እስራኤል ከሃማስ ጋ የገጠመችዉን ፍጥጫ ለመመልከት አስቸኳይ ስብሰባ ያደርጋል።

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
ሀምሌ 3/2006ዓ/ም
የህወሓት/ኢህአዲግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ዜጎችን በማፈንና በማሰቃየት ብሎም በመግደል የአፈና አገዛዙን ለረጅም ጊዜ ሲያራምድ መቆየቱ ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ በተለይም ባለፉት 10 ዓመታት የህዝብን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማፈን እስራትና ግድያውን ህጋዊ ለማስመሰል የተለያዩ አፋኝ አዋጆችን አውጥቷል፡፡ እነዚህን አዋጆችንም ተገን አድርጎ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና አባለትን፣ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን፣ እንዲሁም የእምነት ተቋማት መሪዎችን እና በአገዛዙ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ማሰሩን፣ ማሰቃየቱንና ግድያውን ተያይዞታል፡፡ በህገ መንግስቱ የተካተቱ የሰብዓዊ መብቶችንና ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን በሙሉ የሚጥሰውና የአምባገነንነት ስልጣኑን ለማራዘም ሲል ያፀደቀው የፀረ-ሽብር አዋጅ ከፀደቀበት እለት አንስቶ ኢህአዴግ ለስልጣኔ ያሰጉኛል የሚላቸውን ፍፁም ሰላማዊ ታጋዮችንና ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው በድፍረት የፃፉ ጋዜጠኞችን ብሎም የእምነት ነፃነታችን ይከበር ብለው የጠየቁ የሀይማኖት መሪዎችን በጠራራ ፀሃይ ያለምንም ወንጀል በዚሁ ህገ ወጥ አዋጅ ‹‹የፀረ ሽብር ግብረ ሀይል›› በሚባል ማንነቱ በማይታወቅ የጨለማ ቡድን ወደ እስር ቤት እያጋዘ ይገኛል፡፡
ይህን የሚያጋልጡ ሚዲያዎችንም ለማፈን እስር ቤቶችን ጨምሮ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር እያፈሰሰ የአየር ሞገድ ያውካል፤ በዚህ ሳያበቃ በሀገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን የሚያሰሙ ፖለቲከኞችን ለማሸማቀቅ እንደ ኢሳት ያሉ ሚዲያዎችን የአሸባሪ ልሳን ብሎ በመፈረጅ ሚዲያውን የሚጠቀሙትን ደግሞ ከአሸባሪዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው አድርጎ መወንጀሉን ቀጥሎበታል፡፡ እንደሰማያዊ እምነት ማንም አካል መልእክት የሚያስተላለፍበትን የሚዲያ ተቋም ሊመርጥለት እንደማይችል መንግስት እንዲገነዘበው ከዚህ በፊት በግልፅ ያሳወቀ ሲሆን አሁንም ፓርቲው በዚሁ የፀና አቋሙ እንደሚቀጥል በድጋሚ ይገልፃል፡፡
ባጠቃለይ የዚህን ገዢ አካል የእውር ድንብር ሀገር የማስተዳደር ጉዞ ለመታገል በርካቶች በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ቢሆንም በህወሓት/ኢህአዲግ ግፍና መከራ ተገፍተው ስርዓቱን በሃይል እናስወግዳለን ብለው ሀገር ጥለው የተሰደዱ ዜጎችም እንዳሉ ይታወቃል፡፡ የህወሓት/ኢህአዲግ ማናለብኝነትና የስልጣን ጥመኝነትም በግለሰቦች ላይ ከሚያስከትለው ማህበራዊ ቀውስ በላይ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ አለመረጋጋትን አስከትሏል፡፡ በአሁኑ ሰዓትም ይህ ገዢ ፓርቲ የፈጠረው ስርዓት የሀገሪቷን ሰላማዊ የፖለቲካ ምህዳር በማጥበብ ሀገራችንን ወደ አልተፈለገ አለመረጋጋትና ቀውስ እየመራት ይገኛል፡፡ፓርቲያችንም እነዚህን ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎችም በቅርቡ እየተፈፀሙ የሚገኙ ህገ ወጥ ድርጊቶች ስላሳሰበው ይህን መግለጫ ለማውጣት ተገዷል:-
