በኢትዮጵያ ተወልደው፣ በ 3 ዓመታቸው እሥራኤል በመግባት ፤ በዚያ ያደጉ የተማሩና የፓርላማ (ክኔሰት) አባል የሆኑት ፔኒና ታማኖ-ሻታ የተባሉት የ 32 ዓመት ወ/ሮ ፣ ከትናንት በስቲያ ደም ለመለገሥ ተዘጋጅተው ፤ በጤና ጥበቃ ሚንስቴር መመሪያ

የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ ትላንት አዲስ ጠ/ሚ መሰየማቸው ተዘገበ። ፕሬዝደንት መሐሙድ የቀድሞውን ጠ/ሚ ካባረሩ ሳምንታት ቢቆጠሩም ጠ/ሚ ሺርዶን ግን ኣሻፈረኝ ብለው ቆይተው ነበር። የሶማሊያው ም/ቤት የመተማመኛ ድምጽ ከነፈጋቸው በኃላ ግን ሺርዶን ስልጣን መልቀቃቸው ታውቐል።

የስፖርት አዋቂዎች እንደሚሉት ማንዴላ ከዓለማችን ፖለቲከኞችና የመብት ተሟጋቾች በተለየ ስፖርትን በሰላም መሣሪያነት ተጠቅመዋል ። ለስፖርት ትልቅ ቦታ ይሰጡ የነበሩት ማንዴላ በተለያዩ ዓለም ዓቀፍ የስፖርት ተቋማትና በስፖርት ዓዋቂዎች ዘንድ ትልቅ ከበሬታ አላቸው ።

የኢትዮጵያ መንግሥት ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሰላማዊ ትግል መንገድ እየተዘጋ ነዉ አለ፦ ህዝቡን ወደ ትጥቅ ትግል እንዳይወስድ እንደሚሰጋ አስጠነቀቀም።

ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ነጻነት ለሀገሬ)
ኔልሰን ማንዴላ Nelson Mandela
ኔልሰን ሮሺስላሽላ ማንዴላ ለነጻነት የሚያደርጉትን ረዥሙን ጉዞ እ.ኤ.አ በ2013 መገባደጃ ወር ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ደመደሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ …

ታህሳስ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :- በሽብር ወንጀል ተከሰው በእስር ላይ የሚገኙት የድምጻችን ይሰማ መሪዎች ተከላከሉ መባላቸውን ጠበቃ  ተማም አባ ቡልጉ ተናግረዋል። 12 ሰዎች በነጻ የተለቀቁ ሲሆን፣ እነ አቶ አቡበከር አህመድና ሌሎች ደግሞ በተከሰሱበት ሽብር የማድረግ ወንጀል ሳይሆን ሽብር በማነሳሳት ጉዳይ ላይ እንዲካለከሉ ተበይኖአል። ሙራድ ሹኩር ጀማል፣  ኑሩ ቱርኪ  ኑሩ፣ ሼህ ባህሩ ኡመር ሸኩር …

ታህሳስ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :- የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ መድረክ  ዓርብ ታህሳስ 4 ቀን 2006 ዓ.ም በአገሪቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰጥ ሲሆን፣  ዶ/ር መረራ ጉዲና ለኢሳት እንደገለጹት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው አፈና እየተባባሰ መሄዱ መግለጫውን ለመስጠት አስገድዷቸዋል። የሳውድ አረቢያ መንግስት በኢትዮጵያውያን ላይ የወሰደውን እርምጃ ለመቃወም መድረክ ቢጠይቅም በገዢው ፓርቲ መከልከሉን ዶ/ር መረራ አውስተዋል …

ታህሳስ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :- የቀድሞ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ዋና ዳሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ ክሳቸው በየትኛው ፍርድ ቤት ይታይ በሚለው ጉዳይ ላይ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የመጨረሻ ውሳኔውን እንዲያሳውቅ ሲል የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ትእዛዝ በመስጠት ለታህሳስ 22 ቀን 2006 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ። ፍ/ቤቱ ቀደም ሲል በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ጉዳዩን …

ታህሳስ ፫(ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :- ማክሰኞ በደቡብ አፍሪካ ስዌቶ በተደረገው የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት የኔልሰን ማንዴላ መታሰቢያ  ከመድረክ ይተላለፍ የነበረውን ዝግጅት በምልክት ቋንቋ መስማት ለተሳናቸው ዜጎች እንዲያስተላልፍ  ተመድቦ የነበረው  ሰው፤ ያሳይ የነበረው አካላዊ እንቅስቃሴና ምልክት የውሸት እንደነበር መጋለጡን ዓለማቀፍ ብዙሀን መገናኛ እየዘገቡ ነው። ድርጊቱ የደቡብ አፍሪካን መንግስትና በ ዓለማቀፍ ደረጃም መስማት የተሳናቸውን የህብረተሰብ …

