ከሶስት ቀናት በፊት ቀትር ላይ አንድ የስልክ ጥሪ ደረሰኝ ። አንድ እዚህ ጅዳ የሚገኝ ወዳጀ ነበር ። ይህ ወዳጀ በስደተኛ ዜጎቻችንና በኮንትራት ሰራተኞች ላይ የከፋ ግፍ ሲፈጸም ፣ ዜጎች በራሳችን መንግስት ተወካዮች በጅዳና ሪያድ መጠለያዎች ፍዳቸውን ሲያዩ ፣ ኢትዮጵያውያን ሲያመን ህመሙ ዘልቆ ሲያመው እና የአረቡ መገናኛ ብዙሃን ስማችን አጉድፈው ክብራችን ቀንሰው መረጃ ሲያሰራጩ በስጨት ብለው […]

በኢጣልያ የባህር ክልል አካባቢ ሐሙስ፣ መስከረም 23 ቀን፣ 2006 ዓም ወደ አውሮጳ ለመግባት በሞከሩ አፍሪቃውያን ስደተኞች ላይ እንደገና ዘግናኝ የመሰመጥ አደጋ ከደረሰ በኋላ የአውሮጳ ህብረት አባል ሀገራት የህብረቱ የስደተኞችና እና የውጭ ዜጎች ጉዳይ ፖሊሲ ሰብዓዊነት እንዲታከልበት እና ለስደተኞች ደህንነት

ተክለሚካኤል አበበ (ቶሮንቶ ካናዳ)

የኛ ነገር፡ ክፍል 16፤ ከኔ ማእዘን፤

 

እንደ መግቢያ

 

1.       ይህ ጽሁፍ ሲታሽ፤ ሲሰቃይ እዚህ የደረሰ የቁጭት ጽሁፍ ነው፡፡ ወዲህም ግንቦትሰባትየምወደውበሱ ግን ደስ ያላለኝ ፓርቲስለሆነና፤ ዲባቶ ብርሀኑ ጋ ለኢሳት ዝግጅት ወደቶሮንቶ ስለሚዘልቅ፤ ያንዳንዶቻችንን ቁጭትና ጭንቀት ለመገለጽ የተሰናዳ ጽኁፍ ነውቀደም ያሉት የራስን የሆነን አካል የተቸሁባቸው ጽሁፎቼ ባንዳንድ ወዳጆቼ ዘንድ ቅሬታ ፈጥረዋል፡፡ በዚህ ጽሁፍ ውስጥ ወዳጅን የሚያስቀይመውን ንጥረ ነገር ለመሽረፍ ጥረት አድርጌያለሁ፡፡ ቀድሞውንስ በግል መንገሩ አይሻልም ወይ ለምን መጸፍ አስፈለገ ለሚሉት መልሱን ወደመጨረሻ እሰጣለሁ፡፡ ደግሞስ ፖለቲከኞች ወደ አደባባይ ሲወጡ ለመተቸት ተዘጋጅተው አይደለምን? ስለዚህ የሌሎችን ሀሳብ እተቻለሁ፤ የእኔም እንዲተች እነሆኝ፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

ዩሱፍ ያሲን

በየታሪክ መጋጠሚያው የሚወጥር ጥያቄ

በተለያዩ የሀገራችን ወሳኝ የታሪክ ምዕራፎች ኢትዮጵያ ለመፃኢ እድሏ ዕጣ ፈንታ ወሳኝ በሆነ መስቀለኛ የታሪክ መጋጣሚያ ላይ ትገኛለች ሲባል ደጋግመን ሰምተናል። በርካታ ጊዜያት መንታ መንገድ ላይ ናት ተብሎ ሲነገር እንሰማለን።

ሙሉውን አስነብበኝ …

መስከረም ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ባለፈው ሳምንት በመላ አገሪቱ የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞችን እየሰበሰበ በ2005 የስራ አፈጻጸምና የ2006 ዓም በጀት እቅድ ትግበራ ላይ ሲያወያይ ቢሰነበትም፣ ለኢሳት ሚደርሱት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በሁሉም ቦታዎች ላይ በተደረጉት ስብሰባዎች ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጥሞታል። በአዳማ የተካሄደውን ስብሰባና ተሰብሳቢዎች ያቀረቡዋቸውን ቅሬታዎች ኢሳት ቀደም ብሎ የዘገበ ሲሆን፣ በአማራ ክልል …

መስከረም ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከምዘና ፈተና ጋር በተያያዘ በተማሪዎችና እና በዩኒቨርስቲው አስተዳደር መካከል በተፈጠረ ልዩነት ከ3 ሺ በላይ ተማሪዎች ዩኒቭረስቲውን ለቀው እንዲወጡ በመታዘዛቸው በቤተክርስቲያናትና በሰዎች ቤት ተጠልለለው እንደሚገኙ ተማሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። ተማሪዎቹ ከእረፍት በተመለሱበት ማግስት በቂ ዝግጅት ሳያደርጉ የምዘና ፈተና ውሰዱ መባላቸውን ተቃውመው ተጨማሪ የጥናት ጊዜ እንዲሰጣቸው በመጠየቃቸው ችግር መፈጥሩን ገልጸዋል። …

መስከረም ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ብሉበርግ የአለማቀፍ አጥኚዎች ቡድንን ዋቢ በማድረግ እንደዘገበው መንግስት በማስገንባት ላይ ያለው የአባይ ግድብ መሰረቱ ችግሮች ሊኖሩበት ስለሚችል መንግስት እንደገና እንዲያስጠና መክሯል። ግድቡ በታችኞቹ ተፋሰስ አገሮች ላይ የሚያስከትለው ጉዳት በደንብ መጠናት አለበት ሲሉ የባለሙያዎቹ ቡድን አስተያየቱን ሰጥቷል። የግድቡን መሰረት ለማጠንከር መሰረታዊ የሆነ ለውጥ ያስፈልጋል በማለት ያመለከቱት ባለሙያዎች፣ “ድክመት …