1. ሰኔ 16 2006 ዓ.ም የየመን መንግስት የዓለም አቀፍ ስምምነቶችንና ድንጋጌዎችን በመጣስና በሰው ሀገር የውስጥ ጉዳይ በመግባት የአማፂ ቡድን ግንቦት ሰባት ዋና ፀሃፊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን መያዟ ይታወሳል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ለህወሓት/ ኢህአዴግ ተላልፈው መሰጠታቸውን ከ16 ቀናት በኋላ መታወቁና ይህንንም ሁለቱ ሀይሎች ማመናቸው ተሰምቷል፡፡ ነፃነት በሌለበት ሀገር ዜጎች ሰብዓዊ ክብራቸውን ለማስጠበቅ የሚያደርጉት ጥረት የሌሎች ሀገር መንግስታት የሚያደርጉትን ጣልቃ ገብነት በዓለም አቀፍ ስምምነቶችም ሆነ በተለይ በሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ጥላ የሚያጠላ መሆኑን ግንዛቤ አለመወሰዱ እጅግ የሚያሳዝን ድርጊት ነው፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከተያዙ በኋላ ላለፉት 16 ቀናት በምን አይነት ሁናቴ እንደቆዩ ህዝብና ቤተሰቦቻቸው እንዲያውቁት አለመደረጉ፤ ስለ አያያዛቸው ሁኔታም በማህበረሰቡና በፓርቲያችን ውስጥ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንዲኖር አድርጓል፡፡ሰማያዊ ፓርቲ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሰብዓዊ አያያዝ እያሳሰበው ህወሓት መራሹ የኢህአዴግ አገዛዝ አያያዛቸውን ግልፅ እንዲያደርግ ሰብዓዊ ክብራቸውም እንዲጠበቅ በጥብቅ ያሳስባል፡፡
2. በዚሁ ሳምንት ገዢው ፓርቲ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ የአምባገነኑን መንግስት ህወሓት/ኢህአዲግን ሲታገሉ የነበሩ ፖለቲከኞችን በስመ አሸባሪ ከያሉበት እየለቀመ ህገ-ወጥ እስራት መፈፀሙ ይታወቃል፡፡ ህወሓት/ኢህአዲግ ይህ ግብታዊ ተግባሩ ምንም እንኳን አዲስ ባይሆንም በአሁኑ ወቅት ለውጥን ለማምጣት በቆራጥነት እየታገሉ ያሉ ሰላማዊ ታጋዮችን ማሰሩ በሀገር ውስጥ በህጋዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ፓርቲዎችን ከአማፂ ቡድኖች ጋር ግንኙነት ያላቸው በማስመሰል ሰላማዊ ትግሉን ለማዳከምና መጪውን 2007 ዓ/ም ምርጫ ያለ ተቀናቃኝ ለማለፍ የሚደረግ ህገ ወጥ እንቅስቃሴ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ የፓርቲያችን ብ/ም/ቤት ምክትል ሰብሳቢ የሆነው አቶ የሺዋስ አሰፋ በሰላማዊ ትግሉ በቁርጠኝነት እየተሳተፈ ባለበት ሁኔታ ለእስር መዳረጉ፤ የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው፤ የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሀላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄን በመፍጠር ላይ ያለው የአረና /ትግራይ/ ፓርቲ አመራር አባል የሆኑትን አቶ አብረሃ ደስታ ለእስር መዳረጋቸው ህወኃት/ኢህአዴግ የመጨረሻው መጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ያረጋግጣል፡፡ በመሆኑም አገዛዙ እያካሄደ ያለውን መንግስታዊ ሽብር አቁሞ ለሀገርም ሆነ ለራሱ የሚበጀውን መንገድ እንዲከተል እያሳሰብን የታሰሩት የፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን፡፡