የሳውዲ አረቢያ መንግስት ህገወጥ ስደተኞች ያላቸውን የውጪ ዜጎች ከኣገሩ ለማስወጣት በጀመረው መጠነ ሰፊ ዘመቻ አኩዋያ የኢትዮጵያ መንግስትም 30 000 ያህል ዜጎችን ወደ ኣገራቸው ለመመለስ መገደዱን ባለፈው ወር ማስታወቁ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በአሸባሪነት ጥርጣሬ ካሰራቸዉ የኢትዮጵያ የሙስሊሞች ጉዳይ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ መሪዎች፥ አባላትና ተባባሪዎች መካካል አስራ-ሁለቱ በነፃ እንዲለቀቁ ተወሰነ።

ከግማሽ ም/ዓመት በፊት አንጋፋው የደቡብ ኣፍሪካ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ኢትዮጵያ ውስጥ ስልጠና ላይ በነበሩበት ወቅት የተቃጣባቸውን የግድያ ሙከራ ያከሸፉት ኢትዮጵያዊ ወታደር በቀብራቸው ለመገኘት እያሰቡ ነው።

ኬንያ የምሥራቅ አፍሪቃ የዕድገትና መረጋጋት ሞተር መሆኗ ነው የሚነገርላት።ፕሬዚዳንት ዑሑሩ ኬንያታና ምክትላቸው ዊልያም ሩቶ በሄግ ፤ ኔዘርላንድስ ዓለም አቀፍ የጦር ወንጀለኞች መርማሪ ፍርድ ቤት፤ ቢከሰሱም፤ አገራቸው፤ እ ጎ አ በ 2010 አዲስ

የኢትዮጵያዉ የመስቀል በዓል አከባበር በተባበሩት መንግስታት የሳይንስ የትምህርትና ባህል ማዕከል /UNESCO/መዝገብ በዓለም ቅርስነት ተመዝግቦአል። የዚህ ክብረ በዓል በዓለም መዝገብ መፃፉ ለኢትዮጵያ የሚያመጣዉ ፋይዳ ምን ይሆን? ኢትዮጵያ እስከ ዛሪ ዘጠኝ ታሪካዊ ቅርሶችን በ UNESCO መዝገብ በማፃፍ ከአፍሪቃ ቀዳሚዋ ሀገር መሆንዋ ያዉቃሉ?

አዲስ አበባ እና ዋሽንግተን ዲሲ እህትማማች ከተሞች ሆኑ። ሁለቱ ከተሞች ይህን የሚ,ለከተውን ስምምነት ትናንት በዩ ኤስ አሜሪካ የዋሽንግተን ዲሲ ከተማ ተፈራርመዋል። ስምምነቱ የኤኮኖሚ፣ የትምህርት እና የልማቱን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክር ፣ የልምድ ልውውጥ እንዲኖር የሚያደርግ መሆኑ ተገልጾዋል።

መንግስት በኢትዬጲያ ሙስሊሞች ላይ የጥፋተኘነት ውሳኔ ማስተላለፉን ምንጮች አስታወቁ፡፡ ለታህሳስ 3 በተቀጠረው የብይን ቀነ ቀጠሮ መሰረት 10 ተከሳሾችን ነፃ ናቸው ሲል ፍርድ ቤቱ ያሰናበተ ሲሆን የተቀሩት ላይ ግን በሽብር ድርጊት ፈፃሚነት ወንጀል ጥፋተኛ ናችሁ ሲል ብይን አስተላልፏል፡፡ በዚህም መሰረት ሁሉም በዕድሜ የገፉት አባቶች ዶ/ር ከማል ገለቱ፣ሼህ አብዱረህማን፣ሼህ ሃጂ ኢብራሂም፣ ሼህ ጣሂር፣.ሼህ ሱልጣን አማን፣ ኡስታዝ ጀማል […]


There are about eight journalists and media related associations in Ethiopia. None of them, however, have been heard speaking out for either jailed or exiled journalists. Ethiopia is one of the highest jailor of journalists (CPJ, names it 2nd where as Addis Standard, a local media, named it 3rdin its December issue). According to Article 19, twelve Ethiopian journalists are prosecuted in “relation to terrorism”. On the other hand, one of the famous “journalists association” – Ethiopian National Journalists Union (ENJU – IFJ member) president, Anteneh Abrham told Ethiopian Radio and Television Agency that he feels proud that Ethiopia hasn’t jailed any journalist for what s/he has written.

The Press Release (Amharic)
It is in this time of desperation a committee of eight independent journalists initiated a formation of a new “Ethiopian Journalists Forum (EJF)”. The committee called for ‘founding meeting’ today, Dec 12/2013 at Ethiopian Hotel where more than 20 journalists attended. 