መስከረም ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ላምባዱሳ እየተባለ በሚጠራው የጣሊያን ደሴት አካባቢ በጀልባ መስጠም ከሞቱት መካከል የ11 ሰዎች አስከሬን ቢገኙም፣ ከ200 በላይ ሰዎች አሁንም የገቡበት አልታወቀም። ፖፕ ፍራንሲስ በስፍራው ተገኝተው አደጋውን ከተመለከቱ በሁዋላ ሀዘናቸውን ገልጸዋል፣ ችግሩን ዝም ብለው የሚያዩትን አገራትም ወቅሰዋል። ብዙ የጣሊያን ባለስልጣናት የህጻናቱን አስከሬን እያዩ ስሜታቸውን መቆጣጠር ተስኖአቸው ሲያለቅሱ ታይቷል። እስካሁን …

መስከረም ፳፬ ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል ኮርፖሬሽንን የሥራ ሂደት ለማስተዳደር አንድ የህንድ ኩባንያ ተመረጠ፡፡ ፖወር ግሪድ ኮርፖሬሽን ኦፍ ኢንድያ የተባለው ኩባንያ የኢትዮጵያን ኤሌክትሪክ ሀይል ለማስተዳደር የሁለት ዓመት ኮንትራት ተሰጥቶታል፡፡ መንግስት ድርጅቱን ለውጭ ኩባንያ መስጠት የወሰነው በድርጅቱ ውስጥ ለውጥ ማምጣት ባለመቻሉና የተሻለ ስራን በሀገሪቱ ለማስተዋወቅ እንደሆነ ተገልጿል፡፡ የውሃ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር የሆኑት …

መስከረም ፳፬ ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የደቡብ ክልል ብሔራዊ መንግስት መስተዳደር በክልሉ ያሉ ከተሞችን አስመልክቶ ዶክመንተሪ ፊልም ለማሰራት ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል 19 ሚሊዮን ብር ለመፍቀድ ስብሰባ መቀመጡን ምንጮች ለኢሳት ገለጹ፡፡ በፖለቲካ ውሳኔ ለመንግስታዊው ዋልታ የመረጃ ማዕከል ሊሰጥ የታቀደው ፕሮጀክት የደቡብ ክልል መገናኛ ብዙሀንን ቅር ማሰኘቱ ታውቋል፡፡ የክልሉ መገናኛ ብዙሀን በቂ መሳሪያና የሰው ሀይል እያለው ስራውን …

መስከረም ፳፬ ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ከዋሉት የአዳማ ጉምሩክ የህግ ማስከበሪያ ሀላፊ ከነበሩት ግለሰብ ሰባት ነጥብ አራት ሚሊዮን ጥሬ ገንዘብ መያዙን የፌደራል ስነ ምግባር ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ገለጹ፡፡ ሀላፊ የነበሩት አቶ ተመስገን ስዩም 12 የነዳጅ ማመላለሻ ቦቴዎችን በሌላ ሰው ስም ገዝተው ለተገዙት መኪኖች ውክልና በመውሰድ መኪኖቹን ለሌሎች ሰዎች ሸጠዋል የሚል …

ከሊቢያ ወደ ጣሊያን 500 አፍሪካውያ ስደተኞችን ይዛ ትጓዝ የነበረች ጀልባ በደረሰባት የእሳት አደጋ በትንሹ 130 ስደተኞች በአሰቃቂ ሁኔታ መሞታቸው ተሰማ፡፡ ከአቅሟ በላይ ለተሻለ ኑሮ ፍለጋ ወደ ጣሊያን የሚሄዱ ስደተኞችን የጫነችው ጀልባ በመጨናነቋ ከተሳፋሪዎች አንዱ እርዳታን ለማግኘት ሲል በለኮሰው እሳት ጀልባዋ መቀጣጠሏን አሶሼትድ ፕሬስ ከጣሊያን ዘግቧል፡፡ የእሳት ምልክትን ከሩቅ አይተው ሰዎች ለእርዳታ ይደርሱልናል በሚል የተለኮሰው እሳት …

በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር መስሪያ ቤት ስራ ከጀመሩ ሁለት ወራት ያስቆጠሩት ምክትል ሚንስትሯ ሊንዳ ቶማስ ግሪንፊልድ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ መንግሥታቸው በአፍሪቃ በተለይም በቀፍሪቃ ቀንድን የሚከተለውን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አብራርተዋል።

ምስራቅ ኢትዮጵያ ውስጥ የምድር ባቡር የቀን ሰራተኞች በቀን ክፍያ በደል ደርሶብናል እያሉ ነው። እነዚሁ በምዕራብ ሃራርጌ ዞን አሰቦት አካባቢ የሚገኙ የምድር ባቡር ሰራተኞች እንደሚሉት ሌላ ቦታ ለተመሳሳይ ስራ በቀን የሚከፈለው ከ50 እስከ 100 ብር ሲሆን እነሱ ግን 25 እና 30 ብር ብቻ እየተከፈላቸው ነው።

ሄኖክ የሽጥላ (ገጣሚ)

ከምን ልጀምር? እንደው ይጨንቃል፤ ደሞ ዝም ቢሉት ያንቃል። አሁን ይሄን የምጥፈው ለማስተማር ነው ለማካረር? በልጅነቴ አንድ አብሮ አደጌ በጣም የሚወዳቸው እናቱና አባቱ እየተጋጩ ቢያስቸግሩት፣ ሄኒ አሁን አንተ በኔ ቦታ ብትሆን ማንን ትጠላለህ? ብሎ የጠየቀኝ ትዝ አለኝ። ማንን ልጥላ? ለማን አግዤስ ማንን ላውግዝ? ማንንስ ልውቀስ? ማንንስ ልጥቀስ? ሲደብር።

ሙሉውን አስነብበኝ …

በኢጣልያ ደሴት፤ ላምፔዱዛ አቅራቢያ ፣ ትናንት በእሳት ከተያያዛች በኋላ በሰጠመችው ጀልባ ውስጥ ከነበሩት ስደተኞች ደብዛቸው የጠፋውን ፍለጋ ዛሬም ቀጥሏል ።ከሊቢያ የባህር ጠረፍ 500 የሚሆኑ ስደተኞች አጭቃ ላምፔዱዛ የባህር ዳርቻ የደረሰችው ይህችው ጀልባ የኤርትራ እና የሶማሊያ ስደተኞች ነበር ያሳፈረችው ።