በመጨረሻም ፓርቲያችንን መንግስት እያደረገ ያለው ሽብርን የመንዛትና ህግን የመጣስ ተግባሩ መቼም ቢሆን ከሰላማዊ ትግሉ እንደማያቆመውና ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በአፅንኦት እየገለፀ እነዚህንና ከላይ የተጠቀሱትን የገዢውን ፓርቲ መርህ አልባነት፣ ህገ-ወጥነት እና የለየለት አምባገነንነትን አሁን ካለው ነባራዊ እውነታ ጋር አጣምሮ የትግል ስልቱን ደረጃ ከፍ ወዳለ ምዕራፍ ማሸጋገር እንዳለበት አምኗል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ ለምናደርጋቸው ሀገር አቀፍ ንቅናቄዎች መላው የሀገሪቱ ህብረተሰብ በንቃት ተዘጋጅቶ እንዲጠብቅ ጥሪውን እያስተላለፈ ለዚህም ቁርጠኛ አመራር ለመስጠት ዝግጁነቱን ለመግለፅ ይወዳል፡፡በዚህ አምባገነንነትን ለመታገል በሚደረገው ንቅናቄም በሀገር ውስጥ የሚገኙ ህጋዊና ሰላማዊ ፓርቲዎች፤አለም አቀፍ ተቋማት፤የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፤ሲቪክ ማህበራት፤መላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከሰላማዊ ትግሉ ጎን በጋራ እንድንቆም እንጠይቃለን፡፡
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር
ሰማያዊ ፓርቲ
ሀምሌ 3/2006ዓ/ም
አቡጊዳ – እነ ሃብታሙ ፍርድ ቤት አልቀረቡም – አብርሃ ደስታ የት እንዳለ አይታወቅም « ከትላንት በስቲያ የተያዙት የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በዛሬው እለት አራዳ ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ የፍኖተ ነፃነት የፖሊስ ምንጮች የፍኖተ ነፃነት የፖሊስ ምንጮች እንደጠቆሙት የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወጣት ሀብታሙ አያሌው፣ የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ም/ኃላፊ የሆነው አቶ ዳንኤል ሺበሺ እንዲሁም […]
ከመኢአድ/አንድነት ውህደት አመቻች ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ………………………………………………………… የውህደት አመቻች ኮሚቴውን በማሰር ውህደቱን ማደናቀፍ አይቻልም!!! ኢህአዴግ ሰሞኑን የጀመረው እስር የአንድነት/መኢአድን ውህደት የማደናቀፍ አቅም እንደሌለው ለኢትዮጵያ ህዝብ ማረጋገጥ እንወዳለን …………………………………………… በኢትዮጵያችን በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለማምጣት እየታገሉ የሚገኙት አንድነትና መኢአድ ከጥልቅ ውይይት በኋላ ወቅታዊው የፖለቲካ ሁኔታ የሚፈልገውን በመገንዘብ፤ የህዝቡን ጥያቄ መመለስ የሚችል የበተባበረ የፖለቲካ ሃይል ለመፍጠር እንዲቻል […]
አገር ቤት ያሉ መሪዎች ቁርጠኝነት ያስደንቀኛል። ግርማ ሰይፉ «ለመታሰር እንዘጋጅ» አለ። ዳንኤል ተፈራ «ገዥዎች፣ እመኑኝ ባሮጌው መንገዳችሁ በርካቶችን ነፃነት ናፋቂዎች በሰፋፊ እስር ቤታችሁ ታጉሩ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የዚህን ትውልድ የነፃነት መንፈስ ግን ልታስሩት አትችሉም» አለ። የፍኖት ዋና አዘጋጅ ነብዩ «ጨቋኞችን መታገል ፅድቅ እንጂ ኩነኔ እንደሌለው አምናለሁ፤ ጭቆናን እምቢ በማለቴ የምጠጣት እያንዳንዷ ፅዋ በፈጣሪ ዘንድ ወሮታ […]
ግፍና ሰቆቃ ወልዶናል – የአዲስ አበባ አንድነት ሕዝብ ግንኙነት ያሬድ አማረ ************************************************************ እንታሰራለን ስንል አንፈታም ማለት አይደለም ፤ በትግል ውስጥ አልፈን እናሸንፋለን ስንልም ላንሞት እንችላለንም ለማለት አይደለም ፡፡ ሊሰመርበት የሚገባው ግን በሰላማዊ ትግሉ ማሳ ላይ ዘር ሆነን ተዘርተን ብዙ ፍሬ እንዳፈራን በተራዳን ወቅትና ወደ ጎተራ በአንድነት ተሰባስበን በገባን ወቅት የተነሳንለት ዓላማ ጥልቅና ምጡቅ እንደሆነ ልባችን […]