The committee, in its presser, mentioned that ‘the Forum under-formation will independently work to support and upgrade the professionalism of journalists in particular and the media in general’.  It also added that its goals include working:

  1. for the respect of Freedom of Expression granted in the FDRE constitution article 30;
  2. for the benefit of journalists;
  3. for promoting professional excellence of journalists through trainings;
  4. for strengthening the relationship/communication among journalists;
  5.  for facilitation of financial, material and legal support whenever needed;
  6. for recognizing journalists who are contributing positively to the sector;
The committee, in its response to questions raised by attendants of the meeting expressed that it recognizes the challenge (jailing and exiling) of journalists and the ‘Forum’ aims to elevate it – and this has been mentioned as a major point that distinguishes the new ‘Forum’ from other existing ‘Journalists Associations’.

Before the conclusion of the meeting, Journalist Ayalew Asres (from the now defunct Negadras newspaper) gave the following comments so that the committee should consider before it calls for general assembly:

  • The term ‘Forum’ might be confusing with a political coalition that is referred by the same term – Forum;
  • The committee should not be called ‘founding’ but ‘coordinating’ as it is working to coordinate;
  • Working for the respect of ‘Freedom of Expression’ should not be the role of the ‘Forum’ rather practicing it;

With this, the committee concluded the meeting inviting journalists, bloggers and other stakeholders to join the effort to establish the ‘Forum’ officially as soon as possible.

ከጥቂት ሳምንታት በፊት ነው፤ አምስት ኢትዮጵያውያን ሰብሰብ ብለን እራት እየበላን ነበር፡፡ አንደኛው በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ‹‹ነጻ›› የጋዜጠኞች ማኅበራት የአንዱ ፕሬዚደንት ነው፡፡ በጨዋታችን መሐል የተናገረው ነገር ሁላችንንም አስደነገጠን፡፡ በዚህ ዘመን እንዲህ የሚያምን “ዘመነኛ” ሰው አለ እንዴ!?

ሰውዬው ያወራልን ሌሊት ወደጅብነት ስለሚለወጡ ሰዎች ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ሁላችንም አፍረን ስናፈገፍግ ከመሐላችን አንዱ “እንዲህ ዓይነት ነገር እውነት ነው ብለህ ታምናለህ?” ብሎ ጠየቀው፡፡ እሱ ሆዬ በሙሉ መተማመን እኛን እንዳላዋቂ በመቁጠር ሌሊት ወደጅብነት የሚለወጡ ሰዎች እንዳሉ ያስረዳን ጀመር፡፡

ይህንን ትዝታዬን የቀሰቀሰው ትላንት ጋዜጠኛ Masresha Mammo የጻፈው ማስታወሻ ነው፡፡ ርዕሰ ጉዳዩ የተለየ ስለነበር እኔ ግን ለዚህች ጽሑፌ የሚጠቅመኝን ገንጥዬ አጣቅሳለሁ፡፡ ማስረሻ እንዲህ ይላል፤

‹‹…ተወልጄ ያደግኹት ከእንጦጦ ተራራ ስር ቀጨኔ በምትባል ሰፈር ውስጥ ነው፡፡ […] ቀጨኔ ላይ ያለው ማኅበረሰብ ወደአዲስ አበባ የተሰደደው የተሻለ ኑሮ ፍለጋ ሲል አልነበረም፡፡ ቡዳ ነው የሚል ስም ስለተለጠፈበት ‹ልጆቻችንን በልተው ጨረሷቸው› በሚል ግድያው ስለበዛበት ነበር፡፡ አንድ ቀጥቃጭ አባቱ፣ ወይም ሸማኔ ወንድሙ፣ አሊያም ሸክለኛ እናቱ በዚሁ ሰበብ ሲገደሉበት፤ በምላሹ እሱም ደሙን ተወጥቶ ይሸሻል፡፡ ይሰደዳል፡፡…
‹‹ይኼ ማኅበረሰብ ለሺሕ ዓመታት ለኢትዮጵያ ሕዝብ የጀርባ አጥንት ኾኖ ቆይቷል፡፡ በቴክኖሎጂ ላልሰለጠነችው ኢትዮጵያ ማረሻ እና ወገል ያቀርባል፣ እንዳይበርዳቸው ልብስ ይሠራላቸዋል፣ ለመመገቢያቸው የሚኾኑትን ሸክላዎች እና የዕደ ጥበብ ውጤቶች ሁሉ ይሰጣቸዋል፡፡ ያለዚህ ማኅበረሰብ ኢትዮጵያን ወደኋላ ዞር ብላችኹ አስቧት፡፡ [ማኅበረሰቡ] በሚኖርባት በየትኛውም የአገሪቱ ክልል ግን ስሙ ቡዳ ነው፡፡