ዩናይትድ ስቴትስ ለሩዋንዳ የምትሰጠዉን ወታደራዊ እርዳታ እንደምታቆም አስታወቀች። የዋሽንግተን አስተዳደር እንዳለው እርዳታው የሚቋረጠው ሩዋንዳ ፣ ህፃናትን በውትድርና በማሰለፍ የሚከሰሰውን

በቤተ ክርስቲያናችን ዐውደ ምሕረት ሰፍነውና በቢሮክራሲዋ ውስጥ ተሰግስገው የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄን ለሚያራምዱ ድርጅቶች ተልእኮ አስፈጻሚና የቅስቀሳ ኃይል የኾኑ ሕገ ወጥ ቡድኖችና ግለሰቦች የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ለመመከት በኦርቶዶክሳዊ ቀናዒነትና በበጎ ፈቃድ ተሰባስቦ በጥቅምት ወር ፳፻፫ ዓ.ም አገልግሎቱን የጀመረው የፀረ – ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ሰባክያንና ዘማርያን ጥምረት÷ ባለፈው ሳምንት አጋማሽ ወቅታዊ ጉዳዮችን የገመገመበትንና ቀጣይ የአገልግሎት አቅጣጫዎችን የተለመበትን የግማሽ ቀን …

የተከበሩ ግርማ ሠይፉ ማሩ, Girma Seifuይህንን የማፊያ ቡድን በማፍረስ ታሪክ ይስሩ!

ግርማ ሠይፉ ማሩ

በ2005 ዓ.ም. የምክር ቤት ዘመን መጨረሻ ላይ የደህንነት መስሪያ ቤቱን በሚኒስትር ደረጃ ለማዋቀር የሚረዳ አንድ አዋጅ ለምክር ቤት ቀርቦ ፀድቆዋል። ይህ አዋጅ ሲፀድቅ ከነቅሬታዬ ያለኝን ድጋፍ መስጠቴ ይታወቃል።

ሙሉውን አስነብበኝ …

Based on a facebook status update I wrote on October 1, 2013 on which I mentioned OLF (Oromo Liberation Front was dead) I had an interesting discussion on twitter. I thought, though boring, it would also be helpful in provoking discussion on the Oromo-Ethiopia politics and future, if you get a few lines of the discussion. Enjoy! Below is the status update I published:
They give a term their own meaning; then, they condemn it.

For me, Ethiopianism is one of these purposely made confusing terms. It is used by OLF’ites to refer to Abyssinianism (which is dominated by Amhara, Tigre and a few southerners esp. the Guraghe people culture). Ethiopia is a country that’s wider than that Abyssinia now. Yes, Abbyssinians have used force, abused rights, marginalized some cultures and languages but that don’t make wrong the fact that they created a bigger sovereign State. Bigger is better in either political power or economical strength. That State – Ethiopia – is home of all regardless of differences in language, cultural values and religious beliefs. The only thing that makes it look like a comfortable home for few is its political setting. Its political setting has always been different to its societal setting.

Political leaders of Ethiopia, unfortunately, couldn’t successfully create regimes that favor every member of the society equally and impartially.

Ethiopia is a sovereign State. Any Ethiopian has the right and the obligation to struggle to make Ethiopia an inclusive one for all because it is meant to be like that. Therefore, Ethiopianism can be defined and redefined as a State that accommodates all varieties of social values, language and cultural differences. Be it in Federalism or whatever you have, Ethiopiaism can be defined as an accommodating one to be in the future; but not as the discriminatory one as in the past.

I am not in delusion about the presence of politicians or activists who work to profit from defaming or faking common values. For me, they will eventually perish.

I have a good example how political entrepreneurship perishes the good cause. OLF, especially for introducing Oromummaa, was a great party. Oromumma is a movement to create pride in and promote the Oromo language, the Oromo Culture and the Oromo indigenous Religion. The Oromo people loved it and accepted OLF as redeemer of the people. But, OLF couldn’t be in the place when needed. Dirty political games and interests have washed their cause away from the OLFites mind. And, only if they think that will make them look like more Oromo than the other (there is no such thing though) they do anything. That’s how they created lines between societies who are living together to profit from the split. Now, the only benefit OLF do is used to TPLF as a means to jail Oromo youth dissidents.

By the way, it has been so long since OLF has died; but, its ghost – like Meles’ ghost – is leading many. I suggest it is time to wake up and listen to the pain of the people you are claiming struggling for. Stand by it and help solving its challenges. Don’t confuse it.

Here is part of the twitter discussion:

Bira’anuu Biyo (@BiraanuuBiyo): @befeqe, you can feed your followers and yourself momentarily happiness by declaring #OLF is dead. We know, you can’t fool the Quubee generation.


Me (@befeqe): You don’t know the people; not even its pain.

Oromo Network (@Oromo_NT): @befeqe, why do you think people believe in a party supposedly long dead? OLF may die, but what it stands or stood for will never die.


Me: People believe in OLF because it was the first genuine party for the people. Not anymore. Sooner or later people distinguish between the people and the party. Oromummaa was its only legacy.

@Oromo_NT: Even in a democratic Ethiopia, if she ever becomes one, there will be a political party that will advocate for Oromo Self Determination.


Me: In democratic Ethiopia oneness may not really means one being. It will be united-ness.

@Oromo_NT: I can assure you that I and my likes will form a political party that will seek independence from Ethiopia even if Ethiopia democratizes.


Me: You’ll have the right but I doubt your success.

@Oromo_NT: Fair enough! But you guys assume that Oromos love being Ethiopian without even doing a single empirical research on their attitude.


Me: don’t you guys me. Who am I? Anyway, I believe the self-determination narration is an insult or niqet to the Oromo people.

@Oromo_NT: You guys are those of you who think you can speak for Oromos without even studying what Oromos want.


Me: Emmm… I can’t argue with your take of who I am. Let’s proceed the important discussion.

@Oromo_NT: You cannot build oneness on the foundations of conquest and annexation. That legacy must be undone first through self determination.