በ፲፱፻፹፯ ዓ.ም. ዳግመኛ ከተከፈተ ወዲህ የተመረቁት ደቀ መዛሙርት ብዛት 2175 ደርሷል የተቋማዊ ነፃነት ዕጦትና የበጀት እጥረት ‹‹ጥናትና ምርምር ላይ እንዳላተኩር አድርጎኛል፡፡›› መሠረቱ የወጣው ሕንፃ ሥራ እንዲቆም በጀቱም እንዲመለስ የተላለፈው ትእዛዝ አወዛግቧል ወደ ዩኒቪርስቲ ደረጃ የማሸጋገሩ ሒደት በግንባታ ላይ የሚገኘውን ሕንፃ መጠናቀቅ ይጠብቃል ‹‹ከዛሬው ደስታችኹ የሚበልጥ ደስታ ከፊታችኹ ስለተዘጋጀ ደስታችኹ ዕጥፍ ድርብ ነው፡፡›› /ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ/ …![]()
ሐምሌ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአገር ውስጥ እና በውጭ ከፍተኛ ጫና የተፈጠረበት የኢህአዴግ መንግስት የአቶ አንዳርጋቸውን ምስል በቴሌቪዥን ካቀረበ በሁዋላ የተለያዩ አስተያየቶች በማህበራዊ የመገናኛ መንገዶችና በስልክ እየተሰጡ ነው።አብዛኛው አስተያየት ሰጪ በቴሌቪዥን የቀረበው ምስልና ድምጽ መቆራረጡን ፣ ኢቲቪን የሚያክል ድርጅት ጥራት ያለው ቀረጻ ለማካሄድ አለመቻሉ ገዢው ፓርቲ ለፕሮፓጋንዳ የሚሆን ነገር ለማግኘት አለመቻሉን ገልጸዋል። ሚኒሊክ ሳልሳዊ …
ሐምሌ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢሳት ከአገር ቤት በተከታታይ የሚደወሉ ስልኮችን ለማስተናገድ ከአቅሙ በላይ እንደሆነበት እየገለጸ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ደዋዮች አቶ ለአቶ አንዳርጋቸው ያላቸውን ከበሬታ የሚገልጹና ኢህአዴግን በሃይል ለማንበርከክ የሚታገሉትን ቡድኖች ለመቀላቀል እንዴት እንደሚቻል የሚጠይቁ ናቸው። በሌላ ዜና ደግሞ የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የተፈጸመውን የአፈና ተግባር አውግዟል። ትህዴን ” የወያኔ አምባገነን …
ሐምሌ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢህአዴግ የጸጥታ ሃይሎች የአንድነት ፓርቲን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆነውን ወጣት ሃብታሙ አያሌውን ፣ የፓርቲውን የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሽበሺ፣ የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት ምክትል ሰብሳቢ የሆነውን የሽዋስ አሰፋን እንዲሁም በማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን ከመቀሌ በመጻፍ የሚታወቀውና አረና ፓርቲ አባል የሆነው መምህር አአብራሃ ደስታን ይዞ አስሯል። እሰረኞቸ ማእከላዊ በሚባለው …
Yemisirach Hailemariam, Andargachew’s wife, full interview
Andargachew’s wife Yemisirach Hailemariam and brother Bizuneh Tsigie, report
Ethiopia opposition leaders arrested
ዘወትር ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ላይ ኢትዮጵያና ኤርትራ ውስጥ ለሚገኙ አድማጮች በአማርኛ የሚተላለፉ ዜናዎች፣ ቃለመጠይቆችና ሌሎችም ትኩስ ዘገባዎች፤ እንዲሁም በባሕል፣ በጤና፣ በሴቶች፣ በቤተሰብና በወጣቶች፣ በፖለቲካ፣ በግብርና፣ በንግድ፣ በተፈጥሮ አካባቢ፣ በሣይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በስፖርት፣ በሌሎችም አካባቢያዊና የመላ አፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መደበኛ ዝግጅቶች የተካተቱባቸው የአንድ ሰዓት ዕለታዊ ሥርጭቶች