‹‹ቡዳ ማለት ደግሞ፤ ቀን ቀን ጋቢ ለብሶ የሚኖር፣ ማታ ማታ ወደ ጅብነት የሚቀየር ማለት ነው፡፡ ይህ አስተሳሰብ እና አመለካከት የሚመራው በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ውስጥ ነበር፡፡…››

ማስረሻ ‹‹ነበር›› ይበል እንጂ ዛሬም ድረስ ከዚህ ባልተለየ መንገድ የሚያምኑ ‹‹ምሁራን›› ሳይቀሩ አሉ፡፡ ልዩነቱ በዚህ ዘመን በተለይ በከተማ እንዳይገዳደሉ ሕግ ያግዳቸዋል፤ በገጠር ግን አሁንም በግልጽ አለ፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት የሄድኩበት የገጠር አካባቢ ውስጥ ካሉ ‹‹ቡዳ›› ወይም ‹‹ባለእጅ›› ከሚባሉ ሰዎች/ቤተሰብ አባላት ጋር እንዳልገናኝ እና ‹‹ዓይናቸው እንዳልገባ›› አብረውኝ ያሉ ሰዎች ሲጠብቁኝ እና ሲያከላክሉኝ ነበር፡፡ ዛሬም እናቴን ብቻ ሳይሆን ወጣት ጓደኞቼን ሳይቀር ቡዳ የሚባል ነገር የለም ብዬ ማሳመን ይከብደኛል፡፡

ይህ ሰዎችን የማግለያ ሰበብ ነው፡፡ ሰዎችን ንዑስ-ሰው አድርጎ የመቁጠር አባዜ ነው፡፡ የሰብኣዊ መብት ዋና ፅንሰ ሐሳቡ ደግሞ ሰዎች ሁሉ ዕኩል ናቸው የሚለው ነው፡፡ ያንን የማያምኑ ሰዎች ባሉበት አገር በመንግሥት ጥረት ብቻ ሰብኣዊ መብት አይከበርም፡፡
— 
እዚህ ጽሑፍ ላይ የተሰጡ ለማየት እዚህ ጠቅ ያድርጉ!

የዛሬ 600 ዓመት አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የተባለ ኢትዮጵያዊ ደራሲ ‹አርጋኖን› የተሰኘ መጽሐፍ ይደርሳል፡፡ ይህንን መጽሐፍ የተመለከቱ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንትም እጅግ ያደንቁና ለንጉሡ ለዐፄ ዳዊት ያቀርባሉ፡፡ ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም መጽሐፉን ተመልክተው በማድነቅ በወርቅ ቀለም እንዲጻፍ አዘዙ፡፡ አባ ጊዮርጊስንም ሸለሙ፡፡ ከተወሰነ ጊዜ በኋላም አባ ጊዮርጊስ ‹መጽሐፈ ምሥጢር› የተባለ መጽሐፍ ደረሰ፡፡ ይህንን የተመለከቱ ሊቃውንትም አድናቆታቸውን ‹‹ቄርሎስና ዮሐንስ አፈወርቅ በሀገራችን ተገኙ፤ ኢትዮጵያም እንደ ሮምና ቁስጥንጥንያ፣ እንደ እስክንድርያም ሆነች› ብለው በማሸብሸብ ነበር የገለጡት፡፡

ከስድስት መቶ ዓመታት በኋላ ያለችው ኢትዮጵያ ግን ለደራሲዎቿ ቦታ የሌላት፣ ማንበብና መጻፍም ብርቅ የሆነባት፣ ድራፍት ቤት እንጂ መጻሕፍት ቤት፣ ጫት ቤት እንጂ የመጻሕፍት ማከፋፈያ ቤት የማይበረታታባት ሀገር ሆናለች፡፡ ክልል ያላት በክልል ደረጃ የሚጠቀስ ቤተ መጻሕፍት የሌላት፣ መንግሥት ያላት፣ ነገር ግን መንግሥት ዕውቅና የሚሰጠው ድርሰትና ደራሲ የሌላት ሀገር ሆናለች፡፡ ለጀማሪ አቀንቃኞች የሰጠችውን አይዶል እንኳን ያህል ለበካር ደራስያን ለመስጠት ያልፈቀደች ሀገር ሆናለች፡፡ ለአርተር ራምቦ እንጂ ለጸጋዬ ገብረ መድኅን ቦታ የሌላት ሀገር ሆናለች፡፡ ለፑሽኪን እንጂ ለሐዲስ ዓለማየሁ አደባባይ የሌላት ምድር ሆናለች፡፡ ደራሲዎቿ ሲኖሩ ሳይሆን ሲሞቱ ዜና የምትሠራ ሀገር ሆናች፡፡

ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ መጽሐፈ ብርሃን በተሰኘው መጽሐፉ ላይ ‹‹እስመ ጽሙዐን ለትምህርት ብሔረ ኢትዮጵያ ኄራን – ምርጦቹ የኢትዮጵያ ሰዎች ትምህርትን የተጠሙ ናቸው›› ይላል፡፡ በዚህ ጥማታቸውም የተነሣ ሕንድ ተሻግረው እነ መጽሐፈ በርለዓምን፣ ግሪክ ገብተው እነ ዜና እስክንድርን፣ አምጥተው ነበር፡፡ ኢትዮጵያዊቷ ንግሥተ ሳባ እንኳን ወደ ሰሎሞን የሄደችው ‹ጥበብን ፍለጋ› መሆኑን ቅዱሳት መጻሕፍት ይናገራሉ፡፡ እዚህች ሀገር ውስጥ ቆዳ ለጫማ ከመዋሉ በፊት ለመጽሐፍ ነበር የዋለው፤ ብርዕ ለማገዶ ከመዋሉ በፊት ለጽሕፈት ነበር የዋለው፤ ቀለም ለግድግዳ ከመዋሉ በፊት ለፊደል ነበር የዋለው፡፡

በዚህች ሀገር ጥንታዊ ታሪክ መጻሕፍትን መጻፍ ብቻ ሳይሆን፤ ማንበብ፣ ማስነበብ፣ ማስጻፍ፣ ሲነበቡ መስማት ጭምር እጅግ የተከበረ ነገር ነበር፡፡ የተከበረ ብቻም ሳይሆን የቅድስናም ምንጭ ነበር፡፡ በየገድላቱና ድርሳናቱም ‹የጻፈ ያስጻፈ፣ ያነበበ የተረጎመ፣ የሰማ ያሰማ› የሚሉት ቃል ኪዳኖች መጻፍን ብቻ ሳይሆን የተጻፈውን ማንበብ፣ ማንበብ ለማይችሉትም ድምጽን ከፍ አድርጎ እያነበቡ ማሰማት፣ ሲነበብም በጽሞና መስማት ጭምር ዋጋ እንዲኖራቸው ያደረጉ ነበሩ፡፡ የደራስያኑ መጻሕፍት እንዳሁኑ በማተሚያ ማሽን በብዛት አይባዙም ነበርና ለጸሐፊዎች ከፍሎ ማስጻፍ፣ ዋጋ ተቀብሎ በሚገባ መጻፍ የሚያስመሰግን የሚያጸድቅም ነገር መሆኑን ኢትዮጵያውያን ያምኑ ነበር፡፡

ለዚህም ነው በዚያ ሁሉ የእርስ በርስ ጦርነቶች ውስጥ አልፋ፣ አንዳንድ ጊዜም ሀገሪቱ ራስዋ ከጥፋት በተአምራት የተረፈችባቸውን ታሪኮች አስመዝግባ፣ ነገር ግን አያሌ የብራና መጻሕፍትን እስከ ዛሬ ድረስ ጠብቃ ለማቆየት የቻለችው፡፡ በመከራም ጊዜ ከከብቶቿና ከበጎቿ፣ ከእህሏና ከማሯ፣ ከወርቋና ከብሯ ይልቅ መጻሕፍቷን ለማቆየት ነበር ሩጫዋ፡፡ በገድለ ዜና ማርቆስ ላይ በ15ኛው መክዘ መጨረሻ ላይ የተፈጠረውን የእርስ በርስ ጦርነት በመሸሽ የገዳሙ መነኮሳት ከሸዋ ወደ ደቡብ ጎንደር ሲሰደዱ ከአንድ ሺ የሚበልጡ መጻሕፍትን በሦስት ቦታ ዋሻ ውስጥ ደብቀው ማስቀመጣቸውን ይነግረናል፡፡

የደራስያኑ የድርሰት ሥራ የተወደደ፣ ባለቤትነቱም የተከበረ በመሆኑ በቃል የሚፈስሰው ቅኔ እንኳን ‹የእገሌ ቅኔ; እየተባለ ይጠቀስ ነበር እንጂ የባለቤትነት መብቱን የሚያስከብርለት ሕግና ሕግ አስከባሪ አካል የለም ተብሎ አይደፈርም ነበር፡፡ በአንድ ወቅት ጎጃም ከመምህሩ የሰማውን ቅኔ ትግራይ ሄዶ እንደራሱ አድርጎ ሲቀኝ የተሰማ ተማሪ ቅኔውን ሲጨርስ ‹ቅኔያቸውስ ደረሰን፣ ለመሆኑ የኔታ ደኅና ናቸው?› የሚል ውርደት የገጠመው ለደራስያኑ የባለቤትነት መብት ጠበቃ የሆነ ማኅበረሰብ ስለነበረን ነው፡፡ የጎንደሩ ደብረ ብርሃን ሥላሴ ለሸዋው ደብረ ብርሃን ሥላሴ 2000 መክሊት ወርቅ  ‹ደብረ ብርሃን› የሚለውን ስም ለመጠቀም የከፈለውኮ ለባለቤትነት መብት ክብር የነበረው ሕዝብ ስለነበረን ነው፡፡