Me: It is the definitions you have given to unity that forces you draw this conclusion. Unity isn’t oneness. It’s united-ness for the better.

@Ze_Alem: @Oromo_NT, It obvious that EPRDF fear every Oromo as OLF member not the people of Ethiopia. Why separation if we bring equality?


@Oromo_NT: @Ze_Alem, one may want Oromia as a country just for the sake of it alone.

Me: The Oromo people paid a lot to the present Ethiopia. They can’t just leave it all.


@Oromo_NT: When they leave they will take what is their own. There is really nothing to miss. Why would I want to be united with people I cannot trust with my liberty and freedom? What has my community gotten since Adowa? …. Oromos paid not for Ethiopia but because Italy also came to enslave them too.

Mesfin Meshesha (@kobele): @Oromo_NT, can you cite a book or any historical evidence on that?


@Oromo_NT: @kobele, western Oromos had wanted to establish an independent Oromo confederation when Italy came but when that failed they fought. If Britain hadn’t refused to act on their request, western Oromia would have parted ways with Ethiopia.

@kobele: Who do you mean by Oromo in this case? It needs an organization to make such a claim, right?


Me: You can’t just runaway though. Besides, if there is democracy majority rules. Why bother about trust? Others should.

@Oromo_NT: Why is it a niqet if Oromos do not want to run or be part of Ethiopia? It is true Oromos should not beg for their independence.


Me: No! The narrations undermine the people of Oromo.

@Oromo_NT: In that case change the name of the country to Oromia & ditch Ethiopia. That would be a good start.


Me: That’s a better narration but still there are lots of questions.

@Oromo_NT: What are those questions?


Me: For e.g. Oromo is major ethnic group not majority as in 50%+1 but Ethiopia isn’t an ethnic group.

@Oromo_NT: Why then should Oromos bear a name of country that subjugated them for a century when they can have their own country? Ethiopia is a Trojan horse hiding in her belly an ethnic group that defined what it means being an Ethiopian. A fatal blow to brand. The name Ethiopia does not resonate with me, I do not relate to it.


Me: Do the majority of the people worry about that? Should that be the question? It’s beyond my response but OLF too has no real answer for that.

@Oromo_NT: Since you are with Zone9, why don’t you conduct a survey in Oromia to find out the prevailing attitude?


Me: We would if we could. (Money?) We will think about it though. It would be nice but the survey may not get true attitudes. People may doubt our intention. They might think of us as cadres of TPLF.

@Oromo_NT: There are ways of conducting anonymous surveys or even use other means to ensure confidentiality. It is better than nothing if done correctly. Otherwise, how else would you know public attitude on issues like this?


Me: Sure. detailed studies should be done but until then investigating all ways & discussing them would help from making fatal mistakes

@Oromo_NT: haha, some farmers may not even know the name Ethiopia or who the prime minister is. But ask those who deal with Ethiopia.

ኢትዮጵያን ለማጥፋት ከተሾመ የወንበዴ መንግሥት ፍትህንና ወገንተኝነትን መጠበቅ ቂልነት መሆኑን በ22 ዓመታት ያልተረዳ ዜጋ፣ የማይሆን ጥያቄ ጠይቆ የማይሆን መልስ ቢሰጠው ሊገረም አይገባውም፡፡ ከነተረቱ “ራሷ ሄዳ ጣፊያ የከለከሏት ‹ምላስ ሰምበር ላኩልኝ› አለች” ይባላል፡፡ ወያኔ ከመነሻው ሀገርንና ዜጋን ድራሹን ለማጥፋት መነሳቱንና ይሄ ሁሉ ሕዝብ በዓለም ዙሪያ እንዲበተን ያስገደደው ራሱ ወያኔ መሆኑን እየተገነዘብን በራሱ አምሳል የተቀረጹ ድፍን ቅል […]

ክቡር ፕሬዚደንት ግርማ ሆይ፣ ኢትዮጵያንና “ሕዝቦቿ”ን የሚወዱ ከሆነ ቀጥዬ የምነግርዎትን ከልብ እንዲሰሙኝ በሚያምኑት እለምነዎታለሁ፡፡ ሰሞኑን በጡረታ ሊሰናበቱ እንደሆነ ከተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ዜና ዘገባ ሰማሁ፡፡ በመጀመሪያ ሥራዎን ጨርሰው ለዚህ በመብቃትዎ እንኳን ደስ ያለዎ፡፡ ቀጥዬም በሥራ ዘመንዎ ምን እንደሠሩና እኛ በምናውቅልዎም ሆነ እርስዎ በሚያውቋቸው ምክንያቶች የተነሣ ምን ምን መሥራት ፈልገው ሊሠሩ እንዳልቻሉ “ፕሬዚደንታዊ የሥልጣን ዘመን”ዎን የኋሊዮሽ በማሰብ […]

ይድረስ ለተከበራችሁ የአንድነት ደጋፊወቻችን እና ለኢትዮጵያውያን ሚዲያዎች በሙሉ በቅድሚያ ሰላምታችን ባላችሁበት ይድረሳችሁ። ላለፉት ሶስት ወራት የተደረገዉ የመጀመሪያዉ ዙር የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት እንቅስቃሴ፣ በኛ ግምት በጣም በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋልብለን እናምናለን። በዚህ ሂደት ብዙዎች ኢትዮጵያውያን ሚዲያዎች እና ደጋፊወቻችን በሙሉላደረጉልን ድጋፍና ትብብር ምስጋናችን ከፍተኛ ነው:: የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ የሰሜን አሜሪካ አንድነት ፓርቲ ደጋፊ ግብረ ኃይል ያዘጋጀውን ቴሌ […]

ጉዳዩ ‘ሲሪዬስ’ ነው፤ በተለይ በአዲስ አበባ። ግን ማንም ደንታ የሰጠው አይመስልም። ዘርፈ ብዙ የትራንስፖርት አገልግሎት ችግሮች በምሬታችን ላይ ምሬት እየጨመሩ ነው። ኪሳራውን ግን እስካሁን አላሰላነውም። ለምን ይህን ጽሑፍ ከአንዲት ወዳጄጋ ሰሞኑን በሰራነው ግምታዊ (ወይም ግብታዊ) ስሌት አንጀምረውም።

አዲስ አበባ ውስጥ ቢያንስ አንድ ሚሊዮን ሠራተኞች አሉ። ከዚያ ውስጥ በቃ 50ሺሕዎቹ ብቻ በትራንስፖርት ችግር አንድ ሰዓት አረፈዱ እንበል፤ 50ሺሕ የሥራ ሰዓት ባከነ ማለት አይደለም? በቀኑ የሥራ ሰዓት 8 ስናካፍለው  በድምሩ በየቀኑ 6,250 ሰው ከሥራው እንደቀረ (ወይም 6,250 የሥራ ቀናት እንደባከኑ) መቁጠር ይቻላል። በዓመት አስሉትማ!