እ ጎ አ ካለፈው ጥር ወር መግቢያ ወዲህ፣ በዩናይትድ ስቴትስ ፣ ኒው ዮርክ፤ ቢል ደ ብላሲዮ የተባሉት የዴሞክራቱ ፓርቲ አባል የከተማይቱን የከንቲባነት ሥልጣን ከመረከባቸው በፊት፤ ከዚያ በፊት ፣ 3 ጊዜ ተመርጠው እ ጎ አ ከ ጥር 1፤ 2002
የመን ለኢትዮጵያ መንግሥት አሳልፋ የሰጠቻቸው የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዴሞክራሲ ፓርቲ ዋና ፀሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በኢትዮጵያ እሥር ቤት ውስጥ ይበደላሉ ብሎ እንደሚፈራ ዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሂዩመን ራይትስ ዋች አስታወቀ ።
ደቡብ ሱዳን ሶስተኛ ዓመት የነፃነት በዓሏን ዛሬ አከበረች ።ርዕሠ-ከተማ ጁባ ዉስጥ በከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ በተከበረው በዚሁ የነፃነት በዓል ላይ የደቡብ ሱዳን መሪ ሳልቫ ኪር ፣ተቀናቃናቸው የቀድሞው ምክትል ፕሬዝዳንት ሪክ ማቻር የሰላም ንግግሩን እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል ።
የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆነው ወጣት ሀብታሙ አያሌው፣ በትላንትናው ዕለት በማዕከላዊ እስር ቤት ከታሰረበት ጊዜ ጀምሮ በቤተሰቦቹ እና በወዳጅ ጓደኞቹ እንዳይጎበኝ በመደረጉ ያለበትን ሁኔታ ለማወቅ እንዳልተቻለ የፓርቲው አመራሮች ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡ አመራሮቹ አክለውም፣ በዛሬው ዕለት ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት ያመሩት፣ የሀብታሙ ጠበቆች አቶ ተማም አባቡልጉ እና አቶ ገበየሁ እስረኛውን መጠየቅ አትችሉም ተብለው መባረራቸውን አስረድተዋል፡፡
ሐብታሙን ይህ ይገልጸው ይሆን ? ********************************* በምረቃ መጽሔቱ ፎቶ ስር‹‹የፈራ ይመለስ››ብሎ ነበር ******************************************** ሐብታሙ አያሌው ራሱን ለፈጣሪው ያስገዛ ሐይማኖተኛ ሆኖ ያገኙት ኢህአዴጎች በአነጋገሩና ነገሮችን ለመግለጽ ያለውን ውስጣዊ ድፍረት ተገንዝበው ከቤተክርስቲያን ጠለፉት ፡፡አባላቸው አደረጉት፡፡ሐብታሙ አባል የሆነበት ኢህአዴግ ጭንቅ ውስጥ ነበርና በልጁ የመናገርና የማሳመን ችሎታ ለመጠቀም ከወጣቶች አደረጃጀት አንስቶ እስከ ወጣቶች ፌደሬሽን ፕሬዘዳንትነት አድርሶታል፡፡ በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር […]
የሰሞኑ የኢትዮጵያችን ሁኔታ ሀዘን፣ ቁጣ፣ ንዴት፣ እልህ፣ ብሎም የደስታ ስሜትን የቀላቀለ ነበር፡፡ የእሰሩ ሁኔታ ቀጥሏል፡፡ ዛሬ እንኳን ከአንድነት ፓርቲ አቶ ሀብታሙ አያሌው እና ከሰማያዊ ፓርቲ አቶ የሺዋስ አሰፋ መታሰራቸውን ሰምተናል፣ አውቀናል፡፡ የዚህ መሰል አካሄድ ግን መዘዘን የሚስከትል ይመስለኛል፡፡ አሁን አሁን ሰዎች እንደጥጃ ከቤታቸው፣ ከየመንገዱ፣ ከሚሰሩባቸው ቦታዎች …እየተወሰዱ መታሰራቸው በሀገራችን እየተለመደ የመጣ አዲስ ክስተት ሆኗል፡፡ ሥልጣን […]
የፓርላማ አባልና የአንድነት ከፍተኛ አመራር አባል አቶ ግርማ ሰይፉ የኢሕአዴግ መንግስት በሰላም የሚታገሉ ወጣት ፖለቲከኞችን የማሰሩን ጉዳይ እብድነት ብለዉታል። «እነዚህ ሰዎች አብደው መሆን ይኖርበታል፡፡ ሀብታሙ አያሌውን ፖሊሶች ይዘውት እንደሄዱ ሰማው፡፡ ስልኩ ይጠራል ግን አይመልስም፡፡ የእነርሱን ሃሳብ የሚቃወም ሁሉ አሸባሪ እየመሰላቸው በሽብር እራሳቸውን እያናወዛቸው ያለ ይመሰለኛል፡፡ ሀብታሙን ሊያስሩት ይችላሉ በህዝብ ውስጥ ያለውን የነፃነት መንፈስ ግን ማስረ […]