ዛሬ ግን በዚህች ታሪካዊት ምድር፤ በዚህች ሥነ ጽሑፍ ተፈጥሮ፣ አድጎ፣ ዳብሮ፣ ሠልጥኖ ለወግ ለማዕረግ ደርሶባት በነበረች ሀገር፤ ደራስያንና ድርሰት የተረሱ ዕቃዎች ሆነዋል፡፡ እነርሱን የሚያበረታታ፣ የሚሸልም፣ ዕውቅና የሚሰጥ፣ ማዕረግ የሚሰጥ፣ በዝተውና መልተው ምድርን እንዲሞሏት የሚያደርግ ማኅበረሰብም፣ ተቋምም መንግሥትም አጥታለች፡፡

በታደሉት ሀገሮች የዓመቱ ምርጥ ደራሲ፣ የዓመቱ ምርጥ መጽሐፍ፣ በዓመቱ በብዙ ቅጅ የተሸጠ መጽሐፍ እየተባለ ደራስያንንና ድርሰትን የሚያበረታታ፣ እንደ ጻፉበት ጉዳይም በየዘርፋቸው የሚሸልም ተቋምና መንግሥት አለ፡፡ በስማቸው መንገዶችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ አደባባዮችን፣ ፓርኮችን፣ ሙዝየሞችን የሚሰይም መንግሥትና ሕዝብ አላቸው፡፡ ሥራዎቻቸው ብቻ ሳይሆን የሠሩባቸው ቤቶችና የተጠቀሙባቸው ቁሳቁሶች ሳይቀር የሀገሪቱ ታሪክና ቅርስ ሆነው ይጎበኛሉ፡፡

ለመሆኑ የገብረ ሕይወት ባይከዳኝ፣ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ፣ የብላታ ማኅተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል፣ የአለቃ ሐዲስ ዓለማየሁ፣ የአቤ ጉበኛ፣ የበዓሉ ግርማ፣ ቤታቸው የት ነው? የት ነበር የጻፉት? ረቂቃቸው አለን? የጻፉበት ብዕር አለን? ምን ሰየምንላቸው? በምን እናስታውሳቸዋለን? ለመሆኑ የኢትዮጵያን የድርሰት ጉዞ የሚያሳይ አንድ ሙዝየም እንኳን አለን? የሺ ዓመታት የሥነ ጽሑፍ ታሪክ የምንደሰኩር ጀግኖች ሥነ ጽሑፋችን ከየት ተነሥቶ የት ደረሰ? የድርሰት ጉዟችን ከየት መጥቶ የት ጋ ደረሰ? የዕውቀት አባቶቻችንና እናቶቻችን እነማን ነበሩ? እስካሁን ምን ያህል ደራስያንን አፍርተናል? እነማን መቼ ተነሡ? እነማንስ ምን ሠሩ? የመጀመሪያው ገጣሚ፣ የመጀመሪያው የልቦለድ ደራሲ፣ የመጀመሪያው የወግ ጸሐፊ፣ የመጀመሪያው የቴአትር ደራሲ፣ የመጀመሪያው ሃይማኖታዊ መጽሐፍ ደራሲ፣ የመጀመሪያው የጋዜጣ ጽሑፍ ጸሐፊ፣ የመጀመሪያው የፊልም ጽሑፍ ጸሐፊ፣ የመጀመሪያው የጉዞ ማስተዋሻ ጸሐፊ ማነው? ብንባል አንዳች ስምምነት አለን? የምናሳየውስ ነገር አለን? የትስ ነው መረጃው ያለው? ለተተኪው ትውልድስ የት ወስደን ነው የምናሳየው?

የሀገር የሥልጣኔ ሕዳሴ የሚጀምረው ከዕውቀትና ከኪነ ጥበብ ሕዳሴ ነው፡፡ የአውሮፓንም ሆነ የእስያን የሕዳሴ ታሪክ ብንመለከት ዕውቀት ያልመራው ኪነጥበብ ያላቀጣጠለው ሕዳሴ አናገኝም፡፡ የኢኮኖሚውንም፣ የባሕሉንም፣ የፖለቲካውንም ሕዳሴ ዕውቀት ሊመራ ኪነ ጥበብም ሊያቀጣጥለው ይገባዋል፡፡ ኪነ ጥበቡ ደግሞ ፖለቲካ መር፣ ብሔር መር፣ ገንዘብ መር ሳይሆነ ዕውቀት መር መሆን አለበት፡፡ ሕዳሴ የተሳካና የጸና እንዲሆን የዕውቀት አባቶችና እናቶች ያስፈልጉታል፡፡ የሚታወቁ ሳይሆን የሚያውቁ፣ የሚናገሩ ሳይሆን የሚነገርላቸው፣ ‹አለን አለን› የሚሉ ሳይሆን ‹አሉ አሉ› የሚባልላቸው የዕውቀት ምንጮች ያስፈልጋሉ፡፡