ዛሬን እየኖሩ ስለነገ ስርዓት መያዝ መጨነቅ ይቻላል?

እኛ ሰፈር ጠዋት፣ ጠዋት ከወትሮው የከፋ የታክሲ እጥረትና ትርምስ ካለ፥ ትራፊክ ፖሊስ በአካባቢው አለ ማለት ነው። ታክሲዎቹ ትርፍ ሰው የሚጭኑት ትራፊክ ፖሊስ ሳይኖር ብቻ በመሆኑ የሥራ ሰዓት እና ቀጠሮ የረፈደበት ሰው ትራፊክ  ፖሊሶቹን ሲያይ እንደስርዓት አስከባሪ ሳይሆን እንደ ችግር ፈጣሪ ባይመለከታቸው ይገርማል።

ጠዋትና ማታ (የሥራ መውጫና መግቢያ ሰዓቶች ላይ) የትራንስፖርት አማራጮቹ አቅም ከትራንስፖርት ፈላጊዎቹ ቁጥርጋ አይጣጣምም። ስለዚህ ምንም እንኳን ለትራንስፖርት ዘርፉ ስርዓት መያዝ ሲባል የትራፊክ ሕግጋቱን ማክበር አስፈላጊ ቢሆንም ዛሬን ለመኖር ሲባል አገልግሎት  ጪዎቹም ሆኑ ተገልጋዮቹ ተባብረው ስርዓቱን ይጥሳሉ። ስርዓቱን የመጣሱ ነገር ወደባሕልነት ሊያድግ የሚችል  መሆኑ አሁን የሚያስጨንቀው ሰው የለም።

“200 ሺሕ ብር ያለው ሰው የሚያሾረው ኢንደስትሪ”

አንድ እሁድ ከምሽቱ 2:30 ላይ ቦሌ ቆሜ የአራት ኪሎ ታክሲ እየጠበቅኩ ነበር። ያለወትሮው አካባቢው በጊዜ ጭር አለብኝ። ታክሲ ያገኘሁት ከአንድ ሰዓት ጥበቃ በኋላ ነበር — ያውም አቆራርጬ! አራት ኪሎን ስሄድ ያው ሆነብኝ። ከዚያ እንደኔው ታክሲ የቸገረው መንገደኛ ምስጢሩን ነገረኝ —  “ዛሬ እኮ ማንቼ ደርቢ ስላለበት ነው” በማለት። ለካስ የታክሲ ሾፌሮችና ረዳቶች ኳስ ለማየት ሥራ በጊዜ እየጨረሱ ገብተው ነው። ይሄኔ ነበር አንድ ወዳጄ ሁሌም የሚናገራት ነገር ትዝ ያለችኝ፤ “ሁለት መቶ ሺሕ ብር ያለው ሰው የሚቆጣጠረው የትራንስፖርት ኢንደስትሪ”።

ግለሰቦች የየራሳቸውን ታክሲ እየገዙ እንደፈለጉ ይሠሩበታል ካልፈለጉ ሥራ ያስፈቱታል። የገዛ ንብረታቸው ስለሆነ መብታቸው ነው።  ችግሩ በዘርፉ ስርዓት ያላቸው ማኅበራት እንዲኖሩ መንግሥታዊ ማበረታቻም ሆነ ግልጽ አቅጣጫ አለመኖሩ ነው። አሊያንስ ባስ ሥራ ሲጀምር ደስ ያለኝ በዚያ ተስፋ ነው። ቢያንስ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሳቢያ አገልግሎቱ አይቋረጥም።

ስርዓቱን በየቀኑ እየተደባደቡ/እየተደበደቡ ማስከበር ይቻላል?

የአዲስ አበባ ትራፊክ ጽ/ቤት ሁሉም ታክሲዎች የሚንቀሳቀሱበትን አካባቢ ታሪፍ በይፋ እንዲለጥፉ የሚያዝ መመሪያ አለው። ባለታክሲዎቹ ግን አይተገብሩትም።

ለምሳሌ ከአራት ኪሎ አምባሳደር እና መልስ ዋጋው በመመሪያው መሰረት ዕኩል 1·35 ቢሆንም ስንመለስ ዳገት ነው በሚል ባለታክሲዎቹ 2·70 ይጠይቃሉ። አንድ ተሳፋሪ ‘የለም ዋጋው ይሄ አይደለም፣ አልከፍልም’ ካለ ያለው ዕድል ሁለት ነው፤ ወይ ወርዶ በእግር መሄድ አሊያም መደባደብ። መደባደብ ውስጥ መደብደብም አለ። ለአንድ ቀን አይደለም፣ በየቀኑ።

አንዳንዶች የተሳፋሪውን ተባብሮ አለማደም ተጠያቂ ያደርጋሉ። ስንት ዓይነት ተሳፋሪ አለ? ስንት አንገብጋቢ ጉዳይ ያለበት አለ? ዛሬ ብቻ የመጣ አለ? በየሄደበት በታክሲዎች ለማደም እየተባበረ ዕድሜና ግዜውን ሊያባክን አይችልም። ሁሉም ሰው ብዙ ኑሮ አለበት። ይህንን ስርዓት ለማስከበር ደሞዝ የሚከፈላቸው የምር፣ ለሕዝቡ በሚበጅ መልኩ ማስከበር አለባቸው።
ስርዓቱን ለማስከበር ስርዓቱ የሚፈልገውን ሟሟላትም ያስፈልጋል። በርካታ የሕዝብ ማመላለሻ አማራጮች፣ የባቡርም ይሁን አውራ ጎዳና ግንባታ/እድሳት ገድሎ የማይገድለው አማራጭ መንገድ፣… ከልብ  መታሰብ አለበት። ምክንያቱም በመሐል ቤት ዜጎች እየተጨፈለቁ ነው።

መስከረም ፳፫(ሃያ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፓርቲዎቹ ባወጡት መግለጫ የሶስት ወር ሕዝባዊ ንቅናቄችን ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር በመሆን በአዲስ አበባ ለማጠናቀቅ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የከንቲባው ጽ/ቤት መስከረም 3 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም ሠላማዊ ሠልፉን በመስከረም 19 ቀን ማድረግ እንደምንችል  የሚገልፅ የዕውቅና ደብባቤ ቢሰጠንም ፣  በእጅ አዙር ሠልፉን በመስቀል አደባባይ እንዳናደርግ ከመከልከሉም በላይ ከሕግ ውጨ በመከላከያ በፀጥታ ተቋማት …

መስከረም ፳፫(ሃያ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በአብዛኛው የኤርትራንና የሶማሊያን ዜጎች ከጣሊያን በመጫን ወደ አውሮፓ በማቅናት ላይ የነበረችው ጀልባ ላምፔዱሳ በሚባለው የጣሊያን ደሴት አካባቢ ስትደርስ በመስጠሙዋ በውስጧ ከተሳፈሩት መካከል ከ130 በላይ የሚሆኑት መሞታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽነር አስታውቋል። እስካሁን 150 ሰዎችን ለማትረፍ የተቻለ ሲሆን፣ የ130 ሰዎች አስከሬን ደግሞ በወደብ ሰራተኞች  ተሰብስቧል። ጀልባዋ 500 …

መስከረም ፳፫(ሃያ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ መለስ በስልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት  ብዙ ስራዎችን መሸከማቸው አፈጻጸም ላይ ድክመት ማምጣቱን በመገምገም የማሻሻያ እርምጃ መወሰዱን  ምክትል ጠ/ሚኒስትርና የኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበር   አቶ ደመቀ መኮንን አስታወቁ፡፡ አቶ ደመቀ ከመንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉትና ትላንትናና ዛሬ ታትሞ በወጣው ቃለምልልሳቸው ላይ አቶ መለስ ብዙ ስራዎችን መሸከማቸው አንዳንድ ዘርፎችን …

መስከረም ፳፫(ሃያ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፖሊዩ ቫይረስ በተከሰተበት አካባቢ ሳይታወቅ ጉደት አድርሶዋል፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናት በበሺታው መጠቃታቸውን በሚኒስቴሩ የእናቶችና ህጻናት ጤና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ በቀለ ለጋዜጠኖች ተናግረዋል፡፡ በሐገራችን ኢትዩጵያ እና አጎራባች አገሮች የተከሰተውን የፖሊዮ በሽታ ወረርሽኝ ለመከላከል በአገር አቀፍ ደረጃ እድሜያቸው ከ5 አመት በታች ለሆኑ ህጻናት የፖሊዩ ቫይረስ መከላከያ ክትባት መስጠት አስፈላጊ …

የመስተዳድሩን ፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት የጠቀሱ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት የከተማይቱን እቅድ ማሸጋሸግ ያስፈለገው ከፌደራሉ የእድገት እና ለውጥ (ትራንስፎርሜሽን) እቅድ ጋር ለማጣጣም ነው ተብሏል።

የአደጋ ደራሽ ሰራተኞች ካገኙት 82 አስክሪን መካከል በርካታ ሴቶች እና ሁለት ህጻናት ይገኙበታል። እንደ ከተማዋ ከንቲባ የጀልባዋ ተሳፋሪዎች ዛሪ ማለዳ በጀልባዋ ዋ ላይ ሳሉ እሳት ከተነሳ በኋላ፤ ለብዙ ሰዓታት ባህሩ ዉስጥ ነበሩ።አብዛኞቹ ተሳፋሪዎች ከኤርትራ እና ከሶማልያ እንደሆኑ ፖሊስ ተናግሯል።

(ከወልደሚካኤል መሸሻ)

ውድ አንባቢያን ይህን ጽሑፍ ጀምሬ ያጠናቀቅሁት ወደ እ . ኤ. አ በ2012 መጀመሪያ ነው። ለምን እስከአሁን አቆየኸው? የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀሬ ነው ታዲያ። ተገቢ ጥያቄ ነው። የተለያዩ አቅጣጫዎችን የማየትና የማሰላሰል ሁኔታ በአንድ በኩል፣ በሌላ ደግሞ በአነሰኛ መጽሐፍ መልክ ባሳትመውስ የሚል አሳብ እየተደቀነብኝ መጥቶ ነው። ሁለቱም ተራ በተራ ተፈታተኑኝ። የትኛውን እንደምመርጥ ማውጣት ማውረዱን ቀጠልሁ። ጽሑፍን እንድያዩትና አሳባቸውን እንዲሰጡኝ ለጥቂት ወዳጆቼ ላክሁ። አንዳንዶቹ ቶሎ ጽሑፉ እንዲወጣ የሚገፋፋ አሳብ ሰጡኝ። አንዳንዶች ከማስጠበቅ ውጭ ላያልፉ ሆኑ። በዚህ ላይ እያለሁ ለጽሑፉ መሠረት የሆነው የእምዬ ጠላት በመርዘኛ ብዕሩ ብቅ ማለቱን ሰማሁ። ወዳጆቹ ከወዲህ ወዲያ እያሉ መሆኑንም አዳመጥሁ። እርሱም የእምዬ ልጆችን የማባላቱን ሥራ ማጠናቀቁን ከወብሳይቱ ተመለከትሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በዛሬዋ ቱርክ ኢያዞሎክ፣ በጥንታዊቷ የኤፌሶን ከተማ ተገኝቶ ነበር፡፡ በዚህች ከተማ እጅግ የታወቀች፣ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች አማንያን የሚጎርፉላት፣ ምስሏን የሚሠሩ አንጥረኞች ብር በቁና የሚያተርፉባት አርጤምስ የምትባል ጣዖት ትመለክ ነበር፡፡ ጳውሎስ እዚህ ከተማ ገብቶ ወደ አርጤምስ ቤተ መቅደስ በመጓዝ ‹‹አርጤምስ አምላክ አይደለችም›› ብሎ አስተማረ፡፡