እነዚህ የዕውቀት ምንጮች ዕውቀታቸውን እንደ ጉንፋን ማጋባት እንዲችሉ መጻፍ አለባቸው፡፡ ጊዜ ወስደው፣ ዐቅም ሰብስበው፣ መረጃ አስሰው፣ ሰርዘው ደልዘው፣ ቀምረው ሰድረው መጻፍ አለባቸው፡፡ የምንጠቅሰው፣ የምንመራበት፣ ብርሃን የምናይበት፣ ዓይነ ልቡናችንን የምናበራበት የዕውቀት ማዕድ ማዘጋጀት አለባቸው፡፡ ይኼ ደግሞ የደራሲው የጸሐፊው ድርሻ ብቻ አይደለም፡፡ የጥንት እናቶቻችንና አባቶቻችን ቀለም ገዝተው፣ ብራና አስፍቀው፣ ለጸሐፊው ድርጎ ሰጥተው፣ ርስት ከፍለው፣ ዋጋ ቆርጠው፣ ሲጨርስም ሸልመው ያስጽፉ እንደነበረው ሁሉ ደራስያኑን የሚያበረታታ፣ የድካማቸውን ዋጋ እንዲያገኙ የሚያደርግ፣ ለውጥ የሚያመጣ ዓይነተኛ ሥራ ሠርተው ሲገኙም የሚሸልም መንግሥትና ሕዝብ ያስፈልጋል፡፡ ከወረቀትና ከማተሚያ ዋጋ እስከ ሥራ ግብር፣ ከማከፋፈያ ችግር እስከ መብት ማስከበር፤ ከትምህርት ቤት የንባብ ባህል እስከ ሀገራዊ የጽሕፈትና የንባብ አብዮት፣ ከዓመታዊ ሽልማት እስከ የማዕረግ ስሞች፣ የሚሰጥ ተቋማዊ አሠራርና ባህል ያስፈልገናል፡፡ የሀገር ሥልጣኔ ከድርሰት ሥልጣኔ እንደሚጀምረው ሁሉ የሀገር ሞትም ከድርሰት ሞት ይጀምራልና፡፡ 

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው

ይህችን እህት በጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት በር ተቀምጣ ካየኋት ሳምንት አልፏል። አልፎ አልፎ ላነጋግራት ብሞክርም መልስ አትሰጥም። መጀመሪያ የየኋት ቀን አካባቢ ከስራ ለተፈናቀሉ እህቶች አነሰም በዛ መጠለያ እያለ ፣ ለምን በር ላይ ትሆናለች? ብየ የጠየቅኳቸው የቆንስሉ ጸጥታ አስከባሪ ” አንተየ የዚህች እህት ጉዳይ አስቸጋሪ ነው ። ከመጠለያው ብዙ ቆይታለች ፣ አሁን በር ላይ የሆነችው ሃገር […]

ባለፈው ሳምንት ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የደቡብ አፍሪካው የጸረ-ዓፓርታይድ እንቅስቃሴ መሪና የነጻነት አባት ኔልሰን ማንዴላ እዚህ ዋሽንግተን ዲሲ ውስጥ በዛሬው እለት በተካሄደ የጸሎት ስነ ስርዓት ታስበዋል።

በብሄራዊ ካቴድራል በተካሄደው በዚህ ሥነ ሥርዓት የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን፥ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፥ የኮንግረስ አባላትና ዲፕሎማቶች፤ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

ታህሳስ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :- መንግስት በውጭ አገር ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ሀቅሙ ላላቸው ዜጎች የ40 በ60 እንዲሁም በአዲስ አበባ በአነስተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ ዜጎች ደግሞ የ10 በዘጠና እና የ20 በ80 የቤት ልማት እዶችን ዘርግቷል። በ10/90 850 ሺ በ 20/80 ደግሞ 350 ሺ የአዲስ አበባ ነዋሪ ተመዝግቦ እድሉን በመጠባበቅ ላይ ሲሆን ከ12 ሺ በላይ በውጭ አገር …

ታህሳስ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች እና በሰሜን የአገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ከተሞች መብራት በተደጋጋሚ እየተቋረጠ ሲሆን፣ መብራት ሀይል የተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ተናበው ለመስራት አልቻሉም በሚል ወቀሳ አሰምቷል።  በጉዳዩ ዙሪያ ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው የኢትዩጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ     40 በመቶ የሚሆነው ኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥ የሚፈጠረው በሰው ሰራሺ አደጋ ነው ያሉ …

ታህሳስ ፪(ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :- መምህራኑ ለኢሳት እንደተናገሩት ያለፍላጎታቸው ለአባይ ግድብ ማሰሪያ በሚል ከደሞዛቸው ላይ ገንዘብ መቆረጡን በመቃወም የተቆረጠው ገንዘብ ተመልሶ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ሙሉ ደሞዛችን እስካልተሰጠን ድረስ ምንም አይነት ክፍያ አንቀበለም ያሉት መምህራኑ፣ እስከ ፊታችን አርብ ሙሉ ደሞዛችን የማይሰጠን ከሆነ የስራ ማቆም አድማ እንዳርጋለን ሲሉ አስጠንቅቀዋል። በደቡብ ክልል መንግስት ለአባይ ግድብ ማሰሪያ በሚል …

ተመስገን ደሳለኝ (አዲስ አበባ)

ባለፈው ሳምንት የምስራቅ ኢትዮጵያ ፖለቲካን ተጨባጭ እውነታዎችን ቃኝቼ ተከታዩን ክፍል በይደር አቆይቼው እንደነበረ ይታወሳል፤ እነሆም ዛሬ እንዲህ እቀጥላለሁ፡-
ሐረር እንደ ማሳያ
(መቼም ኢህአዴግ በብቸኝነት የሚኩራራበት የፖለቲካ ‹ስኬት›፣ ለዘመናት አንድ ሆኖ የኖረ ሕዝብን ‹ብሔር ብሔረሰቦች› በሚል ከፋፋይ የ‹ክርስትና ስም› እጥምቆ በአደባባይ ማስጨፈር ከሆነ ሰነባብቷል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ …

በርካታ የሂሳብ ጥናትና ምርምር ሥራዎችን አቅርበዋል ።በራሳቸው ስም የሚጠራ የሂሳብ ስሌት እሳቤም ፈጥረዋል ። እኚህ መምህር ከመላው አሜሪካን ለውድድር ከቀረቡ 360 ከፍተኛ መምህራን እጎአ የ2013 ምርጥ የዩኒቨርስቲ ምሁር በመባል ተመረጠዋል ።

ትናንት ፤ በእስቶክሆልም ፤ ስዊድን ፣ በኔልሰን ማንዴላ የመጨረሻ የስንብት ሥነ ሥርዓት ሳቢያ ታላላቅ ዓለም አቀፍ እንግዶች ተመናምነው ፣ ሆኖም ከ 1,300 በላይ ታዳሚዎች በተገኙበት ስብሰባ ፣ በ3 ቱም የተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፎች ውድድር ፣ የዘንድሮዎቹ አሸናፊዎች ሽልማታቸውን ተቀብለዋል።

ለቀድሞው የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዚደንት እና ዋነኛው የፀረአፓርታይድ ታጋይ ለኔልሰን ማንዴላ ትናንት በጆሀንስበርግ በሶዌቶ በሚገኝ ስቴድዮም ይፋ ስንብት በተደረገበት ጊዜ ከመላው ደቡብ አፍሪቃ የመጣው ሕዝብ

የግርማ ካሣን ጽሑፎች አልፎ አልፎ አነባቸዋለሁ፡፡ ሀገር ወዳድ መሆኑን ይጠቁማሉ – ጽሑፎቹ፡፡ ታታሪ ሰው ይመስለኛል፤ በጥረቱና በሀገር ፍቅር ስሜቱ እወደዋለሁ፡፡ ሁልጊዜ ሳይታክት ይጽፋል፡፡ ሳይታክቱ የሚጽፉ ብፁዓንነት የሚበዛባቸው ቢሆን ዕድለኞች ግን ናቸው፡፡ ብዙዎቻችን እየደከመን መጻፍ ቀርቶ ማንበባችንንም እያቆምን በምንገኝበት ሰዓት አዘውትሮ መጻፍ መታደል ነው፡፡ አያ ግርማ ሰሞኑን የጻፋቸውን ሁለት ያህል መጣጥፎች አንብቤያለሁ፡፡ ሁለቱም ግንቦት ሰባትን ለመንቀፍ […]

‹‹በነበረው ሒደት በተለያየ ምክንያት የበደላችኹንን ኹሉ ይቅር ብለናችኋል›› (በጋሻው ደሳለኝ፣ ኅዳር ፳፱ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.፤ ለሐዋሳ ደ/ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ምእመናን የተናገረው) ‹‹ይኼ ጉልበት ላይ መውደቅ፣ ይቅርታ መጠየቅ በፍጹም እንዳያደርገው፡፡ ጉልበት ላይ መውደቅ፣ ይቅርታ መጠየቅ ማለት ጥፋተኛ ነኝ፤ ተሸማቅቄ እኖራለኹኝ ማለት ነው፤››   (በጋሻው ደሳለኝ፣ በግንቦት ፳፻፬ ዓ.ም. የክብረ መንግሥት ግብረ አበሮቹን ሲመክር) ይቅርታ ጠያቂ ሳይኾን …