ይህን ሲሰሙ የአርጤምስ ወዳጆች፣ ምስሏን በመሥራት የሚያተርፉት አንጥረኞችና፣ አርጤምስን ለመሳለም ከሚመጡ አማኞች ጠቀም ያለ ትርፍ የሚያገኙ ነጋዴዎች በከተማዋ ሑከት አስነሡ፡፡ ከተማዋ ተደበላለቀች፡፡ ከየአቅጣጫው ሕዝቡ ወደ ቤተ መቅደሱ አደባባይ ጎረፈ፡፡ የሐዋርያት ሥራ እንዲህ ይላል፡፡ ‹‹ብዙዎች ወዲያና ወዲህ እያሉ ይጮኻሉ፡፡ በጉባኤው ድብልቅልቅ ሆኖ፣ የሚበልጡት ስለምን እንደተሰበሰቡ እንኳን አያውቁም ነበር፡፡››

አርጤምሳዊነት ባልተረዱት፣ ምስክርነት በማይሰጡበት፣ በማያውቁት ጉዳይ ላይ ሌሎች ስላደረጉት ብቻ፣ ወይም ደግሞ ሕዝቡ ሁሉ ሲያከናውነው ስለታየ ብቻ መደገፍ ወይም መቃወም፣ ወይም ያንኑ መሥራት ማለት ነው፡፡ የሚሰበሰቡበትን ምክንያት ሳያውቁ መሰብሰብ፣ የሚደግፉበትን ምክንያት ሳያውቁ መደገፍ፣ የሚቃወሙበትን ምክንያት ሳያውቁት መደገፍ፣ የሚወዱበት ምክንያት ሳይኖር መውደድ፣ የሚጠሉበትንም ምክንያት ሳይረዱት መጥላት ነው፡፡

ለምን? ሲባል ‹‹እኔ ከሰው እለያለሁ እንዴ›፣ ሰው ሁሉ እንዲህ እያደረገኮ ነው፣ መቼም አንድ ምክንያት አይጠፋም ብዬ፣ እነ እገሌ ሲሄዱ ሄድኩ፣ ዝም ብሎ ያስጠላኛል፣ እንዲሁ ጥሎብኝ እወደዋለሁ፤ ከሰው ጋር ሲኖሩ ሞኝ ሆኖ፣ አህያ ሲጭኑ ሦስት ሆኖ ስለሚባል፣ እየተባለ ዝም ብሎ መደገፍና መቃወም ነው አርጤምሳዊነት፡፡

መመሪያ ስለሆነ፣ አድርጉ ስለተባልን፣ አሠራር ነው፣ የተለመደ ነው፣ በኛ ጊዜ አልተጀመረም፣ ድሮም የነበረ ነው፣ ምን ይደረግ ታዝዘን ነው፣ እኔ ከማን እበልጣለሁ፣ እኔ ከማን አንሣለሁ፣ ከበላይ የመጣ ነው፣ ውጡ ስለተባልን ነው፣ የሚሉ ነገሮችን የምትሰሙባቸው መሥሪያ ቤቶች ካሉ እነዚህ መሥሪያ ቤቶች በአርጤምሳውያን የሚመሩ ወይም የተሞሉ ናቸው ማለት ነው፡፡ ይፈርማሉ፤ ለምን? ማብራራት አይችሉም፤ ይሰበሰባሉ፤ ለምን ተሰበሰባችሁ? ሳትሰበሰቡ ማድረግ አትችሉም ነበር ወይ? ሲባሉ ምክንያት ያለው መልስ የላቸውም፡፡ ይውደም ይላሉ፤ ማንን እንደሆነ አያውቁትም፡፡ ይቅደም ይላሉ ማን እንደሚቀድም ግን አልወሰኑም፡፡

አንዳንዶች ጓደኞቻቸው ያደረጉት፣ የተከተሉት፣ ያወሩት፣ የወደዱት፣ የጠሉት፣ የደገፉት፣ የተቃወሙት ሁሉ ትክክል ነው ብለው ያምናሉ፡፡ አመክንዮ የላቸውም፡፡ የተደረገውን ከመድገም በቀር፡፡ ከዚህም አልፈው ከራሳቸው አእምሮ ይልቅ በሰው አእምሮ ያስባሉ፡፡ ሌላውን ሰው መከተል እንጂ የት ይወስደኛል፣ ለምን አከተለዋለሁ፣ ትክክል ነው ወይ? እኔ የተሻለ ሃሳብ የለኝም ወይ? ብለው አይጠይቁም፡፡ እንዲሁ ይከተላሉ፡፡

አርጤምሳውያን ሰውን እንጂ ሃሳብን አይከተሉም፡፡ ሰውን እንጂ ሃሳብን አይቃወሙም፡፡ ለእነርሱ ቁም ነገሩ እነማን አሉበት? የሚለው እንጂ ምን ነገር አለበት? የሚለው አይደለም፡፡ አንድ ጊዜ አንድ ድልድይ ላይ ብዙ ሰዎች ተሰብስበዋል፡፡ ተሰብስበውም ወደ ድልድዩ ሥር ይመለከታሉ፡፡ እኔ ማዶ ቆሜያለሁ፡፡ ቀስ በቀስ ድልድዩ ላይ ቆመው የሚመለከቱት ሰዎች ቁጥራቸው እየበዛ መጣ፡፡ በኋላም በድልድዩ ላይ መኪና ማለፍ እስኪያቅተው ድረስ በሰው ተሞላ፡፡የምጠብቀው መኪና መጣልኝና በድልድዩ ላይ ለማለፍ ከሌሎች መኪኖች ኋላ ወረፋ ያዝን፡፡ መኪኖቹ በሕዝብ በተጣበበው ድልድይ ላይ እንደ ዔሊ እየተንፏቀቁ ነበር የሚጓዙት፡፡ እንዳጋጣሚ ሆኖ ነገሩ ሲጀመር አካባቢ ድልድዩ ላይ ያየሁትን ሰው አገኘሁትና የመስኮቱን መስተዋት አውርጄ ‹‹ምንድን ነው ጉዳዩ?›› ብዬ ጠየቅኩት፡፡

እጁን ኪሱ ውስጥ ከትቶ ትከሻውን እያራገፈ ‹‹የሆነ ነገር ሳይገባ አይቀርም›› አለኝ፡፡

‹‹አንተ አላየኸውም›› አልኩት፡፡

‹‹አላየሁትም፤ አንዳንዶች ከብት ነው ይላሉ፣ ሌሎቹ ደግሞ ሰው ነው ይላሉ›› አለኝ፡፡

‹‹አንተ ምን ትላለህ›› አልኩት

‹‹እኔ እንጃ›› አለ፡፡

‹‹ይህንን ካላጣራህ ታድያ ለምን መጣህ››  አልኩት

‹‹ሰው ሲሰበሰብ ጊዜ ዝም ብዬ ነው የመጣሁት›› አለኝ፡፡

ቢያንስ ከሠላሳ ደቂቃ በላይ ቆሟል፡፡ እንዲህ ሰው ሳይጨናነቅ ነበር የመጣው፡፡ የመጣበትን ምክንያት ግን አያውቀውም፡፡ ሰው ተሰበሰበ፣ እርሱም አብሮ ተሰበሰበ፡፡ ሰው ወደ ድልድዩ ሥር ያያል፤ እርሱም ያያል፡፡ ምን እንደሚያይ ግን አያውቅም፡፡ ብቻ ያያል፡፡ አርጤምሳዊ፡፡

አርጤምሳውያን ነገሩ ሳያስቃቸው ነው የሚስቁት፡፡ የተሰበሰበው ሰው ከሳቀ ይስቃሉ፡፡ ቀልዱ ግን ላይገባቸው ይችላል፡፡ ባይገባቸውም ያጨበጭባሉ፡፡ ከዐዋቂ መካከል ከተቀመጡም ራስ ሲነቀነቅ ሲያዩ ይነቀንቃሉ፡፡ የሆነ ወረቀት ሲታደል ካገኙ ይቀበላሉ፤ ግን አያነቡትም፡፡ ማስተዋሻ ሲሰጥ ካዩ ተስገብግበው ይወስዳሉ፤ ግን አይጽፉበትም፡፡ የሆነ ምዝገባ ነገር ከተመለከቱ ወደ ሲኦል ለመሄድ ቢሆን እንኳን አያጣሩም፤ ብቻ ይመዘገባሉ፡፡ የሆነ ኮሚቴ፣ ማኅበር፣ ቡድን ሲመሠረት ዘለው ይገባሉ፤ ዓላማው፣ አሠራሩ፣ ማንነቱ አይመለከታቸውም፡፡ ዓላማቸው መቀላቀል ብቻ ነው፡፡

ኢሜይል አላቸው፣ የሚገናኙት ሰው የለም፤ ፌስ ቡክ አላቸው የሚለጥፉት ነገር የለም፡፡ ትዊተር አላቸው፣ የሚያስተላልፉት ነገር የለም፡፡ በሞባይላቸው ይቀዳሉ፣ እነርሱስ ከማን ያንሳሉ፡፡ ግን የቀዱትን አያዳምጡትም፡፡ እንዲያውም በቀጣዩ ደምስሰው ሌላ ይቀዱበታል፡፡ በሞባይል ፎቶ ያነሣሉ፤ ደግመው ግን አያዩትም፡፡ አርጤምሳውያን፡፡

አርጤምሳውያን ቤት የሚገዙት፣ መኪና የሚገዙት፣ ድርጅት የሚከፍቱት፣ ልብስ የሚገዙት፣ ውጭ የሚሄዱት፣ ርዳታ የሚረዱት፣ ድግስ የሚደግሱት፣ ሞባይል የሚቀይሩት፣ ምክንያት ስላላቸው አይደለም፡፡ እገሌ ስላደረገው፣ የዘመኑ ፋሽን ስለሆነ፣ ሰው እጅ ላይ ስላዩት፣ የሆነ ሰው ሲያወራለት ስለሰሙ ብቻ ነው፡፡  

አንድ ሰው መንገድ ዳር ቆሞ ይለምናል፡፡ ‹‹አግኝቼ ያጣሁ ነኝ›› ይላል ደጋግሞ፡፡ ከሚያልፉት መንገደኞች አንዱ ጠጋ አለውና ‹‹እውነት አንተ አግኝተህ ያጣህ ነህ?›› ሲል ጠየቀው፡፡ ይለምን የነበረው ሰውም ‹አዎ›› ሲል መለሰ፡፡ መንገደኛውም ‹‹ለመሆኑ ከዶሮ ብልቶች በጣም ጣፋጩ ምንድን ነው?›› ሲል ጠየቀው፡፡ ሲለምን የነበረው ሰውም ‹‹ቆዳው›› ሲል መለሰለት፡፡ መንገደኛው ሰው ‹‹እውነትም አንተ አግኝተህ ያጣህ ነህ›› ብሎ ጠቀም ያለ ገንዘብ ሰጠው፡፡

ከጎኑ ቆሞ ሲያይ የነበረ አንድ ሰው ቀበል አደረገና ‹‹አግኝቼ ያጣሁ›› ማለት ጀመረ፡፡ 
ሌላ መንገደኛም ጠጋ ብሎ ‹‹አግኝተህ ያጣህ ከሆንክ ከበግ ሥጋ የሚጣፍጠው ምንድን ነው›› ሲል ጠየቀው

‹‹ቆዳ›› አለ አሉ፡፡

  © ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የወጣ ነው

ሊብያ ውስጥ የሚገኙ ከአምስት መቶ ሃምሣ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራዊያን ስደተኞች ሰሃራ በረሃ ውስጥ በሚገኝ እሥር ቤት መታጎራቸውንና እንግልት እንደሚደርስባቸው በመግለፅ አማርረዋል፡፡